Logo
Getu Temesgen
2 hours ago

መምህር የሽጥላ ሞገስ አስቸኳይ መልእክት አላቸው - እንስማቸው

ወሎ መርሣ የሚገኘው የሰዳቱ አቡነ ተክለሃይማኖት አንድነት ገዳም አስቸኳይ መልእክት

ግንቦት 29 እና 30 ከምሽቱ 1፡00 ጀምሮ የቀጥታ ሥርጭት መርሐግብር አዘጋጅቷል። ውኃ የለም በገዳሙ። እንድረስላቸው።

አቢሲኒያ-2555552222
አማራ ባንክ-9900050734076
013200269023200 አዋሽ
1000753661615ንግድ

https://cash.app/$Abunetek...

0911644781
0911981096
0911216958
0911671379
0911631126

መርሐግብሩን
በኦርቶዶክሳውያን ቲክታከሮች
በቋንቋዬነሽ ሚዲያ
በመንክር ሚዲያ
በደረጀዘ ወይንዬ ሚዲያ
በዚቅ ሚዲያ
በተአምኖ ሚዲያ
በአዛሔል ሚዲያ ተከታተሉ
Getu Temesgen
10 hours ago
♦️በሠንዳፋ አንድ አትሌት በጥይት ተመቶ ህይወቱ ማለፉ ብዙዎችን አስደንግጧል

👉አትሌቲክሱ ላይ የተፈጠረው ምንድነው?

👉ከአትሌት በተተኮሠ ጥይት የአንድ አትሌት ህይወት መጥፋቱ ተሠምቷል

👉ገዳዩ አትሌት ሟቹን አትሌት በጥይት ተኩሶ ገድሎ ሊያመልጥ ሲል በቦታው የነበሩ አርሶ አደሮች ተቷኩሰው ወደ ከተማ ሳይገባ ተይዟል

👉ገዳዩ አትሌት ከነመሳሪያው እጅ ከፍንጅ ተይዞ በቁጥጥር ስር ውሏል

👉 ለግድያ ያበቃቸው ምክንያት እየተጣራ ነው።

👉የገዳይም የሟችም ማንነት እንገልፃለን

👉በቀጣይ የሚመለከታቸውን አነጋግረን ሙሉውንና ትክክለኛውን መረጃ ይዘን እንቀርባለን

✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ (ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)

Getu Temesgen
11 hours ago
ፊፋ የስፒድን ዜማ በአልበሙ አካተተ !
#ethiopia | እውቁ አሜሪካዊ ' ስትሪመር ' አይ ሾው ስፒድ ለ 2026 ዓለም ዋንጫ የራሱን ዜማ ይፋ አድርጎ ነበር።

ስፒድ ይፋ ያደረገው ዜማ ከፍተኛ ተቀባይነት ሲያገኝ ሲሆን በ ዩቲዩብ በርካታ ተመልካቾች ተመልክተውታል።

ፊፋ አሁን ላይ የስፒድን ዜማ በዓለም ዋንጫ አልበም ዝርዝር ውስጥ ማካተቱን አሳውቆታል።

ስፒድ ፊፋ በይፋ ማረጋገጫ እንደሰጠው በቀጥታ ስርጭት ለአድናቂዎቹ የፅሁፍ ማረጋገጫ መልዕክቱን አሳይቷል።

ዜማው ' Champions ' የሚል መጠርያ ያለው ሲሆን ዩቲዩብ ላይ 11 ሚልዮን እይታ አግኝቷል።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #tikvahethsport #sport #ethiopia #getutemesgen #getu

