4 days ago
ከ40 ሀገራት ጥያቄ ጀርባ ያለው የብሪክስ+ ሚስጥር እና የኢትዮጵያ አዲሱ የስትራቴጂ ማዕከልነት
******************
ባለፉት ሃያ ዓመታት ውስጥ የብሪክስ ስብስብ ከተመሰረተበት የመጀመሪያ ደረጃ የኢኮኖሚ ትስስር ዓላማ አልፎ፣ የዓለም አቀፉን የጂኦ-ፖለቲካ እና የአህጉራዊ ትብብር መዋቅር በከፍተኛ ሁኔታ ወደቀየረ ታላቅ የባለብዙ ወገን እንቅስቃሴነት ተሸጋግሯል።
በአሁኑ ወቅት ወደ 40 የሚጠጉ ሀገራት ስብስቡን ለመቀላቀል ፍላጎት ማሳየታቸው፣ የደቡቡ ዓለም የበለጠ አካታች፣ ፍትሃዊ እና ሚዛናዊ የሆነ የዓለም አቀፍ አስተዳደር ስርዓት ለመገንባት ያለውን ጽኑ ፍላጎት በግልጽ የሚያንፀባርቅ ነው።
ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት የታየው የዓለም አቀፍ ጂኦ-ፖለቲካ ለውጥ ዋና ማሳያ፣ ሀገራት በጋራ ተሳትፎ እና በሉዓላዊ እኩልነት ላይ የተመሰረተ አዲስ የትብብር መንገድ መከተላቸው ነው።
ብሪክስ ስብስቡን እያሰፋና አዳዲስ አጋርነቶችን እየፈጠረ የመጣበት አካሄድ፣ በንግድ መስመሮች፣ በኃይል ኮሪደሮች፣ በታዳሽ ኃይል እና በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዙሪያ ዘላቂ ትብብርን የሚያጎለብት ስትራቴጂካዊ መድረክ እንዲሆን አድርጎታል።
ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ፍላጎት የሚታይበት የዚህ ታሪካዊ ለውጥ አካል መሆኗ በዲፕሎማሲያዊ፣ በሎጂስቲክስ እና በኢንዱስትሪ ዘርፎች ዘላቂ ስትራቴጂካዊ ጥቅሞችን ያስገኝላታል።
የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ እና የሰፊ ህዝብ ባለቤት እንደመሆኗ መጠን፣ አህጉሪቱን ከብሪክስ የንግድ እና የሎጂስቲክስ መዋቅር ጋር የምታገናኝ ዋና ድልድይ ሆና ታገለግላለች።
ይህም የአፍሪካን የልማት አጀንዳዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ በትልቁ ለማስደመጥ እና አህጉራዊ የዲፕሎማሲ መሪነቷን የበለጠ ለማጠናከር ታላቅ ዕድል ይፈጥርላታል።
ከዚሁ ጎን ለጎን የሀገራችን የላቀ የአቪዬሽን አቅም እና የመሰረተ ልማት ዝርጋታ አህጉራዊ ትስስርን በፍጥነት የሚያፋጥን በመሆኑ፣ ስብስቡ በምስራቅ አፍሪካ ለሚያደርጋቸው የንግድና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች ኢትዮጵያን ዋና የሎጂስቲክስና የንግድ መግቢያ ያደርጋታል።
ከዚህም ባሻገር የኢትዮጵያ ታዳሽ የኃይል አቅርቦት እና የሎጂስቲክስ አቅም ከብሪክስ አባል ሀገራት የቴክኖሎጂ እና የፋብሪካዎች ሽግግር ጋር ሲጣመር፣ ኢትዮጵያ ከጥሬ እቃ ላኪነት ወጥታ ወደ ቀጠናዊ የአምራችነትና የኢንዱስትሪ ማዕከልነት እንድትሸጋገር ትልቅ መዋቅራዊ መሰረት ይጥላል።
በሰለሞን ገዳ
#ethiopia #brics #globaleconomy #diplomacy #investment
******************
ባለፉት ሃያ ዓመታት ውስጥ የብሪክስ ስብስብ ከተመሰረተበት የመጀመሪያ ደረጃ የኢኮኖሚ ትስስር ዓላማ አልፎ፣ የዓለም አቀፉን የጂኦ-ፖለቲካ እና የአህጉራዊ ትብብር መዋቅር በከፍተኛ ሁኔታ ወደቀየረ ታላቅ የባለብዙ ወገን እንቅስቃሴነት ተሸጋግሯል።
በአሁኑ ወቅት ወደ 40 የሚጠጉ ሀገራት ስብስቡን ለመቀላቀል ፍላጎት ማሳየታቸው፣ የደቡቡ ዓለም የበለጠ አካታች፣ ፍትሃዊ እና ሚዛናዊ የሆነ የዓለም አቀፍ አስተዳደር ስርዓት ለመገንባት ያለውን ጽኑ ፍላጎት በግልጽ የሚያንፀባርቅ ነው።
ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት የታየው የዓለም አቀፍ ጂኦ-ፖለቲካ ለውጥ ዋና ማሳያ፣ ሀገራት በጋራ ተሳትፎ እና በሉዓላዊ እኩልነት ላይ የተመሰረተ አዲስ የትብብር መንገድ መከተላቸው ነው።
ብሪክስ ስብስቡን እያሰፋና አዳዲስ አጋርነቶችን እየፈጠረ የመጣበት አካሄድ፣ በንግድ መስመሮች፣ በኃይል ኮሪደሮች፣ በታዳሽ ኃይል እና በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዙሪያ ዘላቂ ትብብርን የሚያጎለብት ስትራቴጂካዊ መድረክ እንዲሆን አድርጎታል።
ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ፍላጎት የሚታይበት የዚህ ታሪካዊ ለውጥ አካል መሆኗ በዲፕሎማሲያዊ፣ በሎጂስቲክስ እና በኢንዱስትሪ ዘርፎች ዘላቂ ስትራቴጂካዊ ጥቅሞችን ያስገኝላታል።
የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ እና የሰፊ ህዝብ ባለቤት እንደመሆኗ መጠን፣ አህጉሪቱን ከብሪክስ የንግድ እና የሎጂስቲክስ መዋቅር ጋር የምታገናኝ ዋና ድልድይ ሆና ታገለግላለች።
ይህም የአፍሪካን የልማት አጀንዳዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ በትልቁ ለማስደመጥ እና አህጉራዊ የዲፕሎማሲ መሪነቷን የበለጠ ለማጠናከር ታላቅ ዕድል ይፈጥርላታል።
ከዚሁ ጎን ለጎን የሀገራችን የላቀ የአቪዬሽን አቅም እና የመሰረተ ልማት ዝርጋታ አህጉራዊ ትስስርን በፍጥነት የሚያፋጥን በመሆኑ፣ ስብስቡ በምስራቅ አፍሪካ ለሚያደርጋቸው የንግድና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች ኢትዮጵያን ዋና የሎጂስቲክስና የንግድ መግቢያ ያደርጋታል።
ከዚህም ባሻገር የኢትዮጵያ ታዳሽ የኃይል አቅርቦት እና የሎጂስቲክስ አቅም ከብሪክስ አባል ሀገራት የቴክኖሎጂ እና የፋብሪካዎች ሽግግር ጋር ሲጣመር፣ ኢትዮጵያ ከጥሬ እቃ ላኪነት ወጥታ ወደ ቀጠናዊ የአምራችነትና የኢንዱስትሪ ማዕከልነት እንድትሸጋገር ትልቅ መዋቅራዊ መሰረት ይጥላል።
በሰለሞን ገዳ
#ethiopia #brics #globaleconomy #diplomacy #investment
9 days ago
የ"ራሴን በጉያዬ፣ የሌላውን በጋራ" የግብጽ የሞኝ ብልጠት አካሄድ ዳግም ሲጋለጥ
********************
ኢትዮጵያ የዓባይን ውኃ 85 በመቶ የምታመነጭ እና ለታችኛው ተፋሰስ ሀገራት የሕይወት እስትንፋስ የሆነች ሀገር ነች።
ይሁን እንጂ ግብጽ ይህንን የማይካድ የተፈጥሮ እውነት ወደ ጎን በመተው ለረጅም ዘመናት "የዓባይ ውኃ ብቸኛ ባለቤት እኔ ነኝ" የሚል የሞኝ ብልጠት ፖለቲካ ስታራምድ ኖራለች።
ካይሮ ይህንን የውኃ ሞኖፖል ለማስቀጠል መሠረት የምታደርገው ኢትዮጵያን ያገለሉትን እና ጊዜ ያለፈባቸውን የ1929 እና የ1959 የቅኝ ግዛት ዘመን 'ስምምነቶች'ን ነው።
ከዚህም አልፋ የውኃ ድርሻዬ የምትለውን ለማረጋገጥ በቀጣናው የውክልና ፖለቲካን በመጠቀም ሀገራት እርስ በርስ እንዲጋጩ፣ ትርምስ እንዲፈጠር እና ኢትዮጵያ በውስጥ ችግር ተተብትባ የራሷን ጸጋ እንዳትጠቀም የተለያዩ የሴራ ድሮችን ስታደራ መኖሯ የአደባባይ ምሥጢር ነው።
ለዘመናት የዓባይ ወንዝን በብቸኝነት ለመጠቀም ስትከተለው የቆየው ይህ አካሄድ ሀገሪቱ በዜሮ ድምር ስሌት የምትመራ እና ከመጠን ያለፈ ራስ ወዳድ መሆኗን በተግባር ያረጋገጠ ነው።
ኢትዮጵያ ከደጇ የሚመነጨውን ተፈጥሯዊ ሀብቷን የመጠቀም ሉዓላዊ መብቷን ስታነሣ አምርራ የምትቃወመው ግብጽ፣ በቀይ ባሕር የባሕር ላይ ደኅንነት ዙሪያ ፍጹም ተቃራኒ የሆነ እና "ዐይናችሁን ጨፍኑ ላሞኛችሁ" የሚል ሌላ የሴራ አካሄድ ይዛ ብቅ ማለቷ ነው።
የታችኛው ተፋሰስ ሀገር የሆነችው ግብጽ በዓባይ ወንዝ አጠቃቀም ላይ "የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ድምፅ እና ይሁንታ ሊኖራቸው ይገባል" በማለት የኢትዮጵያን ሉዓላዊ መብት ስትገዳደር ኖራለች።
በተቃራኒው ግን በቀይ ባሕር ጉዳይ ላይ ስትጠየቅ "ውይይት እና ውሳኔው የሚመለከተው የባሕሩ ተዋሳኝ ሀገራትን ብቻ ነው" የሚል የሞኝ ዜማ ማቀንቀን ከጀመረች ውላ አድራለች። ይህ ተቃራኒ እና ሚዛን የሳተ አካሄድ ዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ ለማወናበድ እና የማይመስሉ ጥያቄዎችን በማንሣት ኢትዮጵያን ከጂኦ-ፖለቲካዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነቷ ለማግለል ያሰላችው ያረጀ ስትራቴጂዋ ነው።
ይህንን የካይሮን የሚጣረስ እና የተፈጥሮ ሕግን የሚቃረን አካሄድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሁለት ዓመታት በፊት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ባደረጉት ታሪካዊ ማብራሪያ በግልጽ አስቀምጠውታል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀይ ባሕር እና ዓባይ ከኢትዮጵያ ዕድገት እና ሕልውና ጋር በቀጥታ የተሣሠሩ መሠረታዊ ጉዳዮች መሆናቸውን በመጠቆም፣ ተፈጥሯዊ ትሥሥራቸውን አብራርተዋል።
ዓባይ ከኢትዮጵያ እየፈለቀ ለግብጽ የሕልውና ጉዳይ ከሆነ እና ስለ እርሱ በግልጽ መነጋገር ከቻለች ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት ኢትዮጵያ በጂኦግራፊያዊ እስር ቤት ታሥራ መኖር ስለማትችል ስለ ቀይ ባሕር መነጋገርም ሆነ መደራደር ነውር ሊሆንባት አይገባም ነው ያሉት።
እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አባባል፣ ተፈጥሮ በውኃ አዙሪት ያስተሣሠረቻቸውን እነዚህን ሁለት የውኃ አካላት እና ጂኦ-ፖለቲካዊ እውነታዎች አንዱን የብቸኝነት ንብረት አድርጎ ሌላውን መከልከል ከፍትሕ እና ከተፈጥሮ ሕግ ጋር ፈጽሞ የሚጣረስ ነው።
የጠቅላይ ሚኒስትሩን ይህንኑ ጽኑ አቋም እና የግብጽን ግብዝነት ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብም በሚገባ መረዳት ጀምሯል።
በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የቀድሞው የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር እና በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር የነበሩት ቲቦር ናዥ ይህንን የግብጽን ጨፍኑ ላሞኛችሁ አካሄድ ሰሞኑን በጥልቅ አመክንዮአዊ መልዕክት አጋልጠውታል።
አምባሳደሩ በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ "ግብጽ እና ኤርትራ በቀይ ባሕር ላይ መወሰን ያለባቸው ተዋሳኝ ሀገራት ብቻ ናቸው ካሉ፤ እንግዲያውስ በአመክንዮ ደረጃ በዓባይ ወንዝ አጠቃቀም ላይም መወሰን ያለባቸው ውኃውን የሚያመነጩት የላይኛው ተፋሰስ ሀገራት ብቻ ናቸው" በማለት የካይሮን ክርክር መሠረተ ቢስነት በአደባባይ አሳይተዋል።
አምባሳደሩ ከዚህ ቀደምም ግብጽ ጊዜ ያለፈበትን አካሄድ ትታ መሬት ላይ ወዳለው እውነታ መምጣት እንዳለባት በተደጋጋሚ አሳስበዋል። ኢትዮጵያን በዛቻ እና በግፊት ማንበርከክ እንደማይቻል የገለጹት አንጋፋው ዲፕሎማት፣ የቀይ ባሕር ደኅንነት ያለ ኢትዮጵያ ንቁ ተሳትፎ ሙሉ ሊሆን እንደማይችል በግልጽ አስምረውበታል።
ግብጽ በአንድ በኩል ኢትዮጵያ የታላቁን ሕዳሴ ግድብ ስትገነባ "የታችኛው ተፋሰስ ፈቃድ ያስፈልጋል" እያለች አቤቱታ ስታሰማ፣ በሌላ በኩል ደግሞ እ.አ.አ በ2020 በሪያድ የተቋቋመውን "የቀይ ባሕር እና የኤደን ባሕረ ሰላጤ ሀገራት ምክር ቤት" በመጠቀም ኢትዮጵያን ከባሕር ደኅንነት ውይይቶች ለማግለል ስትሠራ ቆይታለች።
ይህ የ"ራሴን በጉያዬ፣ የሌላውን በጋራ" የብልጠት ስትራቴጂ አሁን ላይ ጊዜው አልፎበታል። ዛሬ ላይ ኢትዮጵያ ፍትሐዊ የልማት ጥያቄዋን በአግባቡ መጠየቅ እና በውኃዋም ሆነ በባሕር በር አማራጮቿ ተጠቃሚ ለመሆን መንቀሳቀስ በመጀመሯ፣ የግብጽ ያረጀ የሞኖፖል እና የሴራ አካሄድ ፈጽሞ እንደማያዋጣ በተግባር እየተረጋገጠ መጥቷል።
ለግብጽ የሚበጃት ብቸኛ መንገድ ወደ እውነታው መምጣት እና ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ የትብብር ማዕቀፍን መቀበል ብቻ ነው።
ኢትዮጵያ የ130 ሚሊዮን ሕዝቧን የልማት እና የደኅንነት ዋስትና ለማረጋገጥ የጀመረችውን የሰላም እና የፍትሐዊ ተጠቃሚነት ጉዞ ማንም አያስቆመውም።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #redsea #nilebasin #geopolitics #hornofafrica #diplomacy
********************
ኢትዮጵያ የዓባይን ውኃ 85 በመቶ የምታመነጭ እና ለታችኛው ተፋሰስ ሀገራት የሕይወት እስትንፋስ የሆነች ሀገር ነች።
ይሁን እንጂ ግብጽ ይህንን የማይካድ የተፈጥሮ እውነት ወደ ጎን በመተው ለረጅም ዘመናት "የዓባይ ውኃ ብቸኛ ባለቤት እኔ ነኝ" የሚል የሞኝ ብልጠት ፖለቲካ ስታራምድ ኖራለች።
ካይሮ ይህንን የውኃ ሞኖፖል ለማስቀጠል መሠረት የምታደርገው ኢትዮጵያን ያገለሉትን እና ጊዜ ያለፈባቸውን የ1929 እና የ1959 የቅኝ ግዛት ዘመን 'ስምምነቶች'ን ነው።
ከዚህም አልፋ የውኃ ድርሻዬ የምትለውን ለማረጋገጥ በቀጣናው የውክልና ፖለቲካን በመጠቀም ሀገራት እርስ በርስ እንዲጋጩ፣ ትርምስ እንዲፈጠር እና ኢትዮጵያ በውስጥ ችግር ተተብትባ የራሷን ጸጋ እንዳትጠቀም የተለያዩ የሴራ ድሮችን ስታደራ መኖሯ የአደባባይ ምሥጢር ነው።
ለዘመናት የዓባይ ወንዝን በብቸኝነት ለመጠቀም ስትከተለው የቆየው ይህ አካሄድ ሀገሪቱ በዜሮ ድምር ስሌት የምትመራ እና ከመጠን ያለፈ ራስ ወዳድ መሆኗን በተግባር ያረጋገጠ ነው።
ኢትዮጵያ ከደጇ የሚመነጨውን ተፈጥሯዊ ሀብቷን የመጠቀም ሉዓላዊ መብቷን ስታነሣ አምርራ የምትቃወመው ግብጽ፣ በቀይ ባሕር የባሕር ላይ ደኅንነት ዙሪያ ፍጹም ተቃራኒ የሆነ እና "ዐይናችሁን ጨፍኑ ላሞኛችሁ" የሚል ሌላ የሴራ አካሄድ ይዛ ብቅ ማለቷ ነው።
የታችኛው ተፋሰስ ሀገር የሆነችው ግብጽ በዓባይ ወንዝ አጠቃቀም ላይ "የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ድምፅ እና ይሁንታ ሊኖራቸው ይገባል" በማለት የኢትዮጵያን ሉዓላዊ መብት ስትገዳደር ኖራለች።
በተቃራኒው ግን በቀይ ባሕር ጉዳይ ላይ ስትጠየቅ "ውይይት እና ውሳኔው የሚመለከተው የባሕሩ ተዋሳኝ ሀገራትን ብቻ ነው" የሚል የሞኝ ዜማ ማቀንቀን ከጀመረች ውላ አድራለች። ይህ ተቃራኒ እና ሚዛን የሳተ አካሄድ ዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ ለማወናበድ እና የማይመስሉ ጥያቄዎችን በማንሣት ኢትዮጵያን ከጂኦ-ፖለቲካዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነቷ ለማግለል ያሰላችው ያረጀ ስትራቴጂዋ ነው።
ይህንን የካይሮን የሚጣረስ እና የተፈጥሮ ሕግን የሚቃረን አካሄድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሁለት ዓመታት በፊት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ባደረጉት ታሪካዊ ማብራሪያ በግልጽ አስቀምጠውታል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀይ ባሕር እና ዓባይ ከኢትዮጵያ ዕድገት እና ሕልውና ጋር በቀጥታ የተሣሠሩ መሠረታዊ ጉዳዮች መሆናቸውን በመጠቆም፣ ተፈጥሯዊ ትሥሥራቸውን አብራርተዋል።
ዓባይ ከኢትዮጵያ እየፈለቀ ለግብጽ የሕልውና ጉዳይ ከሆነ እና ስለ እርሱ በግልጽ መነጋገር ከቻለች ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት ኢትዮጵያ በጂኦግራፊያዊ እስር ቤት ታሥራ መኖር ስለማትችል ስለ ቀይ ባሕር መነጋገርም ሆነ መደራደር ነውር ሊሆንባት አይገባም ነው ያሉት።
እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አባባል፣ ተፈጥሮ በውኃ አዙሪት ያስተሣሠረቻቸውን እነዚህን ሁለት የውኃ አካላት እና ጂኦ-ፖለቲካዊ እውነታዎች አንዱን የብቸኝነት ንብረት አድርጎ ሌላውን መከልከል ከፍትሕ እና ከተፈጥሮ ሕግ ጋር ፈጽሞ የሚጣረስ ነው።
የጠቅላይ ሚኒስትሩን ይህንኑ ጽኑ አቋም እና የግብጽን ግብዝነት ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብም በሚገባ መረዳት ጀምሯል።
በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የቀድሞው የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር እና በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር የነበሩት ቲቦር ናዥ ይህንን የግብጽን ጨፍኑ ላሞኛችሁ አካሄድ ሰሞኑን በጥልቅ አመክንዮአዊ መልዕክት አጋልጠውታል።
አምባሳደሩ በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ "ግብጽ እና ኤርትራ በቀይ ባሕር ላይ መወሰን ያለባቸው ተዋሳኝ ሀገራት ብቻ ናቸው ካሉ፤ እንግዲያውስ በአመክንዮ ደረጃ በዓባይ ወንዝ አጠቃቀም ላይም መወሰን ያለባቸው ውኃውን የሚያመነጩት የላይኛው ተፋሰስ ሀገራት ብቻ ናቸው" በማለት የካይሮን ክርክር መሠረተ ቢስነት በአደባባይ አሳይተዋል።
አምባሳደሩ ከዚህ ቀደምም ግብጽ ጊዜ ያለፈበትን አካሄድ ትታ መሬት ላይ ወዳለው እውነታ መምጣት እንዳለባት በተደጋጋሚ አሳስበዋል። ኢትዮጵያን በዛቻ እና በግፊት ማንበርከክ እንደማይቻል የገለጹት አንጋፋው ዲፕሎማት፣ የቀይ ባሕር ደኅንነት ያለ ኢትዮጵያ ንቁ ተሳትፎ ሙሉ ሊሆን እንደማይችል በግልጽ አስምረውበታል።
ግብጽ በአንድ በኩል ኢትዮጵያ የታላቁን ሕዳሴ ግድብ ስትገነባ "የታችኛው ተፋሰስ ፈቃድ ያስፈልጋል" እያለች አቤቱታ ስታሰማ፣ በሌላ በኩል ደግሞ እ.አ.አ በ2020 በሪያድ የተቋቋመውን "የቀይ ባሕር እና የኤደን ባሕረ ሰላጤ ሀገራት ምክር ቤት" በመጠቀም ኢትዮጵያን ከባሕር ደኅንነት ውይይቶች ለማግለል ስትሠራ ቆይታለች።
ይህ የ"ራሴን በጉያዬ፣ የሌላውን በጋራ" የብልጠት ስትራቴጂ አሁን ላይ ጊዜው አልፎበታል። ዛሬ ላይ ኢትዮጵያ ፍትሐዊ የልማት ጥያቄዋን በአግባቡ መጠየቅ እና በውኃዋም ሆነ በባሕር በር አማራጮቿ ተጠቃሚ ለመሆን መንቀሳቀስ በመጀመሯ፣ የግብጽ ያረጀ የሞኖፖል እና የሴራ አካሄድ ፈጽሞ እንደማያዋጣ በተግባር እየተረጋገጠ መጥቷል።
ለግብጽ የሚበጃት ብቸኛ መንገድ ወደ እውነታው መምጣት እና ሁሉንም ተጠቃሚ የሚያደርግ ፍትሐዊ የትብብር ማዕቀፍን መቀበል ብቻ ነው።
ኢትዮጵያ የ130 ሚሊዮን ሕዝቧን የልማት እና የደኅንነት ዋስትና ለማረጋገጥ የጀመረችውን የሰላም እና የፍትሐዊ ተጠቃሚነት ጉዞ ማንም አያስቆመውም።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #redsea #nilebasin #geopolitics #hornofafrica #diplomacy
10 days ago
ፓን-አፍሪካዊ ኃይል የሆነው የመደመር ትውልድ
*******************
ኢትዮጵያ ከጥንት ጀምሮ ለመላው ጥቁር ሕዝቦች የነጻነት ተምሳሌት በመሆን የፓን-አፍሪካኒዝም እሳቤ ተፈጥሯዊ ጉልበት ሆና ቆይታለች።
አውሮፓውያን አህጉሪቱን ለመቀራመት ሲነሡ፣ ኢትዮጵያ በከፍታ ላይ የቆመች እና ሥልጣኔን ያጣጣመች ዕድሜ ጠገብ ሀገር ናት።
ታሪካዊው የዓድዋ ድል እስከ አፍንጫው ታጥቆ የመጣውን የቀኝ ገዢ ኃይል በማንበርከክ የነጭ የበላይነትን እሳቤ ገልብጧል፤ የዓድዋ ድል ለፓን-አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አዲስ ጉልበትና የይቻላል መንፈስን አጎናጽፏል።
የትናንቱ የፓን-አፍሪካኒዝም ትግል ማዕከል የፖለቲካ ነጻነት ሲሆን፣ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ዋነኛ ትግል የኢኮኖሚ ነጻነትን ማረጋገጥ ነው።
ታላቁ ፓን-አፍሪካኒስት ጁሊየስ ኔሬሬ እንዳስገነዘቡት፣ በመጀመሪያው የአፍሪካ ቅርምት ጎሳን ከጎሳ ያጋጨው የውጭ ኃይል፣ አሁን ደግሞ ሀገርን ከሀገር በማጋጨት አህጉሪቱን ደካማና የተከፋፈለች ለማድረግ ይጥራል። በእርግጥም በመከፋፈል ውስጥ የሚገኝ ክብርም ሆነ ታላቅነት የለም። ከተከፋፈልን ደካሞች እንሆናለን፤ ከተባበርን ግን በእኛ ላይ የሚመጡትን የጣልቃ ገብነት ኃይሎች አሳፍረን መመለስ እንችላለን።
በዚህ ታሪካዊ መጋጠሚያ ላይ፣ የኢትዮጵያ የመደመር ትውልድ ከራሱ አልፎ ቀጣናውን በፓን-አፍሪካዊ መንፈስ ለማስተሳሰር በጽናት ቆሟል። አፍሪካውያን የማይነጣጠሉ እና ዕጣ ፈንታቸው የተሣሠረ፣ የቀኝ ግዛት ድንበርን የሚሻገር የጠበቀ ወንድማማችነት ያላቸው ሕዝቦች ናቸው።
ለአብነት ያህል፣ ፉላኒ ጎሳ ከ19 በላይ የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ ሲገኝ፣ አካን በጋና እና አይቮሪኮስት፣ ኦሮሞ በኢትዮጵያ እና ኬንያ፣ አፋር በኢትዮጵያ፣ ኤርትራ እና ጅቡቲ፣ እንዲሁም ሶማሌ በቀጣናው የተለያዩ ሀገራት ተሰራጭቶ ይገኛል።
እ.አ.አ በ1902 በቅኝ ገዢዎች በተደረገ የድንበር ከለላ የበርታ ብሔረሰብ በሁለት ተከፍሎ በሱዳን እና በኢትዮጵያ እንዲኖር ተገዷል። ይህን ሐቅ ጠንቅቆ የተረዳው የመደመር ትውልድ፣ እነዚህን ሕዝቦች በፖለቲካ አጥር ማጠር እንደማይቻል በማመን፣ አፍሪካን እንደ አንድ ሕዝብ በማስተሣሠር የማበልጸግ ኃላፊነትን ወስዷል።
ኢትዮጵያ ይህንን የአብሮነት እና የመደመር እሳቤ በተግባር ለማሳየት የሰፋፊ መሠረተ ልማቶችን ትሥሥር እያከናወነች ትገኛለች። የአፍሪካ ኅብረትን አጀንዳ 2063 ለማሳካት እና ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውህደትን እውን ለማድረግ፣ ለጎረቤት ሀገራት ለምሳሌ ለጅቡቲ፣ ለሱዳን እና ለኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ የምጣኔ ሀብት ትሥሥር እያፋጠነች ነው።
