10 hours ago
ኢትዮጵያ ለዓለም ያስተማረችው አዲስ ታሪክ
****************
ትላንት በመላው ኢትዮጵያ በተካሄደው ታሪካዊ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ በ12 ሰዓታት ውስጥ ለመትከል ካቀደችው 800 ሚሊዮን ችግኝ 805 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል አዲስ የዓለም አቀፍ ሥነ ምህዳር ጥበቃ ታሪክ አስመዝግባለች።
ከማለዳው ጀምሮ በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ የመትከያ ስፍራዎች ወጣቶች፣ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አባላት እና ታዋቂ ግለሰቦች በተገኙበት የተካሄደው ይህ ታላቅ ሕዝባዊ ንቅናቄ ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ተፈጥሮአዊ ህልውና እና ለቀጣዩ ትውልድ አረንጓዴ ምድር ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጡበት ሆኗል።
ኢትዮጵያ ካቀደችው በላይ 805 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ባስመዘገበችው በዚህ ታላቅ ስኬት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጠንካራ መልእክቶችን አስተላልፋለች።
የአየር ንብረት መዛባትን ለመከላከል የሚደረገው ጥረት በመግለጫዎች እና በኮንፈረንሶች ብቻ ሳይሆን በተግባር መሬት ላይ በሚወርዱ ግዙፍ ሕዝባዊ ሥራዎች መመራት እንዳለበት በተግባር የተደገፈ መሪነቷን አሳይታለች።
በሌላ በኩል ሀገራችን የራሷን የደን ሽፋን ከማሳደግ እና የደረቁ የውኃ አካላትን ከመመለስ ባለፈ ለጎረቤት ሀገራት ችግኞችን በማካፈል በቀጣናው አረንጓዴ ኢኮኖሚን ለመገንባት የምታደርገውን ጥረት አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጣለች።
ኢትዮጵያ በራሷ አቅም እና በሕዝቧ ንቅናቄ ትልቅ ሀገራዊ ሀላፊነቷን መወጣቷን በመግለጽ የበለፀጉ ሀገራት እና የዓለም አቀፍ አካባቢ ጥበቃ ተቋማት ለአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የገቡትን የፋይናንስ እና የቴክኖሎጂ ድጋፍ ቃል በተግባር እንዲወጡ በድፍረት እንድትሞግት ትልቅ የዲፕሎማሲ ሞራል እና አቅም ፈጥሮላታል።
ይህ ታሪካዊ ስኬት ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተጣለባትን እምነት የሚያጸና ሲሆን፣ ሀገራችን በታላላቅ የዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤዎች ላይ በዘርፉ ያላትን የላቀ የሞራል ልዕልና እና ተደማጭነት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዳግም ያስመሰከረ ነው።
የተመዘገበው 805 ሚሊዮን ችግኝ ተከላ ስኬት የዛሬን የተፈጥሮ ቁስል እያከመ፣ የነገዋን ኢትዮጵያ እና የዓለምን ሥነ ምህዳር ለመጠበቅ በተግባር የተጻፈ ታሪካዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ምዕራፍ ነው።
በሃና ምንዳሁን
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #greenlegacy #planthope #climateresilience #ethiopiarising
****************
ትላንት በመላው ኢትዮጵያ በተካሄደው ታሪካዊ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ በ12 ሰዓታት ውስጥ ለመትከል ካቀደችው 800 ሚሊዮን ችግኝ 805 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል አዲስ የዓለም አቀፍ ሥነ ምህዳር ጥበቃ ታሪክ አስመዝግባለች።
ከማለዳው ጀምሮ በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ የመትከያ ስፍራዎች ወጣቶች፣ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አባላት እና ታዋቂ ግለሰቦች በተገኙበት የተካሄደው ይህ ታላቅ ሕዝባዊ ንቅናቄ ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ተፈጥሮአዊ ህልውና እና ለቀጣዩ ትውልድ አረንጓዴ ምድር ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጡበት ሆኗል።
ኢትዮጵያ ካቀደችው በላይ 805 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ባስመዘገበችው በዚህ ታላቅ ስኬት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጠንካራ መልእክቶችን አስተላልፋለች።
የአየር ንብረት መዛባትን ለመከላከል የሚደረገው ጥረት በመግለጫዎች እና በኮንፈረንሶች ብቻ ሳይሆን በተግባር መሬት ላይ በሚወርዱ ግዙፍ ሕዝባዊ ሥራዎች መመራት እንዳለበት በተግባር የተደገፈ መሪነቷን አሳይታለች።
በሌላ በኩል ሀገራችን የራሷን የደን ሽፋን ከማሳደግ እና የደረቁ የውኃ አካላትን ከመመለስ ባለፈ ለጎረቤት ሀገራት ችግኞችን በማካፈል በቀጣናው አረንጓዴ ኢኮኖሚን ለመገንባት የምታደርገውን ጥረት አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጣለች።
ኢትዮጵያ በራሷ አቅም እና በሕዝቧ ንቅናቄ ትልቅ ሀገራዊ ሀላፊነቷን መወጣቷን በመግለጽ የበለፀጉ ሀገራት እና የዓለም አቀፍ አካባቢ ጥበቃ ተቋማት ለአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የገቡትን የፋይናንስ እና የቴክኖሎጂ ድጋፍ ቃል በተግባር እንዲወጡ በድፍረት እንድትሞግት ትልቅ የዲፕሎማሲ ሞራል እና አቅም ፈጥሮላታል።
ይህ ታሪካዊ ስኬት ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተጣለባትን እምነት የሚያጸና ሲሆን፣ ሀገራችን በታላላቅ የዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤዎች ላይ በዘርፉ ያላትን የላቀ የሞራል ልዕልና እና ተደማጭነት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዳግም ያስመሰከረ ነው።
የተመዘገበው 805 ሚሊዮን ችግኝ ተከላ ስኬት የዛሬን የተፈጥሮ ቁስል እያከመ፣ የነገዋን ኢትዮጵያ እና የዓለምን ሥነ ምህዳር ለመጠበቅ በተግባር የተጻፈ ታሪካዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ምዕራፍ ነው።
በሃና ምንዳሁን
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #greenlegacy #planthope #climateresilience #ethiopiarising
1 day ago
በአንድ ጀንበር 805.3 ሚሊዮን ችግኝ ተተክሏል #greenlegacy #ethiopia #greeneconomy #environmentalprotection #agroforestry #ethiopiannews #climateaction
1 day ago
ለትውልድ የምናወርሰው ህያው ቅርስ
#ethiopia #greenlegacy #planting800million #digitalaudit #geospatialtechnology
Sponsored by
Surafel
1 day ago
በአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኞች የጋምቤላን ማህበረሰብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እያረጋገጡ ነው፦ ርዕሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ
**********************
በጋምቤላ ክልል በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ባለፉት ዓመታት የተተከሉ የደን እና የፍራፍሬ ችግኞች የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እያሳደጉ እንደሚገኙ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድሯ ይህንን ያብራሩት በዛሬው ዕለት ከፍተኛ የክልል አመራሮች እና በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት እየተካሄደ በሚገኘው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ ነው።
በሀገር አቀፍ ደረጃ በሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ ተሳትፎ 800 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀምበር ለመትከል የተያዘውን ታሪካዊ ግብ ለማሳካት፣ የጋምቤላ ክልል ማህበረሰብም ከማለዳው ጀምሮ በነቃ ተሳትፎ ልዩ ልዩ ጠቀሜታ ያላቸውን የደንና የፍራፍሬ ችግኞች በመትከል ላይ ይገኛል፡፡
ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ አለሚቱ መርሃ ግብሩን ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት፣ ባለፉት ሰባት ዓመታት በክልሉ በአረንጓዴ አሻራ የተከናወኑ ተግባራት የደን ሽፋኑ እንዲጨምር እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ዓይነተኛ ሚና ተጫውተዋል።
