1 month ago
ኬፕ ቨርዴ ሁለተኛ ነጥቧን ስታገኝ፤
ግብፅ በዓለም ዋንጫ ታሪኳ የመጀመሪያ ድሏን አስመዘገበች
#ethiopia | በ2026 የዓለም ዋንጫ ውድድር አፍሪካዊቷ ደሴት ሀገር Cape Verde በምድብ ስምንት ሁለተኛ ነጥቧን አግኝታለች። ኬፕ ቨርዴ ከሁለት ጊዜ የዓለም ዋንጫ ሻምፒዮን Uruguay ጋር 2–2 አቻ በመውጣት ያለመሸነፍ ጉዞዋን ቀጥላለች።
በጨዋታው ለኬፕ ቨርዴ ኬቪን ፒና እና ሀሊዮ ቫሬላ ግቦችን ሲያስቆጥሩ፣ ለኡራጓይ ደግሞ ማርከስ አራውሆ እና ማቲያስ ኦሊቬራ ከመረብ አሳርፈዋል። ኬፕ ቨርዴ በሁለት ነጥብ ወደ ጥሎ ማለፉ የመሸጋገር ተስፋዋን አጠናክራለች።
በሌላ የምድቡ ጨዋታ Belgium እና Iran ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል።
በተመሳሳይ ጊዜ Egypt በዓለም ዋንጫ ተሳትፎ ታሪኳ የመጀመሪያ ድሏን አስመዝግባለች። ግብፅ ከ New Zealand ጋር ባደረገችው ጨዋታ በመጀመሪያ ተከትላ ብትቆይም፣ በሙስጠፋ ዚኮ፣ Mohamed Salah እና ማህሙድ ትርዝጌት ግቦች 3–1 በማሸነፍ ታሪካዊ ድል አግኝታለች።
ድሉ ግብፅን በአራት ነጥብ የምድቧ መሪ እንድትሆን አድርጎ ወደ ጥሎ ማለፉ የመድረስ ዕድሏን አስፋፍቷል።።
ግብፅ በዓለም ዋንጫ ታሪኳ የመጀመሪያ ድሏን አስመዘገበች
#ethiopia | በ2026 የዓለም ዋንጫ ውድድር አፍሪካዊቷ ደሴት ሀገር Cape Verde በምድብ ስምንት ሁለተኛ ነጥቧን አግኝታለች። ኬፕ ቨርዴ ከሁለት ጊዜ የዓለም ዋንጫ ሻምፒዮን Uruguay ጋር 2–2 አቻ በመውጣት ያለመሸነፍ ጉዞዋን ቀጥላለች።
በጨዋታው ለኬፕ ቨርዴ ኬቪን ፒና እና ሀሊዮ ቫሬላ ግቦችን ሲያስቆጥሩ፣ ለኡራጓይ ደግሞ ማርከስ አራውሆ እና ማቲያስ ኦሊቬራ ከመረብ አሳርፈዋል። ኬፕ ቨርዴ በሁለት ነጥብ ወደ ጥሎ ማለፉ የመሸጋገር ተስፋዋን አጠናክራለች።
በሌላ የምድቡ ጨዋታ Belgium እና Iran ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል።
በተመሳሳይ ጊዜ Egypt በዓለም ዋንጫ ተሳትፎ ታሪኳ የመጀመሪያ ድሏን አስመዝግባለች። ግብፅ ከ New Zealand ጋር ባደረገችው ጨዋታ በመጀመሪያ ተከትላ ብትቆይም፣ በሙስጠፋ ዚኮ፣ Mohamed Salah እና ማህሙድ ትርዝጌት ግቦች 3–1 በማሸነፍ ታሪካዊ ድል አግኝታለች።
ድሉ ግብፅን በአራት ነጥብ የምድቧ መሪ እንድትሆን አድርጎ ወደ ጥሎ ማለፉ የመድረስ ዕድሏን አስፋፍቷል።።
1 month ago
ኢራን ከአሜሪካ ጋር የገባሁት ስምምነት አልተከበረም በሚል የሆርሙዝ ሰርጥን መልሳ መዝጋቷን አስታወቀች
#ethiopia | የኢራን ማዕከላዊ ወታደራዊ ዕዝ እስራኤል በደቡባዊ ሊባኖስ የምትፈጽመው ጥቃት ከአሜሪካ ጋር የተደረሰውን ስምምነት የሚጥስ በመሆኑ የሆርሙዝ ሰርጥን መዝጋቱን አስታውቋል።
የኢራን አብዮታዊ ዘብ ባሕር ኃይል የባሕር መተላለፊው ለሁሉም መርከቦች በመዘጋቱ ማናቸውም መርከቦች የወደ ሰርጡ የሚቀርቡ ከሆነ ለአደጋ ስለሚጋለጡ መርከባቸውን ከሆርሙዝ እንዲያርቁ አስጠንቅቋል።
አብዮታዊ ዘቡ በአገሪቱ ቴሌቪዥን ባቀረበው መግለጫ አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት መድረሳቸውን ተከትሎ አርብ ዕለት ሙሉ ለሙሉ ለመርከቦች የተከፈተው የባሕር መተላለፊያ ለሁሉም መርከቦች ተመልሶ ዝግ እንደሚሆን አስታውቋል።
ኢራን ከአሜሪካ ጋር በደረሰችው የመግባቢያ ስምምነት ላይ እስራኤል በሊባኖስ ላይ የምታካሂደው ጥቃት እንደሚቆም የተገለጸ ቢሆንም አሁንም ጥቃቱ በመቀጠሉ ኢራን ስምምነቱ ተጥሷል ማለቷን የቢቢሲ እና አልጀዚራ ዘገባ ያመለክታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ethiopian Broadcasting Corporation #hormuzstrait #iran #usa #peace
#ethiopia | የኢራን ማዕከላዊ ወታደራዊ ዕዝ እስራኤል በደቡባዊ ሊባኖስ የምትፈጽመው ጥቃት ከአሜሪካ ጋር የተደረሰውን ስምምነት የሚጥስ በመሆኑ የሆርሙዝ ሰርጥን መዝጋቱን አስታውቋል።
የኢራን አብዮታዊ ዘብ ባሕር ኃይል የባሕር መተላለፊው ለሁሉም መርከቦች በመዘጋቱ ማናቸውም መርከቦች የወደ ሰርጡ የሚቀርቡ ከሆነ ለአደጋ ስለሚጋለጡ መርከባቸውን ከሆርሙዝ እንዲያርቁ አስጠንቅቋል።
አብዮታዊ ዘቡ በአገሪቱ ቴሌቪዥን ባቀረበው መግለጫ አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት መድረሳቸውን ተከትሎ አርብ ዕለት ሙሉ ለሙሉ ለመርከቦች የተከፈተው የባሕር መተላለፊያ ለሁሉም መርከቦች ተመልሶ ዝግ እንደሚሆን አስታውቋል።
ኢራን ከአሜሪካ ጋር በደረሰችው የመግባቢያ ስምምነት ላይ እስራኤል በሊባኖስ ላይ የምታካሂደው ጥቃት እንደሚቆም የተገለጸ ቢሆንም አሁንም ጥቃቱ በመቀጠሉ ኢራን ስምምነቱ ተጥሷል ማለቷን የቢቢሲ እና አልጀዚራ ዘገባ ያመለክታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ethiopian Broadcasting Corporation #hormuzstrait #iran #usa #peace
2 months ago
የዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ከኢራን ጋር በተደረሰው የኒውክሌር ስምምነት ዙሪያ ተግባራዊ እርምጃዎችን ለመውሰድ መዘጋጀቱን አስታወቀ
#ethiopia | የዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ራፋኤል ግሮሲ የኢራንን የኒውክሌር መርሃ ግብር በተመለከተ ወደ ተጨባጭ ተግባር ለመሻገር ዝግጁ መሆናቸውን በይፋ ገልጸዋል።
ኢራን ከአሜሪካ ጋር በፈረመችው አዲስ የመግባቢያ ሰነድ አማካኝነት የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎችን ላለማምረትም ሆነ በባለቤትነት ላለመያዝ ዳግም ቁርጠኝነቷን አረጋግጣለች።
ከዚህ በተጨማሪም ሁለቱ አገራት ኢራን አከማችታው በሚገኘው የበለጸገ ዩራኒየም ጉዳይ ላይ በጋራ ለመወያየት ተስማምተዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ ራፋኤል ግሮሲ ዛሬ ማለዳ በሰጡት መግለጫ ሊያጋጥሙ በሚችሉ የቴክኒክ ፈተናዎች ላይ ብቻ በማተኮር ጊዜን ማባከን ተገቢ እንዳልሆነ አሳስበዋል።
ሁሉም ወገኖች በቅን ልቦና ተሳትፎ በማድረግ ስምምነቱ ግቡን እንዲመታ ይፈልጋሉ በሚል እምነት ድርድሩን እንደሚመሩት የገለጹት ዳይሬክተሩ፣ ስምምነቱን መፈረማቸው ራሱ ሂደቱን በቁም ነገር ለመተግበር ፍላጎት እንዳላቸው የሚያሳይ ምልክት መሆኑን ጠቁመዋል።
ኤጀንሲው ስለ ተወሰኑ ጉዳዮችና ፍተሻ ሊደረግባቸው ስለሚገቡ ስፍራዎች በቂና አስተማማኝ መረጃ እንዳለው የጠቀሱት ግሮሲ፣ ሆኖም ከሂደቱ ቀድሞ መደምደሚያ ላይ መድረስ ትክክል እንዳልሆነና በአሁኑ ወቅት በቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ለመወያየት እጅግ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንደሚገኙ አስገንዝበዋል።
#iran #nuclear #iaea #rafaelgrossi #worldnews #internationalrelations #usa #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ራፋኤል ግሮሲ የኢራንን የኒውክሌር መርሃ ግብር በተመለከተ ወደ ተጨባጭ ተግባር ለመሻገር ዝግጁ መሆናቸውን በይፋ ገልጸዋል።
ኢራን ከአሜሪካ ጋር በፈረመችው አዲስ የመግባቢያ ሰነድ አማካኝነት የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎችን ላለማምረትም ሆነ በባለቤትነት ላለመያዝ ዳግም ቁርጠኝነቷን አረጋግጣለች።
ከዚህ በተጨማሪም ሁለቱ አገራት ኢራን አከማችታው በሚገኘው የበለጸገ ዩራኒየም ጉዳይ ላይ በጋራ ለመወያየት ተስማምተዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ ራፋኤል ግሮሲ ዛሬ ማለዳ በሰጡት መግለጫ ሊያጋጥሙ በሚችሉ የቴክኒክ ፈተናዎች ላይ ብቻ በማተኮር ጊዜን ማባከን ተገቢ እንዳልሆነ አሳስበዋል።
ሁሉም ወገኖች በቅን ልቦና ተሳትፎ በማድረግ ስምምነቱ ግቡን እንዲመታ ይፈልጋሉ በሚል እምነት ድርድሩን እንደሚመሩት የገለጹት ዳይሬክተሩ፣ ስምምነቱን መፈረማቸው ራሱ ሂደቱን በቁም ነገር ለመተግበር ፍላጎት እንዳላቸው የሚያሳይ ምልክት መሆኑን ጠቁመዋል።
ኤጀንሲው ስለ ተወሰኑ ጉዳዮችና ፍተሻ ሊደረግባቸው ስለሚገቡ ስፍራዎች በቂና አስተማማኝ መረጃ እንዳለው የጠቀሱት ግሮሲ፣ ሆኖም ከሂደቱ ቀድሞ መደምደሚያ ላይ መድረስ ትክክል እንዳልሆነና በአሁኑ ወቅት በቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ ለመወያየት እጅግ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንደሚገኙ አስገንዝበዋል።
#iran #nuclear #iaea #rafaelgrossi #worldnews #internationalrelations #usa #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
ሰበር - እስራኤልን ከጨዋታ ውጭ ያደረገው የትራምፕ አወዛጋቢ ስምምነት! - አሜሪካ እና ኢራን ታረቁ? ማዕቀቡ ተነሳ! 🇺🇸🇮🇷💥 #trump #iran #israel #geopolitics #worldnews
2 months ago
የኢራን ደጋፊዎች ትኬት ተሰረዘ
#ethiopia | ብሔራዊ ቡድን ደጋፊዎች የቀረበው የስታዲየም መግቢያ ትኬት መሰረዙን የኢራን እግርኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።
ትኬቱ በምን ምክንያት እንደተሰረዘ ግን አልተነገረም።
ፌዴሬሽኑ ቡድኑ ማግኘት የሚገባውን የትኬት ኮታ መከልከሉን አውግዟል።
ፊፋ የገለልተኝነት እና ፍትሀዊነት መርሆዎችን እንዲያከብርም ጠይቋል።
መሰረዙን ተከትሎ ኢራናውያን ደጋፊዎች ስታዲየም መግባት አይችሉም።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #aradafm #worldcup #fifa #iran
#ethiopia | ብሔራዊ ቡድን ደጋፊዎች የቀረበው የስታዲየም መግቢያ ትኬት መሰረዙን የኢራን እግርኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።
ትኬቱ በምን ምክንያት እንደተሰረዘ ግን አልተነገረም።
ፌዴሬሽኑ ቡድኑ ማግኘት የሚገባውን የትኬት ኮታ መከልከሉን አውግዟል።
ፊፋ የገለልተኝነት እና ፍትሀዊነት መርሆዎችን እንዲያከብርም ጠይቋል።
መሰረዙን ተከትሎ ኢራናውያን ደጋፊዎች ስታዲየም መግባት አይችሉም።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #aradafm #worldcup #fifa #iran
2 months ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ ምን እያደረጉ ነው? - እስራኤል ለኢራን ጥቃት ምላሽ ትሰጣለች??
