Logo
FastMereja
11 hours ago
በመንገዳችን ላይ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ

FastMereja
14 hours ago
ምነው የተከበረው የሰው ልጅ ህይዋት እንዲህ እረከሰ ?!!!
ደመ*ና—ደም መና!!

በምስራቅ አርሲ በውድ ወገኖቻችን ላይ የተፈፀመውን አሰቃቂ ጥቃት በመስማቴ የተሰማኝን ጥልቅና መሪር ሐዘን ለመግለፅ እወዳለሁ።

የብዝኃ ኃይማኖትና ብሔር ብሔረሰቦች እናት የሆነችውን ሀገራችንን ሰላም ለማናጋት፤ ለዘመናት የተገነባውን የሕዝቦች የእርስ በርስ የጠበቀ ትስስር ለመበጠስ፤ ብሎም የዜጎችን ነፍስ ለርካሽ ዓለማዊ ግባቸው ማሳኪያ ለመጠቀም ያሰፈሰፉ እኩያን በተደጋጋሚ እየፈፀሙት ያለውን ሀገር አጥፊ ድርጊት አጥብቄ እኮንናለሁ። አወግዛለሁም።

የሰውን ልጅ ክቡር ህይዎት የሚያጠፉና የሃገራችን ኢትዮጵያን ዕድገት የሚገታ እኩይ ተግባር ላይ ተሰማርተው በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች እየፈፀሙት ያለውን መጠነ ሰፊ ጥፋት የሚመለከተው አካል አፋጣኝ እርምጃ በመውሰድ የዜጎችን በሰላም ወጥቶ የመግባት ሰብዓዊ መብት ማረጋገጥ ይገባዋል።

በሰላም ወጥተው ስለመግባታቸው መተማመኛ የሌላቸውን ዜጎች ያቀፈች ሀገር ወደፊት የመራመድ ዕድሏ የቀጨጨ፣ የማደግ ተስፋዋ የመነመነ ነውና ስለ ሀገሬ ያገባኛል፣ ይመለከተኛል የሚል ሁሉ ‹ሀይ› ሊል ይገባል።

ከምንም በላይ ደሞ መሰል አስነዋሪ ድርጊቶችን እንደመልካም አጋጣሚ በመጠቀም በሕዝቦች መካከል አለመተማመንን የሚዘሩ ኃላፊነት የጎደላቸው ግለሰቦች የጉዳዩን አደገኛነት ከግምት በማስገባት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡና ቆም ብለው እንዲያስቡ አበክሬ ለመግለፅ እወዳለሁ።

አላህ የተበዳዮችን እምባ እንዲያብስ፤ ለበዳዮችም የእጃቸውን እንዲሰጣቸውና ፍትሕን እንዲያሰፍንልን የበረታ ዱዓዬ ነው።

ሰላም ለሀገራችን!

(ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ል)

ኡስታዝ ያሲን ኑሩ

FastMereja
14 hours ago
የንፁሀን እልቂት በቃ ሊባል ይገባል!!

በኦሮሚያ ክልል በአርሲ ዞን በአሰኮ ወረዳ፣ በሺርካ ወረዳ እና ሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ ታጣቂዎች ንፁሀን የኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታዮችን በመግደል በርካቶችን ከቤት ንብረታቸው ማፈናቀላቸውን በመስማቴ እጅግ አዝኛለው:: ይህን ሰይጣናዊ የጥፋት ተግባርም በፅኑ አወግዛለሁ

በአርሲ በተደጋጋሚ ንፁሀኖችን ኢላማ ያደረገ ጥቃት እየተበራከተ በየጊዜው ለቅሶ እና ዋይታ ብቻ እየተሰማ ያለ መፍትሄ መቀጠሉ እጅግ ያሳምማል::

ንፁሃን ዜጎች እያለቁ ያለው ከውጪ በመጣ ወራሪ ጠላት ሳይሆን ወንድም ወንድሙ ላይ እየሰነዘረው ባለው አሳዛኝ ከጭካኔ ጥቃት ነው::

በሀገሩ ምድር በድህነት ህይወቱን እየመራ ለሚገኝ ንፁህ ህዝብ ከግራ እና በቀኝ ጠብመንጃ በታጠቁ ሃይሎች በማያውቁት አጀንዳ ለሞት፣ ለእልቂት፣ ለስደት መዳረጉ ልብ ሰባሪ ነው::

ይህ የንፁሀን እልቂት በቃ ሊባል ይገባል!!

ሁሉም ኢትዮጵያዊ የዚህ መሰሉን እልቂት ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ለማስቆም እጅ ለእጅ ተያይዞ ሊቆም ይገባል::

በአርሲ በተደጋጋሚ እየተፈፀመ በሚገኘው ጥቃት ህይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን ቤተሰቦች መፅናናትን እመኛለው::

ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖቻችንም ቶሎ ያገግሙ ዘንድ አላህ እንዲረዳቸው እንዲሁም የተፈናቀሉትም ወደቄያቸው ደህንነታቸው ተጠብቆ ባስቸኳይ ይመለሱ ዘንድ ልባዊ ምኞቴ ነው

አላህ ሀገራችንን እና ወገኖቻችንን ይጠብቅልን::

ሰላም መግባባቱን እና መተዛዘኑን በመላው ሀገራችን ሀያሉ ጌታችን አላህ(ሱ.ወ) ያስፍንልን

ኡስታዝ አቡበከር አህመድ

FastMereja
14 hours ago
የንፁሃን ደም መፍሰስ ይብቃ፣ ለዘላቂ ሰላም በጋራ እንምከር!

በሀገራች የዜጎች ሞት ስፍራ አየቀያየረ ቀጥሏል።​ ዛሬ ደግሞ በተደጋጋሚ ሞት እየተሰማበት ባለው በምስራቅ አርሲ ዞን በንፁሃን በኦርቶዶክስ ከርስትያን ወገኖቻችን ላይ ዘግናኝ ጭፍጨፋ መደረጉን፣ ቤተ ክርስቲያንና የአማኞች መኖሪያ ቤቶች መቃጠላቸውን ከሚዲያዎች ዘገባ መረዳት ችያለሁ። መሰል ጥቃቶች ራስን በተጠቂዎች ቦታ አድርገን ካየን በእጅጉ ልብን በኃዘን ይሰብራል።

የንፁሃን ደም ያለአግባብ መፍሰስ እና የዜጎች መገደል በአስቸኳይ ሊቆም ይገባል። ግና እንዴትና መቼ? እንዴትስ ላለፉት ዓመታት በንጹሃን ዜጎችና በቤተ እምነቶች (መስጊድና ቤተክርስቲያን) ላይ የደረሱት ጥቃቶች የአንዱ ፈጻሚዎች እንኳ በህግ ቁጥጥር ስር ማዋልና ተጠያቂ ማድረግ ሳይቻል ቀረ? ከድርጊቱ በላይ መደጋገሙ፣ ከመደጋገሙ በላይ ፈጻሚዎቹ ሁሌም ያልታወቁ እየተባሉ መፍትሄ ማምጣት አለመቻል አደገኛ ነው።

