Logo
FIDEL POST NEWS
2 months ago
የፌዴራል ፖሊስ በአርቲስቶችና በፊንቴክ ኢንቨስትመንት ባለቤቶች ላይ ክስ መመስረቱን አስታወቀ

​የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በፊንቴክ ኢንቨስትመንት ድርጅት መስራቾችና በግብረ አበሮቻቸው ላይ የ1.7 ቢሊዮን ብር የማጭበርበር ወንጀል ምርመራ አጠናቆ ለዐቃቤ ሕግ መላኩን ገለጸ።

መስራቾቹ ዳንኤል ዮሃንስ እና ግርማይ ገብረሚካኤል ከ1,200 በላይ ዜጎችን "ከወለድ ነፃ የመኪና ብድር እናመቻቻለን" በማለት እያንዳንዳቸውን እስከ 1.3 ሚሊዮን ብር በማስከፈል ማጭበርበራቸው ተገልጿል።

​ድርጅቱ ከቻይናው ቢ.ዋይ.ዲ (BYD) ካምፓኒ ጋር ውል ሳይኖረው የሐሰት መረጃዎችን በመጠቀም ህዝቡን ሲያታልል መቆየቱ ተረጋግጧል።

በወንጀሉ ተባባሪ በመሆንና የተጋነነ ማስታወቂያ በመስራት የተጠረጠሩ ሰለሞን ቦጋለ፣ ሰራዊት ፍቅሬ እና መንሱር ጀማልን ጨምሮ ሰባት ታዋቂ አርቲስቶችና ባለሙያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።

እነዚህ ግለሰቦች እያንዳንዳቸው 8 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ መኪና በስጦታ መልክ ተቀብለዋል ተብሏል።

ፖሊስ በ19 ዓይነት የወንጀል ድርጊቶች ላይ የጀመረውን ምርመራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
FIDEL POST NEWS
2 months ago
​"በጓደኛዬ ቀብር ላይ የገዛ እናቴን ቀበርኩ" — በስዊድን ሆስፒታል የተፈጠረው አስደንጋጭ ስህተት

​በስዊድን ሶደርተልያ ከተማ በሚገኝ አንድ ሆስፒታል ውስጥ በተፈጠረ እጅግ አሳዛኝና አስደንጋጭ ስህተት፣ የሁለት ሟቾች አስከሬን በመቀያየሩ ቤተሰቦች ለከፍተኛ ስቃይና ድንጋጤ ተዳርገዋል።

​ሁኔታው የተጀመረው የ78 ዓመቷ ወርዳ አትዋን ሳርሀን ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ተከትሎ ነው።

ቤተሰቦቻቸው የቀብር ሥነ-ሥርዓቱን ለመፈጸም አስከሬን ለመረከብ ወደ ሆስፒታሉ ባቀኑበት ወቅት፣ ሆስፒታሉ "አስከሬኑ ቀድሞ ተወስዷል" የሚል አስደንጋጭ ምላሽ ሰጥቷቸዋል።

​በምርመራ እንደተደረሰበት ከሆነ፣ ሌላኛው ቤተሰብ የወርዳን አስከሬን የራሳቸው ሟች መስሏቸው ወስደው ቀብረዋል። ይበልጥ የሚያሳዝነው ደግሞ የወርዳ ልጅ ባሴም ቡስታን አዚዝ፣ የቤተሰብ ጓደኛው በነበረው ሰው ቀብር ላይ ተገኝቶ ሳያውቀው የገዛ እናቱን ሲቀብር መቆየቱ ነው።

​ሁለቱም ቤተሰቦች የማንዳያን ሃይማኖታዊ ማህበረሰብ አባላት በመሆናቸው፣ አስከሬኖች በነጭ ጨርቅ ተጠቅልለው ነበር። ይህ ሁኔታ በመቃብር ቤት ውስጥ አስከሬኑን በዐይን ለይቶ ለማወቅ አስቸጋሪ አድርጎታል።

​ሆኖም ግን፣ በሆስፒታሉ የቀረው አስከሬን ከወርዳ በ20 ሴንቲሜትር የሚረዝም መሆኑን ቤተሰቦች ወዲያውኑ አስተውለዋል። ሌላኛው ቤተሰብም አስከሬኑን በሚረከቡበት ወቅት "ሟቹ ለምን አነሰ?" የሚል ጥርጣሬ አድሮባቸው የነበረ ቢሆንም፣ "ከሞት በኋላ አስከሬን ሊኮማተር ይችላል" የሚል የተሳሳተ ምላሽ ተሰጥቷቸው እንደነበር ታውቋል።

​የሆስፒታሉ አስተዳደር ለተፈጠረው ከፍተኛ ግድፈት ሙሉ ኃላፊነት በመውሰድ ለቤተሰቦቹ ይቅርታ ጠይቋል። የሆስፒታሉ ዳይሬክተር አና ገርበር ኤክብሎም "እንዲህ ያለ ስህተት ዳግም እንዳይከሰት ጥብቅ ምርመራ እናደርጋለን" ብለዋል።

​ቤተሰቦቹ አስከሬኖችን መልሶ ከመቆፈርና ከማውጣት ይልቅ፣ ሟቾች ባሉበት መቃብር እንዲያርፉ ወስነዋል። ሆኖም ግን በትክክለኛው ስም የመቃብር ድንጋዮቹ እንዲቀየሩ ስምምነት ላይ ተደርጓል።

​ምንጭ፦ አፍተንብላዴት

FIDEL POST NEWS
2 months ago
ጊፍት ሪል ስቴት ለፋሲካ በዓል የ15 በመቶ የዋጋ ቅናሽ ያደረገበት የቤት ሽያጭ ኤክስፖ አስጀመረ

​አንጋፋው ጊፍት ሪል ስቴት የፋሲካን በዓል ምክንያት በማድረግ፣ በመገንባት ላይ ባሉ የመኖሪያ አፓርትመንቶች እና የንግድ ሱቆች ላይ የ15 በመቶ ቅናሽ ያደረገበት የሽያጭ ኤክስፖ ዛሬ መጋቢት 19 ቀን አስጀምሯል።

እስከ ሚያዚያ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ለአንድ ወር የሚቆየው ይህ መርሐ-ግብር፣ ደንበኞች በ2 በመቶ ቅድመ ክፍያ ብቻ የቤት ባለቤት የሚሆኑበትን ዕድል ማመቻቸቱ ተገልጿል።

​በዚሁ የሽያጭ ኤክስፖ ላይ 1,200 የሚሆኑ ቤቶች ለገበያ የቀረቡ ሲሆን፣ ድርጅቱ በለገሃር አካባቢ በሚገኘው "ጊፍት ሜትሮፖሊታን" ሳይት 4 ሺህ ቤቶችን በመገንባት ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል።

