14 hours ago
IMF ለኢትዮጵያ የ468 ሚሊዮን ዶላር ተጨማሪ የገንዘብ ድጋፍ የሚያስገኝ የስምምነት ደረጃ ላይ መድረሱን አስታወቀ
የኔታ ሚዲያ
የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የባለሙያዎች ቡድን እና የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት በ3.4 ቢሊዮን ዶላር የተራዘመ የብድር ማዕቀፍ (ECF) አምስተኛው ክለሳ ላይ ከስምምነት መድረሳቸውን ድርጅቱ አስታወቀ።
ይህ በባለሙያዎች ደረጃ የተደረሰው ስምምነት በIMF ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሲጸድቅ ኢትዮጵያ ወደ 468 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚጠጋ ተጨማሪ ገንዘብ ማግኘት የምትችል ይሆናል።
በአልቫሮ ፒሪስ የተመራው የIMF የባለሙያዎች ቡድን ከአምስተኛው ክለሳ ጋር በተያያዘ ከግንቦት 1 እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በአካል ከዚያ በኋላ ደግሞ በበይነ መረብ (ቨርቿል) ውይይት ሲያደርግ ቆይቷል።
የልዑካን ቡድኑ መሪ አልቫሮ ፒሪስ ባወጡት መግለጫ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት አገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳቸውን በተሳካ ሁኔታ መተግበራቸውን መቀጠላቸውን ገልጸዋል።
እ.ኤ.አ እስከ 2026 መጀመሪያ ድረስ የምርት አመላካቾች፣ ወጪ ንግድ፣ የውጭ ምንዛሬ ክምችት እና የመንግሥት ገቢ መሻሻል ማሳየታቸውንና የዋጋ ንረትም መቀነሱን ጠቁመዋል።
ሆኖም በመካከለኛው ምስራቅ የተቀሰቀሰው ጦርነት በንግድ እንቅስቃሴ ላይ መስተጓጎል መፍጠሩን፣ ጊዜያዊ የነዳጅ እጥረት ማስከተሉን እና የገቢ ነዳጅና ማዳበሪያ ዋጋን በከፍተኛ ሁኔታ ማናሩን መግለጫው አመልክቷል።
ይህ ትልቅ ውጫዊ ተጽዕኖ ቢሆንም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አሁንም ጠንካራ መሆኑንና በምርት ዕድገትና በሸማቾች ዋጋ ንረት ላይ ያሳደረው ተጽዕኖ እስካሁን መጠነኛ መሆኑ ተገልጿል።
የIMF መግለጫ በመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ምክንያት ዓለም አቀፋዊ አለመረጋጋትና የሸቀጦች ዋጋ መዋዠቅ በመጨመሩ፣ በኢኮኖሚው ላይ ሊደቀኑ የሚችሉ ስጋቶች መጨመራቸውን ያስጠነቅቃል። በመሆኑም ለነዚህ አዳዲስ ተግዳሮቶች ብልህ ምላሽ መስጠትና የሀብት አጠቃቀምን በጥንቃቄ መምራት እንደሚያስፈልግ አሳስቧል።
ማክሮ-ኢኮኖሚያዊ መረጋጋትን በዘላቂነት ለማስቀጠል የሚከተሉት መሠረታዊ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ድርጅቱ መክሯል፦
• የገንዘብ ፖሊሲ ማጥበቅ፦ የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲን ማስቀጠል።
• የውጭ ምንዛሬ ገበያ ማሻሻያ፦ የውጭ ምንዛሬ ገበያው ይበልጥ ግልጽና ውጤታማ በሆነ መንገድ እንዲሠራ ማድረግ።
• የአገር ውስጥ ገቢና ወጪ አስተዳደር፦ የአገር ውስጥ ገቢ ማሰባሰብን ማሳደግና የወጪ አስተዳደርን በጥንቃቄ በመምራት የፋይናንስ ዘላቂነትን ማረጋገጥ።
• መዋቅራዊ ማሻሻያዎች፦ የንግድ አካባቢን ማሻሻል፣ የፋይናንስ ዘርፉን ጥንካሬ ማጠናከርና የግል ዘርፉ መር ለሆነ ዕድገት በር መክፈት።
የውጭ ዕዳ ሽግሽግ
የኢትዮጵያን የዕዳ ዘላቂነት ለመመለስ የሚያስችል አጠቃላይ የውጭ ዕዳ ሽግሽግ (treatment) ለማግኘት መልካም ግስጋሴ እየታየ መሆኑን IMF ገልጿል። ከባለሥልጣናት አበዳሪዎች ጋር የሚደረገው የዕዳ መልሶ ማዋቀር ውይይት እንደተጠበቀው እየገፋ ሲሆን ከቦንድ ባለቤቶች ጋር የሚደረገው ድርድርም መቀጠሉ ተጠቅሷል።
የIMF ልዑካን ቡድን በአዲስ አበባ በነበረው ቆይታ ከገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ፣ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ እና ከሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ እንዲሁም ከግል ዘርፉና ከልማት አጋሮች ተወካዮች ጋር ፍሬያማ ውይይት ማድረጉን በመግለጽ ለተደረገለት ትብብር ምስጋና አቅርቧል።
ይህ አምስተኛው ክለሳ በIMF ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሲጸድቅ ኢትዮጵያ በዚሁ ማዕቀፍ እስካሁን ያገኘችው አጠቃላይ የገንዘብ ድጋፍ ወደ 2.65 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ከፍ ይላል።
የኔታ ሚዲያ
የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የባለሙያዎች ቡድን እና የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት በ3.4 ቢሊዮን ዶላር የተራዘመ የብድር ማዕቀፍ (ECF) አምስተኛው ክለሳ ላይ ከስምምነት መድረሳቸውን ድርጅቱ አስታወቀ።
ይህ በባለሙያዎች ደረጃ የተደረሰው ስምምነት በIMF ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሲጸድቅ ኢትዮጵያ ወደ 468 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚጠጋ ተጨማሪ ገንዘብ ማግኘት የምትችል ይሆናል።
በአልቫሮ ፒሪስ የተመራው የIMF የባለሙያዎች ቡድን ከአምስተኛው ክለሳ ጋር በተያያዘ ከግንቦት 1 እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በአካል ከዚያ በኋላ ደግሞ በበይነ መረብ (ቨርቿል) ውይይት ሲያደርግ ቆይቷል።
የልዑካን ቡድኑ መሪ አልቫሮ ፒሪስ ባወጡት መግለጫ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት አገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳቸውን በተሳካ ሁኔታ መተግበራቸውን መቀጠላቸውን ገልጸዋል።
እ.ኤ.አ እስከ 2026 መጀመሪያ ድረስ የምርት አመላካቾች፣ ወጪ ንግድ፣ የውጭ ምንዛሬ ክምችት እና የመንግሥት ገቢ መሻሻል ማሳየታቸውንና የዋጋ ንረትም መቀነሱን ጠቁመዋል።
ሆኖም በመካከለኛው ምስራቅ የተቀሰቀሰው ጦርነት በንግድ እንቅስቃሴ ላይ መስተጓጎል መፍጠሩን፣ ጊዜያዊ የነዳጅ እጥረት ማስከተሉን እና የገቢ ነዳጅና ማዳበሪያ ዋጋን በከፍተኛ ሁኔታ ማናሩን መግለጫው አመልክቷል።
ይህ ትልቅ ውጫዊ ተጽዕኖ ቢሆንም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አሁንም ጠንካራ መሆኑንና በምርት ዕድገትና በሸማቾች ዋጋ ንረት ላይ ያሳደረው ተጽዕኖ እስካሁን መጠነኛ መሆኑ ተገልጿል።
የIMF መግለጫ በመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ምክንያት ዓለም አቀፋዊ አለመረጋጋትና የሸቀጦች ዋጋ መዋዠቅ በመጨመሩ፣ በኢኮኖሚው ላይ ሊደቀኑ የሚችሉ ስጋቶች መጨመራቸውን ያስጠነቅቃል። በመሆኑም ለነዚህ አዳዲስ ተግዳሮቶች ብልህ ምላሽ መስጠትና የሀብት አጠቃቀምን በጥንቃቄ መምራት እንደሚያስፈልግ አሳስቧል።
ማክሮ-ኢኮኖሚያዊ መረጋጋትን በዘላቂነት ለማስቀጠል የሚከተሉት መሠረታዊ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ድርጅቱ መክሯል፦
• የገንዘብ ፖሊሲ ማጥበቅ፦ የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲን ማስቀጠል።
• የውጭ ምንዛሬ ገበያ ማሻሻያ፦ የውጭ ምንዛሬ ገበያው ይበልጥ ግልጽና ውጤታማ በሆነ መንገድ እንዲሠራ ማድረግ።
• የአገር ውስጥ ገቢና ወጪ አስተዳደር፦ የአገር ውስጥ ገቢ ማሰባሰብን ማሳደግና የወጪ አስተዳደርን በጥንቃቄ በመምራት የፋይናንስ ዘላቂነትን ማረጋገጥ።
• መዋቅራዊ ማሻሻያዎች፦ የንግድ አካባቢን ማሻሻል፣ የፋይናንስ ዘርፉን ጥንካሬ ማጠናከርና የግል ዘርፉ መር ለሆነ ዕድገት በር መክፈት።
የውጭ ዕዳ ሽግሽግ
የኢትዮጵያን የዕዳ ዘላቂነት ለመመለስ የሚያስችል አጠቃላይ የውጭ ዕዳ ሽግሽግ (treatment) ለማግኘት መልካም ግስጋሴ እየታየ መሆኑን IMF ገልጿል። ከባለሥልጣናት አበዳሪዎች ጋር የሚደረገው የዕዳ መልሶ ማዋቀር ውይይት እንደተጠበቀው እየገፋ ሲሆን ከቦንድ ባለቤቶች ጋር የሚደረገው ድርድርም መቀጠሉ ተጠቅሷል።
የIMF ልዑካን ቡድን በአዲስ አበባ በነበረው ቆይታ ከገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ፣ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ እና ከሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ እንዲሁም ከግል ዘርፉና ከልማት አጋሮች ተወካዮች ጋር ፍሬያማ ውይይት ማድረጉን በመግለጽ ለተደረገለት ትብብር ምስጋና አቅርቧል።
ይህ አምስተኛው ክለሳ በIMF ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሲጸድቅ ኢትዮጵያ በዚሁ ማዕቀፍ እስካሁን ያገኘችው አጠቃላይ የገንዘብ ድጋፍ ወደ 2.65 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ከፍ ይላል።
17 hours ago
ኢራን በኩዌት አውሮፕላን ማረፊያ ላይ በፈጸመችው የድሮን ጥቃት በርካቶች መጎዳታቸው ተገለጸ
የኢራን ድሮኖች የኩዌት አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ረቡዕ ማለዳ ጥቃት መፈጸማቸውን ተከትሎ በረራዎች መቋረጣቸው ተገለጸ።
በኩዌት የአውሮፕላን ማረፊያ ላይ ጥቃት የተፈጸመው ቴህራን እና ዋሺንግተን አንዳቸው በሌላኛቸው ላይ ጥቃት ከፈጸሙ በኋላ ሲሆን በርካታ ሰዎች መጎዳታቸውም ተገልጿል።
ሁለት የኢራን ዜና ወኪሎች ቴህራን የተኩስ አቁሙን ለማራዘም ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን ንግግር ማቋረጧን ማክሰኞ ዕለት ዘግበዋል።
ትራምፕ ግን ዘገባውን አጣጥለው ንግግሮች እየተካሄዱ ናቸው ብለዋል።
የኩዌት መከላከያ ቃል አቀባይ ብርጋዴር ጄነራል ሳዑድ አብዱላዚዝ አል ኦታእቢ “በርካታ ጥቃት ፈጻሚ ድሮኖች” የኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የመንገደኞች ማስተናገጃን ዒላማ ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል።
በጥቃቱ የመንገደኞች ማስተናገጃው ክፉኛ መጎዳቱን የገለጹ ሲሆን “በርካታ ሰዎችን” አቁስሏል ብለዋል።
የአውሮፕላን ማረፊያው በኢራን ጦርነት ምክንያት ተዘግቶ ከቆየ በኋላ ለአገልግሎት ክፍት የሆነው ከሁለት ቀናት በፊት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም. ነበር።
ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ የአሜሪካ ጦር ኢራን በኩዌት እና ባህሬን ላይ ጥቃት መፈጸሟን ጠቅሶ በወታደራዊ ተቋማቷ ላይ የአጸፋ ምላሽ ድብደባ ማካሄዱን አስታውቋል።
የአሜሪካ ጦር አክሎም በኩዌት የሚገኙ የጦር ሰፈሮቹን ዒላማ ያደረጉ “በርካታ ድሮኖችን መትተን ጥለናል” ሲል አስታውቋል።
የኢራን ፈጥኖ ደራሽ አብዮታዊ ዘብ በባህሬን የሚገኝ የአሜሪካ ባሕር ኃይል ዋና ማዘዣ እና ኩዌትን በስም ሳይጠቅስ ሌላ አገር ላይ ጥቃት መፈጸሙን ገልጿል።
አክሎም ጥቃቱን የፈጸመው የአሜሪካ ጦር የጣለውን እገዳ ለማለፍ እየተንቀሳቀሰች የነበረች ነዳጅ ጫን መርከብ ሞተር ላይ ጥቃት መፈጸሙን ተከትሎመሆኑን ጠቅሷል።
አብዮታዊ ዘቡ በመግለጫው “ከዚህ በፊት ለማንኛውም ጥቃት የምንሰጠው ምላሽ የተለየ እና የከፋ እንደሚሆን ተናግረን በነበረው መሠረተ እረምጃውን ወስደናል” ብሏል።
BBC
የኢራን ድሮኖች የኩዌት አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ረቡዕ ማለዳ ጥቃት መፈጸማቸውን ተከትሎ በረራዎች መቋረጣቸው ተገለጸ።
በኩዌት የአውሮፕላን ማረፊያ ላይ ጥቃት የተፈጸመው ቴህራን እና ዋሺንግተን አንዳቸው በሌላኛቸው ላይ ጥቃት ከፈጸሙ በኋላ ሲሆን በርካታ ሰዎች መጎዳታቸውም ተገልጿል።
ሁለት የኢራን ዜና ወኪሎች ቴህራን የተኩስ አቁሙን ለማራዘም ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን ንግግር ማቋረጧን ማክሰኞ ዕለት ዘግበዋል።
ትራምፕ ግን ዘገባውን አጣጥለው ንግግሮች እየተካሄዱ ናቸው ብለዋል።
የኩዌት መከላከያ ቃል አቀባይ ብርጋዴር ጄነራል ሳዑድ አብዱላዚዝ አል ኦታእቢ “በርካታ ጥቃት ፈጻሚ ድሮኖች” የኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የመንገደኞች ማስተናገጃን ዒላማ ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል።
በጥቃቱ የመንገደኞች ማስተናገጃው ክፉኛ መጎዳቱን የገለጹ ሲሆን “በርካታ ሰዎችን” አቁስሏል ብለዋል።
የአውሮፕላን ማረፊያው በኢራን ጦርነት ምክንያት ተዘግቶ ከቆየ በኋላ ለአገልግሎት ክፍት የሆነው ከሁለት ቀናት በፊት ግንቦት 24/2018 ዓ.ም. ነበር።
ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ የአሜሪካ ጦር ኢራን በኩዌት እና ባህሬን ላይ ጥቃት መፈጸሟን ጠቅሶ በወታደራዊ ተቋማቷ ላይ የአጸፋ ምላሽ ድብደባ ማካሄዱን አስታውቋል።
የአሜሪካ ጦር አክሎም በኩዌት የሚገኙ የጦር ሰፈሮቹን ዒላማ ያደረጉ “በርካታ ድሮኖችን መትተን ጥለናል” ሲል አስታውቋል።
የኢራን ፈጥኖ ደራሽ አብዮታዊ ዘብ በባህሬን የሚገኝ የአሜሪካ ባሕር ኃይል ዋና ማዘዣ እና ኩዌትን በስም ሳይጠቅስ ሌላ አገር ላይ ጥቃት መፈጸሙን ገልጿል።
አክሎም ጥቃቱን የፈጸመው የአሜሪካ ጦር የጣለውን እገዳ ለማለፍ እየተንቀሳቀሰች የነበረች ነዳጅ ጫን መርከብ ሞተር ላይ ጥቃት መፈጸሙን ተከትሎመሆኑን ጠቅሷል።
አብዮታዊ ዘቡ በመግለጫው “ከዚህ በፊት ለማንኛውም ጥቃት የምንሰጠው ምላሽ የተለየ እና የከፋ እንደሚሆን ተናግረን በነበረው መሠረተ እረምጃውን ወስደናል” ብሏል።
BBC
19 hours ago
በኢትዮጵያ የአውሮጳ ኅብረት ልዑክ እና በአዲስ አበባ የሚገኙ የኅብረቱ አባል አገራት ኤምባሲዎች ስለ ሰባተኛው የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ያወጡት መግለጫ
በኢትዮጵያ የአውሮጳ ኅብረት ልዑክ እና በአዲስ አበባ የሚገኙ የኅብረቱ አባል አገራት ኤምባሲዎች ግንቦት 24 ቀን 2018 ምርጫ ያልተካሔደባቸው የምርጫ ክልሎች ድምጽ የመስጠት “ዕድል ይሰጣቸዋል” የሚል ተስፋ እንዳላቸው አስታወቁ።
በኢትዮጵያ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ምርጫ መካሄዱን በበጎ እንደሚቀበሉ የኅብረቱ ተልዕኮ መቀመጫቸውን በአዲስ አበባ ካደረጉ 25 ኤምባሲዎች ጋር በጋራ ባወጡት መግለጫ አስታውቀዋል።
ምርጫው በተካሔደ በሁለተኛው ቀን ዛሬ ረቡዕ መግለጫውን ከኅብረቱ ጋር ካወጡ የአውሮፓ ኅብረት አባል አገራት ኤምባሲዎች መካከል የጀርመን እና የፈረንሳይ የዲፕሎማሲ ተልዕኮዎች ይገኙበታል። የአውሮፓ ኅብረት አባል አገር ያልሆኑት ካናዳ፣ ኖርዌይ እና ስዊትዘርላንድም ምርጫን በተመለከተ በመግለጫው አቋማቸውን ካንጸባረቁ መካከል ናቸው።
በመግለጫው “የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የምርጫ ሠራተኞች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ዕጩዎች እና የሲቪል ማኅበራት ተዋናዮች ያበረከቱትን አስተዋጽዖ እናደንቃለን” ብለዋል።
የአፍሪካ ኅብረት እና የምሥራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) እንደ ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ያላቸውን ጠቃሚ ሚና እንገነዘባለን ያለው የጋራ መግለጫው ዘገባዎቻቸውን በጉጉት እንደሚጠብቅም አስታውቋል።
ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ምርጫ ማካሄድ ያልቻሉ የምርጫ ክልሎች በሙሉ ይህን ለማድረግ እድሉ እንደሚሰጣቸው ተስፋ እናደርጋለን ሲል በኢትዮጵያ የኅብረቱ ልዑካንና የኅብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ተልዕኮዎች የጋራ መግለጫ አስታውቋል።
DW Amharic
በኢትዮጵያ የአውሮጳ ኅብረት ልዑክ እና በአዲስ አበባ የሚገኙ የኅብረቱ አባል አገራት ኤምባሲዎች ግንቦት 24 ቀን 2018 ምርጫ ያልተካሔደባቸው የምርጫ ክልሎች ድምጽ የመስጠት “ዕድል ይሰጣቸዋል” የሚል ተስፋ እንዳላቸው አስታወቁ።
በኢትዮጵያ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ምርጫ መካሄዱን በበጎ እንደሚቀበሉ የኅብረቱ ተልዕኮ መቀመጫቸውን በአዲስ አበባ ካደረጉ 25 ኤምባሲዎች ጋር በጋራ ባወጡት መግለጫ አስታውቀዋል።
ምርጫው በተካሔደ በሁለተኛው ቀን ዛሬ ረቡዕ መግለጫውን ከኅብረቱ ጋር ካወጡ የአውሮፓ ኅብረት አባል አገራት ኤምባሲዎች መካከል የጀርመን እና የፈረንሳይ የዲፕሎማሲ ተልዕኮዎች ይገኙበታል። የአውሮፓ ኅብረት አባል አገር ያልሆኑት ካናዳ፣ ኖርዌይ እና ስዊትዘርላንድም ምርጫን በተመለከተ በመግለጫው አቋማቸውን ካንጸባረቁ መካከል ናቸው።
በመግለጫው “የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የምርጫ ሠራተኞች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ዕጩዎች እና የሲቪል ማኅበራት ተዋናዮች ያበረከቱትን አስተዋጽዖ እናደንቃለን” ብለዋል።
የአፍሪካ ኅብረት እና የምሥራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግሥታት ባለሥልጣን (ኢጋድ) እንደ ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች ያላቸውን ጠቃሚ ሚና እንገነዘባለን ያለው የጋራ መግለጫው ዘገባዎቻቸውን በጉጉት እንደሚጠብቅም አስታውቋል።
ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ምርጫ ማካሄድ ያልቻሉ የምርጫ ክልሎች በሙሉ ይህን ለማድረግ እድሉ እንደሚሰጣቸው ተስፋ እናደርጋለን ሲል በኢትዮጵያ የኅብረቱ ልዑካንና የኅብረቱ አባል ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ተልዕኮዎች የጋራ መግለጫ አስታውቋል።
DW Amharic
21 hours ago
በኒው ዌይ ኢትዮጵያ የተዘጋጀው የመጀመሪያው የአርሜንያ ጉዞ በስኬት ተጠናቀቀ ።
በኒው ዌይ ኢትዮጵያ አስጎብኚ ድርጅት የተዘጋጀው ለ5 ቀናት የቆየው የእናታችን የቅድስት አርሴማን ጨምሮ የበርካታ ገዳማት ጉብኝት እንዲሁም የከተማ ውስጥ ቱር ስኬታማ እንደነበር በተጓዦች ተመስክሮለታል።
በሁለተኛ እና ሶስተኛ ዙር ጉዞውን በሰኔ 17/2018 እና በሀምሌ 4/2018 እንደሚያደርግም ተገልፁዋል
በእነዚም ጉዞዎች ወደ አርሜንያ የደርሶ መልስ ትኬት፣ የአልጋ እና ቁርስ፣የቱር መኪና እና አስጎብኚ እንዲሁም የቪዛ እና ኢንሺራንስ ኒው ዌይ ኢትዮዽያ አስተካክሎ በእንክብካቤ ወስዶ እንደሚመልሳችሁ አሁንም ቃል ይገባል።
ለበለጠ መረጃ በዚህ በስልክ ይደውሉ :- +251978333435 ይደውሉ በተጨመሪም በውጪ ሀገር ለምትገኙ ውድ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ ለወዳጅ ዘመድዎ በWhatsApp ቁጥራችን በማስመዝገብ መጋበዝ ይችላሉ
ኒው ዌይ ኢትዮጲያ ከሚጎበኙ ቦታዎች መካከል :-
1.የእናታችን የቅድስት አርሴማ መቃብር የሚገኝበት ገዳም
2. በአለማችን የመጀመሪያ ጥንታዊው ገዳም የቅዱስ ጎርጎሪዎስ 13 ዓመት ክርስትናን በመስበኩ ከመሬት በታች የታሰረበት ገዳም
3. የመዳኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በስቅለቱ ጊዜ ጎኑን የተወጋበት ጦር የሚገኝበት ገዳምና ሌሎች ገዳማትን እንጎበኛለን። እንዲሁም የአርሜኒያ ከተሞችን እንጎበኛለን።
በተጨማሪም በTiktok . https://www.tiktok.com/@ne...