በተለይም የተተከሉ የፍራፍሬ ችግኞች ለቤት ውስጥ ምግብነት ከመዋል አልፈው ለገበያ በመቅረብ ላይ እንደሚገኙ የጠቆሙት ርዕሰ መስተዳድሯ፣ ይህም የማህበረሰቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ መቻሉን አስረድተዋል።
በቀጣይም በክልሉ የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን አሉታዊ ተፅዕኖ ለመቀነስ፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እንዲሁም ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት ሊሆኑ የሚችሉ የደንና የፍራፍሬ ችግኞችን በስፋት የመትከል ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ችግኝ የመትከል እና የመንከባከብ ባህል በሚገባ እየዳበረ በመምጣቱ፣ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም የታቀደውን ግብ በማሳካት የላቀ ስኬት ይመዘገባል ተብሎ በከፍተኛ ተስፋ ይጠበቃል።
በሚፍታህ አብዱልቃድር
#greenlegacy #gambella #ethiopia #treeplanting #climateaction
**********************
በጋምቤላ ክልል በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ባለፉት ዓመታት የተተከሉ የደን እና የፍራፍሬ ችግኞች የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እያሳደጉ እንደሚገኙ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ ገለጹ።
ርዕሰ መስተዳድሯ ይህንን ያብራሩት በዛሬው ዕለት ከፍተኛ የክልል አመራሮች እና በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት እየተካሄደ በሚገኘው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ ነው።
በሀገር አቀፍ ደረጃ በሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ ተሳትፎ 800 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀምበር ለመትከል የተያዘውን ታሪካዊ ግብ ለማሳካት፣ የጋምቤላ ክልል ማህበረሰብም ከማለዳው ጀምሮ በነቃ ተሳትፎ ልዩ ልዩ ጠቀሜታ ያላቸውን የደንና የፍራፍሬ ችግኞች በመትከል ላይ ይገኛል፡፡
ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ አለሚቱ መርሃ ግብሩን ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት፣ ባለፉት ሰባት ዓመታት በክልሉ በአረንጓዴ አሻራ የተከናወኑ ተግባራት የደን ሽፋኑ እንዲጨምር እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ዓይነተኛ ሚና ተጫውተዋል።
በተለይም የተተከሉ የፍራፍሬ ችግኞች ለቤት ውስጥ ምግብነት ከመዋል አልፈው ለገበያ በመቅረብ ላይ እንደሚገኙ የጠቆሙት ርዕሰ መስተዳድሯ፣ ይህም የማህበረሰቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ መቻሉን አስረድተዋል።
በቀጣይም በክልሉ የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን አሉታዊ ተፅዕኖ ለመቀነስ፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እንዲሁም ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት ሊሆኑ የሚችሉ የደንና የፍራፍሬ ችግኞችን በስፋት የመትከል ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ችግኝ የመትከል እና የመንከባከብ ባህል በሚገባ እየዳበረ በመምጣቱ፣ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም የታቀደውን ግብ በማሳካት የላቀ ስኬት ይመዘገባል ተብሎ በከፍተኛ ተስፋ ይጠበቃል።
በሚፍታህ አብዱልቃድር
#greenlegacy #gambella #ethiopia #treeplanting #climateaction
1 day ago
u1260u12a0u1295u12f5 u1300u121du1260u122d u12e8800 u121au120au12eeu1295 u127du130du129d u1270u12a8u120b - u1270u1235u134bu1295 u12a5u1295u1275u12a8u120d
#ethiopia #greenlegacy ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
በአንድ ጀምበር የ800 ሚሊዮን ችግኝ ተከላ - ተስፋን እንትከል
#ethiopia #greenlegacy
1 day ago
u1208u120du1306u127bu127du1295 u1218u1220u1228u1275 u12a5u12e8u1270u12a8u120du1295 u1290u12cd
#greenlegacy #ethiopia #ebc ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ለልጆቻችን መሠረት እየተከልን ነው
#greenlegacy #ethiopia #ebc
1 day ago
#ethiopia | "ኢትዮጵያውያን ዝቅ ብለው ለመሬት አደራ ይሰጣሉ፤ ምድርም የተሰጣትን አደራ እጥፍ አድርጋ ትመልሳለች፡፡"
- የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር
እናት አለም መለሰ
***
በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የተዘጋጀው ታሪካዊ ሀገራዊ መርሐ ግብር በይፋ ተጀመረ
ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 800 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል አዲስ ታሪክ ለመጻፍ ያቀደችውን ሀገራዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ዛሬ በይፋ ጀምራለች።
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ በሰጡት መግለጫ፣ መላው ኢትዮጵያውያን የተጎሳቀለችውን ምድር ለመመለስና ለቀጣይ ትውልድ ዘላቂ አሻራ ለማኖር በአንድነት መነሳታቸውን ገልጸዋል።
ሚኒስትሯ፣ “ኢትዮጵያውያን ዝቅ ብለው ለምድር አደራ ይሰጣሉ፤ ምድርም የተሰጣትን አደራ እጥፍ አድርጋ ትመልሳለች” በማለት የሕዝቡን የአንድነት መንፈስና ለተፈጥሮ ያለውን ቁርጠኝነት አድንቀዋል።
በ“ኑ ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ሐሳብ የሚካሄደው የዘንድሮው ዘመቻ፣ በመደመር መርህ ሁሉም የማኅበረሰብ ክፍሎች በንቃት እንዲሳተፉና 800 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ቀን የመትከል ግብ እንዲሳካ ጥሪ ቀርቧል።
መርሐ ግብሩ ዛሬ ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም. እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ድረስ በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ ሁሉም ክልሎችና የማኅበረሰብ ክፍሎች ተሳትፎ በሰፊው እንደሚከናወን ተገልጿል።
ይህ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በአካባቢ ጥበቃ፣ የደን ሽፋን መጨመር፣ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም እና ለቀጣዩ ትውልድ አረንጓዴ ኢትዮጵያን ለማስረከብ ከሚደረጉ ሀገራዊ ጥረቶች መካከል ቁልፍ ተነሳሽነት መሆኑ ተጠቅሷል።
#አረንጓዴአሻራ #greenlegacy #ethiopia #planttrees #climateaction #ጌጡተመስገን #getutemesgen
- የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር
እናት አለም መለሰ
***
በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የተዘጋጀው ታሪካዊ ሀገራዊ መርሐ ግብር በይፋ ተጀመረ
ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 800 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል አዲስ ታሪክ ለመጻፍ ያቀደችውን ሀገራዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ዛሬ በይፋ ጀምራለች።
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ በሰጡት መግለጫ፣ መላው ኢትዮጵያውያን የተጎሳቀለችውን ምድር ለመመለስና ለቀጣይ ትውልድ ዘላቂ አሻራ ለማኖር በአንድነት መነሳታቸውን ገልጸዋል።
ሚኒስትሯ፣ “ኢትዮጵያውያን ዝቅ ብለው ለምድር አደራ ይሰጣሉ፤ ምድርም የተሰጣትን አደራ እጥፍ አድርጋ ትመልሳለች” በማለት የሕዝቡን የአንድነት መንፈስና ለተፈጥሮ ያለውን ቁርጠኝነት አድንቀዋል።
በ“ኑ ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ሐሳብ የሚካሄደው የዘንድሮው ዘመቻ፣ በመደመር መርህ ሁሉም የማኅበረሰብ ክፍሎች በንቃት እንዲሳተፉና 800 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ቀን የመትከል ግብ እንዲሳካ ጥሪ ቀርቧል።