#israel #iran #middleeasttensions #netanyahu #geopolitics
Sponsored by
Surafel
2 months ago
እስካሁን ያላባራው የአሜሪካ እና የኢራን ውዝግብ
******************
በአሜሪካ፣ እስራኤል እና ኢራን መካከል ስላለው የተኩስ አቁም ድርድር እርስ በርሱ የሚጋጭ መረጃ እየወጣ ነው።
ከኢራን አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ጋር ቅርበት ያላቸው የኢራን የዜና ወኪሎች ፋርስ እና ተስኒም፣ ኢራን ከተኩስ አቁም አደራዳሪዎች ጋር የምታደርገውን ግንኙነት ሙሉ በሙሉ ማቋረጧን ዘግበዋል።
ኢራን በሊባኖስ (በእስራኤል እና በሂዝቦላህ መካከል) ያለው ግጭት ካልቆመ በስተቀር ድርድሩ እንደማይቀጥል ገልጻለች።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ግን “ሀሰት” ሲሉ ይህን ዘገባ አስተባብለዋል። "ንግግሩ ትናንትም ዛሬም ያለማቋረጥ እንደቀጠለ ነው፤ ኢራን ስምምነት ላይ የምትደርስበት ጊዜው አሁን ነው" ብለዋል።
የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ስለ ግንኙነቱ መቋረጥ የተባለውን ባያረጋግጡም፣ ስለ ኑክሌር ድርድሩ ሂደት ግን ተስፋ ሰጪ ሁኔታዎች እንዳሉ ጠቁመዋል።
ኢራን በሆርሙዝ የንግድ መስመር ላይ ያላትን ስትራቴጂያዊ የበላይነት በመጠቀም፣ አሜሪካ እስራኤል በሊባኖስ ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት እንድታስቆም እየጠየቀች ትገኛለች።
#middleeast #iran #usa #trump
******************
በአሜሪካ፣ እስራኤል እና ኢራን መካከል ስላለው የተኩስ አቁም ድርድር እርስ በርሱ የሚጋጭ መረጃ እየወጣ ነው።
ከኢራን አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ጋር ቅርበት ያላቸው የኢራን የዜና ወኪሎች ፋርስ እና ተስኒም፣ ኢራን ከተኩስ አቁም አደራዳሪዎች ጋር የምታደርገውን ግንኙነት ሙሉ በሙሉ ማቋረጧን ዘግበዋል።
ኢራን በሊባኖስ (በእስራኤል እና በሂዝቦላህ መካከል) ያለው ግጭት ካልቆመ በስተቀር ድርድሩ እንደማይቀጥል ገልጻለች።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ግን “ሀሰት” ሲሉ ይህን ዘገባ አስተባብለዋል። "ንግግሩ ትናንትም ዛሬም ያለማቋረጥ እንደቀጠለ ነው፤ ኢራን ስምምነት ላይ የምትደርስበት ጊዜው አሁን ነው" ብለዋል።
የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ስለ ግንኙነቱ መቋረጥ የተባለውን ባያረጋግጡም፣ ስለ ኑክሌር ድርድሩ ሂደት ግን ተስፋ ሰጪ ሁኔታዎች እንዳሉ ጠቁመዋል።
ኢራን በሆርሙዝ የንግድ መስመር ላይ ያላትን ስትራቴጂያዊ የበላይነት በመጠቀም፣ አሜሪካ እስራኤል በሊባኖስ ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት እንድታስቆም እየጠየቀች ትገኛለች።
#middleeast #iran #usa #trump
3 months ago
የኢራን የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ቀጥታ የስናይፐር እና የክላሽንኮቭ ስልጠና ማስተላለፍ ጀመሩ!
#ethiopia | በኢራን፣ በአሜሪካ እና በእስራኤል መካከል ያለው ወታደራዊ ፍጥጫ እና ውጥረት እጅግ አስፈሪ ደረጃ ላይ በደረሰበት በዚህ ወቅት፣ የኢራን ብሔራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች (IRIB) ታሪክ ከየቀኑ የዜና እወጃ ወጥተው የቀጥታ የስልጠና መድረክ መሆናቸውን ዓለም በደነገጠ ስሜት እየተከታተለው ይገኛል።
የጣቢያዎቹ የዜና አቅራቢዎችና ጋዜጠኞች ራሳቸው የጦር መሣሪያዎችን በአደባባይ በመያዝ እና የቀጥታ ተኩስ ልምምድ በማድረግ ላይ ናቸው።
በእነዚህ የቀጥታ የቴሌቪዥን ሥርጭቶች ላይ በስፋት ጥቅም ላይ እየዋለ የሚገኘው የምሥራቅ ጀርመን ስሪት የሆነው እና በ7.62×39 ሚሊሜትር ጥይት የሚተኩሰው ‘MPi-KMS’ የተባለው የክላሽንኮቭ (AK-47) የጦር መሣሪያ ዓይነት ነው።
የቴሌቪዥን አቅራቢዎቹ የጦር መሣሪያውን እንዴት መፍታት፣ መግጠም፣ ጥይት መክተት እና ኢላማን መምታት እንደሚቻል ከእስላማዊ አብዮት ጥበቃ ጦር (IRGC) መኮንኖች ጋር በመሆን ለሕዝብ ቀጥታ ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ።
ኢራን ይህንን ያልተለመደ የቴሌቪዥን ስርጭት “ሕይወትን ለኢራን መስዋዕት ማድረግ” (Sacrifice Life For Iran) ከሚለው አገር አቀፍ የዝግጁነት ዘመቻ ጋር ያገናኘችው ሲሆን፣ እስካሁን ድረስ ከ31 ሚሊዮን በላይ ዜጎች በፈቃደኝነት ለዚህ የክተት ጥሪ መመዝገባቸውን የመንግስት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ከዚህም በተጨማሪ በቴህራን እና በኬርማንሻህ ከተሞች የሚገኙ ታዳጊ ወጣቶች በአደባባዮች እና በመስጊዶች በተዘጋጁ ወታደራዊ ድንኳኖች ውስጥ የጦር መሣሪያ አያያዝ፣ የውጊያ ስልቶች እና የአገር መከላከያ ስልጠናዎችን እየወሰዱ ይገኛሉ።
የኢራን ብሔራዊ ቴሌቪዥን ከፍተኛ ባለሥልጣን የሆኑት ሞህሴን ባርመህኒ የሀገሪቱ ሚዲያዎች ሙሉ በሙሉ “የጦርነት አቋም” (Wartime Posture) መያዝ እንዳለባቸው በይፋ ያወጁ ሲሆን፣ በአንድ የቀጥታ ስርጭት ፕሮግራም ላይ የቴሌቪዥን አቅራቢው ክላሽንኮቭ መሣሪያውን ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬትስ (UAE) ባንዲራ አነጣጥሮ ሲተኩስ የታየበት ትዕይንት በባህረ ሰላጤው ሀገራት ዘንድ ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ቁጣንና ውግዘትን አስከትሏል ሲል መናኸሪያ ኤፍ ኤም ዘግቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #iran #war #television
#usarmy #peace
#ethiopia | በኢራን፣ በአሜሪካ እና በእስራኤል መካከል ያለው ወታደራዊ ፍጥጫ እና ውጥረት እጅግ አስፈሪ ደረጃ ላይ በደረሰበት በዚህ ወቅት፣ የኢራን ብሔራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች (IRIB) ታሪክ ከየቀኑ የዜና እወጃ ወጥተው የቀጥታ የስልጠና መድረክ መሆናቸውን ዓለም በደነገጠ ስሜት እየተከታተለው ይገኛል።
የጣቢያዎቹ የዜና አቅራቢዎችና ጋዜጠኞች ራሳቸው የጦር መሣሪያዎችን በአደባባይ በመያዝ እና የቀጥታ ተኩስ ልምምድ በማድረግ ላይ ናቸው።
በእነዚህ የቀጥታ የቴሌቪዥን ሥርጭቶች ላይ በስፋት ጥቅም ላይ እየዋለ የሚገኘው የምሥራቅ ጀርመን ስሪት የሆነው እና በ7.62×39 ሚሊሜትር ጥይት የሚተኩሰው ‘MPi-KMS’ የተባለው የክላሽንኮቭ (AK-47) የጦር መሣሪያ ዓይነት ነው።
የቴሌቪዥን አቅራቢዎቹ የጦር መሣሪያውን እንዴት መፍታት፣ መግጠም፣ ጥይት መክተት እና ኢላማን መምታት እንደሚቻል ከእስላማዊ አብዮት ጥበቃ ጦር (IRGC) መኮንኖች ጋር በመሆን ለሕዝብ ቀጥታ ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ።
ኢራን ይህንን ያልተለመደ የቴሌቪዥን ስርጭት “ሕይወትን ለኢራን መስዋዕት ማድረግ” (Sacrifice Life For Iran) ከሚለው አገር አቀፍ የዝግጁነት ዘመቻ ጋር ያገናኘችው ሲሆን፣ እስካሁን ድረስ ከ31 ሚሊዮን በላይ ዜጎች በፈቃደኝነት ለዚህ የክተት ጥሪ መመዝገባቸውን የመንግስት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ከዚህም በተጨማሪ በቴህራን እና በኬርማንሻህ ከተሞች የሚገኙ ታዳጊ ወጣቶች በአደባባዮች እና በመስጊዶች በተዘጋጁ ወታደራዊ ድንኳኖች ውስጥ የጦር መሣሪያ አያያዝ፣ የውጊያ ስልቶች እና የአገር መከላከያ ስልጠናዎችን እየወሰዱ ይገኛሉ።
የኢራን ብሔራዊ ቴሌቪዥን ከፍተኛ ባለሥልጣን የሆኑት ሞህሴን ባርመህኒ የሀገሪቱ ሚዲያዎች ሙሉ በሙሉ “የጦርነት አቋም” (Wartime Posture) መያዝ እንዳለባቸው በይፋ ያወጁ ሲሆን፣ በአንድ የቀጥታ ስርጭት ፕሮግራም ላይ የቴሌቪዥን አቅራቢው ክላሽንኮቭ መሣሪያውን ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬትስ (UAE) ባንዲራ አነጣጥሮ ሲተኩስ የታየበት ትዕይንት በባህረ ሰላጤው ሀገራት ዘንድ ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ቁጣንና ውግዘትን አስከትሏል ሲል መናኸሪያ ኤፍ ኤም ዘግቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #iran #war #television
#usarmy #peace
3 months ago
ቻይና እና አሜሪካ የሆርሙዝ የባሕር ሰርጥ ክፍት ሆኖ እንዲቆይ ተስማሙ
**********************
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ በቤጂንግ ባደረጉት የፊት ለፊት ውይይት በሆርሙዝ የባሕር ሰርጥ ዙሪያ መክረዋል።
በውይይታቸውም በኢራን ጦርነት ሳቢያ በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ ያለው ውጥረት በበረታበት በዚህ ወቅት፣ ስትራቴጂያዊው የሆርሙዝ ባሕር ሰርጥ “ነፃ የኃይል አቅርቦት ፍሰትን ለመደገፍ ሲባል የግድ ክፍት ሆኖ መቆየት አለበት” በሚለው ነጥብ ላይ ፕሬዚዳንት ሺ መስማማታቸውን ኋይት ሐውስ አስታውቋል።
በሌላ በኩል፣ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቅቺ በኒው ዴልሂ፣ በተካሄደው ስብሰባ ላይ የብሪክስ (BRICS) አባል ሀገራት አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የከፈቱትን ጦርነት እንዲያወግዙት አሳስበዋል።
ሚኒስትሩ “ቴህራን ለማንኛውም ዓይነት ውጫዊ ጫና በፍጹም እጅ እንደማትሰጥ” በአፅንኦት መናገራቸውን አልጀዚራ ዘግቧል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በደቡብ ሊባኖስ ከተሞች እና መንደሮች ላይ የእስራኤል ጥቃቶች አሁንም የቀጠሉ ቢሆንም፣ ግጭቱን በዘላቂነት ለማስቆም ያለመ የሊባኖስ እና የእስራኤል ተደራዳሪዎች ሦስተኛ ዙር የቀጥታ ውይይት በዋሽንግተን ዲሲ በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።
#globalnews #usa #china #iran #hormuzstrait #brics #diplomacy
**********************
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ በቤጂንግ ባደረጉት የፊት ለፊት ውይይት በሆርሙዝ የባሕር ሰርጥ ዙሪያ መክረዋል።
በውይይታቸውም በኢራን ጦርነት ሳቢያ በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ ያለው ውጥረት በበረታበት በዚህ ወቅት፣ ስትራቴጂያዊው የሆርሙዝ ባሕር ሰርጥ “ነፃ የኃይል አቅርቦት ፍሰትን ለመደገፍ ሲባል የግድ ክፍት ሆኖ መቆየት አለበት” በሚለው ነጥብ ላይ ፕሬዚዳንት ሺ መስማማታቸውን ኋይት ሐውስ አስታውቋል።
በሌላ በኩል፣ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቅቺ በኒው ዴልሂ፣ በተካሄደው ስብሰባ ላይ የብሪክስ (BRICS) አባል ሀገራት አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የከፈቱትን ጦርነት እንዲያወግዙት አሳስበዋል።