Instagram.https://www.instagram.com/...
Facebook.https://www.facebook.com/s...
ይመዝገቡ።
ኒው ዌይ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚታወቁ ዓለም አቀፍ ደረጃዎች የኮርፖሬት ቱሪዝምን ለማደራጀት እና የተሟላ አገልግሎትን ለመስጠት ዝግጅቱን ጨርሷል።
በኒው ዌይ ኢትዮጵያ አስጎብኚ ድርጅት የተዘጋጀው ለ5 ቀናት የቆየው የእናታችን የቅድስት አርሴማን ጨምሮ የበርካታ ገዳማት ጉብኝት እንዲሁም የከተማ ውስጥ ቱር ስኬታማ እንደነበር በተጓዦች ተመስክሮለታል።
በሁለተኛ እና ሶስተኛ ዙር ጉዞውን በሰኔ 17/2018 እና በሀምሌ 4/2018 እንደሚያደርግም ተገልፁዋል
በእነዚም ጉዞዎች ወደ አርሜንያ የደርሶ መልስ ትኬት፣ የአልጋ እና ቁርስ፣የቱር መኪና እና አስጎብኚ እንዲሁም የቪዛ እና ኢንሺራንስ ኒው ዌይ ኢትዮዽያ አስተካክሎ በእንክብካቤ ወስዶ እንደሚመልሳችሁ አሁንም ቃል ይገባል።
ለበለጠ መረጃ በዚህ በስልክ ይደውሉ :- +251978333435 ይደውሉ በተጨመሪም በውጪ ሀገር ለምትገኙ ውድ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ ለወዳጅ ዘመድዎ በWhatsApp ቁጥራችን በማስመዝገብ መጋበዝ ይችላሉ
ኒው ዌይ ኢትዮጲያ ከሚጎበኙ ቦታዎች መካከል :-
1.የእናታችን የቅድስት አርሴማ መቃብር የሚገኝበት ገዳም
2. በአለማችን የመጀመሪያ ጥንታዊው ገዳም የቅዱስ ጎርጎሪዎስ 13 ዓመት ክርስትናን በመስበኩ ከመሬት በታች የታሰረበት ገዳም
3. የመዳኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በስቅለቱ ጊዜ ጎኑን የተወጋበት ጦር የሚገኝበት ገዳምና ሌሎች ገዳማትን እንጎበኛለን። እንዲሁም የአርሜኒያ ከተሞችን እንጎበኛለን።
በተጨማሪም በTiktok . https://www.tiktok.com/@ne...
Instagram.https://www.instagram.com/...
Facebook.https://www.facebook.com/s...
ይመዝገቡ።
ኒው ዌይ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚታወቁ ዓለም አቀፍ ደረጃዎች የኮርፖሬት ቱሪዝምን ለማደራጀት እና የተሟላ አገልግሎትን ለመስጠት ዝግጅቱን ጨርሷል።
21 hours ago
ራዕይና የህዝብ እምነት
*******
ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የሀገሪቱን የቀጣይ አምስት ዓመታት እጣ ፈንታ የሚወስን ሀገራዊ ምርጫ በተካሄደበት ማግስት ግንቦት 25 በማለዳ የሀገሪቱና የአዲስ አበባ ከተማ አመራሮች እንጦጦ ላይ ተከስተው ነበር። ጫና ሳይበግረው ህዝቡ እስከ እኩለ ሌሊት በመጠበቅ ዴሞክራሲያዊ መብቱን ለመተግበር ያሳየውን ቁርጠኝነት በማድነቅ ያመሰገኑት ጠ/ሚ/ር አብይ እና ከንቲባ አዳነች ህዝቡን ለመካስ የጀመሩትን ስራ ለማስቀጠል ሰበብ ፈልገው ጊዜ ማባካን ተገቢ ባለመሆኑ ነው እዛ የተገኙት። በውጤቱም ለከተማዋም ሆነ ለህዝቡ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለውን የወንዝ ዳርቻ ልማት መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
በመሰረቱ እነዚህ ሁለቱ መሪዎች ለሚባክን ጊዜ ምንም ጊዜ እንደሌላቸው አብረዋቸው የሰሩ ባልደረቦቻቸውና የስራቸው ውጤት ምስክሮቻቸው ናቸው። ለሚሰሩት ስራ የሰዓት ገደብ የላቸውም፣ ቀን ብቻ ሳይሆን ማታም መደበኛ የስራ ሰዓታቸው ነው። የነበረ አሰራር ከውጤታማነት እንዲጎትታቸው አይፈቅዱም፣ ቀልጣፋና ዘመናዊ አሰራር እውን ማድረግ መርሃቸው ነው። ለጊዜያዊና ወቅታዊ ውዳሴም ሆነ ኩነኔ ጆሮ የላቸውም፣ በምስጋናም ሆነ በእርግማን ከትልቁ መዳረሻቸው እንደማይጎድሉ ተረድተዋል።
እኔ ግን እላችኋለሁ የእነዚህ መሪዎች ትጋት ገፊ ምክንያት ራዕያቸው ነው፣ የእነዚህ መሪዎች ትጋት ገፊ ምክንያት የህዝቡ እምነት ነው። ድህነትን፣ ጉስቁልናን፣ ኋላ ቀርነትን በመፀየፍ፣ የበለፀገችና ተወዳዳሪ ሀገር እውን የማድረግ ራዕይ የትጋታቸው መሰረታዊ ጉልበት ነው። በብዙ እልህ አስጨራሽ ተግዳሮት ውስጥ ቢያልፉም ከስምንት ዓመት በፊት ያዩት እና ዛሬም ህዝቡ በእነርሱ ላይ ያለው የፀና እምነት ለትጋታቸው ተጨማሪ ጉልበት ሆኗቸዋል።
ማህበራዊ ፍትህ የሰፈነባት፣ የበለፀገች፣ ተወዳዳሪና የዜጎችዋ ክብር የተመለሰላት ሀገር እውን እስኪያደርጉ ድረስ እረፍት እንደማይኖራቸው ሰርተው ያመጡት ውጤት ብቻ ሳይሆን ለነገ የሚናገሩት ቃልና የሚገቡት ተስፋ ይመሰክራል። ተናግረው ማድረግን በተግባር ያሳዩ መሆናቸው ደግሞ ራዕያቸውን ለመደገፍና ቃላቸውን ለማመን ምክንያት ይሆናል።
መልዕክት አለኝ:- ራዕያቸው፣ ትጋታቸውና ቁጭታቸው የገባን ቀኝ እጃችንን እንስጣቸው፤ በሌቦች፣ በጽንፈኞችና በስልጣን ጥመኞች ሴራ የተጠራጠርናቸው ደግሞ ረጋ ብለን በስራቸው እንመዝናቸው። ደግሜ የገባኝን እላለሁ እነዚህ መሪዎች መዳረሻቸውን ከመነሻቸው አይተው የተነሱ ናቸውና ራዕያቸውን ሳያሳኩ ለመቆም፣ ለማረፍ፣ ተስፋ ለመቁረጥ ሀሳብም ጊዜም አይኖራቸውም።
ተፃፈ በይመጣል ባህሩ
*******
ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የሀገሪቱን የቀጣይ አምስት ዓመታት እጣ ፈንታ የሚወስን ሀገራዊ ምርጫ በተካሄደበት ማግስት ግንቦት 25 በማለዳ የሀገሪቱና የአዲስ አበባ ከተማ አመራሮች እንጦጦ ላይ ተከስተው ነበር። ጫና ሳይበግረው ህዝቡ እስከ እኩለ ሌሊት በመጠበቅ ዴሞክራሲያዊ መብቱን ለመተግበር ያሳየውን ቁርጠኝነት በማድነቅ ያመሰገኑት ጠ/ሚ/ር አብይ እና ከንቲባ አዳነች ህዝቡን ለመካስ የጀመሩትን ስራ ለማስቀጠል ሰበብ ፈልገው ጊዜ ማባካን ተገቢ ባለመሆኑ ነው እዛ የተገኙት። በውጤቱም ለከተማዋም ሆነ ለህዝቡ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለውን የወንዝ ዳርቻ ልማት መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
በመሰረቱ እነዚህ ሁለቱ መሪዎች ለሚባክን ጊዜ ምንም ጊዜ እንደሌላቸው አብረዋቸው የሰሩ ባልደረቦቻቸውና የስራቸው ውጤት ምስክሮቻቸው ናቸው። ለሚሰሩት ስራ የሰዓት ገደብ የላቸውም፣ ቀን ብቻ ሳይሆን ማታም መደበኛ የስራ ሰዓታቸው ነው። የነበረ አሰራር ከውጤታማነት እንዲጎትታቸው አይፈቅዱም፣ ቀልጣፋና ዘመናዊ አሰራር እውን ማድረግ መርሃቸው ነው። ለጊዜያዊና ወቅታዊ ውዳሴም ሆነ ኩነኔ ጆሮ የላቸውም፣ በምስጋናም ሆነ በእርግማን ከትልቁ መዳረሻቸው እንደማይጎድሉ ተረድተዋል።
እኔ ግን እላችኋለሁ የእነዚህ መሪዎች ትጋት ገፊ ምክንያት ራዕያቸው ነው፣ የእነዚህ መሪዎች ትጋት ገፊ ምክንያት የህዝቡ እምነት ነው። ድህነትን፣ ጉስቁልናን፣ ኋላ ቀርነትን በመፀየፍ፣ የበለፀገችና ተወዳዳሪ ሀገር እውን የማድረግ ራዕይ የትጋታቸው መሰረታዊ ጉልበት ነው። በብዙ እልህ አስጨራሽ ተግዳሮት ውስጥ ቢያልፉም ከስምንት ዓመት በፊት ያዩት እና ዛሬም ህዝቡ በእነርሱ ላይ ያለው የፀና እምነት ለትጋታቸው ተጨማሪ ጉልበት ሆኗቸዋል።
ማህበራዊ ፍትህ የሰፈነባት፣ የበለፀገች፣ ተወዳዳሪና የዜጎችዋ ክብር የተመለሰላት ሀገር እውን እስኪያደርጉ ድረስ እረፍት እንደማይኖራቸው ሰርተው ያመጡት ውጤት ብቻ ሳይሆን ለነገ የሚናገሩት ቃልና የሚገቡት ተስፋ ይመሰክራል። ተናግረው ማድረግን በተግባር ያሳዩ መሆናቸው ደግሞ ራዕያቸውን ለመደገፍና ቃላቸውን ለማመን ምክንያት ይሆናል።
መልዕክት አለኝ:- ራዕያቸው፣ ትጋታቸውና ቁጭታቸው የገባን ቀኝ እጃችንን እንስጣቸው፤ በሌቦች፣ በጽንፈኞችና በስልጣን ጥመኞች ሴራ የተጠራጠርናቸው ደግሞ ረጋ ብለን በስራቸው እንመዝናቸው። ደግሜ የገባኝን እላለሁ እነዚህ መሪዎች መዳረሻቸውን ከመነሻቸው አይተው የተነሱ ናቸውና ራዕያቸውን ሳያሳኩ ለመቆም፣ ለማረፍ፣ ተስፋ ለመቁረጥ ሀሳብም ጊዜም አይኖራቸውም።
ተፃፈ በይመጣል ባህሩ
1 day ago
የተገለጠው እውነታ
በ ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ
በምሥራቃዊው ኢትዮጵያ ይልቁንም በሐረር፣ አርሲና ባሌ አካባቢዎች ላይ ትኩረት አድርጎና አቅዶ ክርስቲያኖችን የሚገድል፣ የሚያፈናቅል እና የሚያሳድድ የአክራሪ ክንፍ መኖሩ ተደጋግሞ ሲነገር ኖሯል። ይህ አካል ደርግ ወድቆ ኢህአዴግ ከተተካበት ጊዜ ጀምሮ ማንኛዋንም የለውጥ፣ የምርጫ እና የመሳሰሉትን የጫና ወቅቶች ጠብቆ አደጋ ያላደረሰበት ጊዜ የለም።
ከተቻለ የመንግሥት መዋቅርን በመጠቀምና በየዘመኑ ያለውን የፖለቲካ ትኩሳት እንደ ጥሩ አጋጣሚ በመጠቀም እና ለሚገድላቸው አካላት ከወቅቱ ፖለቲካ አንጻር የሚስማማ ታርጋ በመስጠት የሚቻለውን ያህል ይገድላል፣ ያፈናቅላል፣ ያሳድዳል።
ይህ የተገለጠ እውነት ነው። ተደጋግሞም ተነግሯል፣ ተገልጿል። ሆኖም እንደዚህ ዘመን እንደ ልቡ ክርስቲያኖችን የሚያጸዳበት ስለመኖሩ ግን አላውቅም። በእኔ እምነት ኢህአዴግ ከመጣበት ጀምሮ የተፈጸሙት ተደምረው በዚህ ዓመት ብቻ የፈጸመውን የመግደልና የማሳደድ ተግባር የሚያክሉ አይመስለኝም። ይህ ሁሉ ሲሆን አንድም መንግሥታዊ ተቋም ሐዘኔታ ሲያሳዩ፣ አንድም አካል ተጠያቂ ሲደረግ ዓይተንም ሰምተንም አናውቅም።
ይህም የተገለጠ እውነት ነው።
ምንም ቢሆን፣ ማንም ቢሆኑ ይህ ሁሉ መከራ የሚደርስባቸው ሰዎች ደግሞም ዜጎች ነበሩ። በደቡብ አፍሪካ ላለው ከሀገራችን ውጡ የሚል ዐመጽ ዜጎቹን ለመከላከል መንግሥት በኢንባሲው በኩል እየሠራ እንደሆነ የሚገልጽ ዜና ከሰማንና ለዚህኛው መንግሥት በዝምታ የሚያልፍ ከሆነ ድርጊቱን የሚፈጽመው እርሱም ጭምር ነው የሚለውን ወቀሳ እውነት ነው ብሎ በአዎንታ እንደተቀበለው ለመረዳት ግዴታችን ጭምር ይሆናል። ይህ በእውነት ከልብ ያሳዝናል።
አንድ የተረጋገጠና የትገለጠ እውነት ደግሞ አለ። የሰው ደም በከንቱ ፈስሶ አይቀርም። እግዚአብሔር የሚባል ተበቃይ አምላክ አለና። ለንስሐ ጊዜ ቢሰጥም "በቀል የእኔ ነው" ያለውና "ከኦሪትና ከነቢያት አንዲት ቃል ከምታልፍ ሰማይና ምድር ቢያልፍ ይቀላል" ያለው አምላክ ቃሉ የታመነ ነውና አይቀርም። እርሱ ሁላችንንም ይቅር ይበለን፣ የመከራውንም ወቅት አሳልፎ ለሰላምና ለፍቅር ያብቃን።
በ ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ
በምሥራቃዊው ኢትዮጵያ ይልቁንም በሐረር፣ አርሲና ባሌ አካባቢዎች ላይ ትኩረት አድርጎና አቅዶ ክርስቲያኖችን የሚገድል፣ የሚያፈናቅል እና የሚያሳድድ የአክራሪ ክንፍ መኖሩ ተደጋግሞ ሲነገር ኖሯል። ይህ አካል ደርግ ወድቆ ኢህአዴግ ከተተካበት ጊዜ ጀምሮ ማንኛዋንም የለውጥ፣ የምርጫ እና የመሳሰሉትን የጫና ወቅቶች ጠብቆ አደጋ ያላደረሰበት ጊዜ የለም።
ከተቻለ የመንግሥት መዋቅርን በመጠቀምና በየዘመኑ ያለውን የፖለቲካ ትኩሳት እንደ ጥሩ አጋጣሚ በመጠቀም እና ለሚገድላቸው አካላት ከወቅቱ ፖለቲካ አንጻር የሚስማማ ታርጋ በመስጠት የሚቻለውን ያህል ይገድላል፣ ያፈናቅላል፣ ያሳድዳል።
ይህ የተገለጠ እውነት ነው። ተደጋግሞም ተነግሯል፣ ተገልጿል። ሆኖም እንደዚህ ዘመን እንደ ልቡ ክርስቲያኖችን የሚያጸዳበት ስለመኖሩ ግን አላውቅም። በእኔ እምነት ኢህአዴግ ከመጣበት ጀምሮ የተፈጸሙት ተደምረው በዚህ ዓመት ብቻ የፈጸመውን የመግደልና የማሳደድ ተግባር የሚያክሉ አይመስለኝም። ይህ ሁሉ ሲሆን አንድም መንግሥታዊ ተቋም ሐዘኔታ ሲያሳዩ፣ አንድም አካል ተጠያቂ ሲደረግ ዓይተንም ሰምተንም አናውቅም።
ይህም የተገለጠ እውነት ነው።
ምንም ቢሆን፣ ማንም ቢሆኑ ይህ ሁሉ መከራ የሚደርስባቸው ሰዎች ደግሞም ዜጎች ነበሩ። በደቡብ አፍሪካ ላለው ከሀገራችን ውጡ የሚል ዐመጽ ዜጎቹን ለመከላከል መንግሥት በኢንባሲው በኩል እየሠራ እንደሆነ የሚገልጽ ዜና ከሰማንና ለዚህኛው መንግሥት በዝምታ የሚያልፍ ከሆነ ድርጊቱን የሚፈጽመው እርሱም ጭምር ነው የሚለውን ወቀሳ እውነት ነው ብሎ በአዎንታ እንደተቀበለው ለመረዳት ግዴታችን ጭምር ይሆናል። ይህ በእውነት ከልብ ያሳዝናል።
አንድ የተረጋገጠና የትገለጠ እውነት ደግሞ አለ። የሰው ደም በከንቱ ፈስሶ አይቀርም። እግዚአብሔር የሚባል ተበቃይ አምላክ አለና። ለንስሐ ጊዜ ቢሰጥም "በቀል የእኔ ነው" ያለውና "ከኦሪትና ከነቢያት አንዲት ቃል ከምታልፍ ሰማይና ምድር ቢያልፍ ይቀላል" ያለው አምላክ ቃሉ የታመነ ነውና አይቀርም። እርሱ ሁላችንንም ይቅር ይበለን፣ የመከራውንም ወቅት አሳልፎ ለሰላምና ለፍቅር ያብቃን።
1 day ago
የአቡነ ሀብተ ማርያም ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏
በነገሥታት ፊት የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ።
የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ገዳም ስትገባ የተቀደሰ ልጅ እንደምትወልድ ተነግሯት የተመለሰችው እናቱ ዮስቲና ትባላለች። ልጅም ሲወልዱ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕገ እግዚአብሔርም አንጸው አሳደጉት።
በቤተ ክርስቲያንም የሰማውን “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የምትል ጸሎት እጅጉን ቢወዳት ሌሊቱን ሙሉ በቤቱ እየጸለያት የሚጋደል ሆነ። አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ ጓደኞቹን “ዝናም ይዘንማልና ወደቤት እንግባ” አላቸው። ቃሉን ሊሰሙት ባይወዱ በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ኃይለኛ ዝናም ዘነመ። ገና በአዳጊነት እድሜውም ብዙ ተአምራት ያደርግ ነበር፡፡
በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር። በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ 500 ጊዜ ይሰግዳል። እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ ጌታችን ተገለጠለት። አቡነ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፡፡
ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ ስለማንበቡ፣ ስለተጋድሎው፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። ከሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትንና ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የብርሃን ሠረገላም ሰጠው፣ መታሰቢያውን የሚያደርጉትን እንደሚምርለትም፣ ቃል ኪዳን ገባለት። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው ስትለይም ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፤ ገዳማቸውን እንደግፍ ከበረከታቸውም እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
በነገሥታት ፊት የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ።
የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ገዳም ስትገባ የተቀደሰ ልጅ እንደምትወልድ ተነግሯት የተመለሰችው እናቱ ዮስቲና ትባላለች። ልጅም ሲወልዱ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕገ እግዚአብሔርም አንጸው አሳደጉት።
በቤተ ክርስቲያንም የሰማውን “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የምትል ጸሎት እጅጉን ቢወዳት ሌሊቱን ሙሉ በቤቱ እየጸለያት የሚጋደል ሆነ። አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ ጓደኞቹን “ዝናም ይዘንማልና ወደቤት እንግባ” አላቸው። ቃሉን ሊሰሙት ባይወዱ በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ኃይለኛ ዝናም ዘነመ። ገና በአዳጊነት እድሜውም ብዙ ተአምራት ያደርግ ነበር፡፡
በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር። በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ 500 ጊዜ ይሰግዳል። እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ ጌታችን ተገለጠለት። አቡነ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፡፡
ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ ስለማንበቡ፣ ስለተጋድሎው፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። ከሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትንና ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የብርሃን ሠረገላም ሰጠው፣ መታሰቢያውን የሚያደርጉትን እንደሚምርለትም፣ ቃል ኪዳን ገባለት። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው ስትለይም ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፤ ገዳማቸውን እንደግፍ ከበረከታቸውም እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
1 day ago
የንጹኃን ደም እየፈሰሰ "መረጃ የለንም" የሚሉ አስተዳዳሪዎች — የመንግሥት መዋቅር የሞራል ክስረት!