ከዚህ በተጨማሪም በ6 ኪሎ፣ ቦሌ መድኃኒዓለም፣ ፊጋ፣ 22 ማዞሪያ፣ ተክለሃይማኖት እና ሲ.ኤም.ሲ አካባቢዎች የሚገነቡ ከ16 ሺህ በላይ የመኖሪያ እና የንግድ ቤቶች ለማስተዋወቅ መቻሉን የድርጅቱ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ዶ/ር ሰለሞን አሊ ገልፀዋል።

​የሪል እስቴት መንደሮቹ ትምህርት ቤቶችን፣ የሕክምና ተቋማትን፣ የገበያ ማዕከላትንና የመዝናኛ ስፍራዎችን ያካተቱ ዘመናዊ መንደሮች መሆናቸው ተመላክቷል።

ጊፍት ሪል ስቴት እስካሁን በሲ.ኤም.ሲ እና በፈረስ ቤት ሦስት ትልልቅ መንደሮችን ገንብቶ ለነዋሪዎች ማስረከቡ የሚታወስ ሲሆን፣ የአሁኑ የለገሃር ፕሮጀክትም የዚሁ ሰፊ የቤት ግንባታ ማስፋፊያ አካል መሆኑ ታውቋል።
FIDEL POST NEWS
2 months ago
የመጀመሪያዋ የኢንግሊዝ ቤተክርስቲያን መሪ ሳራ ሙላሊ ማን ናቸው?

​ሳራ ሙላሊ መጋቢት 16 ቀን 2018 ዓ.ም በካንተርበሪ  የቅዱስ አንግሊካን ቤተክርስቲያን የመጀመሪያዋ ሴት መሪ በመሆን ተሹመዋል።

ይህም በዩናይትድ ኪንግደም እና በዓለም አቀፍ የሃይማኖት ማህበረሰብ ዘንድ ትልቅ ታሪካዊ ክስተት ሆኖ ተመዝግቧል።

​ሹመት፦ የቀድሞ ነርስ፣ ባለትዳር እና የሁለት ልጆች እናት የሆኑት የ63 ዓመቷ ሳራ ሙላሊ፤ በደቡብ ምስራቅ እንግሊዝ በሚገኘው የካንተርበሪ ካቴድራል በይፋ ስልጣናቸውን ተረክበዋል።

​ታዳሚዎች፦ በሥነ-ሥርዓቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ኪር ስታርመር፣ አልጋወራሹ ልዑል ዊሊያም እና ባለቤታቸው ካትሪን ጨምሮ ወደ 2,000 የሚጠጉ ሰዎች ተገኝተዋል።

​ተተኪነት፦ አዲሷ መሪ የተተኩት በህዳር 2024 በጾታዊ ጥቃት ቅሌት አያያዝ ምክንያት ከኃላፊነታቸው የለቀቁትን ጀስቲን ዌልቢን ነው።

​የሳራ ሙላሊ የጉዞ መስመር

​ሳራ ሙላሊ ከዚህ ቀደም በ2018 የለንደን የመጀመሪያዋ ሴት ጳጳስ በመሆን ተሹመው ነበር። ወደ ካንተርበሪ ከመምጣታቸው በፊትም ከለንደኑ ቅዱስ ጳውሎስ ካቴድራል በመነሳት የእግር ጉዞ መንፈሳዊ ጉዞ አድርገዋል።

​በቃለ መሃላ ስነ-ስርዓታቸው ላይ፦
​"የእንግሊዝ ቤተክርስቲያንን፣ የአንግሊካን ህብረትን እና በመላው ዓለም የሚገኘውን የክርስቶስ ቤተክርስቲያንን ለማገልገል በፊታችሁ ቃል እገባለሁ" ብለዋል።

​ያሉባቸው ፈተናዎች

​ምንም እንኳን ሹመቱ ታሪካዊ ቢሆንም፣ በዓለም ዙሪያ ባሉ የአንግሊካን ማህበረሰቦች ዘንድ በተለይም በአፍሪካ በሚገኙ ሊቀ ጳጳሳት ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞና ክፍፍል ገጥሞታል። በአሁኑ ወቅት በአንግሊካን እምነት ተከታዮች ዘንድ ሰፊ ልዩነቶች ያሉ ሲሆን፣ አዲሷ መሪ እነዚህን ክፍፍሎች የማስታረቅ ከባድ ኃላፊነት ይጠብቃቸዋል።

​ለማወቅ ያህል፦ የአንግሊካን ቤተክርስቲያን በ16ኛው ክፍለ ዘመን ንጉስ ሄንሪ ስምንተኛ ከካቶሊክ ቤተክርስቲያን ጋር ግንኙነታቸውን ካቋረጡ በኋላ የተመሰረተች የዩናይትድ ኪንግደም ብሔራዊ ቤተክርስቲያን ናት።

ምንጭ: AFP
FIDEL POST NEWS
2 months ago
ጣሊያን የቤት እንስሳ ለሞተበት ሠራተኛ ሶስት ቀን የሐዘን ፈቃድ ልትሰጥ ነው

​በጣሊያን ሀገር የቤት እንስሳ ለሞተባቸው ወይም ለታመሙባቸው ሠራተኞች የሚከፈልበት የሥራ ፈቃድ እንዲሰጥ የሚጠይቅ አዲስ የሕግ ረቂቅ ቀረበ።

ይህ ተነሳሽነት በጣሊያን የሚገኙ የቤት እንስሳት እንደ ቤተሰብ አባል የሚታዩበትን ማህበራዊ እውነታ መሠረት ያደረገ ነው።

ረቂቁ አንድ የቤት እንስሳ (ውሻ ወይም ድመት) ሲሞት ሠራተኛው ለሦስት ቀናት የሚከፈልበት የሐዘን ፈቃድ እንዲያገኝ ይጠይቃል።

ለቤት እንስሳት ድንገተኛ ሕክምና በዓመት ስምንት ሰዓታት ከሥራ ገበታ የመቅረት መብት እንዲኖር ረቂቁ ይደነግጋል።

56% የሚሆኑ የጣሊያን ቤተሰቦች የቤት እንስሳ ያላቸው ሲሆን፣ የእንስሳቱ መታመም ወይም መሞት በሠራተኛው የሥነ-ልቦና እና የሥራ ምርታማነት ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር ጥናቶች ያመለክታሉ።

ምንጭ: ላ ሪፐብሊካ
FIDEL POST NEWS
2 months ago
አሜሪካ የFBI ዳይሬክተር 'ኢሜል' የሰበረውን ለጠቆመ 10 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት አቀረበች

​የኢራን ደጋፊ ነው የሚባለው "ሓንዳላ" የሃከሮች ቡድን የFBI ዳይሬክተር ካሽ ፓቴልን የግል የጂሜል አካውንት በመስበር የግል ፎቶዎቻቸውንና ከ300 በላይ ኢሜሎችን ይፋ አድርጓል።

