14 days ago
የዓድዋ ድል መታሰቢያን የጎበኘው ‘ዲላን ፔጅ’ ኢትዮጵያ በቅኝ ያልተገዛችበትን ታሪካዊ ዳራ በአድናቆት ተመልክቶታል
**********************
በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተከታዮችን ያፈራው እንግሊዛዊው የቲክቶክ ተፅዕኖ ፈጣሪ ‘ዲላን ፔጅ’ በኢትዮጵያ እያደረገው ባለው ጉብኝት የሀገራችንን ገጽታ ለዓለም በማስተዋወቅ ላይ ይገኛል።
ዲላን በአዲስ አበባ ቆይታው የወንዝ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማትን ጨምሮ በመዲናዋ የተከናወኑ ቁልፍ የልማት ሥራዎችን እና የቱሪስት መዳረሻዎችን ተዟዙሮ ተመልክቷል።
በጉብኝቱ መሃል በአዲስ አበባ የወንዝ ዳርቻ ልማት መስክ አረንጓዴ ዐሻራውን በማሳረፍ የልማት ተሳትፎውን በማኅበራዊ ሚዲያ ለተከታዮቹ አጋርቷል።
ዝነኛው ቲክቶከር በፒያሳ የሚገኘውን የዓድዋ ድል መታሰቢያም የጎበኘ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ያልተገዛችበትን ታሪካዊ ፋና በአድናቆት ተመልክቷል።
በስፍራው ሲደርስ ደማቅ አቀባበል የተደረገለት ሲሆን፤ በባህላዊ የአፈላል ሥነ-ሥርዓት የተዘጋጀለትን የኢትዮጵያ ቡና ከመቅመስ በተጨማሪ የመታሰቢያ ስጦታዎች ተበርክተውለታል።
ዲላን ስለኢትዮጵያ ጉብኝቱ በሰጠው አስተያየት፣ ጉብኝቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ስለ አፍሪካ ያለውን የተዛባ አመለካከት ለመቀየር የሚያግዝ እንደሆነም ተናግሯል።
ተፅዕኖ ፈጣሪው ከአዲስ አበባ በተጨማሪ ወደፊት ሐረር እና አፋርን ጨምሮ የተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎችን ለመጎብኘት ያለውን ፍላጎት ገልጿል።
በቢታኒያ ሲሳይ
#dylanpage #ethiopia #addisababa #adwa #adwavictorymemorial #corridordevelopment #riversidedevelopment #greenlegacy #ebc
**********************
በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተከታዮችን ያፈራው እንግሊዛዊው የቲክቶክ ተፅዕኖ ፈጣሪ ‘ዲላን ፔጅ’ በኢትዮጵያ እያደረገው ባለው ጉብኝት የሀገራችንን ገጽታ ለዓለም በማስተዋወቅ ላይ ይገኛል።
ዲላን በአዲስ አበባ ቆይታው የወንዝ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማትን ጨምሮ በመዲናዋ የተከናወኑ ቁልፍ የልማት ሥራዎችን እና የቱሪስት መዳረሻዎችን ተዟዙሮ ተመልክቷል።
በጉብኝቱ መሃል በአዲስ አበባ የወንዝ ዳርቻ ልማት መስክ አረንጓዴ ዐሻራውን በማሳረፍ የልማት ተሳትፎውን በማኅበራዊ ሚዲያ ለተከታዮቹ አጋርቷል።
ዝነኛው ቲክቶከር በፒያሳ የሚገኘውን የዓድዋ ድል መታሰቢያም የጎበኘ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ያልተገዛችበትን ታሪካዊ ፋና በአድናቆት ተመልክቷል።
በስፍራው ሲደርስ ደማቅ አቀባበል የተደረገለት ሲሆን፤ በባህላዊ የአፈላል ሥነ-ሥርዓት የተዘጋጀለትን የኢትዮጵያ ቡና ከመቅመስ በተጨማሪ የመታሰቢያ ስጦታዎች ተበርክተውለታል።
ዲላን ስለኢትዮጵያ ጉብኝቱ በሰጠው አስተያየት፣ ጉብኝቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ስለ አፍሪካ ያለውን የተዛባ አመለካከት ለመቀየር የሚያግዝ እንደሆነም ተናግሯል።
ተፅዕኖ ፈጣሪው ከአዲስ አበባ በተጨማሪ ወደፊት ሐረር እና አፋርን ጨምሮ የተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎችን ለመጎብኘት ያለውን ፍላጎት ገልጿል።
በቢታኒያ ሲሳይ
#dylanpage #ethiopia #addisababa #adwa #adwavictorymemorial #corridordevelopment #riversidedevelopment #greenlegacy #ebc
17 days ago
የሀሮማያ ሐይቅ ዳግም መወለድ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የተፈጥሮን ጉዳት እያከመ ለመሆኑ ሕያው ማሳያ ነው፦ ተመስገን ጥሩነህ
*********************
በ1996 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ ጠፍቶ የነበረው የሀሮማያ ሐይቅ፣ በአረንጓዴ አሻራ እና በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ጥረት ዛሬ ወደ ቀደመ ውበትና ሥሪቱ መመለሱ ታውቋል።
