22 days ago
የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሪ ክምችት ከሪፎርሙ በፊት ከነበረው በ20 እጥፍ አድጓል
**********************
የውጭ ምንዛሪ መጠባበቂያ ክምችት በ2018 በጀት ዓመት ከፍተኛ ጭማሪ በማሳየት መጠኑ ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በፊት ከነበረው በ20 እጥፍ ማደጉን የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ አስታውቋል።
ኮሚቴው ከ7ኛ ስብሰባው በኋላ በሰጠው መግለጫ እንዳብራራው፥ በሐምሌ ወር 2016 ተግባራዊ ከተደረገው ሁሉን አቀፍ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ማግስት ሀገራችን በአጠቃላይ የውጭ ኢኮኖሚ ሚዛን ትርፍ ማስመዝገብ ችላለች።
ይህም ከሪፎርሙ በፊት ከነበረው ጉድለት አንፃር ሲታይ ዘርፉ ከፍተኛ መሻሻል ላይ መሆኑን ያመላክታል።
አጠቃላይ የማሻሻያ እርምጃዎቹ የውጭ ገበያ ተወዳዳሪነትን እና የውጭ ምንዛሪ ገቢን በማሳደግ የውጭ ኢኮኖሚ ዘርፉን ዘላቂነት እያረጋገጡ መሆኑ ተገልጿል።
በበጀት ዓመቱ የተመዘገበው የሸቀጦች ወጪ ንግድ ገቢ በሶስት እጥፍ ማደግ፣ እንዲሁም በግለሰቦች እና በመንግሥት የሃዋላ ፍሰት ላይ የታየው አበረታች መሻሻል የሸቀጦች ገቢ ንግድ መጨመርን በከፊል እንዲያካክስ ረድቶታል።
በዚህም የተነሳ በ2016 በጀት ዓመት 6.2 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ደርሶ የነበረው የሂሳብ ሚዛን ጉድለት በ2018 በጀት ዓመት ወደ 1.8 ቢሊዮን ዶላር በከፍተኛ ሁኔታ ሊቀንስ መቻሉ በመግለጫው ተጠቁሟል።
በተጨማሪም በበጀት ዓመቱ የተመዘገበው የካፒታል ሂሳብ ትርፍ ለአጠቃላይ የክፍያ ሚዛኑ መሻሻል የጎላ አስተዋፅዖ ማበርከቱ ተገልጿል።
ኮሚቴው የዓለም አቀፉን የገንዘብ ድርጅት (IMF) የሐምሌ 2018 ትንበያ ዋቢ በማድረግ እንደገመገመው፣ በመካከለኛው ምሥራቅ የተከሰተው ግጭት ቀደም ሲል ሲጠበቅ የነበረው የተረጋጋ የዓለም ኢኮኖሚ አቅጣጫ እንዲዛባ አድርጓል።
በመሆኑም ዓለም አቀፍ ዕድገት በ2026 ወደ 3.0 በመቶ እንደሚቀንስ እና በ2027 ደግሞ መጠነኛ መሻሻል በማሳየት 3.4 በመቶ እንደሚሆን ተተንብዮአል።
በተመሳሳይ፣ አጠቃላይ የዓለም የዋጋ ግሽበት በ2026 ወደ 4.7 በመቶ ጭማሪ ካሳየ በኋላ በ2027 ወደ 3.9 በመቶ ይቀንሳል ተብሎ የሚጠበቅ ቢሆንም፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የአለመረጋጋት ስጋቶች አሁንም ድረስ መቀጠላቸውን ኮሚቴው አስገንዝቧል።
#ethiopia #ebc #nationalbankofethiopia #foreignexchange #economicreform #macroeconomics #exportgrowth #imf #globaleconomy
**********************
የውጭ ምንዛሪ መጠባበቂያ ክምችት በ2018 በጀት ዓመት ከፍተኛ ጭማሪ በማሳየት መጠኑ ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በፊት ከነበረው በ20 እጥፍ ማደጉን የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ አስታውቋል።
ኮሚቴው ከ7ኛ ስብሰባው በኋላ በሰጠው መግለጫ እንዳብራራው፥ በሐምሌ ወር 2016 ተግባራዊ ከተደረገው ሁሉን አቀፍ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ማግስት ሀገራችን በአጠቃላይ የውጭ ኢኮኖሚ ሚዛን ትርፍ ማስመዝገብ ችላለች።
ይህም ከሪፎርሙ በፊት ከነበረው ጉድለት አንፃር ሲታይ ዘርፉ ከፍተኛ መሻሻል ላይ መሆኑን ያመላክታል።
አጠቃላይ የማሻሻያ እርምጃዎቹ የውጭ ገበያ ተወዳዳሪነትን እና የውጭ ምንዛሪ ገቢን በማሳደግ የውጭ ኢኮኖሚ ዘርፉን ዘላቂነት እያረጋገጡ መሆኑ ተገልጿል።
በበጀት ዓመቱ የተመዘገበው የሸቀጦች ወጪ ንግድ ገቢ በሶስት እጥፍ ማደግ፣ እንዲሁም በግለሰቦች እና በመንግሥት የሃዋላ ፍሰት ላይ የታየው አበረታች መሻሻል የሸቀጦች ገቢ ንግድ መጨመርን በከፊል እንዲያካክስ ረድቶታል።
በዚህም የተነሳ በ2016 በጀት ዓመት 6.2 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ደርሶ የነበረው የሂሳብ ሚዛን ጉድለት በ2018 በጀት ዓመት ወደ 1.8 ቢሊዮን ዶላር በከፍተኛ ሁኔታ ሊቀንስ መቻሉ በመግለጫው ተጠቁሟል።
በተጨማሪም በበጀት ዓመቱ የተመዘገበው የካፒታል ሂሳብ ትርፍ ለአጠቃላይ የክፍያ ሚዛኑ መሻሻል የጎላ አስተዋፅዖ ማበርከቱ ተገልጿል።
ኮሚቴው የዓለም አቀፉን የገንዘብ ድርጅት (IMF) የሐምሌ 2018 ትንበያ ዋቢ በማድረግ እንደገመገመው፣ በመካከለኛው ምሥራቅ የተከሰተው ግጭት ቀደም ሲል ሲጠበቅ የነበረው የተረጋጋ የዓለም ኢኮኖሚ አቅጣጫ እንዲዛባ አድርጓል።
በመሆኑም ዓለም አቀፍ ዕድገት በ2026 ወደ 3.0 በመቶ እንደሚቀንስ እና በ2027 ደግሞ መጠነኛ መሻሻል በማሳየት 3.4 በመቶ እንደሚሆን ተተንብዮአል።
በተመሳሳይ፣ አጠቃላይ የዓለም የዋጋ ግሽበት በ2026 ወደ 4.7 በመቶ ጭማሪ ካሳየ በኋላ በ2027 ወደ 3.9 በመቶ ይቀንሳል ተብሎ የሚጠበቅ ቢሆንም፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የአለመረጋጋት ስጋቶች አሁንም ድረስ መቀጠላቸውን ኮሚቴው አስገንዝቧል።
#ethiopia #ebc #nationalbankofethiopia #foreignexchange #economicreform #macroeconomics #exportgrowth #imf #globaleconomy
1 month ago
የኢትዮጵያ የማዕድን አብዮት - ከ0.2 በመቶ የኢኮኖሚ ድርሻ ወደ ዋነኛ የኢኮኖሚ ሞተርነት