​ጥቃቱን ተከትሎ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስለ ሃከሮቹ መረጃ ለሚሰጥ እስከ 10 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት እንደሚሰጥ አስታውቋል።

FBI የተሰረቁት መረጃዎች የቆዩ መሆናቸውንና የመንግስት ምስጢር እንዳልተጋለጠ ቢገልጽም፣ ድርጊቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የሳይበር ጦርነት አባብሶታል።
FIDEL POST NEWS
2 months ago
ትራምፕ ፦ "አዲሱ የኢራን መንፈሳዊ መሪ ወይ ሞተዋል ወይም በጽኑ ታመዋል"

​የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፍሎሪዳ በተካሄደ የኢኮኖሚ ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ የኢራን መንፈሳዊ መሪ በሕይወት ስለመኖራቸው ጥርጣሬ እንዳላቸው ገለጹ።

ትራምፕ "የኢራን አዲሱ መንፈሳዊ መሪ ወይ ሞተዋል ወይም በጣም አስጊ ሁኔታ ላይ ናቸው" ብለዋል።

ሙጅተባ ካሚኒ ለረጅም ጊዜ አለመታየታቸው ለዚህ ማሳያ መሆኑን ጠቁመዋል።

​በሌላ በኩል፣ ትራምፕ የኢራን ባለስልጣናት እሳቸው የሀገሪቱ መንፈሳዊ መሪ እንዲሆኑ በውስጥ መስመር ጥያቄ አቅርበውልኛል ሲሉ ቢናገሩም፣ የኢራን አብዮታዊ ዘብ "ፕሬዝዳንቱ ውሸታም ናቸው" በማለት አስተባብለዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ቪትኮፍ ከኢራን ጋር የሰላም ስምምነት ለመድረስ በዚህ ሳምንት ድርድር እንደሚጀመር ይጠበቃል ብለዋል።
FIDEL POST NEWS
2 months ago
በትግራይ አንዲት ሴትን በስለት አስፈራርተው በቡድን የደፈሩ ግለሰቦች የ10 ዓመት እስራት ተፈረደባቸው

​በትግራይ ክልል ደቡባዊ ምስራቅ ዞን፣ ሕንጣሎ ወረዳ ልዩ ስሙ ሕዋነ ቀበሌ ውስጥ አንዲት እንስትን በስለት አስፈራርተው በቡድን የደፈሩ ሁለት ግለሰቦች በ10 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጡ።

​ወንጀለኞቹ ድርጊቱን የፈጸሙት ሐምሌ 11 ቀን 2017 ዓ.ም ምሽት ላይ ተበዳይዋ ከሥራ ወደ ቤቷ በመመለስ ላይ ሳለች አፍነው በመውሰድ ነው።

ግለሰቦቹ በወቅቱ እጅ ከፍንጅ ባለመያዛቸው የምርመራ ሂደቱ ረጅም ጊዜ የፈጀ ቢሆንም፣ በሰውና በሰነድ ማስረጃ ጥፋተኝነታቸው በመረጋገጡ የዞኑ ማእከላዊ ፍርድ ቤት ዛሬ መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ.ም የቅጣት ውሳኔውን አስተላልፏል።

​ተበዳይዋ በውሳኔው መደሰቷን ገልጻ፣ ሆኖም ወንጀሉን ያስተባበረው ግለሰብ በነፃ መለቀቁ እንዳሳዘናትና ጉዳዩ በድጋሚ እንዲታይላት ጠይቃለች።

ምንጭ: የዞኑ ኮሚኒኬሽን ቢሮ
FIDEL POST NEWS
2 months ago
ሰብአዊ እርዳታ የጫኑና ጠፍተው የነበሩ ሁለት ጀልባዎች በሰላም ኩባ ደረሱ

​ከሜክሲኮ ከተነሱ በኋላ ጠፍተው ይሆናል ተብሎ ተሰግቶባቸው የነበሩ ሰብአዊ እርዳታ የጫኑ ሁለት ጀልባዎች ተገኝተው "በሰላም" ደሴቲቱ (ኩባ) መድረሳቸውን የአሜሪካ የባህር ዳርቻ ጠባቂ አስታወቀ።

​የባህር ዳርቻ ጠባቂው ቃል አቀባይ አንቶኒ ራዲቺ "ዛሬ ከሰአት ሁለቱ የባህር ላይ መንኮራኩሮች በሰላም ወደ ኩባ መሻገራቸውን የሚገልጽ ሪፖርት ደርሶናል።" ብለዋል።

​አክለውም የአሜሪካ ባለስልጣናት ጀልባዎቹን በመፈለጉ ሂደት ላይ ተሳትፎ እንዳልነበራቸው ገልጸዋል።
FIDEL POST NEWS
2 months ago
ዋልያዎቹ ሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔን 3 ለ 0 አሸነፉ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋልያዎቹ) ለ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በሚያደርገው የቅድመ ማጣሪያ የመጀመሪያ ጨዋታ የሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔን አቻውን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፏል።

​በሞሮኮ ኤል አብዲ ስታዲየም ዛሬ ምሽት በተካሄደው በዚህ ጨዋታ ​አቤል ያለው ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የቡድኑን መሪነት ሲያጠናክር ​ከነዓን ማርክነህ ቀሪዋን አንድ ግብ አክሎ ጨዋታው በዋልያዎቹ የበላይነት እንዲጠናቀቅ አድርገዋል።

ሁለቱ ቡድኖች የመልስ ጨዋታቸውን በቀጣይ ሳምንት ማክሰኞ በድሬዳዋ ስታዲየም የሚያደርጉ ይሆናል።
FIDEL POST NEWS
2 months ago
" ሰባቱ ወዲያው ተገደሉ። አንዱን የሞተ መስሏቸው ጥለውት ሄዱ። አልሞተም ግን እግሩ ከጥቅም ውጭ ሆኗል። ስድስቱ በሰፊ ጉድጓድ በአንድ ቦታ ተቀብረዋል " - የፋብሪካው ሠራተኞች

➡️ " አንድ የከባድ መኪና ሹፌር እና ረዳትም ተገድለው ተገኝተዋል። የሰዎች መታገት የተለመደ ሆኗል። የጸጥታ አካላት አሉ ግን እያዩ እንዳላዩ ነው የሚሆኑት " - ነዋሪ

በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሸዋ ዞን ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት የመተሐራ ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞችን እና ሌሎችን ጨምሮ በሁለት ቀናት ብቻ ዘጠኝ ሰዎች ሲገደሉ፣ ሌሎች መጎዳታቸውን የፋብሪካው ሠራተኞች እና ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ጉዳዩን ያጣራ አንድ የአካባቢው ነዋሪ በሰጠን ማብራሪያ፣ የፋብሪካው ሠራተኞች በታጣቂዎች የተገደሉት መጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ/ም መሆኑን ገልጾ። " አንድ የፋብሪካውን አመራር ለማጥቃት ሂደው ነው ሰባቱን አጃቢዎቹን የገደሏቸው " ብሏል።