ይህ የሐይቁ ዳግም መወለድ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከሰጣቸው ታላላቅ ፍሬዎች አንዱ ሲሆን፣ አረንጓዴ አሻራ ለኢትዮጵያ የውኃ አካላትና ለተፋሰስ ልማት ቁልፍ ኢኒሼቲቭ መሆኑን በተግባር ያረጋገጠ ስኬት ሆኗል።
ይህ የተመዘገበው ስኬት በመደመር እሳቤ ልማትን ማረጋገጥ ብቻ ሳይሆን፣ የተፈጥሮን ጫና መቋቋምና መግራት እንደሚቻል ትልቅ ማረጋገጫ መሆኑ ተገልጿል። በተጨማሪም ወደ ስፍራው በተደረገው ጉዞ በአካባቢው ለተደረገው ደማቅ አቀባበል ምስጋና መቅረቡ ታውቋል።
#haramayalake #greenlegacy #ethiopia
*********************
በ1996 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ ጠፍቶ የነበረው የሀሮማያ ሐይቅ፣ በአረንጓዴ አሻራ እና በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ጥረት ዛሬ ወደ ቀደመ ውበትና ሥሪቱ መመለሱ ታውቋል።
ይህ የሐይቁ ዳግም መወለድ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከሰጣቸው ታላላቅ ፍሬዎች አንዱ ሲሆን፣ አረንጓዴ አሻራ ለኢትዮጵያ የውኃ አካላትና ለተፋሰስ ልማት ቁልፍ ኢኒሼቲቭ መሆኑን በተግባር ያረጋገጠ ስኬት ሆኗል።
ይህ የተመዘገበው ስኬት በመደመር እሳቤ ልማትን ማረጋገጥ ብቻ ሳይሆን፣ የተፈጥሮን ጫና መቋቋምና መግራት እንደሚቻል ትልቅ ማረጋገጫ መሆኑ ተገልጿል። በተጨማሪም ወደ ስፍራው በተደረገው ጉዞ በአካባቢው ለተደረገው ደማቅ አቀባበል ምስጋና መቅረቡ ታውቋል።
#haramayalake #greenlegacy #ethiopia
1 month ago
ከምኞት ወደ እውነት፦ የኢትዮጵያ አዲሱ የሉዓላዊነት ጉዞ በ21ኛው ክፍለ ዘመን
**************
የኢትዮጵያ ታሪካዊ የሉዓላዊነት ጽንሰ-ሀሳብ በአብዛኛው የተገነባው ዜጎቿ ሀገርን ለማዳን በጦር ሜዳ ላይ በከፈሉት ወደር የለሽ መስዋዕትነት እና ባፈሰሱት ደም ነው።
በደም የተጠበቀ ታሪካዊ ነጻነቷን በኢኮኖሚ፣ በቴክኖሎጂ እና በአእምሮ በዳበረ የተሟላ ሉዓላዊነት ለማጽናት ታሪካዊ ጉዞ ላይ ትገኛለች፡፡
በ21ኛው ክፍለ ዘመን እውነተኛ ሉዓላዊነት ከድንበር ጥበቃ ባለፈ ከምግብ እና ከሌሎች የውጭ ጥገኝነት መላቀቅ መሆኑን በተግባር እያስመሰከረች ነው፡፡
በግብርናው ዘርፍ በየዓመቱ ለስንዴ ግዢ ይወጣ የነበረውን አንድ ቢሊዮን ዶላር በማስቀረት ራስን መቻል ለዚህ ትልቅ ማሳያ ነው፡፡
በ"ሌማት ትሩፋት" እና በ"አረንጓዴ አሻራ" መርሐግብሮች የተመዘገቡ ስኬቶችም የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ብሔራዊ ክብርን ከፍ አድርገዋል፡፡
በኢንዱስትሪው ዘርፍ "ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ ወደ ሥራ የተመለሱ 993 ፋብሪካዎች የኢኮኖሚ ሉዓላዊነታችንን እያጠናከሩ ይገኛሉ፡፡
እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም ያሉ የታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶች የኃይል ሉዓላዊነታችንን በማረጋገጥ የኢንዱስትሪውን ዕድገት እያፋጠኑ ነው፡፡
በቴክኖሎጂው ዘርፍ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ፣ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ እና የ5 ሚሊዮን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ወጣቶችን በክህሎት በማስታጠቅ ቴክኖሎጂያዊ ጥገኝነትን ለማስቀረት ውጤታማ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡
ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲው መስክም የራሷን ትርክት በራሷ ለመጻፍ የጀመረችው ጉዞ የዚሁ የተሟላ ሉዓላዊነት ማሳያ ነው፡፡ ይህ ታሪካዊ ሽግግር ለነገው ትውልድ የምናወርሰው ታላቅ ሀገራዊ ቃል ኪዳን ነው፡፡
ሙሉ መረጃውን ለማንበብ በአስተያየት መስጫ ውስጥ ያለውን ሊንክ ይጫኑ፡፡ 🔗
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #sovereignty #economictransformation #digitalethiopia #ethiopiatamrit #greenlegacy