*************************
የኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ ለበርካታ አሥርት ዓመታት በፖሊሲ ክፍተት፣ በሕገ-ወጥ የኮንትሮባንድ ንግድ እና በተደራጀ ብክነት ምክንያት እምቅ አቅሙ ሙሉ በሙሉ ተዘንግቶ ቆይቷል።
ዛሬ ላይ ግን በአዲሱ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ከሀገራችን 5 ዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ በመሆን ታሪካዊ ትንሣኤውን አብስሯል።
ሀገራችን ስትገነባው የቆየችው በመንግሥት ከፍተኛ ወጪ ላይ የተመሠረተ እና ለዕዳ ተጋላጭ ያደረጋት የኢኮኖሚ ሞዴል ፈታኝ ሆኖ መቆየቱ ይታወቃል።
ይህን በማክሮ ኢኮኖሚ አለመረጋጋት፣ በዋጋ ግሽበት እና በውጭ ምንዛሬ እጥረት የተተበተበ ማነቆ በዘላቂነት ለመቅረፍ የተተገበረው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ፣ ማዕድንን ከመረሳት ወደ ብሔራዊ ኢኮኖሚ አንቀሳቃሽነት በውጤታማነት አሸጋግሮታል።
ይህ መዋቅራዊ ለውጥ በመረጃ እና በቁጥር ሲመዘን እጅግ አስደናቂ ሆኖ እናገኘዋለን። በ2010 ዓ.ም የማዕድን ዘርፍ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) የነበረው ድርሻ 0.2 በመቶ ብቻ ነበረ። በ2017 ዓ.ም ይህ ቁጥር የ7 እጥፍ ብልጫ በማሳየት ወደ 1.4 በመቶ ማደግ ችሏል።
በተለይም በወርቅ ምርት እና ኤክስፖርት ላይ የታየው ለውጥ በታሪካችን ወደር የማይገኝለት እመርታ ነው።
ባህላዊ የማዕድን ቁፋሮን ወደ መደበኛ የንግድ ሥርዓት በማስገባት በተደረገው ስኬታማ የፖሊሲ ማሻሻያ፣ የሀገራችን የወርቅ ኤክስፖርት ገቢ ከ100 ሚሊዮን ዶላር ወደ 3.48 ቢሊዮን ዶላር በማደግ የ35 እጥፍ ጭማሪ አስመዝግቧል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በቅርቡ የተገበረው በገበያ ላይ የተመሠረተ የውጭ ምንዛሬ ተመን ሥርዓት ደግሞ አምራቾች ምርታቸውን በመደበኛው የፋይናንስ ሥርዓት እንዲያቀርቡ በማድረግ ለዚህ ስኬት ትልቅ ሞተር ሆኗል።
በሌላ በኩል "ኢትዮጵያ ታምርት" በተሰኘው ሀገራዊ ንቅናቄ የማዕድን ዘርፉ ከማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪው ጋር በጥብቅ በመተሳሰሩ፣ ገቢ ምርትን በሀገር ውስጥ በመተካት ከፍተኛ ድል ተመዝግቧል።
ለአብነት ያህል የአርጆ የድንጋይ ከሰል ማበልጸጊያ ፋብሪካን መመልከት በቂ ነው። ይህ ዘመናዊ ፋብሪካ በየዓመቱ የከሰል ድንጋይ ለማስገባት ይወጣ የነበረውን ከ300 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ምርት እንዲተካ አስችሏል።
በተመሳሳይ የኖራ ድንጋይ የሀገር ውስጥ ምርት ድርሻ ከ17 በመቶ ወደ 75 በመቶ ከፍ ማለቱ፣ እንደ ለሚ ናሽናል ሲሚንቶ እና ሙገር የመሳሰሉ ግዙፍ ፋብሪካዎች የማምረቻ ወጪያቸውን በከፍተኛ ደረጃ እንዲቀንሱ አድርጓል።
ይህ በማዕድን ዘርፉ የታየው ዕድገት በማክሮ ኢኮኖሚው ላይ ብቻ ሳይሆን፣ ሰፊ ማኅበራዊ ፋይዳንም አምጥቷል።
በአሁኑ ወቅት ኢንዱስትሪው ከ1 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎቻችን ቀጥተኛ የሥራ ዕድል ፈጥሯል። ከ4 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን ደግሞ ኑሯቸውን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በዚህ ዘርፍ ላይ መስርተዋል።
በአጠቃላይ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው የማዕድን ዘርፉን ከድቅድቅ ጨለማ አውጥቶ የሀገራችንን የኢንዱስትሪ ሽግግር የሚያፋጥን ሞተር አድርጎታል።
ይህ የማዕድን ዘርፍ ስኬት ዘርፉ የኢትዮጵያን የብልጽግና ጉዞ ዕውን የሚያደርግ አስተማማኝ ምሰሶ መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #mining #madeinethiopia #economicreform #goldexport #ebc
*************************
የኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ ለበርካታ አሥርት ዓመታት በፖሊሲ ክፍተት፣ በሕገ-ወጥ የኮንትሮባንድ ንግድ እና በተደራጀ ብክነት ምክንያት እምቅ አቅሙ ሙሉ በሙሉ ተዘንግቶ ቆይቷል።
ዛሬ ላይ ግን በአዲሱ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ከሀገራችን 5 ዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ በመሆን ታሪካዊ ትንሣኤውን አብስሯል።
ሀገራችን ስትገነባው የቆየችው በመንግሥት ከፍተኛ ወጪ ላይ የተመሠረተ እና ለዕዳ ተጋላጭ ያደረጋት የኢኮኖሚ ሞዴል ፈታኝ ሆኖ መቆየቱ ይታወቃል።
ይህን በማክሮ ኢኮኖሚ አለመረጋጋት፣ በዋጋ ግሽበት እና በውጭ ምንዛሬ እጥረት የተተበተበ ማነቆ በዘላቂነት ለመቅረፍ የተተገበረው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ፣ ማዕድንን ከመረሳት ወደ ብሔራዊ ኢኮኖሚ አንቀሳቃሽነት በውጤታማነት አሸጋግሮታል።
ይህ መዋቅራዊ ለውጥ በመረጃ እና በቁጥር ሲመዘን እጅግ አስደናቂ ሆኖ እናገኘዋለን። በ2010 ዓ.ም የማዕድን ዘርፍ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) የነበረው ድርሻ 0.2 በመቶ ብቻ ነበረ። በ2017 ዓ.ም ይህ ቁጥር የ7 እጥፍ ብልጫ በማሳየት ወደ 1.4 በመቶ ማደግ ችሏል።
በተለይም በወርቅ ምርት እና ኤክስፖርት ላይ የታየው ለውጥ በታሪካችን ወደር የማይገኝለት እመርታ ነው።