ጥቃት አድራሾቹ፣ " መሬታችን ተወስዷል " የሚል ጥያቄ እንዳላቸውም ገልጿል። ጥቃቱ የደረሰው " ጮሬ " በሚባለው የፋብሪካው ካምፕ መሆኑን ያስረዳው ነዋሪው፣ " ሟቾቹ የስኳር ፋብሪካው የጥበቃ ሠራተኞች ናቸው። ታጣቂዎቹ ድንገት መጥተው ተኩስ ፈጽመውባቸው ወዲያው ነው ጫካ የሚገቡት " ሲልም ተናግሯል።

በተያያዘ፣ " ሰባቱ ሰዎች ከመገደላቸው ከአንድ ቀን በፊት መተሐራ እና ወለንጭቲ መካከል የከባድ መኪና ሹፌር እና ረዳትም ተገድለው ተገኝተዋል። በአካባቢው የሰዎች መታገት የተለመደ ሆኗል። የጸጥታ አካላት አሉ ግን እያዩ እንዳላዩ ነው የሚሆኑት " ሲልም ገልጿል።

ሌላኛው ነዋሪ፣ ከ2010  ጀምሮ በየዓመቱ እስከ ዘጠኝ ሰው " የሚገደልበት " ሁኔታ መኖሩን አስረድተው፣ " ህዝቡ ዘላቂ የሆነ መፍትሄ እያገኘ አይደለም " ሲሉ ገልጸዋል።

የሰሞኑን ጎድያ በተመከለተም፣ " በአንድ መኪና ላይ ነው ሰባቱንም የመንግስት ተቀጣሪዎች፤ የስንት ልጆች አባቶችን በአንድ ቀን ገድለውብናል " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ሰሞኑን የተገደሉት የመተሐራ ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞች " ትልልቅ ሰዎች ናቸው " ሲሉ ያስረዱ አንድ ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁ የፋብሪካው ሠራተኛ ደግሞ፣ ጥቃቱን " አሳዛኝ " ሲሉ ጠርተውታል።

ሰባቱ ሠራተኞች የተገደሉት አንድ የፋብሪካውን አመራር አጅበው በነበረበት ወቅት መሆኑን ተናግረዋል።

የታጣቁት አካላት የፋብሪካው ሠራተኞች ላይ ተኩስ የከፈቱባቸው " ገና ከፒካፕ መኪና ላይ ሳይወርዱ " መሆኑን፣ በዚህም ሌሎቹ ሲገደሉ አብረው የነበሩት አመራሩ " የውሃ ቦይ ውስጥ ገብተው፣ እየተሳቡ " የተኩሱን ቦታ በመራቅ በህይወት መትረፋቸውን አስረድተዋል።

እኚሁ የፋብሪካው ሠራተኛ፣ ይህ ጥቃት ተፈጽሟል ብሎ ለመናገር እንኳ ከፍተኛ ስጋት እንዳለባቸው ገልጸዋል።

ሌላኛው የፋብሪካው ሠራተኛ በበኩላቸው፣ ግድያው የተፈጸመበት " ጮሬ " በተሰኘው ቦታ አጠገብ መሆኑን ገልጸዋል።

በአጠቃላይ ከሟቾቹ ጋር ዘጠኝ ሰዎች ነበሩ ብለው፣ " ሰባቱ ወዲያው ተገደሉ። አንዱ የሞተ መስሏቸው ጥለውት ሄዱ። አልሞተም ግን እግሩ ከጥቅም ውጭ ሆኗል። አንዱ ደግሞ ተርፏል " ብለዋል። " ስድስቱ በሰፊ ጉድጓድ በአንድ ቦታ ተቀብረዋል " ነው ያሉት።

አዲስ የመጡት የፋብሪካው ሥራ አስኪያጅ ለሟች ቤተሰቦች " በየቤታቸው ሂደው ለእያንዳንዳቸው 150 ሺሕ ብር ሰጥተዋል። 'የተማረ ልጅ ካላቸው በቋሚነት ሥራ እንቀጥራን፣ ካልተማሩ በመደብ 6 የአባታቶቻቸውን ቦታ ይይዛሉ' ሲሉም ቃል ገብተዋል " ሲሉ ተናግረዋል።

ጥቃቱ ከደረሰ በኋላ ያለውን ድባብ ሲያስረዱ ደግሞ፣ ለጊዜው "መከላከያ ገብቷል" ብለዋል።

የአካባቢው ነዋሪ ግን፣ " በአካባቢው የጸጥታ ችግር ተንሰራፍቷል። በሰላም ወጥቶ መግባት በጣም አስቸጋሪ ሆኗል " ሲሉም የሁነቱን አሳሳቢነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

" ከአንድ ወር በፊት ሁለት ልጆች ታግተው 2 ሚሊዮን ብር ተጠይቆባቸው ነበር። 2 ሚሊዮን ብር ተሰብስቦ አንድ ልጅ ወስዶ ሰጣቸው። በኋላም ለቀቋቸው። ከፍተኛ ድብደባ እና ራሳቸውን እስኪስቱ ድረስ የረሃብ ስቃይ አድርሰውባቸው መንገድ ላይ ነው የጣሏቸው " ሲሉም አስታውሰዋል።

" ገንዘቡን ያደረሰው ልጅ ግን ተገድሏል" በማለት አዝነዋል። ከመተሐራ ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞች መካከል አንዱ በበኩላቸው፣ ታጣቂዎቹ "ከአዳማ መተሐራ መንገድ በኃይለኛው እያገቱ ነው፤ ተሳፋሪም መውሰድ ጀምረዋል " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የስኳር ፋብሪካውንም ሆነ ሌሎች የአካባቢውን ኃላፊዎች ለማግኘት ለቀናት ያደረገው ጥረት ለጊዜው ያልተሳካ ሲሆን፣ ጥረቱ ይቀጥላል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#tikvahethiopiafamilyaa

tikvahethiopia
FIDEL POST NEWS
2 months ago
ባለንበት በዚህ ሰው ሰራሽ በሆነና በግርግር በታመሰ ዓለም ውስጥ፣ አሁንም ቢሆን በየጥጋጥጉ ተደብቀው የሚገኙ ውበቶችና ጥልቅ የሆኑ ስሜቶች (ቅኔዎች) አሉ። ዋናው ቁምነገር ከውጫዊው ገጽታና ከዚህ የቴክኖሎጂ ሽኩቻ ባሻገር በጥልቀት ማየት መቻል ነው።

​ታላቁ ገጣሚ ጆን ኪትስ

ሰላም አዳር ይሁንላቹ
FIDEL POST NEWS
2 months ago
የነዳጅ እጥረት በኪሳችሁና በጊዜያችሁ ላይ ያሳደረው ጫና አጋሩን እስቲ?