**************
የኢትዮጵያ ታሪካዊ የሉዓላዊነት ጽንሰ-ሀሳብ በአብዛኛው የተገነባው ዜጎቿ ሀገርን ለማዳን በጦር ሜዳ ላይ በከፈሉት ወደር የለሽ መስዋዕትነት እና ባፈሰሱት ደም ነው።
በደም የተጠበቀ ታሪካዊ ነጻነቷን በኢኮኖሚ፣ በቴክኖሎጂ እና በአእምሮ በዳበረ የተሟላ ሉዓላዊነት ለማጽናት ታሪካዊ ጉዞ ላይ ትገኛለች፡፡
በ21ኛው ክፍለ ዘመን እውነተኛ ሉዓላዊነት ከድንበር ጥበቃ ባለፈ ከምግብ እና ከሌሎች የውጭ ጥገኝነት መላቀቅ መሆኑን በተግባር እያስመሰከረች ነው፡፡
በግብርናው ዘርፍ በየዓመቱ ለስንዴ ግዢ ይወጣ የነበረውን አንድ ቢሊዮን ዶላር በማስቀረት ራስን መቻል ለዚህ ትልቅ ማሳያ ነው፡፡
በ"ሌማት ትሩፋት" እና በ"አረንጓዴ አሻራ" መርሐግብሮች የተመዘገቡ ስኬቶችም የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ብሔራዊ ክብርን ከፍ አድርገዋል፡፡
በኢንዱስትሪው ዘርፍ "ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ ወደ ሥራ የተመለሱ 993 ፋብሪካዎች የኢኮኖሚ ሉዓላዊነታችንን እያጠናከሩ ይገኛሉ፡፡
እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም ያሉ የታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶች የኃይል ሉዓላዊነታችንን በማረጋገጥ የኢንዱስትሪውን ዕድገት እያፋጠኑ ነው፡፡
በቴክኖሎጂው ዘርፍ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ፣ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ እና የ5 ሚሊዮን ኮደሮች ኢኒሼቲቭ ወጣቶችን በክህሎት በማስታጠቅ ቴክኖሎጂያዊ ጥገኝነትን ለማስቀረት ውጤታማ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡
ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲው መስክም የራሷን ትርክት በራሷ ለመጻፍ የጀመረችው ጉዞ የዚሁ የተሟላ ሉዓላዊነት ማሳያ ነው፡፡ ይህ ታሪካዊ ሽግግር ለነገው ትውልድ የምናወርሰው ታላቅ ሀገራዊ ቃል ኪዳን ነው፡፡
ሙሉ መረጃውን ለማንበብ በአስተያየት መስጫ ውስጥ ያለውን ሊንክ ይጫኑ፡፡ 🔗
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #sovereignty #economictransformation #digitalethiopia #ethiopiatamrit #greenlegacy
1 month ago
አዲሱ የአራዳ ፓርክ የታሪክ ማስታወሻ የውበት ምንጭና የዘመናዊነት መገለጫ
#ethiopia | የአራዳ ፓርክ ቀደም ሲል የነበረውን የቆሻሻ የብክለትና የድህነት ገጽታ ሙሉ በሙሉ በመቀየር በአዲስ መልክ የተገነባ ታላቅ ፕሮጀክት ነው::
ይህ ስራ የቆዩ አሉታዊ የታሪክ አሻራዎችን በማጥፋት የኢትዮጵያን አዲስ ማንነትና ውበት ለትውልድ በሚተርክ መልኩ ተከናውኗል::
ከፒያሳ አካባቢ የለቀቁ ነዋሪዎች ለሰብአዊ ክብር ከማይመጥኑ ቤቶች ወጥተው መሰረተ ልማት ወደተሟላላቸው ዘመናዊ መኖሪያዎች እንዲገቡ ተደርጓል::
ነዋሪዎቹ ማህበራዊ ትስስራቸውን ሳይበጥሱ እድርና እቁባቸውን ጠብቀው እንዲኖሩ መደረጉም የልማቱ ልዩ ገጽታ ነው:: ፒያሳ ዳግም የተገነባችው እውነተኛ ስልጣኔን በሚያንጸባርቅ መልኩ ሲሆን በአካባቢው የነበሩ ወንዞችም ከቆሻሻ ጸድተው ለስራ እድል ፈጠራና ለቱሪስት መዳረሻነት እንዲውሉ ተደርገዋል::
በ40 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው የአራዳ ፓርክ የሚከተሉትን ዋና ዋና አገልግሎቶች ይዟል
የመንገድና የትራንስፖርት መሰረተ ልማት
5 ኪሎ ሜትር የአስፓልት መንገድ 6 ኪሎ ሜትር የእግረኛ መንገድ 5 ኪሎ ሜትር የብስክሌት መስመር እና 5 ኪሎ ሜትር የመሮጫ ትራክ ተገንብቶለታል::
የንግድና የፋይናንስ ዘርፍ
ከፒያሳ ለተነሱ ነጋዴዎች ቅድሚያ የሚሰጥባቸው 131 ዘመናዊ ሱቆች 7 ካፌና ሬስቶራንቶች አንድ ትልቅ ሱፐርማርኬት እና የባንክ ቅርንጫፍ ተካተዋል::
የመዝናኛና የስፖርት አገልግሎቶች
ዘመናዊ የአካል ብቃት ማእከል 7 አዳራሾች 8 ፕላዛዎች 3 አንፊ ቴአትሮች እና ማራኪ የሆነ ተንቀሳቃሽ ፏፏቴ ይገኛሉ:: በተጨማሪም 100 ሜትር ርዝመት ያለው የሀገሪቱ ረጅሙ የሰንደቅ ዓላማ መስቀያ በዚሁ ፓርክ ተተክሏል::
የህጻናትና ቤተሰብ ስፍራዎች