Getu Temesgen
11 hours ago
የንፁሃን ደም መፍሰስ ይብቃ፡ ለዘላቂ ሰላም በጋራ እንምከር!
#ethiopia | በሀገራች የዜጎች ሞት ስፍራ አየቀያየረ ቀጥሏል።​ዛሬ ደግሞ በተደጋጋሚ ሞት እየተሰማበት ባለው በምስራቅ አርሲ ዞን በንፁሃን በኦርቶዶክስ ከርስትያን ወገኖቻችን ላይ ዘግናኝ ጭፍጨፋ መደረጉን፣ ቤተ ክርስቲያንና የአማኞች መኖሪያ ቤቶች መቃጠላቸውን ከሚዲያዎች ዘገባ መረዳት ችያለሁ። መሰል ጥቃቶች ራስን በተጠቂዎች ቦታ አድርገን ካየን በእጅጉ ልብን በኃዘን ይሰብራል።

የንፁሃን ደም ያለአግባብ መፍሰስ እና የዜጎች መገደል በአስቸኳይ ሊቆም ይገባል።ግና እንዴትና መቼ? እንዴትስ ላለፉት ዓመታት በንጹሃን ዜጎችና በቤተ እምነቶች(መስጊድና ቤተክርስቲያን) ላይ የደረሱት ጥቃቶች የአንዱ ፈጻሚዎች እንኳ በህግ ቁጥጥር ስር ማዋልና ተጠያቂ ማድረግ ሳይቻል ቀረ? ከድርጊቱ በላይ መደጋገሙ፣ከመደጋገሙ በላይ ፈጻሚዎቹ ሁሌም ያልታወቁ እየተባሉ መፍትሄ ማምጣት አለመቻል አደገኛ ነው።

ዘላቂ መፍትሄ ይገኝ ዘንድ ቆም ብሎ ማሰብ፣በ ስሜት ተጽዕኖ ስር ከመውደቅ በራቀ መልኩ ነገሮችን መመርመር፣መምከርና በጋራ መፍትሄ መፈለግ ግድ ይላል።

ክቡር የሆነው የሰው ልጅ ነፍስ እንዲህ መርከሱ እጅግ አደገኛ ነገር ነው።አላህ በቁርኣን እንዲህ ይለናል።

مِنۡ أَجۡلِ ذَٰلِكَ كَتَبۡنَا عَلَىٰ بَنِيٓ إِسۡرَـٰٓءِيلَ أَنَّهُۥ مَن قَتَلَ نَفۡسَۢا بِغَيۡرِ نَفۡسٍ أَوۡ فَسَادٖ فِي ٱلۡأَرۡضِ فَكَأَنَّمَا قَتَلَ ٱلنَّاسَ جَمِيعٗا وَمَنۡ أَحۡيَاهَا فَكَأَنَّمَآ أَحۡيَا ٱلنَّاسَ جَمِيعٗاۚ وَلَقَدۡ جَآءَتۡهُمۡ رُسُلُنَا بِٱلۡبَيِّنَٰتِ ثُمَّ إِنَّ كَثِيرٗا مِّنۡهُم بَعۡدَ ذَٰلِكَ فِي ٱلۡأَرۡضِ لَمُسۡرِفُونَ
— سورة المائدة (5:32)

"በዚህ ምክንያት በእስራኤል ልጆች ላይ እነሆ ያለ ነፍስ (መግደል) ወይም በምድር ላይ ያለማጥፋት (ካልሆነ በስተቀር) ነፍስን የገደለ ሰው ሰዎቹን ሁሉ እንደገደለ ነው፤ ሕያው ያደረጋትም ሰው ሰዎቹን ሁሉ ሕያው እንዳደረገ ነው ማለትን ጻፍን፡፡ መልክተኞቻችንም በግልጽ ተዓምራት በእርግጥ መጡዋቸው፡፡ ከዚያም ከዚህ በኋላ ከእነሱ ብዙዎቹ በምድር ላይ ወሰንን አላፊዎች ናቸው፡፡"
— አል-ማኢዳህ (5:32)