ከኬንያ ጋር የተዘረጋው የመንገድ መሠረተ ልማት፣ እንዲሁም በውኃ ተፋሰሶች ላይ የሚሠሩ ታላላቅ ግድቦች የዚሁ ታላቅ ፓን-አፍሪካዊ አሰባሳቢ ትሥሥር አካላት ናቸው።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ባለፉት ሦስት ዐሥርት ዓመታት በሩዋንዳ፣ ላይቤሪያ፣ ሱዳን፣ ብሩንዲ እና ሶማሊያ የሰላም ማስከበር ተልዕኮውን በብቃት በመወጣት አህጉራዊ እና ቀጣናዊ መረጋጋትን አረጋግጧል። ይህም ኢትዮጵያ ለፓን-አፍሪካኒዝም ያላትን የተግባር ቁርጠኝነት ያረጋግጣል።
የ21ኛው ክፍለ ዘመን ፓን-አፍሪካኒዝም አፍሪካውያን በቅኝ ገዢዎች የተሰመሩላቸውን የፖለቲካ ድንበሮች በማንሣት፣ አህጉሪቱን ወደ አንድ የጋራ ነጻ ንግድ ቀጣና በማምራት የኢኮኖሚ ነጻነታቸውን የሚያረጋግጡበት ወሳኝ ምዕራፍ ነው።
የአፍሪካ ሕዝብ ብዛት ከ1.4 ቢሊዮን አልፎ ወደፊት በእጥፍ እንደሚያድግ ሲገመት፣ ይህ ታላቅ አምራች ኃይል እና ሰፊ ገበያ ትልቅ የመልማት አቅም ነው። በተጨማሪም አህጉሪቱ የተፈጥሮ ማዕድን፣ ነዳጅ፣ የውኃ ሀብት እና ሊታረስ የሚችል ሰፊ ለም መሬት፣ እንዲሁም የተለያዩ ማዕድናትን ጨምሮ የተትረፈረፈ ጸጋ ባለቤት ናት።
ከምዕራባውያን ገበያ ጥገኝነት ተላቅቀን ይህንን እምቅ ሀብት በማቀናጀት እና የምናመርተውን ምርት እርስ በርስ ብንለዋወጥ ታላቅ ስኬትን እንጎናጸፋለን።
ኢትዮጵያ ትናንት የፖለቲካ ነፃነት ዓርማ እንደነበረች ሁሉ፣ ዛሬ ደግሞ የመደመር ትውልድን በማስተባበር በቀጣናዊ ሰላም፣ በመሠረተ ልማት ዝርጋታ እና በአህጉራዊ ውህደት የላቀ ሚና በመጫወት ላይ ያለች ጽኑ ፓን-አፍሪካዊ ኃይል ናት።
አዲሱ ትውልድ አፍሪካውያን በመተባበር እና በወንድማማችነት ላይ የተመሠረተ ጠንካራ ኅብረት እንዲፈጥሩ በጽናት የቆመ ኃይል ሆኖ ይቀጥላል፤ ምክንያቱም ለአፍሪካውያን ችግር ብቸኛው መፍትሔ ያለው በራሳቸው በአፍሪካውያን እጅ በመሆኑ ነው።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #hornofafrica #medemer #medemergeneration #diplomacy
*******************
ኢትዮጵያ ከጥንት ጀምሮ ለመላው ጥቁር ሕዝቦች የነጻነት ተምሳሌት በመሆን የፓን-አፍሪካኒዝም እሳቤ ተፈጥሯዊ ጉልበት ሆና ቆይታለች።
አውሮፓውያን አህጉሪቱን ለመቀራመት ሲነሡ፣ ኢትዮጵያ በከፍታ ላይ የቆመች እና ሥልጣኔን ያጣጣመች ዕድሜ ጠገብ ሀገር ናት።
ታሪካዊው የዓድዋ ድል እስከ አፍንጫው ታጥቆ የመጣውን የቀኝ ገዢ ኃይል በማንበርከክ የነጭ የበላይነትን እሳቤ ገልብጧል፤ የዓድዋ ድል ለፓን-አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አዲስ ጉልበትና የይቻላል መንፈስን አጎናጽፏል።
የትናንቱ የፓን-አፍሪካኒዝም ትግል ማዕከል የፖለቲካ ነጻነት ሲሆን፣ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ዋነኛ ትግል የኢኮኖሚ ነጻነትን ማረጋገጥ ነው።
ታላቁ ፓን-አፍሪካኒስት ጁሊየስ ኔሬሬ እንዳስገነዘቡት፣ በመጀመሪያው የአፍሪካ ቅርምት ጎሳን ከጎሳ ያጋጨው የውጭ ኃይል፣ አሁን ደግሞ ሀገርን ከሀገር በማጋጨት አህጉሪቱን ደካማና የተከፋፈለች ለማድረግ ይጥራል። በእርግጥም በመከፋፈል ውስጥ የሚገኝ ክብርም ሆነ ታላቅነት የለም። ከተከፋፈልን ደካሞች እንሆናለን፤ ከተባበርን ግን በእኛ ላይ የሚመጡትን የጣልቃ ገብነት ኃይሎች አሳፍረን መመለስ እንችላለን።
በዚህ ታሪካዊ መጋጠሚያ ላይ፣ የኢትዮጵያ የመደመር ትውልድ ከራሱ አልፎ ቀጣናውን በፓን-አፍሪካዊ መንፈስ ለማስተሳሰር በጽናት ቆሟል። አፍሪካውያን የማይነጣጠሉ እና ዕጣ ፈንታቸው የተሣሠረ፣ የቀኝ ግዛት ድንበርን የሚሻገር የጠበቀ ወንድማማችነት ያላቸው ሕዝቦች ናቸው።
ለአብነት ያህል፣ ፉላኒ ጎሳ ከ19 በላይ የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ ሲገኝ፣ አካን በጋና እና አይቮሪኮስት፣ ኦሮሞ በኢትዮጵያ እና ኬንያ፣ አፋር በኢትዮጵያ፣ ኤርትራ እና ጅቡቲ፣ እንዲሁም ሶማሌ በቀጣናው የተለያዩ ሀገራት ተሰራጭቶ ይገኛል።
እ.አ.አ በ1902 በቅኝ ገዢዎች በተደረገ የድንበር ከለላ የበርታ ብሔረሰብ በሁለት ተከፍሎ በሱዳን እና በኢትዮጵያ እንዲኖር ተገዷል። ይህን ሐቅ ጠንቅቆ የተረዳው የመደመር ትውልድ፣ እነዚህን ሕዝቦች በፖለቲካ አጥር ማጠር እንደማይቻል በማመን፣ አፍሪካን እንደ አንድ ሕዝብ በማስተሣሠር የማበልጸግ ኃላፊነትን ወስዷል።
ኢትዮጵያ ይህንን የአብሮነት እና የመደመር እሳቤ በተግባር ለማሳየት የሰፋፊ መሠረተ ልማቶችን ትሥሥር እያከናወነች ትገኛለች። የአፍሪካ ኅብረትን አጀንዳ 2063 ለማሳካት እና ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውህደትን እውን ለማድረግ፣ ለጎረቤት ሀገራት ለምሳሌ ለጅቡቲ፣ ለሱዳን እና ለኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ የምጣኔ ሀብት ትሥሥር እያፋጠነች ነው።
ከኬንያ ጋር የተዘረጋው የመንገድ መሠረተ ልማት፣ እንዲሁም በውኃ ተፋሰሶች ላይ የሚሠሩ ታላላቅ ግድቦች የዚሁ ታላቅ ፓን-አፍሪካዊ አሰባሳቢ ትሥሥር አካላት ናቸው።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ባለፉት ሦስት ዐሥርት ዓመታት በሩዋንዳ፣ ላይቤሪያ፣ ሱዳን፣ ብሩንዲ እና ሶማሊያ የሰላም ማስከበር ተልዕኮውን በብቃት በመወጣት አህጉራዊ እና ቀጣናዊ መረጋጋትን አረጋግጧል። ይህም ኢትዮጵያ ለፓን-አፍሪካኒዝም ያላትን የተግባር ቁርጠኝነት ያረጋግጣል።
የ21ኛው ክፍለ ዘመን ፓን-አፍሪካኒዝም አፍሪካውያን በቅኝ ገዢዎች የተሰመሩላቸውን የፖለቲካ ድንበሮች በማንሣት፣ አህጉሪቱን ወደ አንድ የጋራ ነጻ ንግድ ቀጣና በማምራት የኢኮኖሚ ነጻነታቸውን የሚያረጋግጡበት ወሳኝ ምዕራፍ ነው።
የአፍሪካ ሕዝብ ብዛት ከ1.4 ቢሊዮን አልፎ ወደፊት በእጥፍ እንደሚያድግ ሲገመት፣ ይህ ታላቅ አምራች ኃይል እና ሰፊ ገበያ ትልቅ የመልማት አቅም ነው። በተጨማሪም አህጉሪቱ የተፈጥሮ ማዕድን፣ ነዳጅ፣ የውኃ ሀብት እና ሊታረስ የሚችል ሰፊ ለም መሬት፣ እንዲሁም የተለያዩ ማዕድናትን ጨምሮ የተትረፈረፈ ጸጋ ባለቤት ናት።
ከምዕራባውያን ገበያ ጥገኝነት ተላቅቀን ይህንን እምቅ ሀብት በማቀናጀት እና የምናመርተውን ምርት እርስ በርስ ብንለዋወጥ ታላቅ ስኬትን እንጎናጸፋለን።
ኢትዮጵያ ትናንት የፖለቲካ ነፃነት ዓርማ እንደነበረች ሁሉ፣ ዛሬ ደግሞ የመደመር ትውልድን በማስተባበር በቀጣናዊ ሰላም፣ በመሠረተ ልማት ዝርጋታ እና በአህጉራዊ ውህደት የላቀ ሚና በመጫወት ላይ ያለች ጽኑ ፓን-አፍሪካዊ ኃይል ናት።
አዲሱ ትውልድ አፍሪካውያን በመተባበር እና በወንድማማችነት ላይ የተመሠረተ ጠንካራ ኅብረት እንዲፈጥሩ በጽናት የቆመ ኃይል ሆኖ ይቀጥላል፤ ምክንያቱም ለአፍሪካውያን ችግር ብቸኛው መፍትሔ ያለው በራሳቸው በአፍሪካውያን እጅ በመሆኑ ነው።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #hornofafrica #medemer #medemergeneration #diplomacy
12 days ago
u1240u12ed u1263u1205u122du1293 u12e8u12a4u12f0u1295 u1263u1215u1228 u1230u120bu1324 u12e8u12a2u1275u12eeu1335u12eb u1218u1270u1295u1348u123bu12ceu127d u1293u1278u12cd - u1320u1245u120bu12ed u121au1292u1235u1275u122d u12d0u1262u12ed u12a0u1215u1218u12f5 (u12f6/u122d)
#seaoutlet #redsea #diplomacy #rasalula #ethiopia #economy #maritime #ebcdotstream ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ቀይ ባህርና የኤደን ባሕረ ሰላጤ የኢትዮጵያ መተንፈሻዎች ናቸው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
#seaoutlet #redsea #diplomacy #rasalula #ethiopia #economy #maritime #ebcdotstream
13 days ago
ውኃ የሚወቅጠው የግብጽ ዲፕሎማሲ እና የማይቀለበሰው የኢትዮጵያ ልማት
*********************
የግብፅ የውኃ ሀብት እና መስኖ ሚኒስቴር “በዓለም አቀፍ ሕግ መርሆዎች ላይ የተመሰረተ የውኃ መብቴን ለማስከበር ቁርጠኛ ነኝ” በሚል ያወጣው መግለጫ፣ የካይሮ ፖለቲከኞች ለዘመናት ሲያላምጡት የኖሩትና አሁንም መላቀቅ ያቃታቸው የተለመደ የሚዲያ ፍጆታ ነው።
ይህ መግለጫ መሬት ላይ ካለው ነባራዊ እውነት ጋር የማይገናኝ ነው፡፡ ዋናው ዓላማውም ኢትዮጵያ በውኃ ሀብቷ እያስመዘገበች ያለው የልማት ስኬት እና የጂኦ-ፖለቲካዊ ሚዛን ለውጥ የፈጠረባቸውን የሥነ-ልቦና መረበሽ ለመሸፈን የሚደረግ መፍጨርጨር ነው።
ካይሮ ዓለም አቀፍ ሕግን እንደ ሽፋን ብትጠቀምም፣ ትክክለኛው የውስጥ ሕመሟ የውኃ እጥረት ሳይሆን፣ የኢትዮጵያን ማንሰራራት እንደ ስጋት የመመልከትና የተፈጥሮ ሃብቷን ለመጠቀም የምታደርገውን ጥረት ለመግታት ያለመ ነው።
ግብፅ በረሃን እያለማች፣ ቶሽካን በመሳሰሉ ፕሮጀክቶች ከፍተኛ ውኃ የሚጠይቁ ሰብሎችን በበረሃ እያመረተች፣ በሌላ በኩል ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ጸጋዋን ተጠቅማ ዜጎቿን ከድህነት ለማውጣት የምታደርገውን ጥረት እንደ ሥጋት መመልከቷ የፖለቲካ ግብዝነቷ ማሳያ ነው።
ታሪካዊ ዳራዎችን ወደ ኋላ መለስ ብለን ስንፈትሽ ግብፅ ኢትዮጵያን በውኃ ሀብቷ እንዳትጠቀም ስትጎነጉነው የኖረችው ሤራ ዘርፈ ብዙ ነው። በአንድ በኩል ኢትዮጵያ ፈፅሞ ዕውቅና ያልሰጠቻቸውን የ1929 እና የ1959 (እ.አ.አ) የቅኝ ግዛት ውሎችን እንደ ብቸኛ የሕግ ማዕቀፍ እያነሳች ለማስፈራራት ትሞክራለች።
በሌላ በኩል ደግሞ፣ ኢትዮጵያ የውኃ ሃብቷን ለማልማት ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ብድር እና እርዳታ እንዳይሰጧት ያልቆፈረችው የዲፕሎማሲ ጉድጓድ አልነበረም።
ከዚህም አልፎ ኢትዮጵያ ዕረፍት አግኝታ ወደ ልማቷ እንዳታተኩር የውስጥ ግጭቶችን በሎጂስቲክስ እና በፋይናንስ በመደገፍ እንዲሁም ፀረ-ሰላም ኃይሎችን በማሰባሰብ የዜሮ ድምር ፖለቲካ ስታራምድ ኖራለች።
ይሁን እንጂ ይህ የዘመናት ሤራ ከሽፎ፣ ኢትዮጵያ የውጭ የፋይናንስ በሮች መዘጋትን በገዛ ዜጎቿ አቅምና ላብ ተክታ ልማቷን እውን ስታደርግ ማየቷ ካይሮን ወደ ያልተገባ መደናገጥ ከትቷታል። የአሁኑ መሠረተ ቢስ መግለጫም የዚሁ ድንጋጤ ማስተጋቢያ ነው።
የኢትዮጵያ በዓባይ ውኃ ላይ ያላት አቋም ከመቼውም ጊዜ በላይ የጠራ፣ ዓለም አቀፍ የውኃ ሕግጋትን ያከበረ እና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ ነው።
ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ስትገነባም ሌሎች የተፋሰሱን ሀገራት በማግለል ሳይሆን፣ በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ላይ ተመስርታ ነው። ለዚህም ማሳያው ግድቡ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ከታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጋር ያደረገችው ተከታታይ ውይይት እና ያሳየችው ግልፅነት ነው።
ከዚህም ባሻገር የናይል ተፋሰስ ሀገራት የትብብር ማዕቀፍ (CFA) በቅርቡ ወደ ትግበራ መግባቱ የጋራ ተጠቃሚነትን በተግባር ያረጋገጠ እና የግብፅን የብቻ የበላይነት ፍላጎት ሕገ-ወጥነት ያጋለጠ ትልቅ ፖለቲካዊ እና ሕጋዊ ድል ነው።
የግብፅ የአሁኑ ጥያቄ እና ጩኸት ጊዜ ያለፈበት እና አዲሱን የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ያላገናዘበ ነው። ካይሮ ጉዳዩ ፈፅሞ የማይመለከታቸውን የሩቅ ኃይሎችና ተቋማት ደቦ በመሰብሰብ ኢትዮጵያ ላይ ጫና ለመፍጠር የምታደርገው ጥረት ዛሬ ላይ ውኃ አያነሳም።
የኢትዮጵያ ሕዝብም ሆነ መንግሥት በዲፕሎማሲ ጫና እጁ የማይጠመዘዝ መሆኑን በሕዳሴው ግድብ ስኬት በተግባር አሳይቷል።
በመሆኑም ለግብፅ የሚበጃት ብቸኛው አዋጭ አማራጭ ከንቱ ከሆነው የሚዲያ ፕሮፓጋንዳ እና የደቦ ዲፕሎማሲ ወጥታ፣ አዲሱን የትብብር ማዕቀፍ (CFA) በመቀበል ከኢትዮጵያ እና ከተቀሩት የተፋሰሱ ሀገራት ጋር በጋራ መሥራት ብቻ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ebc #ethiopia #gerd #nilebasin #africansolutions #abay #diplomacy
*********************
የግብፅ የውኃ ሀብት እና መስኖ ሚኒስቴር “በዓለም አቀፍ ሕግ መርሆዎች ላይ የተመሰረተ የውኃ መብቴን ለማስከበር ቁርጠኛ ነኝ” በሚል ያወጣው መግለጫ፣ የካይሮ ፖለቲከኞች ለዘመናት ሲያላምጡት የኖሩትና አሁንም መላቀቅ ያቃታቸው የተለመደ የሚዲያ ፍጆታ ነው።
ይህ መግለጫ መሬት ላይ ካለው ነባራዊ እውነት ጋር የማይገናኝ ነው፡፡ ዋናው ዓላማውም ኢትዮጵያ በውኃ ሀብቷ እያስመዘገበች ያለው የልማት ስኬት እና የጂኦ-ፖለቲካዊ ሚዛን ለውጥ የፈጠረባቸውን የሥነ-ልቦና መረበሽ ለመሸፈን የሚደረግ መፍጨርጨር ነው።
ካይሮ ዓለም አቀፍ ሕግን እንደ ሽፋን ብትጠቀምም፣ ትክክለኛው የውስጥ ሕመሟ የውኃ እጥረት ሳይሆን፣ የኢትዮጵያን ማንሰራራት እንደ ስጋት የመመልከትና የተፈጥሮ ሃብቷን ለመጠቀም የምታደርገውን ጥረት ለመግታት ያለመ ነው።
ግብፅ በረሃን እያለማች፣ ቶሽካን በመሳሰሉ ፕሮጀክቶች ከፍተኛ ውኃ የሚጠይቁ ሰብሎችን በበረሃ እያመረተች፣ በሌላ በኩል ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ጸጋዋን ተጠቅማ ዜጎቿን ከድህነት ለማውጣት የምታደርገውን ጥረት እንደ ሥጋት መመልከቷ የፖለቲካ ግብዝነቷ ማሳያ ነው።
ታሪካዊ ዳራዎችን ወደ ኋላ መለስ ብለን ስንፈትሽ ግብፅ ኢትዮጵያን በውኃ ሀብቷ እንዳትጠቀም ስትጎነጉነው የኖረችው ሤራ ዘርፈ ብዙ ነው። በአንድ በኩል ኢትዮጵያ ፈፅሞ ዕውቅና ያልሰጠቻቸውን የ1929 እና የ1959 (እ.አ.አ) የቅኝ ግዛት ውሎችን እንደ ብቸኛ የሕግ ማዕቀፍ እያነሳች ለማስፈራራት ትሞክራለች።
በሌላ በኩል ደግሞ፣ ኢትዮጵያ የውኃ ሃብቷን ለማልማት ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ብድር እና እርዳታ እንዳይሰጧት ያልቆፈረችው የዲፕሎማሲ ጉድጓድ አልነበረም።
ከዚህም አልፎ ኢትዮጵያ ዕረፍት አግኝታ ወደ ልማቷ እንዳታተኩር የውስጥ ግጭቶችን በሎጂስቲክስ እና በፋይናንስ በመደገፍ እንዲሁም ፀረ-ሰላም ኃይሎችን በማሰባሰብ የዜሮ ድምር ፖለቲካ ስታራምድ ኖራለች።
ይሁን እንጂ ይህ የዘመናት ሤራ ከሽፎ፣ ኢትዮጵያ የውጭ የፋይናንስ በሮች መዘጋትን በገዛ ዜጎቿ አቅምና ላብ ተክታ ልማቷን እውን ስታደርግ ማየቷ ካይሮን ወደ ያልተገባ መደናገጥ ከትቷታል። የአሁኑ መሠረተ ቢስ መግለጫም የዚሁ ድንጋጤ ማስተጋቢያ ነው።
የኢትዮጵያ በዓባይ ውኃ ላይ ያላት አቋም ከመቼውም ጊዜ በላይ የጠራ፣ ዓለም አቀፍ የውኃ ሕግጋትን ያከበረ እና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ ነው።
ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ስትገነባም ሌሎች የተፋሰሱን ሀገራት በማግለል ሳይሆን፣ በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ላይ ተመስርታ ነው። ለዚህም ማሳያው ግድቡ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ከታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጋር ያደረገችው ተከታታይ ውይይት እና ያሳየችው ግልፅነት ነው።
ከዚህም ባሻገር የናይል ተፋሰስ ሀገራት የትብብር ማዕቀፍ (CFA) በቅርቡ ወደ ትግበራ መግባቱ የጋራ ተጠቃሚነትን በተግባር ያረጋገጠ እና የግብፅን የብቻ የበላይነት ፍላጎት ሕገ-ወጥነት ያጋለጠ ትልቅ ፖለቲካዊ እና ሕጋዊ ድል ነው።
የግብፅ የአሁኑ ጥያቄ እና ጩኸት ጊዜ ያለፈበት እና አዲሱን የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ያላገናዘበ ነው። ካይሮ ጉዳዩ ፈፅሞ የማይመለከታቸውን የሩቅ ኃይሎችና ተቋማት ደቦ በመሰብሰብ ኢትዮጵያ ላይ ጫና ለመፍጠር የምታደርገው ጥረት ዛሬ ላይ ውኃ አያነሳም።
የኢትዮጵያ ሕዝብም ሆነ መንግሥት በዲፕሎማሲ ጫና እጁ የማይጠመዘዝ መሆኑን በሕዳሴው ግድብ ስኬት በተግባር አሳይቷል።
በመሆኑም ለግብፅ የሚበጃት ብቸኛው አዋጭ አማራጭ ከንቱ ከሆነው የሚዲያ ፕሮፓጋንዳ እና የደቦ ዲፕሎማሲ ወጥታ፣ አዲሱን የትብብር ማዕቀፍ (CFA) በመቀበል ከኢትዮጵያ እና ከተቀሩት የተፋሰሱ ሀገራት ጋር በጋራ መሥራት ብቻ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ebc #ethiopia #gerd #nilebasin #africansolutions #abay #diplomacy
19 days ago
የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ለአፍሪካ ቀንድ ደኅንነት ዋስትና ነው
***************************
በፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ ቀጥተኛ የባሕር በር ማግኘቷ የራሷን የንግድ እና የደኅንነት ፍላጎት ከማሟላት ባለፈ ለመላው የአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደት፣ ሰላም እና የጋራ ብልጽግና መረጋገጥ እጅግ ግዙፍ አስተዋጽዖ አለው።
በምሥራቅ አፍሪካ ትልቅ የሕዝብ ቁጥር እና የገበያ አቅም ያላት ሀገር ወደብ አልባ ሆና እንድትቀጥል መደረጉ የቀጣናውን የኢኮኖሚ እምቅ አቅም ሙሉ በሙሉ እንዳይወጣ ማነቆ ሆኖ ቆይቷል።
በመሆኑም ኢትዮጵያ የባሕር በር የምታገኝበት አማራጭ ላይ መድረሷ ኢኮኖሚዋን በማሳደግ ለመላው ቀጣና አዲስ የልማት ምዕራፍ የሚከፍት ስልታዊ እርምጃ ነው።
ይህ ዕድል በቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስር ረገድ ያለው ሚና እጅግ የጎላ ነው። የኢትዮጵያ ወደብ ማግኘት በቀጣናው የሚንቀሳቀሱ የንግድ መርከቦች፣ የመሰረተ ልማት ዝርጋታዎች እና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ይበልጥ እንዲነቃቁ ያደርጋል።
በዚህም ኢትዮጵያ ለወጪ እና ገቢ ንግድ የምትከፍለው ወጪ በእጅጉ ስለሚቀንስ በሀገር ውስጥ በእያንዳንዱ ዜጋ ኪስ ላይ ትርጉም ያለው ለውጥ ያመጣል።
ከዚህም ባሻገር ኢትዮጵያ የምታመርተውን የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በቀላሉ እና በአነስተኛ ወጪ ለጎረቤት ሀገራት እንዲሁም ለዓለም አቀፍ ገበያ ለማቅረብ የምታደርገውን ጥረት ያግዛል።
ይህ የቀጣናውን የጋራ ተጠቃሚነት መርሕ የሚያረጋግጥ እና የአፍሪካ ቀንድ ሀገራትን የንግድ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ነው።
ከኢኮኖሚው ባለፈ የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤት መሆን ለቀይ ባሕር እና ለኤደን ባሕረ ሰላጤ ቀጣናዊ ፀጥታ አስተማማኝ ዋስትና ይሰጣል።
ኢትዮጵያ ጠንካራ የባሕር ኃይል በመገንባት በቀጣናው የሚስተዋሉትን ሕገ-ወጥ የሰዎች እና የጦር መሳሪያ ዝውውር እንዲሁም ሽብርተኝነትን የመሳሰሉ የደኅንነት ስጋቶችን ለመከላከል ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ ለመሥራት ያላትን አቅም ከፍ ያደርገዋል።
በመሆኑም ጠንካራ እና የባሕር በር ያላት ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የሰላም ምሰሶ በመሆን፣ ቀጣናው ለዓለም አቀፍ የጂኦ-ፖለቲካ ፈተናዎች ተጋላጭ ሳይሆን የሰላም እና የልማት ማዕከል እንዲሆን ታላቅ ዲፕሎማሲያዊ እና ወታደራዊ አቅም ትሆናለች።
በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የባሕር በር የማግኘት ጥያቄ የጠበበ የራስ ወዳድነት ፍላጎት ሳይሆን፣ ቀጣናዊ ትስስርን ለማጠናከር የተዘረጋ ታሪካዊ ድልድይ ነው።
ኢትዮጵያ ይህንን ስትራቴጂያዊ ግብ በሰከነ ውይይት፣ በዲፕሎማሲያዊ ድርድር እና በጋራ ልማት መርሕ ላይ መስርታ ከአጎራባች ሀገራት ጋር በመደጋገፍ፣ የአፍሪካ ቀንድን የነገ ክብር እና ብልጽግና በፅኑ መሠረት ላይ ለመገንባት የምታደርገውን ጉዞ በእጅጉ ያሳልጠዋል።
በሃና ምንዳሁን
#ethiopia #ebc #hornofafrica #redsea #peaceanddevelopment #diplomacy
***************************
በፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ ቀጥተኛ የባሕር በር ማግኘቷ የራሷን የንግድ እና የደኅንነት ፍላጎት ከማሟላት ባለፈ ለመላው የአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ውህደት፣ ሰላም እና የጋራ ብልጽግና መረጋገጥ እጅግ ግዙፍ አስተዋጽዖ አለው።
በምሥራቅ አፍሪካ ትልቅ የሕዝብ ቁጥር እና የገበያ አቅም ያላት ሀገር ወደብ አልባ ሆና እንድትቀጥል መደረጉ የቀጣናውን የኢኮኖሚ እምቅ አቅም ሙሉ በሙሉ እንዳይወጣ ማነቆ ሆኖ ቆይቷል።
በመሆኑም ኢትዮጵያ የባሕር በር የምታገኝበት አማራጭ ላይ መድረሷ ኢኮኖሚዋን በማሳደግ ለመላው ቀጣና አዲስ የልማት ምዕራፍ የሚከፍት ስልታዊ እርምጃ ነው።
ይህ ዕድል በቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስር ረገድ ያለው ሚና እጅግ የጎላ ነው። የኢትዮጵያ ወደብ ማግኘት በቀጣናው የሚንቀሳቀሱ የንግድ መርከቦች፣ የመሰረተ ልማት ዝርጋታዎች እና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ይበልጥ እንዲነቃቁ ያደርጋል።