መርሐ ግብሩ ዛሬ ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም. እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ድረስ በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ ሁሉም ክልሎችና የማኅበረሰብ ክፍሎች ተሳትፎ በሰፊው እንደሚከናወን ተገልጿል።
ይህ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በአካባቢ ጥበቃ፣ የደን ሽፋን መጨመር፣ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም እና ለቀጣዩ ትውልድ አረንጓዴ ኢትዮጵያን ለማስረከብ ከሚደረጉ ሀገራዊ ጥረቶች መካከል ቁልፍ ተነሳሽነት መሆኑ ተጠቅሷል።
#አረንጓዴአሻራ #greenlegacy #ethiopia #planttrees #climateaction #ጌጡተመስገን #getutemesgen
Sponsored by
Surafel
1 day ago
በአንድ ጀምበር የ800 ሚሊዮን ችግኝ ተከላ - ተስፋን እንትከል
#ethiopia #greenlegacy
በአንድ ጀምበር የ800 ሚሊዮን ችግኝ ተከላ - ተስፋን እንትከል
#ethiopia #greenlegacy
2 days ago
u12e8u12a5u129b u12e8u1201u120bu127du1295u121d u1200u1308u122d u12e8u121bu120du1260u1235 u1309u12de
#ethiopia #greenlegacy #pmabiyahmed #ebc ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
የእኛ የሁላችንም ሀገር የማልበስ ጉዞ
#ethiopia #greenlegacy #pmabiyahmed #ebc
2 days ago
u1260u12a0u1295u12f5 u1300u121du1260u122d u12e8800 u121au120au12eeu1295 u127du130du129d u1270u12a8u120b - u1270u1235u134bu1295 u12a5u1295u1275u12a8u120d
#ethiopia #greenlegacy ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
በአንድ ጀምበር የ800 ሚሊዮን ችግኝ ተከላ - ተስፋን እንትከል
#ethiopia #greenlegacy
2 days ago
"ዛሬ ታሪክ የምንሰራበት ቀን ነው፤ 800 ሚሊዮን ተስፋዎችን አብረን እንትከል"
Ethiopian Broadcasting Corporation #ethiopia #climateaction #greenlegacy #አረንጓዴአሻራ #greenethiopia #ebc
Ethiopian Broadcasting Corporation #ethiopia #climateaction #greenlegacy #አረንጓዴአሻራ #greenethiopia #ebc
2 days ago
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ለነገው የአንድ ጀምበር አረንጓዴ ዐሻራ የተደረገ ቅድመ ዝግጅት (በምሥል)
#ethiopia #climateaction #greenlegacy #southwestethiopiaregion #greenethiopia #ebc
#ethiopia #climateaction #greenlegacy #southwestethiopiaregion #greenethiopia #ebc
2 days ago
በነገው የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ በንቃት ለመሳተፍ ተዘጋጅተናል - የኢሉአባቦር ዞን ነዋሪዎች
*****************
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) ሀገራዊ ጥሪ በመቀበል በነገው ዕለት በሚካሄደው የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር በንቃት ለመሳተፍ መዘጋጀታቸውን የኢሉአባቦር ዞን ነዋሪዎች ገለጹ።
የዞኑ ነዋሪዎች እንዳሉት፣ ባለፉት ተከታታይ ዓመታት በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በተከሏቸው ችግኞች በየአካባቢያቸው የተራቆቱ ስፍራዎች መልሰው አገግመዋል።
የአካባቢ ጥበቃ ሥራው ሥነ ምሕዳር እንዲያገግም፣ የአፈር ለምነት እንዲሻሻል እንዲሁም ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር አስችሏል።
የተከሏቸውን ፍራፍሬ ለምግብነት በማዋል እና ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆን መጀመራቸውንም ነዋሪዎቹ ለኢቢሲ ተናግረዋል።
በዞን ደረጃ የነገውን የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ ዕቅድ ለማሳካት የሚያስችል በቂ ቅድመ ዝግጅት ስለመደረጉ ተገልጿል።
አስቀድሞ በተለዩ 299 የችግኝ ተከላ ሳይቶች የጉድጓድ ቁፋሮ ተከናውኖ የሚተከሉ ችግኞችም ወደየስፍራው ተጓጉዘዋል ነው የተባለው።
በሚፍታህ አብዱልቃድር
#ethiopia #climateaction #greenlegacy #iluabbaborzone #greenethiopia #ebc
*****************
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) ሀገራዊ ጥሪ በመቀበል በነገው ዕለት በሚካሄደው የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር በንቃት ለመሳተፍ መዘጋጀታቸውን የኢሉአባቦር ዞን ነዋሪዎች ገለጹ።
የዞኑ ነዋሪዎች እንዳሉት፣ ባለፉት ተከታታይ ዓመታት በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በተከሏቸው ችግኞች በየአካባቢያቸው የተራቆቱ ስፍራዎች መልሰው አገግመዋል።
የአካባቢ ጥበቃ ሥራው ሥነ ምሕዳር እንዲያገግም፣ የአፈር ለምነት እንዲሻሻል እንዲሁም ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር አስችሏል።
የተከሏቸውን ፍራፍሬ ለምግብነት በማዋል እና ለገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ መሆን መጀመራቸውንም ነዋሪዎቹ ለኢቢሲ ተናግረዋል።
በዞን ደረጃ የነገውን የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ ዕቅድ ለማሳካት የሚያስችል በቂ ቅድመ ዝግጅት ስለመደረጉ ተገልጿል።
አስቀድሞ በተለዩ 299 የችግኝ ተከላ ሳይቶች የጉድጓድ ቁፋሮ ተከናውኖ የሚተከሉ ችግኞችም ወደየስፍራው ተጓጉዘዋል ነው የተባለው።
በሚፍታህ አብዱልቃድር
#ethiopia #climateaction #greenlegacy #iluabbaborzone #greenethiopia #ebc
2 days ago
የሐረማያ ሐይቅ ማንሰራራት፦ የአረንጓዴ ዐሻራ ትሩፋት ማሳያ
********************
በተፈጥሯዊ እና በሰው ሰራሽ ምክንያት ሙሉ በሙሉ ደርቆ ወደ አቧራማ ሜዳነት ተቀይሮ የነበረው ታሪካዊው ሐረማያ ሐይቅ አሁን ላይ በዘላቂ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ እና በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አማካኝነት ወደ ቀድሞ ይዘቱ ተመልሷል።
የሐረማያ ሐይቅ በዚህ መልኩ ማገገሙ በዕቅድ እና በጋራ ጥረት የተራቆቱ ሌሎች ተፋሰሶችንም ወደነበሩበት ሁኔታ መመለስ እንደሚቻል የሚያሳይ ሕያው ማረጋገጫ ሆኗል።
ሐረማያ ሐይቅ ለሐረማያ እና ለሐረር ከተሞች፣ ለሐረማያ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም ለአካባቢው ነዋሪዎች ዋነኛ የንጹህ መጠጥ ውኃና የግብርና መሠረት የነበረ ቢሆንም፣ በከፍተኛ የደን መጨፍጨፍ እና በደለል መሞላት ምክንያት ውኃ የመያዝ አቅሙን አጥቶ ተስፋ ተቆርጦበት የነበረ ነው።
ሆኖም ባለፉት ዓመታት በሐይቁ የላይኛው ተፋሰስ አካባቢዎች በተከናወነ የችግኝ ተከላ እና የእርከን ሥራ ወደ ሐይቁ ይገባ የነበረውን ከፍተኛ ደለል ከምንጩ መግታት ተችሏል።
በሌላ በኩል በሐይቁ ዙሪያ በተሠሩ የውኃ ማሳረፊያዎች አማካኝነት የዝናብ ውኃ ወደ መሬት እንዲሰርግ በማድረግ የሐይቁን ከርሰ ምድር ውኃ ክምችት እንዲጨምር ሆኗል።
በዚህም ሐይቁ ዳግም ውኃ መያዝ በመጀመሩ ቀደም ሲል አካባቢውን ለቀው የተሰደዱ በርካታ አእዋፍ፣ የጠፉ ዓሳዎች እና ሌሎች የውኃ ሕይወቶች እየተመለሱ ይገኛሉ።
የሐረማያ ሐይቅ ተሞክሮ ነገ የሚካሄደው የአንድ ጀምበር አረንጓዴ ዐሻራ ሀገር አቀፍ ንቅናቄ ተራ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ሳይሆን የታመመ ተፈጥሮን አክሞ የማዳን ሀገራዊ ጥረት መሆኑን የሚያስረግጥ ነው።
ይህ ተሞክሮ እያንዳንዱ ችግኝ የተራቆቱ አካባቢዎችን መልሶ የማቋቋም፣ የውኃ አካላትን የመታደግ እና የተጎዳ ተፈጥሮን የማከም ወሳኝ ድርሻ ይጫወታል።
ነገ በአንድ ጀምበር በጋራ የምናኖረው አረንጓዴ ዐሻራ የዛሬን የተፈጥሮ ቁስል እያከመ፣ የነገዋን ኢትዮጵያ በውኃ ሀብት እና በልምላሜ ሙሉ የሚያደርግ ታሪካዊ ተግባር ነው።
በሐና ምንዳሁን
#ethiopia #climateaction #greenlegacy #800milliontrees #lakeharamaya #ebc #ebcdotstream
********************
በተፈጥሯዊ እና በሰው ሰራሽ ምክንያት ሙሉ በሙሉ ደርቆ ወደ አቧራማ ሜዳነት ተቀይሮ የነበረው ታሪካዊው ሐረማያ ሐይቅ አሁን ላይ በዘላቂ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ እና በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አማካኝነት ወደ ቀድሞ ይዘቱ ተመልሷል።