ይህ ቁርኣናዊ መለኮታዊ መመሪያ የሰው ልጅ ሕይወት ነፍስ በማለት በመጥራት ያለ ምንም የዘር፣ የሃይማኖትና የብሔር ልዩነት ፍጹም የተከበረና የማይደፈር መሆኑን ያረጋግጣል።

በአንቀጹ መሠረት አንዲትን ንጹሕ ነፍስ ያለ አግባብ መቅጠፍ መላውን የሰውን ዘር እንደ ማጥፋት የሚቆጠር እጅግ ከባድ ወንጀል ሲሆን፣ በተቃራኒው ደግሞ አንዲትን ነፍስ ከአደጋ መታደግና ማዳን መላውን የሰው ልጅ ሕይወት እንደ ማኖር የሚቆጠር ታላቅ ሰብአዊ በጎነት ነው።

እንደ ዜጋ ማድረግ የምንችለው ለሟች ቤተሰቦችና ወገኖቻች መጽናናትን መመኘት ብቻ በመሆኑ እያዘንኩ ለሟች ቤተሰቦች መጽናናትን እመኛለሁ።

ህዝባችንና ሀገራችንን ከጥፋትና ከእልቂት ጠብቅልን።አላህ ሆይ! እውነቱ እንዲወጣ፣ የንጹዃን ደምም አፍሳሾች መቀጣጫ ይሆኑ ዘንድ የእጃቸውን እንዲያገኙ አድርግልን።አላህ በቃችሁ በለን!

ኡዝታዝ አህመዲን ጀበል

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu

Getu Temesgen
10 hours ago
#ethiopia | ይህ መከራ ... እየሰፋ ነው | ሳንጠፋፋ መፍትሔ እንፈልግ | ፋርማሲ ቤቶች ጥብቅ መመርያ ተሰጣቸው | የአሜሪካና ኢራን ድርድር

" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
Getu Temesgen
11 hours ago
"በሚሊተሪ ካምፓች እና በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ምርጫ ሰኔ 2 ይካሄዳል" - የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በሚሊተሪ ካምፓች እና በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በተመዘገቡባቸው ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ የመራጮች ምዝገባ ሰኔ 1 ቀን እንደሚያካሂድ የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን በዛሬው ዕለት በሪፖርቱ ጠቅሶት ነበር።

ይህንን አስመልክቶ ማብራሪያ እንዲሰጡበት ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበላቸው የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሚሊተሪ ካምፓች እና በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በተመዘገቡባቸው ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ምርጫው በተለየ ቀን እንደሚካሄድ አረጋግጠዋል።

ሆኖም ህብረቱ "June-8 / ሰኔ 1" ቀን እንደሚካሄድ ሪፖርቱ ቢጠቅስም፥ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ግን ምርጫው በእነዚህ ልዩ ጣቢያዎች የሚካሄደው #ሰኔ_2 መሆኑን ነው የገለጹት።

ይህ የተፈጠረበትን ምክንያትም ቦርዱ ያለበትን የተጨናነቀ ጊዜ ታሳቢ በማድረግ ውጤቶቹም "በፍጥነት ተጠቃለው መቅረብ የሚችሉ ውጤቶች በመሆናቸው " ነው ሲሉ ቦርዱ ከሌሎች ውጤቶች ጋር አብሮ የሚያቀርባቸው መሆኑን ገልጸዋል።

ከዚህ ቀደም በሀገር ውስጥ ተፈናቃይ ካምፖች 28,632 እንዲሁም በሚሊተሪ ካምፖች 126,498 ሺ መራጮች መመዝገባቸው መገለጹ ይታወሳል።

በተጨማሪም ህብረቱ የተጠናቀቀ ውጤት የሚገለጽበትን ቀን በተመለከተ ህብረቱ ሰኔ 4 መሆኑን በሪፖርቱ ጠቅሷል።

የቦርዱ ሰብሳቢ በበኩላቸው ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ቦርዱ ከገጠመው የድምጽ በይፋ የማሳወቅ ሥራ እስከ 20 ቀን የመግፋት መብት እንዳለውም ጠቁመዋል።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu

Getu Temesgen
13 hours ago
የም/ቤቱ 23ኛ መደበኛ ስብሰባ ነገ ይካሄዳል
#ethiopia | ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም፤ የ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ 23ኛ መደበኛ ስብሰባውን ነገ ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ያካሄዳል።

ምክር ቤቱ በነገው ስብሰባው በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ ልማት ባንክ፣ እንዲሁም በኢትዮጵያ እና በዓለም አቀፍ የልማት ማኅበር መካከል የተደረጉ የብድር ስምምነቶችን ለማፅደቅ የወጡ ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

በሌላ በኩል ምክር ቤቱ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በሴራሊዮን ሪፐብሊክ፣ በአንጎላ ሪፐብሊክ፣ በባንግላዲሽ ሕዝባዊ ሪፐብሊክ እንዲሁም በኢስዋቲኒ ንጉሠ ነገሥት መንግሥታት መካከል የተፈረሙትን የሁለትዮሽ የአየር አገልግሎት ስምምነት ረቂቅ አዋጆች አስመልክቶ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ ያፀድቃል።

በተጨማሪም ምክር ቤቱ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በሩሲያ ፌዴሬሽን መካከል የጋራ የባዮሎጂ ምርምር ማዕከል ለማቋቋም የተፈረመውን ስምምነት ረቂቅ አዋጅ አስመልክቶ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ ረቂቅ አዋጁን ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

በተያያዘም በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. መንግሥት እና በቬትናም ሶሻሊስት ሪፐብሊክ መንግሥት መካከል የዲፕሎማቲክ ወይም የኦፊሻል የአገልግሎት ፓስፖርት ለያዙ ዜጎች ቪዛን ለማስቀረት የተፈረመውን ስምምነት ረቂቅ አዋጅ አስመልክቶ የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ ያፀድቃል።

በመጨረሻም ምክር ቤቱ የፌዴራል ታክስ አስተዳደር ማሻሻያ፣ የግብርና ቢዝነስ ኩባንያ፣ የምግብ ሥርዓትና ሥርዓተ ምግብ፣ የኢትዮጵያ የካርበን ገበያ እንዲሁም የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ለሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴዎች ይመራል ያለው መናኸሪያ ኤፍ ኤም ነው።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu

Getu Temesgen
13 hours ago
ሪያል ማድሪድ ለውሾች ማልያ አዘጋጀ !
#ethiopia | ሪያል ማድሪድ በዛሬው ዕለት በሚቀጥለው የውድድር ዘመን የሚጠቀመውን ማልያ ይፋ አድርጓል።

ሎስ ብላንኮዎቹ በአዱስ ማልያቸው ለውሻ የሚሆንም ማዘጋጀታቸውን አሳውቀዋል።

የክለቡ ደጋፊዎች ለውሾቻቸው በአዲዳስ የተዘጋጀውን ልዩ ማልያ ማግኘት እንደሚችሉ ተገልጿል።

ማልያው ለእንስሳቱ እንደሚመች ሆኖ በልዩነት መዘጋጀቱ ተነግሯል።

በዛሬው ዕለት በ 150 ዩሮ ለሽያጭ የቀረቡት የውሻ ማልያዎች ተሸጠው መጠናቀቃቸውን የክለቡ ይፋዊ ድረገጽ ያሳያል።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #tikvahethsport #sports #ጌጡተመስገን

Getu Temesgen
16 hours ago
የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት

ነገ ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን ኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች ፦

⏰ ከጠዋቱ 2:00-12:00

👉 በአዳማ ሪጅን አዳማ ቆርቆሮ፣
⏰ ከጠዋቱ 2:00-11:00
አዳማ ፈትል ፋብሪካ፣ ሬድሬስ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ፣ አህዋን ፋብሪካ