በዚህም ኢትዮጵያ ለወጪ እና ገቢ ንግድ የምትከፍለው ወጪ በእጅጉ ስለሚቀንስ በሀገር ውስጥ በእያንዳንዱ ዜጋ ኪስ ላይ ትርጉም ያለው ለውጥ ያመጣል።
ከዚህም ባሻገር ኢትዮጵያ የምታመርተውን የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በቀላሉ እና በአነስተኛ ወጪ ለጎረቤት ሀገራት እንዲሁም ለዓለም አቀፍ ገበያ ለማቅረብ የምታደርገውን ጥረት ያግዛል።
ይህ የቀጣናውን የጋራ ተጠቃሚነት መርሕ የሚያረጋግጥ እና የአፍሪካ ቀንድ ሀገራትን የንግድ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ነው።
ከኢኮኖሚው ባለፈ የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤት መሆን ለቀይ ባሕር እና ለኤደን ባሕረ ሰላጤ ቀጣናዊ ፀጥታ አስተማማኝ ዋስትና ይሰጣል።
ኢትዮጵያ ጠንካራ የባሕር ኃይል በመገንባት በቀጣናው የሚስተዋሉትን ሕገ-ወጥ የሰዎች እና የጦር መሳሪያ ዝውውር እንዲሁም ሽብርተኝነትን የመሳሰሉ የደኅንነት ስጋቶችን ለመከላከል ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ ለመሥራት ያላትን አቅም ከፍ ያደርገዋል።
በመሆኑም ጠንካራ እና የባሕር በር ያላት ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የሰላም ምሰሶ በመሆን፣ ቀጣናው ለዓለም አቀፍ የጂኦ-ፖለቲካ ፈተናዎች ተጋላጭ ሳይሆን የሰላም እና የልማት ማዕከል እንዲሆን ታላቅ ዲፕሎማሲያዊ እና ወታደራዊ አቅም ትሆናለች።
በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የባሕር በር የማግኘት ጥያቄ የጠበበ የራስ ወዳድነት ፍላጎት ሳይሆን፣ ቀጣናዊ ትስስርን ለማጠናከር የተዘረጋ ታሪካዊ ድልድይ ነው።
ኢትዮጵያ ይህንን ስትራቴጂያዊ ግብ በሰከነ ውይይት፣ በዲፕሎማሲያዊ ድርድር እና በጋራ ልማት መርሕ ላይ መስርታ ከአጎራባች ሀገራት ጋር በመደጋገፍ፣ የአፍሪካ ቀንድን የነገ ክብር እና ብልጽግና በፅኑ መሠረት ላይ ለመገንባት የምታደርገውን ጉዞ በእጅጉ ያሳልጠዋል።
በሃና ምንዳሁን
#ethiopia #ebc #hornofafrica #redsea #peaceanddevelopment #diplomacy
22 days ago
የባሕር በር ፍላጎት እና ብሔራዊ መግባባት
**********************
በኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ዙሪያ እንደ ሀገር በጋራ ለመቆም እና ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስከበር ሀገራዊ ምክክር ወሳኝ ምሰሶ መሆኑ ይታወቃል።
የመደመር መንግሥት የባሕር በር ጥያቄን በዓለም አቀፍ መድረክ ፍትሐዊ እና ሕጋዊ አጀንዳ በማድረግ እየሠራ ቢሆንም፣ ይህን ለማሳካት የውስጥ አንድነት እና የጋራ ብሔራዊ መግባባት መፍጠር ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ሆኗል።
የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ በባሕር በር ጉዳይ ላይ የሚፈጥረው የጋራ መድረክ፣ በወሳኝ ብሔራዊ ጥቅሞች ዙሪያ ሀገራዊ አቅምን በማስተባበር ለመረባረብ ትልቅ ዕድል ነው።
የባሕር በርን ጨምሮ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የነበረው አለመግባባት ለጦርነት እና ለግጭት ዳርጎን እንደነበር ይታወቃል።
አሁን ግን በሀገራዊ ምክክር ሂደቱ የጦርነት ወሬን በማስቀረት በምትኩ በጋራ ጥቅሞች ላይ መመካከርን ባህል ለማድረግ እየተሠራ ይገኛል።
የባሕር በር ጥያቄ የሁሉም ዜጎች የጋራ ፍላጎት እንዲሆን መደረጉ እንደ አንድ ትልቅ ብሔራዊ ስኬት የሚታይ ሲሆን፣ ይህን አጀንዳ በዘላቂነት ለማሳካት ደግሞ የውስጥ የፖለቲካ ልዩነቶችን ወደ ጎን መተው ያስፈልጋል።
እንደ ሀገር በአንድነት ካልቆምን የልማትም ሆነ የዲፕሎማሲ ሥራዎች ውጤታማ ሊሆኑ ስለማይችሉ፣ በታላላቅ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ መግባባት የግድ ይላል።
በሀገራዊ ምክክር የፖለቲካ ባህልን ከግጭት ወደ ንግግር መቀየር የባሕር በርን የመሳሰሉ ብሔራዊ ጥቅሞችን ለማስጠበቅ ትልቅ አቅም የሚፈጥር ነው።
ይህ ሂደት የኢትዮጵያ ሕዝቦችን አንድነት የሚያጠናክር፣ የጋራ መግባባትን የሚፈጥር እና ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተቀባይነት የሚያጎለብት መሆኑ ታምኖበታል።
በሃና ምንዳሁን
#ethiopia #diplomacy #nationaldialogue #nationalinterest #seaaccess #ebc
**********************
በኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ዙሪያ እንደ ሀገር በጋራ ለመቆም እና ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስከበር ሀገራዊ ምክክር ወሳኝ ምሰሶ መሆኑ ይታወቃል።
የመደመር መንግሥት የባሕር በር ጥያቄን በዓለም አቀፍ መድረክ ፍትሐዊ እና ሕጋዊ አጀንዳ በማድረግ እየሠራ ቢሆንም፣ ይህን ለማሳካት የውስጥ አንድነት እና የጋራ ብሔራዊ መግባባት መፍጠር ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ሆኗል።
የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ በባሕር በር ጉዳይ ላይ የሚፈጥረው የጋራ መድረክ፣ በወሳኝ ብሔራዊ ጥቅሞች ዙሪያ ሀገራዊ አቅምን በማስተባበር ለመረባረብ ትልቅ ዕድል ነው።
የባሕር በርን ጨምሮ በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የነበረው አለመግባባት ለጦርነት እና ለግጭት ዳርጎን እንደነበር ይታወቃል።
አሁን ግን በሀገራዊ ምክክር ሂደቱ የጦርነት ወሬን በማስቀረት በምትኩ በጋራ ጥቅሞች ላይ መመካከርን ባህል ለማድረግ እየተሠራ ይገኛል።
የባሕር በር ጥያቄ የሁሉም ዜጎች የጋራ ፍላጎት እንዲሆን መደረጉ እንደ አንድ ትልቅ ብሔራዊ ስኬት የሚታይ ሲሆን፣ ይህን አጀንዳ በዘላቂነት ለማሳካት ደግሞ የውስጥ የፖለቲካ ልዩነቶችን ወደ ጎን መተው ያስፈልጋል።
እንደ ሀገር በአንድነት ካልቆምን የልማትም ሆነ የዲፕሎማሲ ሥራዎች ውጤታማ ሊሆኑ ስለማይችሉ፣ በታላላቅ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ መግባባት የግድ ይላል።
በሀገራዊ ምክክር የፖለቲካ ባህልን ከግጭት ወደ ንግግር መቀየር የባሕር በርን የመሳሰሉ ብሔራዊ ጥቅሞችን ለማስጠበቅ ትልቅ አቅም የሚፈጥር ነው።
ይህ ሂደት የኢትዮጵያ ሕዝቦችን አንድነት የሚያጠናክር፣ የጋራ መግባባትን የሚፈጥር እና ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተቀባይነት የሚያጎለብት መሆኑ ታምኖበታል።
በሃና ምንዳሁን
#ethiopia #diplomacy #nationaldialogue #nationalinterest #seaaccess #ebc
Sponsored by
Surafel
1 month ago
የኢትዮጵያ የኢነርጂ ዲፕሎማሲ - ለቀጣናዊ ትሥሥር የተዘረጋ ድልድይ
*************************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ በታሪኳ አዲስ እና ስልታዊ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ይህ ምዕራፍ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በኩራት ከመቁጠር እና ከመቀኘት ባለፈ እነዚያን እምቅ ሀብቶች ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ እና የጂኦፖለቲካ አቅም በመለወጥ ሀገራዊ ልዕልናን ለማረጋገጥ የሚደረግ የታሪክ መታጠፊያ ነው።
ለረጅም ዘመናት በድህነት፣ በዕርዳታ ጥገኝነት እና በውስጥ ስጋቶች ታጥሮ የቆየው የቀድሞው ዲፕሎማሲ ዛሬ በተግባር ተረትቷል። በምትኩም ቀጣናዊ ትሥሥርን የሉዓላዊነት እና የአህጉራዊ መሪነት ማረጋገጫ ያደረገው የመደመር መንግሥት ስልታዊ ራዕይ በተጨባጭ መሬት እየረገጠ ይገኛል።
በተለይም የታዳሽ ኃይል ሀብትን የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ዋና ምሰሶ አድርጎ የመጠቀም ስትራቴጂ፣ የሀገርን የፖለቲካ ተጽዕኖ እና "ለስላሳ ኃይል" (Soft Power) ከፍ ወዳለ ማዕረግ እያሸጋገረው ነው።
ኃይል ለአዳዲስ የቴክኖሎጂ አብዮቶች፣ ለዲጂታል ኢኮኖሚ እና ለሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) መሠረታዊ ግብዓት በሆነበት በዚህ በ21ኛው ክፍለ ዘመን፣ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የኃይል ማዕከል የመሆን ሕልሟን ወደ እውንነት እየቀየረችው ነው።
ይህ እውነታ በወረቀት ላይ በሰፈሩ የይስሙላ ስምምነቶች ሳይሆን፣ በድንበር ተሻጋሪ የኤሌክትሪክ መስመሮች በተግባር የተመሰከረ ሐቅ ነው። ባለፉት ጥቂት የለውጥ ዓመታት የተወሰዱት ቁርጠኛ እርምጃዎች ሱዳን፣ ጅቡቲ እና ኬንያ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ዋነኛ ተጠቃሚዎች እንዲሆኑ አስችለዋል።
የታላቁ የሕዳሴ ግድብ፣ የኮይሻ እና ሌሎች ግዙፍ ፕሮጀክቶች የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ከመሙላት ባለፈ፣ የቀጣናውን የጋራ ዕድገት የሚያረጋግጡ የትሥሥር ድልድዮች ሆነዋል። አሁን ደግሞ ይህ ቁርኝት ወደ ሌሎች ጎረቤት ሀገራት ጭምር መሻገሩ የነገውን ቀጣናዊ ትሥሥር ይበልጥ ብሩህ ያደርገዋል።
ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚደረገው ይህ ዘላቂ ትሥሥር፣ ከንግድ ልውውጥ እና ከገቢ ምንጭነት ባሻገር፣ አንዱ ሀገር ለሌላው የሕልውና ዋስትና የሚሆንበት እና የቀጣናውን ዘላቂ ሰላም በጽኑ መሠረት ላይ የሚገነባ ስልታዊ መሣሪያ መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል።
በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው ረገድም ሀገራችን ከታሪካዊው የልመና አዙሪት ወጥታ በክብር እና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ ፖሊሲን በቁርጠኝነት እየተገበረች ትገኛለች። የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነትን መተግበር፣ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት እና የብሪክስ አባል መሆን የኢትዮጵያን የፋይናንስ እና የኢንቨስትመንት አድማስ በሰፊው ከፍቶታል።
ይህ የፖሊሲ መዋቅር የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ለመቶ ሺዎች ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩ ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶችም በጎረቤት ሀገራት ኢንቨስት በማድረግ አህጉራዊ የኢኮኖሚ አሻራቸውን እንዲያስፋፉ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል።
የኢትዮጵያ የነገ ራዕይ ከአፍሪካ ቀንድ ተሻግሮ እስከ ሰሜን አፍሪካ እና አውሮፓ የሚዘልቅ ታላቅ የኃይል መረብ የመዘርጋት ታላቅ አልሚነት ነው። በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ከውኃ ኃይል በተጨማሪ በፀሐይ፣ በነፋስና በጂኦተርማል ኃይል ላይ የሚደረገው ኢንቨስትመንት የታዳሽ ኃይል ብዝኃነትን በማረጋገጥ፣ ኢትዮጵያን የቀጣናው አስተማማኝ የኃይል "ባንክ" ያደርጋታል።
ይህ ዘላቂ ጉዞ ሀገራችንን ከተረጂነት አዙሪት ሙሉ በሙሉ በማውጣት፣ በዓለም አቀፍ መድረክ በራሷ የምትቆም፣ ክብሯ የተጠበቀ እና የምሥራቅ አፍሪካ የሰላም እና የብልጽግና ፋና እንድትሆን ያደርጋታል።
ምክንያቱም የዚህች ታላቅ ሀገር እውነተኛ እና ዘላቂ ብልጽግና ሊረጋገጥ የሚችለው፣ በራሷ አቅም በልጽጋ ለጎረቤቶቿም የብርሃን እና የዕድገት ዋስትና መሆን ስትችል ብቻ ነው ብለን እናምናለን።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #energy #diplomacy
*************************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ በታሪኳ አዲስ እና ስልታዊ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ይህ ምዕራፍ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በኩራት ከመቁጠር እና ከመቀኘት ባለፈ እነዚያን እምቅ ሀብቶች ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ እና የጂኦፖለቲካ አቅም በመለወጥ ሀገራዊ ልዕልናን ለማረጋገጥ የሚደረግ የታሪክ መታጠፊያ ነው።
ለረጅም ዘመናት በድህነት፣ በዕርዳታ ጥገኝነት እና በውስጥ ስጋቶች ታጥሮ የቆየው የቀድሞው ዲፕሎማሲ ዛሬ በተግባር ተረትቷል። በምትኩም ቀጣናዊ ትሥሥርን የሉዓላዊነት እና የአህጉራዊ መሪነት ማረጋገጫ ያደረገው የመደመር መንግሥት ስልታዊ ራዕይ በተጨባጭ መሬት እየረገጠ ይገኛል።
በተለይም የታዳሽ ኃይል ሀብትን የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ዋና ምሰሶ አድርጎ የመጠቀም ስትራቴጂ፣ የሀገርን የፖለቲካ ተጽዕኖ እና "ለስላሳ ኃይል" (Soft Power) ከፍ ወዳለ ማዕረግ እያሸጋገረው ነው።
ኃይል ለአዳዲስ የቴክኖሎጂ አብዮቶች፣ ለዲጂታል ኢኮኖሚ እና ለሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) መሠረታዊ ግብዓት በሆነበት በዚህ በ21ኛው ክፍለ ዘመን፣ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የኃይል ማዕከል የመሆን ሕልሟን ወደ እውንነት እየቀየረችው ነው።
ይህ እውነታ በወረቀት ላይ በሰፈሩ የይስሙላ ስምምነቶች ሳይሆን፣ በድንበር ተሻጋሪ የኤሌክትሪክ መስመሮች በተግባር የተመሰከረ ሐቅ ነው። ባለፉት ጥቂት የለውጥ ዓመታት የተወሰዱት ቁርጠኛ እርምጃዎች ሱዳን፣ ጅቡቲ እና ኬንያ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ዋነኛ ተጠቃሚዎች እንዲሆኑ አስችለዋል።
የታላቁ የሕዳሴ ግድብ፣ የኮይሻ እና ሌሎች ግዙፍ ፕሮጀክቶች የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ከመሙላት ባለፈ፣ የቀጣናውን የጋራ ዕድገት የሚያረጋግጡ የትሥሥር ድልድዮች ሆነዋል። አሁን ደግሞ ይህ ቁርኝት ወደ ሌሎች ጎረቤት ሀገራት ጭምር መሻገሩ የነገውን ቀጣናዊ ትሥሥር ይበልጥ ብሩህ ያደርገዋል።
ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚደረገው ይህ ዘላቂ ትሥሥር፣ ከንግድ ልውውጥ እና ከገቢ ምንጭነት ባሻገር፣ አንዱ ሀገር ለሌላው የሕልውና ዋስትና የሚሆንበት እና የቀጣናውን ዘላቂ ሰላም በጽኑ መሠረት ላይ የሚገነባ ስልታዊ መሣሪያ መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል።
በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው ረገድም ሀገራችን ከታሪካዊው የልመና አዙሪት ወጥታ በክብር እና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ ፖሊሲን በቁርጠኝነት እየተገበረች ትገኛለች። የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነትን መተግበር፣ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት እና የብሪክስ አባል መሆን የኢትዮጵያን የፋይናንስ እና የኢንቨስትመንት አድማስ በሰፊው ከፍቶታል።
ይህ የፖሊሲ መዋቅር የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ለመቶ ሺዎች ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩ ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶችም በጎረቤት ሀገራት ኢንቨስት በማድረግ አህጉራዊ የኢኮኖሚ አሻራቸውን እንዲያስፋፉ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል።
የኢትዮጵያ የነገ ራዕይ ከአፍሪካ ቀንድ ተሻግሮ እስከ ሰሜን አፍሪካ እና አውሮፓ የሚዘልቅ ታላቅ የኃይል መረብ የመዘርጋት ታላቅ አልሚነት ነው። በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ከውኃ ኃይል በተጨማሪ በፀሐይ፣ በነፋስና በጂኦተርማል ኃይል ላይ የሚደረገው ኢንቨስትመንት የታዳሽ ኃይል ብዝኃነትን በማረጋገጥ፣ ኢትዮጵያን የቀጣናው አስተማማኝ የኃይል "ባንክ" ያደርጋታል።
ይህ ዘላቂ ጉዞ ሀገራችንን ከተረጂነት አዙሪት ሙሉ በሙሉ በማውጣት፣ በዓለም አቀፍ መድረክ በራሷ የምትቆም፣ ክብሯ የተጠበቀ እና የምሥራቅ አፍሪካ የሰላም እና የብልጽግና ፋና እንድትሆን ያደርጋታል።
ምክንያቱም የዚህች ታላቅ ሀገር እውነተኛ እና ዘላቂ ብልጽግና ሊረጋገጥ የሚችለው፣ በራሷ አቅም በልጽጋ ለጎረቤቶቿም የብርሃን እና የዕድገት ዋስትና መሆን ስትችል ብቻ ነው ብለን እናምናለን።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #energy #diplomacy
1 month ago
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የሌሎችን ሉዓላዊነት የማይጋፋ፣ ይልቁንም የጋራ ሰላምና ልማት ማረጋገጥን ታሳቢ ያደረገ ነው - ምሁራን
*****************************
ኢትዮጵያ ከባሕር በር መራቋ ለኢኮኖሚ ዕድገቷ ትልቅ ፈተና መደቀኑን የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና የዘርፉ ባለሙያዎች ገልጸዋል።
የባሕር በር ለኢትዮጵያ የብሔራዊ ጥቅም እና የሕልውና ጉዳይ በመሆኑ፣ በመደመር እሳቤ ታግዞ የጋራ ተጠቃሚነትን በሚያረጋግጥ ዲፕሎማሲያዊ መንገድ መፈጸም እንዳለበት ተመላክቷል።
የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ፣ ኢትዮጵያ ከባሕር በር መራቋ ታሪካዊ መዘዝ ያለው መሆኑን ተናግረዋል።
ሚኒስትሩ አያይዘውም፣ በውስጥም በውጪም የኢትዮጵያን ዕድገት የማይፈልጉ አካላት በመደራጀት ሀገራችን ወደብ እንዳትጠቀም የተለያዩ መሰናክሎችን ሲፈጥሩ መቆየታቸውን አንስተዋል።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የውሃ ሀብት መምህር የሆኑት በለጠ ብርሃኑ (ዶ/ር)፣ በአሁኑ የዓለም የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የባሕር በር ወይም ወደብ ማግኘት ለአንድ ሀገር ዕድገት ወሳኝ መሆኑን በአፅንዖት ገልጸዋል።
የባሕር በር ከሌለ የሀገር ዕድገት ውስን እንደሚሆን የገለጹት ዶ/ር በለጠ፣ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ አቅም ማደጉና የሕዝብ ቁጥር መጨመሩ ደግሞ ጉዳዩን አንገብጋቢ አድርጎታል ብለዋል።
አክለውም፣ መፍትሄው በመደማመጥ እና በዲፕሎማሲያዊ አካሄድ የምስራቅ አፍሪካን ቀጣናዊ ውህደት ማረጋገጥ መሆኑን ጠቁመዋል።
የፖለቲካ እና ዲፕሎማሲ መምህሩ ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ በበኩላቸው፣ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ከፖለቲካዊ ጠቀሜታው ባሻገር ለኢትዮጵያም ሆነ ለኤርትራ ሕዝቦች የጋራ ብልጽግና ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
የባሕር በርን በጋራ ማልማት እና መጠቀም ለሁለቱም ሀገራት የወደፊት ዕድገት ቁልፍ መፍትሔ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለዓመታት ሲንከባለል የመጣውን የባሕር በር ጥያቄ አሁን ላይ በዲፕሎማሲያዊ ጥበብ እንደ አዲስ እያነሳችው ትገኛለች።
ይህ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የሌሎች ሀገራትን ሉዓላዊነት የማይጋፋ፣ ይልቁንም ቀጣናዊ የጋራ ሰላምና ልማት ማረጋገጥን ታሳቢ ያደረገ መሆኑም ተመላክቷል።
በሃና ምንዳሁን
#ethiopia #seaaccess #seaport #nationalinterest #redsea #hornofafrica #diplomacy #regionalintegration #ebc
*****************************
ኢትዮጵያ ከባሕር በር መራቋ ለኢኮኖሚ ዕድገቷ ትልቅ ፈተና መደቀኑን የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና የዘርፉ ባለሙያዎች ገልጸዋል።
የባሕር በር ለኢትዮጵያ የብሔራዊ ጥቅም እና የሕልውና ጉዳይ በመሆኑ፣ በመደመር እሳቤ ታግዞ የጋራ ተጠቃሚነትን በሚያረጋግጥ ዲፕሎማሲያዊ መንገድ መፈጸም እንዳለበት ተመላክቷል።
የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ፣ ኢትዮጵያ ከባሕር በር መራቋ ታሪካዊ መዘዝ ያለው መሆኑን ተናግረዋል።