ሚኒስትሩ “ቴህራን ለማንኛውም ዓይነት ውጫዊ ጫና በፍጹም እጅ እንደማትሰጥ” በአፅንኦት መናገራቸውን አልጀዚራ ዘግቧል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በደቡብ ሊባኖስ ከተሞች እና መንደሮች ላይ የእስራኤል ጥቃቶች አሁንም የቀጠሉ ቢሆንም፣ ግጭቱን በዘላቂነት ለማስቆም ያለመ የሊባኖስ እና የእስራኤል ተደራዳሪዎች ሦስተኛ ዙር የቀጥታ ውይይት በዋሽንግተን ዲሲ በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።
#globalnews #usa #china #iran #hormuzstrait #brics #diplomacy
3 months ago
እንከባበር! - ኢራን
#ethiopia | ኢራን በኩዌት የታሰሩ ዜጎቿን በተመለከተ የአጸፋ እርምጃ የመውሰድ መብት እንዳለት አስታወቀች
በፋርስ ባሕረ ሰላጤ አቅራቢያ አራት ኢራናውያን በኩዌት የጸጥታ ኃይሎች መታሰራቸውን ተከትሎ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሀገራቸው ተመጣጣኝ ምላሽ የመስጠት መብት እንዳላት አስታውቃለችል፡፡
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቅቺ በሰጡት መግለጫ ኩዌት በሕገወጥ መንገድ በኢራን የባሕር ጓዝ ላይ ጥቃት መፈጸሟንና ዜጎቿን ማሰሯን ገልጸው የታሰሩት ግለሰቦች በአስቸኳይ እንዲፈቱ ጠይቀዋል፡፡
በሌላ በኩል የኩዌት የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ በባሕር በኩል ወደ ሀገር ውስጥ ለመግባት ሲሞክሩ የተያዙት አራት ግለሰቦች የኢራን አብዮታዊ ዘበኛ አባላት መሆናቸውን እንዳመኑ ይፋ አድርጓል፡፡
ይህንን ድርጊት ተከትሎ ዮርዳኖስ የኩዌትን ሉዓላዊነት የሚጋፋ ተግባር ነው ስትል ድርጊቱን ያወገዘች ሲሆን ለኩዌት ያላትን ሙሉ ድጋፍ ገልጻለች፡፡
ኢራን ግን ግለሰቦቹ ከአብዮታዊ ዘበኛው ጋር ግንኙነት አላቸው መባሉን አስተባብላለች፡፡
#iran #kuwait #middleeast #diplomacy #jordan #redsea #internationalnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ኢራን በኩዌት የታሰሩ ዜጎቿን በተመለከተ የአጸፋ እርምጃ የመውሰድ መብት እንዳለት አስታወቀች
በፋርስ ባሕረ ሰላጤ አቅራቢያ አራት ኢራናውያን በኩዌት የጸጥታ ኃይሎች መታሰራቸውን ተከትሎ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሀገራቸው ተመጣጣኝ ምላሽ የመስጠት መብት እንዳላት አስታውቃለችል፡፡
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቅቺ በሰጡት መግለጫ ኩዌት በሕገወጥ መንገድ በኢራን የባሕር ጓዝ ላይ ጥቃት መፈጸሟንና ዜጎቿን ማሰሯን ገልጸው የታሰሩት ግለሰቦች በአስቸኳይ እንዲፈቱ ጠይቀዋል፡፡
በሌላ በኩል የኩዌት የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ በባሕር በኩል ወደ ሀገር ውስጥ ለመግባት ሲሞክሩ የተያዙት አራት ግለሰቦች የኢራን አብዮታዊ ዘበኛ አባላት መሆናቸውን እንዳመኑ ይፋ አድርጓል፡፡
ይህንን ድርጊት ተከትሎ ዮርዳኖስ የኩዌትን ሉዓላዊነት የሚጋፋ ተግባር ነው ስትል ድርጊቱን ያወገዘች ሲሆን ለኩዌት ያላትን ሙሉ ድጋፍ ገልጻለች፡፡
ኢራን ግን ግለሰቦቹ ከአብዮታዊ ዘበኛው ጋር ግንኙነት አላቸው መባሉን አስተባብላለች፡፡
#iran #kuwait #middleeast #diplomacy #jordan #redsea #internationalnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Sponsored by
Surafel
3 months ago
ትራምፕ በኢራን ጉዳይ የቻይና ድጋፍ አያስፈልገኝም አሉ
#ethiopia | የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዋሽንግተን ከቴህራን ጋር ለገባችበት ዲፕሎማሲያዊ እና ፖለቲካዊ ፍጥጫ የቻይናው ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ እርዳታ እንደማያስፈልጋቸው በይፋ አስታወቁ።
ዛሬ ለጋዜጠኞች መግለጫ የሰጡት ፕሬዝዳንቱ፣ አሜሪካ በኢራን ጉዳይ ላይ የራሷን የውሳኔ አቅጣጫ እንደምትከተልና ከቤጂንግ የሚመጣን ማንኛውንም ዓይነት ጣልቃ ገብነትም ሆነ ድጋፍ እንደማትጠብቅ በግልጽ አመልክተዋል።
በአሜሪካ እና በቻይና መካከል ያለው ግንኙነት በንግድ ጦርነትና በጂኦ-ፖለቲካዊ ጉዳዮች ሳቢያ ውጥረት ውስጥ ባለበት በዚህ ወቅት፣ የትራምፕ ንግግር ዋሽንግተን በመካከለኛው ምስራቅ ያላትን የበላይነት ለማሳየትና የግሏን የኃይል እርምጃ ለመውሰድ ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑ ተነግሯል። አል አራቢያ እንደዘገበው፣ ይህ የፕሬዝዳንቱ ግልጽ አቋም በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲው መድረክ ከፍተኛ ትኩረትን ስቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#trump #usa #iran #china #geopolitics #xijinping #whitehouse #internationalnews #alarabiya #diplomacy
#ethiopia | የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዋሽንግተን ከቴህራን ጋር ለገባችበት ዲፕሎማሲያዊ እና ፖለቲካዊ ፍጥጫ የቻይናው ፕሬዝዳንት ዢ ጂንፒንግ እርዳታ እንደማያስፈልጋቸው በይፋ አስታወቁ።
ዛሬ ለጋዜጠኞች መግለጫ የሰጡት ፕሬዝዳንቱ፣ አሜሪካ በኢራን ጉዳይ ላይ የራሷን የውሳኔ አቅጣጫ እንደምትከተልና ከቤጂንግ የሚመጣን ማንኛውንም ዓይነት ጣልቃ ገብነትም ሆነ ድጋፍ እንደማትጠብቅ በግልጽ አመልክተዋል።
በአሜሪካ እና በቻይና መካከል ያለው ግንኙነት በንግድ ጦርነትና በጂኦ-ፖለቲካዊ ጉዳዮች ሳቢያ ውጥረት ውስጥ ባለበት በዚህ ወቅት፣ የትራምፕ ንግግር ዋሽንግተን በመካከለኛው ምስራቅ ያላትን የበላይነት ለማሳየትና የግሏን የኃይል እርምጃ ለመውሰድ ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑ ተነግሯል። አል አራቢያ እንደዘገበው፣ ይህ የፕሬዝዳንቱ ግልጽ አቋም በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲው መድረክ ከፍተኛ ትኩረትን ስቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#trump #usa #iran #china #geopolitics #xijinping #whitehouse #internationalnews #alarabiya #diplomacy
3 months ago
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው ጦርነት ሊያበቃ ነው? አዲሱ ስምምነት ምን ይዟል?
********************
ኢራን ከአሜሪካ የቀረበላትን አዲስ የውሳኔ ሃሳብ እየመረመረች መሆኑን ያስታወቀች ሲሆን፣ ሁለቱ ወገኖች በባህረ ሰላጤው ያለውን ጦርነት በይፋ ለማቆም በሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ላይ ለመስማማት መቃረባቸው ተሰምቷል።
የፓኪስታን እና ሌሎች ከሽምግልና ሂደቱ ጋር ግንኙነት ያላቸው ምንጮች እንደገለጹት፣ ስምምነቱ ጦርነቱን የሚገታ ባለ 14 ነጥብ የውሳኔ ሃሳብ የያዘ ነው።
ይህ የአንድ ገጽ ሰነድ እንደ የኑክሌር መርሃ ግብር ያሉ ውስብስብ ጉዳዮችን ለጊዜው ወደ ጎን በመተው፣ ይልቁንም በሆርሙዝ የባህር ሰርጥ በኩል ያለውን የመርከብ ጉዞ መክፈት፣ በኢራን ላይ የተጣሉ ማዕቀቦችን ማንሳት እና በቀጣይ ውይይቶች በኑክሌር መርሃ ግብሩ ላይ ገደቦችን ስለማድረግ በሚሉ ነጥቦች ላይ ትኩረት ያደርጋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ፣ ሀገራቸው አቋሟን በሽምግልናው ግንባር ቀደም ሚና ባላት ፓኪስታን በኩል የምታሳውቅ መሆኑን ተናግረዋል።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በማህበራዊ ሚዲያ ባሰፈሩት ጽሑፍ "ኢራን በተስማማንበት ጉዳይ ላይ ከተስማማች" ጦርነቱ ሊያበቃ እንደሚችል የገለጹ ቢሆንም፣ ስምምነት ለመፈረም ፊት ለፊት ለመገናኘት ግን ገና መሆኑን ለኒውዮርክ ፖስት ተናግረዋል።
በሌላ በኩል የአሜሪካ ወታደራዊ አጋር የሆነችው እስራኤል ስለ ስምምነቱ መቃረብ መረጃው እንደሌላት ገልጻ፣ ለተጨማሪ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ዝግጅት እያደረገች መሆኑን አስታውቃለች።
በመሀመድ ፊጣሞ
#ebc #iran #usa #peacedeal #donaldtrump #gulfwar #worldpolitics
********************
ኢራን ከአሜሪካ የቀረበላትን አዲስ የውሳኔ ሃሳብ እየመረመረች መሆኑን ያስታወቀች ሲሆን፣ ሁለቱ ወገኖች በባህረ ሰላጤው ያለውን ጦርነት በይፋ ለማቆም በሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ላይ ለመስማማት መቃረባቸው ተሰምቷል።
የፓኪስታን እና ሌሎች ከሽምግልና ሂደቱ ጋር ግንኙነት ያላቸው ምንጮች እንደገለጹት፣ ስምምነቱ ጦርነቱን የሚገታ ባለ 14 ነጥብ የውሳኔ ሃሳብ የያዘ ነው።
ይህ የአንድ ገጽ ሰነድ እንደ የኑክሌር መርሃ ግብር ያሉ ውስብስብ ጉዳዮችን ለጊዜው ወደ ጎን በመተው፣ ይልቁንም በሆርሙዝ የባህር ሰርጥ በኩል ያለውን የመርከብ ጉዞ መክፈት፣ በኢራን ላይ የተጣሉ ማዕቀቦችን ማንሳት እና በቀጣይ ውይይቶች በኑክሌር መርሃ ግብሩ ላይ ገደቦችን ስለማድረግ በሚሉ ነጥቦች ላይ ትኩረት ያደርጋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ፣ ሀገራቸው አቋሟን በሽምግልናው ግንባር ቀደም ሚና ባላት ፓኪስታን በኩል የምታሳውቅ መሆኑን ተናግረዋል።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በማህበራዊ ሚዲያ ባሰፈሩት ጽሑፍ "ኢራን በተስማማንበት ጉዳይ ላይ ከተስማማች" ጦርነቱ ሊያበቃ እንደሚችል የገለጹ ቢሆንም፣ ስምምነት ለመፈረም ፊት ለፊት ለመገናኘት ግን ገና መሆኑን ለኒውዮርክ ፖስት ተናግረዋል።
በሌላ በኩል የአሜሪካ ወታደራዊ አጋር የሆነችው እስራኤል ስለ ስምምነቱ መቃረብ መረጃው እንደሌላት ገልጻ፣ ለተጨማሪ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ዝግጅት እያደረገች መሆኑን አስታውቃለች።
በመሀመድ ፊጣሞ
#ebc #iran #usa #peacedeal #donaldtrump #gulfwar #worldpolitics
3 months ago
በሆርሙዝ የባህር ሰርጥ የኢራን ስልታዊ የበላይነት እየተዳከመ መሆኑ ተገለጸ
#ethiopia | የባህር ላይ ደህንነት ተንታኞች እንደሚሉት፣ አሜሪካ በሆርሙዝ የባህር ሰርጥ በኩል የንግድ መርከቦችን በሃይል ማሳለፍ መቻሏ፣ ኢራን በቀጠናው ላይ የነበራትን የቁጥጥርና የመደራደር አቅም ጥያቄ ውስጥ ጥሎታል። ዋሽንግተን በባህረ ሰርጡ አዲስ የመተላለፊያ መንገድ መክፈቷን ተከትሎ፣ ወታደራዊና ስልታዊ ድል መቀዳጀቷ እየተነገረ ይገኛል።
ኢራን በስልታዊ የበላይነት መዳከሟ ተስፋ በመቁረጥ፣ እንደ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ባሉ የቀጠናው አጋር ሀገራት ላይ ጥቃት ልትሰነዝር ትችላለች የሚሉ ስጋቶች ተነስተዋል። ይሁን እንጂ የቴህራን ባለስልጣናት ለፖለቲካዊ ቀውሶች ወታደራዊ መፍትሄ እንደሌለ በመግለጽ የሚከተሉትን ነጥቦች አጽንኦት ሰጥተዋል፡-
አሜሪካ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በሌሎች ሀገራት ግፊት ወደማይወጡበት የጦርነት አረንቋ እንዳይገቡ።
ኢራን በኤምሬትስ ላይ የተሰነዘሩ ጥቃቶችን ባታረጋግጥም፣ ለዲፕሎማሲያዊ ንግግሮች በሯ ክፍት መሆኑን ገልጻለች።
የጎረቤት ሀገር ፓኪስታን በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለውን ልዩነት ለማጥበብና ውጥረቱን ለማርገብ ከፍተኛ ጥረት እያደረገች መሆኑ ተመላክቷል።