ዘላቂ መፍትሄ ይገኝ ዘንድ ቆም ብሎ ማሰብበ ስሜት ተጽዕኖ ስር ከመውደቅ በራቀ መልኩ ነገሮችን መመርመር፣ መምከርና በጋራ መፍትሄ መፈለግ ግድ ይላል።

ክቡር የሆነው የሰው ልጅ ነፍስ እንዲህ መርከሱ እጅግ አደገኛ ነገር ነው። አላህ በቁርኣን እንዲህ ይለናል።

"በዚህ ምክንያት በእስራኤል ልጆች ላይ እነሆ ያለ ነፍስ (መግደል) ወይም በምድር ላይ ያለማጥፋት (ካልሆነ በስተቀር) ነፍስን የገደለ ሰው ሰዎቹን ሁሉ እንደገደለ ነው፤ ሕያው ያደረጋትም ሰው ሰዎቹን ሁሉ ሕያው እንዳደረገ ነው ማለትን ጻፍን፡፡ መልክተኞቻችንም በግልጽ ተዓምራት በእርግጥ መጡዋቸው፡፡ ከዚያም ከዚህ በኋላ ከእነሱ ብዙዎቹ በምድር ላይ ወሰንን አላፊዎች ናቸው፡፡"
— አል-ማኢዳህ (5:32)

ይህ ቁርኣናዊ መለኮታዊ መመሪያ የሰው ልጅ ሕይወት ነፍስ በማለት በመጥራት ያለ ምንም የዘር፣ የሃይማኖትና የብሔር ልዩነት ፍጹም የተከበረና የማይደፈር መሆኑን ያረጋግጣል።

በአንቀጹ መሠረት አንዲትን ንጹሕ ነፍስ ያለ አግባብ መቅጠፍ መላውን የሰውን ዘር እንደ ማጥፋት የሚቆጠር እጅግ ከባድ ወንጀል ሲሆን፣ በተቃራኒው ደግሞ አንዲትን ነፍስ ከአደጋ መታደግና ማዳን መላውን የሰው ልጅ ሕይወት እንደ ማኖር የሚቆጠር ታላቅ ሰብአዊ በጎነት ነው።

እንደ ዜጋ ማድረግ የምንችለው ለሟች ቤተሰቦችና ወገኖቻች መጽናናትን መመኘት ብቻ በመሆኑ እያዘንኩ ለሟች ቤተሰቦች መጽናናትን እመኛለሁ።

ህዝባችንና ሀገራችንን ከጥፋትና ከእልቂት ጠብቅልን።አላህ ሆይ! እውነቱ እንዲወጣ፣ የንጹዃን ደምም አፍሳሾች መቀጣጫ ይሆኑ ዘንድ የእጃቸውን እንዲያገኙ አድርግልን። አላህ በቃችሁ በለን!

ኡስታዝ አህመዲን ጀብል

FastMereja
19 hours ago
የጌዴኦ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በአቶ ጸጋዬ ታደሰ ላይ የሞት ቅጣት ወሰነ

​#fastmereja | የጌዴኦ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ በሰው ሕይወት ማጥፋት ወንጀል ተከሰው ሲጠየቁ የቆዩት አቶ ጸጋዬ ታደሰ ላይ የሞት ቅጣት ውሳኔ አሳለፈ።

​የጌዴኦ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የወንጀል ችሎት፣ ለዛሬ ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም ቀጠሮ ይዞ የነበረውን የምርመራና የውሳኔ ሂደት በማጠናቀቅ ተከሳሹን በሞት እንዲቀጡ ወስኗል።

​ፍርድ ቤቱ ቀደም ሲል ለግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም የነበረውን የቅጣት ውሳኔ ለመስማት ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረ ቢሆንም፣ በወቅቱ የቀረቡ የቅጣት ማቅለያ እና ማክበጃ ነጥቦችን ለመመርመር ለዛሬ ቀጠሮ አስተላልፎ ነበር።

​በዛሬው የችሎት ውሎ፤ ​ተከሳሹ ካቀረቧቸው የቅጣት ማቅለያዎች መካከል ሁለቱን ፍርድ ቤቱ ተቀብሏል።​በተመሳሳይ፣ አቃቤ ህግ ካቀረባቸው ልዩ የቅጣት ማክበጃዎች መካከል ሁለቱን ፍርድ ቤቱ ተቀብሎ ተመልክቷል። ​ፍርድ ቤቱ የቀረቡትን የቅጣት ማቅለያና ማክበጃ ነጥቦች በአንክሮ በመገምገም፣ በሂደቱ የነበረውን የሞት ቅጣት መነሻ ውሳኔ በማጽናት የመጨረሻ ብይን ሰጥቷል።

​የዲላ ማረሚያ ተቋም የተላለፈውን የሞት ቅጣት ውሳኔ ተከታትሎ እንዲያስፈጽም ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ማስተላለፉን የጌዴኦ ዞን ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት መረጃ ያመለክታል።

FastMereja
17 hours ago
የአቡነ ሀብተ ማርያም ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏

በነገሥታት ፊት የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ።

በምጽዋትና በስገድት የምትጋደለው እናቱ ዮስቴና ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ወደ በረኃ ሄደች። በዚያ ያገኘችው ባሕታዊም በመንፈስ ቅዱስ ተገልጦለት ከእርሷ ቅዱስ ፍሬ እንደሚወጣ ነግሮ ወደ ዓለም እንድትመለስ አዘዛት። እርሷም “እግዚአብሔር የወደደው ይሁን” ብላ እያመሰገነች ተመልሰች፡፡ የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ከዚህች የተባረከች ሴት ጋር ተጋባ። እርሷም በበጎ ምግባርና ሥራ የተጌጠች፣ በሕግ ተወስና በጾም፣ በጸሎት፣ የምትተጋ ነበረች። ከጥቂት ጊዜያት በኋላም ወንድ ልጅ ወለደች። እንደ ሥርዓቱም ሲጠመቅ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕገ እግዚአብሔር አንጸው አሳደጉት። ወደ ቤተ ክርስቲያንም ሲወስዱት “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የሚለውን ጸሎት ቢሰማ እጅጉን ወደዳት። እርሷንም ይዞ ከቤቱ ሌሊቱን የሚጸልይና የሚጋደል ሆነ።

አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ የበግ ጠባቂዎቹን “ዛሬ ዝናም ይዘንማልና እንግባ” አላቸው። እነርሱም “ምን ደመና አለ፤ ቀኑ ብራ ነው” አሉት። እርሱ ግን በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ ኃይለኛ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ዝናም ዘነመ። በሌላም ጊዜ እንዲሁ አንድ እረኛ የሀብተ ማርያምን በትሩን በጉልበት ነጠቀው። “መልስልኝ” ብሎ በስመ እግዚአብሔር ቢያምለውም እምቢ አለው። በተወው ጊዜ እግዚአብሔር ያን እረኛ በአየር ላይ ሠቅሎ አዋለው። እረኞቹም ሀብተ ማርያምን ሲለምኑት፣ እግዚአብሔር ነውና ስለ ስሙ ብሎ የቀጣው መሐሪው እርሱ ከወደደ ይማረው ሲል ያ እረኛ ተፈታና ወረደ። መጥቶም ከአባታችን እግር ስር ወደቀ፡፡ በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር። በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ 500 ጊዜ ይሰግዳል።

እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ አምላካችን ተገለጠለት። አባ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፡፡ ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ በማንበቡ፣ ረኃብና ጥምን በመታገሡ፣ በልቡ ቂምንና በቀልን ባለማኖሩ፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። የቅዱስ ማቴዎስንና የቅዱስ ማርቆስን ወንጌል ሲያነብ ከሌሎች ሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትን የብርሃን ሠረገላ ሰጠው፡፡

የቅዱስ ሉቃስንና የቅዱስ ዮሐንስን ወንጌል ሲያነብም ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የእሳት ሠረገላ ሰጠውና ቃል ኪዳን ገባለት። መታሰቢያውን ለሚያደርጉና በስሙ ለሚዘክሩ፣ ከእነርሱ ጋር የሚኖርበትን አምስት መቶ የወርቅ አምዶች ያሏትን ቦታ ሰጠሁህ አለው። ቅዱሳን መላእክት ሁሉ እየተደሰቱ አባታችን አቡነ ሐብተ ማርያምን “ወንድማችን ወደማያልቀው ሰማያዊ ደስታ ልንወስድህ መጥተናል” አሉት። ይህንንም በተናገረ ጊዜ ጌታችን በሦስትነቱ ተገልጦ ታየው። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው በሰላም ተለየች። ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ እያመሰገኑ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ በዓታቸውን እናጽና ገዳማቸውን እንደግፍ የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

FastMereja
18 hours ago
ቻናል 1 ቴሌቪዥን ይቅርታ ጠየቀ።

​#fastmereja I ቻናል 1 ቴሌቪዥን ባስተላለፈው መዝናኛ ፕሮግራም ሳቢያ ህዝብን ይቅርታ ጠየቀ።

​ቻናል 1 ቴሌቪዥን እሁድ ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም “እሁድን አንድ ላይ” በተሰኘው መዝናኛ ፕሮግራሙ ውስጥ፣ “ተረኛው ሐኪም” በሚል ንዑስ ክፍል “የመራቢያ አካላትን ማስዋብ ተጀመረ” በሚል ርዕስ ያሰራጨው ይዘት ከህግ እና ከህብረተሰቡ እሴት ጋር የሚቃረን መሆኑን በማመን ይፋዊ የይቅርታ መግለጫ አውጥቷል።

​ጣቢያው ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ የቀረበው ይዘት በመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቁጥር 1238/2013 አንቀጾች ከተደነገጉት ግዴታዎች፣ በተለይም “ጨዋ የቋንቋ አጠቃቀም”፣ “የአካለ መጠን ያልደረሱ ህጻናትን ደህንነት መጠበቅ” እንዲሁም “የማህበረሰቡን ሞራልና ባህላዊ እሴቶች ማክበር” ከሚሉት መርሆዎች ጋር በእጅጉ የተጋጨ መሆኑን አምኗል።

​የቻናል 1 ቴሌቪዥን አመራሮች፣ ፕሮግራሙ ህጻናት በሚመለከቱበት ሰዓት ያለ ቅድመ ማስጠንቀቂያ መቅረቡ እና የርዕሰ ጉዳዩን ይዘት ከማህበረሰባችን ነባራዊ ሁኔታ አንጻር ሳይመዘን መሰራጨቱ የሙያ ስነምግባር ጥሰት እንደሆነ በመግለጽ፣ ይህንን ስህተት በመፈጸማቸው የተሰማቸውን ጥልቅ ማዘን ገልጸዋል።

​ጣቢያው ለወደፊቱ በህግና በስነምግባር መመሪያዎች መሰረት አገልግሎት ለመስጠት ቃል በመግባት፣ በፕሮግራሙ ሳቢያ ቅር ለተሰኙ አድማጭ ተመልካቾቹ በሙሉ ይቅርታ ጠይቋል።

FastMereja
20 hours ago
ዛሬ የአርሰናል እግር ኳስ ክለብን እና በኢትዮጵያ የሚገኙ እልል ያሉ ላደጋፊዎቹ ያለንን አድናቆት እና አክብሮት የምንገልጸበትን ይህን ድንቅ ዝግጅት በመደገፋችን እጅግ ኩራት ይሰማናል። አርሰናል በአለም ላይ ካሉ እውቅ የእግር ኳስ ክለቦች አንዱ ሲሆን፣ በአገራችንም ለክለቡ ጥልቅ ፍቅር ያላቸው ታማኝ ደጋፊዎች አሉት።

ከኢትዮጵያ ብራንዶች በግንባር ቀደም ከሚጠሩት መሃል እንደመሆናችን፣ ሐበሻ በእግር ኳስ፣ በመዝናኛ እና የስፖርት አድናቂዎችን በአንድነት የሚያሰባስበው የዚህ ዝግጅት አካል በመሆኗናችን ክብር ይሰማናል።

በሐበሻ የላቀ ጥራትን፣ ከኢትዮጵያ ባህል፣ ቅርስ እና እሴቶች ጋር ያለንን ጠንካራ ትስስር ይበልጥ እያጠበቅን፣ ከፍተኛ ጥራት ያላቸውን ምርቶች እና የማይረሱ ልምዶችን ለደንበኞቻችን እንዲሁም ለስፖርት ቤተሰቡ በሙሉ በማቅረባችን እንኮራለን።

የጋራ ፍላጎቶችን እና መገለጫዎችን በማክበር እና ማሕበረሰቡን የሚያቀራርቡ ሁኔታዎችን በመፍጠር ረገድ ታላላቅ ብራንዶች ከምርት ያለፈ ፋይዳ እንዳላቸው እናምናለን። እንደዚህ ባሉ አጋርነቶች አማካኝነትም ተጠቃሚዎቻችንን የሚያነሳሱ፣ የሚያሳትፉ እና የሚያዝናኑ መድረኮችን መደገፋችንን እንቀጥላለን።

ለዝግጅቱ አዘጋጆች፣ ለአርሰናል ደጋፊዎች እና ዛሬ ከእኛ ጋር ለተገኙት በሙሉ እናመሰግናለን።
ሐበሻ – በኢትዮጵያዊነታችን የምንኮራ፣ ለጥራት የቆምን፣ በፈጠራ የምንመራ፣ እና ልዩ ድባብ በመፍጠር ሰዎችን በአንድነት ለማዝናናት በቁርጠኛነት የተነሳን።

FastMereja
23 hours ago
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያናችን እና በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ።

ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ የኀዘን መልእክት እንደሚከተለው ነው፦

መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

‹‹ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦ የአገልጋዮችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት።››
(መዝሙረ ዳዊት ፸፰፥፪)

በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው።
የእምነት ነፃነት ተደፍሮ መቶ ዓመታት ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተቃጠለበት፣ እንዲሁም የካራ ኩፍቴና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በተዘረፈበት በዚህ ክፉ ቀን፤ በርካታ ምእመናን በግፍ መሰዋታቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬአቸው መፈናቀላቸው ቤተ ክርስቲያናችንን በእጅጉ ያሳዘነ ክስተት ነው።

የሰላም፣ የፍቅርና የታሪክ ማህደር የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በምድራዊ መከራ ውስጥ ያሉትን ምእመናን በምታጽናናበት በዚህ ወቅት ራሷ በፈተና ውስጥ ሆና ከመቸገሯም በላይ በአርሲ ምድር በተደጋጋሚ የሚስተዋለው በደልና ግፍ በሁላችንም ልቡና ውስጥ "እስከ መቼ?" የሚል የቁጭት እና የኀዘን ጥያቄን ፈጥሯል።

በመሆኑም ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን።

በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

በመጨረሻም ቤተ ክርስቲያናችን ለሰላም፣ ለይቅርታና ለሰው ልጆች ክብር ሁል ጊዜ የምትቆም መሆኑን በመግለጽ ይህንን የኀዘን ሰዓት አምላካችን በምሕረቱ ያሳልፍልን፣ የሞቱትን ነፍሶቻቸውን በመንግሥቱ ይቀበልልን፣ የተጎዱትንም በቸርነቱ ያጽናናልን በማለት አባታዊ የኀዘን መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።

እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
አሜን።

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

© የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት

FastMereja
1 day ago
ኢዜማን ምረጥ ያለው ኢህአዴግ በእስራት ተቀጣ

​#fastmereja I በደቡብ አሪ ወረዳ፣ ገድር ቀበሌ በምርጫ ዕለት የተከለከለ የፖለቲካ ቅስቀሳ በማድረጉ የተከሰሰው አቶ ኢህአዴግ ኃይሉ የ6 ወር ቀላል እስራት ተፈረደበት።

​የዐቃቤ ህግ ክስ እንደሚያስረዳው፣ ተከሳሹ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ምርጫ ጣቢያ አቅራቢያ ድምፅ ለመስጠት ወደ ጣቢያው ይሄድ የነበረን ወጣት ለኢዜማ ድምፅ እንዲሰጥ በመገፋፋት በምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 የተደነገገውን ክልከላ ጥሷል።

​ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የደቡብ አሪ ወረዳ ፍርድ ቤት፣ የዐቃቤ ህግን የሰው ምስክሮች እና የተከሳሹን የእምነት ክህደት ቃል ካዳመጠ በኋላ ተከሳሹ መከላከያ ማስረጃ ማቅረብ ባለመቻሉ ጥፋተኛ ብሎታል። ፍርድ ቤቱ ተከሳሹ የሦስት ልጆች አሳዳጊ መሆኑን እንደ ማቅለያ በመቀበል፣ በቀጣይ ለሌሎችም ማስጠንቀቂያ ይሆን ዘንድ በ6 ወር ቀላል እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አሳልፏል። ፍርዱ ለሁለት ዓመት በግልጽ ገደብ እንዲፈጸም ታዟል።

FastMereja
2 days ago
የዳሽን ባንክ ቅሬታችን ምላሽ አግኝቷል።

ዛሬ የዳሽን ባንክ የደንበኛ ቅሬታ አቅርበን ነበር ቅሬታውን የተመለከቱ የዳሽን ባንክ የስራ ኃላፊዎች የቀረበውን ቅሬታ ተቀብለው አስቸኳይ ምላሽ መስጠት ችሏል። ከልብ እናመሰግናለን።

FastMereja
2 days ago
ቢቢሲ በአርሲ በደረሰው ጥቃት ላይ መረጃ ለመጠየቅ ለኦሮሚያ ክልል ኮሚዩኒክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ እና የክልሉ ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አራርሳ መርዳሳ በተደጋጋሚ ቢደውልም ስልካቸው ባለመነሳቱ ምላሽ ማግኘት አልቻለም።

ቢቢሲ አፋን ኦሮሞ የአርሲ ዞን ኮሚዩኒኬሽን ጽህፈት ቤት ኃላፊ የሆኑትን አቶ ሶሪ ወጊን ስለተፈጸመው ጥቃት ማክሰኞ አመሻሽ ላይ ላቀረበላቸው ጥያቄ "እስከአሁን የደረሰን መረጃ የለም፤ እናጣራለን" የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ጥቃቱ ከተፈጸመባቸው አካበቢዎች አንዱ የሆነው የሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ አስተዳዳሪ ሐሰን መሐመድም ሰዎች ስለሞቱበት እና ንብረት ስለወደመበት ክስተት "መረጃ የለንም" የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

FastMereja
2 days ago
የአርሰናል የፕሪሚየር ሊግ ድል በአዲስ አበባ "WE CHAMPIONS 2026" ታሪካዊ ፌስቲቫል ሊካሄድ ነው

​#fastmereja | አርሰናል ከ22 ዓመታት በኋላ ያነሳውን የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ ለማክበር ግንቦት 29/2018 በአዲስ አበባ ስታዲየም ታሪካዊ የእግር ኳስና የመዝናኛ ፌስቲቫል ይካሄዳል። በቫርደስ ኢንተርቴይመንት የተዘጋጀውና በአዋሽ ባንክ (አዋሽብር ፕሮ) ዋና ስፖንሰርነት የሚከናወነው ይህ ዝግጅት፣ ከ30 ሺህ በላይ ታዳሚዎችን እና ዓለም አቀፍ እንግዶችን በአንድ ላይ ያሰባስባል።

​ዝግጅቱ የክለቡን ድል ከመዘከር ባለፈ፣ ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ዝግጅቶችን የማስተናገድ አቅሟን ለዓለም የምታሳይበት መድረክ እንደሚሆን ይጠበቃል። በስፍራውም ታዋቂ ድምፃውያን እና የስፖርት ቤተሰቦች ይታደማሉ።

በክስተቱ ላይ የቀድሞው የአርሰናል እና የኮትዲቯር ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች ኢማኑኤል ኢቡዌ በልዩ እንግድነት ይገኛል። ከእርሱ በተጨማሪ በዓለም ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ካላቸው የእግር ኳስ ሚዲያዎች አንዱ የሆነው AFTV ልዑካን ቡድን ወደ ኢትዮጵያ ይመጣል። በቡድኑ ውስጥ፡

​ሊ ዳጅስ (Lee Judges) – አቅራቢ (ዩናይትድ ኪንግደም)

​ሴሲል ጂ ቶማስ (Cecil Jee Thomas) – አቅራቢ (ዩናይትድ ኪንግደም)