ሚኒስትሩ አያይዘውም፣ በውስጥም በውጪም የኢትዮጵያን ዕድገት የማይፈልጉ አካላት በመደራጀት ሀገራችን ወደብ እንዳትጠቀም የተለያዩ መሰናክሎችን ሲፈጥሩ መቆየታቸውን አንስተዋል።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የውሃ ሀብት መምህር የሆኑት በለጠ ብርሃኑ (ዶ/ር)፣ በአሁኑ የዓለም የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የባሕር በር ወይም ወደብ ማግኘት ለአንድ ሀገር ዕድገት ወሳኝ መሆኑን በአፅንዖት ገልጸዋል።
የባሕር በር ከሌለ የሀገር ዕድገት ውስን እንደሚሆን የገለጹት ዶ/ር በለጠ፣ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ አቅም ማደጉና የሕዝብ ቁጥር መጨመሩ ደግሞ ጉዳዩን አንገብጋቢ አድርጎታል ብለዋል።
አክለውም፣ መፍትሄው በመደማመጥ እና በዲፕሎማሲያዊ አካሄድ የምስራቅ አፍሪካን ቀጣናዊ ውህደት ማረጋገጥ መሆኑን ጠቁመዋል።
የፖለቲካ እና ዲፕሎማሲ መምህሩ ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ በበኩላቸው፣ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ከፖለቲካዊ ጠቀሜታው ባሻገር ለኢትዮጵያም ሆነ ለኤርትራ ሕዝቦች የጋራ ብልጽግና ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።
የባሕር በርን በጋራ ማልማት እና መጠቀም ለሁለቱም ሀገራት የወደፊት ዕድገት ቁልፍ መፍትሔ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ለዓመታት ሲንከባለል የመጣውን የባሕር በር ጥያቄ አሁን ላይ በዲፕሎማሲያዊ ጥበብ እንደ አዲስ እያነሳችው ትገኛለች።
ይህ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የሌሎች ሀገራትን ሉዓላዊነት የማይጋፋ፣ ይልቁንም ቀጣናዊ የጋራ ሰላምና ልማት ማረጋገጥን ታሳቢ ያደረገ መሆኑም ተመላክቷል።
በሃና ምንዳሁን
#ethiopia #seaaccess #seaport #nationalinterest #redsea #hornofafrica #diplomacy #regionalintegration #ebc
1 month ago
“ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ከድንበር በላይ የሚጋሩት ነገር አለ፤ እሱም እጅግ ውድ የሆነውን ሕዝባችንን እና የጋራ ዕጣ ፈንታችንን ነው”
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #diplomacy #pmoethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #diplomacy #pmoethiopia
1 month ago
ከ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ማግስት፦ የነገዋ ኢትዮጵያ አቅጣጫ እና ከመንግሥት የሚጠበቁ ኃላፊነቶች
***************************
የዘንድሮው 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዞ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ታሪካዊ ምዕራፍ ነው።
ምርጫውን አሸንፎ መንግሥት የሚመሰርተው ፓርቲ የሕዝብን አደራ ተቀብሎ ሀገራችንን ወደ ተሻለ ምዕራፍ የማሻገር ከባድ ኃገራዊ ኃላፊነት ይወድቅበታል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተለያዩ መድረኮች ባስተላለፏቸው መልዕክቶች፣ የፓርላማውን አብላጫ ድምጽ በማግኘት መንግሥት የሚመሰርተው ፓርቲ ድርብ ኃላፊነት እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።
ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሻገር የተጀመሩ እና በዕቅድ የተያዙ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን በተሻለ ሁኔታ መፈጸም ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው። ከእነዚህ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፡-
ሰብዓዊነትን ማዕከል ያደረገ አመራር እና የጸጥታ ተቋማት ግንባታ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ "ሰብዓዊነትን ማዕከል ያደረገ አመራር" አስፈላጊነትን ደጋግመው አንስተዋል።
አዲስ የሚመሰረተው መንግሥትም ይህን መርህ በተግባር በመተርጎም የዜጎችን ደኅንነት እና ሰላም ማስቀደም ይጠበቅበታል።
የጸጥታ እና የደኅንነት ተቋማትን ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ የሆኑ፣ ዘመናዊ እና ሕዝብን የሚያገለግሉ አድርጎ የመገንባቱ የሪፎርም ሥራ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ሲሠራ ቆይቷል። ይህ አሁንም ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
የዜጎች ደኅንነት በእኩልነት ሲረጋገጥ እና የጸጥታ መዋቅሩ የሁሉንም ኢትዮጵያዊ መብት ለማስጠበቅ ሲቆም ብቻ ሀገራዊ መረጋጋትን እና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ማሳካት ይቻላል።
ጎረቤትን ያስቀደመ ዲፕሎማሲ እና ቀጣናዊ ትስስር
በውጭ ግንኙነት ረገድ አሸናፊው ፓርቲ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስጠብቅ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ሥራ መሥራት ይኖርበታል።
መንግሥት የሚከተለውን ጎረቤት ተኮር የዲፕሎማሲ ስትራቴጂ ይበልጥ በማጠናከር ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስር ውስጥ ያላትን የመሪነት ሚና ማስቀጠል ይጠበቅበታል።
ከዚህም ባሻገር ለመካከለኛው ምሥራቅ እና ለባሕረ ሰላጤው ጂኦፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች የቅርብ ትኩረት ሊሰጥ ይገባል።
በቀጣናው ሊፈጠሩ የሚችሉ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎችን የሚቋቋም ሚዛናዊ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲን መተግበር በቀጣይ ከመንግሥት የሚጠበቅ ወሳኝ ኃላፊነት ነው።
የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ
አዲስ የሚመሰረተው መንግሥት ሌላው ትልቅ ኃላፊነት ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትን ማረጋገጥ ነው።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርን በማስፋት የኢትዮጵያን የደን ሽፋን ከማሳደግ ባለፈ፣ ሀገራችን ከካርበን ንግድ ተጠቃሚ የምትሆንበትን "የአረንጓዴ ወርቅ" የኢኮኖሚ ሥርዓት መገንባት ይገባዋል።
ይህ አካሄድ የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባሻገር፣ አዲስ የውጭ ምንዛሬ ማስገኛ አቅም በመፍጠር የዜጎችን ተጠቃሚነት ያረጋግጣል።
የሀገራዊ ምክክር ውጤትን ተግባራዊ ማድረግ
አዲሱ መንግሥት ትልቅ ትኩረት ሊሰጣቸው ከሚገቡ ጉዳዮች መካከል የሀገራዊ ምክክሩን ውጤት ተቀብሎ ወደ ተግባር መቀየር ቀዳሚው ነው።
የምክክሩ ውጤት የነገዋን የበለጸገች እና የተረጋጋች ኢትዮጵያን ለመገንባት ጠንካራ መሰረት የሚጥል ነው።
የምክክሩ ውጤት የሕግ የበላይነት የነገሰባት፣ ሰብዓዊ መብቶች ይበልጥ የሚከበሩባት እና የተጠናከረ የፍትሕ ሥርዓት የተረጋገጠባት ሀገር ለመገንባት ወሳኝ ግብዓት ነው።
የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም
ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ውጤታማነቱ እየታየ ይገኛል። በዚህም ኢትዮጵያ በዘንድሮው በጀት ዓመት ማጠቃለያ የ10.2 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት እንደምታስመዘግብ ይጠበቃል።
የመንግሥት ቀጣዩ ዋና ሥራ ይህ ዕድገት ወደ እያንዳንዱ ዜጋ ሕይወት እንዲወርድ ማድረግ ነው።
ለዚህም የዋጋ ንረትን መቆጣጠር፣ የኑሮ ውድነትን ማቃለል እና የውጭ ብድር ጫናን ማስተካከል ከአዲሱ መንግሥት የሚጠበቁ እና ፈጣን ምላሽ የሚሹ አንገብጋቢ የቤት ሥራዎች ናቸው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopia #economicreform #macroeconomy #diplomacy #greenlegacy #ebc
***************************
የዘንድሮው 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዞ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ታሪካዊ ምዕራፍ ነው።
ምርጫውን አሸንፎ መንግሥት የሚመሰርተው ፓርቲ የሕዝብን አደራ ተቀብሎ ሀገራችንን ወደ ተሻለ ምዕራፍ የማሻገር ከባድ ኃገራዊ ኃላፊነት ይወድቅበታል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተለያዩ መድረኮች ባስተላለፏቸው መልዕክቶች፣ የፓርላማውን አብላጫ ድምጽ በማግኘት መንግሥት የሚመሰርተው ፓርቲ ድርብ ኃላፊነት እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።
ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሻገር የተጀመሩ እና በዕቅድ የተያዙ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን በተሻለ ሁኔታ መፈጸም ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው። ከእነዚህ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፡-
ሰብዓዊነትን ማዕከል ያደረገ አመራር እና የጸጥታ ተቋማት ግንባታ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ "ሰብዓዊነትን ማዕከል ያደረገ አመራር" አስፈላጊነትን ደጋግመው አንስተዋል።
አዲስ የሚመሰረተው መንግሥትም ይህን መርህ በተግባር በመተርጎም የዜጎችን ደኅንነት እና ሰላም ማስቀደም ይጠበቅበታል።
የጸጥታ እና የደኅንነት ተቋማትን ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ የሆኑ፣ ዘመናዊ እና ሕዝብን የሚያገለግሉ አድርጎ የመገንባቱ የሪፎርም ሥራ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ሲሠራ ቆይቷል። ይህ አሁንም ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
የዜጎች ደኅንነት በእኩልነት ሲረጋገጥ እና የጸጥታ መዋቅሩ የሁሉንም ኢትዮጵያዊ መብት ለማስጠበቅ ሲቆም ብቻ ሀገራዊ መረጋጋትን እና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ማሳካት ይቻላል።
ጎረቤትን ያስቀደመ ዲፕሎማሲ እና ቀጣናዊ ትስስር
በውጭ ግንኙነት ረገድ አሸናፊው ፓርቲ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስጠብቅ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ሥራ መሥራት ይኖርበታል።
መንግሥት የሚከተለውን ጎረቤት ተኮር የዲፕሎማሲ ስትራቴጂ ይበልጥ በማጠናከር ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስር ውስጥ ያላትን የመሪነት ሚና ማስቀጠል ይጠበቅበታል።
ከዚህም ባሻገር ለመካከለኛው ምሥራቅ እና ለባሕረ ሰላጤው ጂኦፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች የቅርብ ትኩረት ሊሰጥ ይገባል።
በቀጣናው ሊፈጠሩ የሚችሉ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎችን የሚቋቋም ሚዛናዊ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲን መተግበር በቀጣይ ከመንግሥት የሚጠበቅ ወሳኝ ኃላፊነት ነው።
የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ
አዲስ የሚመሰረተው መንግሥት ሌላው ትልቅ ኃላፊነት ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትን ማረጋገጥ ነው።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርን በማስፋት የኢትዮጵያን የደን ሽፋን ከማሳደግ ባለፈ፣ ሀገራችን ከካርበን ንግድ ተጠቃሚ የምትሆንበትን "የአረንጓዴ ወርቅ" የኢኮኖሚ ሥርዓት መገንባት ይገባዋል።
ይህ አካሄድ የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባሻገር፣ አዲስ የውጭ ምንዛሬ ማስገኛ አቅም በመፍጠር የዜጎችን ተጠቃሚነት ያረጋግጣል።
የሀገራዊ ምክክር ውጤትን ተግባራዊ ማድረግ
አዲሱ መንግሥት ትልቅ ትኩረት ሊሰጣቸው ከሚገቡ ጉዳዮች መካከል የሀገራዊ ምክክሩን ውጤት ተቀብሎ ወደ ተግባር መቀየር ቀዳሚው ነው።
የምክክሩ ውጤት የነገዋን የበለጸገች እና የተረጋጋች ኢትዮጵያን ለመገንባት ጠንካራ መሰረት የሚጥል ነው።
የምክክሩ ውጤት የሕግ የበላይነት የነገሰባት፣ ሰብዓዊ መብቶች ይበልጥ የሚከበሩባት እና የተጠናከረ የፍትሕ ሥርዓት የተረጋገጠባት ሀገር ለመገንባት ወሳኝ ግብዓት ነው።
የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም
ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ውጤታማነቱ እየታየ ይገኛል። በዚህም ኢትዮጵያ በዘንድሮው በጀት ዓመት ማጠቃለያ የ10.2 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት እንደምታስመዘግብ ይጠበቃል።
የመንግሥት ቀጣዩ ዋና ሥራ ይህ ዕድገት ወደ እያንዳንዱ ዜጋ ሕይወት እንዲወርድ ማድረግ ነው።
ለዚህም የዋጋ ንረትን መቆጣጠር፣ የኑሮ ውድነትን ማቃለል እና የውጭ ብድር ጫናን ማስተካከል ከአዲሱ መንግሥት የሚጠበቁ እና ፈጣን ምላሽ የሚሹ አንገብጋቢ የቤት ሥራዎች ናቸው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopia #economicreform #macroeconomy #diplomacy #greenlegacy #ebc
2 months ago
ከፈተና ወደ ከፍታ፦ “ኢትዮጵያን ማንም አያሸንፍም” የሚለው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል በተግባር ሲገለጥ
******************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰኔ 23 ቀን 2013 ዓ.ም “ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ማንም አያሸንፍም” ማለታቸው ይታወሳል።
ይህ ታሪካዊ መልዕክት በወቅቱ ከነበረው ውስብስብ የጸጥታ እና የፖለቲካ ውጥረት አኳያ ስሜት ቀስቃሽ መፈክር አልነበረም፤ ይልቁንም ሀገራችን ፈተናዎችን በጽናት አልፋ ወደ ከፍታ የምታደርገውን ጉዞ ያበሰረ የተግባር ቃል እንጂ።
በወቅቱ በትግራይ ክልል ለሕግ ማስከበር እና ለመልሶ ማቋቋም ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት፣ እንዲሁም ከፍተኛ ዓለም አቀፋዊ ጫናዎች የበረቱበት ጊዜ በመሆኑ፣ የሀገር ቀጣይነት ራሱ ትልቅ ጥያቄ ውስጥ የወደቀ መስሎ ነበር።
ይሁን እንጂ መፍረሷን የተመኙ ታሪካዊ ኃይሎች በየአቅጣጫው ቢሴሩም ያ የተስፋ ቃል ባለፉት አምስት ዓመታት በሁሉም ግንባሮች ወደ ተጨባጭ ድል ተቀይሯል። ሀገራችን በፖለቲካ፣ በዲፕሎማሲ እና በኢኮኖሚ ዘርፎች ታላላቅ ስኬቶችን በማስመዝገብ መዋቅራዊ ሽግግር እያደረገች ትገኛለች።
ፖለቲካዊ ሽግግር እና የሀገረ መንግሥት ግንባታ
በፖለቲካው መስክ ያጋጠሙ የውስጥ መከፋፈሎችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ታሪካዊ እርምጃዎች ተወስደዋል።
በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የተፈረመው የሰላም ስምምነት በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረውን ጦርነት በዘላቂነት ማስቆም የቻለ ሲሆን ኢትዮጵያ ‘የአፍሪካን ችግሮች በአፍሪካዊ መፍትሔ’ በሚለው መርህ ችግሯን መፍታት መቻሏን በተግባር ያረጋገጠችበት ነው።
በተጨማሪም የዘመናት የፖለቲካ ቁርሾዎችን በጠረጴዛ ዙሪያ ለመፍታት የተቋቋመው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሰፊ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራዎችን አከናውኖ፣ ዋናውን ሀገር አቀፍ የምክክር ጉባኤ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ይገኛል። ይህም ልዩነቶችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታት የተጀመረውን የሽግግር ሂደት በተጨባጭ ያሳያል።
እነዚህ ተቋማዊ ግንባታዎችና የፀጥታ መዋቅር ማሻሻያዎች የሕዝብን አንድነት በማጠናከር የመከፋፈል አጀንዳዎችን ማክሸፍ ችለዋል።
የዲፕሎማሲ እና የሉዓላዊነት ድሎች
በዲፕሎማሲው መድረክ ኢትዮጵያ ያልተገቡ ዓለም አቀፍ ጫናዎችን እና የተዛቡ ትርክቶችን በጥበብ በማለፍ ብሔራዊ ጥቅሟን አስከብራለች። እ.አ.አ በ2024 የብሪክስ (BRICS) ሙሉ አባል መሆኗ የሀገራችንን የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
በሌላ በኩል የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቅቆ ኃይል ማመንጨት የጀመረ ሲሆን በአፍሪካ ግዙፍ የሆነው ይህ ፕሮጀክት ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ከማጠናከር ባለፈ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን እያሳደገ ይገኛል።
የናይል ተፋሰስ የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት (CFA) በይፋ መጽደቁም የዘመናት የአንድ ወገን ተጠቃሚነት ታሪክን ወደ ፍትሐዊና የጋራ ተጠቃሚነት የለወጠ ታላቅ የዲፕሎማሲ ድል ተጠቃሽ ነው።
የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና አገራዊ ግስጋሴ
የሀገራችን ሁለንተናዊ አሸናፊነት በኢኮኖሚው ዘርፍም ጎልቶ ታይቷል። ተግባራዊ የተደረገው ሁለገብ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ኢንቨስትመንትን የሚስቡ ውጤታማ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ማክሮ-ኢኮኖሚውን አነቃቅቷል።
በጥቁር ገበያ ይባክን የነበረውን የውጭ ምንዛሬ ወደ ሕጋዊ ሥርዓት በማስገባት፣ በታሪክ ከፍተኛ የተባለ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ላይ መድረስ ተችሏል።
በግብርናው ዘርፍ፣ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የታየው መዋቅራዊ ሽግግር ሀገራችንን ከምግብ ጥገኝነት እያላቀቃት ሲሆን ምርቱ መጨመር ብቻ በዓመት ወደ 1 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሪ ማዳን አስችሏል።
ሜጋ ፕሮጀክቶች፣ የከተማ ልማት እና አረንጓዴ አሻራ
ይህ ሁለንተናዊ መነቃቃት በታላላቅ ፕሮጀክቶችም በግልጽ እየታየ ይገኛል። በአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን በቀጣዩ ሁለት ዓመታት ይህን ቁጥር 65 ቢሊዮን ለማድረስ እየተሠራ ነው።
በመዲናችን አዲስ አበባ የተጀመረው እና የዓለምን ትኩረት የሳበው የከተማ ኮሪደር ልማት በአሁኑ ወቅት ወደ 75 የሀገራችን ከተሞች በመስፋፋት ከተሜነትን እያዘመነ ይገኛል።
በእነዚህ ዓመታት የተለወጠችው አዲስ አበባ “ደህንነቷ አስተማማኝ አይደለም” በማለት ይቀርቡ የነበሩ አሉታዊ ትርክቶችን በማክሸፍ የዲፕሎማቶች እና ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ተመራጭ መናኸሪያ ሆናለች።
በተጓዳኝም የአርሶ አደሩን ሕይወት የሚያዘምኑ የገጠር ኮሪደሮች እና ሞዴል መንደሮች ግንባታ ተጀምሯል። በመሰረተ ልማት ረገድ በ"ሚሽን 300" እና በ"አሰንት" ፕሮጀክቶች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች አዲስ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ መሆን ችለዋል።
በዓመት 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ያለው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታም በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል።
ምንም እንኳን ከቀድሞ የተወረሰ የዕዳ ጫና እና እንደ የዋጋ ንረት ያሉ ማኅበራዊ ፈተናዎች አሁንም ሙሉ በሙሉ ባይቀረፉም፣ ባለፉት አምስት ዓመታት የተመዘገቡት እነዚህ ታሪካዊ ስኬቶች የኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ የማይቀለበስ መሆኑን የሚያረጋግጡ ሕያው ምስክሮች ናቸው።
ከዚህ አኳያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “ኢትዮጵያን፣ ኢትዮጵያዊነትን ማንም አያሸንፍም” ሲሉ የተናገሩት ቃል መሬት የነካና በተጨባጭ መረጃዎች የተረጋገጠ አገራዊ ሀቅ መሆኑን ማየት እንችላለን።