የሐረማያ ሐይቅ በዚህ መልኩ ማገገሙ በዕቅድ እና በጋራ ጥረት የተራቆቱ ሌሎች ተፋሰሶችንም ወደነበሩበት ሁኔታ መመለስ እንደሚቻል የሚያሳይ ሕያው ማረጋገጫ ሆኗል።
ሐረማያ ሐይቅ ለሐረማያ እና ለሐረር ከተሞች፣ ለሐረማያ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም ለአካባቢው ነዋሪዎች ዋነኛ የንጹህ መጠጥ ውኃና የግብርና መሠረት የነበረ ቢሆንም፣ በከፍተኛ የደን መጨፍጨፍ እና በደለል መሞላት ምክንያት ውኃ የመያዝ አቅሙን አጥቶ ተስፋ ተቆርጦበት የነበረ ነው።
ሆኖም ባለፉት ዓመታት በሐይቁ የላይኛው ተፋሰስ አካባቢዎች በተከናወነ የችግኝ ተከላ እና የእርከን ሥራ ወደ ሐይቁ ይገባ የነበረውን ከፍተኛ ደለል ከምንጩ መግታት ተችሏል።
በሌላ በኩል በሐይቁ ዙሪያ በተሠሩ የውኃ ማሳረፊያዎች አማካኝነት የዝናብ ውኃ ወደ መሬት እንዲሰርግ በማድረግ የሐይቁን ከርሰ ምድር ውኃ ክምችት እንዲጨምር ሆኗል።
በዚህም ሐይቁ ዳግም ውኃ መያዝ በመጀመሩ ቀደም ሲል አካባቢውን ለቀው የተሰደዱ በርካታ አእዋፍ፣ የጠፉ ዓሳዎች እና ሌሎች የውኃ ሕይወቶች እየተመለሱ ይገኛሉ።
የሐረማያ ሐይቅ ተሞክሮ ነገ የሚካሄደው የአንድ ጀምበር አረንጓዴ ዐሻራ ሀገር አቀፍ ንቅናቄ ተራ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ሳይሆን የታመመ ተፈጥሮን አክሞ የማዳን ሀገራዊ ጥረት መሆኑን የሚያስረግጥ ነው።
ይህ ተሞክሮ እያንዳንዱ ችግኝ የተራቆቱ አካባቢዎችን መልሶ የማቋቋም፣ የውኃ አካላትን የመታደግ እና የተጎዳ ተፈጥሮን የማከም ወሳኝ ድርሻ ይጫወታል።
ነገ በአንድ ጀምበር በጋራ የምናኖረው አረንጓዴ ዐሻራ የዛሬን የተፈጥሮ ቁስል እያከመ፣ የነገዋን ኢትዮጵያ በውኃ ሀብት እና በልምላሜ ሙሉ የሚያደርግ ታሪካዊ ተግባር ነው።
በሐና ምንዳሁን
#ethiopia #climateaction #greenlegacy #800milliontrees #lakeharamaya #ebc #ebcdotstream
2 days ago
በምስራቅ ሸዋ ዞን ለነገው የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ዝግጅት ተጠናቅቋል
#ethiopia #climateaction #greenlegacy #eastshoazone #greenethiopia #ebc
#ethiopia #climateaction #greenlegacy #eastshoazone #greenethiopia #ebc
2 days ago
"ነገን ዛሬ በመትከል፣ ለትውልድ ለም ኢትዮጵያን እናወርሳለን።" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
#ethiopia #greenlegacy #pmabiyahmed #plantinghope #ebc
#ethiopia #greenlegacy #pmabiyahmed #plantinghope #ebc
2 days ago
የአረንጓዴ ዐሻራ የሰባት ዓመታት ሰባት አንኳር ስኬቶች
*************
አረንጓዴ ዐሻራ በኢትዮጵያ ምድር ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ባለፉት ሰባት ዓመታት፣ ሀገራችንን ከአፈር መሸርሸር እና ከበረሃማነት የመታደግ ሀገራዊ ራዕይ ብቻ ሳይሆን፤ የምድርን ሕይወት የሚያድስ፣ የዜጎችን ሥነ-ልቦናዊ አስተሳሰብ የሚቀርጽ እና ኢኮኖሚያዊ አቅም የሚገነባ ታላቅ ሕዝባዊ ንቅናቄ ሆኖ ዘልቋል።
ይህ ሀገራዊ የሕልውና ጥረት ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስትራቴጂዎች ጋር ተናብቦ ባለፉት ሰባት ዓመታት ያስመዘገባቸው ሰባት ዋና ዋና ተጨባጭ ስኬቶች እንደሚከተለው ተተንትነዋል።
1. የችግኝ ብዛትን ከጽድቀት ምጣኔ ጋር ያጣመረ አዲስ ታሪካዊ ሽግግር
ባለፉት ሰባት ዓመታት በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞች መተከላቸው ብቻ ሳይሆን፣ የተከላው ዋና ትኩረት ወደ ጥራት እና ድኅረ-ተከላ እንክብካቤ በማደጉ የችግኞች ጽድቀት ምጣኔ ከ80 በመቶ በላይ ማደግ ችሏል።
ይህም ቀደም ሲል የነበረውን "መተከል እንጂ አለመጽደቅ" የሚል የብክነት ታሪክን በመቀየር በቆላ እና በደጋ አካባቢዎች የተጎዱ መሬቶች በፍጥነት አረንጓዴ እንዲለብሱ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ሚዛን እንዲጠበቅ አድርጓል።
2. ከአካባቢ ጥበቃ ወደ የምግብ ዋስትና የተደረገ መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግር
አረንጓዴ ዐሻራ ከተፈጥሮ የደን ዛፎች ባሻገር እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ፣ አፕል እና ቡና ያሉ ፍሬያማ ተክሎችን በስፋት አካትቷል።
ይህ ስትራቴጂያዊ እርምጃ ፕሮጀክቱን ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጥ እና አባወራዎችን የገበያ ተጠቃሚ የሚያደርግ፣ ብሎም የሀገራችን የግብርና ምርት የወጪ ንግድ የሚያሳድግ የኢኮኖሚ ሞተር አድርጎታል።
ይህም የአካባቢ ጥበቃን ከዜጎች የዕለት ተዕለት ኑሮ ማሻሻል ግብ ጋር በማስተሳሰር ዘላቂነቱ የተረጋገጠ የልማት ምሰሶ እንዲሆን አስችሎታል።
3. የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ እና የወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ
በመላ ሀገራችን የተቋቋሙት በዐሥር ሺዎች የሚቆጠሩ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ለብዙ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣቶች እና ለሴቶች አዲስ እና ዘላቂ የገቢ ምንጭ ሆነዋል።
ችግኝ ማፍላት፣ መንከባከብ እና ለገበያ ማቅረብ በራሱ አዲስ የኢንቨስትመንት ዘርፍ እና የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የሀገራችንን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ጅማሮ በጠንካራ መሠረት ላይ አኑሮታል።
ችግኞች ከተተከሉ በኋላ የሚደረገው ጥበቃ እና ክብካቤም በርካታ ወጣቶችን ተጠቃሚ ያደረገ ቋሚ የሥራ ዘርፍ መሆን ችሏል።
4. የውኃ ሀብት እና የታላላቅ ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች ዋስትና
በስፋት የተከናወነው የደን ልማት እና የአፈር ጥበቃ ሥራ የአፈር መሸርሸርን በመቀነስ፣ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ያሉ ሀገራዊ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫዎች በደለል እንዳይሞሉ የመከላከል ታሪካዊ ሚና ተጫውቷል።
በተጨማሪም የከርሰ ምድር ውኃ መጠን እንዲያገግም እና የደረቁ የምንጭ ውኃዎች መልሰው እንዲፈልቁ በማድረግ አስተማማኝ የውኃ ዋስትናን እያረጋገጠ ይገኛል።
ይህ ታላላቅ መሠረተ ልማቶችን የመጠበቅ አቅም ለኢትዮጵያ ብልጽግና ብቻ ሳይሆን፣ ሀገራችን የውኃ ምንጭ ለሆነችላቸው የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጭምር ትልቅ ትሩፋት ነው።
5. አረንጓዴ ዲፕሎማሲ እና የቀጣናዊ ትሥሥር ማጠናከሪያ
ኢትዮጵያ ያዘጋጀቻቸውን ችግኞች እንደ ጂቡቲ፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ኬንያ ላሉት ጎረቤት ሀገራት በማጋራት፣ የምሥራቅ አፍሪካን እና የአፍሪካ ቀንድን የቀጣና አየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮት በጋራ የመከላከል መሪነት ሚናዋን በተግባር አሳይታለች።
ይህም አረንጓዴ ዐሻራን የድንበር ተሻጋሪ ዲፕሎማሲ፣ የቀጠናው ሰላም እና የጋራ ልማት መሣሪያ አድርጎታል።
በርካታ የአፍሪካ ሀገራትም የኢትዮጵያን ፈለግ በመከተል የአረንጓዴ ልማትን በሀገሮቻቸው እያስፋፉ ይገኛሉ።
ከዚህ ባሻገር፣ ኢትዮጵያ ባመጣቻቸው ተጨባጭ ስኬቶች “ዘላቂ የደን ልማት አያያዝ እና አጠቃቀም” በሚል ዘርፍ ከዓለም የምግብ እና እርሻ ድርጅት (FAO) ከፍተኛ እውቅናን አግኝታለች።
6. የከተሞች ሥነ-ምኅዳር መታደስ እና የኮሪደር ልማት ውበት
አረንጓዴ ዐሻራ በገጠር ተራራዎች ብቻ ተወስኖ ሳይቀር ወደ ከተሞች በመግባት የዘመናዊ ፓርኮች ግንባታ፣ የከተማ አረንጓዴ ልማት እና አሁን ላይ በስፋት እየተተገበረ ላለው የኮሪደር ልማት ዋነኛ አካል ሆኗል።
ይህም የከተሞችን የአየር ጥራት በከፍተኛ ደረጃ ከመጨመሩም በላይ፣ የሥነ-ሕይወት ስብጥርን ወደ ነበረበት በመመለስ እና ለዜጎች ምቹ የመዝናኛ እና የኑሮ አካባቢን በመፍጠር የከተሞቻችንን ገጽታ ሙሉ በሙሉ በመለወጥ ላይ ይገኛል።
7. ሕዝባዊ ንቅናቄ እና የዜግነት አገልግሎት ባህል ግንባታ
በአንድ ጀምበር በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ችግኝ የመተከል ልምዳቸው፣ የአካባቢ ጥበቃን ከዘመቻነት አውጥቶ የባህል እና የዜግነት ግዴታ አካል አድርጎታል።
ይህም የሕዝባዊ ወንድማማችነትን ያጠናከረ እና የአካባቢ ጥበቃ ግንዛቤን በማሳደግ ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር እጅግ ግዙፍ ማኅበራዊ እና ሥነ-ልቦናዊ ስኬት ነው።