ባህላዊ የማዕድን ቁፋሮን ወደ መደበኛ የንግድ ሥርዓት በማስገባት በተደረገው ስኬታማ የፖሊሲ ማሻሻያ፣ የሀገራችን የወርቅ ኤክስፖርት ገቢ ከ100 ሚሊዮን ዶላር ወደ 3.48 ቢሊዮን ዶላር በማደግ የ35 እጥፍ ጭማሪ አስመዝግቧል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በቅርቡ የተገበረው በገበያ ላይ የተመሠረተ የውጭ ምንዛሬ ተመን ሥርዓት ደግሞ አምራቾች ምርታቸውን በመደበኛው የፋይናንስ ሥርዓት እንዲያቀርቡ በማድረግ ለዚህ ስኬት ትልቅ ሞተር ሆኗል።
በሌላ በኩል "ኢትዮጵያ ታምርት" በተሰኘው ሀገራዊ ንቅናቄ የማዕድን ዘርፉ ከማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪው ጋር በጥብቅ በመተሳሰሩ፣ ገቢ ምርትን በሀገር ውስጥ በመተካት ከፍተኛ ድል ተመዝግቧል።
ለአብነት ያህል የአርጆ የድንጋይ ከሰል ማበልጸጊያ ፋብሪካን መመልከት በቂ ነው። ይህ ዘመናዊ ፋብሪካ በየዓመቱ የከሰል ድንጋይ ለማስገባት ይወጣ የነበረውን ከ300 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ምርት እንዲተካ አስችሏል።
በተመሳሳይ የኖራ ድንጋይ የሀገር ውስጥ ምርት ድርሻ ከ17 በመቶ ወደ 75 በመቶ ከፍ ማለቱ፣ እንደ ለሚ ናሽናል ሲሚንቶ እና ሙገር የመሳሰሉ ግዙፍ ፋብሪካዎች የማምረቻ ወጪያቸውን በከፍተኛ ደረጃ እንዲቀንሱ አድርጓል።
ይህ በማዕድን ዘርፉ የታየው ዕድገት በማክሮ ኢኮኖሚው ላይ ብቻ ሳይሆን፣ ሰፊ ማኅበራዊ ፋይዳንም አምጥቷል።
በአሁኑ ወቅት ኢንዱስትሪው ከ1 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎቻችን ቀጥተኛ የሥራ ዕድል ፈጥሯል። ከ4 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን ደግሞ ኑሯቸውን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በዚህ ዘርፍ ላይ መስርተዋል።
በአጠቃላይ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው የማዕድን ዘርፉን ከድቅድቅ ጨለማ አውጥቶ የሀገራችንን የኢንዱስትሪ ሽግግር የሚያፋጥን ሞተር አድርጎታል።
ይህ የማዕድን ዘርፍ ስኬት ዘርፉ የኢትዮጵያን የብልጽግና ጉዞ ዕውን የሚያደርግ አስተማማኝ ምሰሶ መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #mining #madeinethiopia #economicreform #goldexport #ebc
1 month ago
በታሪካችን ለመጀመሪያ ጊዜ፣ የኢንዱስትሪ ዘርፍ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት ድርሻ ከግብርና እና ከአገልግሎት በልጧል - ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር)
**************************
የብሔራዊ ባንክ ገዢ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ታከናውናለች በሚል መሪ ቃል በተደረገው መድረክ ላይ፣ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያ በፋይናንስ፣ በወጪ ንግድ እና በኢንዱስትሪ ዘርፎች ያመጣውን አስደናቂ ሀገራዊ ለውጥ በዝርዝር አቅርበዋል።
የኢኮኖሚ ዕድገቱ ወደ ተከታታይ የሥራ ዕድል ፈጠራ መሸጋገሩን የገለፁት ዶ/ር ኢዮብ፣ ዘንድሮ ብቻ በተለያዩ ዘርፎች 4.9 ሚሊዮን አዳዲስ የሥራ ዕድሎች መፈጠራቸውን ጠቅሰዋል።
ከዚህም ጋር ተያይዞ የኢንዱስትሪው አቅም አጠቃቀም ከ49 በመቶ ወደ 66.3 በመቶ ማደጉን፣ ይህም በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢንዱስትሪው ዘርፍ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ድርሻ ከግብርና እና ከአገልግሎት ዘርፎች መብለጡን አብስረዋል።
የተደረገው የውጭ ምንዛሬ ተመን ማሻሻያም በወጪ ንግድ ዘርፍ የኢትዮጵያን ተወዳዳሪነት በከፍተኛ ደረጃ እንዳሳደገው ዶ/ር ኢዮብ አብራርተዋል።
በዚህም፣ የወጪ ንግድ በ2010 ዓ.ም ከነበረበት 2.83 ቢሊዮን ዶላር ባለፈው ዓመት ወደ 8.33 ቢሊዮን ዶላር ማደጉንና ዘንድሮ ደግሞ 11 ቢሊዮን ዶላር ይደርሳል ተብሎ እንደሚጠበቅ አስታውቀዋል።
ይህ የወጪ ንግድ ዕድገት የዓለም አቀፍ ዋጋ መጨመር ውጤት ብቻ ሳይሆን፣ በፖሊሲ ለውጡ የመጣ መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግር መሆኑንም ገልጸዋል።
የፋይናንስ ዘርፉን በተመለከተም፣ የባንክ ኢንዱስትሪው አጠቃላይ ሀብት ባለፉት 8 ዓመታት ውስጥ በ680 በመቶ፣ ተቀማጭ ገንዘብ ደግሞ በ654 በመቶ ማደጉን ተናግረዋል።
ይህን ተከትሎም 93.8 በመቶ የሚሆነው ብድር ለግል ዘርፉ እየቀረበ መሆኑ ሌላው ትልቅ ስኬት ነው ብለዋል።
ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለመንግሥት የልማት ድርጅቶች በሰጠው ብድር ምክንያት 845 ቢሊዮን ብር የማይመለስ ዕዳ ተሸክሞ ለቀውስ ተጋልጦ እንደነበር ያስታወሱት ዶ/ር ኢዮብ፣ መንግሥት በወሰደው እርምጃ ዕዳውን ወደ ሰነድ በማዞር እና ካፒታሉን በ3 እጥፍ በማሳደግ ባንኩን መታደግ መቻሉን አስረድተዋል።
በአሁኑ ሰዓት የባንክ ኢንዱስትሪው የተበላሸ ብድር ምጣኔ 3.07 በመቶ ብቻ ሲሆን፣ ይህም ብሔራዊ ባንክ ካስቀመጠው የ5 በመቶ ጣሪያ በታች መሆኑን አብራርተዋል።