አራት ዘመናዊ የህጻናት መጫወቻዎች እና ህጻናት ስለ ሀገራቸው ግንዛቤ የሚያገኙበት ትንሿ ከተማ የተሰኘ ልዩ ስፍራ ተዘጋጅቷል::
የአረንጓዴ ልማትና የንጽህና አገልግሎት
15 ሄክታር መሬት በሳርና በተክሎች የተሸፈነ ሲሆን 22 የህዝብ መጸዳጃ ቤቶች እና 131 መኪናዎችን የሚይዝ ሰፊ ማቆሚያ ተገንብቷል::
ይህ ፕሮጀክት የመሬት አጠቃቀምን በብቃት ያረጋገጠ ሲሆን ከመሬት በታች ለሱቆችና ለአዳራሾች ከላይ ደግሞ ለፕላዛ አገልግሎት እንዲውል ተደርጓል::
እንዲሁም በአካባቢው የነበሩ ከ700 በላይ ታሪካዊ ቤቶችና ህንጻዎች ይዘታቸውን ሳይለቁ እንዲታደሱ ተደርጓል::
በአጠቃላይ ፓርኩ ከንግድ እስከ ስፖርት እንዲሁም ከቤተሰብ መዝናኛ እስከ ስነ ጥበብ መድረኮችን የያዘ የከተማዋ አዲስ የቱሪስት መስህብ ነው::
#aradapark #piassa #addisababacity #urbandevelopment #greenlegacy #tourismethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የአራዳ ፓርክ ቀደም ሲል የነበረውን የቆሻሻ የብክለትና የድህነት ገጽታ ሙሉ በሙሉ በመቀየር በአዲስ መልክ የተገነባ ታላቅ ፕሮጀክት ነው::
ይህ ስራ የቆዩ አሉታዊ የታሪክ አሻራዎችን በማጥፋት የኢትዮጵያን አዲስ ማንነትና ውበት ለትውልድ በሚተርክ መልኩ ተከናውኗል::
ከፒያሳ አካባቢ የለቀቁ ነዋሪዎች ለሰብአዊ ክብር ከማይመጥኑ ቤቶች ወጥተው መሰረተ ልማት ወደተሟላላቸው ዘመናዊ መኖሪያዎች እንዲገቡ ተደርጓል::
ነዋሪዎቹ ማህበራዊ ትስስራቸውን ሳይበጥሱ እድርና እቁባቸውን ጠብቀው እንዲኖሩ መደረጉም የልማቱ ልዩ ገጽታ ነው:: ፒያሳ ዳግም የተገነባችው እውነተኛ ስልጣኔን በሚያንጸባርቅ መልኩ ሲሆን በአካባቢው የነበሩ ወንዞችም ከቆሻሻ ጸድተው ለስራ እድል ፈጠራና ለቱሪስት መዳረሻነት እንዲውሉ ተደርገዋል::
በ40 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው የአራዳ ፓርክ የሚከተሉትን ዋና ዋና አገልግሎቶች ይዟል
የመንገድና የትራንስፖርት መሰረተ ልማት
5 ኪሎ ሜትር የአስፓልት መንገድ 6 ኪሎ ሜትር የእግረኛ መንገድ 5 ኪሎ ሜትር የብስክሌት መስመር እና 5 ኪሎ ሜትር የመሮጫ ትራክ ተገንብቶለታል::
የንግድና የፋይናንስ ዘርፍ
ከፒያሳ ለተነሱ ነጋዴዎች ቅድሚያ የሚሰጥባቸው 131 ዘመናዊ ሱቆች 7 ካፌና ሬስቶራንቶች አንድ ትልቅ ሱፐርማርኬት እና የባንክ ቅርንጫፍ ተካተዋል::
የመዝናኛና የስፖርት አገልግሎቶች
ዘመናዊ የአካል ብቃት ማእከል 7 አዳራሾች 8 ፕላዛዎች 3 አንፊ ቴአትሮች እና ማራኪ የሆነ ተንቀሳቃሽ ፏፏቴ ይገኛሉ:: በተጨማሪም 100 ሜትር ርዝመት ያለው የሀገሪቱ ረጅሙ የሰንደቅ ዓላማ መስቀያ በዚሁ ፓርክ ተተክሏል::
የህጻናትና ቤተሰብ ስፍራዎች
አራት ዘመናዊ የህጻናት መጫወቻዎች እና ህጻናት ስለ ሀገራቸው ግንዛቤ የሚያገኙበት ትንሿ ከተማ የተሰኘ ልዩ ስፍራ ተዘጋጅቷል::
የአረንጓዴ ልማትና የንጽህና አገልግሎት
15 ሄክታር መሬት በሳርና በተክሎች የተሸፈነ ሲሆን 22 የህዝብ መጸዳጃ ቤቶች እና 131 መኪናዎችን የሚይዝ ሰፊ ማቆሚያ ተገንብቷል::
ይህ ፕሮጀክት የመሬት አጠቃቀምን በብቃት ያረጋገጠ ሲሆን ከመሬት በታች ለሱቆችና ለአዳራሾች ከላይ ደግሞ ለፕላዛ አገልግሎት እንዲውል ተደርጓል::
እንዲሁም በአካባቢው የነበሩ ከ700 በላይ ታሪካዊ ቤቶችና ህንጻዎች ይዘታቸውን ሳይለቁ እንዲታደሱ ተደርጓል::
በአጠቃላይ ፓርኩ ከንግድ እስከ ስፖርት እንዲሁም ከቤተሰብ መዝናኛ እስከ ስነ ጥበብ መድረኮችን የያዘ የከተማዋ አዲስ የቱሪስት መስህብ ነው::
#aradapark #piassa #addisababacity #urbandevelopment #greenlegacy #tourismethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ሚድሮክን አመሠገኑ
#ethiopia | ትላንት ምሽት በአዲስ አበባ ከተማ ሌላ አዲስ ታሪክ ተፅፏል። የከተማዋን ውበትና የነዋሪዎቿን ማህበራዊ ትስስር ይበልጥ ያጠናክራል የተባለው "የሳር ቤት ፕላዛ" በከንቲባ አዳነች አቤቤ እና በከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ተመርቆ ለህዝብ አገልግሎት ክፍት ሆኗል።
ይህ ፕላዛ ልዩ የሚያደርገው ግንባታው የተከናወነበት 1.3 ሄክታር መሬት የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የግል ይዞታ የነበረ ቢሆንም፣ ድርጅቱ መሬቱን ለህዝብ መናፈሻነት እንዲውል በልዩ በጎ ፍቃድ መፍቀዱ ነው።