በአርሲ ሀገረ ስብከት ሦስት ወረዳዎች ውስጥ የንጹኃን ኦርቶዶክሳውያን ደም በገዛ ቀያቸው እንደ ጎርፍ በፈሰሰበት፣ የ101 ዓመት ታሪካዊ ቤተ ክርስቲያን በደመኛ እሳት በጋየበት እና በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ሜዳ ላይ በተጣሉበት በዚህ አስከፊ ሰዓት፤ የመንግሥት መዋቅር ያሳየው ፍጹም ደንታ ቢስነት እና ቸልተኝነት የኃላፊነት ብቻ ሳይሆን የሞራል ክስረት መድረሱን በግልጽ ያሳያል።
የሟቾች ስም ዝርዝር፣ ዕድሜያቸው እና የተገደሉበት ወረዳ ሳይቀር ተለይቶ በይፋ እየተነገረ ባለበት ሁኔታ፣ የአካባቢው መሪዎች እና የክልሉ ከፍተኛ ባለሥልጣናት "መረጃ የለንም" እና "እናጣራለን" የሚሉ ሰበቦችን ማቅረባቸው በቁስል ላይ እንጨት የመስደድ ያህል አሳፋሪ ድርጊት ነው።
ቢቢሲ ስለደረሰው አረመኔያዊ ጥቃት መረጃ ለመጠየቅ ወደ ኦሮሚያ ክልል ኮሚዩኒክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ እና የክልሉ ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አራርሳ መርዳሳ በተደጋጋሚ ቢደውልም ስልካቸውን ዘግተው መቀመጣቸው፣ የመንግሥት ባለሥልጣናት ዜጎች ሲታረዱ ከተጠያቂነት እና ከሕዝብ ጥያቄ ለመሸሽ የትጥቅ ያህል የሚጠቀሙበት የተለመደ አድርባይነት ማረጋገጫ ነው።
ከሁሉም በላይ ግን፣ ጥቃቱ ከተፈጸመባቸው ግንባር ቀደም ቀጠናዎች አንዱ በሆነው በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ የገዛ ነዋሪዎቹ እነ አቶ ንጉሱ ማንደፍሮ እና አቶ በቀለ ኃ/ሚካኤል ተለይተው ሲታረዱ፣ የወረዳው አስተዳዳሪ ሐሰን መሐመድ "መረጃ የለንም" ማለታቸው ፍጹም የሚያስጠይቅና የሚያስቆጣ ነው።
እዚህ ላይ በግልጽ ሊጠየቁ የሚገቡ ጠንከር ያሉ ጥያቄዎች አሉ፦
አንድ የወረዳ አስተዳዳሪ የገዛ ወረዳው ነዋሪዎች ተለይተው ሲታረዱና አብያተ ክርስቲያናት ሲጋዩ መረጃ ከሌለው፣ የዚህ አስተዳዳሪና የመዋቅሩ ጥቅሙ ምንድን ነው? ወንበሩ ላይ የተቀመጠው ሕዝብን ለመጠበቅ ነው ወይስ ሬሳ ለመቁጠር?
የአርሲ ዞን ኮሚዩኒኬሽን ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሶሪ ወጊ "እስከአሁን የደረሰን መረጃ የለም" ሲሉ፣ ይህ የዞን መዋቅር ከሕዝቡ ሰቆቃ እና ከገዳዮች እኩል ርቀት ላይ መሆኑን እያመኑ አይደለምን?
የንጹኃን ደም እየጮኸ፣ እናቶች ጽላት አቅፈው በየበርሃው እየተሰደዱ ባሉበት አንገብጋቢ ወቅት፣ መረጃን ለመሸሸግ መሞከር ገዳዮችን በተዘዋዋሪ ከማበረታታት አይተናነስም። ዜጎችን ከጥቃት መከላከል ያልቻለ መዋቅር፣ ቢያንስ የደረሰውን ጥፋት አምኖ በአስቸኳይ ፍትሕ ከመስጠት ይልቅ "አላወቅንም" በሚል ድንቁርና ራሱን ነፃ ለማውጣት መሞከሩ በታሪክም በሕግም የሚያስጠይቅ ከባድ የቅሌት ማህተም ነው።
በአርሲ ሀገረ ስብከት ሦስት ወረዳዎች ውስጥ የንጹኃን ኦርቶዶክሳውያን ደም በገዛ ቀያቸው እንደ ጎርፍ በፈሰሰበት፣ የ101 ዓመት ታሪካዊ ቤተ ክርስቲያን በደመኛ እሳት በጋየበት እና በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ሜዳ ላይ በተጣሉበት በዚህ አስከፊ ሰዓት፤ የመንግሥት መዋቅር ያሳየው ፍጹም ደንታ ቢስነት እና ቸልተኝነት የኃላፊነት ብቻ ሳይሆን የሞራል ክስረት መድረሱን በግልጽ ያሳያል።
የሟቾች ስም ዝርዝር፣ ዕድሜያቸው እና የተገደሉበት ወረዳ ሳይቀር ተለይቶ በይፋ እየተነገረ ባለበት ሁኔታ፣ የአካባቢው መሪዎች እና የክልሉ ከፍተኛ ባለሥልጣናት "መረጃ የለንም" እና "እናጣራለን" የሚሉ ሰበቦችን ማቅረባቸው በቁስል ላይ እንጨት የመስደድ ያህል አሳፋሪ ድርጊት ነው።
ቢቢሲ ስለደረሰው አረመኔያዊ ጥቃት መረጃ ለመጠየቅ ወደ ኦሮሚያ ክልል ኮሚዩኒክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ እና የክልሉ ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አራርሳ መርዳሳ በተደጋጋሚ ቢደውልም ስልካቸውን ዘግተው መቀመጣቸው፣ የመንግሥት ባለሥልጣናት ዜጎች ሲታረዱ ከተጠያቂነት እና ከሕዝብ ጥያቄ ለመሸሽ የትጥቅ ያህል የሚጠቀሙበት የተለመደ አድርባይነት ማረጋገጫ ነው።
ከሁሉም በላይ ግን፣ ጥቃቱ ከተፈጸመባቸው ግንባር ቀደም ቀጠናዎች አንዱ በሆነው በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ የገዛ ነዋሪዎቹ እነ አቶ ንጉሱ ማንደፍሮ እና አቶ በቀለ ኃ/ሚካኤል ተለይተው ሲታረዱ፣ የወረዳው አስተዳዳሪ ሐሰን መሐመድ "መረጃ የለንም" ማለታቸው ፍጹም የሚያስጠይቅና የሚያስቆጣ ነው።
እዚህ ላይ በግልጽ ሊጠየቁ የሚገቡ ጠንከር ያሉ ጥያቄዎች አሉ፦
አንድ የወረዳ አስተዳዳሪ የገዛ ወረዳው ነዋሪዎች ተለይተው ሲታረዱና አብያተ ክርስቲያናት ሲጋዩ መረጃ ከሌለው፣ የዚህ አስተዳዳሪና የመዋቅሩ ጥቅሙ ምንድን ነው? ወንበሩ ላይ የተቀመጠው ሕዝብን ለመጠበቅ ነው ወይስ ሬሳ ለመቁጠር?
የአርሲ ዞን ኮሚዩኒኬሽን ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሶሪ ወጊ "እስከአሁን የደረሰን መረጃ የለም" ሲሉ፣ ይህ የዞን መዋቅር ከሕዝቡ ሰቆቃ እና ከገዳዮች እኩል ርቀት ላይ መሆኑን እያመኑ አይደለምን?
የንጹኃን ደም እየጮኸ፣ እናቶች ጽላት አቅፈው በየበርሃው እየተሰደዱ ባሉበት አንገብጋቢ ወቅት፣ መረጃን ለመሸሸግ መሞከር ገዳዮችን በተዘዋዋሪ ከማበረታታት አይተናነስም። ዜጎችን ከጥቃት መከላከል ያልቻለ መዋቅር፣ ቢያንስ የደረሰውን ጥፋት አምኖ በአስቸኳይ ፍትሕ ከመስጠት ይልቅ "አላወቅንም" በሚል ድንቁርና ራሱን ነፃ ለማውጣት መሞከሩ በታሪክም በሕግም የሚያስጠይቅ ከባድ የቅሌት ማህተም ነው።
1 day ago
በትራምፕ እና በኔታንያሁ መካከል የተካሄደው የቁጣ ስልክ ጥሪ
“ምንድነው የምታደርገው?” ትራምፕ
ኢራን በእስራኤል የሊባኖስ ዘመቻ ምክንያት ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን ንግግር እንደምታቋርጥ ከተናገረች በኋላ፣ በሁለቱ መሪዎች መካከል የቁጣ የስልክ ጥሪ ልውውጥ መደረጉ ተነገረ
ዶናልድ ትራምፕ ቤሩት ደቡባዊ የከተማ ዳርቻዎች ላይ የአየር ጥቃት ለመጀመር በመዛቱ ምክንያት የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁን በቁጣ መጋፈጣቸውን አንድ ዘገባ አመልክቷል።
በሁለቱ መሪዎች መካከል የሚደረጉ ከፍተኛ የደረጃ ውይይቶችን በተደጋጋሚ ይፋ የሚያደርገው ‘አክሲዮስ’ የተሰኘው የአሜሪካ ድረ-ገጽ እንደዘገበው፤ ሰኞ ዕለት በተደረገው የስልክ ጥሪ ላይ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ላይ “ምንድነው የምታደርገው?” በማለት በቁጣ ጮኸውባቸዋል።
በእስራኤል መገናኛ ብዙሃን መካድ የገጠመው ይህ ዘገባ፣ አንድ የአሜሪካ ባለስልጣን ትራምፕ ለኔታንያሁ የተናገሩትን ሲያጠቃልሉ፦ **“አብደሃል። እኔ ባልኖር ኖሮ አሁን እስር ቤት ነበርክ። እኔ ነኝ እያዳንኩህ ያለሁት። አሁን ሁሉም ሰው ይጠላሃል። በዚህ ምክንያት ሁሉም ሰው እስራኤልን እየጠላት ነው”ማለታቸውን ጠቅሷል።
የስልክ ጥሪው የተደረገው ኔታንያሁ የእስራኤል ጦር ወደ እስራኤል የድሮን ጥቃቶችን ለሰነዘረውና በኢራን ለሚደገፈው የሂዝቦላ ሚሊሺያ ኢላማ ለማድረግ በቤሩት ደቡባዊ ዳሂያ አካባቢ ላይ የቦምብ ጥቃት እንዲጀምር ትዕዛዝ ከሰጡ በኋላ ነው።
የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት በደቡብ ቤሩት የሚኖሩ የሊባኖስ ሲቪሎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ማሳሰቢያ የሰጠ ሲሆን፣ ይህንን ተከትሎም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተሰደዋል።
ኢራን ማክሰኞ ዕለት በሰጠችው መግለጫ፤ እስራኤል በደቡብ ሊባኖስ እያካሄደች ባለው ዘመቻ ምክንያት ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን የሰላም ንግግር እንደምታቋርጥ አስታውቃለች።
ቴህራን የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥን ለመክፈትና አሜሪካ በኢራን ወደቦች ላይ የጣለችውን እገዳ ለማንሳት የሚደረጉ ድርድሮችን ለማመቻቸት ሲባል፣ ሊባኖስም የተኩስ አቁም ስምምነቱ አካል መሆን አለባት ስትል ሞግታለች።
በኮንትሮባንድና የንግግር ማቋረጥ ዙሪያ የተሰማው ይህ መግለጫ፤ ትራምፕ ተደራዳሪዎች ሊፈርሙበት የሚችሉትን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውንና እሳቸውም ለመፈረም እያሰቡበት መሆኑን ከተናገሩ ከጥቂት ቀናት በኋላ የተሰማ ሲሆን፣ በሁለቱ መሪዎች መካከል የተደረገው የስልክ ጥሪም ይህንን ተከትሎ የመጣ ነው።
ቻናል 12 (Channel 12) የተሰኘው ታዋቂና ገለልተኛ የእስራኤል የዜና አውታር ግን የጥሪውን ዝርዝር መረጃ አስተባብሏል። የጣቢያው ዋና የፖለቲካ ተንታኝ አሚት ሴጋል እንዳለው፤ ትራምፕ በኔታንያሁ ላይ ግላዊ ጥቃት እንዳልሰነዘሩና ሁለቱ መሪዎች ሂዝቦላ በእስራኤል ላይ የሚያደርገውን ጥቃት ካቆመ፣ እስራኤልም በቤሩት የከተማ ዳርቻዎች ላይ ጥቃት ከመሰንዘር እንድትቆጠብ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ገልጿል።
በኔታንያሁ እና በትራምፕ ጥምረት መካከል የተፈጠረው ውጥረት
ምንም እንኳን እስራኤል በአካባቢው የአሜሪካ ዋና አጋር ሆና ብትቀጥልም እና ሁለቱ መሪዎች በየካቲት ወር በኔታንያሁ ግፊት በኢራን ላይ በጋራ ጥቃት ቢሰነዝሩም፣ ትራምፕና ኔታንያሁ ባለፈው ጊዜ የሻከረ ግንኙነት ነበራቸው።
ትራምፕ ባለፈው ዓመት የአየር ኃይል፣ ሚሳኤሎችና ድሮኖችን ያካተተ የ12 ቀናት የጋራ ጥቃት ልውውጥ በተደረገበት ወቅት ኢራን እና እስራኤል ምን እያደረጉ እንደሆነ አያውቁም በማለት በይፋ ተቆጥተው ነበር።
ኔታንያሁ ጆ ባይደንን በ2020 ትራምፕ በተቃወሙት ምርጫ ማሸነፋቸውን ተከትሎ የእንኳን አደረሰህ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ፣ ትራምፕ ስለ ኔታንያሁ ሲናገሩ ጠንከር ያለ የስድብ ቃል ተጠቅመው ነበር።
ትራምፕ ከተለያዩ የሪፐብሊካን ፓርቲ ክፍሎች ጫና እየገጠማቸው ነው። ለአይሁድ ደጋፊ የሆኑ አጋሮቻቸው አሜሪካ ከኢራን ጋር ባላት ግጭት የበለጠ እንድትገፋበት ሲጠይቁ፣ ሌሎች ደግሞ ከኖቬምበር የዩኤስ የአጋማሽ ዘመን ምርጫ በፊት የሚደርሰውን ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ለመቀነስ ጦርነቱ በአስቸኳይ እንዲያበቃ ይፈልጋሉ።
ከትራምፕ ጋር የሚነጋገረውና ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆነው ፕሮ-እስራኤል የቶክ ሾው አቅራቢ ማርክ ሌቪን እንደጻፈው፤ “የኢራን አገዛዝ ከዚህ መረጃ መውጣት (Leak) ተጠቃሚ ይሆናል፣ እኛን ደካማና ለስምምነት የምንቸኩል አድርጎ ይመለከተናል - አልፎ ተርፎም ለሂዝቦላ ጥበቃ እንደመቆም ይቆጥረዋል” ብሏል።
ኔታንያሁም ቢሆኑ በፖለቲካዊ ጫና ውስጥ ናቸው።
የእስራኤል ፓርላማ በዚህ ሳምንት ክኔሴትን (Knesset) ለመበተን እና ቅድመ ምርጫ ለመጥራት የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ በመጀመሪያ ንባብ የደገፈው ሲሆን፣ በእስራኤል የደህንነት ሁኔታ ምክንያት በተደጋጋሚ ተራዝሞ የነበረው የሙስና ክስ ችሎታቸውም እንዲቀጥል ቀጠሮ ተይዟል።
“ምንድነው የምታደርገው?” ትራምፕ
ኢራን በእስራኤል የሊባኖስ ዘመቻ ምክንያት ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን ንግግር እንደምታቋርጥ ከተናገረች በኋላ፣ በሁለቱ መሪዎች መካከል የቁጣ የስልክ ጥሪ ልውውጥ መደረጉ ተነገረ
ዶናልድ ትራምፕ ቤሩት ደቡባዊ የከተማ ዳርቻዎች ላይ የአየር ጥቃት ለመጀመር በመዛቱ ምክንያት የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁን በቁጣ መጋፈጣቸውን አንድ ዘገባ አመልክቷል።
በሁለቱ መሪዎች መካከል የሚደረጉ ከፍተኛ የደረጃ ውይይቶችን በተደጋጋሚ ይፋ የሚያደርገው ‘አክሲዮስ’ የተሰኘው የአሜሪካ ድረ-ገጽ እንደዘገበው፤ ሰኞ ዕለት በተደረገው የስልክ ጥሪ ላይ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ላይ “ምንድነው የምታደርገው?” በማለት በቁጣ ጮኸውባቸዋል።
በእስራኤል መገናኛ ብዙሃን መካድ የገጠመው ይህ ዘገባ፣ አንድ የአሜሪካ ባለስልጣን ትራምፕ ለኔታንያሁ የተናገሩትን ሲያጠቃልሉ፦ **“አብደሃል። እኔ ባልኖር ኖሮ አሁን እስር ቤት ነበርክ። እኔ ነኝ እያዳንኩህ ያለሁት። አሁን ሁሉም ሰው ይጠላሃል። በዚህ ምክንያት ሁሉም ሰው እስራኤልን እየጠላት ነው”ማለታቸውን ጠቅሷል።
የስልክ ጥሪው የተደረገው ኔታንያሁ የእስራኤል ጦር ወደ እስራኤል የድሮን ጥቃቶችን ለሰነዘረውና በኢራን ለሚደገፈው የሂዝቦላ ሚሊሺያ ኢላማ ለማድረግ በቤሩት ደቡባዊ ዳሂያ አካባቢ ላይ የቦምብ ጥቃት እንዲጀምር ትዕዛዝ ከሰጡ በኋላ ነው።
የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት በደቡብ ቤሩት የሚኖሩ የሊባኖስ ሲቪሎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ማሳሰቢያ የሰጠ ሲሆን፣ ይህንን ተከትሎም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተሰደዋል።
ኢራን ማክሰኞ ዕለት በሰጠችው መግለጫ፤ እስራኤል በደቡብ ሊባኖስ እያካሄደች ባለው ዘመቻ ምክንያት ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን የሰላም ንግግር እንደምታቋርጥ አስታውቃለች።
ቴህራን የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥን ለመክፈትና አሜሪካ በኢራን ወደቦች ላይ የጣለችውን እገዳ ለማንሳት የሚደረጉ ድርድሮችን ለማመቻቸት ሲባል፣ ሊባኖስም የተኩስ አቁም ስምምነቱ አካል መሆን አለባት ስትል ሞግታለች።
በኮንትሮባንድና የንግግር ማቋረጥ ዙሪያ የተሰማው ይህ መግለጫ፤ ትራምፕ ተደራዳሪዎች ሊፈርሙበት የሚችሉትን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውንና እሳቸውም ለመፈረም እያሰቡበት መሆኑን ከተናገሩ ከጥቂት ቀናት በኋላ የተሰማ ሲሆን፣ በሁለቱ መሪዎች መካከል የተደረገው የስልክ ጥሪም ይህንን ተከትሎ የመጣ ነው።
ቻናል 12 (Channel 12) የተሰኘው ታዋቂና ገለልተኛ የእስራኤል የዜና አውታር ግን የጥሪውን ዝርዝር መረጃ አስተባብሏል። የጣቢያው ዋና የፖለቲካ ተንታኝ አሚት ሴጋል እንዳለው፤ ትራምፕ በኔታንያሁ ላይ ግላዊ ጥቃት እንዳልሰነዘሩና ሁለቱ መሪዎች ሂዝቦላ በእስራኤል ላይ የሚያደርገውን ጥቃት ካቆመ፣ እስራኤልም በቤሩት የከተማ ዳርቻዎች ላይ ጥቃት ከመሰንዘር እንድትቆጠብ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ገልጿል።
በኔታንያሁ እና በትራምፕ ጥምረት መካከል የተፈጠረው ውጥረት
ምንም እንኳን እስራኤል በአካባቢው የአሜሪካ ዋና አጋር ሆና ብትቀጥልም እና ሁለቱ መሪዎች በየካቲት ወር በኔታንያሁ ግፊት በኢራን ላይ በጋራ ጥቃት ቢሰነዝሩም፣ ትራምፕና ኔታንያሁ ባለፈው ጊዜ የሻከረ ግንኙነት ነበራቸው።
ትራምፕ ባለፈው ዓመት የአየር ኃይል፣ ሚሳኤሎችና ድሮኖችን ያካተተ የ12 ቀናት የጋራ ጥቃት ልውውጥ በተደረገበት ወቅት ኢራን እና እስራኤል ምን እያደረጉ እንደሆነ አያውቁም በማለት በይፋ ተቆጥተው ነበር።
ኔታንያሁ ጆ ባይደንን በ2020 ትራምፕ በተቃወሙት ምርጫ ማሸነፋቸውን ተከትሎ የእንኳን አደረሰህ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ፣ ትራምፕ ስለ ኔታንያሁ ሲናገሩ ጠንከር ያለ የስድብ ቃል ተጠቅመው ነበር።
ትራምፕ ከተለያዩ የሪፐብሊካን ፓርቲ ክፍሎች ጫና እየገጠማቸው ነው። ለአይሁድ ደጋፊ የሆኑ አጋሮቻቸው አሜሪካ ከኢራን ጋር ባላት ግጭት የበለጠ እንድትገፋበት ሲጠይቁ፣ ሌሎች ደግሞ ከኖቬምበር የዩኤስ የአጋማሽ ዘመን ምርጫ በፊት የሚደርሰውን ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ለመቀነስ ጦርነቱ በአስቸኳይ እንዲያበቃ ይፈልጋሉ።
ከትራምፕ ጋር የሚነጋገረውና ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆነው ፕሮ-እስራኤል የቶክ ሾው አቅራቢ ማርክ ሌቪን እንደጻፈው፤ “የኢራን አገዛዝ ከዚህ መረጃ መውጣት (Leak) ተጠቃሚ ይሆናል፣ እኛን ደካማና ለስምምነት የምንቸኩል አድርጎ ይመለከተናል - አልፎ ተርፎም ለሂዝቦላ ጥበቃ እንደመቆም ይቆጥረዋል” ብሏል።
ኔታንያሁም ቢሆኑ በፖለቲካዊ ጫና ውስጥ ናቸው።
የእስራኤል ፓርላማ በዚህ ሳምንት ክኔሴትን (Knesset) ለመበተን እና ቅድመ ምርጫ ለመጥራት የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ በመጀመሪያ ንባብ የደገፈው ሲሆን፣ በእስራኤል የደህንነት ሁኔታ ምክንያት በተደጋጋሚ ተራዝሞ የነበረው የሙስና ክስ ችሎታቸውም እንዲቀጥል ቀጠሮ ተይዟል።
1 day ago
ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ብሔራዊ የንግድ ፖሊሲ አጸደቀች
ኢትዮጵያ ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ የዘለቀውን የተበታተነ የንግድ አስተዳደር ሥርዓት ለመቀየርና ለላኪዎች፣ አስመጪዎችና ባለሀብቶች ግልጽና ሊተነበይ የሚችል አሠራር ለመፍጠር የሚያስችላትን የመጀመሪያውን ብሔራዊ የንግድ ፖሊሲ አጸደቀች።
በተጠናቀቀው ሳምንት በሚኒስትሮች ምክርቤት የጸደቀው ይህ ፖሊሲ፣ ለበርካታ አስርት ዓመታት የሀገሪቱን የንግድ ዘርፍ ተወዳዳሪነት ሲያዳክሙና ለብልሹ አሠራር በር ሲከፍቱ የቆዩትን እርስ በርሳቸው የሚጋጩ መመሪያዎችንና አሠራሮችን ሙሉ በሙሉ የሚተካ ነው።
የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ እንደገለጹት፣ አዲሱ ማዕቀፍ በተደጋጋሚ ለሚቀያየሩ መመሪያዎች እውቅና የማይሰጥ በመሆኑ በንግድ ቁጥጥር ሥርዓቱ ላይ መረጋጋት፣ ግልጽነትና ተጠያቂነትን ያሰፍናል።