የተደራረቡ ዓለም አቀፍ እና የሀገር ውስጥ ፈተናዎች ቢኖሩም፣ ኢኮኖሚው የመቋቋም አቅሙን የገነባ በመሆኑ ሀገራችን የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት ለመሆን በተገቢው መንገድ ላይ መሆኗን አረጋግጣለች ሲሉ ዶ/ር ኢዮብ ገልጸዋል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #economicreform #industrialgrowth #exportgrowth #financesector #banking #ebc
**************************
የብሔራዊ ባንክ ገዢ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ታከናውናለች በሚል መሪ ቃል በተደረገው መድረክ ላይ፣ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያ በፋይናንስ፣ በወጪ ንግድ እና በኢንዱስትሪ ዘርፎች ያመጣውን አስደናቂ ሀገራዊ ለውጥ በዝርዝር አቅርበዋል።
የኢኮኖሚ ዕድገቱ ወደ ተከታታይ የሥራ ዕድል ፈጠራ መሸጋገሩን የገለፁት ዶ/ር ኢዮብ፣ ዘንድሮ ብቻ በተለያዩ ዘርፎች 4.9 ሚሊዮን አዳዲስ የሥራ ዕድሎች መፈጠራቸውን ጠቅሰዋል።
ከዚህም ጋር ተያይዞ የኢንዱስትሪው አቅም አጠቃቀም ከ49 በመቶ ወደ 66.3 በመቶ ማደጉን፣ ይህም በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢንዱስትሪው ዘርፍ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ድርሻ ከግብርና እና ከአገልግሎት ዘርፎች መብለጡን አብስረዋል።
የተደረገው የውጭ ምንዛሬ ተመን ማሻሻያም በወጪ ንግድ ዘርፍ የኢትዮጵያን ተወዳዳሪነት በከፍተኛ ደረጃ እንዳሳደገው ዶ/ር ኢዮብ አብራርተዋል።
በዚህም፣ የወጪ ንግድ በ2010 ዓ.ም ከነበረበት 2.83 ቢሊዮን ዶላር ባለፈው ዓመት ወደ 8.33 ቢሊዮን ዶላር ማደጉንና ዘንድሮ ደግሞ 11 ቢሊዮን ዶላር ይደርሳል ተብሎ እንደሚጠበቅ አስታውቀዋል።
ይህ የወጪ ንግድ ዕድገት የዓለም አቀፍ ዋጋ መጨመር ውጤት ብቻ ሳይሆን፣ በፖሊሲ ለውጡ የመጣ መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግር መሆኑንም ገልጸዋል።
የፋይናንስ ዘርፉን በተመለከተም፣ የባንክ ኢንዱስትሪው አጠቃላይ ሀብት ባለፉት 8 ዓመታት ውስጥ በ680 በመቶ፣ ተቀማጭ ገንዘብ ደግሞ በ654 በመቶ ማደጉን ተናግረዋል።
ይህን ተከትሎም 93.8 በመቶ የሚሆነው ብድር ለግል ዘርፉ እየቀረበ መሆኑ ሌላው ትልቅ ስኬት ነው ብለዋል።
ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለመንግሥት የልማት ድርጅቶች በሰጠው ብድር ምክንያት 845 ቢሊዮን ብር የማይመለስ ዕዳ ተሸክሞ ለቀውስ ተጋልጦ እንደነበር ያስታወሱት ዶ/ር ኢዮብ፣ መንግሥት በወሰደው እርምጃ ዕዳውን ወደ ሰነድ በማዞር እና ካፒታሉን በ3 እጥፍ በማሳደግ ባንኩን መታደግ መቻሉን አስረድተዋል።
በአሁኑ ሰዓት የባንክ ኢንዱስትሪው የተበላሸ ብድር ምጣኔ 3.07 በመቶ ብቻ ሲሆን፣ ይህም ብሔራዊ ባንክ ካስቀመጠው የ5 በመቶ ጣሪያ በታች መሆኑን አብራርተዋል።
የተደራረቡ ዓለም አቀፍ እና የሀገር ውስጥ ፈተናዎች ቢኖሩም፣ ኢኮኖሚው የመቋቋም አቅሙን የገነባ በመሆኑ ሀገራችን የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት ለመሆን በተገቢው መንገድ ላይ መሆኗን አረጋግጣለች ሲሉ ዶ/ር ኢዮብ ገልጸዋል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #economicreform #industrialgrowth #exportgrowth #financesector #banking #ebc
1 month ago
ከ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ማግስት፦ የነገዋ ኢትዮጵያ አቅጣጫ እና ከመንግሥት የሚጠበቁ ኃላፊነቶች
***************************
የዘንድሮው 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዞ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ታሪካዊ ምዕራፍ ነው።
ምርጫውን አሸንፎ መንግሥት የሚመሰርተው ፓርቲ የሕዝብን አደራ ተቀብሎ ሀገራችንን ወደ ተሻለ ምዕራፍ የማሻገር ከባድ ኃገራዊ ኃላፊነት ይወድቅበታል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተለያዩ መድረኮች ባስተላለፏቸው መልዕክቶች፣ የፓርላማውን አብላጫ ድምጽ በማግኘት መንግሥት የሚመሰርተው ፓርቲ ድርብ ኃላፊነት እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።
ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሻገር የተጀመሩ እና በዕቅድ የተያዙ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን በተሻለ ሁኔታ መፈጸም ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው። ከእነዚህ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፡-
ሰብዓዊነትን ማዕከል ያደረገ አመራር እና የጸጥታ ተቋማት ግንባታ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ "ሰብዓዊነትን ማዕከል ያደረገ አመራር" አስፈላጊነትን ደጋግመው አንስተዋል።
አዲስ የሚመሰረተው መንግሥትም ይህን መርህ በተግባር በመተርጎም የዜጎችን ደኅንነት እና ሰላም ማስቀደም ይጠበቅበታል።
የጸጥታ እና የደኅንነት ተቋማትን ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ የሆኑ፣ ዘመናዊ እና ሕዝብን የሚያገለግሉ አድርጎ የመገንባቱ የሪፎርም ሥራ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ሲሠራ ቆይቷል። ይህ አሁንም ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