​ጀረሚ (Jeremy) – ዲጂታል ይዘት ፈጣሪ (ደቡብ አፍሪካ) ይገኙበታል።
በዚህ ዝግጀት ላይ ከ 10 በላይ የሆኑ እውቅ እና ወጣት ኢትዮጵያዊ ድምፃዊያን የሙዚቃ ስራቸው እንደሚያቀረቡ ተገልጾ ከነዚህም መካከል ታደለ ሮባ ፣ ልጅ ሚካኤል (ፋፍ) ፣ ሳሚ ዳን ፣ አስጌ ዴንዳሾ ፣ ራሄል ጌቱ ፣ ሮቤል ሚዲቅሳ ፣ ዮ ማሪዮስ ፣ ሚክ ዋን ፣ አማኑኤል የማነ ፣ አዲስ ሙላት እንዲሁም እውቁ የዳስሆል/የአፍሮቢትስ ሙዚቃ ተጫዋቹ ፍራንኪዬ ዲ እና ሌሎችም ድምፃዊያን የሙዚቃ ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ::
የዝግጅቱ ብቸኛ የትኬት መሸጫ መድረክ "አዋሽብር ፕሮ" ነው። ደጋፊዎች ትኬታቸውን በሚከተሉት መንገዶች ማግኘት ይችላሉ፦

​በአዋሽብር ፕሮ አፕሊኬሽን
​በአዋሽ ባንክ ቅርንጫፎች (ከ1,000 በላይ ቅርንጫፎች)
​በአዋሽ ብር ፕሮ ኤጀንቶች
​በአዲስ አበባ ስታዲየም በተዘጋጁ ጊዜያዊ መሸጫ ጣቢያዎች (ከግንቦት 25 እስከ ግንቦት 29)

​ከግዢው ጋር በተያያዘ፣ ትኬታቸውን በቅድሚያ ለሚገዙ ደጋፊዎች የ"WE CHAMPIONS 2026" ይፋዊ ማሊያ የማግኘት ዕድል ተመቻችቷል።

FastMereja
2 days ago
የንግድ ድንበሮችን በመሻገር የአፍሪካን ገበያ ይቆጣጠሩ!

የኢትዮጵያን የቢዝነስ መሪዎች፣ ሥራ አስኪያጆች እና ባለሀብቶች ከሩዋንዳ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሾች ጋር የሚያገናኘው ታላቁ የኢትዮጵያ - ሩዋንዳ ቢዝነስ ፎረም 2026 ምዝገባ ጀምሯል። ይህ የ4 ቀናት የቢዝነስ ጉዞ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድ ልውውጥ ለማሳደግ እና አዲስ የኢንቨስትመንት አድማስ ለመክፈት ታስቦ የተዘጋጀ ልዩ መድረክ ነው።
በፎረሙ ላይ በመሳተፍዎ ምን ያተርፋሉ?
• 🤝 አስቀድመው የተመቻቹ እና ያተኮሩ የB2B (የንግድ ለንግድ) ስብሰባዎች
• 🎯 ከታዋቂ ባለሀብቶች እና ዋና የንግድ ውሳኔ ሰጪዎች ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት
• 📈 ወደ ሩዋንዳ ገበያ በምቾት ለመግባት የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ድጋፍ እና የተግባር የመስክ ምልከታ (Site Visits)
•በዛውም በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ የሩዋንዳ ኤግዚቢሽን ላይ ይሳተፋሉ
ዋና ዋና የትኩረት ዘርፎች፦
ግብርና ማቀነባበሪያ (Agro-Processing) | ሪል ስቴት እና ኮንስትራክሽን | ቱሪዝም እና ሆስፒታሊቲ | አይሲቲ እና ኢኖቬሽን | ማኑፋክቸሪንግ (ማምረቻ ዘርፍ)

📅 ቀን፦ hamele 21-24፣ 2018 ዓ.ም (july 28–31, 2026)
📍 ቦታ፦ ኪጋሊ ፣ ሩዋንዳ (Kigali, Rwanda)
⏱️ ቆይታ፦ 4 ቀናት የንግድ ተልዕኮ
የመቀመጫዎች ብዛት በጣም ውስን ስለሆነ አሁኑኑ ይመዝገቡ! 📞 ስልክ ቁጥር፦ +251 911874859/0913174052
📧 ኢሜይል፦ infoalohavistaevents.com
🌐 ድረ-ገጽ፦ www.alohavistaevents.com

በኢትዮጵያ የፌዴራል ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኤምባሲ (ኪጋሊ) እና በሩዋንዳ ልማት ቦርድ (RDB) ትብብር የተዘጋጀ።

FastMereja
2 days ago
የእንጦጦ-ቀጨኔ የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ተመረቀ

​#fastmereja | የፊታችን ማክሰኞ፣ ሰኔ 2 ቀን 2026 ዓ.ም፣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተከናወነው የእንጦጦ-ቀጨኔ የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በይፋ ተመርቆ ለሕዝብ ክፍት ሆኗል። ፕሮጀክቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተመርቋል።

​የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደገለጹት፤ ከዚህ ቀደም ለሰው ኑሮ ምቹ ያልሆነ፣ የተጎሳቆለ እና ለአደጋ የተጋለጠ የነበረው የእንጦጦ እስከ ቀጨኔ ያለው አካባቢ፣ አሁን ላይ ወደ ቀድሞ ተፈጥሯዊ ይዘቱ ተመልሶ ውብ እና ማራኪ ገጽታን ተላብሷል። ይህ ፕሮጀክት የከተማዋን "ሳምባ" በሆነው ደን ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፣ የአካባቢውን ማህበረሰብ ታሪክ እና የስራ ባህል የሚያንጸባርቁ ቅርሶችና ሐውልቶች ተካተውበታል።

​የፕሮጀክቱ ዋና ዋና ይዘቶች፦

ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ 597 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን፣ 9.6 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የወንዝ ዳርቻን ይሸፍናል።

15 ሄክታር መሬት በአረንጓዴ ተሸፍኗል። በውስጡም 210 ቀፎ ዘመናዊ ንብ እርባታ፣ የአበባ ጋርደን እና የእጽዋት ጋርደን የተካተቱበት ነው።

​የመሠረተ ልማት ግንባታዎች፦

​6.4 ኪሎ ሜትር የተሽከርካሪ መንገድ።

​8 ኪሎ ሜትር የሳይክል መንገድ።

​22 ኪሎ ሜትር የእግረኛ መንገድ።

​4 ኪሎ ሜትር የሃይኪንግ መንገድ።

​39 ቼክ ዳሞች የተገነቡ ሲሆን፣ ሁለት አዳዲስ ድልድዮች እና ሶስት ነባር ድልድዮችም እድሳት ተደርጎላቸዋል።

​የከተማ አስተዳደሩ ይህንን ለብዙኃን አገልግሎት እንዲሰጥ ታሳቢ ተደርጎ የተገነባውን የከተማ መናፈሻ፣ የከተማው ነዋሪ እንዲጠቀምበት እና እንዲንከባከበው ጥሪ አቅርቧል። ፕሮጀክቱ ለመዝናኛ፣ ለንግድ እና ለተለያዩ ማህበራዊ ኩነቶች ምቹ ሆኖ የተዘጋጀ መሆኑም ተገልጿል።

FastMereja
2 days ago
በሰለም ስጠቀም የነበረውን አፕሊኬሽን ስራ አቁመው እያንከራተቱኝ ነው።

ሰሞኑን ንግድ ባንክ መመላለስ የስራ ቦታዬ ነው የሚመስለው፣ በዲጂታል ዘመን ንግድ ባንክ ምክንያቱ ምን እንደሆነ በማላውቀው ተደጋጋሚ እያመላለሰኝ ነው።