ተግዳሮቶቻችንን ወደ ዕድል በመቀየር እነዚህን አበረታች ውጤቶች አጠናክረን በመቀጠል፣ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ የሁሉም ዜጋ ርብርብና ብሔራዊ መግባባት ወሳኝ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #resilience #economicgrowth #diplomacy #nationaldialogue #ebc
******************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰኔ 23 ቀን 2013 ዓ.ም “ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ማንም አያሸንፍም” ማለታቸው ይታወሳል።
ይህ ታሪካዊ መልዕክት በወቅቱ ከነበረው ውስብስብ የጸጥታ እና የፖለቲካ ውጥረት አኳያ ስሜት ቀስቃሽ መፈክር አልነበረም፤ ይልቁንም ሀገራችን ፈተናዎችን በጽናት አልፋ ወደ ከፍታ የምታደርገውን ጉዞ ያበሰረ የተግባር ቃል እንጂ።
በወቅቱ በትግራይ ክልል ለሕግ ማስከበር እና ለመልሶ ማቋቋም ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት፣ እንዲሁም ከፍተኛ ዓለም አቀፋዊ ጫናዎች የበረቱበት ጊዜ በመሆኑ፣ የሀገር ቀጣይነት ራሱ ትልቅ ጥያቄ ውስጥ የወደቀ መስሎ ነበር።
ይሁን እንጂ መፍረሷን የተመኙ ታሪካዊ ኃይሎች በየአቅጣጫው ቢሴሩም ያ የተስፋ ቃል ባለፉት አምስት ዓመታት በሁሉም ግንባሮች ወደ ተጨባጭ ድል ተቀይሯል። ሀገራችን በፖለቲካ፣ በዲፕሎማሲ እና በኢኮኖሚ ዘርፎች ታላላቅ ስኬቶችን በማስመዝገብ መዋቅራዊ ሽግግር እያደረገች ትገኛለች።
ፖለቲካዊ ሽግግር እና የሀገረ መንግሥት ግንባታ
በፖለቲካው መስክ ያጋጠሙ የውስጥ መከፋፈሎችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ታሪካዊ እርምጃዎች ተወስደዋል።
በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የተፈረመው የሰላም ስምምነት በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረውን ጦርነት በዘላቂነት ማስቆም የቻለ ሲሆን ኢትዮጵያ ‘የአፍሪካን ችግሮች በአፍሪካዊ መፍትሔ’ በሚለው መርህ ችግሯን መፍታት መቻሏን በተግባር ያረጋገጠችበት ነው።
በተጨማሪም የዘመናት የፖለቲካ ቁርሾዎችን በጠረጴዛ ዙሪያ ለመፍታት የተቋቋመው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሰፊ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራዎችን አከናውኖ፣ ዋናውን ሀገር አቀፍ የምክክር ጉባኤ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ይገኛል። ይህም ልዩነቶችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታት የተጀመረውን የሽግግር ሂደት በተጨባጭ ያሳያል።
እነዚህ ተቋማዊ ግንባታዎችና የፀጥታ መዋቅር ማሻሻያዎች የሕዝብን አንድነት በማጠናከር የመከፋፈል አጀንዳዎችን ማክሸፍ ችለዋል።
የዲፕሎማሲ እና የሉዓላዊነት ድሎች
በዲፕሎማሲው መድረክ ኢትዮጵያ ያልተገቡ ዓለም አቀፍ ጫናዎችን እና የተዛቡ ትርክቶችን በጥበብ በማለፍ ብሔራዊ ጥቅሟን አስከብራለች። እ.አ.አ በ2024 የብሪክስ (BRICS) ሙሉ አባል መሆኗ የሀገራችንን የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
በሌላ በኩል የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቅቆ ኃይል ማመንጨት የጀመረ ሲሆን በአፍሪካ ግዙፍ የሆነው ይህ ፕሮጀክት ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ከማጠናከር ባለፈ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን እያሳደገ ይገኛል።
የናይል ተፋሰስ የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት (CFA) በይፋ መጽደቁም የዘመናት የአንድ ወገን ተጠቃሚነት ታሪክን ወደ ፍትሐዊና የጋራ ተጠቃሚነት የለወጠ ታላቅ የዲፕሎማሲ ድል ተጠቃሽ ነው።
የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና አገራዊ ግስጋሴ
የሀገራችን ሁለንተናዊ አሸናፊነት በኢኮኖሚው ዘርፍም ጎልቶ ታይቷል። ተግባራዊ የተደረገው ሁለገብ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ኢንቨስትመንትን የሚስቡ ውጤታማ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ማክሮ-ኢኮኖሚውን አነቃቅቷል።
በጥቁር ገበያ ይባክን የነበረውን የውጭ ምንዛሬ ወደ ሕጋዊ ሥርዓት በማስገባት፣ በታሪክ ከፍተኛ የተባለ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ላይ መድረስ ተችሏል።
በግብርናው ዘርፍ፣ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የታየው መዋቅራዊ ሽግግር ሀገራችንን ከምግብ ጥገኝነት እያላቀቃት ሲሆን ምርቱ መጨመር ብቻ በዓመት ወደ 1 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሪ ማዳን አስችሏል።
ሜጋ ፕሮጀክቶች፣ የከተማ ልማት እና አረንጓዴ አሻራ
ይህ ሁለንተናዊ መነቃቃት በታላላቅ ፕሮጀክቶችም በግልጽ እየታየ ይገኛል። በአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን በቀጣዩ ሁለት ዓመታት ይህን ቁጥር 65 ቢሊዮን ለማድረስ እየተሠራ ነው።
በመዲናችን አዲስ አበባ የተጀመረው እና የዓለምን ትኩረት የሳበው የከተማ ኮሪደር ልማት በአሁኑ ወቅት ወደ 75 የሀገራችን ከተሞች በመስፋፋት ከተሜነትን እያዘመነ ይገኛል።
በእነዚህ ዓመታት የተለወጠችው አዲስ አበባ “ደህንነቷ አስተማማኝ አይደለም” በማለት ይቀርቡ የነበሩ አሉታዊ ትርክቶችን በማክሸፍ የዲፕሎማቶች እና ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ተመራጭ መናኸሪያ ሆናለች።
በተጓዳኝም የአርሶ አደሩን ሕይወት የሚያዘምኑ የገጠር ኮሪደሮች እና ሞዴል መንደሮች ግንባታ ተጀምሯል። በመሰረተ ልማት ረገድ በ"ሚሽን 300" እና በ"አሰንት" ፕሮጀክቶች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች አዲስ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ መሆን ችለዋል።
በዓመት 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ያለው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታም በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል።
ምንም እንኳን ከቀድሞ የተወረሰ የዕዳ ጫና እና እንደ የዋጋ ንረት ያሉ ማኅበራዊ ፈተናዎች አሁንም ሙሉ በሙሉ ባይቀረፉም፣ ባለፉት አምስት ዓመታት የተመዘገቡት እነዚህ ታሪካዊ ስኬቶች የኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ የማይቀለበስ መሆኑን የሚያረጋግጡ ሕያው ምስክሮች ናቸው።
ከዚህ አኳያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “ኢትዮጵያን፣ ኢትዮጵያዊነትን ማንም አያሸንፍም” ሲሉ የተናገሩት ቃል መሬት የነካና በተጨባጭ መረጃዎች የተረጋገጠ አገራዊ ሀቅ መሆኑን ማየት እንችላለን።
ተግዳሮቶቻችንን ወደ ዕድል በመቀየር እነዚህን አበረታች ውጤቶች አጠናክረን በመቀጠል፣ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ የሁሉም ዜጋ ርብርብና ብሔራዊ መግባባት ወሳኝ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #resilience #economicgrowth #diplomacy #nationaldialogue #ebc
Sponsored by
Surafel
2 months ago
የእሥራኤል 78ኛ ዓመት የነፃነት ቀን፤
የሰባ ዓመታት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት
#ethiopia | በአዲስ አበባ የሚገኘው የእሥራኤል ኤምባሲ የሀገሪቱን 78ኛ ዓመት የነፃነት ቀን ዮም ሃአትዝማውትን ደማቅ በሆነ ስነ ስርዓት አክብሯል።
በዓሉ በእሥራኤል የቀን አቆጣጠር መሰረት በሚያዝያ ወር መከበር የነበረበት ቢሆንም በወቅቱ በነበሩ አካባቢያዊ ክስተቶች ሳቢያ ወደ ሌላ ጊዜ መሸጋገሩ ተገልጾ በተለይ የዕለቱ የክብር እንግዶች ላሳዩት ትዕግስትና ላበረከቱት ወዳጅነት ምስጋና ቀርቧል።
በክብረ በዓሉ ላይ ንግግር ያደረጉት በኢትዮጵያ የእሥራኤል አምባሳደር ዶ/ር አብርሃም ንጉሤ ሀገራቸው እ.ኤ.አ. በ1948 ነፃነቷን ካወጀችበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ የህልውና ፈተናዎችን በጽናት መወጣቷን አስታውሰዋል።
እሥራኤል በዘመናዊ መዋቅር የ78 ዓመት ወጣት ሀገር ብትሆንም ታሪኳ ከአብርሃምና ከሙሴ ዘመን የሚቀዳ የ4 ሺህ ዓመታት ጥንታዊ ቅርስና የነፃነት ታሪክ መሠረት እንዳለው አብራርተዋል።
ይህ የዘንድሮ በዓል በኢትዮጵያና በእሥራኤል መካከል የተጀመረውን ዘመናዊ የሁለትዮሽ መደበኛ ግንኙነት 70ኛ ዓመት ወርቃማ ኢዮቤልዩ የሚዘክር በመሆኑ ልዩ ትርጉም አለው።
አምባሳደር ዶ/ር አብርሃም ሰፊ ገለጻ አኳያ እ.ኤ.አ. በ1956 በአዲስ አበባ የመጀመሪያው የእሥራኤል ቆንስላ መከፈቱ ለዘመናዊው ትስስር መነሻ ቢሆንም የሁለቱ ሕዝቦች ወዳጅነት ግን በንግሥተ ሳባና በንጉሥ ሰሎሞን ታሪክ ላይ የተገነባ የ3 ሺህ ዓመታት ጥልቅ ታሪካዊ መሠረት ያለው መሆኑ ተገልጿል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል የነበረው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከ1973 እስከ 1989 ላለፉት 16 ዓመታት ተቋርጦ የነበረ ቢሆንም በሕዝቦች ልብ ውስጥ ባለው ጠንካራ ትስስር ምክንያት ይበልጥ በጠነከረ መሠረት ላይ ሊመለስ ችሏል።
በአሁኑ ወቅት የሁለትዮሽ ግንኙነቱ እጅግ ከፍተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የተጠቀሰ ሲሆን ባለፉት ወራት የእስራኤሉ ፕሬዚዳንት ይስሐቅ ሄርዞግ በአዲስ አበባ ያደረጉት ታሪካዊ ጉብኝት እንዲሁም የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሐደራ አበራ በእስራኤል ያደረጉት የፖለቲካ ምክክር የዚህ ማረጋገጫዎች ናቸው ብለዋል።
አምባሳደር ዶ/ር አብርሃም አያይዘውም ሀገራቱ በማሻቭ በኩል በግብርና ቴክኖሎጂ፣ በውሃ አጠቃቀም፣ በጤና እና በቴክኖሎጂ ዘርፎች በጋራ እያከናወኗቸው ያሉ የልማት ሥራዎች ስኬታማ መሆናቸው ተነስቷል። የባህል ትስስሩን ይበልጥ ለማሳደግም በቅርቡ የሁለቱ ሀገራት የሙዚቃ ባለሙያዎች የተሳተፉበት የእሥራኤል-ኢትዮጵያ የባህል ምሽት ተካሂዷል።
ከ35 ዓመታት በፊት በሰሎሞን ዘመቻ በ36 ሰዓታት ውስጥ ከ14 ሺህ በላይ የቤተ እሥራኤል ማህበረሰብ አባላት ወደ እስራኤል መጓዛቸውና በአሁኑ ወቅት ቁጥራቸው ከ180 ሺህ በላይ የደረሱት ቤተእስራኤላውያን ለሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ዋነኛ የሕዝብ ድልድይ መሆናቸው አውስተዋል።
በመጨረሻም ጥቅምት 2023 የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ እሥራኤል አሁንም የደኅንነት ስጋቶች ቢገጥሟትም የታገቱ ዜጎቿን በሙሉ ባለፈው ጥቅምት ወር ማስመለስ መቻሏ ትልቅ እፎይታን የፈጠረ ሲሆን የሀገሪቱ ኢኮኖሚና ቴክኖሎጂ አሁንም በጠንካራ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
በኢትዮጵያ ለሦስት ዓመታት በምክትል አምባሳደርነት ያገለገሉትን ቶመር ባር-ላቪን የሥራ ዘመን መጠናቀቅን አስመልክቶ በኤምባሲው ስም ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምስጋና የቀረበላቸው ሲሆን የበዓሉ ታዳሚዎች በባህላዊ የሙዚቃና የምግብ ዝግጅቶች እጅግ ደስ የሚል ጊዜን አሳልፈዋል።
በዚህ ልዩ የክብር ሥነ ሥርዓት ላይ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰሎሞን ሶካ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የመካከለኛው ምስራቅ፣ እስያና ፓስፊክ ሀገራት ጉዳዮች ምክትል ዋና ዳይሬክተር አምሃ ኃይለጊዮርጊስ፣ የፓርላማ አባላት፣ አምባሳደሮች፣ የሃይማኖት አባቶችና የንግዱ ማህበረሰብ ተወካዮች ተገኝተዋል።
#israel #yomhaatzmaut #ethioisrael #diplomacy #history #culture #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
የሰባ ዓመታት የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት
#ethiopia | በአዲስ አበባ የሚገኘው የእሥራኤል ኤምባሲ የሀገሪቱን 78ኛ ዓመት የነፃነት ቀን ዮም ሃአትዝማውትን ደማቅ በሆነ ስነ ስርዓት አክብሯል።
በዓሉ በእሥራኤል የቀን አቆጣጠር መሰረት በሚያዝያ ወር መከበር የነበረበት ቢሆንም በወቅቱ በነበሩ አካባቢያዊ ክስተቶች ሳቢያ ወደ ሌላ ጊዜ መሸጋገሩ ተገልጾ በተለይ የዕለቱ የክብር እንግዶች ላሳዩት ትዕግስትና ላበረከቱት ወዳጅነት ምስጋና ቀርቧል።
በክብረ በዓሉ ላይ ንግግር ያደረጉት በኢትዮጵያ የእሥራኤል አምባሳደር ዶ/ር አብርሃም ንጉሤ ሀገራቸው እ.ኤ.አ. በ1948 ነፃነቷን ካወጀችበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ የህልውና ፈተናዎችን በጽናት መወጣቷን አስታውሰዋል።
እሥራኤል በዘመናዊ መዋቅር የ78 ዓመት ወጣት ሀገር ብትሆንም ታሪኳ ከአብርሃምና ከሙሴ ዘመን የሚቀዳ የ4 ሺህ ዓመታት ጥንታዊ ቅርስና የነፃነት ታሪክ መሠረት እንዳለው አብራርተዋል።
ይህ የዘንድሮ በዓል በኢትዮጵያና በእሥራኤል መካከል የተጀመረውን ዘመናዊ የሁለትዮሽ መደበኛ ግንኙነት 70ኛ ዓመት ወርቃማ ኢዮቤልዩ የሚዘክር በመሆኑ ልዩ ትርጉም አለው።
አምባሳደር ዶ/ር አብርሃም ሰፊ ገለጻ አኳያ እ.ኤ.አ. በ1956 በአዲስ አበባ የመጀመሪያው የእሥራኤል ቆንስላ መከፈቱ ለዘመናዊው ትስስር መነሻ ቢሆንም የሁለቱ ሕዝቦች ወዳጅነት ግን በንግሥተ ሳባና በንጉሥ ሰሎሞን ታሪክ ላይ የተገነባ የ3 ሺህ ዓመታት ጥልቅ ታሪካዊ መሠረት ያለው መሆኑ ተገልጿል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል የነበረው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከ1973 እስከ 1989 ላለፉት 16 ዓመታት ተቋርጦ የነበረ ቢሆንም በሕዝቦች ልብ ውስጥ ባለው ጠንካራ ትስስር ምክንያት ይበልጥ በጠነከረ መሠረት ላይ ሊመለስ ችሏል።
በአሁኑ ወቅት የሁለትዮሽ ግንኙነቱ እጅግ ከፍተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የተጠቀሰ ሲሆን ባለፉት ወራት የእስራኤሉ ፕሬዚዳንት ይስሐቅ ሄርዞግ በአዲስ አበባ ያደረጉት ታሪካዊ ጉብኝት እንዲሁም የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሐደራ አበራ በእስራኤል ያደረጉት የፖለቲካ ምክክር የዚህ ማረጋገጫዎች ናቸው ብለዋል።
አምባሳደር ዶ/ር አብርሃም አያይዘውም ሀገራቱ በማሻቭ በኩል በግብርና ቴክኖሎጂ፣ በውሃ አጠቃቀም፣ በጤና እና በቴክኖሎጂ ዘርፎች በጋራ እያከናወኗቸው ያሉ የልማት ሥራዎች ስኬታማ መሆናቸው ተነስቷል። የባህል ትስስሩን ይበልጥ ለማሳደግም በቅርቡ የሁለቱ ሀገራት የሙዚቃ ባለሙያዎች የተሳተፉበት የእሥራኤል-ኢትዮጵያ የባህል ምሽት ተካሂዷል።
ከ35 ዓመታት በፊት በሰሎሞን ዘመቻ በ36 ሰዓታት ውስጥ ከ14 ሺህ በላይ የቤተ እሥራኤል ማህበረሰብ አባላት ወደ እስራኤል መጓዛቸውና በአሁኑ ወቅት ቁጥራቸው ከ180 ሺህ በላይ የደረሱት ቤተእስራኤላውያን ለሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ዋነኛ የሕዝብ ድልድይ መሆናቸው አውስተዋል።
በመጨረሻም ጥቅምት 2023 የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ እሥራኤል አሁንም የደኅንነት ስጋቶች ቢገጥሟትም የታገቱ ዜጎቿን በሙሉ ባለፈው ጥቅምት ወር ማስመለስ መቻሏ ትልቅ እፎይታን የፈጠረ ሲሆን የሀገሪቱ ኢኮኖሚና ቴክኖሎጂ አሁንም በጠንካራ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
በኢትዮጵያ ለሦስት ዓመታት በምክትል አምባሳደርነት ያገለገሉትን ቶመር ባር-ላቪን የሥራ ዘመን መጠናቀቅን አስመልክቶ በኤምባሲው ስም ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምስጋና የቀረበላቸው ሲሆን የበዓሉ ታዳሚዎች በባህላዊ የሙዚቃና የምግብ ዝግጅቶች እጅግ ደስ የሚል ጊዜን አሳልፈዋል።
በዚህ ልዩ የክብር ሥነ ሥርዓት ላይ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰሎሞን ሶካ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የመካከለኛው ምስራቅ፣ እስያና ፓስፊክ ሀገራት ጉዳዮች ምክትል ዋና ዳይሬክተር አምሃ ኃይለጊዮርጊስ፣ የፓርላማ አባላት፣ አምባሳደሮች፣ የሃይማኖት አባቶችና የንግዱ ማህበረሰብ ተወካዮች ተገኝተዋል።
#israel #yomhaatzmaut #ethioisrael #diplomacy #history #culture #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የደስታ መግለጫ ለህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር
#pmabiyahmed #ethiopia #india #diplomacy #leadership #globalsouth #ethiopianbroadcastingcorporation
2 months ago
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት
****************
"ታላቅ ወንድሜ እና ውድ ወዳጄ ክቡር ናሬንድራ ሞዲ፣ የዓለማችንን ትልቁን እና እጅግ ንቁ የሆነውን የዲሞክራሲ ማህበረሰብ ዘላቂ እምነት በማግኘት፣ ህንድን በራዕይ እና በቁርጠኝነት በተከታታይ ሶስት የዲሞክራሲያዊ የስልጣን ዘመናት በመምራት ላስመዘገቡት ታሪካዊ ስኬት የተሰማኝን ደስታ እገልጻለሁ።
የእርሳቸው አመራር በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎችን ከድህነት ያወጣ፣ የዲጂታል ሕዝባዊ መሰረተ ልማትን በከፍተኛ ደረጃ ያስፋፋ እና ከዚህ ቀደም ታይቶ የማይታወቅ የመሰረተ ልማት እድገትን በማምጣት ፈጣን የኢኮኖሚ መነቃቃትን ያስገኘ ነው። በተጨማሪም በተከታታይነት ለደቡቡ የዓለም ክፍል (Global South) ጠንካራ ድምጽ በመሆን አገልግለዋል።"
#pmabiyahmed #ethiopia #india #diplomacy #leadership #globalsouth #ethiopianbroadcastingcorporation
****************
"ታላቅ ወንድሜ እና ውድ ወዳጄ ክቡር ናሬንድራ ሞዲ፣ የዓለማችንን ትልቁን እና እጅግ ንቁ የሆነውን የዲሞክራሲ ማህበረሰብ ዘላቂ እምነት በማግኘት፣ ህንድን በራዕይ እና በቁርጠኝነት በተከታታይ ሶስት የዲሞክራሲያዊ የስልጣን ዘመናት በመምራት ላስመዘገቡት ታሪካዊ ስኬት የተሰማኝን ደስታ እገልጻለሁ።
የእርሳቸው አመራር በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎችን ከድህነት ያወጣ፣ የዲጂታል ሕዝባዊ መሰረተ ልማትን በከፍተኛ ደረጃ ያስፋፋ እና ከዚህ ቀደም ታይቶ የማይታወቅ የመሰረተ ልማት እድገትን በማምጣት ፈጣን የኢኮኖሚ መነቃቃትን ያስገኘ ነው። በተጨማሪም በተከታታይነት ለደቡቡ የዓለም ክፍል (Global South) ጠንካራ ድምጽ በመሆን አገልግለዋል።"
#pmabiyahmed #ethiopia #india #diplomacy #leadership #globalsouth #ethiopianbroadcastingcorporation
2 months ago
የኢትዮጵያ ስልታዊ ዲፕሎማሲ፦ ከውስጥ ጽናት እስከ ዓለም አቀፍ ከፍታ
********************
(የዕለቱ መልእክት)
ዲፕሎማሲ በዓለም አቀፍ መድረክ የሀገር ብሔራዊ ጥቅም፣ ሉዓላዊነት እና ክብር ሳያስደፍሩ የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚቀመር ረቂቅ የፖለቲካ ጥበብ ነው።
ዓለም በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ወታደራዊ ሽኩቻዎች በታመሰችበት በዚህ ዘመን የውጭ ግንኙነት መርሆዎችን እንደየአካባቢያዊና ዓለም አቀፋዊ ተለዋዋጭ ሁኔታዎች እያስተካከሉ ጥቅምን ማስከበር የህልውና ጉዳይ ነው።
ባለፉት ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ምኅዳር ያጋጠሙትን ፈተናዎች የተሻገረው በዘፈቀደ ሳይሆን፣ "የውስጥ ጥንካሬ ለውጭ ዲፕሎማሲ ስኬት መሠረት ነው" የሚል ጽኑ እምነትን ሰንቆ ስልታዊና ጥልቀት ባለው የሪፎርም መነጽር በመመራቱ ነው።
በዚህም የተመዘገቡት ዘርፈ ብዙ ስኬቶች ኢትዮጵያ ካጋጠሟት ፈተናዎች አንጻር ሲመዘኑ እጅግ አስደማሚ ናቸው። እነዚህ ድሎች ሊመዘገቡ የቻሉት ቀደም ሲል የነበረውን በጥቂት ሀገራት ላይ ብቻ ያተኮረ የውጭ ፖሊሲ በመለወጥ፣ በአዲስ መልክ የተቀረጸ ገቢራዊ የሆነ የብዝኃነት ፖሊሲን በተግባር በመተርጎም ነው።