የዜጎች ደኅንነት በእኩልነት ሲረጋገጥ እና የጸጥታ መዋቅሩ የሁሉንም ኢትዮጵያዊ መብት ለማስጠበቅ ሲቆም ብቻ ሀገራዊ መረጋጋትን እና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ማሳካት ይቻላል።
ጎረቤትን ያስቀደመ ዲፕሎማሲ እና ቀጣናዊ ትስስር
በውጭ ግንኙነት ረገድ አሸናፊው ፓርቲ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስጠብቅ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ሥራ መሥራት ይኖርበታል።
መንግሥት የሚከተለውን ጎረቤት ተኮር የዲፕሎማሲ ስትራቴጂ ይበልጥ በማጠናከር ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስር ውስጥ ያላትን የመሪነት ሚና ማስቀጠል ይጠበቅበታል።
ከዚህም ባሻገር ለመካከለኛው ምሥራቅ እና ለባሕረ ሰላጤው ጂኦፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች የቅርብ ትኩረት ሊሰጥ ይገባል።
በቀጣናው ሊፈጠሩ የሚችሉ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎችን የሚቋቋም ሚዛናዊ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲን መተግበር በቀጣይ ከመንግሥት የሚጠበቅ ወሳኝ ኃላፊነት ነው።
የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ
አዲስ የሚመሰረተው መንግሥት ሌላው ትልቅ ኃላፊነት ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትን ማረጋገጥ ነው።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርን በማስፋት የኢትዮጵያን የደን ሽፋን ከማሳደግ ባለፈ፣ ሀገራችን ከካርበን ንግድ ተጠቃሚ የምትሆንበትን "የአረንጓዴ ወርቅ" የኢኮኖሚ ሥርዓት መገንባት ይገባዋል።
ይህ አካሄድ የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባሻገር፣ አዲስ የውጭ ምንዛሬ ማስገኛ አቅም በመፍጠር የዜጎችን ተጠቃሚነት ያረጋግጣል።
የሀገራዊ ምክክር ውጤትን ተግባራዊ ማድረግ
አዲሱ መንግሥት ትልቅ ትኩረት ሊሰጣቸው ከሚገቡ ጉዳዮች መካከል የሀገራዊ ምክክሩን ውጤት ተቀብሎ ወደ ተግባር መቀየር ቀዳሚው ነው።
የምክክሩ ውጤት የነገዋን የበለጸገች እና የተረጋጋች ኢትዮጵያን ለመገንባት ጠንካራ መሰረት የሚጥል ነው።
የምክክሩ ውጤት የሕግ የበላይነት የነገሰባት፣ ሰብዓዊ መብቶች ይበልጥ የሚከበሩባት እና የተጠናከረ የፍትሕ ሥርዓት የተረጋገጠባት ሀገር ለመገንባት ወሳኝ ግብዓት ነው።
የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም
ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ውጤታማነቱ እየታየ ይገኛል። በዚህም ኢትዮጵያ በዘንድሮው በጀት ዓመት ማጠቃለያ የ10.2 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት እንደምታስመዘግብ ይጠበቃል።
የመንግሥት ቀጣዩ ዋና ሥራ ይህ ዕድገት ወደ እያንዳንዱ ዜጋ ሕይወት እንዲወርድ ማድረግ ነው።
ለዚህም የዋጋ ንረትን መቆጣጠር፣ የኑሮ ውድነትን ማቃለል እና የውጭ ብድር ጫናን ማስተካከል ከአዲሱ መንግሥት የሚጠበቁ እና ፈጣን ምላሽ የሚሹ አንገብጋቢ የቤት ሥራዎች ናቸው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopia #economicreform #macroeconomy #diplomacy #greenlegacy #ebc
***************************
የዘንድሮው 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዞ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ታሪካዊ ምዕራፍ ነው።
ምርጫውን አሸንፎ መንግሥት የሚመሰርተው ፓርቲ የሕዝብን አደራ ተቀብሎ ሀገራችንን ወደ ተሻለ ምዕራፍ የማሻገር ከባድ ኃገራዊ ኃላፊነት ይወድቅበታል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተለያዩ መድረኮች ባስተላለፏቸው መልዕክቶች፣ የፓርላማውን አብላጫ ድምጽ በማግኘት መንግሥት የሚመሰርተው ፓርቲ ድርብ ኃላፊነት እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።
ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሻገር የተጀመሩ እና በዕቅድ የተያዙ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን በተሻለ ሁኔታ መፈጸም ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው። ከእነዚህ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፡-
ሰብዓዊነትን ማዕከል ያደረገ አመራር እና የጸጥታ ተቋማት ግንባታ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ "ሰብዓዊነትን ማዕከል ያደረገ አመራር" አስፈላጊነትን ደጋግመው አንስተዋል።
አዲስ የሚመሰረተው መንግሥትም ይህን መርህ በተግባር በመተርጎም የዜጎችን ደኅንነት እና ሰላም ማስቀደም ይጠበቅበታል።
የጸጥታ እና የደኅንነት ተቋማትን ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ የሆኑ፣ ዘመናዊ እና ሕዝብን የሚያገለግሉ አድርጎ የመገንባቱ የሪፎርም ሥራ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ሲሠራ ቆይቷል። ይህ አሁንም ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