በኦላይን ያያዘኩትን ፋይዳ በድንገት አልተያያዘም ብሎ ረጅም ሰልፍ አሰልፎ ከፈተልኝ አሁን ደግሞ ቅዳሜ በድንገት አፕሊኬሽኑ ስራ አቁሞ ድጋሜ ወደ አሰልቺው ቅርጫፍ መስሪያ ቤት ብሄድም ገበያ መስሏል የህዝቡ ብዛት... ጉዳዬን አስረድቼ ለአይፎን ከሰዓት ና አሁን ሲስተም እየሰራ አይደለም ብለው ሸኙን።

እሁድ እና ሰኞን አሳልፌ ዛሬ ወደ ሌላኛው ቅርጫፍ ስሄድ እንደተለመደው በህዝብ ተጨናንቋል በዛ ላይ ሲስተም የለም OTP እያለከ አይደለም ብለው ሸኙን።

ባንኩ ለምንድነው በዚህ ዲጅታል ዘመን ህዝቡን በቅርጫፉ የሚያከማቸው፣ ለምንስ ነው የባንኩ አፕሊኬሽኖች ያለ ምክንያት ስራ የሚያቆሙት?

FastMereja
2 days ago
ይድረስ ለዳሽን ባንክ

ለአስቸኳይ ስራ ገንዘብ ተፈልጎ ቅዳሜ ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓም በ5:50 ከዳሽን ባንክ ወደ ሌላ ባንክ 20ሺህ ብር ገንዘብ በዳሽን ሱፐር አፕ ብናስተላልፍም ገንዘቡ እስከ አሁን ሊደርስ አልቻለም።

ጉዳዩን ለማመልከት ወደ 6333 በተደጋጋሚ ብንደውልም ስልክ አያነሱም፣ ወደ ቅርጫፍ መስሪያ ቤት ሄደን ስንጠይቅ 6333 ላይ ካልሆነ እኛ መፍትሄ መስጠት አንችልም የሚል ምላሽ ነው የሰጡን።

አሁንም በተደጋጋሚ ወደ 6333 ብንደውልም ስልኩ በስህተት እንኳን አንድ ጊዜም አይነሳም።

ባንኩ ይህን መልዕክት ተመልክቶ መልስ ይስጠን።

FastMereja
2 days ago
"ምርጫ ጣቢያው ሙሉ በሙሉ እንዲዘጋ ተወስኗል"

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቡርጂ የምርጫ ጣቢያ ተፈጽሟል በተባለ ሕገ-ወጥ ድርጊት ምክንያት፣ ጣቢያው ሙሉ በሙሉ እንዲዘጋ መወሰኑን የቦርዱ ሰብሳቢ ወይዘሮ ሜላተወርቅ ኃይሉ አስታወቁ።

የቦርዱ ሰብሳቢ እንደገለጹት "በቡርጂ ምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎች እራሳቸው በምርጫ ጣቢያ በድምጽ መስጫ ወረቀት ላይ ምልክት እያደረጉ ድምጽ ሲሰጡ ስለተገኙ ያ ምርጫ ጣቢያ ሙሉ በሙሉ እንዲዘጋ ቦርዱ ወስኖ ዘግቷል። ይሄን ድርጊት የፈጸሙ አስፈጻሚዎች ላይ በቀጣይ የሚወሰደውን እርምጃ በቀጣይ ያሳውቃል" ብለዋል።

Via: አርትስ ቲቪ

FastMereja
2 days ago
በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ከ10 በላይ ኦርቶዶክሳውያን ሲገደሉ
የ101 ዓመት እድሜ ያለው የቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ወድሟል።

የመድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ላይም ዘረፋ የተካሄደ ሲሆን ምእመናን ጽላቱን ይዘው ተሰደዋል፤ መኖሪያ ቤታቸውም ተቃጥሏል።

ከግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት፣ አሰኮ ወረዳ፣ ጠላታ ጨፋ ቀበሌ እና ካራ ኩፍቴና በሚባሉ አካባቢዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ ያነጣጠረ አሰቃቂ ግድያ ተፈጽሟል።

በአሰኮ ወረዳ ጠላታ ጨፋ ቀበሌ ብቻ በታጣቂ ኃይሎች በተፈጸመ ሰብአዊነት በጎደለው ጥቃት ከ10 በላይ ንጹሃን ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል።

በአካባቢው 101 ዓመታትን ዕድሜ ያስቆጠረው፣ የጠላታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ወውደሙ ተገልጿል።

በተመሳሳይ ጥቃት በካራ ኩፍቴና መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ላይ ጥቃት የተሰነዘረ ሲሆን፣ የቤተክርስቲያኑ ንብረት የሆኑ ቤቶች በመቃጠላቸው ምእመናን የመድኃኔዓለምን ቅዱስ ጽላት ይዘው በእግራቸው ወደሌላ አካባቢ መሸሻቸው ታውቋል።

በዚሁ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በሺርካ ወረዳ በሁለት ወጣት ኦርቶዶክሳውያን ላይ ዘግናኝ ግድያ መፈጸሙ ተሰምቷል።

ድርጊቱ የተፈጸመው ሚታና ዋጂ ቀበሌ ሲሆን፣ ታጣቂዎች ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ወደ ወጣቶቹ መኖሪያ ቤት በመግባት በቁጥጥር ስር እንዳዋሏቸውና በመቀጠልም ወጣቶቹን ወደ ሚታና ጋዶ ቀበሌ በመውሰድ፣ አንደኛውን በስለት አር ደው፣ ሁለተኛውን ደግሞ በጥይት በመምታት በጭካኔ ሕይወታቸውን እንዳጠፉት ተገልጿል።

ሕይወታቸውን ያጡት የእነዚህ ወጣቶች ሥርዓተ ቀብር ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በጋዶ ማሕደረ ስብሐት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን፣ ምዕመናንና በቤተሰብ በተገኘበት በአንድ መቃብር ተፈጽሟል።

በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በአገልጋዮችና ምእመናን ላይ በተደጋጋሚ ጥቃት እንደሚፈጸምበት ማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ለዓመታት መረጃ እያደረሰ ቢሆንም ዛሬም ድረስ ዘላቂ መፍትሔ አልተገኘም።

መረጃው የማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ነው። #fastmereja

FastMereja
2 days ago
አሰልቺው ቃለምልልስ

ድምፃዊት ሃሊማ በሰይፉ በኢቢኤስ ላይ ቀርባ ነበር ተጀምሮ እስኪጠናቀቀ ድረስ ታገቢያለሽ… አታገቢም… ጭቅጭቅ ለረጅም ደቂቃ ተመሳሳይ ነገር ተደርጎ ተጠናቋል። ይህም አሰልቺው ቃለ ምልልስ ተብሏል። ሃሊማ ላለፉት በርካታ ጊዜያት ሰይፉ ጋር ቀርባ ተመሳሳይ ጭቅጭቅ በማድረግ ህዝቡን አሰልችተውታል።