​የመካከለኛው ምስራቅ ፖለቲካዊ ቀውስ በዓለም የነዳጅ ገበያ ላይ የፈጠረው ንረት፣ በቤታችን ደጃፍ ደርሶ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያችንን ክፉኛ እየፈተነው ይገኛል።

​ዛሬ ላይ በየማደያው የሚታየው ረጅም የነዳጅ ሰልፍ፣ በየመንገዱ የሚስተዋለው የትራንስፖርት እጥረት እና ያለ አግባብ የሚጠየቁ ክፍያዎች የብዙዎቻችንን ትዕግስት እየፈተኑ ነው።

ማለዳ ከቤት ወጥቶ በሰዓቱ ስራ መድረስ ብርቅ እያስቸገረ መጥቷል።

ትርፍ ሰዓትና ጉልበት ብቻ ሳይሆን፣ ከኪሳችን የሚወጣው ያልተገባ ክፍያም የኑሮ ውድነቱን አባብሶታል።

​እናንተስ?

​በየቀኑ ለትራንስፖርት የምታጠፉት ሰዓት ምን ያህል ጨመረ?

​ካላችሁ ወርሃዊ ገቢ ላይ የትራንስፖርት ወጪው ምን ያህል ድርሻ ያዘባችሁ?

​ይህንን ፈታኝ ወቅት ለማለፍ ምን አይነት አማራጮችን (ለምሳሌ፦ በእግር መጓዝ፣ ጉዞን መቀነስ...) እየተጠቀማችሁ ነው?

​ሀሳባችሁን በኮሜንት አጋሩን ! 👇
FIDEL POST NEWS
2 months ago
የኢራን ሃከሮች የFBI ዳይሬክተርን የኢሜል አካውንት ሰበሩ

​በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው ዲፕሎማሲያዊ ውጥረት በከረረበት በዚህ ወቅት፣ የኢራን ደጋፊ እንደሆነ የሚነገርለት "ሃንዳላ" የተሰኘ የሃከሮች ቡድን የፌዴራል ምርመራ ቢሮ (FBI) ዳይሬክተር የሆኑትን የካሽ ፓቴልን የግል የኢሜል አካውንት መጥለፉን አስታውቋል።

ቡድኑ የዳይሬክተሩን የግል ፎቶግራፎች እና የሥራ ልምድ (CV) መረጃዎችን በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ያሰራጨ ሲሆን፣ ድርጊቱ በአሜሪካ ከፍተኛ የደህንነት ተቋማት ላይ ትልቅ መደናገጥን ፈጥሯል።
FIDEL POST NEWS
2 months ago
በኢራን የዩራኒየም ማበልጸጊያ ጣቢያ ላይ የአየር ጥቃት ተሰነዘረ

​በመካከለኛው ኢራን ያዝድ ከተማ አቅራቢያ የሚገኘውና "ቢጫው ኬክ" ተብሎ የሚጠራውን የዩራኒየም ዱቄት የሚያመርተው ፋብሪካ የአየር ጥቃት እንደተሰነዘረበት የኢራን መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

የአገሪቱ የአቶሚክ ኢነርጂ ድርጅት ጥቃቱ በፈቃድ በ"አሜሪካ-በእስራኤል " የተፈጸመ መሆኑን ገልጿል።

​የፋርስ የዜና ወኪል እንደዘገበው ከሆነ፣ ጥቃቱ በፈርዱ አካባቢ በሚገኘው የዩራኒየም ማቀነባበሪያ ላይ ያረፈ ቢሆንም፣ እስካሁን በደረሰው የመጀመሪያ ደረጃ ግምገማ ምንም ዓይነት የጨረር ስርጭት አለመከሰቱ ገልፇል።

በአካባቢው ነዋሪዎች ላይ የሚደርስ የጤና ስጋት እንደሌለ ተገልጿል።

​"ቢጫው ኬክ" ለኑክሌር ጦር መሣሪያ ዝግጅት ወይም ለሃይል ማመንጫነት የሚያገለግለው ዩራኒየም እንዲበለጽግ የሚደረግበት የመጀመሪያው ወሳኝ ግብዓት ነው።
FIDEL POST NEWS
2 months ago
የመጀመሪያ አጋማሽ ውጤት

🇸🇹 ሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ 0-2 ኢትዮጵያ 🇪🇹

23' ከነአን ማርክነህ

32' አቤል ያለው
FIDEL POST NEWS
2 months ago
በቻይና ታላቅ ግንብ ላይ ጉዳት ያደረሱ ሁለት ሴቶች ታሰሩ

​"በቪዲዮ እየተቀረጸች መቧጨር ጀመረች" ሲል አንድ ምስክር በግርምት ተናግሯል።

አንዲት ሴት በዩኔስኮ የዓለም ቅርስ በሆነው ስፍራ ላይ ስሟን በኩራት ቧጭራ ጽፋ ነበር።

ነገር ግን ደስታዋ ብዙ አልቆየም፤ ፖሊሶች በፍጥነት ደርሰው ሴቶቹን ይዘዋቸው ሄደዋል።

ከቻይና ማህበራዊ ሚዲያ የተገኘ
FIDEL POST NEWS
2 months ago
" ‎ይህ አይነቱ የወንጀል ድርጊት በአከባቢው ሲፈፀም የመጀመሪያ ነው። የሞት ፍርድ ውሳኔም የመጀመሪያ ነው " - አቶ ነጋልኝ ዓለሙ

በቡርጂ ዞን በውርስ ምክንያት 3 የቤተሰባቸውን አባላትን በጥይት ደብድበው የገደሉ ተከሳሾች በሞት እንዲቀጡ ተወሰነ።

‎ይህ በአከባቢው የመጀመሪያው የሞት ፍርድ ውሳኔ እንደሆነ ተገልጿል።

የወንጀል ድርጊቱ የተፈጸመው ‎ነሐሴ 16/2017 ዓ/ም ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ገደማ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሶያማ ዙሪያ ወረዳ ገራ ቀበሌ መሆኑን በዞን ፍትህ መምሪያ የልዩ ልዩ ወንጀሎች ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ነጋልኝ ዓለሙ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

በዚሁ ቀበሌ አቶ ዋቶ ወርቁ የተባሉ አዛውንት ዕድሜያቸው እየገፋ መምጣቱን ተከትሎ በአከባቢው ባህል መሰረት ልጆቻቸውን ጠርተው የመሬት ውርስ ክፍፍል ማድረግ ይጀምራሉ።

ይህ እየሆነ ባለበት በሂደቱ ተቃርኖ የነበራቸው የአዛውንቱ የመጀመሪያ ልጅ እና የልጅ ልጃቸው ሁለቱም የክላሽ ኮቭ መሳሪያ በመታጠቅ በቤተሰብ አባላቱ ላይ ተኩስ መክፈታቸውን አቶ ነጋልኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