ፖሊሲው የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ከለመደው ያልተቀነባበሩ የግብርና ምርቶች ኤክስፖርት ጥገኝነት በማውጣት፣ ወደ ማኑፋክቸሪንግ፣ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶች፣ አገልግሎቶችና ቱሪዝም ዘርፎች ላይ እንዲያተኩር ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተጠቁሟል።
የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት የንግድ ልማት አገልግሎትና ፖሊሲ ጥበቃ ምክትል ዋና ጸሐፊ አቶ ካሳሁን ማሞ፣ ምክር ቤቱ እንዲህ ዓይነት ሁሉን አቀፍ ፖሊሲ እንዲወጣ ለረጅም ጊዜ ሲወተውት እንደነበር አስታውሰዋል። ፖሊሲው የግል ባለሀብቱ በልበ ሙሉነት እንዲያቅድና ኢንቨስት እንዲያደርግ የሚያግዝ መሆኑን አስረድተዋል።
Via capital
ኢትዮጵያ ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ የዘለቀውን የተበታተነ የንግድ አስተዳደር ሥርዓት ለመቀየርና ለላኪዎች፣ አስመጪዎችና ባለሀብቶች ግልጽና ሊተነበይ የሚችል አሠራር ለመፍጠር የሚያስችላትን የመጀመሪያውን ብሔራዊ የንግድ ፖሊሲ አጸደቀች።
በተጠናቀቀው ሳምንት በሚኒስትሮች ምክርቤት የጸደቀው ይህ ፖሊሲ፣ ለበርካታ አስርት ዓመታት የሀገሪቱን የንግድ ዘርፍ ተወዳዳሪነት ሲያዳክሙና ለብልሹ አሠራር በር ሲከፍቱ የቆዩትን እርስ በርሳቸው የሚጋጩ መመሪያዎችንና አሠራሮችን ሙሉ በሙሉ የሚተካ ነው።
የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ እንደገለጹት፣ አዲሱ ማዕቀፍ በተደጋጋሚ ለሚቀያየሩ መመሪያዎች እውቅና የማይሰጥ በመሆኑ በንግድ ቁጥጥር ሥርዓቱ ላይ መረጋጋት፣ ግልጽነትና ተጠያቂነትን ያሰፍናል።
ፖሊሲው የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ከለመደው ያልተቀነባበሩ የግብርና ምርቶች ኤክስፖርት ጥገኝነት በማውጣት፣ ወደ ማኑፋክቸሪንግ፣ እሴት የተጨመረባቸው ምርቶች፣ አገልግሎቶችና ቱሪዝም ዘርፎች ላይ እንዲያተኩር ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተጠቁሟል።
የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት የንግድ ልማት አገልግሎትና ፖሊሲ ጥበቃ ምክትል ዋና ጸሐፊ አቶ ካሳሁን ማሞ፣ ምክር ቤቱ እንዲህ ዓይነት ሁሉን አቀፍ ፖሊሲ እንዲወጣ ለረጅም ጊዜ ሲወተውት እንደነበር አስታውሰዋል። ፖሊሲው የግል ባለሀብቱ በልበ ሙሉነት እንዲያቅድና ኢንቨስት እንዲያደርግ የሚያግዝ መሆኑን አስረድተዋል።
Via capital
Sponsored by
Surafel
2 days ago
በአርሲ ሀገረ ስብከት በደረሰ ጥቃት የ13 ሰዎች ሕይወት አለፈ የአንድ ክፍለ ዘመን ዕድሜ ያለው ቤተ ክርስቲያንም ወደመ
የአርሲ ሀገረ ስብከት ሚዲያን ጠቅሶ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ጥቃቱ የተፈጸመው ከግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአሰኮ፣ በሺርካ እና በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳዎች ላይ ነው። በጥቃቱ ሳቢያ የ101 ዓመት ዕድሜ ያለው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት የፈረሰ ሲሆን፣ በካራ ኩፍተና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ላይ ደግሞ ከፍተኛ ዘረፋ ተፈጽሟል። በዚህም ምክንያት ምእመናን የቤተ ክርስቲያኑን ጽላት ይዘው ለመሰደድ ተገድደዋል።
ብፁዕነታቸው እንደገለጹት፣ በጥቃቱ ሳቢያ በአሰኮ ወረዳ ብቻ ከ280 በላይ ሰዎች ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉ ሲሆን፣ የነዋሪዎች መኖሪያ ቤቶች ተቃጥለዋል፤ ከብቶቻቸውና ንብረቶቻቸውም ተዘርፈዋል።
"ኦርቶዶክሳውያኑ ተወልደው ካደጉበት፣ ወልደው ከሳሙበት ቀያቸው በማንነታቸውና በሃይማኖታቸው ብቻ እየተለዩ ጥቃት ደርሶባቸዋል" ያሉት ሊቀ ጳጳሱ፣ ከጥቃቱ የተረፉት ነዋሪዎች ይዘውት የሸሹት እምነታቸውን ብቻ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት ሜዳ ላይ ወድቀው ለከፍተኛ ችግር መጋለጣቸውን ጠቁመዋል።
በተፈጸመው በዚህ ጥቃት ሕይወታቸውን ያጡት 13ቱ ሰዎች ስም ዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል፦
1. አቶ ደምረው አበራ (የ70 ዓመት)
2. አቶ ከፈለኝ ልክየለው (የ56 ዓመት)
3. አቶ ሐይሉ ንጉሴ (የ70 ዓመት)
4. አቶ እሸቴ ዳመና (የ42 ዓመት)
5. አቶ አበባየሁ ዳኜ (የ42 ዓመት)
6. አቶ ሰሙ አባይነህ (የ70 ዓመት)
7. ስማቸው ያልተጠቀሰ 1 የአካባቢው ሚሊሻ
8. አቶ አማረ በላይነህ (የ80 ዓመት)
9. ተሬ ደሴ (የ25 ዓመት)
10. ወጣት ገነነ ጥላሁን (በሺርካ ወረዳ)
11. ሙርቴሳ ጥላሁን (በሺርካ ወረዳ)
12. አቶ ንጉሱ ማንደፍሮ (በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ)
13. አቶ በቀለ ኃ/ሚካኤል (በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ)
ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ በተፈጸመው አረመኔያዊ ድርጊት የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን በመግለጽ፣ "የሞቱትን ወገኖቻችንን እግዚአብሔር አምላክ ነፍሳቸውን በመንግሥተ ሰማያት ያሳርፍልን፤ ያዘኑትን እና በሜዳ ላይ ወድቀው የሚገኙትን የተፈናቀሉ ወገኖቻችንን እግዚአብሔር ያጽናናልን" ሲሉ የጸሎትና የማጽናኛ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
የአርሲ ሀገረ ስብከት ሚዲያን ጠቅሶ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ጥቃቱ የተፈጸመው ከግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአሰኮ፣ በሺርካ እና በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳዎች ላይ ነው። በጥቃቱ ሳቢያ የ101 ዓመት ዕድሜ ያለው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት የፈረሰ ሲሆን፣ በካራ ኩፍተና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ላይ ደግሞ ከፍተኛ ዘረፋ ተፈጽሟል። በዚህም ምክንያት ምእመናን የቤተ ክርስቲያኑን ጽላት ይዘው ለመሰደድ ተገድደዋል።
ብፁዕነታቸው እንደገለጹት፣ በጥቃቱ ሳቢያ በአሰኮ ወረዳ ብቻ ከ280 በላይ ሰዎች ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉ ሲሆን፣ የነዋሪዎች መኖሪያ ቤቶች ተቃጥለዋል፤ ከብቶቻቸውና ንብረቶቻቸውም ተዘርፈዋል።
"ኦርቶዶክሳውያኑ ተወልደው ካደጉበት፣ ወልደው ከሳሙበት ቀያቸው በማንነታቸውና በሃይማኖታቸው ብቻ እየተለዩ ጥቃት ደርሶባቸዋል" ያሉት ሊቀ ጳጳሱ፣ ከጥቃቱ የተረፉት ነዋሪዎች ይዘውት የሸሹት እምነታቸውን ብቻ በመሆኑ በአሁኑ ወቅት ሜዳ ላይ ወድቀው ለከፍተኛ ችግር መጋለጣቸውን ጠቁመዋል።
በተፈጸመው በዚህ ጥቃት ሕይወታቸውን ያጡት 13ቱ ሰዎች ስም ዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል፦
1. አቶ ደምረው አበራ (የ70 ዓመት)
2. አቶ ከፈለኝ ልክየለው (የ56 ዓመት)
3. አቶ ሐይሉ ንጉሴ (የ70 ዓመት)
4. አቶ እሸቴ ዳመና (የ42 ዓመት)
5. አቶ አበባየሁ ዳኜ (የ42 ዓመት)
6. አቶ ሰሙ አባይነህ (የ70 ዓመት)
7. ስማቸው ያልተጠቀሰ 1 የአካባቢው ሚሊሻ
8. አቶ አማረ በላይነህ (የ80 ዓመት)
9. ተሬ ደሴ (የ25 ዓመት)
10. ወጣት ገነነ ጥላሁን (በሺርካ ወረዳ)
11. ሙርቴሳ ጥላሁን (በሺርካ ወረዳ)
12. አቶ ንጉሱ ማንደፍሮ (በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ)
13. አቶ በቀለ ኃ/ሚካኤል (በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ)
ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ በተፈጸመው አረመኔያዊ ድርጊት የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን በመግለጽ፣ "የሞቱትን ወገኖቻችንን እግዚአብሔር አምላክ ነፍሳቸውን በመንግሥተ ሰማያት ያሳርፍልን፤ ያዘኑትን እና በሜዳ ላይ ወድቀው የሚገኙትን የተፈናቀሉ ወገኖቻችንን እግዚአብሔር ያጽናናልን" ሲሉ የጸሎትና የማጽናኛ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
2 days ago
ይቺም ሻማ ሰልችታለች!
===============
በአገራችን ለሚቀጥሉት ብዙ አሥርት ዓመታት ምናልባትም አሁን በሕይወት የምንገኝ ሰዎች በአጠቃላይ ሳናይ የምንሞተው ነገር የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ''ኃላፊነቴን በአግባቡ ስላልተወጣሁ ሥራዬን በፈቃዴ ለቅቄያለሁ፤ ከ'ኔ የተሻለ ሰው ይምራው'' የሚለው ነው።
በአርሲ ዞን በኦርቶዶክስ ክርስትና አማኞች እና አብያተ-ክርስትያናት ላይ በተደጋጋሚ ጥቃቶች እየተሰነዘሩ ብዙ ሰው በአሰቃቂ ሁኔታ ሞተ፤ አብያተ-ክርስትያናት እና ቅርሶችም ወደሙ፤ በነዋሪዎቹ ዘንድ ሥጋትና ጥርጣሬ ሰፈነ።
ይሄን ተደጋጋሚ ጥቃት ለማስቀረት የተሠራ ሥራ አለ? ሰላም ማስከበር 100% የክልሉ መንግሥት ሥራ አይደለም እንዴ? ምን አድርጓል? ሰላም ማስከበር ካቃታቸው በኢትዮጵያ ሕግ መሠረት ''አልቻልንም፤ የፌዴራል መንግሥት ጣልቃ ይግባልን'' ይባላል እኮ! መቼም ''እኔ ለዚህ ኃላፊነት ብቁ ሆኜ አልተገኘሁም፤ የተሻለ ብስለትና ልምድ ያለው ሰው ይተካኝ'' የሚሉ ኃላፊዎችን በሕይወት እያለን እንደማናይ ዕሙን ነው።
ሰው ባለቀ ቁጥር ይቺን ሻማ ብልጭ ማድረግ ምን ፋይዳ አለው? ይሰለቻል። የክልሉ መንግሥት ለዚህ ዞን ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ሕዝቡን ይጠብቅ። በጊዜ መፍትሔ ካልተሰጠው የዚህ ዳፋ የማይተርፈው ሰው የለም።
እንደ አንድ ተርታ ዜጋ በደረሰው ጉዳት ሐዘኔን ለመግለጽ እወዳለሁ። 😥
Awlet Ahmed
===============
በአገራችን ለሚቀጥሉት ብዙ አሥርት ዓመታት ምናልባትም አሁን በሕይወት የምንገኝ ሰዎች በአጠቃላይ ሳናይ የምንሞተው ነገር የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ''ኃላፊነቴን በአግባቡ ስላልተወጣሁ ሥራዬን በፈቃዴ ለቅቄያለሁ፤ ከ'ኔ የተሻለ ሰው ይምራው'' የሚለው ነው።
በአርሲ ዞን በኦርቶዶክስ ክርስትና አማኞች እና አብያተ-ክርስትያናት ላይ በተደጋጋሚ ጥቃቶች እየተሰነዘሩ ብዙ ሰው በአሰቃቂ ሁኔታ ሞተ፤ አብያተ-ክርስትያናት እና ቅርሶችም ወደሙ፤ በነዋሪዎቹ ዘንድ ሥጋትና ጥርጣሬ ሰፈነ።
ይሄን ተደጋጋሚ ጥቃት ለማስቀረት የተሠራ ሥራ አለ? ሰላም ማስከበር 100% የክልሉ መንግሥት ሥራ አይደለም እንዴ? ምን አድርጓል? ሰላም ማስከበር ካቃታቸው በኢትዮጵያ ሕግ መሠረት ''አልቻልንም፤ የፌዴራል መንግሥት ጣልቃ ይግባልን'' ይባላል እኮ! መቼም ''እኔ ለዚህ ኃላፊነት ብቁ ሆኜ አልተገኘሁም፤ የተሻለ ብስለትና ልምድ ያለው ሰው ይተካኝ'' የሚሉ ኃላፊዎችን በሕይወት እያለን እንደማናይ ዕሙን ነው።
ሰው ባለቀ ቁጥር ይቺን ሻማ ብልጭ ማድረግ ምን ፋይዳ አለው? ይሰለቻል። የክልሉ መንግሥት ለዚህ ዞን ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ሕዝቡን ይጠብቅ። በጊዜ መፍትሔ ካልተሰጠው የዚህ ዳፋ የማይተርፈው ሰው የለም።
እንደ አንድ ተርታ ዜጋ በደረሰው ጉዳት ሐዘኔን ለመግለጽ እወዳለሁ። 😥
Awlet Ahmed
2 days ago
ፋይዳን ከባንክ ሂሳብ ጋር ለማስተሳሰር የነበሩ ሰልፎችን ማስቀረት እንደተቻለ ተገለጸ
ፋይዳ መታወቂያን ከባንክ የሂሳብ ጋር ለማስተሳስር የነበረው ሰልፍ እና መጉላላት በተገልጋይዎች ዘንድ ቅሬታን ፈጥሮ እንደነበር ይታወቃል፡፡
ከፋይዳ መታወቂያ ጋር በተገናኘ ባንኮች ላይ የነበሩ ሰልፎችን በማስቀረትና የሚቀርቡ ጥያቄዎችን በፍጥነት ምላሽ በመስጠት በአሁኑ ወቅት የባንክ ሂሳብን ከፋይዳ ጋር የማስተሳሰር ሂደቱ መሻሻል የታየበት መሆኑ ተገልጾዋል፡፡
የባንክ ሂሳብን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ማስተሳሰር በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም መጀመሩን ያስታወሱት የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የባለድርሻ አካላትና የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ሳሚናስ ሰይፉ ናቸው።
ባንኮች ከሚሰሩት ስራ በተጨማሪ በኦንላይን ሊንክ ወይም ማስፈንጠሪያዎችን በመጠቀም ሲሰራበት መቆየቱን ተናግረዋል።
ስራው በሚገባው ልክ እንዲጠናቀቅ ለማድረግም የማብቂያ ቀናቶች መራዘማቸውን ያስታወሱ ሲሆን በመጨረሻዎቹ ቀናት በደንበኞች አገልግሎት ላይ ጫና ፈጥሮ እንደነበር አንስተዋል።
ይሁን እንጂ ችግሩን በቶሎ በመፍታት አሁን ላይ በተለያዩ ባንኮች ውስጥ ከፋይዳ ማስተሳሰር ጋር የተገናኙ ሰልፎች እንደማይታዩና የሚቀርቡ ጥያቄዎችም በፍጥነት ምላሽ እያገኙ መሆኑን አመላክተዋል።
ለአገልግሎቱ ምቹ የሆነ ሁኔታ እስከተፈጠረ ድረስ ወዲያውኑ ወደትግበራ መግባት የተሻለ መሆኑን ጠቁመዋል።
የፋይዳ መታወቂያን ከባንክ ጋር የማስተሳሰር ሂደቱን በዋነኛነት ብሔራዊ ባንክ በበላይነት እየመራው እና በጥሩ ሂደት ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
#አሐዱ
ፋይዳ መታወቂያን ከባንክ የሂሳብ ጋር ለማስተሳስር የነበረው ሰልፍ እና መጉላላት በተገልጋይዎች ዘንድ ቅሬታን ፈጥሮ እንደነበር ይታወቃል፡፡
ከፋይዳ መታወቂያ ጋር በተገናኘ ባንኮች ላይ የነበሩ ሰልፎችን በማስቀረትና የሚቀርቡ ጥያቄዎችን በፍጥነት ምላሽ በመስጠት በአሁኑ ወቅት የባንክ ሂሳብን ከፋይዳ ጋር የማስተሳሰር ሂደቱ መሻሻል የታየበት መሆኑ ተገልጾዋል፡፡
የባንክ ሂሳብን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ማስተሳሰር በታህሳስ ወር 2018 ዓ.ም መጀመሩን ያስታወሱት የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የባለድርሻ አካላትና የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ሳሚናስ ሰይፉ ናቸው።
ባንኮች ከሚሰሩት ስራ በተጨማሪ በኦንላይን ሊንክ ወይም ማስፈንጠሪያዎችን በመጠቀም ሲሰራበት መቆየቱን ተናግረዋል።
ስራው በሚገባው ልክ እንዲጠናቀቅ ለማድረግም የማብቂያ ቀናቶች መራዘማቸውን ያስታወሱ ሲሆን በመጨረሻዎቹ ቀናት በደንበኞች አገልግሎት ላይ ጫና ፈጥሮ እንደነበር አንስተዋል።
ይሁን እንጂ ችግሩን በቶሎ በመፍታት አሁን ላይ በተለያዩ ባንኮች ውስጥ ከፋይዳ ማስተሳሰር ጋር የተገናኙ ሰልፎች እንደማይታዩና የሚቀርቡ ጥያቄዎችም በፍጥነት ምላሽ እያገኙ መሆኑን አመላክተዋል።
ለአገልግሎቱ ምቹ የሆነ ሁኔታ እስከተፈጠረ ድረስ ወዲያውኑ ወደትግበራ መግባት የተሻለ መሆኑን ጠቁመዋል።
የፋይዳ መታወቂያን ከባንክ ጋር የማስተሳሰር ሂደቱን በዋነኛነት ብሔራዊ ባንክ በበላይነት እየመራው እና በጥሩ ሂደት ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
#አሐዱ
2 days ago
በቀጣይ ሳምንት ከኢራን ጋር ስምምነት ላይ ሊደረስ እንደሚችል ትራምፕ ተናገሩ
ከኢራን ጋር የተኩስ አቁም ለማራዘም እና የሆርሙዝ ወሽመጥን ለመክፈት በቀጣይ ሳምንት ስምምነት ላይ እንደሚደረስ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለኤቢሲ በሰጡት ቃለ ምልልስ ተናገሩ።
“አሁን ላይ ነገሮች በጣም ጥሩ ናቸው። ውስን ችግር ነበር፤ ነገር ግን እንዳያችሁት በፍጥነት ፈትቼዋለሁ” ሲሉ በስልክ በሰጡት ቃለ ምልልስ ገልጸዋል።
ትራምፕ ችግር ብለው የጠቀሱት እስራኤል በሊባኖስ ላይ የምታደርሰው ጥቃት ኢራንን ማስቆጣቱን ነው።
ሄዝቦላህ በእስራኤል ላይ ጥቃት ማድረስ እንዲያቆም ከአሜሪካ የቀረበለትን ሐሳብ መቀበሉን ሊባኖስ አስታውቃለች። እስራኤልም በሊባኖስ መዲና ቤሩት ጥቃት ላለመፈጸም መስማማቷም ተገልጿል።
ትራምፕ ከጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ እና ከሄዝቦላህ ተወካዮች ጋር መወያየታቸውን ጠቅሰው “ተኩስ ለማቆም ተስማምተዋል” ብለዋል።
ትራምፕ “ሄዝቦላህን አትተኩሱ ብያቸዋለሁ። ቢቢ [ኔታንያሁ] እንዳይተኩስም ነግሬዋለሁ። ሁለቱም ተኩስ አቁመዋል” ሲሉም አክለዋል።
በቀጣይ ሳምንት የሆርሙዝ ወሽመጥ ይከፈታል ብለው እንደሚያምኑም ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል።
BBC
ከኢራን ጋር የተኩስ አቁም ለማራዘም እና የሆርሙዝ ወሽመጥን ለመክፈት በቀጣይ ሳምንት ስምምነት ላይ እንደሚደረስ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለኤቢሲ በሰጡት ቃለ ምልልስ ተናገሩ።
“አሁን ላይ ነገሮች በጣም ጥሩ ናቸው። ውስን ችግር ነበር፤ ነገር ግን እንዳያችሁት በፍጥነት ፈትቼዋለሁ” ሲሉ በስልክ በሰጡት ቃለ ምልልስ ገልጸዋል።
ትራምፕ ችግር ብለው የጠቀሱት እስራኤል በሊባኖስ ላይ የምታደርሰው ጥቃት ኢራንን ማስቆጣቱን ነው።
ሄዝቦላህ በእስራኤል ላይ ጥቃት ማድረስ እንዲያቆም ከአሜሪካ የቀረበለትን ሐሳብ መቀበሉን ሊባኖስ አስታውቃለች። እስራኤልም በሊባኖስ መዲና ቤሩት ጥቃት ላለመፈጸም መስማማቷም ተገልጿል።
ትራምፕ ከጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ እና ከሄዝቦላህ ተወካዮች ጋር መወያየታቸውን ጠቅሰው “ተኩስ ለማቆም ተስማምተዋል” ብለዋል።
ትራምፕ “ሄዝቦላህን አትተኩሱ ብያቸዋለሁ። ቢቢ [ኔታንያሁ] እንዳይተኩስም ነግሬዋለሁ። ሁለቱም ተኩስ አቁመዋል” ሲሉም አክለዋል።
በቀጣይ ሳምንት የሆርሙዝ ወሽመጥ ይከፈታል ብለው እንደሚያምኑም ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል።
BBC
2 days ago
በልዩ ቅናሽ የጊፍት ማህበረሰብን ይቀላቀሉ!