* ባለቤትነት፦ በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የተገነባ።
* ስፋት፦ 1.3 ሄክታር።
* አላማ፦የነዋሪዎችን የኑሮ ጫና ማቅለል እና ማህበራዊ መስተጋብርን ማጠናከር።
"አዲስ እሳቤ እና ትልቅ ለውጥ" — ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ከንቲባዋ በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ እንደገለጹት፣ የግል ሴክተሩ ከመንግስት ጋር በመቀናጀት ለከተማዋ እድገት እያሳየ ያለው ተነሳሽነት የሚደነቅ ነው። በተለይም ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የራሱን ይዞታ ለህዝብ ጥቅም እንዲውል ማድረጉን "አዲስ እሳቤ" ሲሉ አሞካሽተውታል።
"በከተማችን የምናከናውናቸው የልማት ስራዎች ለሰው ልጅ ክብርና ጥቅም የሚሰጡ ናቸው። ሚድሮክ በወንዝ ዳር ልማትም ጭምር አብሮን በመስራቱ በነዋሪዎች ስም ከልብ አመሰግናለሁ" — ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ይህ አዲስ ፕላዛ በአካባቢው ለሚገኙ ነዋሪዎች ከእለት ተእለት ውጥረት ማረፊያ ከመሆኑም ባለፈ፣ አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ምቹ እና ሳቢ የማድረግ ሰፋ ያለ ስትራቴጂ አካል ነው። መንግስትና የግል ባለሀብቱ እጅና ጓንት ሆነው ሲሰሩ የሚያስመዘግቡት ውጤት ማሳያ ተደርጎም ተወስዷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #አዲስአበባ #የሳርቤትፕላዛ #ልማት #ሚድሮክ #አዳነችአቤቤ #ኢትዮጵያ #addisababa #development #greenlegacy
#ethiopia | ትላንት ምሽት በአዲስ አበባ ከተማ ሌላ አዲስ ታሪክ ተፅፏል። የከተማዋን ውበትና የነዋሪዎቿን ማህበራዊ ትስስር ይበልጥ ያጠናክራል የተባለው "የሳር ቤት ፕላዛ" በከንቲባ አዳነች አቤቤ እና በከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ተመርቆ ለህዝብ አገልግሎት ክፍት ሆኗል።
ይህ ፕላዛ ልዩ የሚያደርገው ግንባታው የተከናወነበት 1.3 ሄክታር መሬት የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የግል ይዞታ የነበረ ቢሆንም፣ ድርጅቱ መሬቱን ለህዝብ መናፈሻነት እንዲውል በልዩ በጎ ፍቃድ መፍቀዱ ነው።
* ባለቤትነት፦ በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የተገነባ።
* ስፋት፦ 1.3 ሄክታር።
* አላማ፦የነዋሪዎችን የኑሮ ጫና ማቅለል እና ማህበራዊ መስተጋብርን ማጠናከር።
"አዲስ እሳቤ እና ትልቅ ለውጥ" — ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ከንቲባዋ በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ እንደገለጹት፣ የግል ሴክተሩ ከመንግስት ጋር በመቀናጀት ለከተማዋ እድገት እያሳየ ያለው ተነሳሽነት የሚደነቅ ነው። በተለይም ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የራሱን ይዞታ ለህዝብ ጥቅም እንዲውል ማድረጉን "አዲስ እሳቤ" ሲሉ አሞካሽተውታል።
"በከተማችን የምናከናውናቸው የልማት ስራዎች ለሰው ልጅ ክብርና ጥቅም የሚሰጡ ናቸው። ሚድሮክ በወንዝ ዳር ልማትም ጭምር አብሮን በመስራቱ በነዋሪዎች ስም ከልብ አመሰግናለሁ" — ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ይህ አዲስ ፕላዛ በአካባቢው ለሚገኙ ነዋሪዎች ከእለት ተእለት ውጥረት ማረፊያ ከመሆኑም ባለፈ፣ አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ምቹ እና ሳቢ የማድረግ ሰፋ ያለ ስትራቴጂ አካል ነው። መንግስትና የግል ባለሀብቱ እጅና ጓንት ሆነው ሲሰሩ የሚያስመዘግቡት ውጤት ማሳያ ተደርጎም ተወስዷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #አዲስአበባ #የሳርቤትፕላዛ #ልማት #ሚድሮክ #አዳነችአቤቤ #ኢትዮጵያ #addisababa #development #greenlegacy
2 months ago
ከበረሃማነት ወደ ምድር ገነት፦
የአርሶ አደር አብነት ዴላሞ አስደናቂ የስኬት ጉዞ!