የዜጎች ደኅንነት በእኩልነት ሲረጋገጥ እና የጸጥታ መዋቅሩ የሁሉንም ኢትዮጵያዊ መብት ለማስጠበቅ ሲቆም ብቻ ሀገራዊ መረጋጋትን እና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ማሳካት ይቻላል።
ጎረቤትን ያስቀደመ ዲፕሎማሲ እና ቀጣናዊ ትስስር
በውጭ ግንኙነት ረገድ አሸናፊው ፓርቲ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስጠብቅ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ሥራ መሥራት ይኖርበታል።
መንግሥት የሚከተለውን ጎረቤት ተኮር የዲፕሎማሲ ስትራቴጂ ይበልጥ በማጠናከር ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስር ውስጥ ያላትን የመሪነት ሚና ማስቀጠል ይጠበቅበታል።
ከዚህም ባሻገር ለመካከለኛው ምሥራቅ እና ለባሕረ ሰላጤው ጂኦፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች የቅርብ ትኩረት ሊሰጥ ይገባል።
በቀጣናው ሊፈጠሩ የሚችሉ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎችን የሚቋቋም ሚዛናዊ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲን መተግበር በቀጣይ ከመንግሥት የሚጠበቅ ወሳኝ ኃላፊነት ነው።
የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ
አዲስ የሚመሰረተው መንግሥት ሌላው ትልቅ ኃላፊነት ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትን ማረጋገጥ ነው።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርን በማስፋት የኢትዮጵያን የደን ሽፋን ከማሳደግ ባለፈ፣ ሀገራችን ከካርበን ንግድ ተጠቃሚ የምትሆንበትን "የአረንጓዴ ወርቅ" የኢኮኖሚ ሥርዓት መገንባት ይገባዋል።
ይህ አካሄድ የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባሻገር፣ አዲስ የውጭ ምንዛሬ ማስገኛ አቅም በመፍጠር የዜጎችን ተጠቃሚነት ያረጋግጣል።
የሀገራዊ ምክክር ውጤትን ተግባራዊ ማድረግ
አዲሱ መንግሥት ትልቅ ትኩረት ሊሰጣቸው ከሚገቡ ጉዳዮች መካከል የሀገራዊ ምክክሩን ውጤት ተቀብሎ ወደ ተግባር መቀየር ቀዳሚው ነው።
የምክክሩ ውጤት የነገዋን የበለጸገች እና የተረጋጋች ኢትዮጵያን ለመገንባት ጠንካራ መሰረት የሚጥል ነው።
የምክክሩ ውጤት የሕግ የበላይነት የነገሰባት፣ ሰብዓዊ መብቶች ይበልጥ የሚከበሩባት እና የተጠናከረ የፍትሕ ሥርዓት የተረጋገጠባት ሀገር ለመገንባት ወሳኝ ግብዓት ነው።
የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም
ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ውጤታማነቱ እየታየ ይገኛል። በዚህም ኢትዮጵያ በዘንድሮው በጀት ዓመት ማጠቃለያ የ10.2 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት እንደምታስመዘግብ ይጠበቃል።
የመንግሥት ቀጣዩ ዋና ሥራ ይህ ዕድገት ወደ እያንዳንዱ ዜጋ ሕይወት እንዲወርድ ማድረግ ነው።
ለዚህም የዋጋ ንረትን መቆጣጠር፣ የኑሮ ውድነትን ማቃለል እና የውጭ ብድር ጫናን ማስተካከል ከአዲሱ መንግሥት የሚጠበቁ እና ፈጣን ምላሽ የሚሹ አንገብጋቢ የቤት ሥራዎች ናቸው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopia #economicreform #macroeconomy #diplomacy #greenlegacy #ebc
Sponsored by
Surafel
2 months ago
የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለኮንስትራክሽን ዘርፍ ያስገኘው ትሩፋት
*****************
በቅርቡ በኢትዮጵያ የተተገበሩት የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ከፍተኛ መነቃቃት ፈጥረዋል።
ይህ መነቃቃት ለሀገራችን የኮንስትራክሽን ዘርፍ የግብዓት አቅርቦት ዋነኛ የጀርባ አጥንት እየሆነ መጥቷል።
ዘርፉ ከዚህ ቀደም የነበረውን የግብዓት ጥገኝነት በመስበር ለግንባታ የሚያስፈልጉ ቁልፍ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት መጀመሩ፣ የውጭ ምንዛሬን ከማዳን ባለፈ አጠቃላይ የኢኮኖሚ ዕድገቱን እያፋጠነው ይገኛል።
ከ7 ዓመታት በፊት ፋብሪካዎች በማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት፣ በኃይል መቆራረጥ እና በግብዓት እጥረት ምክንያት በአማካይ የማምረት አቅማቸውን 47 በመቶ ብቻ ይጠቀሙ ነበር።
ሆኖም ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመንግሥት በተወሰዱ የማሻሻያ እርምዎች ተዘግተው የነበሩ 993 ፋብሪካዎች ወደ ሥራ ተመልሰዋል። በተለይ የማኑፋክቸሪንግ እና የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪዎች ደግሞ ፈጣን መዋቅራዊ ለውጥ ማስመዝገብ ችለዋል።
በተተገበሩት ማሻሻያዎች በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪው ዘርፍ የማምረት አቅም ወደ 67 በመቶ ከፍ ያለ ሲሆን፣ የዘርፉ ዕድገትም ከ4.8 በመቶ ወደ 10.7 በመቶ ከፍ ብሏል።
በጥቅሉ የኢንዱስትሪው ዘርፍ መነቃቃት ለኮንስትራክሽን ዘርፍ ካበረከታቸው አስተዋጽኦዎች ዋነኛው ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት መተካት መቻሉ ነው።