በአጠቃላይ አረንጓዴ ዐሻራ ባለፉት ሰባት ዓመታት የተፈጥሮ ሀብታችንን ከመመለስ አልፎ ሀገራዊ አንድነትን ያጠናከረ፣ የማክሮ ኢኮኖሚ አቅማችንን የገነባ እና ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ አቅራቢ ሀገር ያደረገ አንጸባራቂ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #greenlegacy #climateaction #greendiplomacy #greeneconomy
*************
አረንጓዴ ዐሻራ በኢትዮጵያ ምድር ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ባለፉት ሰባት ዓመታት፣ ሀገራችንን ከአፈር መሸርሸር እና ከበረሃማነት የመታደግ ሀገራዊ ራዕይ ብቻ ሳይሆን፤ የምድርን ሕይወት የሚያድስ፣ የዜጎችን ሥነ-ልቦናዊ አስተሳሰብ የሚቀርጽ እና ኢኮኖሚያዊ አቅም የሚገነባ ታላቅ ሕዝባዊ ንቅናቄ ሆኖ ዘልቋል።
ይህ ሀገራዊ የሕልውና ጥረት ከሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስትራቴጂዎች ጋር ተናብቦ ባለፉት ሰባት ዓመታት ያስመዘገባቸው ሰባት ዋና ዋና ተጨባጭ ስኬቶች እንደሚከተለው ተተንትነዋል።
1. የችግኝ ብዛትን ከጽድቀት ምጣኔ ጋር ያጣመረ አዲስ ታሪካዊ ሽግግር
ባለፉት ሰባት ዓመታት በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞች መተከላቸው ብቻ ሳይሆን፣ የተከላው ዋና ትኩረት ወደ ጥራት እና ድኅረ-ተከላ እንክብካቤ በማደጉ የችግኞች ጽድቀት ምጣኔ ከ80 በመቶ በላይ ማደግ ችሏል።
ይህም ቀደም ሲል የነበረውን "መተከል እንጂ አለመጽደቅ" የሚል የብክነት ታሪክን በመቀየር በቆላ እና በደጋ አካባቢዎች የተጎዱ መሬቶች በፍጥነት አረንጓዴ እንዲለብሱ እና ሥነ-ምኅዳራዊ ሚዛን እንዲጠበቅ አድርጓል።
2. ከአካባቢ ጥበቃ ወደ የምግብ ዋስትና የተደረገ መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግር
አረንጓዴ ዐሻራ ከተፈጥሮ የደን ዛፎች ባሻገር እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ፣ አፕል እና ቡና ያሉ ፍሬያማ ተክሎችን በስፋት አካትቷል።
ይህ ስትራቴጂያዊ እርምጃ ፕሮጀክቱን ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ የቤተሰብ የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጥ እና አባወራዎችን የገበያ ተጠቃሚ የሚያደርግ፣ ብሎም የሀገራችን የግብርና ምርት የወጪ ንግድ የሚያሳድግ የኢኮኖሚ ሞተር አድርጎታል።
ይህም የአካባቢ ጥበቃን ከዜጎች የዕለት ተዕለት ኑሮ ማሻሻል ግብ ጋር በማስተሳሰር ዘላቂነቱ የተረጋገጠ የልማት ምሰሶ እንዲሆን አስችሎታል።
3. የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ እና የወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ
በመላ ሀገራችን የተቋቋሙት በዐሥር ሺዎች የሚቆጠሩ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ለብዙ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣቶች እና ለሴቶች አዲስ እና ዘላቂ የገቢ ምንጭ ሆነዋል።
ችግኝ ማፍላት፣ መንከባከብ እና ለገበያ ማቅረብ በራሱ አዲስ የኢንቨስትመንት ዘርፍ እና የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ የሀገራችንን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ጅማሮ በጠንካራ መሠረት ላይ አኑሮታል።
ችግኞች ከተተከሉ በኋላ የሚደረገው ጥበቃ እና ክብካቤም በርካታ ወጣቶችን ተጠቃሚ ያደረገ ቋሚ የሥራ ዘርፍ መሆን ችሏል።
4. የውኃ ሀብት እና የታላላቅ ሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች ዋስትና
በስፋት የተከናወነው የደን ልማት እና የአፈር ጥበቃ ሥራ የአፈር መሸርሸርን በመቀነስ፣ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ያሉ ሀገራዊ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ማመንጫዎች በደለል እንዳይሞሉ የመከላከል ታሪካዊ ሚና ተጫውቷል።
በተጨማሪም የከርሰ ምድር ውኃ መጠን እንዲያገግም እና የደረቁ የምንጭ ውኃዎች መልሰው እንዲፈልቁ በማድረግ አስተማማኝ የውኃ ዋስትናን እያረጋገጠ ይገኛል።
ይህ ታላላቅ መሠረተ ልማቶችን የመጠበቅ አቅም ለኢትዮጵያ ብልጽግና ብቻ ሳይሆን፣ ሀገራችን የውኃ ምንጭ ለሆነችላቸው የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ጭምር ትልቅ ትሩፋት ነው።
5. አረንጓዴ ዲፕሎማሲ እና የቀጣናዊ ትሥሥር ማጠናከሪያ
ኢትዮጵያ ያዘጋጀቻቸውን ችግኞች እንደ ጂቡቲ፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ኬንያ ላሉት ጎረቤት ሀገራት በማጋራት፣ የምሥራቅ አፍሪካን እና የአፍሪካ ቀንድን የቀጣና አየር ንብረት ለውጥ ተግዳሮት በጋራ የመከላከል መሪነት ሚናዋን በተግባር አሳይታለች።
ይህም አረንጓዴ ዐሻራን የድንበር ተሻጋሪ ዲፕሎማሲ፣ የቀጠናው ሰላም እና የጋራ ልማት መሣሪያ አድርጎታል።
በርካታ የአፍሪካ ሀገራትም የኢትዮጵያን ፈለግ በመከተል የአረንጓዴ ልማትን በሀገሮቻቸው እያስፋፉ ይገኛሉ።
ከዚህ ባሻገር፣ ኢትዮጵያ ባመጣቻቸው ተጨባጭ ስኬቶች “ዘላቂ የደን ልማት አያያዝ እና አጠቃቀም” በሚል ዘርፍ ከዓለም የምግብ እና እርሻ ድርጅት (FAO) ከፍተኛ እውቅናን አግኝታለች።
6. የከተሞች ሥነ-ምኅዳር መታደስ እና የኮሪደር ልማት ውበት
አረንጓዴ ዐሻራ በገጠር ተራራዎች ብቻ ተወስኖ ሳይቀር ወደ ከተሞች በመግባት የዘመናዊ ፓርኮች ግንባታ፣ የከተማ አረንጓዴ ልማት እና አሁን ላይ በስፋት እየተተገበረ ላለው የኮሪደር ልማት ዋነኛ አካል ሆኗል።
ይህም የከተሞችን የአየር ጥራት በከፍተኛ ደረጃ ከመጨመሩም በላይ፣ የሥነ-ሕይወት ስብጥርን ወደ ነበረበት በመመለስ እና ለዜጎች ምቹ የመዝናኛ እና የኑሮ አካባቢን በመፍጠር የከተሞቻችንን ገጽታ ሙሉ በሙሉ በመለወጥ ላይ ይገኛል።
7. ሕዝባዊ ንቅናቄ እና የዜግነት አገልግሎት ባህል ግንባታ
በአንድ ጀምበር በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ችግኝ የመተከል ልምዳቸው፣ የአካባቢ ጥበቃን ከዘመቻነት አውጥቶ የባህል እና የዜግነት ግዴታ አካል አድርጎታል።
ይህም የሕዝባዊ ወንድማማችነትን ያጠናከረ እና የአካባቢ ጥበቃ ግንዛቤን በማሳደግ ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር እጅግ ግዙፍ ማኅበራዊ እና ሥነ-ልቦናዊ ስኬት ነው።
በአጠቃላይ አረንጓዴ ዐሻራ ባለፉት ሰባት ዓመታት የተፈጥሮ ሀብታችንን ከመመለስ አልፎ ሀገራዊ አንድነትን ያጠናከረ፣ የማክሮ ኢኮኖሚ አቅማችንን የገነባ እና ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ ለአየር ንብረት ለውጥ መፍትሔ አቅራቢ ሀገር ያደረገ አንጸባራቂ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #greenlegacy #climateaction #greendiplomacy #greeneconomy
Sponsored by
Surafel
2 days ago
u12a0u1236u1233 u1260u12a0u1295u12f5 u1300u121du1260u122d u12a0u123bu122bu12cbu1295 u120du1273u1296u122d u1270u12d8u130bu1305u1273u1208u127d
#ebcdotstream #greenlegacy ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
አሶሳ በአንድ ጀምበር አሻራዋን ልታኖር ተዘጋጅታለች
#ebcdotstream #greenlegacy
3 days ago
Flying higher, growing greener. Planting the trees of tomorrow because sustainablity is part of our journey. #ethiopianairlines #greenlegacy
3 days ago
Flying higher, growing greener. Planting the trees of tomorrow because sustainablity is part of our journey. #ethiopianairlines #greenlegacy
3 days ago
800 ሚሊዮን ችግኞች በአንድ ጀምበር ኢትዮጵያ ለዓለም የምታሳየው ታሪካዊ የአረንጓዴ አሻራ
************************
ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን ዘመነ-ተሻጋሪ ተጽዕኖ ለመቋቋም፣ የተጎዱ መሬቶችን ለማደስ እና የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ህይወት ለማሻሻል ያለመ ሀገራዊ ራዕይ ሰንቃ በመንቀሳቀስ ላይ ትገኛለች።
የዚሁ ዘላቂ ጥረት አካል የሆነውና በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የተያዘው ግብ፣ ሀገራችን ለአረንጓዴ ልማትና ለአካባቢ ጥበቃ ያላትን ጽኑ ቁርጠኝነት ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዳግም በተግባር የሚያስመሰክር ታሪካዊ ምዕራፍ ነው።