#ethiopia | በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከምባታ ዞን የሚገኘው ወጣት አርሶ አደር አብነት ዴላሞ፣ ፈተናን ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር የግብርናን ትርጉም የቀየረ ብርቱ ወጣት ነው።
በአንድ ወቅት የገነባው ግዙፍ የውሃ ገንዳ ፈርሶ ንብረቱ ቢወድም፣ ተስፋ ሳይቆርጥ ተነስቶ ዛሬ ለሀገር ሞዴል የሚሆን ስራ ሰርቷል።
የአብነት ስኬት ምንጮች፦
ተቀናጀ ግብርና፦ በ10 ሄክታር መሬት ላይ የአትክልትና ፍራፍሬ፣ የሌማት ትሩፋት፣ የቡናና ቅመማ ቅመም ልማትን በማቀናጀት ውጤታማ ሆኗል።
አግሮ-ቱሪዝም (Agro-Tourism)፦
ግቢውን በውብ አበቦችና ዛፎች አስጊጦ፣ ለተመራማሪዎችና ለእንግዶች የሚያገለግሉ ዘመናዊ መኝታ ቤቶችን፣ የስብሰባ አዳራሽና ሎጅ መሰል አገልግሎቶችን በመገንባት የገጠር ኮሪደር ልማትን በተግባር አሳይቷል።
ለ10 ወጣቶች በቋሚነት እንዲሁም እስከ 80 ለሚደርሱ ወጣቶች በጊዜያዊነት የስራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፣ ከ400 በላይ አርሶ አደሮችን በቴክኖሎጂና በምክር ይደግፋል።
በ50 ሄክታር መሬት ላይ ትልቅ የቴክኖሎጂ ሽግግር የሚደረግበት የተቀናጀ የግብርና ማዕከል ለመገንባት በዝግጅት ላይ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በግንቦት 2017 ዓ.ም የአብነትን የስራ ቦታ ጎብኝተው፣ እንዲህ ያሉ ወጣቶች የሀገርን የብልጽግና ጉዞ ዕውን እንደሚያደርጉ መመስከራቸው ይታወሳል።
አዘጋጅ፡- ሰለሞን ደምሰው
ፎቶ፡- ጌታቸው ምትኩ
#getu #abnetdelamo #modelfarmer #agriculture #ethiopia #agriculturaltransformation #ከማምረትበላይ #beyondproduction #agrotourism #ethiopiaagriculture #greenlegacy #successstory #jobcreation #kembata #ethiopia #አርሶአደር #ስኬት #ግብርና #አረንጓዴአሻራ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
የአርሶ አደር አብነት ዴላሞ አስደናቂ የስኬት ጉዞ!
#ethiopia | በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከምባታ ዞን የሚገኘው ወጣት አርሶ አደር አብነት ዴላሞ፣ ፈተናን ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር የግብርናን ትርጉም የቀየረ ብርቱ ወጣት ነው።
በአንድ ወቅት የገነባው ግዙፍ የውሃ ገንዳ ፈርሶ ንብረቱ ቢወድም፣ ተስፋ ሳይቆርጥ ተነስቶ ዛሬ ለሀገር ሞዴል የሚሆን ስራ ሰርቷል።
የአብነት ስኬት ምንጮች፦
ተቀናጀ ግብርና፦ በ10 ሄክታር መሬት ላይ የአትክልትና ፍራፍሬ፣ የሌማት ትሩፋት፣ የቡናና ቅመማ ቅመም ልማትን በማቀናጀት ውጤታማ ሆኗል።
አግሮ-ቱሪዝም (Agro-Tourism)፦
ግቢውን በውብ አበቦችና ዛፎች አስጊጦ፣ ለተመራማሪዎችና ለእንግዶች የሚያገለግሉ ዘመናዊ መኝታ ቤቶችን፣ የስብሰባ አዳራሽና ሎጅ መሰል አገልግሎቶችን በመገንባት የገጠር ኮሪደር ልማትን በተግባር አሳይቷል።
ለ10 ወጣቶች በቋሚነት እንዲሁም እስከ 80 ለሚደርሱ ወጣቶች በጊዜያዊነት የስራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፣ ከ400 በላይ አርሶ አደሮችን በቴክኖሎጂና በምክር ይደግፋል።
በ50 ሄክታር መሬት ላይ ትልቅ የቴክኖሎጂ ሽግግር የሚደረግበት የተቀናጀ የግብርና ማዕከል ለመገንባት በዝግጅት ላይ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በግንቦት 2017 ዓ.ም የአብነትን የስራ ቦታ ጎብኝተው፣ እንዲህ ያሉ ወጣቶች የሀገርን የብልጽግና ጉዞ ዕውን እንደሚያደርጉ መመስከራቸው ይታወሳል።
አዘጋጅ፡- ሰለሞን ደምሰው
ፎቶ፡- ጌታቸው ምትኩ