ኢትዮጵያ በምሥራቅ (እንደ ቻይና እና ሩሲያ) እና በምዕራብ (እንደ አሜሪካ እና የአውሮፓ ኅብረት) ኃይሎች መካከል በአንዱ ወገን ብቻ ሳትጠለል፣ ከሁሉም ጋር ያላትን ግንኙነት በማመጣጠን ብሔራዊ ጥቅሟን የማስከበር ስልታዊ ሚዛኗን ጠብቃለች። ይህንን ፖሊሲ ተከትሎ በተደረገ ከፍተኛ ጥረትም የስትራቴጂካዊ አማራጭ ስኬት የሆነውና በአንድ ወገን ፖለቲካዊ ጫና ውስጥ እንዳትወድቅ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ዋስትና የሚሰጣት የብሪክስ ሙሉ አባል መሆን ተችሏል።
ከተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጋር የተሠራው ስኬታማ የሚዲያ ሥራና ሕዝባዊ ንቅናቄም የሀገርን ገጽታ በአዎንታዊ መልኩ ከመገንባቱ ባለፈ፣ የሕዝብ ዲፕሎማሲ (Citizen Diplomacy) ምን ያህል አቅም እንዳለው ያሳየ ክስተት ሆኗል።
የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ጦርነትን የመከላከያ ጋሻ፣ ሰላምን የማስፈኛ ድልድይ እና የኢኮኖሚ ዕድገትን የማፋጠኛ ሞተር ሆኖ ያገለገለው በተለይ ከብሔራዊ ጥቅምና ሉዓላዊነት ጋር በተያያዙ ትልልቅ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ነው። ለአብነትም ታላቁን የሕዳሴ ግድብ በስኬት ማጠናቀቅ የዲፕሎማሲያችን ትልቅ ድል ነው።
የዚህ አዲስ የዲፕሎማሲ ምዕራፍ ሌላኛው አንጸባራቂ ስኬት፣ ኢትዮጵያ በቅርቡ ያካሄደችው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ ያገኘው ዕውቅና እና አክብሮት ነው። ምርጫው በዲፕሎማሲያዊ መድረክ የኢትዮጵያን የውስጥ ዴሞክራሲያዊ ብስለትና የፖለቲካ መረጋጋት በተግባር ያስመሰከረ ታላቅ ሁነት ሆኗል።
ምርጫው በሰላማዊና ሥልጣኔ በተሞላበት መንገድ መጠናቀቁ፣ ዓለም አቀፍ ተቋማትና አጋር ሀገራት ለኢትዮጵያ የውስጥ ጥንካሬና ሉዓላዊ ምርጫ ያላቸውን አመለካከት በአዎንታዊ መልኩ እንዲቀይሩ አስገድዷቸዋል። ይህም የሀገራችንን የዲፕሎማሲ የሞራል የበላይነት ከፍ ከማድረጉም በላይ፣ የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብና ለኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው ስኬት አስተማማኝ መሠረት ጥሏል።
ለጎረቤት ሀገራት ቅድሚያ የመስጠት ፖሊሲ እና የባሕር በር ለማግኘት የተጀመሩት ስትራቴጂካዊ ጥረቶችም ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ያላትን የመሪነት ሚና ይበልጥ አድምቀውታል።
ይሁንና የወደፊቱ የዲፕሎማሲ ስኬታችን ቀጣይነት እንዲኖረው የውጭ ፖሊሲያችን ይበልጥ በብሔራዊ ጥቅም ላይ ያተኮረ፣ በዕውቀት የሚመራ እና ጠንካራ የውስጥ ሰላምን መሠረት ያደረገ መሆን ይኖርበታል። የተጀመረውን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ ይህ በጽናትና በብልሃት የተገኘው የዲፕሎማሲ ስኬት ሁልጊዜም የንቃትና የጥንካሬ መገለጫችን ሆኖ ሊቀጥል ይገባል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል መልእክት
Ethiopian Broadcasting Corporation #diplomacy #ethiopia #ኢትዮጵያ
********************
(የዕለቱ መልእክት)
ዲፕሎማሲ በዓለም አቀፍ መድረክ የሀገር ብሔራዊ ጥቅም፣ ሉዓላዊነት እና ክብር ሳያስደፍሩ የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚቀመር ረቂቅ የፖለቲካ ጥበብ ነው።
ዓለም በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ወታደራዊ ሽኩቻዎች በታመሰችበት በዚህ ዘመን የውጭ ግንኙነት መርሆዎችን እንደየአካባቢያዊና ዓለም አቀፋዊ ተለዋዋጭ ሁኔታዎች እያስተካከሉ ጥቅምን ማስከበር የህልውና ጉዳይ ነው።
ባለፉት ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ምኅዳር ያጋጠሙትን ፈተናዎች የተሻገረው በዘፈቀደ ሳይሆን፣ "የውስጥ ጥንካሬ ለውጭ ዲፕሎማሲ ስኬት መሠረት ነው" የሚል ጽኑ እምነትን ሰንቆ ስልታዊና ጥልቀት ባለው የሪፎርም መነጽር በመመራቱ ነው።
በዚህም የተመዘገቡት ዘርፈ ብዙ ስኬቶች ኢትዮጵያ ካጋጠሟት ፈተናዎች አንጻር ሲመዘኑ እጅግ አስደማሚ ናቸው። እነዚህ ድሎች ሊመዘገቡ የቻሉት ቀደም ሲል የነበረውን በጥቂት ሀገራት ላይ ብቻ ያተኮረ የውጭ ፖሊሲ በመለወጥ፣ በአዲስ መልክ የተቀረጸ ገቢራዊ የሆነ የብዝኃነት ፖሊሲን በተግባር በመተርጎም ነው።
ኢትዮጵያ በምሥራቅ (እንደ ቻይና እና ሩሲያ) እና በምዕራብ (እንደ አሜሪካ እና የአውሮፓ ኅብረት) ኃይሎች መካከል በአንዱ ወገን ብቻ ሳትጠለል፣ ከሁሉም ጋር ያላትን ግንኙነት በማመጣጠን ብሔራዊ ጥቅሟን የማስከበር ስልታዊ ሚዛኗን ጠብቃለች። ይህንን ፖሊሲ ተከትሎ በተደረገ ከፍተኛ ጥረትም የስትራቴጂካዊ አማራጭ ስኬት የሆነውና በአንድ ወገን ፖለቲካዊ ጫና ውስጥ እንዳትወድቅ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ዋስትና የሚሰጣት የብሪክስ ሙሉ አባል መሆን ተችሏል።
ከተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጋር የተሠራው ስኬታማ የሚዲያ ሥራና ሕዝባዊ ንቅናቄም የሀገርን ገጽታ በአዎንታዊ መልኩ ከመገንባቱ ባለፈ፣ የሕዝብ ዲፕሎማሲ (Citizen Diplomacy) ምን ያህል አቅም እንዳለው ያሳየ ክስተት ሆኗል።
የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ጦርነትን የመከላከያ ጋሻ፣ ሰላምን የማስፈኛ ድልድይ እና የኢኮኖሚ ዕድገትን የማፋጠኛ ሞተር ሆኖ ያገለገለው በተለይ ከብሔራዊ ጥቅምና ሉዓላዊነት ጋር በተያያዙ ትልልቅ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ነው። ለአብነትም ታላቁን የሕዳሴ ግድብ በስኬት ማጠናቀቅ የዲፕሎማሲያችን ትልቅ ድል ነው።
የዚህ አዲስ የዲፕሎማሲ ምዕራፍ ሌላኛው አንጸባራቂ ስኬት፣ ኢትዮጵያ በቅርቡ ያካሄደችው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ ያገኘው ዕውቅና እና አክብሮት ነው። ምርጫው በዲፕሎማሲያዊ መድረክ የኢትዮጵያን የውስጥ ዴሞክራሲያዊ ብስለትና የፖለቲካ መረጋጋት በተግባር ያስመሰከረ ታላቅ ሁነት ሆኗል።
ምርጫው በሰላማዊና ሥልጣኔ በተሞላበት መንገድ መጠናቀቁ፣ ዓለም አቀፍ ተቋማትና አጋር ሀገራት ለኢትዮጵያ የውስጥ ጥንካሬና ሉዓላዊ ምርጫ ያላቸውን አመለካከት በአዎንታዊ መልኩ እንዲቀይሩ አስገድዷቸዋል። ይህም የሀገራችንን የዲፕሎማሲ የሞራል የበላይነት ከፍ ከማድረጉም በላይ፣ የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብና ለኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው ስኬት አስተማማኝ መሠረት ጥሏል።
ለጎረቤት ሀገራት ቅድሚያ የመስጠት ፖሊሲ እና የባሕር በር ለማግኘት የተጀመሩት ስትራቴጂካዊ ጥረቶችም ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ያላትን የመሪነት ሚና ይበልጥ አድምቀውታል።
ይሁንና የወደፊቱ የዲፕሎማሲ ስኬታችን ቀጣይነት እንዲኖረው የውጭ ፖሊሲያችን ይበልጥ በብሔራዊ ጥቅም ላይ ያተኮረ፣ በዕውቀት የሚመራ እና ጠንካራ የውስጥ ሰላምን መሠረት ያደረገ መሆን ይኖርበታል። የተጀመረውን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ ይህ በጽናትና በብልሃት የተገኘው የዲፕሎማሲ ስኬት ሁልጊዜም የንቃትና የጥንካሬ መገለጫችን ሆኖ ሊቀጥል ይገባል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል መልእክት
Ethiopian Broadcasting Corporation #diplomacy #ethiopia #ኢትዮጵያ
Sponsored by
Surafel
2 months ago
አምባሳደር ስለሺ ኡመር የዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲና የወጣቶች አመራር የክብር ሽልማት ተበረከተላቸው
#ethiopia | የሴፍ ላይት ኢኒሼቲቭስ (Safe Light Initiatives) መስራችና ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ስለሺ ኡመር፣ በ«ግሎባል ኤክሰለንስ ኤንድ ሊደርሺፕ አዋርድስ አፍሪካ 2026» (Global Excellence & Leadership Awards Africa 2026) ላይ የ«ቪዥነሪ ሊደር ኢን ግሎባል ዲፕሎማሲ ኤንድ ዩዝ ሊደርሺፕ» (Visionary Leader in Global Diplomacy and Youth Leadership Award) ሽልማት ተሸላሚ ሆነዋል።
በኢንሳይት ሰክሰስ (Insight Success) አዘጋጅነትና በኢንሳይት ኤክሰለንስ አዋርድስ (Insight Excellence Awards) አጋርነት የተበረከተው ይህ ታዋቂ ሽልማት፣ አምባሳደር ስለሺ ወጣቶችን በማብቃት፣ የአመራር ብቃትን በማሳደግ እና ትርጉም ያለው ማህበራዊ ለውጥ በማምጣት ረገድ ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋፅኦ የተሰጠ እውቅና ነው።
ይህ ታላቅ ስኬት በቀጣይነትም ለቀጣዩ ትውልድ መነሳሳትን በመፍጠር ማህበረሰባዊ እድገትን እንደሚያፋጥን ታምኖበታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#safelightinitiatives #globalexcellenceawards2026 #youthleadership #globaldiplomacy #visionaryleader #empoweringyouth #africaleaders
#ethiopia | የሴፍ ላይት ኢኒሼቲቭስ (Safe Light Initiatives) መስራችና ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ስለሺ ኡመር፣ በ«ግሎባል ኤክሰለንስ ኤንድ ሊደርሺፕ አዋርድስ አፍሪካ 2026» (Global Excellence & Leadership Awards Africa 2026) ላይ የ«ቪዥነሪ ሊደር ኢን ግሎባል ዲፕሎማሲ ኤንድ ዩዝ ሊደርሺፕ» (Visionary Leader in Global Diplomacy and Youth Leadership Award) ሽልማት ተሸላሚ ሆነዋል።
በኢንሳይት ሰክሰስ (Insight Success) አዘጋጅነትና በኢንሳይት ኤክሰለንስ አዋርድስ (Insight Excellence Awards) አጋርነት የተበረከተው ይህ ታዋቂ ሽልማት፣ አምባሳደር ስለሺ ወጣቶችን በማብቃት፣ የአመራር ብቃትን በማሳደግ እና ትርጉም ያለው ማህበራዊ ለውጥ በማምጣት ረገድ ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋፅኦ የተሰጠ እውቅና ነው።
ይህ ታላቅ ስኬት በቀጣይነትም ለቀጣዩ ትውልድ መነሳሳትን በመፍጠር ማህበረሰባዊ እድገትን እንደሚያፋጥን ታምኖበታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#safelightinitiatives #globalexcellenceawards2026 #youthleadership #globaldiplomacy #visionaryleader #empoweringyouth #africaleaders
2 months ago
"ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከእኔ ጋር ፊት ለፊት ይወያዩ" - ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ
"ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ ፑቲንን ማግኘት ከፈለጉ ወደ ሞስኮ ሊመጡ ይችላሉ" - ክሬምሊን
******************
በሩሲያ እና ዩክሬን መካከል እየተካሄደ ያለውን ጦርነት ሊያስቆም ይችላል የተባለ አዲስ የዲፕሎማሲ ሐሳብ ከወደ ኪዬቭ ተሰምቷል።
የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ የፊት ለፊት ውይይት ለማድረግ ለሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ቀን እንዲቆርጡ ጠይቀዋል።
ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ለሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በላኩት ደብዳቤ፤ "ቀን አስቀምጥ እና ፊት ለፊት እንገናኝ" ያሉ ሲሆን፣ በገለልተኛ ሀገር ውስጥ ቀጥታ የፊት ለፊት ውይይት ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውንም አስታውቀዋል።
በተጨማሪም በውይይቱ ላይ አሜሪካ እና የአውሮፓ ሀገራት እንዲገኙ እንደሚፈልጉ በደብዳቤያቸው ጠቅሰዋል።
የክሬምሊን ቃል አቀባይ ድሚትሪ ፔስኮቭ የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት የላኩት ደብዳቤ እንደደረሳቸው ያረጋገጡ ሲሆን፣ "ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ ፑቲንን ማግኘት ከፈለጉ ወደ ሞስኮ ሊመጡ ይችላሉ" ብለዋል።
በዚህ ሰዓት የዓለም ትኩረት ያረፈው በአንድ ጥያቄ ላይ ነው፤ ፕሬዚዳንት ፑቲን የዩክሬኑ አቻቸው ያቀረቡላቸውን ጥሪ ይቀበሉ ይሆን? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ሆኗል።
በቢታኒያ ሲሳይ
#ebc #ukraine #russia #zelensky #putin #peacetalks #diplomacy
"ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ ፑቲንን ማግኘት ከፈለጉ ወደ ሞስኮ ሊመጡ ይችላሉ" - ክሬምሊን
******************
በሩሲያ እና ዩክሬን መካከል እየተካሄደ ያለውን ጦርነት ሊያስቆም ይችላል የተባለ አዲስ የዲፕሎማሲ ሐሳብ ከወደ ኪዬቭ ተሰምቷል።
የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ የፊት ለፊት ውይይት ለማድረግ ለሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ቀን እንዲቆርጡ ጠይቀዋል።
ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ለሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በላኩት ደብዳቤ፤ "ቀን አስቀምጥ እና ፊት ለፊት እንገናኝ" ያሉ ሲሆን፣ በገለልተኛ ሀገር ውስጥ ቀጥታ የፊት ለፊት ውይይት ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውንም አስታውቀዋል።
በተጨማሪም በውይይቱ ላይ አሜሪካ እና የአውሮፓ ሀገራት እንዲገኙ እንደሚፈልጉ በደብዳቤያቸው ጠቅሰዋል።
የክሬምሊን ቃል አቀባይ ድሚትሪ ፔስኮቭ የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት የላኩት ደብዳቤ እንደደረሳቸው ያረጋገጡ ሲሆን፣ "ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ ፑቲንን ማግኘት ከፈለጉ ወደ ሞስኮ ሊመጡ ይችላሉ" ብለዋል።
በዚህ ሰዓት የዓለም ትኩረት ያረፈው በአንድ ጥያቄ ላይ ነው፤ ፕሬዚዳንት ፑቲን የዩክሬኑ አቻቸው ያቀረቡላቸውን ጥሪ ይቀበሉ ይሆን? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ሆኗል።
በቢታኒያ ሲሳይ
#ebc #ukraine #russia #zelensky #putin #peacetalks #diplomacy
3 months ago
ቻይና ካሁን በኋላ “ታዳጊ ሀገር'' አትበሉኝ አለች
#ethiopia | በዓለም አቀፍ የንግድና የዲፕሎማሲ መድረክ ላይ ለዓመታት የነበረውን ሚዛን ሙሉ በሙሉ የሚቀይር ታላቅ መግለጫ ከቤጂንግ ተሰምቷል።
ቻይና ከአሁን በኋላ በዓለም አቀፍ ድርድሮች ላይ “ታዳጊ ሀገር” በመሆኗ ብቻ የምታገኛቸውን ልዩ ጥቅማጥቅሞች፣ ተጨማሪ የጊዜ ሰሌዳዎችን እና ቀለል ያሉ የንግድ ግዴታዎችን እንደማትፈልግ በይፋ አስታውቃለች።
ይህ ውሳኔ ለበርካታ ዓመታት ቻይና በአንድ ላይ ይዛቸው የኖረችውን ሁለት ተቃራኒ ማንነቶች—በአንድ በኩል የዓለማችን ግዙፍ የኢንዱስትሪ ማዕከል የመሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ በህጋዊ ሰነዶች ላይ “ታዳጊ ሀገር” ተብሎ የመመዝገብ ታሪክ—የሚያበቃላት ይመስላል።
የቻይና ጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ኪያንግ እንደገለጹት፣ ሀገሪቱ በዓለም የንግድ ድርጅት (WTO) ድርድሮች ላይ የሚሰጠውን “ልዩና የተለየ መብት” (SDT) በገዛ ፈቃዷ ለመተው ወስናለች።
ይህ እርምጃ ቀላል የቴክኒክ ፖሊሲ ለውጥ ሳይሆን፣ ምዕራባውያን ቻይና በታዳጊ ሀገር ስም ተሸሽጋ የራሷን ገበያ ትጠብቃለች በማለት ለአሜሪካና ለአውሮፓ ህብረት ለሚያቀርቡባት ትችት ሙሉ በሙሉ ምላሽ የሰጠ ታላቅ ስልት ነው።
በሌላ በኩል ቻይና ጥቅማጥቅሙን ብትተወውም “የታዳጊ ሀገርነት” ስሟንና ክበቡን ግን በፍፁም የማትለቅ ሲሆን፣ ይህም ከአፍሪካና ከሌሎች በማደግ ላይ ካሉ ሀገራት ጋር ያላትን ወዳጅነት ለማጠናከርና የ“ግሎባል ሳውዝ” (Global South) ህብረት መሪ ሆና ለመቀጠል ያስችላታል።
የዘርፉ ባለሙያዎች እንደሚናገሩት ቻይና በተግባር ብዙም የማትጠቀምበትን ህጋዊ መብት በመተው፣ በምትኩ እጅግ ግዙፍ የሆነ የዲፕሎማሲና የፖለቲካ የበላይነት መግዛት የቻለችበት እውነተኛ የማስተር ክላስ ስልት ተብሎ ሊጠቀስ የሚችል ታሪካዊ ክስተት ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #menahriafm #china #globaltrade #wto #geopolitics #globalsouth #chinaeconomy #internationalrelations #diplomacy
#ethiopia | በዓለም አቀፍ የንግድና የዲፕሎማሲ መድረክ ላይ ለዓመታት የነበረውን ሚዛን ሙሉ በሙሉ የሚቀይር ታላቅ መግለጫ ከቤጂንግ ተሰምቷል።
ቻይና ከአሁን በኋላ በዓለም አቀፍ ድርድሮች ላይ “ታዳጊ ሀገር” በመሆኗ ብቻ የምታገኛቸውን ልዩ ጥቅማጥቅሞች፣ ተጨማሪ የጊዜ ሰሌዳዎችን እና ቀለል ያሉ የንግድ ግዴታዎችን እንደማትፈልግ በይፋ አስታውቃለች።
ይህ ውሳኔ ለበርካታ ዓመታት ቻይና በአንድ ላይ ይዛቸው የኖረችውን ሁለት ተቃራኒ ማንነቶች—በአንድ በኩል የዓለማችን ግዙፍ የኢንዱስትሪ ማዕከል የመሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ በህጋዊ ሰነዶች ላይ “ታዳጊ ሀገር” ተብሎ የመመዝገብ ታሪክ—የሚያበቃላት ይመስላል።
የቻይና ጠቅላይ ሚኒስትር ሊ ኪያንግ እንደገለጹት፣ ሀገሪቱ በዓለም የንግድ ድርጅት (WTO) ድርድሮች ላይ የሚሰጠውን “ልዩና የተለየ መብት” (SDT) በገዛ ፈቃዷ ለመተው ወስናለች።
ይህ እርምጃ ቀላል የቴክኒክ ፖሊሲ ለውጥ ሳይሆን፣ ምዕራባውያን ቻይና በታዳጊ ሀገር ስም ተሸሽጋ የራሷን ገበያ ትጠብቃለች በማለት ለአሜሪካና ለአውሮፓ ህብረት ለሚያቀርቡባት ትችት ሙሉ በሙሉ ምላሽ የሰጠ ታላቅ ስልት ነው።
በሌላ በኩል ቻይና ጥቅማጥቅሙን ብትተወውም “የታዳጊ ሀገርነት” ስሟንና ክበቡን ግን በፍፁም የማትለቅ ሲሆን፣ ይህም ከአፍሪካና ከሌሎች በማደግ ላይ ካሉ ሀገራት ጋር ያላትን ወዳጅነት ለማጠናከርና የ“ግሎባል ሳውዝ” (Global South) ህብረት መሪ ሆና ለመቀጠል ያስችላታል።
የዘርፉ ባለሙያዎች እንደሚናገሩት ቻይና በተግባር ብዙም የማትጠቀምበትን ህጋዊ መብት በመተው፣ በምትኩ እጅግ ግዙፍ የሆነ የዲፕሎማሲና የፖለቲካ የበላይነት መግዛት የቻለችበት እውነተኛ የማስተር ክላስ ስልት ተብሎ ሊጠቀስ የሚችል ታሪካዊ ክስተት ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #menahriafm #china #globaltrade #wto #geopolitics #globalsouth #chinaeconomy #internationalrelations #diplomacy
3 months ago
ኢትዮጵያ እንደ ዓለም ጤና ጉባኤ ያሉ አለም አቀፍ መድረኮችን በመጠቀም የጤና ዲፕሎማሲን በማጠናከር ላይ ትገኛለች - የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ
በጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የተመራዉ የኢትዮጵያ ልዑክ ቡድን በ79 ነኛዉ የዓለም ጤና ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ገብቷል።
ዶ/ር መቅደስ ለልዑካን ቡድኑ ኦሪየንቴሽን በሰጡት መድረክ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በተለይም እንደ የዓለም ጤና ጉባኤ ያሉ አለም አቀፍ መድረኮችን በመጠቀም የጤና ዲፕሎማሲን በማጠናከር ላይ ትገኛለች ብለዋል።
ኢትዮጵያ የዓለም ጤና ድርጅት አባል ሀገር እንደመሆኗ በጉባኤዉ በሚወሰኑ ዉሳኔዎችና ቀጣይ ስራዎች የራሷን ድርሻ እንደምትወጣ ዶ/ር መቅደስ ተናግረዋል።
ወቅታዊ የኢቦላና ሀንታ ቫይረስ ሁኔታን ጨምሮ ሌሎች የዓለማችን ስጋት የሆኑ ወርሽኞችን መከላከልና መቆጣጠር በዋናነት በጉባኤዉ ቀርበዉ ዉይይት እንደሚደረግበት ይጠበቃል።
ከጉኤዉ ቀደም ብለዉ የዎክ ዘ ቶክ (Walk the Talk) ፕሮግራም የተካሄደ ሲሆን 79 ነኛው የዓለም ጤና ጉባኤ ከግንቦት 10-15 /2018 ዓ.ም በስዊዘርላድ ጄኔቫ እንደሚካሄድ ከወጣዉ ፕሮግራም ማወቅ ተችሏል።
"Ethiopia is strengthening health diplomacy by using international forums such as the World Health Assembly" - Health Minister Dr. Mekdes Daba
____________
The Ethiopian delegation led by Health Minister Dr. Mekdes Daba has arrived in Geneva, Switzerland to participate in the 79th World Health Assembly.