ይህ ዘመቻ ተራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ብቻ ሳይሆን፣ ከጫፍ እስከ ጫፍ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በአንድ ልብና በአንድ ዓላማ በመነሳት የሚያደርጉት የተቀናጀ አቅምና አንድነት ማሳያ እንዲሁም የተፈጥሮ ሚዛንን ለመመለስ የተደረገ ትልቅ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው።
በዚህ ታሪካዊ ቀን ከሚተከሉት ችግኞች መካከል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ እና ዘይቱን ያሉ ለምግብነት የሚውሉ የፍራፍሬ ተክሎች ይገኙበታል።
እነዚህ የፍራፍሬ ዛፎች የምግብ አቅርቦትን ከማሳደግ ባሻገር ለገበሬዎች የገቢ ምንጭ በመሆን የገጠር ኢኮኖሚን ለማጠናከር በከፍተኛ ሁኔታ ያግዛሉ።
በተጨማሪም የደን ሽፋን መጨመር የአፈር መሸርሸርን ከመከላከል ባለፈ የከርሰ ምድር ውሃ እንዲጎለብት ያደርጋል፤ ታላላቅ የኃይል ማመንጫ ግድቦች እና የመስኖ መሠረተ ልማቶች በደለል እንዳይሞሉ በመከላከል የአገልግሎት ዘመናቸውን ያራዝማል።
የአካባቢ ሙቀትን በመቀነስና የዝናብ ዘይቤን በማስተካከልም ለግብርናው ዘርፍ የተሻለ እና አስተማማኝ ሁኔታ ይፈጥራል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የነገዋን አረንጓዴ፣ በምግብ ራሷን የቻለች እና የተፈጥሮ ሀብቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያን ለመገንባት የተጣለ ጠንካራ መሠረት ነው።
ዛሬ በትጋት መሬት የሚይዘው እያንዳንዱ ችግኝ የነገው የኢትዮጵያ ብሩህ ተስፋ፣ አረንጓዴ ተፈጥሮ እና ለቀጣዩ ትውልድ የሚተላለፍ ታሪካዊ አሻራ ደማቅ መገለጫ ነው።
በኢንቲሃድ አብራር
#greenlegacy #ethiopia #climateaction #treeplanting #sustainability
************************
ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን ዘመነ-ተሻጋሪ ተጽዕኖ ለመቋቋም፣ የተጎዱ መሬቶችን ለማደስ እና የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ህይወት ለማሻሻል ያለመ ሀገራዊ ራዕይ ሰንቃ በመንቀሳቀስ ላይ ትገኛለች።
የዚሁ ዘላቂ ጥረት አካል የሆነውና በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የተያዘው ግብ፣ ሀገራችን ለአረንጓዴ ልማትና ለአካባቢ ጥበቃ ያላትን ጽኑ ቁርጠኝነት ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዳግም በተግባር የሚያስመሰክር ታሪካዊ ምዕራፍ ነው።
ይህ ዘመቻ ተራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ብቻ ሳይሆን፣ ከጫፍ እስከ ጫፍ በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በአንድ ልብና በአንድ ዓላማ በመነሳት የሚያደርጉት የተቀናጀ አቅምና አንድነት ማሳያ እንዲሁም የተፈጥሮ ሚዛንን ለመመለስ የተደረገ ትልቅ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው።
በዚህ ታሪካዊ ቀን ከሚተከሉት ችግኞች መካከል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ እና ዘይቱን ያሉ ለምግብነት የሚውሉ የፍራፍሬ ተክሎች ይገኙበታል።
እነዚህ የፍራፍሬ ዛፎች የምግብ አቅርቦትን ከማሳደግ ባሻገር ለገበሬዎች የገቢ ምንጭ በመሆን የገጠር ኢኮኖሚን ለማጠናከር በከፍተኛ ሁኔታ ያግዛሉ።
በተጨማሪም የደን ሽፋን መጨመር የአፈር መሸርሸርን ከመከላከል ባለፈ የከርሰ ምድር ውሃ እንዲጎለብት ያደርጋል፤ ታላላቅ የኃይል ማመንጫ ግድቦች እና የመስኖ መሠረተ ልማቶች በደለል እንዳይሞሉ በመከላከል የአገልግሎት ዘመናቸውን ያራዝማል።
የአካባቢ ሙቀትን በመቀነስና የዝናብ ዘይቤን በማስተካከልም ለግብርናው ዘርፍ የተሻለ እና አስተማማኝ ሁኔታ ይፈጥራል።
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የነገዋን አረንጓዴ፣ በምግብ ራሷን የቻለች እና የተፈጥሮ ሀብቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያን ለመገንባት የተጣለ ጠንካራ መሠረት ነው።
ዛሬ በትጋት መሬት የሚይዘው እያንዳንዱ ችግኝ የነገው የኢትዮጵያ ብሩህ ተስፋ፣ አረንጓዴ ተፈጥሮ እና ለቀጣዩ ትውልድ የሚተላለፍ ታሪካዊ አሻራ ደማቅ መገለጫ ነው።
በኢንቲሃድ አብራር
#greenlegacy #ethiopia #climateaction #treeplanting #sustainability
4 days ago
በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ተክለን ታሪክ ለመሥራት - 3 ቀን ቀረን!
በጋራ ተስፋን እንትከል!
Ethiopian Broadcasting Corporation #ethiopia #ebc #greenlegacy #plantinghope @
በጋራ ተስፋን እንትከል!
Ethiopian Broadcasting Corporation #ethiopia #ebc #greenlegacy #plantinghope @
Sponsored by
Surafel
4 days ago
u1260u1228u1203u1295 u12c8u12f0 u1308u1290u1275 u12e8u1218u1240u12e8u122d u1325u1260u1265 #etv #greenlegacy #ebcdotstream #pmoethiopia #pmabiyahmed ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
በረሃን ወደ ገነት የመቀየር ጥበብ #etv #greenlegacy #ebcdotstream #pmoethiopia #pmabiyahmed
5 days ago
የኢትዮጵያ የክተት ጥሪ!
*************
የዘመን ማህደርን ገልጠን ወደ ኋላ ስንመለከት፣ ልክ ከ130 ዓመታት በፊት በ1888 ዓ.ም የኢትዮጵያ ተራሮች በታላቅ የክተት አዋጅ እና በነጋሪት ድምጽ ተንቀጥቅጠው ነበር። ወራሪው የፋሺስት ጦር ሉዓላዊ ድንበራችንን ጥሶ ክብራችንን ሊገፍና ነፃነታችንን ሊቀማ በዘመተ ጊዜ፣ የወቅቱ ንጉሥ አፄ ምኒልክ ያንን ታሪካዊ የክተት ጥሪ አሰሙ።
"ጉልበት ያለህ በጉልበትህ፣ ጉልበት የሌለህ በጸሎትህ እርዳኝ፤ ሀገር የሚያጠፋ ጠላት መጥቷልና ተነስ! ይህን ሳታደርግ ቀርተህ ሀገርህ ስትደፈር ዝም ብትል ግን ማርያምን እጣላሃለሁ!" የሚለው የንጉሡ ጥሪ ኢትዮጵያን ከዳር እስከ ዳር አነቃነቃት።
ያኔ ጥሪው የኅልውና ነበር፤ ሀገር የማዳን፣ ድንበር የተጋፋውን የፋሽስት ወራሪ ኃይል በጀግንነት የመመከት ጥሪ ነበር። በዚህ ብሔራዊ ጥሪ የተንቀሳቀሰው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ እንደ ማዕበል ተምሞ በዓድዋ ተራሮች ላይ በደሙ የነፃነት ታሪክ ጻፈ። ኢትዮጵያም በልጆቿ አንድነት ዳነች።
ዛሬ ደግሞ ዘመን ተቀይሯል። የትናንቱ ጠላት በጀግኖች አባቶቻችን ተሸንፎ ታሪክ ሆኗል። ነገር ግን ዛሬም በድጋሚ ኢትዮጵያ እየተጣራች ነው።
የዛሬዋ ኢትዮጵያ ጥሪ ግን፣ እንደ ትናንቱ የጦርነት የጠላት ወረራ ክተት አይደለም። የዛሬው ጥሪ ምድሪቱን የማከም፣ እናት ሀገርን አረንጓዴ ካባ የማልበስ እና ልምላሜዋን የመመለስ የብልጽግና ጥሪ ነው። ይህ ጥሪ አባቶቻችን በደም እና በአጥንታቸው ያስከበሯትን ውድ ሀገር፣ እኛ በአረንጓዴ ዐሻራችን አድሰን፣ በላባችን አልብሰን ልዕልናዋን በተግባር የምናረጋግጥበት ታሪካዊ አዋጅ ነው።
ኢትዮጵያን በአረንጓዴ ዐሻራ ወደ ከፍታ ማማ የማሸጋገር እና የጀመረችውን የተስፋ ጉዞ የማስቀጠል ተከታታይ እና ያልተቋረጠ የክተት ጥሪ ነው።
እነሆ የዘንድሮው የኢትዮጵያ የክተት ጥሪ ደግሞ ታሪክን በአዲስ መልክ ሊያድስ፣ ተደጋጋሚ ድሎችን ሊያስመዘግብ እና የዓለምን ክብረ ወሰን በድጋሚ ሊሰብር ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም የጋራ ሀገራዊ ቀጠሮ ይዟል።
በዚህ ታሪካዊ ዕለት፣ አዲሱ የመደመር ትውልድ 800 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር ለመትከል ሀገራዊ የክተት አዋጅ ታውጆለታል።
ከማለዳው የንጋት ጮራ ጀምሮ ጀንበር እስክትጠልቅ ድረስ፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እጆች፣ የነገዋን ሀገር በምናብ እያዩ በአንድ ልብ ይሰባሰባሉ። በእነዚህ ጥቂት የብርሃን ሰዓታት ውስጥ 800 ሚሊዮን የተስፋ ዘሮችን በኢትዮጵያ ማህፀን ውስጥ ያኖራሉ።
ይህ የሐምሌ 27ቱ ክተት ከዛፍ ተከላ የዘለለ እጅግ ጥልቅ የሆነ ሀገራዊ ትርጉም አለው። ይህ ድንቅ የአንድ ጀንበር ተአምር፣ የተረሱና የተራቆቱ ተራሮቻችን ዳግም ህይወት የሚዘሩበት፣ የነገው ትውልድ ንጹህ አየር የሚተነፍስበት እና የኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ በጽኑ መሰረት ላይ የሚገነባበት ህያው ታሪክ ነው።
ትናንት አባቶቻችን በነጋሪት ድምጽ ጥሪዋን ሰምተው ሀገር እንዳዳኑ ሁሉ፣ ዛሬም እኛ ልጆቿ ይህንን የአረንጓዴ ዐሻራ ጥሪ ሰምተን በጋራ ስንሰለፍ ኢትዮጵያ በልጆቿ እጅ ትንቆጠቆጣለች፣ ውበቷ ይደምቃል፣ ሉዓላዊነቷም በምጣኔ ሀብት ይረጋገጣል።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ፍቅር ተጣርታለች፤ ምድሪቱን ለማልበስ፣ 800 ሚሊዮን ዐሻራዎችን በአንድ ቀን ለማሳረፍ፣ ክተት ለሐምሌ 27!