#getu #abnetdelamo #modelfarmer #agriculture #ethiopia #agriculturaltransformation #ከማምረትበላይ #beyondproduction #agrotourism #ethiopiaagriculture #greenlegacy #successstory #jobcreation #kembata #ethiopia #አርሶአደር #ስኬት #ግብርና #አረንጓዴአሻራ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
4 months ago
🌍 "ለአረንጓዴ ምድር በአንድነት መተባበር!" 🤝🌿
#ethiopia | 25 ትምህርት ቤቶች ለአካባቢ ጥበቃ በጋራ ሊሰሩ ስምምነት አደረጉ
በዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ት/ቤት አዘጋጅነት በተካሄደ መድረክ፤ 25 የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች የአካባቢ ጥበቃን በትምህርት ቤቶች ውስጥ በጋራ ለመተግበር የሚያስችል ታሪካዊ ስምምነት ተፈራረሙ።
የስምምነቱ ዋና ዋና ትኩረቶች፡-
✅ መሠረታዊ መርሆች: Reduce, Reuse, Recycle እና Repeat የሚሉ መርሆችን በተማሪዎች፣ በመምህራንና በወላጆች ዘንድ ማስረፅ።
✅ ዲጂታል ሽግግር: የወረቀት አጠቃቀምን በመቀነስ ወደ ዲጂታል አሰራር መሸጋገር።
✅ አረንጓዴ ትውልድ: ከአረንጓዴ አሻራ እና ከተባበሩት መንግሥታት የዘላቂ ልማት ግቦች ጋር በተጣጣመ መልኩ ኃላፊነት የሚሰማው ትውልድ ማፍራት።
የዋን ፕላኔት በጎ ተግባራት:
የት/ቤቱ መስራች አቶ ዘላለም አማረ እንደገለጹት፤ ትምህርት ቤቱ ከተመሠረተበት 20 ዓመታት ውስጥ ከትምህርት ባሻገር ለማህበረሰቡ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል፡-
💧 ተማሪዎችን በማስተባበር ለ500 አባወራዎች ንፁህ የመጠጥ ውሃ እንዲያገኙ አድርጓል።
📚 ከ400 በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የነፃ ትምህርት እድል የሰጠ ሲሆን በቀጣይም ተደራሽነቱን እንደሚያሰፋ ተገልጿል።
ለአረንጓዴ ነገ፣ ዛሬ እንተባበር!
#oneplanetschool #greenschools #environment #sustainability #education #ethiopia #greenlegacy #sdgs #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
#ethiopia | 25 ትምህርት ቤቶች ለአካባቢ ጥበቃ በጋራ ሊሰሩ ስምምነት አደረጉ
በዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ት/ቤት አዘጋጅነት በተካሄደ መድረክ፤ 25 የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች የአካባቢ ጥበቃን በትምህርት ቤቶች ውስጥ በጋራ ለመተግበር የሚያስችል ታሪካዊ ስምምነት ተፈራረሙ።
የስምምነቱ ዋና ዋና ትኩረቶች፡-
✅ መሠረታዊ መርሆች: Reduce, Reuse, Recycle እና Repeat የሚሉ መርሆችን በተማሪዎች፣ በመምህራንና በወላጆች ዘንድ ማስረፅ።
✅ ዲጂታል ሽግግር: የወረቀት አጠቃቀምን በመቀነስ ወደ ዲጂታል አሰራር መሸጋገር።
✅ አረንጓዴ ትውልድ: ከአረንጓዴ አሻራ እና ከተባበሩት መንግሥታት የዘላቂ ልማት ግቦች ጋር በተጣጣመ መልኩ ኃላፊነት የሚሰማው ትውልድ ማፍራት።
የዋን ፕላኔት በጎ ተግባራት:
የት/ቤቱ መስራች አቶ ዘላለም አማረ እንደገለጹት፤ ትምህርት ቤቱ ከተመሠረተበት 20 ዓመታት ውስጥ ከትምህርት ባሻገር ለማህበረሰቡ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል፡-
💧 ተማሪዎችን በማስተባበር ለ500 አባወራዎች ንፁህ የመጠጥ ውሃ እንዲያገኙ አድርጓል።
📚 ከ400 በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የነፃ ትምህርት እድል የሰጠ ሲሆን በቀጣይም ተደራሽነቱን እንደሚያሰፋ ተገልጿል።
ለአረንጓዴ ነገ፣ ዛሬ እንተባበር!