********
የህልምዎን መኖሪያ ቤት ወይም ንግድ ቦታ ለማግኘት ይህ መልካም አጋጣሚ ነው!
በልዩ ቅናሽ ያቀረብናቸው ዘመናዊ አፓርትመንቶችና ንግድ ሱቆች በሽያጭ ላይ ይገኛሉ።
ጊፍት ሪል ስቴት በአዲስ አበባ በተመረጡ አካባቢዎች ፕሮጀክቶችን በማቅረብ “ማህበረሰብን እንገነባለን” የሚለውን ራዕይ እውን እያደረገ ነው።
የሽያጭ ፕሮጀክቶቻችን
📍 ለገሃር
📍 ተክለሃይማኖት
📍 አትላስ
📍 ሲኤምሲ
📍 ፈረስ ቤት
📍 22 ማዞሪያ
ለምን ጊፍት ሪል ስቴትን ይመርጣሉ?
✅ ለመኖሪያም ሆነ ለንግድ ተስማሚ አማራጮች
✅ በምርጥና ተፈላጊ አካባቢዎች የሚገኙ ፕሮጀክቶች
✅ ዘመናዊ ዲዛይንና ጥራት ያላቸው ግንባታዎች
✅ ልዩ ቅናሽ እና ምቹ የክፍያ አማራጮች
ይፍጠኑ!
ይህን ውስን የቅናሽ እድል አያምልጥዎ! ዛሬውኑ የጊፍት ማህበረሰብን ይቀላቀሉ!
ጊፍት ሪል ስቴት
ማህበረሰብን እንገነባለን!
📞 ለበለጠ መረጃ፦
+251 984 6565 65
+251 979 6565 65
🌐 ድረ-ገጽ፦
www.giftrealestate.com.et
********
የህልምዎን መኖሪያ ቤት ወይም ንግድ ቦታ ለማግኘት ይህ መልካም አጋጣሚ ነው!
በልዩ ቅናሽ ያቀረብናቸው ዘመናዊ አፓርትመንቶችና ንግድ ሱቆች በሽያጭ ላይ ይገኛሉ።
ጊፍት ሪል ስቴት በአዲስ አበባ በተመረጡ አካባቢዎች ፕሮጀክቶችን በማቅረብ “ማህበረሰብን እንገነባለን” የሚለውን ራዕይ እውን እያደረገ ነው።
የሽያጭ ፕሮጀክቶቻችን
📍 ለገሃር
📍 ተክለሃይማኖት
📍 አትላስ
📍 ሲኤምሲ
📍 ፈረስ ቤት
📍 22 ማዞሪያ
ለምን ጊፍት ሪል ስቴትን ይመርጣሉ?
✅ ለመኖሪያም ሆነ ለንግድ ተስማሚ አማራጮች
✅ በምርጥና ተፈላጊ አካባቢዎች የሚገኙ ፕሮጀክቶች
✅ ዘመናዊ ዲዛይንና ጥራት ያላቸው ግንባታዎች
✅ ልዩ ቅናሽ እና ምቹ የክፍያ አማራጮች
ይፍጠኑ!
ይህን ውስን የቅናሽ እድል አያምልጥዎ! ዛሬውኑ የጊፍት ማህበረሰብን ይቀላቀሉ!
ጊፍት ሪል ስቴት
ማህበረሰብን እንገነባለን!
📞 ለበለጠ መረጃ፦
+251 984 6565 65
+251 979 6565 65
🌐 ድረ-ገጽ፦
www.giftrealestate.com.et
2 days ago
🚨 "እባካችሁ ድምፅ ሁኑን!" — ከምስራቅ አርሲ ጫካዎች የተሰማ የድረሱልን ጥሪ!
መላው አገር በምርጫው ትኩረት በተጠመደበት በዚህ ወቅት፣ በምስራቅ አርሲ አሰኮ ወረዳ በንጹሐን ኦርቶዶክሳውያን ላይ ዘግናኝ ጥቃት እየተፈጸመ ይገኛል።
📌 እስካሁን የደረሰው ጉዳት፦
የሕይወት መጥፋት፦ከ37 በላይ ንጹሐን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል።
የንብረት ውድመት፦234 መኖሪያ ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተቃጥለዋል።
የሃይማኖት ተቋማት፦ታሪካዊው የጠላታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል እና የኩፍቴና መድኃኔዓለም አብያተ ክርስቲያናት ወድመዋል።
⚠️ ወቅታዊ ሁኔታ፦
ጥቃቱ አሁንም በተለያዩ ቀበሌዎች (ዘዲቡ፣ እሬቻ ሚካኤል፣ ሱንቴ ማርያም...) የቀጠለ ሲሆን፣ አቅመ-ቢስ እናቶችና ሕፃናት ሕይወታቸውን ለማዳን ንብረታቸውን ጥለው በጫካዎች ውስጥ ተደብቀው ይገኛሉ።
🙏 ነፍስ ይማር!
መላው አገር በምርጫው ትኩረት በተጠመደበት በዚህ ወቅት፣ በምስራቅ አርሲ አሰኮ ወረዳ በንጹሐን ኦርቶዶክሳውያን ላይ ዘግናኝ ጥቃት እየተፈጸመ ይገኛል።
📌 እስካሁን የደረሰው ጉዳት፦
የሕይወት መጥፋት፦ከ37 በላይ ንጹሐን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል።
የንብረት ውድመት፦234 መኖሪያ ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተቃጥለዋል።
የሃይማኖት ተቋማት፦ታሪካዊው የጠላታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል እና የኩፍቴና መድኃኔዓለም አብያተ ክርስቲያናት ወድመዋል።
⚠️ ወቅታዊ ሁኔታ፦
ጥቃቱ አሁንም በተለያዩ ቀበሌዎች (ዘዲቡ፣ እሬቻ ሚካኤል፣ ሱንቴ ማርያም...) የቀጠለ ሲሆን፣ አቅመ-ቢስ እናቶችና ሕፃናት ሕይወታቸውን ለማዳን ንብረታቸውን ጥለው በጫካዎች ውስጥ ተደብቀው ይገኛሉ።
🙏 ነፍስ ይማር!
3 days ago
የምርጫ ቦርድ በሰልፍ ላይ ለሚገኙ መራጮች የድምፅ መስጫ ሰዓት መራዘሙን ገለጸ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዕለቱ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ማብቂያ እስከሆነው 12:00 ሰዓት ድረስ በምርጫ ጣቢያዎች ተገኝተው በሰልፍ ላይ የነበሩ መራጮች በሙሉ ድምፅ ሰጥተው እስኪያጠናቅቁ ድረስ ሂደቱ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
ይህ ውሳኔ የተላለፈው በምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 49 ንዑስ አንቀጽ 4 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ሲሆን፣ ቦርዱ አስገዳጅ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙ የድምፅ መስጫ ሰዓትን ማራዘም እንደሚችል በሕጉ ላይ ተደንግጓል።
ውሳኔው የወጣው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ነው።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዕለቱ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ማብቂያ እስከሆነው 12:00 ሰዓት ድረስ በምርጫ ጣቢያዎች ተገኝተው በሰልፍ ላይ የነበሩ መራጮች በሙሉ ድምፅ ሰጥተው እስኪያጠናቅቁ ድረስ ሂደቱ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
ይህ ውሳኔ የተላለፈው በምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 49 ንዑስ አንቀጽ 4 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ሲሆን፣ ቦርዱ አስገዳጅ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙ የድምፅ መስጫ ሰዓትን ማራዘም እንደሚችል በሕጉ ላይ ተደንግጓል።
ውሳኔው የወጣው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ነው።
3 days ago
የጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏
በተወለዱ በሦስተኛው ቀን ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው “አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ” በማለት ሥላሴን አመስግነዋል፡፡
አባታቸው ጸጋ ዘአብና እናታቸው እግዚእ ኃረያ ፍሥሐ ጽዮን ብለው ሰየሟቸው፡፡ በአንድ ወቅት ታዳጊው ፍሥሐ ጽዮን ወደ ጫካ ለአደን በሔዱበት ጌታችን ተገልጦ ጸጋ መንፈስ ቅዱን አሳደረባቸው፡፡ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ለስብከተ ወንጌል እንደሚልካቸውም አስረዳቸው፡፡ በተወለዱ በ15 ዓመታቸው መዓርገ ዲቊናን፣ በ22 ዓመታቸው ደግሞ መዓርገ ቅስናን ከግብጻዊው ጳጳስ አባ ቄርሎስ ተቀብለዋል፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ስማቸውም ተክለ ሃይማኖት እንደሚባል፣ ትርጓሜውም ተክለ አብ፣ ተክለ ወልድ፣ ተክለ መንፈስ ቅዱስ ማለት እንደሆነ አበሠራቸው፡፡
ወላጆቻቸው ካረፉ በኋላም ንብረታቸውን ሁሉ ለቤተ ክርስቲያንና ለነዳያን ሰጥተው ቤታቸውን ትተው ወንጌልን ለማስተማር ወጡ፡፡ በደብረ ዳሞ ገዳም ለ12 ዓመታት ተቀምጠው ሲወርዱ ገመዱ ቢበጠስ ስድስት ክንፍ አውጥተው በረዋል፡፡ በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ ወንጌልን በመስበክና ተአምራትን በማድረግ በርካታ አሕዛብን አጥምቀዋል፤ አብያተ ክርስቲያናትንም አሳንጸዋል፡፡ በደብረ ሊባኖስ ገዳም አስቦ ዋሻ በዙሪያቸው ስምንት ጦሮች ተክለው እጆቻቸውን በትእምርተ መስቀል በመዘርጋት የክርስቶስን ሕማምና ሞት በማሰብ ሌሊትና ቀን ያለ ማቋረጥ በጾምና በጸሎት ሲጋደሉ፤ ከመቆም ብዛት አንድ እግራቸው ተሰብሯል፡፡
ጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ በኋላም ለሰባት ዓመታት በአንድ እግራቸው ቆመው ለሰው ዘር ሁሉ ድኅነትን ለምነዋል፡፡ ከዚህ ዓለም ድካም በሚያርፉበት ቀንም ጌታችን ከእናቱ ከቅዱሳን መላእክት፣ ከወዳጆቹ ጋር መጥቶ የምሕረት ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል፡፡ ዐጽማቸው የፈለሰበት ዕለትም ግንቦት 12 ነው፡፡
የጻድቁን ቃል ኪዳን ያመኑ ገዳማውያን እንደሳቸው ሁሉ ዓለምን ንቀው በተጋድሎ ይኖራሉና ከበረከታቸው እንድንሳተፍ ገዳማቸውን እየደገፍን በዓታቸውን እያጸናን ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
በተወለዱ በሦስተኛው ቀን ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው “አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ” በማለት ሥላሴን አመስግነዋል፡፡
አባታቸው ጸጋ ዘአብና እናታቸው እግዚእ ኃረያ ፍሥሐ ጽዮን ብለው ሰየሟቸው፡፡ በአንድ ወቅት ታዳጊው ፍሥሐ ጽዮን ወደ ጫካ ለአደን በሔዱበት ጌታችን ተገልጦ ጸጋ መንፈስ ቅዱን አሳደረባቸው፡፡ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ለስብከተ ወንጌል እንደሚልካቸውም አስረዳቸው፡፡ በተወለዱ በ15 ዓመታቸው መዓርገ ዲቊናን፣ በ22 ዓመታቸው ደግሞ መዓርገ ቅስናን ከግብጻዊው ጳጳስ አባ ቄርሎስ ተቀብለዋል፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ስማቸውም ተክለ ሃይማኖት እንደሚባል፣ ትርጓሜውም ተክለ አብ፣ ተክለ ወልድ፣ ተክለ መንፈስ ቅዱስ ማለት እንደሆነ አበሠራቸው፡፡
ወላጆቻቸው ካረፉ በኋላም ንብረታቸውን ሁሉ ለቤተ ክርስቲያንና ለነዳያን ሰጥተው ቤታቸውን ትተው ወንጌልን ለማስተማር ወጡ፡፡ በደብረ ዳሞ ገዳም ለ12 ዓመታት ተቀምጠው ሲወርዱ ገመዱ ቢበጠስ ስድስት ክንፍ አውጥተው በረዋል፡፡ በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ ወንጌልን በመስበክና ተአምራትን በማድረግ በርካታ አሕዛብን አጥምቀዋል፤ አብያተ ክርስቲያናትንም አሳንጸዋል፡፡ በደብረ ሊባኖስ ገዳም አስቦ ዋሻ በዙሪያቸው ስምንት ጦሮች ተክለው እጆቻቸውን በትእምርተ መስቀል በመዘርጋት የክርስቶስን ሕማምና ሞት በማሰብ ሌሊትና ቀን ያለ ማቋረጥ በጾምና በጸሎት ሲጋደሉ፤ ከመቆም ብዛት አንድ እግራቸው ተሰብሯል፡፡
ጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ በኋላም ለሰባት ዓመታት በአንድ እግራቸው ቆመው ለሰው ዘር ሁሉ ድኅነትን ለምነዋል፡፡ ከዚህ ዓለም ድካም በሚያርፉበት ቀንም ጌታችን ከእናቱ ከቅዱሳን መላእክት፣ ከወዳጆቹ ጋር መጥቶ የምሕረት ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል፡፡ ዐጽማቸው የፈለሰበት ዕለትም ግንቦት 12 ነው፡፡
የጻድቁን ቃል ኪዳን ያመኑ ገዳማውያን እንደሳቸው ሁሉ ዓለምን ንቀው በተጋድሎ ይኖራሉና ከበረከታቸው እንድንሳተፍ ገዳማቸውን እየደገፍን በዓታቸውን እያጸናን ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
Sponsored by
Surafel
3 days ago
የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎችን ፍጹም ፍትሃዊ እና ከስህተት የጸዱ ለማድረግ፣ ሙሉ በሙሉ በባትሪ ኃይል የሚሰራ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ኳስ ጥቅም ላይ ሊውል መሆኑ ተመልክቷል።
ዘንድሮ ውድድሩን በጋራ የሚያስተናግዱት አሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ከመላው ዓለም የሚመጡ ስፖርተኛችንና የእግር ኳስ አፍቃሪያንን ለመቀበል የመጨረሻ ዝግጅታቸውን እያጠናቀቁ ይገኛሉ።
ይህ የዓለም ዋንጫ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በሶስት ሀገራት በአንድ ጊዜ የሚስተናገድ ከመሆኑም በላይ በስፖርቱ ዓለም አዲስ የቴክኖሎጂ ምዕራፍ የሚከፍትበት ሆኗል።
ከ1970 ጀምሮ ለዓለም ዋንጫ ኳሶችን እያመረተ የሚገኘው አዲዳስ ኩባንያ፣ ዳኞችን በከፍተኛ ሁኔታ ለመርዳት የሚያስችል “ኮኔክቲድ ቦል ቴክኖሎጂ” (Connected Ball Technology) የተገጠመለትንና ትሪዮንዳ የተሰኘውን አዲስ የኤሌክትሮኒክስ ኳስ ይፋ አድርጓል።
የአዲዳስ ቃል አቀባይ እንደገለጹትብበኳሱ ውስጥ የተገጠመው መመርመሪያ (Sensor) ያለ ባትሪ ኃይል መስራት ስለማይችል ኳሱ ከእያንዳንዱ ጨዋታ በፊት የግድ ቻርጅ መደረግ ይኖርበታል።
ኳሱ ሙሉ አቅሙን ተጠቅሞ ሙሉ ጨዋታውንና ከዚያ በላይ በብቃት ማገልገል እንዲችል በጨዋታው ዕለት በስታዲየሙ ውስጥ በተዘጋጀ ልዩ የኃይል መሙያ መደርደሪያ (Cradle) ላይ ቻርጅ ይደረጋል።
ለዚህም በኢንደክሽን አማካኝነት በገመድ አልባ ሥርዓት ቻርጅ የሚደረግ ከፍተኛ ጥራት ያለው ባትሪ ጥቅም ላይ ውሏል።
ይህ ባትሪ ሙሉ በሙሉ ለመሙላት 90 ደቂቃ አካባቢ የሚፈጅ ሲሆንንበጨዋታ ላይ እያለ እስከ 6 ሰዓታት የማገልገል አቅም አለው።
ይህም የአንድን ከፍተኛ የደረጃ ጨዋታ ክፍለ-ጊዜ እጥፍ መቆየት የሚችል ያደርገዋል። በተጨማሪም ኳሱ ከሜዳ ውጭ በሚሆንበት ጊዜ ራሱን ወደ እረፍት ሁነታ (Hibernation mode) በመቀየር ባትሪው ሳይባክን ለቀናት እንዲቆይ ያደርጋል።
በኳሱ ውስጥ በልዩ የመደገፊያ ስርዓት (Suspension system) ተይዞ የተገጠመ 500Hz inertial measurement unit (IMU) የተሰኘ የቪዲዮ ረዳት ዳኝነት (VAR) መረጃዎችን የሚልክ ስስ የኮምፒውተር ቺፕ ይገኛል።
ይህ ሴንሰር እያንዳንዱን የኳስ ንክኪ በከፍተኛ ፍጥነት የሚከታተል ሲሆን የሚከተሉትን ውሳኔዎች በሜዳ ላይ በሴኮንዶች ውስጥ ለመወሰን ይረዳል፦
* ከጨዋታ ውጪ (Off-side) የሆኑ አቋቋሞችን በትክክል መለየት፣
* ኳስ በእጅ መነካቱን (Handballs) ማረጋገጥ፣
* እና ሌሎች አወዛጋቢ ሁነቶችን በቪዲዮ ረዳት ዳኝነቱ (VAR) አማካኝነት በፍጥነት መፍታት።
አዲዳስ እና የቴክኖሎጂ አጋሩ ኪኔክሶን (Kinexon) እንዳስታወቁት፣ ይህ ቴክኖሎጂ ቀደም ሲል በሁለት የፊፋ ውድድሮች እንዲሁም በዩሮ 2024 እና 2025 ላይ የተሞከረ ሲሆን፣ በጨዋታ መሃል ባትሪ አልቆበት የተቀየረ አንድም ኳስ አጋጥሞ አያውቅም።
ባለፈው የ2022ቱ የኳታር ዓለም ዋንጫ ላይም ተመሳሳይ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ ውሎ የነበረ ቢሆንም፣ የዘንድሮው የ2026ቱ ኳስ ግን የሴንሰር አቀማመጥ ለውጥ ተደርጎበታል። በቀደመው ኳስ ሴንሰሩ የተቀመጠው በኳሱ መሃል ላይ ሲሆን፣ በዘንድሮው ስሪት ግን ሴንሰሩ የተገጠመው በኳሱ የጎንዮሽ አካል (Side) ላይ ተቀብሮ ነው።
ኳሱ ከቴክኖሎጂው ባሻገር፣ ሶስቱን አስተናጋጅ ሀገራት ለማክበርና ለመወከል ሲባል በደማቅ ቀይ፣ አረንጓዴ እና ሰማያዊ ቀለማት የተሸለመ ሲሆን፤ የካናዳው የሜፕል ቅጠል (Maple leaf)፣ የሜክሲኮው ንስር (Eagle) እና የአሜሪካው ኮከብ (Star) ምልክቶች በሥነ-ጥበባዊ መልኩ ተካተውበታል።
ዘንድሮ ውድድሩን በጋራ የሚያስተናግዱት አሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ከመላው ዓለም የሚመጡ ስፖርተኛችንና የእግር ኳስ አፍቃሪያንን ለመቀበል የመጨረሻ ዝግጅታቸውን እያጠናቀቁ ይገኛሉ።
ይህ የዓለም ዋንጫ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በሶስት ሀገራት በአንድ ጊዜ የሚስተናገድ ከመሆኑም በላይ በስፖርቱ ዓለም አዲስ የቴክኖሎጂ ምዕራፍ የሚከፍትበት ሆኗል።
ከ1970 ጀምሮ ለዓለም ዋንጫ ኳሶችን እያመረተ የሚገኘው አዲዳስ ኩባንያ፣ ዳኞችን በከፍተኛ ሁኔታ ለመርዳት የሚያስችል “ኮኔክቲድ ቦል ቴክኖሎጂ” (Connected Ball Technology) የተገጠመለትንና ትሪዮንዳ የተሰኘውን አዲስ የኤሌክትሮኒክስ ኳስ ይፋ አድርጓል።
የአዲዳስ ቃል አቀባይ እንደገለጹትብበኳሱ ውስጥ የተገጠመው መመርመሪያ (Sensor) ያለ ባትሪ ኃይል መስራት ስለማይችል ኳሱ ከእያንዳንዱ ጨዋታ በፊት የግድ ቻርጅ መደረግ ይኖርበታል።
ኳሱ ሙሉ አቅሙን ተጠቅሞ ሙሉ ጨዋታውንና ከዚያ በላይ በብቃት ማገልገል እንዲችል በጨዋታው ዕለት በስታዲየሙ ውስጥ በተዘጋጀ ልዩ የኃይል መሙያ መደርደሪያ (Cradle) ላይ ቻርጅ ይደረጋል።
ለዚህም በኢንደክሽን አማካኝነት በገመድ አልባ ሥርዓት ቻርጅ የሚደረግ ከፍተኛ ጥራት ያለው ባትሪ ጥቅም ላይ ውሏል።
ይህ ባትሪ ሙሉ በሙሉ ለመሙላት 90 ደቂቃ አካባቢ የሚፈጅ ሲሆንንበጨዋታ ላይ እያለ እስከ 6 ሰዓታት የማገልገል አቅም አለው።