ይህ በአሜሪካ የሚመራው አዲስ የባህር ላይ እንቅስቃሴ፣ ለዓመታት የዓለምን የነዳጅ አቅርቦት መተላለፊያ በቁጥጥሯ ስር አድርጋ ለቆየችው ኢራን ትልቅ ፈተና እንደሚሆንባት ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#iran #usa #hormuzstrait #geopolitics #middleeast #maritimesecurity #diplomacy
#ethiopia | የባህር ላይ ደህንነት ተንታኞች እንደሚሉት፣ አሜሪካ በሆርሙዝ የባህር ሰርጥ በኩል የንግድ መርከቦችን በሃይል ማሳለፍ መቻሏ፣ ኢራን በቀጠናው ላይ የነበራትን የቁጥጥርና የመደራደር አቅም ጥያቄ ውስጥ ጥሎታል። ዋሽንግተን በባህረ ሰርጡ አዲስ የመተላለፊያ መንገድ መክፈቷን ተከትሎ፣ ወታደራዊና ስልታዊ ድል መቀዳጀቷ እየተነገረ ይገኛል።
ኢራን በስልታዊ የበላይነት መዳከሟ ተስፋ በመቁረጥ፣ እንደ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ባሉ የቀጠናው አጋር ሀገራት ላይ ጥቃት ልትሰነዝር ትችላለች የሚሉ ስጋቶች ተነስተዋል። ይሁን እንጂ የቴህራን ባለስልጣናት ለፖለቲካዊ ቀውሶች ወታደራዊ መፍትሄ እንደሌለ በመግለጽ የሚከተሉትን ነጥቦች አጽንኦት ሰጥተዋል፡-
አሜሪካ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በሌሎች ሀገራት ግፊት ወደማይወጡበት የጦርነት አረንቋ እንዳይገቡ።
ኢራን በኤምሬትስ ላይ የተሰነዘሩ ጥቃቶችን ባታረጋግጥም፣ ለዲፕሎማሲያዊ ንግግሮች በሯ ክፍት መሆኑን ገልጻለች።
የጎረቤት ሀገር ፓኪስታን በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለውን ልዩነት ለማጥበብና ውጥረቱን ለማርገብ ከፍተኛ ጥረት እያደረገች መሆኑ ተመላክቷል።
ይህ በአሜሪካ የሚመራው አዲስ የባህር ላይ እንቅስቃሴ፣ ለዓመታት የዓለምን የነዳጅ አቅርቦት መተላለፊያ በቁጥጥሯ ስር አድርጋ ለቆየችው ኢራን ትልቅ ፈተና እንደሚሆንባት ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#iran #usa #hormuzstrait #geopolitics #middleeast #maritimesecurity #diplomacy
3 months ago
ኢራን ቻይና ገባች
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ በመጣው ውጥረትና በዓለም አቀፉ የነዳጅ ገበያ ላይ የተደቀነውን ስጋት ተከትሎ፣ የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቅቺ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ወደ ቤጂንግ ማቅናታቸው ተሰማ።
ሚኒስትሩ ከቻይናው አቻቸው ዋንግ ዪ ጋር የሚያደርጉት ይኸው ምክክር፣ በአሜሪካ እና በእስራኤል ጥምር ጥቃት ሳቢያ በነዳጅ ማምረቻ ተቋማት ላይ ጉዳት ደርሶ፣ የዓለም የነዳጅ አቅርቦት መስመር ከፍተኛ መናጋት በገጠመው ወቅት የተደረገ በመሆኑ ልዩ ዲፕሎማሲያዊ ትርጉም ተሰጥቶታል።
የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፣ የሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ የዲፕሎማሲ መሪዎች በዋናነት ቀጣላዊና ዓለም አቀፋዊ ወቅታዊ ሁኔታዎች እንዲሁም በጸጥታ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት እንደሚያደርጉ አመልክቷል። ቻይና በበኩሏ ጉብኝቱ በነገው ዕለት እንደሚከናወን አረጋግጣለች።
ይህ ጉብኝት ኢራን ከምስራቁ ኃያል ሀገር ቻይና ጋር ያለውን ስትራቴጂካዊ ትብብር በማጠናከር፣ በምዕራባውያን የሚሰነዘርባትን ጫና ለመቋቋም እና በነዳጅ ገበያው ላይ የተፈጠረውን አለመረጋጋት በጋራ ለመፍታት የምታደርገው ጥረት አካል ተደርጎ ተወስዷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#iran #china #diplomacy #oilmarket #abbasaraghchi #middleeast #geopolitics #new
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ በመጣው ውጥረትና በዓለም አቀፉ የነዳጅ ገበያ ላይ የተደቀነውን ስጋት ተከትሎ፣ የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቅቺ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ወደ ቤጂንግ ማቅናታቸው ተሰማ።
ሚኒስትሩ ከቻይናው አቻቸው ዋንግ ዪ ጋር የሚያደርጉት ይኸው ምክክር፣ በአሜሪካ እና በእስራኤል ጥምር ጥቃት ሳቢያ በነዳጅ ማምረቻ ተቋማት ላይ ጉዳት ደርሶ፣ የዓለም የነዳጅ አቅርቦት መስመር ከፍተኛ መናጋት በገጠመው ወቅት የተደረገ በመሆኑ ልዩ ዲፕሎማሲያዊ ትርጉም ተሰጥቶታል።
የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፣ የሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ የዲፕሎማሲ መሪዎች በዋናነት ቀጣላዊና ዓለም አቀፋዊ ወቅታዊ ሁኔታዎች እንዲሁም በጸጥታ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት እንደሚያደርጉ አመልክቷል። ቻይና በበኩሏ ጉብኝቱ በነገው ዕለት እንደሚከናወን አረጋግጣለች።
ይህ ጉብኝት ኢራን ከምስራቁ ኃያል ሀገር ቻይና ጋር ያለውን ስትራቴጂካዊ ትብብር በማጠናከር፣ በምዕራባውያን የሚሰነዘርባትን ጫና ለመቋቋም እና በነዳጅ ገበያው ላይ የተፈጠረውን አለመረጋጋት በጋራ ለመፍታት የምታደርገው ጥረት አካል ተደርጎ ተወስዷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#iran #china #diplomacy #oilmarket #abbasaraghchi #middleeast #geopolitics #new
3 months ago
ዩናይትድ ስቴትስ የኢራን የባህር ኃይል ንብረት የሆኑ ሰባት ጀልባዎችን መታ መጣሏን አስታወቀች
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት ዳግም ማገርሸቱን ተከትሎ የኢራን ወታደራዊ ኃይሎች በሆርሙዝ ወሽመጥና በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች አቅራቢያ በሚንቀሳቀሱ መርከቦች ላይ የሚሳይልና የሰው አልባ አውሮፕላን ጥቃት ሰንዝረዋል።
ለዚህ ትንኮሳ አፋጣኝ ምላሽ የሰጡት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ጦር በንግድ መርከቦች ላይ እንቅፋት ለመፍጠር የሞከሩ ሰባት የኢራን ትናንሽ የጦር ጀልባዎችን ማውደሙን ይፋ አድርገዋል።
ይህ እርምጃ የተወሰደው ሁለቱ ሀገራት ደርሰውበት የነበረውን የተኩስ አቁም ስምምነት ኢራን መጣሷን ተከትሎ ሲሆን አሜሪካ ፕሮጀክት ፍሪደም በሚሰኘው የባህር ላይ ዘመቻዋ አማካኝነት በወሽመጡ ላይ ያላትን ጥበቃ አጠናክራ ቀጥላለች።
በጉዳዩ ላይ መግለጫ የሰጡት የኢራን ፓርላማ አፈ ጉባኤና ዋና ተደራዳሪ ሞሃመድ ባቄር ጋሊባፍ ሀገራቸው በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ የምታደርገው እንቅስቃሴ ገና ጅምር መሆኑን በመጥቀስ ማስፈራሪያ ሰጥተዋል።
አፈ ጉባኤው የአሜሪካና የባልደረቦቿ በወሽመጡ መገኘት ለአካባቢው ስጋት መሆኑን ገልጸው የአሜሪካ ተጽዕኖ በቅርቡ ያበቃል ብለዋል።
በሌላ በኩል ፕሬዝዳንት ትራምፕ ኢራን ያቀረበችውን ባለ አስራ አራት ነጥብ የሰላም ጥያቄ ውድቅ ለማድረግ ማቀዳቸውን ጠቁመው ሀገሪቱ ለፈጸመችው ድርጊት ተገቢውን ዋጋ እስካሁን አልከፈለችም ሲሉ ጠንከር ያለ አቋማቸውን አንጸባርቀዋል።
#usa #iran #middleeast #worldnews #maritimesecurity #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት ዳግም ማገርሸቱን ተከትሎ የኢራን ወታደራዊ ኃይሎች በሆርሙዝ ወሽመጥና በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች አቅራቢያ በሚንቀሳቀሱ መርከቦች ላይ የሚሳይልና የሰው አልባ አውሮፕላን ጥቃት ሰንዝረዋል።
ለዚህ ትንኮሳ አፋጣኝ ምላሽ የሰጡት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ጦር በንግድ መርከቦች ላይ እንቅፋት ለመፍጠር የሞከሩ ሰባት የኢራን ትናንሽ የጦር ጀልባዎችን ማውደሙን ይፋ አድርገዋል።
ይህ እርምጃ የተወሰደው ሁለቱ ሀገራት ደርሰውበት የነበረውን የተኩስ አቁም ስምምነት ኢራን መጣሷን ተከትሎ ሲሆን አሜሪካ ፕሮጀክት ፍሪደም በሚሰኘው የባህር ላይ ዘመቻዋ አማካኝነት በወሽመጡ ላይ ያላትን ጥበቃ አጠናክራ ቀጥላለች።
በጉዳዩ ላይ መግለጫ የሰጡት የኢራን ፓርላማ አፈ ጉባኤና ዋና ተደራዳሪ ሞሃመድ ባቄር ጋሊባፍ ሀገራቸው በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ የምታደርገው እንቅስቃሴ ገና ጅምር መሆኑን በመጥቀስ ማስፈራሪያ ሰጥተዋል።
አፈ ጉባኤው የአሜሪካና የባልደረቦቿ በወሽመጡ መገኘት ለአካባቢው ስጋት መሆኑን ገልጸው የአሜሪካ ተጽዕኖ በቅርቡ ያበቃል ብለዋል።
በሌላ በኩል ፕሬዝዳንት ትራምፕ ኢራን ያቀረበችውን ባለ አስራ አራት ነጥብ የሰላም ጥያቄ ውድቅ ለማድረግ ማቀዳቸውን ጠቁመው ሀገሪቱ ለፈጸመችው ድርጊት ተገቢውን ዋጋ እስካሁን አልከፈለችም ሲሉ ጠንከር ያለ አቋማቸውን አንጸባርቀዋል።
#usa #iran #middleeast #worldnews #maritimesecurity #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 months ago
“ኢራን ከምድር ገጽ ትጠፋለች!” — ዶናልድ ትራምፕ
#ethiopia | በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ እየተባባሰ የመጣውን ወታደራዊ ውጥረት ተከትሎ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለኢራን እጅግ አስደንጋጭ ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።
ከፎክስ ኒውስ ጋዜጠኛ ትሬይ ይንግስት ጋር ቆይታ ያደረጉት ትራምፕ፣ የንግድ መርከቦችን በማጀብ ላይ ባሉ የአሜሪካ የጦር መርከቦች ላይ የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ ማንኛውንም ዓይነት ጥቃት የምትሰነዝር ከሆነ ሀገሪቱ “ከምድር ገጽ እንድትጠፋ” ይደረጋል ሲሉ በከባድ ቃላት ዝተዋል።
ይህ የአሜሪካ ጠንካራ አቋም የመጣው ዋሽንግተን በስትሬቱ በኩል የሚያልፉ የነዳጅ እና የንግድ መርከቦችን በጦር መርከቦች የማጀብ (Project Freedom) ዘመቻ መጀመሯን ተከትሎ ነው።
ትራምፕ በንግግራቸው አሜሪካ በአሁኑ ወቅት እጅግ ዘመናዊ የጦር መሣሪያ የታጠቀች መሆኑን በመጥቀስ፣ ማንኛውንም ትንኮሳ ለመመከት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
በዛሬው ዕለት ብቻ የአሜሪካ ባህር ኃይል ስድስት የኢራን የፈጣን ጥቃት ጀልባዎችን ማውደሙ የተነገረ ሲሆን፣ ይህም አካባቢውን ወደ ቀጥተኛ ጦርነት ሊያስገባው ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል።
ምንም እንኳን ትራምፕ የኃይል እርምጃ ማስጠንቀቂያ ቢሰጡም፣ ኢራን በድርድር ረገድ የተሻለ አቋም እንድታሳይ ግፊት እያደረጉ መሆኑን ጠቁመዋል።
በአሁኑ ወቅት የፔንታጎን እና የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ሁኔታውን በቅርበት እየተከታተሉ ሲሆን፣ ተጨማሪ መግለጫዎች እንደሚሰጡ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #መናኸሪያfm #trump #iran #straitofhormuz #breakingnews #ethiopia #amharicnewsm