#oneplanetschool #greenschools #environment #sustainability #education #ethiopia #greenlegacy #sdgs #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
5 months ago
በኢትዮጵያ የምግብ ፍላጎት መጨመር አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል
📌ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የሚያስችላትን የ10 ዓመት የጥምር ደን እርሻ (አግሮፎርስትሪ) ስትራቴጂ ይፋ አደረገች
#ethiopia | የግብርና ሚኒስቴር የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል፣ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችለውን ብሔራዊ የአግሮፎርስትሪ (ጥምር ደን እርሻ) ስትራቴጂ ይፋ አደረገ።
ይህ ከ2026 እስከ 2035 እ.ኤ.አ ለሚቀጥሉት አስር ዓመታት የሚያገለግለው ስትራቴጂ፣ ሚኒስቴሩ ከበርካታ የልማት አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር ያዘጋጀው መሆኑ ተገልጿል።
የስትራቴጂው አስፈላጊነት፦🖊
በግብርና ሚኒስቴር የሥራ አመራር ተወካይ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ጫላ ሆርዶፋ እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት የአፈር መሸርሸር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ እና እየጨመረ የመጣው የምግብ ፍላጎት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሰዋል።
ይህ ስትራቴጂም፦🔎
* የአርሶ አደሩን ኑሮ ለማሻሻል፣
* የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃን በሳይንሳዊ መንገድ ለመምራት፣
* የተቀናጀ የግብርና ስራን ለማስፋፋት ትልቅ ሚና ይኖረዋል ብለዋል።
በረሃማነትን የመከላከል ፋይዳ፦
በስትራቴጂው ዝግጅት ላይ የተሳተፈው የዓለም ጥምር ደን እርሻ ምርምር ማዕከል (ICRAF) ኮሚኒኬሽን ኦፊሰር አቶ እዮብ ጌታሁን ለብስራት ሬድዮ በሰጡት ቃል፤ በኢትዮጵያ ቀደም ሲል እርጥበት አዘል የነበሩ አካባቢዎች ወደ ደረቅ መሬትነት እየተቀየሩና በረሃማነት እየተስፋፋ መሆኑን ጠቁመዋል።
ይፋ የሆነው ስትራቴጂ አርሶ አደሮች ዛፎችን ከሰብልና ከእንስሳት እርባታ ጋር አጣምረው እንዲያለሙ (Agroforestry System) በማድረግ፣ የመሬትን ምርታማነት እንዲጨምሩና የአካባቢን አየር ንብረት እንዲያስተካክሉ ይረዳል ተብሏል።
ስትራቴጂው ተግባራዊ መደረጉ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብሯን በዘላቂነት ለማስቀጠል ለምታደርገው ጥረት ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን ተመልክቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia #agriculture #agroforestry #climatechange #greenlegacy #foodsecurity #sustainablefarming #news
📌ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የሚያስችላትን የ10 ዓመት የጥምር ደን እርሻ (አግሮፎርስትሪ) ስትራቴጂ ይፋ አደረገች
#ethiopia | የግብርና ሚኒስቴር የአፈር መሸርሸርን ለመከላከል፣ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችለውን ብሔራዊ የአግሮፎርስትሪ (ጥምር ደን እርሻ) ስትራቴጂ ይፋ አደረገ።
ይህ ከ2026 እስከ 2035 እ.ኤ.አ ለሚቀጥሉት አስር ዓመታት የሚያገለግለው ስትራቴጂ፣ ሚኒስቴሩ ከበርካታ የልማት አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር ያዘጋጀው መሆኑ ተገልጿል።
የስትራቴጂው አስፈላጊነት፦🖊
በግብርና ሚኒስቴር የሥራ አመራር ተወካይ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶክተር ጫላ ሆርዶፋ እንደገለጹት፤ በአሁኑ ወቅት የአፈር መሸርሸር፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ እና እየጨመረ የመጣው የምግብ ፍላጎት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሰዋል።
ይህ ስትራቴጂም፦🔎
* የአርሶ አደሩን ኑሮ ለማሻሻል፣
* የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃን በሳይንሳዊ መንገድ ለመምራት፣
* የተቀናጀ የግብርና ስራን ለማስፋፋት ትልቅ ሚና ይኖረዋል ብለዋል።
በረሃማነትን የመከላከል ፋይዳ፦
በስትራቴጂው ዝግጅት ላይ የተሳተፈው የዓለም ጥምር ደን እርሻ ምርምር ማዕከል (ICRAF) ኮሚኒኬሽን ኦፊሰር አቶ እዮብ ጌታሁን ለብስራት ሬድዮ በሰጡት ቃል፤ በኢትዮጵያ ቀደም ሲል እርጥበት አዘል የነበሩ አካባቢዎች ወደ ደረቅ መሬትነት እየተቀየሩና በረሃማነት እየተስፋፋ መሆኑን ጠቁመዋል።
ይፋ የሆነው ስትራቴጂ አርሶ አደሮች ዛፎችን ከሰብልና ከእንስሳት እርባታ ጋር አጣምረው እንዲያለሙ (Agroforestry System) በማድረግ፣ የመሬትን ምርታማነት እንዲጨምሩና የአካባቢን አየር ንብረት እንዲያስተካክሉ ይረዳል ተብሏል።
ስትራቴጂው ተግባራዊ መደረጉ ኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብሯን በዘላቂነት ለማስቀጠል ለምታደርገው ጥረት ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን ተመልክቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia #agriculture #agroforestry #climatechange #greenlegacy #foodsecurity #sustainablefarming #news
Sponsored by
Surafel