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #greenlegacy #800milliontrees #ethiopiarising #environmentalprotection #ebcdotstream
*************
የዘመን ማህደርን ገልጠን ወደ ኋላ ስንመለከት፣ ልክ ከ130 ዓመታት በፊት በ1888 ዓ.ም የኢትዮጵያ ተራሮች በታላቅ የክተት አዋጅ እና በነጋሪት ድምጽ ተንቀጥቅጠው ነበር። ወራሪው የፋሺስት ጦር ሉዓላዊ ድንበራችንን ጥሶ ክብራችንን ሊገፍና ነፃነታችንን ሊቀማ በዘመተ ጊዜ፣ የወቅቱ ንጉሥ አፄ ምኒልክ ያንን ታሪካዊ የክተት ጥሪ አሰሙ።
"ጉልበት ያለህ በጉልበትህ፣ ጉልበት የሌለህ በጸሎትህ እርዳኝ፤ ሀገር የሚያጠፋ ጠላት መጥቷልና ተነስ! ይህን ሳታደርግ ቀርተህ ሀገርህ ስትደፈር ዝም ብትል ግን ማርያምን እጣላሃለሁ!" የሚለው የንጉሡ ጥሪ ኢትዮጵያን ከዳር እስከ ዳር አነቃነቃት።
ያኔ ጥሪው የኅልውና ነበር፤ ሀገር የማዳን፣ ድንበር የተጋፋውን የፋሽስት ወራሪ ኃይል በጀግንነት የመመከት ጥሪ ነበር። በዚህ ብሔራዊ ጥሪ የተንቀሳቀሰው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ እንደ ማዕበል ተምሞ በዓድዋ ተራሮች ላይ በደሙ የነፃነት ታሪክ ጻፈ። ኢትዮጵያም በልጆቿ አንድነት ዳነች።
ዛሬ ደግሞ ዘመን ተቀይሯል። የትናንቱ ጠላት በጀግኖች አባቶቻችን ተሸንፎ ታሪክ ሆኗል። ነገር ግን ዛሬም በድጋሚ ኢትዮጵያ እየተጣራች ነው።
የዛሬዋ ኢትዮጵያ ጥሪ ግን፣ እንደ ትናንቱ የጦርነት የጠላት ወረራ ክተት አይደለም። የዛሬው ጥሪ ምድሪቱን የማከም፣ እናት ሀገርን አረንጓዴ ካባ የማልበስ እና ልምላሜዋን የመመለስ የብልጽግና ጥሪ ነው። ይህ ጥሪ አባቶቻችን በደም እና በአጥንታቸው ያስከበሯትን ውድ ሀገር፣ እኛ በአረንጓዴ ዐሻራችን አድሰን፣ በላባችን አልብሰን ልዕልናዋን በተግባር የምናረጋግጥበት ታሪካዊ አዋጅ ነው።
ኢትዮጵያን በአረንጓዴ ዐሻራ ወደ ከፍታ ማማ የማሸጋገር እና የጀመረችውን የተስፋ ጉዞ የማስቀጠል ተከታታይ እና ያልተቋረጠ የክተት ጥሪ ነው።
እነሆ የዘንድሮው የኢትዮጵያ የክተት ጥሪ ደግሞ ታሪክን በአዲስ መልክ ሊያድስ፣ ተደጋጋሚ ድሎችን ሊያስመዘግብ እና የዓለምን ክብረ ወሰን በድጋሚ ሊሰብር ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም የጋራ ሀገራዊ ቀጠሮ ይዟል።
በዚህ ታሪካዊ ዕለት፣ አዲሱ የመደመር ትውልድ 800 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር ለመትከል ሀገራዊ የክተት አዋጅ ታውጆለታል።
ከማለዳው የንጋት ጮራ ጀምሮ ጀንበር እስክትጠልቅ ድረስ፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እጆች፣ የነገዋን ሀገር በምናብ እያዩ በአንድ ልብ ይሰባሰባሉ። በእነዚህ ጥቂት የብርሃን ሰዓታት ውስጥ 800 ሚሊዮን የተስፋ ዘሮችን በኢትዮጵያ ማህፀን ውስጥ ያኖራሉ።
ይህ የሐምሌ 27ቱ ክተት ከዛፍ ተከላ የዘለለ እጅግ ጥልቅ የሆነ ሀገራዊ ትርጉም አለው። ይህ ድንቅ የአንድ ጀንበር ተአምር፣ የተረሱና የተራቆቱ ተራሮቻችን ዳግም ህይወት የሚዘሩበት፣ የነገው ትውልድ ንጹህ አየር የሚተነፍስበት እና የኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ በጽኑ መሰረት ላይ የሚገነባበት ህያው ታሪክ ነው።
ትናንት አባቶቻችን በነጋሪት ድምጽ ጥሪዋን ሰምተው ሀገር እንዳዳኑ ሁሉ፣ ዛሬም እኛ ልጆቿ ይህንን የአረንጓዴ ዐሻራ ጥሪ ሰምተን በጋራ ስንሰለፍ ኢትዮጵያ በልጆቿ እጅ ትንቆጠቆጣለች፣ ውበቷ ይደምቃል፣ ሉዓላዊነቷም በምጣኔ ሀብት ይረጋገጣል።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ፍቅር ተጣርታለች፤ ምድሪቱን ለማልበስ፣ 800 ሚሊዮን ዐሻራዎችን በአንድ ቀን ለማሳረፍ፣ ክተት ለሐምሌ 27!
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #greenlegacy #800milliontrees #ethiopiarising #environmentalprotection #ebcdotstream
5 days ago
የኢትዮጵያ ክተት ጥሪ ለአረንጓዴ ዐሻራ!