FastMereja
2 days ago
አርቲስት ማርያማዊት አባተ በፒኤስጂ እና አርሰናል ጨዋታ ፒኤስጂ ያሸንፋል ብዬ 300ሺ ብር ቁማር በልቻለሁ ይህ የቁማር ገንዘብ አካውንቴ ጋር እንዲገባ አልፈልግም፣ ቤተክርስቲያንም መግባት አይችልም፣ ምን ላድርገው ስትል ጥያቄ አቅርባለች።

FastMereja
2 days ago
በኬንያ የአሜሪካ የኢቦላ ማቆያ ማዕከል ሊገነባ ነው መባሉ ህዝባዊ ተቃውሞ አስነሳ
#fastmereja በኬንያ ላይኪፒያ ግዛት ናኙኪ ከተማ የአሜሪካ መንግስት ሊገነባው ባቀደው የኢቦላ መከላከያ ማኳያ ማዕከል ላይ የአካባቢው ነዋሪዎች ዛሬ ሰኞ ከፍተኛ ህዝባዊ ተቃውሞ አደረጉ።

ነዋሪዎቹ የኢቦላ ቫይረስ ተጋላጭ የሆኑ አሜሪካውያንን ለማቆየት በኬንያ አየር ኃይል የጦር ሰፈር ውስጥ ሊገነባ የታቀደውን ባለ 50 አልጋ ማዕከል የተቃወሙት፣ አስቀድሞ ምንም ዓይነት የሕዝብ ውይይትና ምክክር ሳይደረግበት በምስጢር የተወሰነ ነው በሚል ነው።

ነዋሪዎችና ፖሊስ ወደ ግጭት ውስጥ የገቡ ሲሆን የጸጥታ ኃይሎች አስለቃሽ ጭስ በመተኮስ ሰልፈኞችን ለመበተን መገደዳቸው ታውቋል። በተፈጠረው ግርግር ሳቢያ የናኙኪ ከተማ የንግድና የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ የተስተጓጎለ ሲሆን፣ ማዕከሉ ሊገነባ ነው የሚለው ዜና የአካባቢውን የቱሪዝም ዘርፍ ክፉኛ መምታቱ ተገልጿል። በርካታ ዓለም አቀፍ ቱሪስቶች ወደ አካባቢው የሚያደርጉትን የሆቴልና የሆምስቴይ የቦታ ማስያዣ ጥያቄዎችን በጅምላ እየሰረዙ መሆኑን የዘርፉ ባለቤቶች በምሬት ተናግረዋል።

የአካባቢው የንግድ ምክር ቤትና የፖለቲካ መሪዎች መንግስትን በግልጽ እየተቹ ሲሆን፣ የአገሪቱ የጤና ሥርዓት መሰረታዊ ክትባቶችን እንኳን ማቅረብ ባልቻለበት ሁኔታ ዓለም አቀፍ አደጋ የሆነውን የኢቦላ ማቆያ ማዕከል መቀበል አደገኛ መሆኑን ገልጸዋል።

FastMereja
3 days ago
ከኢትዮጵያ እስከ አውሮፓዊቷ ማድሪድ ከተማ፦ ለሪል እስቴትና ለግንባታ ዘርፍ አዲስ የትብብር ምዕራፍ

በኢትዮጵያ የሪል እስቴት፣ የግንባታና የቤት ልማት ዘርፍን በተለያዩ ኢቨንቶች፣ ኤግዚቢሽኖች እና አዋርድ ፕሮግራሞች በማገልገል የሚታወቀው አርኪ ኢቨንት ኦርጋናይዘር፣ ከስፔን ማድሪድ የሚገኘውና የታዋቂውን SIMA Home Expo ጨምሮ በርካታ ዓለም አቀፍ የሪል እስቴት ኢቨንቶችን ከሚያዘጋጀው Planner Exhibitions ጋር ለትብብር ውይይት ወደ ስፔን ሊያቀና ነው።

ግብዣው የቀረበው በኢትዮጵያ በሚካሄደው ኢትዮ ሪል እስቴት አዋርድ እንዲሁም በቀጣይ በኢትዮጵያና በአፍሪካ ደረጃ የግንባታና የቤት ልማት ዘርፍን የሚያበረታቱ ፕሮጀክቶችን፣ ኮንፈረንሶችን፣ ኤግዚቢሽኖችን እና የእውቀት ልውውጥ መድረኮችን በጋራ ለማስፋፋት በሚያስችሉ ሀሳቦች ላይ ለመመካከር ነው።

አርኪ ኢቨንት ኦርጋናይዘርም ይህንን ግብዣ ከተቋማዊ ትብብር በላይ፣ ለኢትዮጵያ እና ለአፍሪካ የሪል እስቴትና የግንባታ ዘርፍ አዳዲስ ዕድሎችን የሚከፍት አጋጣሚ በመሆኑ በበጎ መንፈስ ተቀብሎታል።

በተጨማሪም መንግስት የከፈተውን የሪል እስቴት የኢንቨስትመንት እድል በመጠቀም አውሮፓውያን የሪል እስቴት ኢንቨስተሮችን ወደ ኢትዮጵያ ለመሳብ እና ከአገር ውስጥ ተዋናዮች ጋር የሚያገናኙ የትብብር መድረኮችን ለመፍጠርም ውይይቶች ይደረጋሉ።

ይህ ውይይት በቀጣይ የአለም አቀፍ ኢንቨስትመንት ትስስሮችን ለማጠናከር፣ የኢትዮጵያን የሪል እስቴት ገበያ ለዓለም አቀፍ ተዋናዮች ለማስተዋወቅ እና በአፍሪካ የቤት ልማት ዘርፍ ዘላቂ እድገትን ለማበረታታት ጠቃሚ መሠረት ይጥላል ተብሎ ይጠበቃል።
planner exhibitionsArkievent organizers

FastMereja
3 days ago
በድጋሚ የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳ 12:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽት 12:00 ሰዓት የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ድምፅ የማስፈጸም ሂደት ላይ እንደነበር ይታወቃል። ቦርዱ በሥምሪት ላይ ያለው የክትትል ቡድኑ ያቀረበለትን ሪፖርት ተመልክቶ የሚከተለውን ወሥኗል።

በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 49(4) መሠረት ቦርዱ የምርጫው ነፃና ፍትሐዊነት ይበልጥ ያሰፍናል ብሎ ካመነ የድምፅ መስጫ ሰዓቱን ሊያራዝም እንደሚችል በግልጽ ይደነግጋል። በመሆኑም የድምፅ መስጫ ሂደት ባልተጠናቀቀባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ድምፅ የመስጠት ሂደቱ እስከ ዕኩለ ለሊት 6:00 ሰዓት ድረስ የተራዘመ መሆኑን ቦርዱ ያሳውቃል።

ማሳሰቢያ: የተመዘገቡ መራጮች መርጠው የተጠናቀቁባቸው ጣቢያዎች ላይ አስፈጻሚዎች የድምፅ ቆጠራ ሂደቱን እንዲያከናውኑ ቦርዱ ያስታውሳል።