#ethiopia | በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ እየተባባሰ የመጣውን ወታደራዊ ውጥረት ተከትሎ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለኢራን እጅግ አስደንጋጭ ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።
ከፎክስ ኒውስ ጋዜጠኛ ትሬይ ይንግስት ጋር ቆይታ ያደረጉት ትራምፕ፣ የንግድ መርከቦችን በማጀብ ላይ ባሉ የአሜሪካ የጦር መርከቦች ላይ የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ ማንኛውንም ዓይነት ጥቃት የምትሰነዝር ከሆነ ሀገሪቱ “ከምድር ገጽ እንድትጠፋ” ይደረጋል ሲሉ በከባድ ቃላት ዝተዋል።
ይህ የአሜሪካ ጠንካራ አቋም የመጣው ዋሽንግተን በስትሬቱ በኩል የሚያልፉ የነዳጅ እና የንግድ መርከቦችን በጦር መርከቦች የማጀብ (Project Freedom) ዘመቻ መጀመሯን ተከትሎ ነው።
ትራምፕ በንግግራቸው አሜሪካ በአሁኑ ወቅት እጅግ ዘመናዊ የጦር መሣሪያ የታጠቀች መሆኑን በመጥቀስ፣ ማንኛውንም ትንኮሳ ለመመከት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
በዛሬው ዕለት ብቻ የአሜሪካ ባህር ኃይል ስድስት የኢራን የፈጣን ጥቃት ጀልባዎችን ማውደሙ የተነገረ ሲሆን፣ ይህም አካባቢውን ወደ ቀጥተኛ ጦርነት ሊያስገባው ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል።
ምንም እንኳን ትራምፕ የኃይል እርምጃ ማስጠንቀቂያ ቢሰጡም፣ ኢራን በድርድር ረገድ የተሻለ አቋም እንድታሳይ ግፊት እያደረጉ መሆኑን ጠቁመዋል።
በአሁኑ ወቅት የፔንታጎን እና የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ሁኔታውን በቅርበት እየተከታተሉ ሲሆን፣ ተጨማሪ መግለጫዎች እንደሚሰጡ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #መናኸሪያfm #trump #iran #straitofhormuz #breakingnews #ethiopia #amharicnewsm
Sponsored by
Surafel
3 months ago
የሆርሙዝ ሰርጥ ውጥረት ወደ አዲስ ምዕራፍ ተሸጋግሯል! #us #iran #straitofhormuz #projectfreedom #middleeastconflict #maritimesecurity
3 months ago
አሜሪካ በሆርሙዝ ሰርጥ የንግድ መርከቦችን ለማጀብ ማቀዷን ተከትሎ ኢራን ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ሰጠች
*****************
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሀገራቸው የጦር መርከቦች በሆርሙዝ ሰርጥ የሚያልፉ ገለልተኛ የውጭ ሀገራት የንግድ መርከቦችን የማጀብ እና ደኅንነት የማስጠበቅ ሥራ እንደሚጀምሩ አስታውቀዋል።
ፕሬዝዳንቱ ይህንን ጥረት "ሰብዓዊ ተግባር" ሲሉ የገለጹት ሲሆን፤ ርምጃው የተዘጋውን የውኃ መስመር ለሚያቋርጡ መርከቦች ከለላ ለመስጠት ያለመ መሆኑን አመላክተዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለእስራኤሉ የመገናኛ ብዙኃን ተቋም 'ካን ኒውስ' በሰጡት ቃል፣ ጦርነቱን ለማስቆም በቅርቡ ከኢራን የቀረበውን የሰላም ሀሳብ መርምረው ተቀባይነት የሌለው ሆኖ እንዳገኙት ተናግረዋል።
የኢራን ሀሳብ ውድቅ ቢደረግም፤ አሜሪካ ለቴህራኑ የ14 ነጥብ የውሳኔ ሃሳብ ምላሽ የሚሆን አዲስ የተሻሻለ ረቂቅ ስምምነት ማቅረቧ ተገልጿል።
ይህንን የአሜሪካን ውሳኔ ተከትሎ ኢራን በበኩሏ ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ሰጥታለች።
ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት ንግግር ምላሽ የሰጡት የኢራን ብሔራዊ ደኅንነት ኮሚሽን ምክትል ሰብሳቢ ኢብራሂም አዚዚ፤ ማንኛውም የአሜሪካ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት በሆርሙዝ የውኃ መስመር ላይ የተደረሰውን የተኩስ አቁም ስምምነት የሚጥስ ነው ብለዋል።
የአሜሪካው ዜና አውታር 'አክሲዮስ' በዘገባው እንዳመለከተው ኢራን የሆርሙዝ ሰርጥን መልሳ ለመክፈት አሜሪካ የባሕር ላይ ከበባዋን እንድታነሳና ጦርነቱ እንዲያበቃ የአንድ ወር የድርድር ጊዜ ገደብ አስቀምጣለች።
በሌላ በኩል የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (ሴንትኮም) በሆርሙዝ ሰርጥ ለሚያካሂደው ተልዕኮ ሚሳኤል አውዳሚ የጦር መርከቦችን፣ ከ100 በላይ የጦር አውሮፕላኖችን፣ ድሮኖችን እንዲሁም 15 ሺህ ወታደሮችን እንደሚያሰማራ አስታውቋል።
የመርከቦችን ደኅንነቱ በመጠበቅ ጉዞውን ወደ ነበረበት ለመመለስ የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ኃይሎች ከዛሬ ጀምሮ ለ'ፕሮጀክት ፍሪደም' ዘመቻ ተግባራዊነት ርምጃ መውሰድ እንደሚጀምሩም ተጠቁሟል።
የአሜሪካ የባሕር ኃይል ማዕከላዊ ዕዝ አዛዥ አድሚራል ብራድ ኩፐር አሜሪካ የባሕር ላይ ከበባዋን አጠናክራ እንደቀጠለች ጠቁመው፤ ለዚህ የመከላከያ ተልዕኮ የሚደረገው ጥረት ለቀጣናው ደኅንነት ወሳኝ መሆኑን አስምረውበታል።
በሀና ምንዳሁን
#us #iran #straitofhormuz #projectfreedom #middleeastconflict #maritimesecurity
*****************
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሀገራቸው የጦር መርከቦች በሆርሙዝ ሰርጥ የሚያልፉ ገለልተኛ የውጭ ሀገራት የንግድ መርከቦችን የማጀብ እና ደኅንነት የማስጠበቅ ሥራ እንደሚጀምሩ አስታውቀዋል።
ፕሬዝዳንቱ ይህንን ጥረት "ሰብዓዊ ተግባር" ሲሉ የገለጹት ሲሆን፤ ርምጃው የተዘጋውን የውኃ መስመር ለሚያቋርጡ መርከቦች ከለላ ለመስጠት ያለመ መሆኑን አመላክተዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለእስራኤሉ የመገናኛ ብዙኃን ተቋም 'ካን ኒውስ' በሰጡት ቃል፣ ጦርነቱን ለማስቆም በቅርቡ ከኢራን የቀረበውን የሰላም ሀሳብ መርምረው ተቀባይነት የሌለው ሆኖ እንዳገኙት ተናግረዋል።
የኢራን ሀሳብ ውድቅ ቢደረግም፤ አሜሪካ ለቴህራኑ የ14 ነጥብ የውሳኔ ሃሳብ ምላሽ የሚሆን አዲስ የተሻሻለ ረቂቅ ስምምነት ማቅረቧ ተገልጿል።
ይህንን የአሜሪካን ውሳኔ ተከትሎ ኢራን በበኩሏ ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ሰጥታለች።
ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት ንግግር ምላሽ የሰጡት የኢራን ብሔራዊ ደኅንነት ኮሚሽን ምክትል ሰብሳቢ ኢብራሂም አዚዚ፤ ማንኛውም የአሜሪካ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት በሆርሙዝ የውኃ መስመር ላይ የተደረሰውን የተኩስ አቁም ስምምነት የሚጥስ ነው ብለዋል።
የአሜሪካው ዜና አውታር 'አክሲዮስ' በዘገባው እንዳመለከተው ኢራን የሆርሙዝ ሰርጥን መልሳ ለመክፈት አሜሪካ የባሕር ላይ ከበባዋን እንድታነሳና ጦርነቱ እንዲያበቃ የአንድ ወር የድርድር ጊዜ ገደብ አስቀምጣለች።
በሌላ በኩል የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (ሴንትኮም) በሆርሙዝ ሰርጥ ለሚያካሂደው ተልዕኮ ሚሳኤል አውዳሚ የጦር መርከቦችን፣ ከ100 በላይ የጦር አውሮፕላኖችን፣ ድሮኖችን እንዲሁም 15 ሺህ ወታደሮችን እንደሚያሰማራ አስታውቋል።
የመርከቦችን ደኅንነቱ በመጠበቅ ጉዞውን ወደ ነበረበት ለመመለስ የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ኃይሎች ከዛሬ ጀምሮ ለ'ፕሮጀክት ፍሪደም' ዘመቻ ተግባራዊነት ርምጃ መውሰድ እንደሚጀምሩም ተጠቁሟል።
የአሜሪካ የባሕር ኃይል ማዕከላዊ ዕዝ አዛዥ አድሚራል ብራድ ኩፐር አሜሪካ የባሕር ላይ ከበባዋን አጠናክራ እንደቀጠለች ጠቁመው፤ ለዚህ የመከላከያ ተልዕኮ የሚደረገው ጥረት ለቀጣናው ደኅንነት ወሳኝ መሆኑን አስምረውበታል።
በሀና ምንዳሁን
#us #iran #straitofhormuz #projectfreedom #middleeastconflict #maritimesecurity
3 months ago
ኳሷ አሁን በአሜሪካ ሜዳ ላይ ናት - ኢራን
********************
የኢራን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ካዘም ጋሪባባዲ በሰጡት መግለጫ፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጦርነት በዘላቂነት ለመቋጨት የሚያስችል አዲስና ሁሉን አቀፍ የሰላም ዕቅድ በመካከለኛዋ ፓኪስታን በኩል ለአሜሪካ ማቅረባቸውን አስታውቀዋል።
ጋሪባባዲ "አሁን ኳሷ በአሜሪካ ሜዳ ላይ ናት፤ ዋሽንግተን በዲፕሎማሲያዊ መፍትሔ እና በግጭት ቀጣይነት መካከል መምረጥ ይኖርባታል" ሲሉ ገልጸዋል።
የኢራን መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት፣ ይህ ባለ 14 ነጥብ የሰላም ዕቅድ ቀደም ሲል አሜሪካ ላቀረበችው ባለ 9 ነጥብ ሰነድ እንደ አጸፋዊ ምላሽ የቀረበ ሲሆን፤ የደኅንነት ዋስትናን፣ የአሜሪካ ጦር ከቀጣናው እንዲወጣ፣ ማዕቀቦች እንዲነሱ እና በሊባኖስ ያለውን ጨምሮ ጦርነቱ በሁሉም ግንባሮች እንዲቆም የሚሉ ጥያቄዎችን አካትቷል።
በተጨማሪም ኢራን አሜሪካ ካሳ እንድትከፈላትና ለሆርሙዝ ሰርጥ አዲስ የሥራ ማዕቀፍ እንዲበጅ ፍላጎት እንዳላት ተገልጿል።
ይሁን እንጂ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በ"ትሩዝ ሶሻል" ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት፣ ዕቅዱን በቅርቡ እንደሚመለከቱት ቢገልጹም "ተቀባይነት ይኖረዋል ብዬ መገመት አልችልም" ሲሉ ጥርጣሬያቸውን አንጸባርቀዋል።
ትራምፕ ቀደም ሲል ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በኢራን ውሎች እንዳልረኩና “በከባድ ወታደራዊ እርምጃ እናጠፋቸዋለን" ሲሉ ማስፈራራታቸው ይታወሳል።
አሜሪካ ኢራን የኒውክሌር መርሐ ግብሯን ሙሉ በሙሉ እንድታቆም ብትጠይቅም ቴህራን ግን “ፕሮግራሜ ለሰላማዊ ዓላማ ብቻ ነው” በማለት ጥያቄውን ውድቅ አድርጋዋለች።
ይህ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው አለመግባባት በሳምንቱ የነዳጅ ዋጋ ከ2022 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድ በርሜል ከ120 ዶላር በላይ እንዲጨምር ምክንያት ሆኗል።
በጌቱ ላቀው
#iran #usa #peacetalks #donaldtrump #middleeast #geopolitics #hormuz #oilprices
********************
የኢራን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ካዘም ጋሪባባዲ በሰጡት መግለጫ፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጦርነት በዘላቂነት ለመቋጨት የሚያስችል አዲስና ሁሉን አቀፍ የሰላም ዕቅድ በመካከለኛዋ ፓኪስታን በኩል ለአሜሪካ ማቅረባቸውን አስታውቀዋል።
ጋሪባባዲ "አሁን ኳሷ በአሜሪካ ሜዳ ላይ ናት፤ ዋሽንግተን በዲፕሎማሲያዊ መፍትሔ እና በግጭት ቀጣይነት መካከል መምረጥ ይኖርባታል" ሲሉ ገልጸዋል።
የኢራን መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት፣ ይህ ባለ 14 ነጥብ የሰላም ዕቅድ ቀደም ሲል አሜሪካ ላቀረበችው ባለ 9 ነጥብ ሰነድ እንደ አጸፋዊ ምላሽ የቀረበ ሲሆን፤ የደኅንነት ዋስትናን፣ የአሜሪካ ጦር ከቀጣናው እንዲወጣ፣ ማዕቀቦች እንዲነሱ እና በሊባኖስ ያለውን ጨምሮ ጦርነቱ በሁሉም ግንባሮች እንዲቆም የሚሉ ጥያቄዎችን አካትቷል።