Dr. Mekdes, during the orientation forum she gave to the delegation, stated that Ethiopia is strengthening health diplomacy particularly by using international forums such as the World Health Assembly.
Dr. Mekdes said that as Ethiopia is a member state of the World Health Organization, it will play its own role in the decisions and future works to be decided at the assembly.
Preventing and controlling other world-threatening pandemics, including the current Ebola and Hanta virus situation, is mainly expected to be presented and discussed at the assembly.
Prior to the assembly, the Walk the Talk program was held, and it was possible to know from the released program that the 79th World Health Assembly will be held from May 18-23 / 2026 in Geneva, Switzerland.
በጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የተመራዉ የኢትዮጵያ ልዑክ ቡድን በ79 ነኛዉ የዓለም ጤና ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ገብቷል።
ዶ/ር መቅደስ ለልዑካን ቡድኑ ኦሪየንቴሽን በሰጡት መድረክ እንደገለጹት ኢትዮጵያ በተለይም እንደ የዓለም ጤና ጉባኤ ያሉ አለም አቀፍ መድረኮችን በመጠቀም የጤና ዲፕሎማሲን በማጠናከር ላይ ትገኛለች ብለዋል።
ኢትዮጵያ የዓለም ጤና ድርጅት አባል ሀገር እንደመሆኗ በጉባኤዉ በሚወሰኑ ዉሳኔዎችና ቀጣይ ስራዎች የራሷን ድርሻ እንደምትወጣ ዶ/ር መቅደስ ተናግረዋል።
ወቅታዊ የኢቦላና ሀንታ ቫይረስ ሁኔታን ጨምሮ ሌሎች የዓለማችን ስጋት የሆኑ ወርሽኞችን መከላከልና መቆጣጠር በዋናነት በጉባኤዉ ቀርበዉ ዉይይት እንደሚደረግበት ይጠበቃል።
ከጉኤዉ ቀደም ብለዉ የዎክ ዘ ቶክ (Walk the Talk) ፕሮግራም የተካሄደ ሲሆን 79 ነኛው የዓለም ጤና ጉባኤ ከግንቦት 10-15 /2018 ዓ.ም በስዊዘርላድ ጄኔቫ እንደሚካሄድ ከወጣዉ ፕሮግራም ማወቅ ተችሏል።
"Ethiopia is strengthening health diplomacy by using international forums such as the World Health Assembly" - Health Minister Dr. Mekdes Daba
____________
The Ethiopian delegation led by Health Minister Dr. Mekdes Daba has arrived in Geneva, Switzerland to participate in the 79th World Health Assembly.
Dr. Mekdes, during the orientation forum she gave to the delegation, stated that Ethiopia is strengthening health diplomacy particularly by using international forums such as the World Health Assembly.
Dr. Mekdes said that as Ethiopia is a member state of the World Health Organization, it will play its own role in the decisions and future works to be decided at the assembly.
Preventing and controlling other world-threatening pandemics, including the current Ebola and Hanta virus situation, is mainly expected to be presented and discussed at the assembly.
Prior to the assembly, the Walk the Talk program was held, and it was possible to know from the released program that the 79th World Health Assembly will be held from May 18-23 / 2026 in Geneva, Switzerland.
3 months ago
የሰላም ድርድር መቋረጥ፣ የሆርሙዝ ሰርጥ አዳዲስ ክልከላዎች እና የባራካህ የኑክሌር ጣቢያ ጥቃት
**************
በመካከለኛው ምሥራቅ የሰላም ድርድር ጥረቶች፣ በሆርሙዝ ሰርጥ የባሕር ላይ መተላለፊያ ቁጥጥር እና በተመዘገቡ የጸጥታ ስጋቶች ዙሪያ አዳዲስ ክስተቶች ተመዝግበዋል።
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የነበረው ቀጥተኛ ድርድር መቋረጡን ተከትሎ ዲፕሎማሲያዊ ውጥረቱ ያሻቀበ ሲሆን፣ የንግድ መርከቦች እንቅስቃሴን ለመቆጣጠርም አዳዲስ እርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ።
የፓኪስታን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ሞህሲን ናቅቪ አስቀድሞ ያልተገለጸ የሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ቴህራን መግባታቸውን የፓኪስታኑ ‘ዶን’ ጋዜጣ ዲፕሎማቲክ ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል።
ይህ አስቸኳይ ጉብኝት የተደረገው የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራንን የቅርብ ጊዜ የሰላም አማራጭ ውድቅ ማድረጋቸውን ተከትሎ፣ የሰላም ድርድሩ ሙሉ በሙሉ እንዳይደናቀፍ ለማድረግ የተጀመረው የሽምግልና ጥረት አካል መሆኑ ተገልጿል።
የኢራኑ ‘ተስኒም’ የዜና ወኪል በበኩሉ፣ ሚኒስትሩ ከኢራን አቻቸው ኤስካንዳር ሞሜኒ እና ከፓርላማ አፈ-ጉባኤ መሐመድ ባጌር ጋሊባፍ ጋር ተገናኝተው በዋሽንግተን እና ቴህራን መካከል ያለውን የሰላም ድርድር ማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውን ጠቁሟል።
ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ እንዳስነበበው፣ ፕሬዚዳንት ትራምፕ የኢራንን የሰላም ሃሳብ ውድቅ ቢያደርጉም፤ ኢራን የኑክሌር መርሐ ግብሯን ለ20 ዓመታት እንድታግድ የሚጠይቅ አማራጭ አቅርበዋል።
ይሁን እንጂ የኢራን ባለሥልጣናት በአሜሪካ ወገን ምንም ዓይነት ተጨባጭ የዲፕሎማሲ አካሄድ ለውጥ አልታየም ሲሉ መተቸታቸውን መህር የዜና ወኪል ዘግቧል።
የሆርሙዝ ሰርጥን በተመለከተ ኢራን የባሕር ላይ መተላለፊያውን ለመቆጣጠር አዲስ “ሙያዊ የአሠራር ሥርዓት” ያለችውን የቁጥጥር ሥርዓት ይፋ እንደምታደርግ አስታውቃለች።
የኢራን ፓርላማ የብሔራዊ ደኅንነት ኮሚቴ ሰብሳቢ ኢብራሂም አዚዝን ጠቅሶ ሮይተርስ እንደዘገበው፣ አዲሱ አሠራር ከኢራን ጋር ለሚተባበሩ የንግድ መርከቦች ብቻ ቅድሚያ የሚሰጥ ሲሆን፣ የአሜሪካ ደጋፊ ለሆኑ መርከቦች ግን ዝግ ይሆናል።
በተጨማሪም ኢራን በዲጂታል እና በቢትኮይን ክፍያ የሚሠራ “ሆርሙዝ ሴፍ” የተባለ አዲስ የባሕር ላይ መድን ይፋ ማድረጓን ፋርስ የዜና ወኪል አረጋግጧል።
በሆርሙዝ ሰርጥ ያለው የባሕር ላይ ትራፊክ አሁንም እንደቀዘቀዘ መሆኑን እና አንዳንድ የአውሮፓ ሀገራት መርከቦቻቸው በሰላም እንዲያልፉ ከኢራን አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ጋር ድርድር መጀመራቸውን ብሉምበርግ ዘግቧል።
በሌላ በኩል የቀጣናውን ሰላም ይበልጥ አሳሳቢ የሚያደርግ ክስተት ተመዝግቧል። በተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች በሚገኘው የባራካህ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ የድሮን ጥቃት ደርሷል።
‘አሶሺዬትድ ፕሬስ' እንደዘገበው ጥቃቱ ከኃይል ማመንጫው የውስጠኛው አጥር ውጭ በሚገኝ የኤሌክትሪክ ጄነሬተር ላይ እሳት ቢያስነሳም፣ የኢምሬቶች ባለሥልጣናት እሳቱን በፍጥነት መቆጣጠር መቻሉን እና ምንም ዓይነት የጨረር ስጋትም ሆነ የሰው ጉዳት አለመድረሱን አረጋግጠዋል።
ዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኃይል ኤጀንሲ (IAEA) ዋና ዳይሬክተር ራፋኤል ግሮሲ ጥቃቱን “ተቀባይነት የሌለው” ሲሉ አውግዘውታል።
በመካከለኛው ምሥራቅ በአንድ በኩል ዲፕሎማሲያዊ የሰላም ጥረቶች ቢቀጥሉም፣ በሌላ በኩል እየተከሰቱ ያሉ የጸጥታ ስጋቶች ቀውሱ ወደ ከፋ ጦርነት እንዳያመራ ከፍተኛ ስጋት መፍጠራቸውን ዓለም አቀፍ የጂኦፖለቲካ ተንታኞች በማስጠንቀቅ ላይ ይገኛሉ።
በለሚ ታደሰ
#middleeastcrisis #peacetalks #straitofhormuz #diplomacy #globalenergy
**************
በመካከለኛው ምሥራቅ የሰላም ድርድር ጥረቶች፣ በሆርሙዝ ሰርጥ የባሕር ላይ መተላለፊያ ቁጥጥር እና በተመዘገቡ የጸጥታ ስጋቶች ዙሪያ አዳዲስ ክስተቶች ተመዝግበዋል።
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የነበረው ቀጥተኛ ድርድር መቋረጡን ተከትሎ ዲፕሎማሲያዊ ውጥረቱ ያሻቀበ ሲሆን፣ የንግድ መርከቦች እንቅስቃሴን ለመቆጣጠርም አዳዲስ እርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ።
የፓኪስታን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ሞህሲን ናቅቪ አስቀድሞ ያልተገለጸ የሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ቴህራን መግባታቸውን የፓኪስታኑ ‘ዶን’ ጋዜጣ ዲፕሎማቲክ ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል።
ይህ አስቸኳይ ጉብኝት የተደረገው የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራንን የቅርብ ጊዜ የሰላም አማራጭ ውድቅ ማድረጋቸውን ተከትሎ፣ የሰላም ድርድሩ ሙሉ በሙሉ እንዳይደናቀፍ ለማድረግ የተጀመረው የሽምግልና ጥረት አካል መሆኑ ተገልጿል።
የኢራኑ ‘ተስኒም’ የዜና ወኪል በበኩሉ፣ ሚኒስትሩ ከኢራን አቻቸው ኤስካንዳር ሞሜኒ እና ከፓርላማ አፈ-ጉባኤ መሐመድ ባጌር ጋሊባፍ ጋር ተገናኝተው በዋሽንግተን እና ቴህራን መካከል ያለውን የሰላም ድርድር ማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውን ጠቁሟል።
ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ እንዳስነበበው፣ ፕሬዚዳንት ትራምፕ የኢራንን የሰላም ሃሳብ ውድቅ ቢያደርጉም፤ ኢራን የኑክሌር መርሐ ግብሯን ለ20 ዓመታት እንድታግድ የሚጠይቅ አማራጭ አቅርበዋል።
ይሁን እንጂ የኢራን ባለሥልጣናት በአሜሪካ ወገን ምንም ዓይነት ተጨባጭ የዲፕሎማሲ አካሄድ ለውጥ አልታየም ሲሉ መተቸታቸውን መህር የዜና ወኪል ዘግቧል።
የሆርሙዝ ሰርጥን በተመለከተ ኢራን የባሕር ላይ መተላለፊያውን ለመቆጣጠር አዲስ “ሙያዊ የአሠራር ሥርዓት” ያለችውን የቁጥጥር ሥርዓት ይፋ እንደምታደርግ አስታውቃለች።
የኢራን ፓርላማ የብሔራዊ ደኅንነት ኮሚቴ ሰብሳቢ ኢብራሂም አዚዝን ጠቅሶ ሮይተርስ እንደዘገበው፣ አዲሱ አሠራር ከኢራን ጋር ለሚተባበሩ የንግድ መርከቦች ብቻ ቅድሚያ የሚሰጥ ሲሆን፣ የአሜሪካ ደጋፊ ለሆኑ መርከቦች ግን ዝግ ይሆናል።
በተጨማሪም ኢራን በዲጂታል እና በቢትኮይን ክፍያ የሚሠራ “ሆርሙዝ ሴፍ” የተባለ አዲስ የባሕር ላይ መድን ይፋ ማድረጓን ፋርስ የዜና ወኪል አረጋግጧል።
በሆርሙዝ ሰርጥ ያለው የባሕር ላይ ትራፊክ አሁንም እንደቀዘቀዘ መሆኑን እና አንዳንድ የአውሮፓ ሀገራት መርከቦቻቸው በሰላም እንዲያልፉ ከኢራን አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ጋር ድርድር መጀመራቸውን ብሉምበርግ ዘግቧል።
በሌላ በኩል የቀጣናውን ሰላም ይበልጥ አሳሳቢ የሚያደርግ ክስተት ተመዝግቧል። በተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች በሚገኘው የባራካህ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ የድሮን ጥቃት ደርሷል።
‘አሶሺዬትድ ፕሬስ' እንደዘገበው ጥቃቱ ከኃይል ማመንጫው የውስጠኛው አጥር ውጭ በሚገኝ የኤሌክትሪክ ጄነሬተር ላይ እሳት ቢያስነሳም፣ የኢምሬቶች ባለሥልጣናት እሳቱን በፍጥነት መቆጣጠር መቻሉን እና ምንም ዓይነት የጨረር ስጋትም ሆነ የሰው ጉዳት አለመድረሱን አረጋግጠዋል።
ዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኃይል ኤጀንሲ (IAEA) ዋና ዳይሬክተር ራፋኤል ግሮሲ ጥቃቱን “ተቀባይነት የሌለው” ሲሉ አውግዘውታል።
በመካከለኛው ምሥራቅ በአንድ በኩል ዲፕሎማሲያዊ የሰላም ጥረቶች ቢቀጥሉም፣ በሌላ በኩል እየተከሰቱ ያሉ የጸጥታ ስጋቶች ቀውሱ ወደ ከፋ ጦርነት እንዳያመራ ከፍተኛ ስጋት መፍጠራቸውን ዓለም አቀፍ የጂኦፖለቲካ ተንታኞች በማስጠንቀቅ ላይ ይገኛሉ።
በለሚ ታደሰ
#middleeastcrisis #peacetalks #straitofhormuz #diplomacy #globalenergy
Sponsored by
Surafel
3 months ago
ኢትዮጵያ፦ የዓለም ሰላም ተሟጋች እና የፍትህ ፋና ወጊ
******************
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የተመሠረተበትን 80ኛ ዓመት ስናስብ ኢትዮጵያ ለዓለም ሰላምና ለፍትህ የከፈለችውን መተኪያ የሌለው መስዋዕትነት ማስታወስ ግድ ይላል።
ኢትዮጵያ ዓለም በጋራ ጉዳዮች ላይ ተሰባስቦ እንዲመክር ካላት ጽኑ አቋም የተነሳ እ.አ.አ በ1923 የመንግሥታቱ ማኅበር አባል ብትሆንም፣ ማኅበሩ ግን ከፋሺስት የመርዝ ጋዝ ጥቃት ሊጠብቃት አልቻለም።
ሀገራችን እ.አ.አ በ1936 በመንግሥታቱ ማኅበር ፊት ቀርባ "ዛሬ በእኛ ላይ የደረሰው ነገ በእናንተ ላይ ይደርሳል" በማለት ያሰማችው ትንቢታዊ ማስጠንቀቂያ በዓለም የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ የፍትህ ተሟጋችነታችን ቀዳሚ ማሳያ ነው።
ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ሲያበቃም ኢትዮጵያ ከ51 የተመድ መሥራች ሀገራት አንዷ በመሆን የሀገራትን ሉዓላዊ እኩልነት የሚያረጋግጡ ድንጋጌዎች በቻርተሩ እንዲካተቱ ታሪካዊ ሚና ተጫውታለች።
ከቃላት ባለፈም በአፍሪካና በተለያዩ ሀገራት ለሚገኙ የነጻነት ታጋዮች መጠጊያና ደጋፊ በመሆን ለጥቁር ሕዝብ ኩራት ሆና ቆይታለች።
በሰላም ጥበቃ ረገድም ከኮሪያ ጦርነት ጀምሮ እስካሁን ከ100 ሺህ በላይ ወታደራዊና የፖሊስ አባላትን በማሰማራት የዓለምን ሰላም በመስዋዕትነት ስታስጠብቅ ኖራለች።
ዛሬም ኢትዮጵያ በተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ውስጥ አፍሪካ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና ሊኖራት ይገባል የሚለውን ጥያቄ በግንባር ቀደምነት በማንሳት ላይ ትገኛለች።
ይህ የዘመናት የፍትህ ተሟጋችነቷ ጉዞ የሰው ልጆች ሁሉ ድምጽ በእኩልነት እንዲሰማ ካላት ጽኑ ራዕይ የሚመነጭ ነው።
በለሚ ታደሰ
ዝርዝር ትንታኔውን በአስተያየት መስጫው ካጋራነው ሊንክ ያገኙታል 🔗
#ethiopian #diplomacy #un80 #globaljustice #peacekeeping #unitedafrica
******************
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የተመሠረተበትን 80ኛ ዓመት ስናስብ ኢትዮጵያ ለዓለም ሰላምና ለፍትህ የከፈለችውን መተኪያ የሌለው መስዋዕትነት ማስታወስ ግድ ይላል።
ኢትዮጵያ ዓለም በጋራ ጉዳዮች ላይ ተሰባስቦ እንዲመክር ካላት ጽኑ አቋም የተነሳ እ.አ.አ በ1923 የመንግሥታቱ ማኅበር አባል ብትሆንም፣ ማኅበሩ ግን ከፋሺስት የመርዝ ጋዝ ጥቃት ሊጠብቃት አልቻለም።
ሀገራችን እ.አ.አ በ1936 በመንግሥታቱ ማኅበር ፊት ቀርባ "ዛሬ በእኛ ላይ የደረሰው ነገ በእናንተ ላይ ይደርሳል" በማለት ያሰማችው ትንቢታዊ ማስጠንቀቂያ በዓለም የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ የፍትህ ተሟጋችነታችን ቀዳሚ ማሳያ ነው።
ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ሲያበቃም ኢትዮጵያ ከ51 የተመድ መሥራች ሀገራት አንዷ በመሆን የሀገራትን ሉዓላዊ እኩልነት የሚያረጋግጡ ድንጋጌዎች በቻርተሩ እንዲካተቱ ታሪካዊ ሚና ተጫውታለች።
ከቃላት ባለፈም በአፍሪካና በተለያዩ ሀገራት ለሚገኙ የነጻነት ታጋዮች መጠጊያና ደጋፊ በመሆን ለጥቁር ሕዝብ ኩራት ሆና ቆይታለች።
በሰላም ጥበቃ ረገድም ከኮሪያ ጦርነት ጀምሮ እስካሁን ከ100 ሺህ በላይ ወታደራዊና የፖሊስ አባላትን በማሰማራት የዓለምን ሰላም በመስዋዕትነት ስታስጠብቅ ኖራለች።
ዛሬም ኢትዮጵያ በተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ውስጥ አፍሪካ ቋሚ መቀመጫና ፍትሃዊ ውክልና ሊኖራት ይገባል የሚለውን ጥያቄ በግንባር ቀደምነት በማንሳት ላይ ትገኛለች።
ይህ የዘመናት የፍትህ ተሟጋችነቷ ጉዞ የሰው ልጆች ሁሉ ድምጽ በእኩልነት እንዲሰማ ካላት ጽኑ ራዕይ የሚመነጭ ነው።
በለሚ ታደሰ
ዝርዝር ትንታኔውን በአስተያየት መስጫው ካጋራነው ሊንክ ያገኙታል 🔗
#ethiopian #diplomacy #un80 #globaljustice #peacekeeping #unitedafrica
3 months ago
ቻይና እና አሜሪካ የሆርሙዝ የባሕር ሰርጥ ክፍት ሆኖ እንዲቆይ ተስማሙ
**********************
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ በቤጂንግ ባደረጉት የፊት ለፊት ውይይት በሆርሙዝ የባሕር ሰርጥ ዙሪያ መክረዋል።
በውይይታቸውም በኢራን ጦርነት ሳቢያ በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ ያለው ውጥረት በበረታበት በዚህ ወቅት፣ ስትራቴጂያዊው የሆርሙዝ ባሕር ሰርጥ “ነፃ የኃይል አቅርቦት ፍሰትን ለመደገፍ ሲባል የግድ ክፍት ሆኖ መቆየት አለበት” በሚለው ነጥብ ላይ ፕሬዚዳንት ሺ መስማማታቸውን ኋይት ሐውስ አስታውቋል።
በሌላ በኩል፣ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቅቺ በኒው ዴልሂ፣ በተካሄደው ስብሰባ ላይ የብሪክስ (BRICS) አባል ሀገራት አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የከፈቱትን ጦርነት እንዲያወግዙት አሳስበዋል።
ሚኒስትሩ “ቴህራን ለማንኛውም ዓይነት ውጫዊ ጫና በፍጹም እጅ እንደማትሰጥ” በአፅንኦት መናገራቸውን አልጀዚራ ዘግቧል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በደቡብ ሊባኖስ ከተሞች እና መንደሮች ላይ የእስራኤል ጥቃቶች አሁንም የቀጠሉ ቢሆንም፣ ግጭቱን በዘላቂነት ለማስቆም ያለመ የሊባኖስ እና የእስራኤል ተደራዳሪዎች ሦስተኛ ዙር የቀጥታ ውይይት በዋሽንግተን ዲሲ በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።
#globalnews #usa #china #iran #hormuzstrait #brics #diplomacy
**********************
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ በቤጂንግ ባደረጉት የፊት ለፊት ውይይት በሆርሙዝ የባሕር ሰርጥ ዙሪያ መክረዋል።
በውይይታቸውም በኢራን ጦርነት ሳቢያ በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ ያለው ውጥረት በበረታበት በዚህ ወቅት፣ ስትራቴጂያዊው የሆርሙዝ ባሕር ሰርጥ “ነፃ የኃይል አቅርቦት ፍሰትን ለመደገፍ ሲባል የግድ ክፍት ሆኖ መቆየት አለበት” በሚለው ነጥብ ላይ ፕሬዚዳንት ሺ መስማማታቸውን ኋይት ሐውስ አስታውቋል።
በሌላ በኩል፣ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቅቺ በኒው ዴልሂ፣ በተካሄደው ስብሰባ ላይ የብሪክስ (BRICS) አባል ሀገራት አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የከፈቱትን ጦርነት እንዲያወግዙት አሳስበዋል።
ሚኒስትሩ “ቴህራን ለማንኛውም ዓይነት ውጫዊ ጫና በፍጹም እጅ እንደማትሰጥ” በአፅንኦት መናገራቸውን አልጀዚራ ዘግቧል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በደቡብ ሊባኖስ ከተሞች እና መንደሮች ላይ የእስራኤል ጥቃቶች አሁንም የቀጠሉ ቢሆንም፣ ግጭቱን በዘላቂነት ለማስቆም ያለመ የሊባኖስ እና የእስራኤል ተደራዳሪዎች ሦስተኛ ዙር የቀጥታ ውይይት በዋሽንግተን ዲሲ በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።
#globalnews #usa #china #iran #hormuzstrait #brics #diplomacy
3 months ago
ከምድር ባቡር ፉጨት እስከ ዲጂታል አድማስ፦ ከአንድ ክፍለ ዘመን የተሻገረው የኢትዮ-ፈረንሳይ የማይበጠስ ወዳጅነት!