‎በጥቃቱ አዛውንቱ አቶ ዋቶ ወርቁን እና ሁለት ልጆቻቸው ወዲያውኑ ሲሞቱ ሁለት የቤተሰብ አባላት ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው ወደ አርባምንጭ ሪፌራል ሆስፒታል መላካቸውን ገልፀዋል።

‎ፖሊስም ግለሰቦቹን ከነመሳሪያቸው ኤግዚቢትነት በመያዝ ምርመራ ማድረግ ይጀምራል። መዝገቡንም አደራጅቶ ለዞኑ ዐቃቤ ሕግ ያቀርባል።

‎ዐቃቤ ሕግ መዝገቡን በማደራጀት በሁለቱ ተከሳሾች ላይ በዋና ወንጀል አድራጊነት ፦
• በሶስት የግድያ ወንጀል ክስ በወንጀል ህጉ አንቀጽ 539/1/ሀ መሠረት በከባድ የሰዉ ነብስ ማጥፋት ወንጀል
• ሁለት በህይወት በተረፉ የግል ተበዳዮች ወንጀል ሁለት ክስ በወንጀል ህግ አንቀጽ 27 እና 539/1/ሀ መሠረት ክስ ማቅረቡን አቶ ነጋልኝ አስረድተዋል።

‎ተከሳሾች ፍርድ ቤት ቀርበው የወንጀል ድርጊቱን ስለመፈፀማቸው ተጠይቀው " አልፈፀምንም " በማለት ክደዉ ተከራክረዋል።

አቃቤ ህግ በሰዉና በሰነድ ማስረጃ አምስቱንም ክስ በሚገባ ያስረዳ ሲሆን ተከሳሾች የቀረበባቸዉን ክስ መከላከል ባለመቻላቸው የቡርጂ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ተከሳሾችን በቀረበባቸው ክሶች ጥፋተኛ ናቸው ብሏል።

የፈፀሙት ወንጀል ጭካኔ የተሞላበትና አስነዋሪ መሆኑ ፤ በአከባቢው ከዚህ ቀደም ተደርጎ የማይታወቅ ፤ ከሁለት በላይ የሆነ የቤተሰብ አባላት ላይ በአንድ ጊዜ የተፈፀመ ግድያ መሆኑን ከግምት ውስጥ ገብቷል።

ፍርድ ቤቱ ሁለቱም ተከሳሾች በሞት እንዲቀጡ ውሳኔ አስተላልፏል።

‎ይህ አይነቱ የወንጀል ድርጊት በአከባቢው ሲፈፀም የመጀመሪያ ነው ያሉት አቶ ነጋልኝ የሞት ፍርድ ውሳኔም በዞኑ የመጀመሪያ ነው ሲሉ ገልፀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ/ም

tikvahethiopia
FIDEL POST NEWS
2 months ago
ድመቶች በአንድ ጊዜ ከተለያዩ ወንዶች መፀነስ ይችላሉ።

በአንድ ምጥ የሚወለዱ ድመቶች መልካቸውና ዘራቸው በጣም ተለያይቶ የሚታየውም ለዚህ ነው።
FIDEL POST NEWS
2 months ago
እነዚህ አራት ሰውነትን የመለጠጥ ልምምዶች በፍጥነት ለመተኛት ይረዱዎታል

​በአልጋ ላይ እየተገላበጡ ለሰዓታት መቆየት የቀድሞ ታሪክ ሆኗል። ዛሬ ላይ ተነስተን ሁለት ወይም ሦስት እንቅስቃሴዎችን ካደረግን በኋላ ወዲያውኑ እንቅልፍ ይወስደናል። ይህን ማድረግ ይፈልጋሉ? እንዴት እንደሆነ እናሳይዎታለን።

​የመለጠጥ ልምምዶች ከአተነፋፈስ እና ከጥሞና ጋር በመቀናጀት አካልንና አእምሮን ያዝናናሉ።

​ለእያንዳንዱ አቀማመጥ አስር ሰከንድ መስጠት፦ ለዳሌ፣ ለሆድ፣ ለአንገት እና ለእግር የሚሆኑ እንቅስቃሴዎች።

​ልምምዶቹ

​1. እንቅልፍ ለማግኘት የሚደረግ ትግል

ይህንን እንቅስቃሴ በዳሌ ልምምድ እንጀምር። አልጋው አጠገብ እግርዎን ወረድ አድርገው ይቁሙ። ቀኝ እግርዎን ወደ ፊት ያዙሩ እና ክብደትዎን በትንሹ ወደ ቀኝ ያዘንብሉ። ቀኝ እጅዎን ወደ ጣሪያው፣ ግራ እጅዎን ደግሞ ወደ ታች ይዘርጉ። ይህንን ሁኔታ ለ10 ሰከንድ ይያዙ እና በሌላኛው በኩል ይድገሙት። በጥልቀት መተንፈስዎን አይዘንጉ።

​2. ለሆድ ጡንቻዎች እረፍት መስጠት

አልጋዎ ላይ በሆድዎ ይተኙ። እጆችዎን አጥፈው በትከሻዎ አቅራቢያ ካደረጉ በኋላ ሰውነትዎን ወደ ላይ ይግፉ። ዳሌዎ አልጋው ላይ እንዲያርፍ፣ ትከሻዎ ደግሞ ወደ ላይ እንዲለጠጥ ያድርጉ። አንገትዎ በትከሻዎ ውስጥ እንዳይሰምጥ ቀና አድርገው ይያዙ። በሆድዎ አካባቢ የሚሰማዎትን መሳብ ያስተውሉ፤ ጀርባዎን ቀጥ ለማድረግ ይሞክሩ።

​3. አንገትን ማዝናናት

በመጀመሪያ አልጋው ላይ ቀጥ ብለው ይቀመጡ። ጀርባዎን ሳያጎብጡ አገጭዎን ወደ ደረትዎ ዝቅ ያድርጉ። እጆችዎን አቆላልፈው በአንገትዎ ጀርባ ላይ በቀስታ ያስቀምጡ።

መለጠጡ እንዲጨምር ከፈለጉ እጅዎን በትንሹ ይጫኑ። ከአስር ሰከንድ በኋላ እጅዎን ያንሱ እና ጣሪያውን ለማየት ቀስ ብለው አንገትዎን ወደ ኋላ ያዘንብሉ።

​4. ከራስ እስከ እግር መለጠጥ

አሁን ደግሞ እግሮቻችንን ለእንቅልፍ እናዘጋጅ። እግርዎን ዘርግተው ይቀመጡ እና የላይኛው የሰውነት ክፍልዎን ወደ ፊት በማዘንበል ጣቶችዎን ለመንካት ይሞክሩ። እግርዎ ሳይታጠፍ ቀጥ እንዲል ያድርጉ እና ራስዎን ወደ ጉልበትዎ ያስጠጉ። ይህ የሚከብድዎት ከሆነ እግርዎን አንድ በአንድ በማፈራረቅ መስራት ይችላሉ።