በተጨማሪም ኢራን አሜሪካ ካሳ እንድትከፈላትና ለሆርሙዝ ሰርጥ አዲስ የሥራ ማዕቀፍ እንዲበጅ ፍላጎት እንዳላት ተገልጿል።
ይሁን እንጂ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በ"ትሩዝ ሶሻል" ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት፣ ዕቅዱን በቅርቡ እንደሚመለከቱት ቢገልጹም "ተቀባይነት ይኖረዋል ብዬ መገመት አልችልም" ሲሉ ጥርጣሬያቸውን አንጸባርቀዋል።
ትራምፕ ቀደም ሲል ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በኢራን ውሎች እንዳልረኩና “በከባድ ወታደራዊ እርምጃ እናጠፋቸዋለን" ሲሉ ማስፈራራታቸው ይታወሳል።
አሜሪካ ኢራን የኒውክሌር መርሐ ግብሯን ሙሉ በሙሉ እንድታቆም ብትጠይቅም ቴህራን ግን “ፕሮግራሜ ለሰላማዊ ዓላማ ብቻ ነው” በማለት ጥያቄውን ውድቅ አድርጋዋለች።
ይህ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው አለመግባባት በሳምንቱ የነዳጅ ዋጋ ከ2022 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድ በርሜል ከ120 ዶላር በላይ እንዲጨምር ምክንያት ሆኗል።
በጌቱ ላቀው
#iran #usa #peacetalks #donaldtrump #middleeast #geopolitics #hormuz #oilprices
3 months ago
የአሜሪካ እና የኢራን ጦርነት አሁንም ዓለምን እያሳሰባት ነው።
#usa #iran #uspolitics #warcosts #republicanparty #middleeastconflict #globalnews #economicimpact
3 months ago
"ኢራን ያቀረበችው አዲስ የሰላም ዕቅድ አላረካኝም፦ ፕሬዚዳንት ትራምፕ
********************
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሁለት ወሩን የአሜሪካ-ኢራን ጦርነት ለማስቆም ከቴህራን የቀረበውን አዲስ የሰላም ሀሳብ ብዙም አላረካኝም በማለት ገልጸውታል።
ትራምፕ በዋይት ሀውስ በሰጡት መግለጫ፣ ኢራን ስምምነት ለማድረግ ብትፈልግም ያቀረበችው ሀሳብ ግን ተቀባይነት የሌላቸው ነጥቦች እንዳሉበት ገልጸዋል።
"ኢራን ስምምነት ትፈልጋለች፤ ምክንያቱም ወታደራዊ አቅሟ ተሟጥጧል" ያሉት ትራምፕ፣ በቀረበው ሰነድ ግን እንዳልረኩ እና ኢራን መስማማት የምትችልበት ደረጃ ላይ መሆኗን እንደሚጠራጠሩ ተናግረዋል።
በኢራን ከፍተኛ አመራሮች መካከል "ከባድ አለመግባባት" እንዳለ የገለጹት ፕሬዚዳንቱ፣ ይህም የሰላም ሂደቱን አስቸጋሪ እንዳደረገው ጠቁመዋል።
ፓኪስታን በሽምግልናዋ የቀጠለች ሲሆን፣ አዲሱን የኢራን የሰላም ሀሳብ ለአሜሪካ ያቀረቡት የፓኪስታን ባለስልጣናት ናቸው።
ትራምፕ ለፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሼህባዝ ሸሪፍ እና ለሀገሪቱ ፊልድ ማርሻል አሲም ሙኒር ያላቸውን አክብሮት ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት ያላቸው አማራጭ "ወይ ስምምነት ማድረግ ወይም ኢራንን በከባድ ወታደራዊ እርምጃ ማጥፋት" እንደሆነ ፕሬዚዳንት ትራም በግልጽ ተናግረዋል።
የዩናይትድ ስቴትስ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) ወታደራዊ አማራጮችን አጥንቶ እንዳቀረበላቸውም የተናገሩት ፕሬዚዳንቱ ከሰብዓዊነት አንጻር በቦምብ የመደብደብ እርምጃን እንደማይመርጡ ጠቁመዋል።
በነስሩ ጀማል
#middleeast #peacetalks #iran #us #trump #ebc
********************
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሁለት ወሩን የአሜሪካ-ኢራን ጦርነት ለማስቆም ከቴህራን የቀረበውን አዲስ የሰላም ሀሳብ ብዙም አላረካኝም በማለት ገልጸውታል።
ትራምፕ በዋይት ሀውስ በሰጡት መግለጫ፣ ኢራን ስምምነት ለማድረግ ብትፈልግም ያቀረበችው ሀሳብ ግን ተቀባይነት የሌላቸው ነጥቦች እንዳሉበት ገልጸዋል።
"ኢራን ስምምነት ትፈልጋለች፤ ምክንያቱም ወታደራዊ አቅሟ ተሟጥጧል" ያሉት ትራምፕ፣ በቀረበው ሰነድ ግን እንዳልረኩ እና ኢራን መስማማት የምትችልበት ደረጃ ላይ መሆኗን እንደሚጠራጠሩ ተናግረዋል።
በኢራን ከፍተኛ አመራሮች መካከል "ከባድ አለመግባባት" እንዳለ የገለጹት ፕሬዚዳንቱ፣ ይህም የሰላም ሂደቱን አስቸጋሪ እንዳደረገው ጠቁመዋል።
ፓኪስታን በሽምግልናዋ የቀጠለች ሲሆን፣ አዲሱን የኢራን የሰላም ሀሳብ ለአሜሪካ ያቀረቡት የፓኪስታን ባለስልጣናት ናቸው።
ትራምፕ ለፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሼህባዝ ሸሪፍ እና ለሀገሪቱ ፊልድ ማርሻል አሲም ሙኒር ያላቸውን አክብሮት ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት ያላቸው አማራጭ "ወይ ስምምነት ማድረግ ወይም ኢራንን በከባድ ወታደራዊ እርምጃ ማጥፋት" እንደሆነ ፕሬዚዳንት ትራም በግልጽ ተናግረዋል።
የዩናይትድ ስቴትስ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) ወታደራዊ አማራጮችን አጥንቶ እንዳቀረበላቸውም የተናገሩት ፕሬዚዳንቱ ከሰብዓዊነት አንጻር በቦምብ የመደብደብ እርምጃን እንደማይመርጡ ጠቁመዋል።
በነስሩ ጀማል
#middleeast #peacetalks #iran #us #trump #ebc
3 months ago
ኢራን የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎቿን በአሜሪካ ታደርጋለች - ፊፋ
****************
ኢራን የ2026ቱን የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎቿን በአሜሪካ እንደምታከናውን የዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ፌዴሬሽኖች ማኅበር (ፊፋ) ፕሬዚዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ በድጋሚ አረጋገጡ።
ኢንፋንቲኖ ይህንን ያስታወቁት በቫንኩቨር፣ ካናዳ መካሄድ የጀመረውን የፊፋ ጉባኤን በንግግር በከፈቱበት ወቅት ነው።
በመካከለኛው ምሥራቅ የተቀሰቀሰውን ጦርነት ተከትሎ ኢራን በካናዳ፣ ሜክሲኮ እና አሜሪካ አስተናጋጅነት በሚካሄደው የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ስለመሳተፏ ጥርጣሬ ላይ ወድቆ ነበር።
ይሁን እንጂ ኢንፋንቲኖ ለጉባኤው በሰጡት መግለጫ፣ "በመጀመሪያ ላረጋግጥላችሁ የምፈልገው ኢራን በ2026ቱ የፊፋ ዓለም ዋንጫ ላይ በእርግጠኝነት ትሳተፋለች፤ ጨዋታዎቿንም በአሜሪካ ታደርጋለች" ብለዋል።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከፊፋው ፕሬዚዳንት መግለጫ በኋላ ስለሁኔታው ተጠይቀው በሰጡት መልስ፣ “አዎ መጫወት ይችላሉ” ሲሉ መመለሳቸውን አናዶሉ ዘግቧል።
ቀደም ሲል የኢራን ባለሥልጣናት የምድብ ጨዋታዎቻቸው ከአሜሪካ ወደ ሜክሲኮ እንዲዛወሩ ጠይቀው የነበረ ቢሆንም፣ ጥያቄው በፊፋው ፕሬዚዳንት ጁሊያኒ ኢንፋንቲኖ ውድቅ ተደርጎ ነበር።
ባለፈው ሳምንት ደግሞ የጣሊያን ተወላጅ የሆኑት የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ፓውሎ ዛምፖሊ "ከዓለም ዋንጫ ተሳትፎው ኢራን ተቀንሳ ጣሊያን ትተካ" የሚል ሐሳብ አቅርበው የነበረ ቢሆንም፣ የአሜሪካ መንግሥት ከዚህ ሐሳብ ራሱን ማራቁን የዘገበው ደግሞ ቲአርቲ ነው።
የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮም የኢራን እግር ኳስ ተጫዋቾች በአሜሪካ መልካም አቀባበል እንደሚደረግላቸው መግለጻቸው ይታወሳል።
#ebc #worldcup #iran #usa #fifa
****************
ኢራን የ2026ቱን የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎቿን በአሜሪካ እንደምታከናውን የዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ፌዴሬሽኖች ማኅበር (ፊፋ) ፕሬዚዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ በድጋሚ አረጋገጡ።
ኢንፋንቲኖ ይህንን ያስታወቁት በቫንኩቨር፣ ካናዳ መካሄድ የጀመረውን የፊፋ ጉባኤን በንግግር በከፈቱበት ወቅት ነው።
በመካከለኛው ምሥራቅ የተቀሰቀሰውን ጦርነት ተከትሎ ኢራን በካናዳ፣ ሜክሲኮ እና አሜሪካ አስተናጋጅነት በሚካሄደው የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ስለመሳተፏ ጥርጣሬ ላይ ወድቆ ነበር።
ይሁን እንጂ ኢንፋንቲኖ ለጉባኤው በሰጡት መግለጫ፣ "በመጀመሪያ ላረጋግጥላችሁ የምፈልገው ኢራን በ2026ቱ የፊፋ ዓለም ዋንጫ ላይ በእርግጠኝነት ትሳተፋለች፤ ጨዋታዎቿንም በአሜሪካ ታደርጋለች" ብለዋል።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከፊፋው ፕሬዚዳንት መግለጫ በኋላ ስለሁኔታው ተጠይቀው በሰጡት መልስ፣ “አዎ መጫወት ይችላሉ” ሲሉ መመለሳቸውን አናዶሉ ዘግቧል።
ቀደም ሲል የኢራን ባለሥልጣናት የምድብ ጨዋታዎቻቸው ከአሜሪካ ወደ ሜክሲኮ እንዲዛወሩ ጠይቀው የነበረ ቢሆንም፣ ጥያቄው በፊፋው ፕሬዚዳንት ጁሊያኒ ኢንፋንቲኖ ውድቅ ተደርጎ ነበር።
ባለፈው ሳምንት ደግሞ የጣሊያን ተወላጅ የሆኑት የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ፓውሎ ዛምፖሊ "ከዓለም ዋንጫ ተሳትፎው ኢራን ተቀንሳ ጣሊያን ትተካ" የሚል ሐሳብ አቅርበው የነበረ ቢሆንም፣ የአሜሪካ መንግሥት ከዚህ ሐሳብ ራሱን ማራቁን የዘገበው ደግሞ ቲአርቲ ነው።
የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮም የኢራን እግር ኳስ ተጫዋቾች በአሜሪካ መልካም አቀባበል እንደሚደረግላቸው መግለጻቸው ይታወሳል።
#ebc #worldcup #iran #usa #fifa
3 months ago
በአሜሪካ ተይዘው ከነበሩት የኢራን መርከብ ሠራተኞች መካከል ስድስቱ ተለቀቁ
*****************
በቅርቡ በአሜሪካ ባሕር ኃይል ተይዛ ከነበረችውና ‘ቱስካ’ (Touska) ከተሰኘችው የኢራን የጭነት መርከብ ላይ ስድስት ሰራተኞች ተለቀው ወደ አገራቸው መመለሳቸውን የኢራኑ ታስኒም የዜና ወኪል ዘግቧል።
አሁንም በአሜሪካ ቁጥጥር ሥር የሚገኙት ቀሪዎቹ 22 ሰራተኞች እንዲለቀቁ የኢራን ባለስልጣናት ጥረት እያደረጉ መሆኑን የዜና ምንጩ አክሎ ገልጿል።
አሜሪካ መርከቧን የያዘችው እ.አ.አ በኤፕሪል 20 ሲሆን፣ ምክንያቱ ደግሞ መርከቧ "የሆርሙዝ የባሕር መስመርን ለቃ እንድትወጣ የተሰጣትን ትዕዛዝ ባለማክበሯ ነው" ተብሏል።
ኢራን የሆርሙዝ የባሕር መስመርን መዝጋቷን ተከትሎ፣ አሜሪካም ከአፕሪል 13 ጀምሮ በኢራን ላይ የባሕር እገዳ ጥላ ትገኛለች።
#middleeast #us #iran #hormuz #touska #ebc
*****************
በቅርቡ በአሜሪካ ባሕር ኃይል ተይዛ ከነበረችውና ‘ቱስካ’ (Touska) ከተሰኘችው የኢራን የጭነት መርከብ ላይ ስድስት ሰራተኞች ተለቀው ወደ አገራቸው መመለሳቸውን የኢራኑ ታስኒም የዜና ወኪል ዘግቧል።
አሁንም በአሜሪካ ቁጥጥር ሥር የሚገኙት ቀሪዎቹ 22 ሰራተኞች እንዲለቀቁ የኢራን ባለስልጣናት ጥረት እያደረጉ መሆኑን የዜና ምንጩ አክሎ ገልጿል።
አሜሪካ መርከቧን የያዘችው እ.አ.አ በኤፕሪል 20 ሲሆን፣ ምክንያቱ ደግሞ መርከቧ "የሆርሙዝ የባሕር መስመርን ለቃ እንድትወጣ የተሰጣትን ትዕዛዝ ባለማክበሯ ነው" ተብሏል።