ለዚህ ማሳያ የሚሆኑት የሀገራችንን የሴራሚክ ፍላጎት 70 በመቶ መሸፈን የሚችለው ግዙፉ የባጃይ (ቱለፋ) ሴራሚክስ እና የሀገራችንን 50 በመቶ የሲሚንቶ ፍላጎት የሚያሟላው የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ ናቸው።
ከዚህ ቀደም ከውጭ ለሚገቡ የግንባታ ግብዓቶች ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ይወጣ የነበረ ሲሆን፣ ለአብነትም ለሴራሚክ ግዢ ብቻ ከ74 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ይባክን ነበር።
አሁን በተተገበረው የተኪ ምርት ስትራቴጂ፣ በተያዘው በጀት ዓመት 9 ወራት ብቻ 4.85 ቢሊዮን ዶላር ማዳን ተችሏል።
በሌላ በኩል ቀደም ሲል የፋይናንስ ሥርዓቱ ለመንግሥት የልማት ድርጅቶች ያደላ የነበረ በመሆኑ፣ ለግሉ ዘርፍ ይደርስ የነበረው የብድር መጠን 56.3 በመቶ ብቻ ነበር።
ሆኖም ተግባራዊ በተደረገ ታሪካዊ የብድር ሽግሽግ አስገዳጅ የሆነውን የ27 በመቶ የቦንድ ግዢ በማስቀረት ጭምር ለግል ዘርፉ የሚሰጠው የብድር ድርሻ ወደ 77 በመቶ ከፍ ተደርጓል።
በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የማኑፋክቸሪንግ እና ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ከነበረበት የግብዓት ጥገኝነት አዙሪት ወጥቶ የውጭ ምንዛሬን ወደሚያድን እና የግል ዘርፉን ዋነኛ ሞተር ወዳደረገ የግብዓት ሉዓላዊነት ተሸጋግሯል።
በኢኮኖሚ ማሻሻያው የመጣው ይህ መነቃቃት ሀገራችን በኢንዱስትሪ ብልጽግና ጎዳና ላይ የማይቀለበስ ታሪካዊ እርምጃ መጀመሯን የሚያረጋግጥ እና ለቀጣይ ጠንካራ ሀገራዊ የዕድገት ጉዞ ፅኑ መሠረት የጣለ ነው።
#ethiopia #economicreform #industrialawakening #manufacturing #constructionindustry #importsubstitution #inputsovereignty
*****************
በቅርቡ በኢትዮጵያ የተተገበሩት የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ከፍተኛ መነቃቃት ፈጥረዋል።
ይህ መነቃቃት ለሀገራችን የኮንስትራክሽን ዘርፍ የግብዓት አቅርቦት ዋነኛ የጀርባ አጥንት እየሆነ መጥቷል።
ዘርፉ ከዚህ ቀደም የነበረውን የግብዓት ጥገኝነት በመስበር ለግንባታ የሚያስፈልጉ ቁልፍ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት መጀመሩ፣ የውጭ ምንዛሬን ከማዳን ባለፈ አጠቃላይ የኢኮኖሚ ዕድገቱን እያፋጠነው ይገኛል።
ከ7 ዓመታት በፊት ፋብሪካዎች በማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት፣ በኃይል መቆራረጥ እና በግብዓት እጥረት ምክንያት በአማካይ የማምረት አቅማቸውን 47 በመቶ ብቻ ይጠቀሙ ነበር።
ሆኖም ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመንግሥት በተወሰዱ የማሻሻያ እርምዎች ተዘግተው የነበሩ 993 ፋብሪካዎች ወደ ሥራ ተመልሰዋል። በተለይ የማኑፋክቸሪንግ እና የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪዎች ደግሞ ፈጣን መዋቅራዊ ለውጥ ማስመዝገብ ችለዋል።
በተተገበሩት ማሻሻያዎች በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪው ዘርፍ የማምረት አቅም ወደ 67 በመቶ ከፍ ያለ ሲሆን፣ የዘርፉ ዕድገትም ከ4.8 በመቶ ወደ 10.7 በመቶ ከፍ ብሏል።
በጥቅሉ የኢንዱስትሪው ዘርፍ መነቃቃት ለኮንስትራክሽን ዘርፍ ካበረከታቸው አስተዋጽኦዎች ዋነኛው ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት መተካት መቻሉ ነው።
ለዚህ ማሳያ የሚሆኑት የሀገራችንን የሴራሚክ ፍላጎት 70 በመቶ መሸፈን የሚችለው ግዙፉ የባጃይ (ቱለፋ) ሴራሚክስ እና የሀገራችንን 50 በመቶ የሲሚንቶ ፍላጎት የሚያሟላው የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ ናቸው።
ከዚህ ቀደም ከውጭ ለሚገቡ የግንባታ ግብዓቶች ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ይወጣ የነበረ ሲሆን፣ ለአብነትም ለሴራሚክ ግዢ ብቻ ከ74 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ይባክን ነበር።
አሁን በተተገበረው የተኪ ምርት ስትራቴጂ፣ በተያዘው በጀት ዓመት 9 ወራት ብቻ 4.85 ቢሊዮን ዶላር ማዳን ተችሏል።
በሌላ በኩል ቀደም ሲል የፋይናንስ ሥርዓቱ ለመንግሥት የልማት ድርጅቶች ያደላ የነበረ በመሆኑ፣ ለግሉ ዘርፍ ይደርስ የነበረው የብድር መጠን 56.3 በመቶ ብቻ ነበር።
ሆኖም ተግባራዊ በተደረገ ታሪካዊ የብድር ሽግሽግ አስገዳጅ የሆነውን የ27 በመቶ የቦንድ ግዢ በማስቀረት ጭምር ለግል ዘርፉ የሚሰጠው የብድር ድርሻ ወደ 77 በመቶ ከፍ ተደርጓል።
በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የማኑፋክቸሪንግ እና ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ከነበረበት የግብዓት ጥገኝነት አዙሪት ወጥቶ የውጭ ምንዛሬን ወደሚያድን እና የግል ዘርፉን ዋነኛ ሞተር ወዳደረገ የግብዓት ሉዓላዊነት ተሸጋግሯል።
በኢኮኖሚ ማሻሻያው የመጣው ይህ መነቃቃት ሀገራችን በኢንዱስትሪ ብልጽግና ጎዳና ላይ የማይቀለበስ ታሪካዊ እርምጃ መጀመሯን የሚያረጋግጥ እና ለቀጣይ ጠንካራ ሀገራዊ የዕድገት ጉዞ ፅኑ መሠረት የጣለ ነው።