ይህም የአንድን ከፍተኛ የደረጃ ጨዋታ ክፍለ-ጊዜ እጥፍ መቆየት የሚችል ያደርገዋል። በተጨማሪም ኳሱ ከሜዳ ውጭ በሚሆንበት ጊዜ ራሱን ወደ እረፍት ሁነታ (Hibernation mode) በመቀየር ባትሪው ሳይባክን ለቀናት እንዲቆይ ያደርጋል።
በኳሱ ውስጥ በልዩ የመደገፊያ ስርዓት (Suspension system) ተይዞ የተገጠመ 500Hz inertial measurement unit (IMU) የተሰኘ የቪዲዮ ረዳት ዳኝነት (VAR) መረጃዎችን የሚልክ ስስ የኮምፒውተር ቺፕ ይገኛል።
ይህ ሴንሰር እያንዳንዱን የኳስ ንክኪ በከፍተኛ ፍጥነት የሚከታተል ሲሆን የሚከተሉትን ውሳኔዎች በሜዳ ላይ በሴኮንዶች ውስጥ ለመወሰን ይረዳል፦
* ከጨዋታ ውጪ (Off-side) የሆኑ አቋቋሞችን በትክክል መለየት፣
* ኳስ በእጅ መነካቱን (Handballs) ማረጋገጥ፣
* እና ሌሎች አወዛጋቢ ሁነቶችን በቪዲዮ ረዳት ዳኝነቱ (VAR) አማካኝነት በፍጥነት መፍታት።
አዲዳስ እና የቴክኖሎጂ አጋሩ ኪኔክሶን (Kinexon) እንዳስታወቁት፣ ይህ ቴክኖሎጂ ቀደም ሲል በሁለት የፊፋ ውድድሮች እንዲሁም በዩሮ 2024 እና 2025 ላይ የተሞከረ ሲሆን፣ በጨዋታ መሃል ባትሪ አልቆበት የተቀየረ አንድም ኳስ አጋጥሞ አያውቅም።
ባለፈው የ2022ቱ የኳታር ዓለም ዋንጫ ላይም ተመሳሳይ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ ውሎ የነበረ ቢሆንም፣ የዘንድሮው የ2026ቱ ኳስ ግን የሴንሰር አቀማመጥ ለውጥ ተደርጎበታል። በቀደመው ኳስ ሴንሰሩ የተቀመጠው በኳሱ መሃል ላይ ሲሆን፣ በዘንድሮው ስሪት ግን ሴንሰሩ የተገጠመው በኳሱ የጎንዮሽ አካል (Side) ላይ ተቀብሮ ነው።
ኳሱ ከቴክኖሎጂው ባሻገር፣ ሶስቱን አስተናጋጅ ሀገራት ለማክበርና ለመወከል ሲባል በደማቅ ቀይ፣ አረንጓዴ እና ሰማያዊ ቀለማት የተሸለመ ሲሆን፤ የካናዳው የሜፕል ቅጠል (Maple leaf)፣ የሜክሲኮው ንስር (Eagle) እና የአሜሪካው ኮከብ (Star) ምልክቶች በሥነ-ጥበባዊ መልኩ ተካተውበታል።
3 days ago
በፀጥታ ችግር ምክንያት 143 የምርጫ ጣቢያዎች አለመከፈታቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ገለጸ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት እየተካሄደ ያለውን ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላተወርቅ ኋይሉ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም በፀጥታ ችግር ምክንያት 143 የሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች ምርጫ ሊደርግባቸው ዝግጅት ቢያደርጉም ያልተከፈቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በአማራና በኦሮሚያ አንዳንድ አካባቢዎች ተከፍተው የተዘጉ እንደ ቀርሳ፣ ኩታበር፣ ቢሎኖፖ፣ መኮሳቺና ሌሎች አካባቢዎች የምርጫ ሂደቱ መቋረጡን ጠቁመዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው መራጮች ሰልፍ መሆናቸውን ያነሱት ዋና ሰብሳቢዋ በተለይም በድጅታል ምዝገባ የተመዘገቡ መራጮችን ላይ መዝግየቶች አሉ ብለዋል።
ችግሩን ለመፍታት እና መራጮች በፍጥነት ለማስተናገድ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው ለተፈጠረው መጉላላት ይቅርታ ጠይቀዋል።
እንዲሁም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዘልመም እና ሰዳል አካባቢዎች የኔትወርክ ችግር በመኖሩ መረጃ ለመለዋወጥ ተግዳሮት መሆኑን ተናግረዋል።
#አሐዱ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት እየተካሄደ ያለውን ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላተወርቅ ኋይሉ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም በፀጥታ ችግር ምክንያት 143 የሚሆኑ የምርጫ ጣቢያዎች ምርጫ ሊደርግባቸው ዝግጅት ቢያደርጉም ያልተከፈቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በአማራና በኦሮሚያ አንዳንድ አካባቢዎች ተከፍተው የተዘጉ እንደ ቀርሳ፣ ኩታበር፣ ቢሎኖፖ፣ መኮሳቺና ሌሎች አካባቢዎች የምርጫ ሂደቱ መቋረጡን ጠቁመዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው መራጮች ሰልፍ መሆናቸውን ያነሱት ዋና ሰብሳቢዋ በተለይም በድጅታል ምዝገባ የተመዘገቡ መራጮችን ላይ መዝግየቶች አሉ ብለዋል።
ችግሩን ለመፍታት እና መራጮች በፍጥነት ለማስተናገድ እየተሰራ መሆኑን ገልጸው ለተፈጠረው መጉላላት ይቅርታ ጠይቀዋል።
እንዲሁም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዘልመም እና ሰዳል አካባቢዎች የኔትወርክ ችግር በመኖሩ መረጃ ለመለዋወጥ ተግዳሮት መሆኑን ተናግረዋል።
#አሐዱ
4 days ago
ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚደራደሩባቸው ነጥቦች የበለጠ እንዲጠናከሩ መጠየቃቸው ተዘገበ
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር በሚደረገው ድርድር የቀረቡ በርካታ ነጥቦች ላይ ለውጥ እንዲደረግ መጠየቃቸውን የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ።
ኒው ዮርክ ታይምስ እንደዘገበው፤ ትራምፕ የድርድር ነጥቦቹ የበለጠ እንዲጠናከሩ ይፈልጋሉ። እንደ አዲስ ክለሳ የተደረገበት የድርድር ማዕቀፍም ለኢራን ተልኳል።
አክሲዮስ ባወጣው ዘገባ፤ ከኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር እና ዩራንየም የማበልጸግ ሒደት ጋር የሚያያዙ የድርድሩ ነጥቦች እንዲጠናከሩ ትራምፕ ጠይቀዋል።
ትራምፕ የስምምነቱን ረቂቅ ከተመለከቱ በኋላ ለውጥ እንዲደረግ መጠየቃቸውን ኒው ዮርክ ታይምስ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል።
ትራምፕ እንዲደረግ የጠየቁት ለውጥ ድርድሩን በምን መንገድ ሊቀይረው እንደሚችል ግልጽ አይደለም።
የኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር እና ክምችት ትራምፕ ጠንካራ ለውጥ እንዲደረግባቸው ከጠየቋቸው ነጥቦች መካከል እንደሚገኝበት አክሲዮስ ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል።
የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች እንደሚጠቁሙት እነዚህ ለውጦች ድርድሩን በቀናት ሊያራዝሙ ይችላሉ።
ትራምፕ ባለፈው አርብ በዋይት ሀውስ አስቸኳይ ስብሰባ ቢያደርጉም የመጨረሻ ውሳኔያቸው ይፋ አልሆነም።
የስምምነቱ ረቂቅ የትራምፕን ይሁንታ እየጠበቀ እንደነበር ኤኤፍፒ ዘግቧል። የኢራን ባለሥልጣናትም ረቂቁን ማጽደቃቸውን አላሳወቁም።
BBC
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር በሚደረገው ድርድር የቀረቡ በርካታ ነጥቦች ላይ ለውጥ እንዲደረግ መጠየቃቸውን የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ።
ኒው ዮርክ ታይምስ እንደዘገበው፤ ትራምፕ የድርድር ነጥቦቹ የበለጠ እንዲጠናከሩ ይፈልጋሉ። እንደ አዲስ ክለሳ የተደረገበት የድርድር ማዕቀፍም ለኢራን ተልኳል።
አክሲዮስ ባወጣው ዘገባ፤ ከኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር እና ዩራንየም የማበልጸግ ሒደት ጋር የሚያያዙ የድርድሩ ነጥቦች እንዲጠናከሩ ትራምፕ ጠይቀዋል።
ትራምፕ የስምምነቱን ረቂቅ ከተመለከቱ በኋላ ለውጥ እንዲደረግ መጠየቃቸውን ኒው ዮርክ ታይምስ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል።
ትራምፕ እንዲደረግ የጠየቁት ለውጥ ድርድሩን በምን መንገድ ሊቀይረው እንደሚችል ግልጽ አይደለም።
የኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር እና ክምችት ትራምፕ ጠንካራ ለውጥ እንዲደረግባቸው ከጠየቋቸው ነጥቦች መካከል እንደሚገኝበት አክሲዮስ ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል።
የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች እንደሚጠቁሙት እነዚህ ለውጦች ድርድሩን በቀናት ሊያራዝሙ ይችላሉ።
ትራምፕ ባለፈው አርብ በዋይት ሀውስ አስቸኳይ ስብሰባ ቢያደርጉም የመጨረሻ ውሳኔያቸው ይፋ አልሆነም።
የስምምነቱ ረቂቅ የትራምፕን ይሁንታ እየጠበቀ እንደነበር ኤኤፍፒ ዘግቧል። የኢራን ባለሥልጣናትም ረቂቁን ማጽደቃቸውን አላሳወቁም።
BBC
4 days ago
ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የ2018 በጀት ዓመት ሳይጠናቀቅ እንደሚካሄድ ተገለጸ
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የ2018 በጀት ዓመት ሳይጠናቀቅ ለማካሄድ ማቀዱን አስታውቋል።
የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ይኽንን የገለጹት የሃይማኖት ተቋማት እና የሲቪክ ማኅበራት አጀንዳዎች በቀረቡበት የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረክ ላይ ነው።
የምክክር ሂደቱን የሚያሳልጡ 192 አመካካሪ ባለሙያዎች ተመርጠው ሥልጠና መውሰዳቸውን ዋና ኮሚሽነሩ ጠቁመዋል። በቀጣይም በዓለም አቀፍ ደረጃ በሰላምና ምክክር ላይ በሚሠሩ ተቋማት ተጨማሪ ሥልጠና እንደሚሰጣቸው ገልጸዋል።
በጉባኤው ላይ በአጠቃላይ አራት ሺሕ ተሳታፊዎች ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል። የምክክር ሂደቱም አምስት መቶ ተሳታፊዎችን በያዙ ስምንት ንዑሳን ጉባኤዎች ተከፋፍሎ የሚካሄድ ሲሆን የውይይቶቹ ማጠቃለያ ምክረ ሐሳብም ይቀርባል።
ኮሚሽኑ የጉባኤውን ዝርዝር መረጃ የዝግጅት ሥራውን እንዳጠናቀቀ ይፋ እንደሚያደርግ ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ጨምረው ገልጸዋል።
#አሐዱ
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋናውን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የ2018 በጀት ዓመት ሳይጠናቀቅ ለማካሄድ ማቀዱን አስታውቋል።
የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ይኽንን የገለጹት የሃይማኖት ተቋማት እና የሲቪክ ማኅበራት አጀንዳዎች በቀረቡበት የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረክ ላይ ነው።
የምክክር ሂደቱን የሚያሳልጡ 192 አመካካሪ ባለሙያዎች ተመርጠው ሥልጠና መውሰዳቸውን ዋና ኮሚሽነሩ ጠቁመዋል። በቀጣይም በዓለም አቀፍ ደረጃ በሰላምና ምክክር ላይ በሚሠሩ ተቋማት ተጨማሪ ሥልጠና እንደሚሰጣቸው ገልጸዋል።
በጉባኤው ላይ በአጠቃላይ አራት ሺሕ ተሳታፊዎች ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል። የምክክር ሂደቱም አምስት መቶ ተሳታፊዎችን በያዙ ስምንት ንዑሳን ጉባኤዎች ተከፋፍሎ የሚካሄድ ሲሆን የውይይቶቹ ማጠቃለያ ምክረ ሐሳብም ይቀርባል።
ኮሚሽኑ የጉባኤውን ዝርዝር መረጃ የዝግጅት ሥራውን እንዳጠናቀቀ ይፋ እንደሚያደርግ ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ጨምረው ገልጸዋል።
#አሐዱ
4 days ago
ፈተናውን ወደ መልካም አጋጣሚ የቀየረው የልዩ ህክምና ክሊኒክ፤ በዘመናዊ ህንጻና ግብዓቶች ስራ እንደገና ጀመረ
በከተማዋ በተካሄደው የኮሪደር ልማት ምክንያት አገልግሎት ሲሰጥበት የነበረው ህንጻ የፈረሰበት የልዩ ህክምና ክሊኒክ፣ አቅሙንና የህክምና መገልገያ መሳሪያዎቹን በከፍተኛ ደረጃ በማዘመን በአዲስ መልክ ተመርቆ ስራ ጀመረ።
ክሊኒኩ በአሁኑ ወቅት አገልግሎቱን በስፋት መቀጠል የጀመረው በየካ ክፍለ ከተማ፣ ታቦት ማደሪያ እግር ኳስ ሜዳ አጠገብ ባስገነባው ባለ 22 ክፍል ዘመናዊ ህንጻ ላይ መሆኑ ታውቋል።
የተቋሙ መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ዳዊት አማረ በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ እንደገለጹት፤ ክሊኒኩ የገጠመውን ፈተና ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር በይዘቱም ሆነ በህክምና መገልገያ መሳሪያዎች እራሱን በከፍተኛ ደረጃ ማዘመን ችሏል።
ተቋሙ በተለይም በውስጥ ደዌ እና በሳንባ ስፔሻሊስት (Pulmonology) የህክምና ዘርፎች ላይ ትኩረት አድርጎ ጥራት ያለው አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን፣ ለድንገተኛና ለአስቸኳይ ህክምና ፈላጊዎችም ቀልጣፋ አደረጃጀት ማዘጋጀቱን ገልጸዋል።
"ጤና የእያንዳንዱ ሰው መሰረታዊ መብት ነው" ያሉት ዶክተር ዳዊት፤ ባለፉት ስድስት ዓመታት በርካታ ታካሚዎችን በታማኝነት ሲያገለግሉ መቆየታቸውንና አሁንም ማህበረሰቡን በተሻለ ጥራትና ምቾት ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን አብራርተዋል።
አዲሱ ህንፃ የህክምና ተቋም ሊያሟላቸው የሚገቡ መስፈርቶችን ሙሉ በሙሉ ያሟላ ከመሆኑም በላይ፣ ህፃናትን ጨምሮ ማንኛውንም ታካሚ በተገቢው ሁኔታ ለማስተናገድ የሚያስችሉ ባለሙያዎችና ዘመናዊ ግብዓቶች ተጠናቀውለታል። ተቋሙ በኮሪደር ልማት ምክንያት ቢፈርስም፣ ላለፉት 14 ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥበት በነበረው በዚሁ አካባቢ ለታካሚዎች ምቹ በሆነ ስፍራ ላይ በላቀ አደረጃጀት ዳግም ስራ መጀመሩ ተገልጿል።
ይህ የልዩ ህክምና ክሊኒክ ለ56 የህክምና ባለሙያዎች የስራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 23 የሚሆኑ ስፔሻሊስት እና ሰብ-ስፔሻሊስት ዶክተሮችን በማሳተፍ ላይ ይገኛል። በጥናት ማጠቃለያውም ላይ ክሊኒኩ ባለፉት ዓመታት አብረዋቸው ለቆሙ ታካሚዎች እና በአስቸጋሪ ወቅቶች ስራው ሳይስተጓጎል ድጋፍ ላደረጉ ባልደረቦቹ ከፍተኛ ምስጋና አቅርቧል።
በከተማዋ በተካሄደው የኮሪደር ልማት ምክንያት አገልግሎት ሲሰጥበት የነበረው ህንጻ የፈረሰበት የልዩ ህክምና ክሊኒክ፣ አቅሙንና የህክምና መገልገያ መሳሪያዎቹን በከፍተኛ ደረጃ በማዘመን በአዲስ መልክ ተመርቆ ስራ ጀመረ።
ክሊኒኩ በአሁኑ ወቅት አገልግሎቱን በስፋት መቀጠል የጀመረው በየካ ክፍለ ከተማ፣ ታቦት ማደሪያ እግር ኳስ ሜዳ አጠገብ ባስገነባው ባለ 22 ክፍል ዘመናዊ ህንጻ ላይ መሆኑ ታውቋል።
የተቋሙ መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ዳዊት አማረ በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ እንደገለጹት፤ ክሊኒኩ የገጠመውን ፈተና ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር በይዘቱም ሆነ በህክምና መገልገያ መሳሪያዎች እራሱን በከፍተኛ ደረጃ ማዘመን ችሏል።
ተቋሙ በተለይም በውስጥ ደዌ እና በሳንባ ስፔሻሊስት (Pulmonology) የህክምና ዘርፎች ላይ ትኩረት አድርጎ ጥራት ያለው አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን፣ ለድንገተኛና ለአስቸኳይ ህክምና ፈላጊዎችም ቀልጣፋ አደረጃጀት ማዘጋጀቱን ገልጸዋል።
"ጤና የእያንዳንዱ ሰው መሰረታዊ መብት ነው" ያሉት ዶክተር ዳዊት፤ ባለፉት ስድስት ዓመታት በርካታ ታካሚዎችን በታማኝነት ሲያገለግሉ መቆየታቸውንና አሁንም ማህበረሰቡን በተሻለ ጥራትና ምቾት ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን አብራርተዋል።
አዲሱ ህንፃ የህክምና ተቋም ሊያሟላቸው የሚገቡ መስፈርቶችን ሙሉ በሙሉ ያሟላ ከመሆኑም በላይ፣ ህፃናትን ጨምሮ ማንኛውንም ታካሚ በተገቢው ሁኔታ ለማስተናገድ የሚያስችሉ ባለሙያዎችና ዘመናዊ ግብዓቶች ተጠናቀውለታል። ተቋሙ በኮሪደር ልማት ምክንያት ቢፈርስም፣ ላለፉት 14 ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥበት በነበረው በዚሁ አካባቢ ለታካሚዎች ምቹ በሆነ ስፍራ ላይ በላቀ አደረጃጀት ዳግም ስራ መጀመሩ ተገልጿል።
ይህ የልዩ ህክምና ክሊኒክ ለ56 የህክምና ባለሙያዎች የስራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 23 የሚሆኑ ስፔሻሊስት እና ሰብ-ስፔሻሊስት ዶክተሮችን በማሳተፍ ላይ ይገኛል። በጥናት ማጠቃለያውም ላይ ክሊኒኩ ባለፉት ዓመታት አብረዋቸው ለቆሙ ታካሚዎች እና በአስቸጋሪ ወቅቶች ስራው ሳይስተጓጎል ድጋፍ ላደረጉ ባልደረቦቹ ከፍተኛ ምስጋና አቅርቧል።
4 days ago
የቤት ፈላጊዎችን ጥያቄ ለመመለስ 24/7 በትጋት ላይ ነን!