ኢራን የሆርሙዝ የባሕር መስመርን መዝጋቷን ተከትሎ፣ አሜሪካም ከአፕሪል 13 ጀምሮ በኢራን ላይ የባሕር እገዳ ጥላ ትገኛለች።
#middleeast #us #iran #hormuz #touska #ebc
Sponsored by
Surafel
3 months ago
"ፓኪስታን ገለልተኛ አይደለችም" በቴህራንና በዋሽንግተን ድርድር ላይ አዲስ ውዝግብ
#ethiopia | የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ በኦማንና በፓኪስታን እያደረጉት ያለው የዲፕሎማሲ "ጥረት" በሀገር ቤት ተቃውሞ ገጠመው። የኢራን ብሔራዊ ደህንነትና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ኮሚሽን ቃል አቀባይ ኢብራሂም ሬዛኢ፤ ፓኪስታን በአሜሪካና በኢራን መካከል ለሚደረገው ድርድር "ትክክለኛ አስታራቂ አይደለችም" ሲሉ በግልጽ ተናግረዋል።
እንደ ሬዛኢ ገለጻ፣ ፓኪስታን ለሽምግልና የሚያስፈልገው ተዓማኒነትና ገለልተኝነት ይጎድላታል።
የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ ከሰሞኑ በኢስላማባድ ከጠቅላይ ሚኒስትር ሼህባዝ ሻሪፍ ጋር ተወያይተዋል። ይሁን እንጂ ኢብራሂም ሬዛኢ በኤክስ (X) ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ጠንከር ያለ መልዕክት የሚከተሉትን ነጥቦች አንስተዋል፦
ፓኪስታን ምንም እንኳ ጥሩ ጎረቤት ብትሆንም፣ ለዋሽንግተን ስለምታደላ ለድርድር ምቹ አይደለችም።
ፓኪስታን አሜሪካን በግልጽ ከመተቸት ትቆጠባለች፤ ይህም ከአስታራቂነት ባህሪ ጋር ይጋጫል።
አሜሪካ በሊባኖስ ጉዳይና በታገዱ የኢራን ንብረቶች ላይ የገባችውን ቃል እንድትፈጽም ፓኪስታን አስፈላጊውን ተፅዕኖ አልፈጠረችም።
የኢራን ሚዲያዎች እንደሚጠቁሙት፣ የሰላም ድርድሩ ከኑክሌር ፋይል በዘለለ ስሱና ወሳኝ የሆኑ ጉዳዮችን አካቷል፦
፦ አዲስ የህግ ማዕቀፍ ማዘጋጀት።
፦ ኢራን ላለፉት ዓመታት ለደረሰባት ኪሳራ ካሳ መጠየቅ።
፦ ተጨማሪ ወታደራዊ እርምጃዎች እንዳይወሰዱ ዋስትና ማግኘት።
፦ በአሜሪካ የተጣሉ የባህር ላይ ገደቦችን ማንሳት።
በአንድ በኩል ሚኒስትር አራግቺ በኢስላማባድና በሙስካት የዲፕሎማሲ ደጃፎችን ሲያንኳኩ፣ በሌላ በኩል በቴህራን ያሉ ህግ አውጪዎች የአደራዳሪውን ማንነት ጥያቄ ውስጥ መክተታቸው ድርድሩን ምን ያህል ውስብስብ እንደሚያደርገው አመላካች ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ኢራን #ፓኪስታን #አሜሪካ #ዲፕሎማሲ #የሰላምድርድር #መካከለኛው ምስራቅ #ዜና #iran #pakistan #usa
#ethiopia | የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ በኦማንና በፓኪስታን እያደረጉት ያለው የዲፕሎማሲ "ጥረት" በሀገር ቤት ተቃውሞ ገጠመው። የኢራን ብሔራዊ ደህንነትና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ኮሚሽን ቃል አቀባይ ኢብራሂም ሬዛኢ፤ ፓኪስታን በአሜሪካና በኢራን መካከል ለሚደረገው ድርድር "ትክክለኛ አስታራቂ አይደለችም" ሲሉ በግልጽ ተናግረዋል።
እንደ ሬዛኢ ገለጻ፣ ፓኪስታን ለሽምግልና የሚያስፈልገው ተዓማኒነትና ገለልተኝነት ይጎድላታል።
የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ ከሰሞኑ በኢስላማባድ ከጠቅላይ ሚኒስትር ሼህባዝ ሻሪፍ ጋር ተወያይተዋል። ይሁን እንጂ ኢብራሂም ሬዛኢ በኤክስ (X) ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት ጠንከር ያለ መልዕክት የሚከተሉትን ነጥቦች አንስተዋል፦
ፓኪስታን ምንም እንኳ ጥሩ ጎረቤት ብትሆንም፣ ለዋሽንግተን ስለምታደላ ለድርድር ምቹ አይደለችም።
ፓኪስታን አሜሪካን በግልጽ ከመተቸት ትቆጠባለች፤ ይህም ከአስታራቂነት ባህሪ ጋር ይጋጫል።
አሜሪካ በሊባኖስ ጉዳይና በታገዱ የኢራን ንብረቶች ላይ የገባችውን ቃል እንድትፈጽም ፓኪስታን አስፈላጊውን ተፅዕኖ አልፈጠረችም።
የኢራን ሚዲያዎች እንደሚጠቁሙት፣ የሰላም ድርድሩ ከኑክሌር ፋይል በዘለለ ስሱና ወሳኝ የሆኑ ጉዳዮችን አካቷል፦
፦ አዲስ የህግ ማዕቀፍ ማዘጋጀት።
፦ ኢራን ላለፉት ዓመታት ለደረሰባት ኪሳራ ካሳ መጠየቅ።
፦ ተጨማሪ ወታደራዊ እርምጃዎች እንዳይወሰዱ ዋስትና ማግኘት።
፦ በአሜሪካ የተጣሉ የባህር ላይ ገደቦችን ማንሳት።
በአንድ በኩል ሚኒስትር አራግቺ በኢስላማባድና በሙስካት የዲፕሎማሲ ደጃፎችን ሲያንኳኩ፣ በሌላ በኩል በቴህራን ያሉ ህግ አውጪዎች የአደራዳሪውን ማንነት ጥያቄ ውስጥ መክተታቸው ድርድሩን ምን ያህል ውስብስብ እንደሚያደርገው አመላካች ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ኢራን #ፓኪስታን #አሜሪካ #ዲፕሎማሲ #የሰላምድርድር #መካከለኛው ምስራቅ #ዜና #iran #pakistan #usa
3 months ago
"ተጨዋቾቹ ይምጡ፤ አብዮታዊ ዘቡ ግን እዛው ይቆይ"
#ethiopia | አሜሪካ በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ላይ ለሚሳተፈው የኢራን ብሔራዊ ቡድን ግልጽ የሆነ የ"ይለፍ" እና የ"ክልከላ" መስመር አስመረቀች። የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርክ ሩቢዮ በሰጡት መግለጫ፣ ዋሽንግተን የኢራን ተጨዋቾች በዓለም ዋንጫው ላይ እንዳይሳተፉ የማገድ ፍላጎት እንደሌላት አስታውቀዋል።
ሚኒስትር ሩቢዮ እንደገለጹት፣ የአሜሪካ ዋነኛ ስጋት ተጨዋቾቹ ሳይሆኑ ከኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ጋር ግንኙነት ያላቸው ግለሰቦች ናቸው። "የእኛ ችግር ስፖርተኞቹ አይደሉም" ያሉት ሚኒስትሩ፣ የአብዮታዊ ዘቡ አባላት እንደ ጋዜጠኛ፣ አሰልጣኝ ወይም የቡድን አባላት ተመስለው ወደ አሜሪካ መግባት እንደማይችሉ በጠንካራ ቃላት አስገንዝበዋል።
ከሚኒስትሩ ጎን የነበሩት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ አስተዳደራቸው በፖለቲካዊ ምክንያቶች በስፖርተኞቹ ላይ ጫና ማሳደር እንደማይፈልግ ገልጸዋል። ይህ መግለጫ ባለፈው የካቲት 28 በአሜሪካ እና እስራኤል የጋራ ጥቃት የተከፈተባት ኢራን፣ በዓለም ዋንጫው ላይ ያላት ተሳትፎ አጠራጣሪ በሆነበት ወቅት የተሰጠ ነው።
ምንም እንኳን በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ውጥረት ከፍተኛ ቢሆንም፣ የኢራን መንግስት ቃል አቀባይ ፋቴሜህ ሞሃጀራኒ ሀገራቸው ለውድድሩ አስፈላጊውን ዝግጅት ማጠናቀቋን አረጋግጠዋል። የኢራን ወጣቶች እና ስፖርት ሚኒስቴር ቡድኑ በውድድሩ ላይ እንዲሳተፍ አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ መሆኑ ተገልጿል።
ኢራን በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ በምድብ ጨዋታዎቿ ከሚከተሉት ሀገራት ጋር ትፋለማለች፦
ቤልጂየም
ግብፅ
ኒውዚላንድ
ውድድሩ በፈረንጆቹ ሰኔ 11 የሚጀምር ሲሆን፣ የኢራን ብሔራዊ ቡድን አባላት ወደ አሜሪካ በሚያደርጉት ጉዞ ላይ የቪዛ እና የደህንነት ምርመራው ጥብቅ እንደሚሆን ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#worldcup2026 #usa #iran #football #internationalrelations #marcorubio #fifa
#ethiopia | አሜሪካ በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ላይ ለሚሳተፈው የኢራን ብሔራዊ ቡድን ግልጽ የሆነ የ"ይለፍ" እና የ"ክልከላ" መስመር አስመረቀች። የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርክ ሩቢዮ በሰጡት መግለጫ፣ ዋሽንግተን የኢራን ተጨዋቾች በዓለም ዋንጫው ላይ እንዳይሳተፉ የማገድ ፍላጎት እንደሌላት አስታውቀዋል።
ሚኒስትር ሩቢዮ እንደገለጹት፣ የአሜሪካ ዋነኛ ስጋት ተጨዋቾቹ ሳይሆኑ ከኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ጋር ግንኙነት ያላቸው ግለሰቦች ናቸው። "የእኛ ችግር ስፖርተኞቹ አይደሉም" ያሉት ሚኒስትሩ፣ የአብዮታዊ ዘቡ አባላት እንደ ጋዜጠኛ፣ አሰልጣኝ ወይም የቡድን አባላት ተመስለው ወደ አሜሪካ መግባት እንደማይችሉ በጠንካራ ቃላት አስገንዝበዋል።
ከሚኒስትሩ ጎን የነበሩት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ አስተዳደራቸው በፖለቲካዊ ምክንያቶች በስፖርተኞቹ ላይ ጫና ማሳደር እንደማይፈልግ ገልጸዋል። ይህ መግለጫ ባለፈው የካቲት 28 በአሜሪካ እና እስራኤል የጋራ ጥቃት የተከፈተባት ኢራን፣ በዓለም ዋንጫው ላይ ያላት ተሳትፎ አጠራጣሪ በሆነበት ወቅት የተሰጠ ነው።
ምንም እንኳን በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ውጥረት ከፍተኛ ቢሆንም፣ የኢራን መንግስት ቃል አቀባይ ፋቴሜህ ሞሃጀራኒ ሀገራቸው ለውድድሩ አስፈላጊውን ዝግጅት ማጠናቀቋን አረጋግጠዋል። የኢራን ወጣቶች እና ስፖርት ሚኒስቴር ቡድኑ በውድድሩ ላይ እንዲሳተፍ አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ መሆኑ ተገልጿል።
ኢራን በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ በምድብ ጨዋታዎቿ ከሚከተሉት ሀገራት ጋር ትፋለማለች፦
ቤልጂየም
ግብፅ
ኒውዚላንድ
ውድድሩ በፈረንጆቹ ሰኔ 11 የሚጀምር ሲሆን፣ የኢራን ብሔራዊ ቡድን አባላት ወደ አሜሪካ በሚያደርጉት ጉዞ ላይ የቪዛ እና የደህንነት ምርመራው ጥብቅ እንደሚሆን ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#worldcup2026 #usa #iran #football #internationalrelations #marcorubio #fifa
3 months ago
''ኢራንን አንተካም!" — ጣልያን
#ethiopia | ፊፋ ኢራንን ከዓለም ዋንጫ አስወግዶ በምትኳ ጣልያንን እንዲያስገባ ያቀረቡት ጥያቄ በራሷ በጣልያን መንግሥትና በስፖርት አመራሮቹ ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጠመው።
የጣልያን ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት ሉቺያኖ ቦንፊግልዮ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ጠንከር ያለ ምላሽ፣ ጣልያን በሜዳ ላይ ባላሳየችው ውጤት በፖለቲካዊ መንገድ ወደ ዓለም ዋንጫ እንድትገባ የቀረበውን ሐሳብ እንደማይቀበሉት ገልጸዋል።
"ይሄ ከተፈጠረ እንደ ስድብ ነው የምወስደው" ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ ማንኛውም ቡድን ለዓለም ዋንጫ ማለፍ ያለበት በችሎታውና በጠንካራ ሥራው መሆን እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።
የሀገሪቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችም የኦሎምፒክ ኮሚቴውን አቋም ተጋርተዋል፦
"ይሄ አስፈላጊ አይደለም፤ ሜዳ ላይ ነው ማለፍ ያለብን" በማለት በጓሮ በር ወደ ውድድሩ የመግባት ፍላጎት እንደሌላቸው አስታውቀዋል።
የኢኮኖሚ ሚኒስትር ጂዮርጌቲ፦ ዜናው በግላቸው እንዳሳፈራቸው ገልጸው፣ "በዛ መንገድ ከሄድን አፍራለሁ" ሲሉ የሐሳቡን አሳፋሪነት ገልጸዋል።
ምንም እንኳን የጣልያን ብሔራዊ ቡድን ለ2026ቱ ዓለም ዋንጫ ባለማለፉ ደጋፊዎቿ ቢያዝኑም፣ የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ግን ከውጤት ይልቅ ለስፖርታዊ ጨዋነትና ለፍትሐዊ ውድድር ቅድሚያ በመስጠት ዓለም አቀፍ አድናቆትን እያገኙ ይገኛሉ።