#ethiopia #economicreform #industrialawakening #manufacturing #constructionindustry #importsubstitution #inputsovereignty
6 months ago
✈️ "የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአፍሪካ ኩራት እና የአህጉሪቱ የትስስር ምሰሶ ነው" — ፕሮፌሰር ጆሴፍ ሜንሳህ
#ethiopia | የዮርክ ዩኒቨርሲቲ ምሁር የሆኑት ጋናዊው ፕሮፌሰር ጆሴፍ ሜንሳህ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አፍሪካን ከራሷና ከቀሪው ዓለም ጋር በማስተሳሰር ረገድ የሚጫወተው ሚና እጅግ የሚደነቅና "የአፍሪካ ኩራት" መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ነው አሉ።
ፕሮፌሰሩ ከኢቲቪ "አዲስ ዳያሎግ" ፕሮግራም ጋር በነበራቸው ቆይታ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
🌍 የአየር መንገዱ ስትራቴጂካዊ መስፋፋት
አየር መንገዱ በአፍሪካ ውስጥ በሎሜ፣ ሉሳካ እና ሊሎንግዌ፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ወደ ፊሊፒንስ እና ጄኔቫ አዳዲስ መዳረሻዎችን በመክፈት የጀመረውን ስትራቴጂካዊ ጉዞ አጠናክሮ መቀጠሉን ምሁሩ አድንቀዋል
🏗️ የቢሾፍቱ ግዙፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት
በ12.5 ቢሊዮን ዶላር የሚገነባው አዲሱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለኢኮኖሚው ትልቅ አቅም እንደሚሆን ፕሮፌሰር ጆሴፍ ገልጸዋል።
ይህ ፕሮጀክት፦
* ለአፍሪካ ትስስር አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ይከፍታል።
* ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል ይፈጥራል።
* ቦታን እና ጊዜን በማቀራረብ ረገድ ትልቅ ለውጥ ያመጣል።
📈 ማክሮ ኢኮኖሚ እና የወጣቱ አቅም
ኢትዮጵያ የጀመረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ "የመፍጠር እና የማደስ" ባህሪ እንዳለው የጠቆሙት ምሁሩ፣ መንግሥት ችግር ሲፈጠር ብቻ ምላሽ ከመስጠት ወጥቶ ለረጅም ጊዜ የሚዘልቁ ዕቅዶች ላይ ማተኮሩን አድንቀዋል። አክለውም፣ ኢትዮጵያ ያላት ከፍተኛ የወጣት ቁጥር ለቀጣይ ሁለት አሥርት ዓመታት ትልቁ ሀብቷ መሆኑን ገልጸው፣ ይህንን አቅም ለመጠቀም በቂ የሥራ ዕድል መፍጠር እንደሚገባ አሳስበዋል።
ኢትዮጵያ የጀመረችው ይህ ስትራቴጂካዊ እርምጃ ሀገሪቱን ወደ ተሻለ ምዕራፍ እንደሚያሸጋግራት ፕሮፌሰር ጆሴፍ ሜንሳህ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopianairlines #africanpride #economicreform #aviationnews #ethiopia #professorjosephmensah #addisdialogue #africaunion #strategicplanning
#ethiopia | የዮርክ ዩኒቨርሲቲ ምሁር የሆኑት ጋናዊው ፕሮፌሰር ጆሴፍ ሜንሳህ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አፍሪካን ከራሷና ከቀሪው ዓለም ጋር በማስተሳሰር ረገድ የሚጫወተው ሚና እጅግ የሚደነቅና "የአፍሪካ ኩራት" መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ነው አሉ።
ፕሮፌሰሩ ከኢቲቪ "አዲስ ዳያሎግ" ፕሮግራም ጋር በነበራቸው ቆይታ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
🌍 የአየር መንገዱ ስትራቴጂካዊ መስፋፋት
አየር መንገዱ በአፍሪካ ውስጥ በሎሜ፣ ሉሳካ እና ሊሎንግዌ፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ወደ ፊሊፒንስ እና ጄኔቫ አዳዲስ መዳረሻዎችን በመክፈት የጀመረውን ስትራቴጂካዊ ጉዞ አጠናክሮ መቀጠሉን ምሁሩ አድንቀዋል
🏗️ የቢሾፍቱ ግዙፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት
በ12.5 ቢሊዮን ዶላር የሚገነባው አዲሱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለኢኮኖሚው ትልቅ አቅም እንደሚሆን ፕሮፌሰር ጆሴፍ ገልጸዋል።
ይህ ፕሮጀክት፦
* ለአፍሪካ ትስስር አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ይከፍታል።
* ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል ይፈጥራል።
* ቦታን እና ጊዜን በማቀራረብ ረገድ ትልቅ ለውጥ ያመጣል።
📈 ማክሮ ኢኮኖሚ እና የወጣቱ አቅም
ኢትዮጵያ የጀመረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ "የመፍጠር እና የማደስ" ባህሪ እንዳለው የጠቆሙት ምሁሩ፣ መንግሥት ችግር ሲፈጠር ብቻ ምላሽ ከመስጠት ወጥቶ ለረጅም ጊዜ የሚዘልቁ ዕቅዶች ላይ ማተኮሩን አድንቀዋል። አክለውም፣ ኢትዮጵያ ያላት ከፍተኛ የወጣት ቁጥር ለቀጣይ ሁለት አሥርት ዓመታት ትልቁ ሀብቷ መሆኑን ገልጸው፣ ይህንን አቅም ለመጠቀም በቂ የሥራ ዕድል መፍጠር እንደሚገባ አሳስበዋል።
ኢትዮጵያ የጀመረችው ይህ ስትራቴጂካዊ እርምጃ ሀገሪቱን ወደ ተሻለ ምዕራፍ እንደሚያሸጋግራት ፕሮፌሰር ጆሴፍ ሜንሳህ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopianairlines #africanpride #economicreform #aviationnews #ethiopia #professorjosephmensah #addisdialogue #africaunion #strategicplanning
Comments