*************
የዘመን ማህደርን ገልጠን ወደ ኋላ ስንመለከት፣ ልክ ከ130 ዓመታት በፊት በ1888 ዓ.ም የኢትዮጵያ ተራሮች በታላቅ የክተት አዋጅ እና በነጋሪት ድምጽ ተንቀጥቅጠው ነበር። ወራሪው የፋሺስት ጦር ሉዓላዊ ድንበራችንን ጥሶ ክብራችንን ሊገፍና ነፃነታችንን ሊቀማ በዘመተ ጊዜ፣ የወቅቱ ንጉሥ አፄ ምኒልክ ያንን ታሪካዊ የክተት ጥሪ አሰሙ።
"ጉልበት ያለህ በጉልበትህ፣ ጉልበት የሌለህ በጸሎትህ እርዳኝ፤ ሀገር የሚያጠፋ ጠላት መጥቷልና ተነስ! ይህን ሳታደርግ ቀርተህ ሀገርህ ስትደፈር ዝም ብትል ግን ማርያምን እጣላሃለሁ!" የሚለው የንጉሡ ጥሪ ኢትዮጵያን ከዳር እስከ ዳር አነቃነቃት።
ያኔ ጥሪው የኅልውና ነበር፤ ሀገር የማዳን፣ ድንበር የተጋፋውን የፋሽስት ወራሪ ኃይል በጀግንነት የመመከት ጥሪ ነበር። በዚህ ብሔራዊ ጥሪ የተንቀሳቀሰው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ እንደ ማዕበል ተምሞ በዓድዋ ተራሮች ላይ በደሙ የነፃነት ታሪክ ጻፈ። ኢትዮጵያም በልጆቿ አንድነት ዳነች።
ዛሬ ደግሞ ዘመን ተቀይሯል። የትናንቱ ጠላት በጀግኖች አባቶቻችን ተሸንፎ ታሪክ ሆኗል። ነገር ግን ዛሬም በድጋሚ ኢትዮጵያ እየተጣራች ነው።
የዛሬዋ ኢትዮጵያ ጥሪ ግን፣ እንደ ትናንቱ የጦርነት የጠላት ወረራ ክተት አይደለም። የዛሬው ጥሪ ምድሪቱን የማከም፣ እናት ሀገርን አረንጓዴ ካባ የማልበስ እና ልምላሜዋን የመመለስ የብልጽግና ጥሪ ነው። ይህ ጥሪ አባቶቻችን በደም እና በአጥንታቸው ያስከበሯትን ውድ ሀገር፣ እኛ በአረንጓዴ ዐሻራችን አድሰን፣ በላባችን አልብሰን ልዕልናዋን በተግባር የምናረጋግጥበት ታሪካዊ አዋጅ ነው።
ኢትዮጵያን በአረንጓዴ ዐሻራ ወደ ከፍታ ማማ የማሸጋገር እና የጀመረችውን የተስፋ ጉዞ የማስቀጠል ተከታታይ እና ያልተቋረጠ የክተት ጥሪ ነው።
እነሆ የዘንድሮው የኢትዮጵያ የክተት ጥሪ ደግሞ ታሪክን በአዲስ መልክ ሊያድስ፣ ተደጋጋሚ ድሎችን ሊያስመዘግብ እና የዓለምን ክብረ ወሰን በድጋሚ ሊሰብር ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም የጋራ ሀገራዊ ቀጠሮ ይዟል።
በዚህ ታሪካዊ ዕለት፣ አዲሱ የመደመር ትውልድ 800 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር ለመትከል ሀገራዊ የክተት አዋጅ ታውጆለታል።
ከማለዳው የንጋት ጮራ ጀምሮ ጀንበር እስክትጠልቅ ድረስ፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እጆች፣ የነገዋን ሀገር በምናብ እያዩ በአንድ ልብ ይሰባሰባሉ። በእነዚህ ጥቂት የብርሃን ሰዓታት ውስጥ 800 ሚሊዮን የተስፋ ዘሮችን በኢትዮጵያ ማህፀን ውስጥ ያኖራሉ።
ይህ የሐምሌ 27ቱ ክተት ከዛፍ ተከላ የዘለለ እጅግ ጥልቅ የሆነ ሀገራዊ ትርጉም አለው። ይህ ድንቅ የአንድ ጀንበር ተአምር፣ የተረሱና የተራቆቱ ተራሮቻችን ዳግም ህይወት የሚዘሩበት፣ የነገው ትውልድ ንጹህ አየር የሚተነፍስበት እና የኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ በጽኑ መሰረት ላይ የሚገነባበት ህያው ታሪክ ነው።
ትናንት አባቶቻችን በነጋሪት ድምጽ ጥሪዋን ሰምተው ሀገር እንዳዳኑ ሁሉ፣ ዛሬም እኛ ልጆቿ ይህንን የአረንጓዴ ዐሻራ ጥሪ ሰምተን በጋራ ስንሰለፍ ኢትዮጵያ በልጆቿ እጅ ትንቆጠቆጣለች፣ ውበቷ ይደምቃል፣ ሉዓላዊነቷም በምጣኔ ሀብት ይረጋገጣል።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ፍቅር ተጣርታለች፤ ምድሪቱን ለማልበስ፣ 800 ሚሊዮን ዐሻራዎችን በአንድ ቀን ለማሳረፍ፣ ክተት ለሐምሌ 27!
#ethiopia #ebc #greenlegacy #800milliontrees #ethiopiarising #environmentalprotection #ebcdotstream
*************
የዘመን ማህደርን ገልጠን ወደ ኋላ ስንመለከት፣ ልክ ከ130 ዓመታት በፊት በ1888 ዓ.ም የኢትዮጵያ ተራሮች በታላቅ የክተት አዋጅ እና በነጋሪት ድምጽ ተንቀጥቅጠው ነበር። ወራሪው የፋሺስት ጦር ሉዓላዊ ድንበራችንን ጥሶ ክብራችንን ሊገፍና ነፃነታችንን ሊቀማ በዘመተ ጊዜ፣ የወቅቱ ንጉሥ አፄ ምኒልክ ያንን ታሪካዊ የክተት ጥሪ አሰሙ።
"ጉልበት ያለህ በጉልበትህ፣ ጉልበት የሌለህ በጸሎትህ እርዳኝ፤ ሀገር የሚያጠፋ ጠላት መጥቷልና ተነስ! ይህን ሳታደርግ ቀርተህ ሀገርህ ስትደፈር ዝም ብትል ግን ማርያምን እጣላሃለሁ!" የሚለው የንጉሡ ጥሪ ኢትዮጵያን ከዳር እስከ ዳር አነቃነቃት።
ያኔ ጥሪው የኅልውና ነበር፤ ሀገር የማዳን፣ ድንበር የተጋፋውን የፋሽስት ወራሪ ኃይል በጀግንነት የመመከት ጥሪ ነበር። በዚህ ብሔራዊ ጥሪ የተንቀሳቀሰው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ እንደ ማዕበል ተምሞ በዓድዋ ተራሮች ላይ በደሙ የነፃነት ታሪክ ጻፈ። ኢትዮጵያም በልጆቿ አንድነት ዳነች።
ዛሬ ደግሞ ዘመን ተቀይሯል። የትናንቱ ጠላት በጀግኖች አባቶቻችን ተሸንፎ ታሪክ ሆኗል። ነገር ግን ዛሬም በድጋሚ ኢትዮጵያ እየተጣራች ነው።
የዛሬዋ ኢትዮጵያ ጥሪ ግን፣ እንደ ትናንቱ የጦርነት የጠላት ወረራ ክተት አይደለም። የዛሬው ጥሪ ምድሪቱን የማከም፣ እናት ሀገርን አረንጓዴ ካባ የማልበስ እና ልምላሜዋን የመመለስ የብልጽግና ጥሪ ነው። ይህ ጥሪ አባቶቻችን በደም እና በአጥንታቸው ያስከበሯትን ውድ ሀገር፣ እኛ በአረንጓዴ ዐሻራችን አድሰን፣ በላባችን አልብሰን ልዕልናዋን በተግባር የምናረጋግጥበት ታሪካዊ አዋጅ ነው።
ኢትዮጵያን በአረንጓዴ ዐሻራ ወደ ከፍታ ማማ የማሸጋገር እና የጀመረችውን የተስፋ ጉዞ የማስቀጠል ተከታታይ እና ያልተቋረጠ የክተት ጥሪ ነው።
እነሆ የዘንድሮው የኢትዮጵያ የክተት ጥሪ ደግሞ ታሪክን በአዲስ መልክ ሊያድስ፣ ተደጋጋሚ ድሎችን ሊያስመዘግብ እና የዓለምን ክብረ ወሰን በድጋሚ ሊሰብር ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም የጋራ ሀገራዊ ቀጠሮ ይዟል።
በዚህ ታሪካዊ ዕለት፣ አዲሱ የመደመር ትውልድ 800 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር ለመትከል ሀገራዊ የክተት አዋጅ ታውጆለታል።
ከማለዳው የንጋት ጮራ ጀምሮ ጀንበር እስክትጠልቅ ድረስ፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እጆች፣ የነገዋን ሀገር በምናብ እያዩ በአንድ ልብ ይሰባሰባሉ። በእነዚህ ጥቂት የብርሃን ሰዓታት ውስጥ 800 ሚሊዮን የተስፋ ዘሮችን በኢትዮጵያ ማህፀን ውስጥ ያኖራሉ።
ይህ የሐምሌ 27ቱ ክተት ከዛፍ ተከላ የዘለለ እጅግ ጥልቅ የሆነ ሀገራዊ ትርጉም አለው። ይህ ድንቅ የአንድ ጀንበር ተአምር፣ የተረሱና የተራቆቱ ተራሮቻችን ዳግም ህይወት የሚዘሩበት፣ የነገው ትውልድ ንጹህ አየር የሚተነፍስበት እና የኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ በጽኑ መሰረት ላይ የሚገነባበት ህያው ታሪክ ነው።
ትናንት አባቶቻችን በነጋሪት ድምጽ ጥሪዋን ሰምተው ሀገር እንዳዳኑ ሁሉ፣ ዛሬም እኛ ልጆቿ ይህንን የአረንጓዴ ዐሻራ ጥሪ ሰምተን በጋራ ስንሰለፍ ኢትዮጵያ በልጆቿ እጅ ትንቆጠቆጣለች፣ ውበቷ ይደምቃል፣ ሉዓላዊነቷም በምጣኔ ሀብት ይረጋገጣል።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ፍቅር ተጣርታለች፤ ምድሪቱን ለማልበስ፣ 800 ሚሊዮን ዐሻራዎችን በአንድ ቀን ለማሳረፍ፣ ክተት ለሐምሌ 27!
#ethiopia #ebc #greenlegacy #800milliontrees #ethiopiarising #environmentalprotection #ebcdotstream
Comments