********
ከ25 ዓመታት በላይ በታማኝነት፣ በጥራትና በተከበረ ስም የተገነባ የስኬት ታሪክ ፈጥረናል!
በሲኤምሲ መንደር 1 እና 2 እንዲሁም በፈረስ ቤት መንደር 3 ቤቶችን ብቻ ሳይሆን የተሟላ ማህበረሰብ ፈጥረናል!
አሁንም በአዲስ አበባ በለገሃር፣ በቦሌ፣ በአትላስ፣ በተ/ሃይማኖት፣ በ22 ማዞሪያ፣ በሲኤምሲና በፈረስ ቤት ሕይወት የሚያብብበት፣ ቤተሰብ የሚያድግበት አካባቢ በጥራት እየገነባን ነው!
በነዚህ መንደሮች የጊፍት ማህበረሰብ አካል ይሁኑ!
ጊፍት ሪል ስቴት
ማህበረሰብ እንገነባለን!
ለበለጠ መረጃ፤
📞 +251 984 6565 65 / +251 979 6565 65
🌐 https://www.giftrealestate...
8 days ago
ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የድምፅ መስጫ ቀንን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ እንዲከናወን መወሠኑ ይታወቃል።
በዚህም መሠረት በመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ሁሉ በዕለቱ ድምፃቸውን ለመስጠት ይችሉ ዘንድ እና የደምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ያለምንም የፀጥታ ችግር ይከናወን ዘንድ ቦርዱ የሚከተሉት ተግባራዊ እንዲሆኑ የምርጫ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/ 2011 አንቀጽ 161 የመተባበር ግዴታ መሠረት ለመንግሥታዊ እና ለማንኛውም መንግሥታዊ ላልሆኑ ተቋማት ያሳውቃል።
በዚህም መሠረት:-
- ዜጎች ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ የፌዴራል እና የክልል መንግሥታዊ ተቋማት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ሥራ ዝግ እንዲያደርጉ፣
- ዜጎች ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ በፌዴራል እና በክልሎች የሚገኙ ማንኛውም መንግሥታዊ ያልሆኑ እና የግል ተቋማት በተመሳሳይ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ዝግ እንዲያደርጉ እያሳወቀ፤
- የአስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት፣ ሆስፒታሎች፣ የዕለት ተዕለት አገልግሎት ሰጪዎችም (ሆቴሎች፣ ሬስቶራንቶች፣ የትራንስፓርት አገልግሎት) በዝግ ቀናት የሚያደርጉትን አገልግሎት በተመሳሳይ የሚያከናውኑ ሲሆን፤ የመተባበር ግዴታው እነዚህን ተቋማት እንቅስቃሴ መዘጋት አያስገድድም።
- የትራንስፓርት አገልግሎት በተለመደው መንገድ የሚቀጥል ቢሆንም፤ ዜጎች ድምፅ ከመስጠት ውጪ ከፍተኛ እንቅስቃሴን የሚፈልጉ ሁነቶችን እና ዕቅዶችን እንዳይይዙ እና እንቅስቃሴያቸውን ድምፅ ለመስጠት ብቻ እንዲያደርጉ ቦርዱ ያበረታታል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም.
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ እንዲከናወን መወሠኑ ይታወቃል።
በዚህም መሠረት በመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ሁሉ በዕለቱ ድምፃቸውን ለመስጠት ይችሉ ዘንድ እና የደምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ያለምንም የፀጥታ ችግር ይከናወን ዘንድ ቦርዱ የሚከተሉት ተግባራዊ እንዲሆኑ የምርጫ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/ 2011 አንቀጽ 161 የመተባበር ግዴታ መሠረት ለመንግሥታዊ እና ለማንኛውም መንግሥታዊ ላልሆኑ ተቋማት ያሳውቃል።
በዚህም መሠረት:-
- ዜጎች ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ የፌዴራል እና የክልል መንግሥታዊ ተቋማት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ሥራ ዝግ እንዲያደርጉ፣
- ዜጎች ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ በፌዴራል እና በክልሎች የሚገኙ ማንኛውም መንግሥታዊ ያልሆኑ እና የግል ተቋማት በተመሳሳይ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ዝግ እንዲያደርጉ እያሳወቀ፤
- የአስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት፣ ሆስፒታሎች፣ የዕለት ተዕለት አገልግሎት ሰጪዎችም (ሆቴሎች፣ ሬስቶራንቶች፣ የትራንስፓርት አገልግሎት) በዝግ ቀናት የሚያደርጉትን አገልግሎት በተመሳሳይ የሚያከናውኑ ሲሆን፤ የመተባበር ግዴታው እነዚህን ተቋማት እንቅስቃሴ መዘጋት አያስገድድም።
- የትራንስፓርት አገልግሎት በተለመደው መንገድ የሚቀጥል ቢሆንም፤ ዜጎች ድምፅ ከመስጠት ውጪ ከፍተኛ እንቅስቃሴን የሚፈልጉ ሁነቶችን እና ዕቅዶችን እንዳይይዙ እና እንቅስቃሴያቸውን ድምፅ ለመስጠት ብቻ እንዲያደርጉ ቦርዱ ያበረታታል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም.
Sponsored by
Surafel
8 days ago
ቀኝ አዝማች በኩረ ምዕመናን ትዛዙ ኮሬ የኢትዮጵያን ባህል፣ ቱሪዝምና በጎ አድራጎት በማስፋፋት የሚታወቁ ታዋቂ ኢንተርፕረነር፣ የባህል አምባሳደር እና ሀገር በቀል ሽማግሌ ናቸው። በተለይም በኢትዮጵያ የመጀመሪያዎቹን እና ግዙፍ የባህል ምግብ ቤቶች አንዱ የሆነውን ዮድ አቢሲኒያ (Yod Abyssinia) ባህላዊ ምግብ ቤት በመመስረታቸው በሰፊው ይታወቃሉ።
ስለ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ዋና ዋና መረጃዎች
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና ባለቤት በ1996 ዓ.ም.
(እ.ኤ.አ. በ2003) ዮድ አቢሲኒያ ባህላዊ ምግብ ቤትን መስርተዋል።
ምግብ ቤቱ የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦች ባህላዊ ምግቦች፣ ሙዚቃዎች እና ውዝዋዜዎች ለአገር ውስጥና ለውጭ አገር ዜጎች በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ ሚና አለው።
እንደ የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ያሉ በርካታ የዓለም መሪዎችን እና የውጭ አገር ዲፕሎማቶችን በምግብ ቤታቸው አስተናግደዋል።
❸ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ለተለያዩ የሃይማኖት ተቋማት እና ችግረኛ ወገኖች ከፍተኛ ድጋፍ በማድረግ ይታወቃሉ።
በበጎ አድራጎት ሥራዎቻቸው ምክንያት በ2016 ዓ.ም የፊላንትሮፒ (የበጎ አድራጎት) ሽልማት አሸናፊ ሆነዋል።
በማኅበረሰቡ ውስጥ ሰላምን ለማስፈንና እርቅ ለማውረድ እንደ ትልቅ የሀገር ሽማግሌ ሆነው ያገለግላሉ።
በጎ ተግባራት እና ማህበራዊ ሀላፊነት በመወጣት አርዓያነት ያለዉን ተግባራት በመስራት ይታወቃል።
የዓመቱን 360 ቀናት ለኢትዮጵያ ሀገራቸዉ እንዲሁም 4 ቀናት ለበጎ አድራጎት ተግባራት ሲውል ፤ 365 ኛውን ቀን ደግሞ ዕድገት እንደሚያስተዋዉቅ የሚያምኑት የድርጅቱ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ናቸዉ።
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ እንዲሁም ድርጅታቸዉ 'ዮድ አቢሲኒያ'ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር፣ ለሜሪጆይ ኢትዮጵያ ፣ ለቶራ የህፃናት ማሳደጊያ ፣ ለሰሊሆም የአእምሮ ህሙማን መርጃ ፣ ለየወደቁትን እናንሳ የአረጋውያን መርጃ ማህበር ለሌሎችም በማገዝና በመርዳት ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት በጎ ስምና አርዓያነትን በተግባር ለማሳየት ችሏል።ወደፊትም ይበልጥ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
❹እዉቅናና ሽልማት
➢የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና
ጳጉሜ 3 ቀን 2016 ዓ.ም ለ12ኛ ጊዜ በተካሄደዉ የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና በቅርስ ባህል እና ቱሪዝም ዘርፍ ዮድ አቢሲኒያ፡የባሕል ምግብ አዳራሽ ተሸልሟል።
የኢትዮጵያን ባህላዊ ምግቦችን ፤ ውዝዋዜዎችን እና ባህላዊ እሴቶችን ለቱሪስቶች እና ማህበረሰቡ የሚያቀርብ ተቋም ሲሆን የኢትዮጵያን እሴቶችን በማስተዋወቅ ረገድ ያስቀመጠው ደማቅ አሻራ ከፍ ያለ ነዉ።
ዮድ አቢሲኒያ ባህል ባንድ
ለቱሪስቶች የአገራችንን ብሔር ብሔረሰቦች ሙዚቃዎች ዉዝዋዜን በማሳየት ቱባ ባህላችንን ሳይበረዝና ሳይከለስ ያሳያል።
➢ የቱሪዝም አዋርድ
የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ሐምሌ 6/2016ዓ.ም በአድዋ መታሰብያ ሙዚየም ባካሄደው የኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤት ምስረታና 1ኛ መደበኛ ጉባኤ ለከተማችን የቱሪዝም ልማትና እድገት የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉ የቱሪዝም ተቋማትና አካላት የቱሪዝም አዋርድ ከተሰጡት መካከል አንዱ ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ ነዉ።
የቱሪዝም ተቋማቱ በሚሰጡት የአገልግሎት ጥራት ባላቸው የቱሪዝም ፈጠራ ስራ እንዲሁም የቱሪስት አያያዝና የመሳሰሉት መስፈርቶችን መነሻ በማድረግ ከዘርፉ 1ኛ በመዉጣት ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ፣የቱሪዝም አዋርድ ተሸልሟል።
➢"የ8ኛዉ የአርአያ ሰው ሽልማት"
ተቀማጭነቱን በሀገረ አሜሪካ ዳላስ ቴክሳስ ያደረገው ዓድዋ የባህልና የታሪክ ኅብረት ለትርፍ ያልተቋቋመ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን በዋናነትም ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን አርአያ የሚሆን ሥራ ለሚሠሩ ግለሰቦችና ተቋማት"የአርአያ ሰው ሽልማት" በሚል ዕውቅና ይሰጣል፡፡
ለ8ኛ ግዜ በአዲስ አበባ ዮድ አቢሲኒያ የባህል አዳራሽ ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም በተመሳሳይ መልኩ ለሀገር ባለውለታዎች በተለይም በባህል ልማት፣ በተፈጥሮ ጥበቃ፣ በቱሪዝም እና ቅርስ እንዲሁም በታሪክ መስኮች ለሀገራቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦችና ተቋማት ሽልማት ከተሰጣቸው መካከል ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ አንዱ ነዉ።
ዓለም አቀፍ እውቅና
የኢትዮጵያን ባህልና ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቃቸው “የባህልና ቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ክብር ተሰጥቷቸዋል።
በቅርቡ (እ.ኤ.አ በ2025) በአሜሪካ ሲያትል በተካሄደው የ42ኛው የኢትዮጵያውያን የስፖርትና ባህል ፌስቲቫል (ESFNA) ላይ ለሀገራቸው ላበረከቱት የላቀ አስተዋፅኦ ልዩ የክብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
❺ዋና ዋና ቅርንጫፎችና አድራሻዎች
ዮድ አቢሲኒያ በአዲስ አበባ በተለያዩ ቁልፍ ቦታዎች ቅርንጫፎችን ከፍቶ ይገኛል፦
ቦሌ ቅርንጫፍ (ዋናው)፦ ቦሌ መድኃኔዓለም አካባቢ፣ ከብራስ ሆስፒታል ከፍ ብሎ የሚገኝ የነበረ ሲሆን አሁን ቀድሞ ከነበረበት በ100 ሜትር ገባ ብሎ ኬኬር ህንፃ አጠገብ ይገኛል።ለቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቅርብ በመሆኑ ለቱሪስቶች ተመራጭ ነው።
ፒያሳ (ቴዎድሮስ አደባባይ) ቅርንጫፍ፦ በቅርቡ በዲል ፕላዛ ፊት ለፊት የተከፈተ አዲስና ዘመናዊ የባህል አዳራሽ፣ የስፖርት ባር (Sport Bar) እና የባዛር ማዕከል ነው።
ዮድ አቢሲኒያ ኢንተርናሽናል ሆቴል፦ ሰዓሊተ ምህረት አደባባይ ከፍ ብሎ፣ ወደ ወሰን በሚወስደው መንገድ ማዕድን ሚኒስቴር አጠገብ የሚገኝ ዘመናዊ ሆቴል ነው።
❻የ"ዮድ" መሪ ቃል በተግባር
የድርጅቱ መሪ ቃል የሃገራችን ኢትዮጵያን ”ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ” የሚል ነው ባለፉት 22 ዓመታት የኢትዮጵያን ባህልና መስተንግዶን ጨምሮ ሲያስተዋውቅ ኖሯል ፡፡ ለዚህም አስተዋፅኦው ”የኢትዮጵያ የባህልና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ዕውቅና ከመንግስት ተሰጥቶታል ፡፡
“ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ” በሚል መርህ ከመላው ዓለም ወደ ሃገራችን ለመጡ እንግዶች የባህል ምግብና መጠጦች መስተንግዶ በመስጠት ፣ የብሔር ብሄረሰቦችን ሙዚቃዎችና ውዝዋዜዎች በማቅረብ ፣ የሀገራችንን የታሪክ የባህልና የቱሪዝም ሃብቶችና ቅርሶቻችንን በማስተዋወቅ የኢትዮጵያን መልካም ገፅታ በመገንባት ብዙ በመስራት ”የኢትዮጵያ የባህል እና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል እውቅናን ለማግኘት ችሏል፡፡
"ዮድ"
ዮድ ብሂል የማነ እግዚአብሔር ገብረት ኃይለ
በእግዚአብሔር ቀኝ ያለ እሱ ኃያልና
ጽኑዕ የሆነ ነው ማለት በሌላ መልኩ"ዮድ" ማለት በጉራጌ ቋንቋ "መመስከር ወይም መናገር" ማለት ነዉ።
ከ1996ዓ.ምማለትምላለፉት 22 ዓመታት በተለያዩ ወቅቶች ወደ ሀገራችን የመጡ በርካታ የሀገራት መሪዎችን ፣ ዲፕሎማቶችን ፣ የዓለም ታላላቅ ሰዎችን፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ፣ ታዋቂ ሰዎች ፣ ባለሀብቶች ፣ አትሌቶች ፣ አርቲስቶች የሚዲያ ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎችም በሺዎች የሚቆጠሩ ቱሪስቶችንና ኢትዮጵያዊያን እንግዶችን ተቀብሎ በፍቅርና በአክብሮት ሲያስተናግድ የቆየው ዮድ አቢሲኒያ በቀጣይም በሀገራችን ለሚከናወኑ ታላላቅ ሁነቶች ሙሉ አገልግሎት ለመስጠት ከወትሮው በተለዬ አኳኋን መዘጋጀቱ ተስተዉሏል።በ500 ብር ካፒታል እና በአነስተኛ የስራ ጅምር በጥረት የተገነባ ካምፓኒ በበርካታ ፈተናዎች ዉስጥ አልፎ ዛሬ በርካታ ቁጥር ላላቸዉ ወገኖቻችን የስራ ዕድል መፍጠር የቻለ ግዙፍ ኩባንያ ለመሆን በቅቷል።
"የሃገራችን ኢትዮጵያን ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ”ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ
ዘጋቢ ጋዜጠኛ ሲሳይ መንግስቴ
ስለ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ዋና ዋና መረጃዎች
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና ባለቤት በ1996 ዓ.ም.