​ምንጭ፦ ስዊዝ ኢሉስትሬትድ መጽሔት
FIDEL POST NEWS
2 months ago
🦜 ሰላይ በቀቀኖች፦ ለአደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪዎች ሲሰልሉ የተያዙት አእዋፋት

ታሪኩ ከ 16 አመት በፊት የተፈፀመ ነው።

​በኮሎምቢያ የሚገኙ የአደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪዎች ፖሊስን ለመሰለል በቀቀኖችን ሲጠቀሙ መቆየታቸው ይሳማል።

የሀገሪቱ የፀጥታ አካላት ለወንጀለኞች የመረጃ ምንጭ በመሆን ያገለግሉ የነበሩ 1,700 በቀቀኖችን በቁጥጥር ስር አውለዋል።

​እነዚህ አእዋፋት ፖሊሶች ወደ ወንጀለኞቹ መደበቂያ ሲቃረቡ አስቀድመው እንዲጮኹና ማስጠንቀቂያ እንዲሰጡ በልዩ ሁኔታ የሰለጠኑ ነበሩ።

ለምሳሌ "ሎሬንዞ" የተባለው በቀቀን ፖሊስ ሲመጣ "ሩጡ! ድመቷ ልትይዛችሁ ነው!" በማለት በመጮኽ ወንጀለኞች እንዲያመልጡ ሲረዳ ተገኝቷል።

​በአሁኑ ወቅት እነዚህ በቀቀኖች በልዩ የእንስሳት ማቆያ ማዕከላት ውስጥ ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል።

​ምንጭ፦ Associated Press እና BBC News
FIDEL POST NEWS
2 months ago
የጣሊያን ብሄራዊ ቡድን ተጫዋቾች ድርጊት በቦስኒያ ቁጣን ቀሰቀሰ

​የ2026 የዓለም ዋንጫ ማጣሪያን ተከትሎ የጣሊያን ብሄራዊ ቡድን ተጫዋቾች ያሳዩት ደስታ በቦስኒያ ደጋፊዎችና ተጫዋቾች ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞ አስነስቷል።

የጣልያን ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች የሆኑት ዲማርኮ፣ ፒዮ ኤስፖዚቶ እና ቪካሪዮ የቦስኒያና ዌልስን የፍጹም ቅጣት ምት ውጤት ሲመለከቱ የነበረው ምስል በቪዲዮ ተቀርጾ ወጥቷል።

​ተጫዋቾቹ ቦስኒያ ስታሸንፍ ያሳዩት ከመጠን ያለፈ ደስታ "ንቀትና እብሪት" ተብሎ ተፈርጇል።

የተጫዋቾቹ የመነጨው ከዌልስ ቦስኒያ ትቀለናለች የሚል መልዕክት አለው የሚል ትችት ተሰንዝሮበታል።

የቦስኒያ ደጋፊዎች በማህበራዊ ሚዲያ "ይህንን ንቀት በዜኒካ ሜዳ ላይ እናሳያችኋለን" ሲሉ ዝተዋል። ድርጊቱ የቀድሞው ተጫዋች ሌሌ አዳኒን ጨምሮ ብዙዎችን ያስገረመ ሲሆን፣ የጣሊያኑ አሰልጣኝ ጋቱሶም በጉዳዩ ዙሪያ ጥያቄ ቀርቦላቸዋል።

ጣሊያን በቀጣይ ማክሰኞ ከቦስኒያ ጋር ለዓለም ዋንጫ ለማለፍ ለምታደርገው ጨዋታ ይህ ክስተት ጨዋታውን ከወዲው አነጋጋሪ አድርጎታል።
FIDEL POST NEWS
2 months ago
ኢትዮጵያ የእቴጌ ጥሩወርቅ ውቤን የፀጉር ጌጥ ከ150 አመት በኋላ ተረከበች

​በዝርፊያ ከሀገር ወጥቶ የነበረው የንግሥት ጥሩወርቅ ውቤ (የዓፄ ቴዎድሮስ ባለቤት) የፀጉር ጌጥ (ወለባ) ወደ ኢትዮጵያ ተመለሰ።

በርስክክቡ ወቅት የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው እንደገለጹት፤ ቅርሱ ሊመለስ የቻለው በባለሥልጣኑ፣ በኢትዮጵያ ወዳጆችና በዜጎች የተቀናጀ ጥረት ነው።

​በተለይም የኢትዮጵያ ንጉሣዊ በጎ አድራጎት ባለአደራ ድርጅት፣ ልዑል ኤርሚያስ ሳህለሥላሴ እና ዶክተር አሉላ ፓንክረስት ለቅርሱ መመለስ ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል።

እስካሁን ባለው ጥረት 72 የተዘረፉ ቅርሶችን ማስመለስ የተቻለ ሲሆን፣ ቀሪዎቹን ለማስመለስም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በትኩረት እንደሚሰራ ተገልጿል።
FIDEL POST NEWS
2 months ago
የፊንቴክ ኢንቨስትመንት ሥራ አስኪያጅ በከባድ የማታለል ወንጀል ተከሰሰ

​በአዲስ አበባ የፊንቴክ ኢንቨስትመንት ሥራ አስኪያጅ የሆኑት ዳንኤል ዮሐንስ፣ ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ በማጭበርበር ወንጀል ክስ ተመሰረተባቸው።

ዐቃቤ ሕግ እንደገለጸው፣ ተከሳሹ "ሄሎ ታክሲ" እና "ፊንቴክ ኢንቨስትመንት" የተባሉ ድርጅቶችን በመጠቀም፣ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በዱቤ እናስረክባለን የሚል አሳሳች ማስታወቂያ በታዋቂ ግለሰቦች እና ማህበራዊ ሚዲያዎች አስነግረዋል።

​ተከሳሹ ከ5 ሺህ በላይ ተመዝጋቢዎችን ለቅድመ ክፍያ እና ለምዝገባ በሚል ከፍተኛ ገንዘብ እንዲከፍሉ ካደረጉ በኋላ፣ መኪኖቹን ሳያስረክቡ ድርጅቱን ዘግተው መሰወራቸው በክሱ ተመልክቷል።

ድርጊቱ የ1996 ዓ.ም የወንጀል ሕግን እና የኮምፒውተር ወንጀል አዋጅን የጣሰ መሆኑ ተገልጿል።

​በተጨማሪም፣ ተከሳሹ ቀደም ሲል በኢንተርፖል ከተያዘ ግብረ-አበር ጋር በመሆን፣ የውሸት ርክክብ ቪዲዮዎችን በማሳየት እና "መኪናዎች በመጓጓዝ ላይ ናቸው" የሚል ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨት 19 ተደራራቢ ወንጀሎችን መፈጸማቸው ተጠቅሷል።