*********************
ከንጉሥ ሳህለ ሥላሴ የሸዋ ግዛት እስከ ዘመናዊቷ ኢትዮጵያ፣ ከታላቁ ገጣሚ አርተር ራምቦ የሐረር ቆይታ እስከ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የትላንትናው ታሪካዊ ጉብኝት... በቅኝ ግዛት ያልተበከለውና በእኩልነት ላይ የተመሠረተው የኢትዮጵያና የፈረንሳይ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዴት ዛሬም ድረስ እንደጸና አለ!
በዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ የሀገራት ግንኙነት እንደየዘመኑ የፖለቲካ ንፋስ መዋዠቅ እና መለዋወጥ የተለመደ ክስተት ነው።
ነገር ግን፣ ከክፍለ ዘመናት መፈራረቅ፣ ከርዕዮተ ዓለም ለውጦች እና ከዓለም አቀፍ ቀውሶች ተርፈው በጽኑ መሠረት ላይ የሚቆሙ ጥቂት የማይበጠሱ የወዳጅነት ገመዶች አሉ።
ከእነዚህ ብርቅዬ ታሪካዊ ትሥሥሮች መካከል የኢትዮጵያ እና የፈረንሳይ የሁለትዮሽ ግንኙነት በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ ነው።
ይህ ግንኙነት የተፀነሰው በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት እንደታየው በቅኝ ግዛት ጌታና ሎሌነት ሳይሆን፣ በሁለት ሉዓላዊ እና ገለልተኛ መንግስታት መካከል በነበረ ፍፁም የእኩልነት መርሕ ላይ መሆኑ ልዩ ያደርገዋል።
የዚህን መረጃ ሙሉ ሐሳብ አስተያየት መስጫው ውስጥ ካለው ሊንክ ያገኛሉ፦
#ebc #ethiopia #france #diplomacy #relations
*********************
ከንጉሥ ሳህለ ሥላሴ የሸዋ ግዛት እስከ ዘመናዊቷ ኢትዮጵያ፣ ከታላቁ ገጣሚ አርተር ራምቦ የሐረር ቆይታ እስከ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የትላንትናው ታሪካዊ ጉብኝት... በቅኝ ግዛት ያልተበከለውና በእኩልነት ላይ የተመሠረተው የኢትዮጵያና የፈረንሳይ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዴት ዛሬም ድረስ እንደጸና አለ!
በዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ ታሪክ ውስጥ የሀገራት ግንኙነት እንደየዘመኑ የፖለቲካ ንፋስ መዋዠቅ እና መለዋወጥ የተለመደ ክስተት ነው።
ነገር ግን፣ ከክፍለ ዘመናት መፈራረቅ፣ ከርዕዮተ ዓለም ለውጦች እና ከዓለም አቀፍ ቀውሶች ተርፈው በጽኑ መሠረት ላይ የሚቆሙ ጥቂት የማይበጠሱ የወዳጅነት ገመዶች አሉ።
ከእነዚህ ብርቅዬ ታሪካዊ ትሥሥሮች መካከል የኢትዮጵያ እና የፈረንሳይ የሁለትዮሽ ግንኙነት በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ ነው።
ይህ ግንኙነት የተፀነሰው በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት እንደታየው በቅኝ ግዛት ጌታና ሎሌነት ሳይሆን፣ በሁለት ሉዓላዊ እና ገለልተኛ መንግስታት መካከል በነበረ ፍፁም የእኩልነት መርሕ ላይ መሆኑ ልዩ ያደርገዋል።
የዚህን መረጃ ሙሉ ሐሳብ አስተያየት መስጫው ውስጥ ካለው ሊንክ ያገኛሉ፦
#ebc #ethiopia #france #diplomacy #relations
3 months ago
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጻፈው “የመደመር መንግሥት“ መጽሐፍ የዓረብኛ ትርጉም ተመረቀ
*************************
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጻፈው “የመደመር መንግሥት“ የአረብኛው ትርጉም በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ አቡዳቢ በዛሬው ዕለት ተመርቋል።
በአቡ ዳቢ የተመረቀው ይህ መጽሐፍ በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ ሁሉም አረብኛ ተናጋሪ ሀገራትና ሕዝቦች፣ ኢትዮጵያ በመደመር መንግሥትና ፍልስፍና እያራመደች የምትገኘውን የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የለውጥ እንቅስቃሴ ትልሞች በጥልቀት እንዲገነዘቡት ዓላማ ያደረገ ነው።
በመጽሐፍ ምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ጀማል በከር (ዶ/ር)፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጻፈው “የመደመር መንግሥት” አረብኛ ትርጉም እውን መሆን በኢትዮጵያና በተቀረው የአረቡ ዓለም በኩል ያሉ የጋራ ጥቅሞችን አስተሳስሮ ለማስቀጠልና የጋራ ጥቅሞቻችንን ለማስጠቅ እንደሚያግዝ ተናግረዋል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲኤታ ሸክ ሻክቡት ቢን ናህያን አልናህያን፣ መጽሐፉ በአረብኛ ቋንቋ ተተርጉሞ መቅረቡ በኢትዮጵያና በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ መካከል የቆየውን ወዳጅነት የበለጠ እንደሚያጠናክረው ገልጸዋል።
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የሀገሪቱ ሚኒስትሮች፣ አምባሳደሮች፣ ዲፕሎማቶችና የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አባላት ታድመዋል።
በሰለሞን ኃይለኢየሱስ ከአቡዳቢ
#ethiopia #medemer #abiyahmed #uae #abudhabi #booklaunch #diplomacy
*************************
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጻፈው “የመደመር መንግሥት“ የአረብኛው ትርጉም በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ አቡዳቢ በዛሬው ዕለት ተመርቋል።
በአቡ ዳቢ የተመረቀው ይህ መጽሐፍ በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ ሁሉም አረብኛ ተናጋሪ ሀገራትና ሕዝቦች፣ ኢትዮጵያ በመደመር መንግሥትና ፍልስፍና እያራመደች የምትገኘውን የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የለውጥ እንቅስቃሴ ትልሞች በጥልቀት እንዲገነዘቡት ዓላማ ያደረገ ነው።
በመጽሐፍ ምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ጀማል በከር (ዶ/ር)፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተጻፈው “የመደመር መንግሥት” አረብኛ ትርጉም እውን መሆን በኢትዮጵያና በተቀረው የአረቡ ዓለም በኩል ያሉ የጋራ ጥቅሞችን አስተሳስሮ ለማስቀጠልና የጋራ ጥቅሞቻችንን ለማስጠቅ እንደሚያግዝ ተናግረዋል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲኤታ ሸክ ሻክቡት ቢን ናህያን አልናህያን፣ መጽሐፉ በአረብኛ ቋንቋ ተተርጉሞ መቅረቡ በኢትዮጵያና በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ መካከል የቆየውን ወዳጅነት የበለጠ እንደሚያጠናክረው ገልጸዋል።
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የሀገሪቱ ሚኒስትሮች፣ አምባሳደሮች፣ ዲፕሎማቶችና የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አባላት ታድመዋል።
በሰለሞን ኃይለኢየሱስ ከአቡዳቢ
#ethiopia #medemer #abiyahmed #uae #abudhabi #booklaunch #diplomacy
3 months ago
3 months ago
የጥቁር ሕዝቦች ድምፅ በተመድ አዳራሽ - ኢትዮጵያ ለነፃነት የከፈለችው ዲፕሎማሲያዊ ዋጋ
********************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያላቸው ትሥሥር እንደ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ብቻ የሚታይ ሳይሆን፣ በታሪክ አውድማ ላይ በፅናት እና በሉዓላዊነት የተገመደ የክብር ሰንሰለት ነው።
ከሰማንያ ዓመታት በፊት ዓለም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍርስራሽ ላይ ቆማ አዲስ ተስፋን ስትፈልግ፣ ኢትዮጵያ ከ51ዱ መሥራች ሀገራት መካከል አንዷ ሆና የቻርተሩን ሰነድ ስትፈርም ተራ ተሳታፊ አልነበረችም።
ይልቁንም፣ የዲፕሎማቶቻችን ድምፅ የኃያላንን የበላይነት ለመሞገት እና የደካማ ሀገራትን መብት ለማስጠበቅ የሚተጋ የፍትሕ ጩኸት ነበር።
በወቅቱ በቅኝ ግዛት ቀንበር ሥር ለነበሩት ወንድም የአፍሪካ እና የእስያ ሕዝቦች፣ ኢትዮጵያ ብቸኛ የነፃነት እና የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት ተሟጋች ሆና መቅረቧ፣ “ለራስ ሲቆርሱ አያሳንሱ” የሚለውን ብሂል ወደ ጎን በመተው ለሰው ልጅ ሁሉ ነፃነት መቆሟን ያሳየ ታላቅ የሞራል ልዕልና ነበር።
ይህ የታሪክ አሻራ ዛሬም በደማቅ ቀለም እየተጻፈ ይገኛል። ኢትዮጵያ ላለፉት ሰማንያ ዓመታት በሚጠጋ ጊዜ ውስጥ ከ100 ሺህ በላይ የሰላም ዘቦችን በተለያዩ የዓለም ክፍሎች በማሠማራት፣ በዓለም ሰላም ማስከበር ሂደት ውስጥ ያላትን የማይናወጥ ሚና በተግባር አሳይታለች።
የሀገራችን ሠራዊት በሄደበት ሥፍራ ሁሉ የሚታወቅበት የጥንካሬ፣ የዲሲፕሊን እና የሕዝባዊነት ገጽታ፣ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰላም አስከባሪ ሠራዊት ከሚያዋጡ ሀገራት ግንባር ቀደም ተጠቃሽ አድርጓታል። ይህ መሥዋዕትነት ለራሳችን ብቻ ሳይሆን ለጎረቤቶቻችን እና ለመላው ዓለም ሰላም መቆማችንን የሚያረጋግጥ የቆራጥነት ማሳያ ነው።
በተመድ እና በአፍሪካ ኅብረት ጥላ ሥር የሚከናወኑት እነዚህ ተልዕኮዎች፣ የኢትዮጵያን የሰላም አምባሳደርነት በዓለም አደባባይ ከፍ አድርገውታል።
ዛሬ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ አዲስ አበባን በተደጋጋሚ መጎብኘታቸው እና የድርጅቱን 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል እዚህ በታሪካዊቷ ከተማችን እንዲከበር መወሰኑ፣ እንዲሁ የተገኘ ድንገተኛ ክስተት አይደለም። ይህ ውሳኔ ኢትዮጵያ ለድርጅቱ ያበረከተችው ታሪካዊ አስተዋፅኦ እና ለዓለም ሰላም የከፈለችው መሥዋዕትነት የተሰጠው ታላቅ እውቅና ነው።
“መልካም ስም ከመቃብር በላይ ይውላል” እንዲሉ፣ የሀገራችን የዲፕሎማሲ ጥንካሬ እና የሠራዊታችን አኩሪ ገጽታ ለስምንት ዐሥርተ ዓመታት ተጠብቆ ቆይቶ ዛሬም በዓለም መድረክ ድምፃችን ጎልቶ እንዲሰማ አድርጎታል።
ይህም የአፍሪካን ዳግም መነሣት የሚያበስር ምልክት እና ለጋራ ብልጽግና የምታደርገውን ጉዞ የሚያፋጥን የጥንካሬ ምሰሶ ነው።
ኢትዮጵያ እና ተመድ በዘላቂ ልማት ግቦች ዙሪያ ያላቸው ትብብርም ሌላው የትሥሥሩ ገጽታ ነው። ድህነትን ለማጥፋት፣ ፕላኔቷን ለመጠበቅ እና ለሁሉም ሰው ሰላምን ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረት፣ ሀገራችን ከድርጅቱ ጋር ያላትን ስትራቴጂክ አጋርነት ይበልጥ ያጠናክረዋል።
ወደፊትም ቢሆን ኢትዮጵያ የድርጅቱ ደጀን እና የልማት ተምሳሌት ሆና በመቀጠል፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ፍትሐዊ ሥርዓት እንዲሰፍን እና የጋራ ብልጽግና እንዲረጋገጥ የነበራትን የሞራል መሪነት አጠናክራ እንደምትቀጥል ጥርጥር የለውም።
የታሪካችን ጥንካሬ እና የሠራዊታችን ፅናት ዛሬም ለዓለም ሰላም ዋስትና፣ ለትውልድም ኩራት ሆኖ ይቀጥላል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ebc #ethiopia #diplomacy #un #un80
********************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ያላቸው ትሥሥር እንደ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ብቻ የሚታይ ሳይሆን፣ በታሪክ አውድማ ላይ በፅናት እና በሉዓላዊነት የተገመደ የክብር ሰንሰለት ነው።
ከሰማንያ ዓመታት በፊት ዓለም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍርስራሽ ላይ ቆማ አዲስ ተስፋን ስትፈልግ፣ ኢትዮጵያ ከ51ዱ መሥራች ሀገራት መካከል አንዷ ሆና የቻርተሩን ሰነድ ስትፈርም ተራ ተሳታፊ አልነበረችም።
ይልቁንም፣ የዲፕሎማቶቻችን ድምፅ የኃያላንን የበላይነት ለመሞገት እና የደካማ ሀገራትን መብት ለማስጠበቅ የሚተጋ የፍትሕ ጩኸት ነበር።
በወቅቱ በቅኝ ግዛት ቀንበር ሥር ለነበሩት ወንድም የአፍሪካ እና የእስያ ሕዝቦች፣ ኢትዮጵያ ብቸኛ የነፃነት እና የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት ተሟጋች ሆና መቅረቧ፣ “ለራስ ሲቆርሱ አያሳንሱ” የሚለውን ብሂል ወደ ጎን በመተው ለሰው ልጅ ሁሉ ነፃነት መቆሟን ያሳየ ታላቅ የሞራል ልዕልና ነበር።
ይህ የታሪክ አሻራ ዛሬም በደማቅ ቀለም እየተጻፈ ይገኛል። ኢትዮጵያ ላለፉት ሰማንያ ዓመታት በሚጠጋ ጊዜ ውስጥ ከ100 ሺህ በላይ የሰላም ዘቦችን በተለያዩ የዓለም ክፍሎች በማሠማራት፣ በዓለም ሰላም ማስከበር ሂደት ውስጥ ያላትን የማይናወጥ ሚና በተግባር አሳይታለች።
የሀገራችን ሠራዊት በሄደበት ሥፍራ ሁሉ የሚታወቅበት የጥንካሬ፣ የዲሲፕሊን እና የሕዝባዊነት ገጽታ፣ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰላም አስከባሪ ሠራዊት ከሚያዋጡ ሀገራት ግንባር ቀደም ተጠቃሽ አድርጓታል። ይህ መሥዋዕትነት ለራሳችን ብቻ ሳይሆን ለጎረቤቶቻችን እና ለመላው ዓለም ሰላም መቆማችንን የሚያረጋግጥ የቆራጥነት ማሳያ ነው።
በተመድ እና በአፍሪካ ኅብረት ጥላ ሥር የሚከናወኑት እነዚህ ተልዕኮዎች፣ የኢትዮጵያን የሰላም አምባሳደርነት በዓለም አደባባይ ከፍ አድርገውታል።
ዛሬ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ አዲስ አበባን በተደጋጋሚ መጎብኘታቸው እና የድርጅቱን 80ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል እዚህ በታሪካዊቷ ከተማችን እንዲከበር መወሰኑ፣ እንዲሁ የተገኘ ድንገተኛ ክስተት አይደለም። ይህ ውሳኔ ኢትዮጵያ ለድርጅቱ ያበረከተችው ታሪካዊ አስተዋፅኦ እና ለዓለም ሰላም የከፈለችው መሥዋዕትነት የተሰጠው ታላቅ እውቅና ነው።
“መልካም ስም ከመቃብር በላይ ይውላል” እንዲሉ፣ የሀገራችን የዲፕሎማሲ ጥንካሬ እና የሠራዊታችን አኩሪ ገጽታ ለስምንት ዐሥርተ ዓመታት ተጠብቆ ቆይቶ ዛሬም በዓለም መድረክ ድምፃችን ጎልቶ እንዲሰማ አድርጎታል።
ይህም የአፍሪካን ዳግም መነሣት የሚያበስር ምልክት እና ለጋራ ብልጽግና የምታደርገውን ጉዞ የሚያፋጥን የጥንካሬ ምሰሶ ነው።
ኢትዮጵያ እና ተመድ በዘላቂ ልማት ግቦች ዙሪያ ያላቸው ትብብርም ሌላው የትሥሥሩ ገጽታ ነው። ድህነትን ለማጥፋት፣ ፕላኔቷን ለመጠበቅ እና ለሁሉም ሰው ሰላምን ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረት፣ ሀገራችን ከድርጅቱ ጋር ያላትን ስትራቴጂክ አጋርነት ይበልጥ ያጠናክረዋል።
ወደፊትም ቢሆን ኢትዮጵያ የድርጅቱ ደጀን እና የልማት ተምሳሌት ሆና በመቀጠል፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ፍትሐዊ ሥርዓት እንዲሰፍን እና የጋራ ብልጽግና እንዲረጋገጥ የነበራትን የሞራል መሪነት አጠናክራ እንደምትቀጥል ጥርጥር የለውም።
የታሪካችን ጥንካሬ እና የሠራዊታችን ፅናት ዛሬም ለዓለም ሰላም ዋስትና፣ ለትውልድም ኩራት ሆኖ ይቀጥላል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ebc #ethiopia #diplomacy #un #un80
3 months ago
እንከባበር! - ኢራን
#ethiopia | ኢራን በኩዌት የታሰሩ ዜጎቿን በተመለከተ የአጸፋ እርምጃ የመውሰድ መብት እንዳለት አስታወቀች
በፋርስ ባሕረ ሰላጤ አቅራቢያ አራት ኢራናውያን በኩዌት የጸጥታ ኃይሎች መታሰራቸውን ተከትሎ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሀገራቸው ተመጣጣኝ ምላሽ የመስጠት መብት እንዳላት አስታውቃለችል፡፡
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቅቺ በሰጡት መግለጫ ኩዌት በሕገወጥ መንገድ በኢራን የባሕር ጓዝ ላይ ጥቃት መፈጸሟንና ዜጎቿን ማሰሯን ገልጸው የታሰሩት ግለሰቦች በአስቸኳይ እንዲፈቱ ጠይቀዋል፡፡
በሌላ በኩል የኩዌት የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ በባሕር በኩል ወደ ሀገር ውስጥ ለመግባት ሲሞክሩ የተያዙት አራት ግለሰቦች የኢራን አብዮታዊ ዘበኛ አባላት መሆናቸውን እንዳመኑ ይፋ አድርጓል፡፡
ይህንን ድርጊት ተከትሎ ዮርዳኖስ የኩዌትን ሉዓላዊነት የሚጋፋ ተግባር ነው ስትል ድርጊቱን ያወገዘች ሲሆን ለኩዌት ያላትን ሙሉ ድጋፍ ገልጻለች፡፡
ኢራን ግን ግለሰቦቹ ከአብዮታዊ ዘበኛው ጋር ግንኙነት አላቸው መባሉን አስተባብላለች፡፡
#iran #kuwait #middleeast #diplomacy #jordan #redsea #internationalnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ኢራን በኩዌት የታሰሩ ዜጎቿን በተመለከተ የአጸፋ እርምጃ የመውሰድ መብት እንዳለት አስታወቀች
በፋርስ ባሕረ ሰላጤ አቅራቢያ አራት ኢራናውያን በኩዌት የጸጥታ ኃይሎች መታሰራቸውን ተከትሎ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሀገራቸው ተመጣጣኝ ምላሽ የመስጠት መብት እንዳላት አስታውቃለችል፡፡
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቅቺ በሰጡት መግለጫ ኩዌት በሕገወጥ መንገድ በኢራን የባሕር ጓዝ ላይ ጥቃት መፈጸሟንና ዜጎቿን ማሰሯን ገልጸው የታሰሩት ግለሰቦች በአስቸኳይ እንዲፈቱ ጠይቀዋል፡፡
በሌላ በኩል የኩዌት የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ በባሕር በኩል ወደ ሀገር ውስጥ ለመግባት ሲሞክሩ የተያዙት አራት ግለሰቦች የኢራን አብዮታዊ ዘበኛ አባላት መሆናቸውን እንዳመኑ ይፋ አድርጓል፡፡
ይህንን ድርጊት ተከትሎ ዮርዳኖስ የኩዌትን ሉዓላዊነት የሚጋፋ ተግባር ነው ስትል ድርጊቱን ያወገዘች ሲሆን ለኩዌት ያላትን ሙሉ ድጋፍ ገልጻለች፡፡
ኢራን ግን ግለሰቦቹ ከአብዮታዊ ዘበኛው ጋር ግንኙነት አላቸው መባሉን አስተባብላለች፡፡
#iran #kuwait #middleeast #diplomacy #jordan #redsea #internationalnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 months ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በሳይንስ ሙዚየም ያደረጉት ጉብኝት #ebc #ethiopia #france #diplomacy
Comments