FastMereja
3 days ago
የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን የምርጫ ትዝብት ሪፖርት

​#fastmereja | የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ባወጣው የጠዋት የምርጫ ሂደት ሪፖርት መሠረት፣ 7ኛው አገራዊ ምርጫ በአብዛኞቹ ክልሎች በሰላማዊ እና በተደራጀ ሁኔታ መጀመሩ ተገልጿል። ይሁን እንጂ በአማራ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች የፀጥታ ስጋት፣ የተኩስ ድምፅ እና የምርጫ ቁሳቁስ እጥረት መከሰቱ ተመዝግቧል።

​የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን በምርጫው ዕለት በሀገር አቀፍ ደረጃ 14,160 ታዛቢዎችን በማሰማራት ሂደቱን ሲከታተል ቆይቷል። የፌዴሬሽኑ ግኝቶች የሚያሳዩት ዋና ዋና ነጥቦች እንደሚከተለው ቀርበዋል፦

📌 ​የምርጫው አጀማመር እና ተሳትፎ፦ ምርጫው በ10 ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ምንም ዓይነት የፀጥታ ችግር ሳይገጥመው በሰላም ተጀምሯል። በብዙ የምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች ተሳትፎ ከጠዋቱ ጀምሮ ከፍተኛ እንደነበር ታዛቢዎች ገልጸዋል።

📌 ​የአማራ ክልል ሁኔታ፦ በደብረ ታቦር፣ ደብረ ጎንደር እና አዊ ዞኖች የተኩስ ድምፅ መሰማቱ የተዘገበ ሲሆን፣ በክልሉ የምርጫ ቁሳቁስ እጥረት መኖሩም ተነግሯል።

📌 ​የጣቢያ መክፈቻ መዘግየት፦ በአማራ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ጋምቤላ፣ ሲዳማ እና አዲስ አበባ አንዳንድ ጣቢያዎች በሰዓቱ ባለመከፈታቸው የጥቂት ደቂቃዎች መዘግየት ታይቷል።

📌 ​የታዛቢዎች ስምሪት፦ ፌዴሬሽኑ 14,160 ታዛቢዎችን በማሰማራት የሴቶችን ደህንነትና የምርጫ ሂደቱን ቢከታተልም፣ በሎጂስቲክስ እና በተደራሽነት ችግር ምክንያት 22,788 የምርጫ ጣቢያዎች ያለ ታዛቢ ቀርተዋል።

📌 ​ምክረ ሃሳብ፦ ፌዴሬሽኑ በአማራ ክልል የፀጥታ ክትትል እንዲጠናከር፣ የጎደሉ የምርጫ ቁሳቁሶች በፍጥነት እንዲሟሉ እና ለሚቀጥሉት ሰዓታት ለአረጋውያንና ለአካል ጉዳተኞች ምቹ ሁኔታ እንዲፈጠር ለሚመለከታቸው አካላት ጥሪ አቅርቧል።

ይህ ሪፖርት በኦሮሚያ እና በአዲስ አበባ ሴቶች ፌዴሬሽን የተሰበሰበውን መረጃ ጨምሮ እንደ ሀገር አቀፍ የፌዴሬሽኑ መረጃ ተቀናጅቶ የቀረበ ነው።

FastMereja
3 days ago
የስፖርት ይዘት ፈጣሪዎች ወድድር ተወዳዳሪ እጩዎችን መጠቆም ተጀመረ።

በ Actually Creative እና E-Receipt የሚዘጋጀው የመጀመሪያው የቲክቶክ የስፖርት ይዘት ፈጣሪዎች ውድድር በቅርብ ቀን ሊካሄድ መሆኑ ተገለፀ።

Sport creators cup የስፖርት ይዘት ፈጣሪዎች በማዝናናት፣ በማስተማርና በማነቃቃት ላሳለፉበት ዓመት እውቅናና ማበረታቻ እንዲሆን ይህ ውድድር የተዘጋጀ ሲሆን ፣ ከ1.5 ሚለየን ብር በላይ ሽልማትም ለተወዳዳሪዎች እንደተዘጋጀ ለማወቅ ተችሏል።

በሁሉም የስፖርት ዘርፍ የሚገኙ ይዘት ፈጣሪዎች የሚሳተፉበት ሲሆን የሚወዳደሩበት (Category) ምድብ በቅርቡ ይፋ ይደረጋል

እርሶም በውድድሩ ሊሳተፍ እንዲሁም ሊሸለም ይገባዋል የምትሉን ይዘት ፈጣሪ (ቲክቶከር) ከስር በተቀመጠው ሊንክ በኩል ጥቆማ እንድታረጉ ጥሪ ቀርቧል።

Sport creators cup
Actually creative
E-Receipt

http://etsportok.com

FastMereja
3 days ago
በጸጥታ ችግር ምክንያት 143 የምርጫ ጣቢያዎች በዛሬው ዕለት አለመከፈታቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። በኦሮሚያ እና በአማራ ክልል “በተወሰኑ ቦታዎች” የድምጽ መስጠት ሂደቱ ከተጀመረ በኋላ የተቋረጠባቸው የምርጫ ጣቢያዎች እንዳሉም ቦርዱ ገልጿል።

ቦርዱ ይህን ያስታወቀው ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24፤ 2018 ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ እየተካሄደ ያለውን ሰባተኛ ጠቅላላ ምርጫ በተመለከተ በሰጠው መግለጫ ነው።

Via: ኢትዮጵያ ኢንሳይደር

FastMereja
3 days ago
ምርጫ ጣቢያዎች በሰው ኃይል እጥረት ተጨናንቀዋል

በአዲስ አበባ የሚገኙ አንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች በዲጂታል የተመዘገቡ መራጮችን ስም ዝርዝር በማኑዋል (በወረቀት) እያመሳከሩ በማሳለፍ ላይ በመሆናቸው ምክንያት ከፍተኛ መስተጓጎል እና የእንግልት ሰልፍ መፈጠሩ ተነገረ። ከንጋቱ 12 ሰዓት ጀምረው ድምፅ ለመስጠት የተሰለፉ ዜጎች በአንድ አስመራጭ ብቻ በመስተናገዳቸው ሳቢያ ለሰዓታት ለመቆም መገደዳቸውንና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጣቸው በምሬት እየጠየቁ ይገኛሉ።

FastMereja
3 days ago
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምፃቸውን ሰጡ

ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ በመላ ሀገሪቱ እየተካሄደ በሚገኘው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በሚወዳደሩበት ምርጫ ጣቢያ በአካል ተገኝተው ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

FastMereja
3 days ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኦሮሚያ ክልል በምትገኘው በሻሻ ዛሬ ጠዋት ለሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጽ ሰጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን ውስጥ በሚገኘው ጎማ 2 የምርጫ ክልል ከሁለት የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ ዕጩዎች ጋር ይወዳደራሉ።

ነፃነትና እኩልነት ፓርቲን የሚወክሉት ዳግም ዋሪሶ እና የኢዜማ ዕጩ ካልድ ጃማል ሀይደር