ጉዳዩን የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ ልዩ ልዩ ወንጀል ችሎት እየተመለከተው ይገኛል።

ምንጭ: FMC
FIDEL POST NEWS
2 months ago
በጣሊያን የሟች ሞዴል አስክሬን አንገት ተቀልቶ ተሰረቀ

​ባለፈው ጥቅምት ወር በሚላን ከተማ በባልደረባዋ 30 ቦታ ቢላዋ ተወግታ የተገደለችው የ33 ዓመቷ ሞዴል ፓሜላ ጄኒኒ አስክሬን በድጋሚ አሰቃቂ ጥቃት ደረሰበት።

አስክሬኑ በቤርጋሞ ክልል በሚገኝ መቃብር ውስጥ ለቤተሰብ መቃብር እንዲዛወር ሲቆፈር፣ የሬሳ ሳጥኑ ተሰብሮና የሟች ጭንቅላት ተቀልቶ ተወስዶ ተገኝቷል።

​ይህ በጣሊያን ከፍተኛ ድንጋጤን የፈጠረው ክስተት፣ ሌላ የ41 ዓመት ሴት ግድያ በተፈጸመ ማግስት የተሰማ ነው።

ፌዴሪካ ቶርዙሎ የተባለችው ሴት በባሏ ተገድላ አስክሬኗ ተቀብሮ ተገኝቷል።

ገዳዩ በቁጥጥር ስር ሲውል፣ ወላጆቹ በሀዘንና በውርደት ራሳቸውን አጥፍተዋል።

እነዚህ ተከታታይ አሰቃቂ ድርጊቶች በሀገሪቱ የሴቶች ጥበቃ ላይ ከፍተኛ ህዝባዊ ቁጣን ቀስቅሰዋል።

ምንጭ: ANSA
FIDEL POST NEWS
2 months ago
ራፐሩ የኔፓል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኑ

​በኔፓል የቀድሞው ታዋቂ ራፐር እና የካትማንዱ ከንቲባ የነበሩት ባሌንድራ ሻህ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን ቃለ መሃላ ፈጸሙ።

የ35 ዓመቱ ወጣት ኢንጂነርና ድምፃዊ፣ በሹመት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ጥቁር ልብስና ጥቁር መነጽር አድርጎ በመቅረብ የብዙዎችን ቀልብ ስቧል።

​የእሱ "ብሔራዊ ነፃነት ፓርቲ" ባለፈው መጋቢት ወር በተካሄደው ምርጫ አሸናፊ መሆኑ ይታወሳል።

ይህ ድል የመጣው እ.ኤ.አ. በ2025 በወጣቶች በተመራውና "የጄነሬሽን ዜድ አብዮት" በተባለው ተቃውሞ የቀድሞው መንግሥት ከወደቀ በኋላ ነው።

ባሌንድራ ሻህ በበዓሉ ላይ ሕገ-መንግሥቱን ለማክበርና ግዴታውን በታማኝነት ለመወጣት ቃል ገብቷል።

ይህ ክስተት በኔፓል ፖለቲካ ውስጥ የወጣቶች የበላይነት የመጣበት አዲስ ምዕራፍ ተደርጎ ተወስዷል።
FIDEL POST NEWS
2 months ago
አሜሪካ በኢራን ላይ ሰው አልባ ጀልባዎችን በሥራ ላይ ማዋሏ ተነገረ

​አሜሪካ በኢራን ላይ በፈጸመችው ዘመቻ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰው አልባ ጀልባዎችን መጠቀምዋን ሮይተርስ ዘገበ።

ፔንታጎን እነዚህ ፈጣን ጀልባዎች ለጥበቃ፣ ለስለላና ለጥቃት ተግባራት መዋላቸውን ገልጿል።

በመካከለኛው ምስራቅ ባህር ላይ ከ450 ሰዓታት በላይ የቆዩት እነዚህ ቴክኖሎጂዎች፣ ለዓመታት ሲለሙ የቆዩ ሲሆን አሁን በተጨባጭ ወታደራዊ እርምጃ ላይ ተሰማርተዋል።
FIDEL POST NEWS
2 months ago
ወደ ኩባ ይጓዙ የነበሩ የረድኤት ጀልባዎች ደብዛቸው ጠፋ

​ከሜክሲኮ ሰብዓዊ እርዳታ በመጫን ወደ ኩባ ሲጓዙ የነበሩ Friendship እና Tigger Moth የተሰኙ ሁለት ጀልባዎች በካሪቢያን ባሕር ላይ መጥፋታቸው ተነገረ።

የሜክሲኮ ባሕር ኃይል ጀልባዎቹን ለመፈለግ ወታደራዊ አውሮፕላኖችን እና የነፍስ አድን ቡድኖችን በስፋት አሰማርቷል።

​በጀልባዎቹ ላይ ከፖላንድ፣ ፈረንሳይ፣ ኩባ እና አሜሪካ የተውጣጡ ዘጠኝ ሰራተኞች የነበሩ ሲሆን፣ ባለፈው ማክሰኞ ወይም ረቡዕ ሃቫና መድረስ ነበረባቸው።

ይሁን እንጂ እስካሁን ምንም ዓይነት ግንኙነት ማድረግ አልተቻለም።

ኩባ በአሜሪካ የኃይል ማዕቀብ ምክንያት ለገጠማት የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ችግር ከሜክሲኮ የሚላክላትን እርዳታ በከፍተኛ ሁኔታ ትጠብቅ ነበር።

የሜክሲኮመንግሥት ከሚመለከታቸው አገራት ዲፕሎማቶች ጋር በመሆን ክትትል እያደረገ ቢሆንም፣ የኩባ መንግሥት እስካሁን ስለ ሁኔታው የሰጠው ይፋዊ መግለጫ የለም።

ምንጭ: Mexican Navy - SEMAR
FIDEL POST NEWS
2 months ago
ዛሬ የቴአትር ቀን ነው

​ዛሬ መጋቢት 18 ቀን በዓለም አቀፍ የቴአትር ተቋም አነሳሽነት “የዓለም የቴአትር ቀን” እየተከበረ ይገኛል።

እ.ኤ.አ. ከ1961 ጀምሮ የሚታሰበው ይህ ዕለት፣ የቴአትር ጥበብ በሰው ልጅ ማህበራዊ ህይወት እና ሰብአዊነት ላይ ያለውን ሚና የሚያጎላ ነው።

እስከዛሬ ካያቹት ቴአትር የወደዳቹት የትኛው ነው? ምርጥ ተዋናያቹስ ማን ነው? ማን ናት?
FIDEL POST NEWS
2 months ago
​አይናችንን ስንጨፍን የምናየው ቀለም 'አይገንግራው' ይባላል፤ ይህም ጥቁር ከምንለው ቀለም የተለየ ነው።