(እ.ኤ.አ. በ2003) ዮድ አቢሲኒያ ባህላዊ ምግብ ቤትን መስርተዋል።
ምግብ ቤቱ የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦች ባህላዊ ምግቦች፣ ሙዚቃዎች እና ውዝዋዜዎች ለአገር ውስጥና ለውጭ አገር ዜጎች በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ ሚና አለው።
እንደ የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ያሉ በርካታ የዓለም መሪዎችን እና የውጭ አገር ዲፕሎማቶችን በምግብ ቤታቸው አስተናግደዋል።
❸ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ለተለያዩ የሃይማኖት ተቋማት እና ችግረኛ ወገኖች ከፍተኛ ድጋፍ በማድረግ ይታወቃሉ።
በበጎ አድራጎት ሥራዎቻቸው ምክንያት በ2016 ዓ.ም የፊላንትሮፒ (የበጎ አድራጎት) ሽልማት አሸናፊ ሆነዋል።
በማኅበረሰቡ ውስጥ ሰላምን ለማስፈንና እርቅ ለማውረድ እንደ ትልቅ የሀገር ሽማግሌ ሆነው ያገለግላሉ።
በጎ ተግባራት እና ማህበራዊ ሀላፊነት በመወጣት አርዓያነት ያለዉን ተግባራት በመስራት ይታወቃል።
የዓመቱን 360 ቀናት ለኢትዮጵያ ሀገራቸዉ እንዲሁም 4 ቀናት ለበጎ አድራጎት ተግባራት ሲውል ፤ 365 ኛውን ቀን ደግሞ ዕድገት እንደሚያስተዋዉቅ የሚያምኑት የድርጅቱ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ናቸዉ።
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ እንዲሁም ድርጅታቸዉ 'ዮድ አቢሲኒያ'ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር፣ ለሜሪጆይ ኢትዮጵያ ፣ ለቶራ የህፃናት ማሳደጊያ ፣ ለሰሊሆም የአእምሮ ህሙማን መርጃ ፣ ለየወደቁትን እናንሳ የአረጋውያን መርጃ ማህበር ለሌሎችም በማገዝና በመርዳት ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት በጎ ስምና አርዓያነትን በተግባር ለማሳየት ችሏል።ወደፊትም ይበልጥ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
❹እዉቅናና ሽልማት
➢የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና
ጳጉሜ 3 ቀን 2016 ዓ.ም ለ12ኛ ጊዜ በተካሄደዉ የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና በቅርስ ባህል እና ቱሪዝም ዘርፍ ዮድ አቢሲኒያ፡የባሕል ምግብ አዳራሽ ተሸልሟል።
የኢትዮጵያን ባህላዊ ምግቦችን ፤ ውዝዋዜዎችን እና ባህላዊ እሴቶችን ለቱሪስቶች እና ማህበረሰቡ የሚያቀርብ ተቋም ሲሆን የኢትዮጵያን እሴቶችን በማስተዋወቅ ረገድ ያስቀመጠው ደማቅ አሻራ ከፍ ያለ ነዉ።
ዮድ አቢሲኒያ ባህል ባንድ
ለቱሪስቶች የአገራችንን ብሔር ብሔረሰቦች ሙዚቃዎች ዉዝዋዜን በማሳየት ቱባ ባህላችንን ሳይበረዝና ሳይከለስ ያሳያል።
➢ የቱሪዝም አዋርድ
የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ሐምሌ 6/2016ዓ.ም በአድዋ መታሰብያ ሙዚየም ባካሄደው የኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤት ምስረታና 1ኛ መደበኛ ጉባኤ ለከተማችን የቱሪዝም ልማትና እድገት የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉ የቱሪዝም ተቋማትና አካላት የቱሪዝም አዋርድ ከተሰጡት መካከል አንዱ ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ ነዉ።
የቱሪዝም ተቋማቱ በሚሰጡት የአገልግሎት ጥራት ባላቸው የቱሪዝም ፈጠራ ስራ እንዲሁም የቱሪስት አያያዝና የመሳሰሉት መስፈርቶችን መነሻ በማድረግ ከዘርፉ 1ኛ በመዉጣት ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ፣የቱሪዝም አዋርድ ተሸልሟል።
➢"የ8ኛዉ የአርአያ ሰው ሽልማት"
ተቀማጭነቱን በሀገረ አሜሪካ ዳላስ ቴክሳስ ያደረገው ዓድዋ የባህልና የታሪክ ኅብረት ለትርፍ ያልተቋቋመ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን በዋናነትም ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን አርአያ የሚሆን ሥራ ለሚሠሩ ግለሰቦችና ተቋማት"የአርአያ ሰው ሽልማት" በሚል ዕውቅና ይሰጣል፡፡
ለ8ኛ ግዜ በአዲስ አበባ ዮድ አቢሲኒያ የባህል አዳራሽ ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም በተመሳሳይ መልኩ ለሀገር ባለውለታዎች በተለይም በባህል ልማት፣ በተፈጥሮ ጥበቃ፣ በቱሪዝም እና ቅርስ እንዲሁም በታሪክ መስኮች ለሀገራቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦችና ተቋማት ሽልማት ከተሰጣቸው መካከል ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ አንዱ ነዉ።
ዓለም አቀፍ እውቅና
የኢትዮጵያን ባህልና ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቃቸው “የባህልና ቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ክብር ተሰጥቷቸዋል።
በቅርቡ (እ.ኤ.አ በ2025) በአሜሪካ ሲያትል በተካሄደው የ42ኛው የኢትዮጵያውያን የስፖርትና ባህል ፌስቲቫል (ESFNA) ላይ ለሀገራቸው ላበረከቱት የላቀ አስተዋፅኦ ልዩ የክብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
❺ዋና ዋና ቅርንጫፎችና አድራሻዎች
ዮድ አቢሲኒያ በአዲስ አበባ በተለያዩ ቁልፍ ቦታዎች ቅርንጫፎችን ከፍቶ ይገኛል፦
ቦሌ ቅርንጫፍ (ዋናው)፦ ቦሌ መድኃኔዓለም አካባቢ፣ ከብራስ ሆስፒታል ከፍ ብሎ የሚገኝ የነበረ ሲሆን አሁን ቀድሞ ከነበረበት በ100 ሜትር ገባ ብሎ ኬኬር ህንፃ አጠገብ ይገኛል።ለቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቅርብ በመሆኑ ለቱሪስቶች ተመራጭ ነው።
ፒያሳ (ቴዎድሮስ አደባባይ) ቅርንጫፍ፦ በቅርቡ በዲል ፕላዛ ፊት ለፊት የተከፈተ አዲስና ዘመናዊ የባህል አዳራሽ፣ የስፖርት ባር (Sport Bar) እና የባዛር ማዕከል ነው።
ዮድ አቢሲኒያ ኢንተርናሽናል ሆቴል፦ ሰዓሊተ ምህረት አደባባይ ከፍ ብሎ፣ ወደ ወሰን በሚወስደው መንገድ ማዕድን ሚኒስቴር አጠገብ የሚገኝ ዘመናዊ ሆቴል ነው።
❻የ"ዮድ" መሪ ቃል በተግባር
የድርጅቱ መሪ ቃል የሃገራችን ኢትዮጵያን ”ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ” የሚል ነው ባለፉት 22 ዓመታት የኢትዮጵያን ባህልና መስተንግዶን ጨምሮ ሲያስተዋውቅ ኖሯል ፡፡ ለዚህም አስተዋፅኦው ”የኢትዮጵያ የባህልና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ዕውቅና ከመንግስት ተሰጥቶታል ፡፡
“ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ” በሚል መርህ ከመላው ዓለም ወደ ሃገራችን ለመጡ እንግዶች የባህል ምግብና መጠጦች መስተንግዶ በመስጠት ፣ የብሔር ብሄረሰቦችን ሙዚቃዎችና ውዝዋዜዎች በማቅረብ ፣ የሀገራችንን የታሪክ የባህልና የቱሪዝም ሃብቶችና ቅርሶቻችንን በማስተዋወቅ የኢትዮጵያን መልካም ገፅታ በመገንባት ብዙ በመስራት ”የኢትዮጵያ የባህል እና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል እውቅናን ለማግኘት ችሏል፡፡
"ዮድ"
ዮድ ብሂል የማነ እግዚአብሔር ገብረት ኃይለ
በእግዚአብሔር ቀኝ ያለ እሱ ኃያልና
ጽኑዕ የሆነ ነው ማለት በሌላ መልኩ"ዮድ" ማለት በጉራጌ ቋንቋ "መመስከር ወይም መናገር" ማለት ነዉ።
ከ1996ዓ.ምማለትምላለፉት 22 ዓመታት በተለያዩ ወቅቶች ወደ ሀገራችን የመጡ በርካታ የሀገራት መሪዎችን ፣ ዲፕሎማቶችን ፣ የዓለም ታላላቅ ሰዎችን፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ፣ ታዋቂ ሰዎች ፣ ባለሀብቶች ፣ አትሌቶች ፣ አርቲስቶች የሚዲያ ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎችም በሺዎች የሚቆጠሩ ቱሪስቶችንና ኢትዮጵያዊያን እንግዶችን ተቀብሎ በፍቅርና በአክብሮት ሲያስተናግድ የቆየው ዮድ አቢሲኒያ በቀጣይም በሀገራችን ለሚከናወኑ ታላላቅ ሁነቶች ሙሉ አገልግሎት ለመስጠት ከወትሮው በተለዬ አኳኋን መዘጋጀቱ ተስተዉሏል።በ500 ብር ካፒታል እና በአነስተኛ የስራ ጅምር በጥረት የተገነባ ካምፓኒ በበርካታ ፈተናዎች ዉስጥ አልፎ ዛሬ በርካታ ቁጥር ላላቸዉ ወገኖቻችን የስራ ዕድል መፍጠር የቻለ ግዙፍ ኩባንያ ለመሆን በቅቷል።
"የሃገራችን ኢትዮጵያን ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ”ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ
ዘጋቢ ጋዜጠኛ ሲሳይ መንግስቴ
8 days ago
ተለያይቻለሁ !!!
ውድ ወዳጆቼ…
ከዛሬ ዘጠኝ ወራት በፊት ከቻናል ዋን የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር የጣቢያው “Creative Director” በመሆን የሥራ ውል ማሰሬንና ሥራ መጀመሬን በማህበራዊ ሚዲያ መግለጼ ይታወሳል።
ሥራ ከጀመርኩበት ቅጽበት ጀምሮ ጣቢያው የቅዳሜ ሾው ያልነበረው በመሆኑ “ቅዳሜኛ” የተሰኘ የመዝናኛና መረጃ (Magazine Format Infotainment Weekly Show) ፕሮግራም ሙሉ በሙሉ በመፍጠርና በማዘጋጀት ላለፉት 6 ወራት በአየር ላይ ቆይቷል። በአጭር ጊዜም ከተመልካቾች ዘንድ እውቅናና ተወዳጅነት ማግኘት ችሏል።
“ቅዳሜኛ” የ3 ሰዓት ቆይታ ያለው ሲሆን በዚህ ቆይታው ውስጥ “ቁራሌው”፣ “ከመወሰንዎ በፊት”፣ “ወጌሻ”፣ “ቢሆንስ”፣ “ቻሌንጅ አንድ”፣ “ሸርሸር”፣ “ለማጅ”፣ “ጨዋታ አንድ”፣ “በላተኞቹ” እና “አቃቂር” የተሰኙ አስተማሪና አዝናኝ ይዘቶችን በመፍጠርና በማዘጋጀት ሰርቻለሁ። እንዲሁም በበዓላት ወቅት የተላለፉ የበዓል ሪያሊቲ ሾዎችንም በመፍጠርና በማዘጋጀት ተሳትፌያለሁ።
ከዚህ በተጨማሪም ለሜንስትሪም ሚዲያው አዲስ የሆኑ ነገር ግን ተሰጥኦ ያላቸው ፕሮግራም አቅራቢዎች አቅማቸውን እንዲያወጡ እድል ከመስጠት ባለፈ፣ ሙያው የሚጠይቀውን ሥነ ምግባር ተከትለው በኃላፊነት እንዲሠሩ ድጋፍና ክትትል ለማድረግ ሞክሬያለሁ።
ሲቀጥል…
አሁን ከዘጠኝ ወራት ቆይታ በኋላ ከጣቢያው ጋር የነበረኝን ውል ማቋረጤን እየገለጽኩ፣ በነበረን የሥራ ጊዜ በትጋትና በመረዳዳት አብረውኝ ለነበሩ የ“ቅዳሜኛ” ሾው አባላት፣ የተቋሙ ካሜራማኖችና ኤዲተሮች ላሳያችሁኝ አክብሮትና ቀናነት ከልብ እያመሰገንኩ ወደፊትም መልካም የሥራ ጊዜ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።
እንዲሁም በጣቢያው ላይ ይተላለፉ የነበሩ ፕሮግራሞችን በመከታተል በተለያየ መንገድ ጠቃሚ አስተያየቶችን ትሰጡኝ የነበራችሁ ወዳጆቼንም በተለይ ማመስገን እወዳለሁ።
አክባሪያችሁ
ሳምሶን ከበደ
Film writer & director | producer|creative director | host
ውድ ወዳጆቼ…
ከዛሬ ዘጠኝ ወራት በፊት ከቻናል ዋን የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር የጣቢያው “Creative Director” በመሆን የሥራ ውል ማሰሬንና ሥራ መጀመሬን በማህበራዊ ሚዲያ መግለጼ ይታወሳል።
ሥራ ከጀመርኩበት ቅጽበት ጀምሮ ጣቢያው የቅዳሜ ሾው ያልነበረው በመሆኑ “ቅዳሜኛ” የተሰኘ የመዝናኛና መረጃ (Magazine Format Infotainment Weekly Show) ፕሮግራም ሙሉ በሙሉ በመፍጠርና በማዘጋጀት ላለፉት 6 ወራት በአየር ላይ ቆይቷል። በአጭር ጊዜም ከተመልካቾች ዘንድ እውቅናና ተወዳጅነት ማግኘት ችሏል።
“ቅዳሜኛ” የ3 ሰዓት ቆይታ ያለው ሲሆን በዚህ ቆይታው ውስጥ “ቁራሌው”፣ “ከመወሰንዎ በፊት”፣ “ወጌሻ”፣ “ቢሆንስ”፣ “ቻሌንጅ አንድ”፣ “ሸርሸር”፣ “ለማጅ”፣ “ጨዋታ አንድ”፣ “በላተኞቹ” እና “አቃቂር” የተሰኙ አስተማሪና አዝናኝ ይዘቶችን በመፍጠርና በማዘጋጀት ሰርቻለሁ። እንዲሁም በበዓላት ወቅት የተላለፉ የበዓል ሪያሊቲ ሾዎችንም በመፍጠርና በማዘጋጀት ተሳትፌያለሁ።
ከዚህ በተጨማሪም ለሜንስትሪም ሚዲያው አዲስ የሆኑ ነገር ግን ተሰጥኦ ያላቸው ፕሮግራም አቅራቢዎች አቅማቸውን እንዲያወጡ እድል ከመስጠት ባለፈ፣ ሙያው የሚጠይቀውን ሥነ ምግባር ተከትለው በኃላፊነት እንዲሠሩ ድጋፍና ክትትል ለማድረግ ሞክሬያለሁ።
ሲቀጥል…
አሁን ከዘጠኝ ወራት ቆይታ በኋላ ከጣቢያው ጋር የነበረኝን ውል ማቋረጤን እየገለጽኩ፣ በነበረን የሥራ ጊዜ በትጋትና በመረዳዳት አብረውኝ ለነበሩ የ“ቅዳሜኛ” ሾው አባላት፣ የተቋሙ ካሜራማኖችና ኤዲተሮች ላሳያችሁኝ አክብሮትና ቀናነት ከልብ እያመሰገንኩ ወደፊትም መልካም የሥራ ጊዜ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።
እንዲሁም በጣቢያው ላይ ይተላለፉ የነበሩ ፕሮግራሞችን በመከታተል በተለያየ መንገድ ጠቃሚ አስተያየቶችን ትሰጡኝ የነበራችሁ ወዳጆቼንም በተለይ ማመስገን እወዳለሁ።
አክባሪያችሁ
ሳምሶን ከበደ
Film writer & director | producer|creative director | host
8 days ago
በመጪው ሰኞ የሚካሄደዉን ሰባተኛውን አጠቃላይ ምርጫን የሚታዘቡ የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢዎች አዲስ አበባ መግባታቸውን ኅብረቱ አስታወቀ።
በቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመራው የኅብረቱ ታዛቢዎች ከ37 አገራት የተውጣጡ እና 73 አባላትን የያዘ መሆኑን በመግለጫው ላይ ተገልጿል።
የአፍሪካ ኅብረት ማክሰኞ ግንቦት 18/2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ የምርጫ ታዛቢዎች በምርጫው ዕለት የድምጽ አሰጣጥ ሂደትን እና ቆጠራን ለመታዘብ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የሚሰማሩ መሆኑ አስታውቋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመላ አገሪቱ ሰኞ ግንቦት 24 የሚደረገውን ሰባተኛው ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ ለመታዘብ ከአፍሪካ ኅብረት ታዛቢዎች በተጨማሪ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) ታዛቢዎች እንደሚገኙ አስታውቋል።
የአፍሪካ ብረት እና የኢጋድ የምርጫ ታዛቢዎች ወደ ኢትዮጵያ የመጡት በኢትዮጵያ መንግሥት ግብዣ መሠረት መሆኑን የምርጫ ቦርድ እና ኅብረቱ አስታውቀዋል።
የምርጫ ታዛቢ ቡድኑ ግምገማውን በኢትዮጵያ የምርጫ ሕግ፣ በአፍሪካ ኅብረት እንዲሁም አስፈላጊ በሆኑ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ለማድረግ በተቀመጡ መስፈርቶች ላይ በመመሥረት ግምገማውን እንደሚያደርግ ተገልጿል።
ታዛቢዎቹ ከምርጫ ቦርድ፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ከዕጩዎች፣ ከመገናኛ ብዙኃን እንዲሁም ከሌሎች የምርጫ ታዛቢዎች ጋር በትብብር እንደሚሠሩ ተጠቅሷል።
ታዛቢ ቡድኑ የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን ግንቦት 26/2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ይፋ የሚያደርግ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ የመጨረሻ ሪፖርቱን ደግሞ ከምርጫው በኋላ በሁለት ወር ውስጥ ያቀርባል ተብሏል።
የኢትዮጵያ ሲቪክ ማኅበራት ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለመታዘብ ከ500 በላይ የሚሆኑ የረጅም ጊዜ ታዛቢዎችን ማሰማራታቸውን አስታውቀዋል።
በቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚመራው የኅብረቱ ታዛቢዎች ከ37 አገራት የተውጣጡ እና 73 አባላትን የያዘ መሆኑን በመግለጫው ላይ ተገልጿል።
የአፍሪካ ኅብረት ማክሰኞ ግንቦት 18/2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ የምርጫ ታዛቢዎች በምርጫው ዕለት የድምጽ አሰጣጥ ሂደትን እና ቆጠራን ለመታዘብ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የሚሰማሩ መሆኑ አስታውቋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመላ አገሪቱ ሰኞ ግንቦት 24 የሚደረገውን ሰባተኛው ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ ለመታዘብ ከአፍሪካ ኅብረት ታዛቢዎች በተጨማሪ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት (ኢጋድ) ታዛቢዎች እንደሚገኙ አስታውቋል።
የአፍሪካ ብረት እና የኢጋድ የምርጫ ታዛቢዎች ወደ ኢትዮጵያ የመጡት በኢትዮጵያ መንግሥት ግብዣ መሠረት መሆኑን የምርጫ ቦርድ እና ኅብረቱ አስታውቀዋል።
የምርጫ ታዛቢ ቡድኑ ግምገማውን በኢትዮጵያ የምርጫ ሕግ፣ በአፍሪካ ኅብረት እንዲሁም አስፈላጊ በሆኑ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ለማድረግ በተቀመጡ መስፈርቶች ላይ በመመሥረት ግምገማውን እንደሚያደርግ ተገልጿል።
ታዛቢዎቹ ከምርጫ ቦርድ፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ከዕጩዎች፣ ከመገናኛ ብዙኃን እንዲሁም ከሌሎች የምርጫ ታዛቢዎች ጋር በትብብር እንደሚሠሩ ተጠቅሷል።
ታዛቢ ቡድኑ የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን ግንቦት 26/2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ይፋ የሚያደርግ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ የመጨረሻ ሪፖርቱን ደግሞ ከምርጫው በኋላ በሁለት ወር ውስጥ ያቀርባል ተብሏል።
የኢትዮጵያ ሲቪክ ማኅበራት ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ለመታዘብ ከ500 በላይ የሚሆኑ የረጅም ጊዜ ታዛቢዎችን ማሰማራታቸውን አስታውቀዋል።
9 days ago
በምርጫ ተሳትፎ ዙሪያ በኢሕአፓ አባላት መካከል ተፈጥሮ የነበረው ውዝግብ በማዕከላዊ ኮሚቴ ውሳኔ መቋጨቱ ተገለጸ
የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መሳተፉን በደገፉ እና በተቃወሙ አባላቱ መካከል ተፈጥሮ የነበረው ውዝግብ በማዕከላዊ ኮሚቴ ውሳኔ መቋጨቱን ለአሐዱ ሬዲዮ ያስታወቁት የፓርቲው ዋና ጸሐፊ ሚስጥረ-ሥላሴ ታምራት ናቸው።
ዋና ጸሐፊዋ በማብራሪያቸው፣ ፓርቲው ከሌሎች 4 ድርጅቶች ጋር በጋራ በመሠረተው ትብብር በምርጫው ለመሳተፍ ቢስማማም ያስቀመጣቸው ቅድመ ሁኔታዎች ነበሩ ብለዋል።
ቅድመ ሁኔታዎቹም፡- በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚታዩ ግጭቶች ቆመው እውነተኛ ድርድር እንዲካሄድ እንዲሁም በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞች እና የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ የሚሉ ናቸው።
የተቀመጡት ጥያቄዎች ባለመሟላታቸው በምርጫው መሳተፍ የለብንም በሚሉና መሳተፍ አለብን ባሉ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች መካከል አለመግባባት ተፈጥሮ እንደነበር ዋና ጸሐፊዋ አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ፤ ማዕከላዊ ኮሚቴው በምርጫው በመሳተፍ መታገል ይሻላል የሚል ውሳኔ በማሳለፉ ውዝግቡ መቋረጡን አብራርተዋል።
ፓርቲው ያስቀመጣቸውን ቅድመ ሁኔታዎች መንግሥት በቸልተኝነት የሚያልፋቸው ከሆነ፣ ምንም እንኳን ምርጫው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የሚካሄድ ቢሆንም እስከ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ ፓርቲው የሚወስናቸው ሌሎች ፖለቲካዊ እርምጃዎችና ውሳኔዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ ዋና ጸሐፊዋ ሚስጥረሥላሴ ታምራት ለአሐዱ ሬዲዮ ተናግረዋል።
#አሐዱ_
የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ መሳተፉን በደገፉ እና በተቃወሙ አባላቱ መካከል ተፈጥሮ የነበረው ውዝግብ በማዕከላዊ ኮሚቴ ውሳኔ መቋጨቱን ለአሐዱ ሬዲዮ ያስታወቁት የፓርቲው ዋና ጸሐፊ ሚስጥረ-ሥላሴ ታምራት ናቸው።
ዋና ጸሐፊዋ በማብራሪያቸው፣ ፓርቲው ከሌሎች 4 ድርጅቶች ጋር በጋራ በመሠረተው ትብብር በምርጫው ለመሳተፍ ቢስማማም ያስቀመጣቸው ቅድመ ሁኔታዎች ነበሩ ብለዋል።
ቅድመ ሁኔታዎቹም፡- በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚታዩ ግጭቶች ቆመው እውነተኛ ድርድር እንዲካሄድ እንዲሁም በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞች እና የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ የሚሉ ናቸው።
የተቀመጡት ጥያቄዎች ባለመሟላታቸው በምርጫው መሳተፍ የለብንም በሚሉና መሳተፍ አለብን ባሉ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች መካከል አለመግባባት ተፈጥሮ እንደነበር ዋና ጸሐፊዋ አስታውሰዋል። ይሁን እንጂ፤ ማዕከላዊ ኮሚቴው በምርጫው በመሳተፍ መታገል ይሻላል የሚል ውሳኔ በማሳለፉ ውዝግቡ መቋረጡን አብራርተዋል።
ፓርቲው ያስቀመጣቸውን ቅድመ ሁኔታዎች መንግሥት በቸልተኝነት የሚያልፋቸው ከሆነ፣ ምንም እንኳን ምርጫው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የሚካሄድ ቢሆንም እስከ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ ፓርቲው የሚወስናቸው ሌሎች ፖለቲካዊ እርምጃዎችና ውሳኔዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ ዋና ጸሐፊዋ ሚስጥረሥላሴ ታምራት ለአሐዱ ሬዲዮ ተናግረዋል።
#አሐዱ_
Sponsored by
Surafel
9 days ago
የዒድ አል አድሐ (ዐረፋ) በዓልን በማስመልከት 9 ጊዜ መድፍ ይተኮሳል
በነገው ዕለት የሚከበረውን 1447ኛው የዒድ አል አድሐ (ዐረፋ) በዓል በማስመልከት 9 ጊዜ መድፍ ይተኮሳል፡፡
መከላከያ ሚኒስቴር እንደገለጸው፥ በዓሉን ምክንያት በማድረግ ነገ ማለዳ 12 ሰዓት ላይ 9 ጊዜ መድፍ የሚተኮስ ይሆናል፡፡
FBC
በነገው ዕለት የሚከበረውን 1447ኛው የዒድ አል አድሐ (ዐረፋ) በዓል በማስመልከት 9 ጊዜ መድፍ ይተኮሳል፡፡
መከላከያ ሚኒስቴር እንደገለጸው፥ በዓሉን ምክንያት በማድረግ ነገ ማለዳ 12 ሰዓት ላይ 9 ጊዜ መድፍ የሚተኮስ ይሆናል፡፡
FBC