ጣልያን "በችሎታችን ካላለፍን በሌላው ስንብት አንገባም" የሚል ጠንካራ መልዕክት ለዓለም አስተላልፋለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#italy #fifa #worldcup2026 #iran #footballnews #sportsmanship #fairplay #azzurri #lucianobonfiglio #andreaabodi #worldcupupdate
#ethiopia | ፊፋ ኢራንን ከዓለም ዋንጫ አስወግዶ በምትኳ ጣልያንን እንዲያስገባ ያቀረቡት ጥያቄ በራሷ በጣልያን መንግሥትና በስፖርት አመራሮቹ ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጠመው።
የጣልያን ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት ሉቺያኖ ቦንፊግልዮ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ጠንከር ያለ ምላሽ፣ ጣልያን በሜዳ ላይ ባላሳየችው ውጤት በፖለቲካዊ መንገድ ወደ ዓለም ዋንጫ እንድትገባ የቀረበውን ሐሳብ እንደማይቀበሉት ገልጸዋል።
"ይሄ ከተፈጠረ እንደ ስድብ ነው የምወስደው" ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ ማንኛውም ቡድን ለዓለም ዋንጫ ማለፍ ያለበት በችሎታውና በጠንካራ ሥራው መሆን እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።
የሀገሪቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችም የኦሎምፒክ ኮሚቴውን አቋም ተጋርተዋል፦
"ይሄ አስፈላጊ አይደለም፤ ሜዳ ላይ ነው ማለፍ ያለብን" በማለት በጓሮ በር ወደ ውድድሩ የመግባት ፍላጎት እንደሌላቸው አስታውቀዋል።
የኢኮኖሚ ሚኒስትር ጂዮርጌቲ፦ ዜናው በግላቸው እንዳሳፈራቸው ገልጸው፣ "በዛ መንገድ ከሄድን አፍራለሁ" ሲሉ የሐሳቡን አሳፋሪነት ገልጸዋል።
ምንም እንኳን የጣልያን ብሔራዊ ቡድን ለ2026ቱ ዓለም ዋንጫ ባለማለፉ ደጋፊዎቿ ቢያዝኑም፣ የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ግን ከውጤት ይልቅ ለስፖርታዊ ጨዋነትና ለፍትሐዊ ውድድር ቅድሚያ በመስጠት ዓለም አቀፍ አድናቆትን እያገኙ ይገኛሉ።
ጣልያን "በችሎታችን ካላለፍን በሌላው ስንብት አንገባም" የሚል ጠንካራ መልዕክት ለዓለም አስተላልፋለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#italy #fifa #worldcup2026 #iran #footballnews #sportsmanship #fairplay #azzurri #lucianobonfiglio #andreaabodi #worldcupupdate
3 months ago
ኢራንን በጣልያን ለመተካት እየታሰበ ነወ ተባለ
#ethiopia | በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ዋዜማ፣ የእግር ኳሱን ዓለም የሚያነጋግር አዲስ ውዝግብ ተነስቷል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ መልዕክተኛ የሆኑት ፓኦሎ ዛምፖሊ፣ ፊፋ ኢራንን ከውድድሩ ውጪ አድርጎ በምትኳ ጣልያንን እንዲያስገባ መጠየቃቸው ታውቋል።
ምንም እንኳን የጣልያን ብሔራዊ ቡድን በሜዳ ላይ በነበረው የማጣሪያ ጨዋታ ለ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ማለፍ ባይችልም፣ ዛምፖሊ ግን ፊፋ በኢራን ላይ የቅጣት እርምጃ እንዲወስድና ለጣልያን ድንገተኛ ዕድል እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበዋል። ጥያቄው በዲፕሎማሲያዊ ጫናዎች የታጀበ እንደሆነ ቢገለጽም፣ በስፖርቱ ማህበረሰብ ዘንድ ግን ግርምትን ፈጥሯል።
ለጣልያን ደጋፊዎች ይህ ትልቅ ተስፋ የሚሰጥ ቢመስልም፣ የፊፋው ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ግን ከሳምንት በፊት በሰጡት ማረጋገጫ ኢራን በውድድሩ ላይ እንደምትሳተፍ በይፋ መናገራቸው ይታወሳል።
ፊፋ እስካሁን ድረስ በፖለቲካዊ ምክንያቶች ቡድኖችን ከመተካት ይልቅ በሜዳ ላይ ለተመዘገበ ውጤት ቅድሚያ እንደሚሰጥ ይታወቃል።
ኢራን በፖለቲካዊ ምክንያቶች እንድትታገድና ጣልያን እንድትተካ የቀረበ ጥያቄ።
ቡድኑ በማጣሪያው ወድቆ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ግን በደብዳቤ የመግባት ዕድል እየተፈለገለት ነው።
ፕሬዝዳንት ኢንፋንቲኖ የኢራንን ተሳትፎ አስቀድመው አረጋግጠዋል።
ይህ ያልተጠበቀ ዲፕሎማሲያዊ ጫና በፊፋ ውሳኔ ላይ ለውጥ ያመጣ ይሆን ወይስ ኢራን በለመደችው መልኩ ጉዞዋን ትቀጥላለች? የሚለው ጉዳይ የብዙዎች መጠባበቂያ ሆኗል። ሆኖም የኳስ ወዳጆች እንደሚሉት "የሜዳ ውጤት በደብዳቤ አይቀየርም"።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #nbc
#fifa2026 #worldcup #italy #iran #gianniinfantino #footballnews #trumpenvoy #worldcupupdate #sportnews
#ethiopia | በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ዋዜማ፣ የእግር ኳሱን ዓለም የሚያነጋግር አዲስ ውዝግብ ተነስቷል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ መልዕክተኛ የሆኑት ፓኦሎ ዛምፖሊ፣ ፊፋ ኢራንን ከውድድሩ ውጪ አድርጎ በምትኳ ጣልያንን እንዲያስገባ መጠየቃቸው ታውቋል።
ምንም እንኳን የጣልያን ብሔራዊ ቡድን በሜዳ ላይ በነበረው የማጣሪያ ጨዋታ ለ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ማለፍ ባይችልም፣ ዛምፖሊ ግን ፊፋ በኢራን ላይ የቅጣት እርምጃ እንዲወስድና ለጣልያን ድንገተኛ ዕድል እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበዋል። ጥያቄው በዲፕሎማሲያዊ ጫናዎች የታጀበ እንደሆነ ቢገለጽም፣ በስፖርቱ ማህበረሰብ ዘንድ ግን ግርምትን ፈጥሯል።
ለጣልያን ደጋፊዎች ይህ ትልቅ ተስፋ የሚሰጥ ቢመስልም፣ የፊፋው ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ግን ከሳምንት በፊት በሰጡት ማረጋገጫ ኢራን በውድድሩ ላይ እንደምትሳተፍ በይፋ መናገራቸው ይታወሳል።
ፊፋ እስካሁን ድረስ በፖለቲካዊ ምክንያቶች ቡድኖችን ከመተካት ይልቅ በሜዳ ላይ ለተመዘገበ ውጤት ቅድሚያ እንደሚሰጥ ይታወቃል።
ኢራን በፖለቲካዊ ምክንያቶች እንድትታገድና ጣልያን እንድትተካ የቀረበ ጥያቄ።
ቡድኑ በማጣሪያው ወድቆ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ግን በደብዳቤ የመግባት ዕድል እየተፈለገለት ነው።
ፕሬዝዳንት ኢንፋንቲኖ የኢራንን ተሳትፎ አስቀድመው አረጋግጠዋል።
ይህ ያልተጠበቀ ዲፕሎማሲያዊ ጫና በፊፋ ውሳኔ ላይ ለውጥ ያመጣ ይሆን ወይስ ኢራን በለመደችው መልኩ ጉዞዋን ትቀጥላለች? የሚለው ጉዳይ የብዙዎች መጠባበቂያ ሆኗል። ሆኖም የኳስ ወዳጆች እንደሚሉት "የሜዳ ውጤት በደብዳቤ አይቀየርም"።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #nbc
#fifa2026 #worldcup #italy #iran #gianniinfantino #footballnews #trumpenvoy #worldcupupdate #sportnews
3 months ago
ስምንቱ ኢራናውያን ሴቶች ከሞት አፋፍ ተመለሱ!
#ethiopia | በኢራን መንግስት የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው የነበሩ ስምንት ሴት ተቃዋሚዎች፣ በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ቀጥተኛ ጣልቃ ገብነትና ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ከሞት ቅጣት መትረፋቸው በይፋ ተነገረ።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ይህንን የምስራች በማህበራዊ ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት፣ ከኢራን ባለስልጣናት ጋር ሲደረግ የነበረው ረጅም ድርድር ስኬታማ በሆነ መንገድ መጠናቀቁን አረጋግጠዋል።
እንደ ፕሬዝዳንቱ ገለጻ፣ ስምምነቱ በሁለት መልክ ተግባራዊ ሆኗል፦
አራቱ ሴቶች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳይ ከእስር እንዲፈቱ ተወስኗል።
ቀሪዎቹ አራቱ ደግሞ የነበረባቸው የሞት ፍርድ ተሰርዞ፣ በአንድ ወር ቀላል እስራት ብቻ እንዲቀጣ ተደርጓል።
ይህ ያልተጠበቀ እርምጃ ለዓመታት ሻክሮ በቆየው በአሜሪካ እና በኢራን ግንኙነት መካከል አዲስ የሰላም ተስፋ ጭሯል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለኢራን መሪዎች ምስጋናቸውን በማቅረብ፣ ይህ ውሳኔ ለወደፊት የሁለቱ ሀገራት የሰላም ድርድር እንደ "ትልቅ የመልካም ፈቃድ ማሳያ" እንደሚቆጠር ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት በመላው ዓለም የሚገኙ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ዜናውን በደስታ እየተቀበሉት ሲሆን፣ ድርጊቱ በዲፕሎማሲ አማካኝነት የሰው ልጆችን ሕይወት መታደግ እንደሚቻል ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ትራምፕ #ኢራን #የሰብዓዊመብት #ዲፕሎማሲ #ሰላም #trump #iran #humanrights #peaceagreement
#ethiopia | በኢራን መንግስት የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው የነበሩ ስምንት ሴት ተቃዋሚዎች፣ በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ቀጥተኛ ጣልቃ ገብነትና ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ከሞት ቅጣት መትረፋቸው በይፋ ተነገረ።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ይህንን የምስራች በማህበራዊ ገፃቸው ባስተላለፉት መልዕክት፣ ከኢራን ባለስልጣናት ጋር ሲደረግ የነበረው ረጅም ድርድር ስኬታማ በሆነ መንገድ መጠናቀቁን አረጋግጠዋል።
እንደ ፕሬዝዳንቱ ገለጻ፣ ስምምነቱ በሁለት መልክ ተግባራዊ ሆኗል፦
አራቱ ሴቶች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳይ ከእስር እንዲፈቱ ተወስኗል።
ቀሪዎቹ አራቱ ደግሞ የነበረባቸው የሞት ፍርድ ተሰርዞ፣ በአንድ ወር ቀላል እስራት ብቻ እንዲቀጣ ተደርጓል።
ይህ ያልተጠበቀ እርምጃ ለዓመታት ሻክሮ በቆየው በአሜሪካ እና በኢራን ግንኙነት መካከል አዲስ የሰላም ተስፋ ጭሯል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለኢራን መሪዎች ምስጋናቸውን በማቅረብ፣ ይህ ውሳኔ ለወደፊት የሁለቱ ሀገራት የሰላም ድርድር እንደ "ትልቅ የመልካም ፈቃድ ማሳያ" እንደሚቆጠር ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት በመላው ዓለም የሚገኙ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ዜናውን በደስታ እየተቀበሉት ሲሆን፣ ድርጊቱ በዲፕሎማሲ አማካኝነት የሰው ልጆችን ሕይወት መታደግ እንደሚቻል ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ትራምፕ #ኢራን #የሰብዓዊመብት #ዲፕሎማሲ #ሰላም #trump #iran #humanrights #peaceagreement
Sponsored by
Surafel
Comments