⏰ ከጠዋቱ 2:30-9:00

👉 በአዳማ ሪጅን ከአዋሽ መልካሳ ወደ አዱላላና አሮሪቲ፣

⏰ ከጠዋቱ 2:30-7:00

👉 በሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን አስኮ ገብርኤል፣ ሳንሱሲ፣ እያሱ ምንጭ፣ ብርጭቆ ኮንዶሚኒየም፣ ከታ አፍያ ዴቄት፣

⏰ ከጠዋቱ 3:00 እስከ ምሽቱ 4:00 ድረስ

👉 በደቡብ አዲስ አበባ ሪጅን ኬኬ ብርድ ልብስ ፋብሪካ፣ ቂሊንጦ ኮንዶሚኒየም፣ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት፣ አስቱ ዩኒቨርስቲ እና ኢንዱስትሪ መንደር፣ ዋልያ ቢራ

⏰ ከጠዋቱ 6:00-9:00

👉 በምዕረብ አደስ አበባ ሪጅን ስልጤ ሰፈር፣ አጃምባ ኮንዶሚኒየም

⏰ ከቀኑ 7፡00- 11፡00

👉 በሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን ሸጎሌ አንበሳ ጋራዥ፣ ሸጎሌ መንደር-7፣ ፊናንስ፣ አበበ ቢቂላ፣ ኳስ ሜዳ፣ መሳለሚያ

⏰ ከቀኑ 7:30-10:30

👉 በሽረ ረጅን እደጋ አርቢ፣ ማይ ቐንታል

ስለሆነም በአካባቢው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻች የጥገና ሥራው ተጠናቆ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትእግስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

​#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

Getu Temesgen
16 hours ago
♦️የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የሚያዘጋጀው ዓመታዊው የግማሽ ማራትን ውድድር እሁድ ይካሄዳል

♦️የተሻለ ውጤት የሚያስመዘግቡ በዴንማርክ ኮፐንሃገን አለም አቀፍ ውድድር ላይ ይሳተፋሉ

እ.ኤ.አ አቆጣጠር ሴፔቴምበር 20 ይካሄዳል ተብሎ ለሚጠበቀው የአለም አትሌቲክስ ግማሽ ማራቶን ውድድር አትሌቶች በወንድም በሴቶችም የሚመረጡበት የአዲስ አበባ ግማሽ ማራቶን ውድድር የፊታችን እሁድ ይካሄዳል።

ጅማሬውንና ፍፃሜውን መስቀል አደባባይ የሚያደርገውና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በየዓመቱ የሚያከናውነው 19ኛው የ21 ኪ.ሜትር የጎዳና ላይ ውድድር በርካታ አትሌቶች በወንድም በሴትም የሚሳተፉበት ሲሆን በውድድሩ የተሻሉ ሆነው የሚያጠናቅቁ አትሌትች በሁለቱም ፃታ ሀገራቸውን ወክለው ሴፕቴምበር 20 በዴንማርክ ኮፐንሃገን የግማሽ ማራቶን ውድድር ላይ የሚያሳትፋቸውን ትኬት ይቆርጣሉ።

የአለም የግማሽ ማራቶን(የጎዳና ውድድርን)በሁለቱም ፆታ ሪከርዱን የያዙት ኢትዮጵያዊያን አቴሌቶች ሲሆኑ በወንዶች አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ 57:30፣በሴቶች ደግሞ ለተሠንበት ግደይ 1:02:52 በሆነ ሠዓት በመግባትና በማሸነፍ የሪከርዱ ባለቤቶች ሆነዋል።

የአለም ግማሽ ማራቶን በዴንማርክ ኮፐንሃገን ሲካሄድ ከግማሽ ማራቶኑ በተጨማሪ የ5ኪ.ሜ እና የ1 ማይልስ ወይም የ1,609ኪ.ሜ ውድድርም እንደሚካሄድ ከተያዘው ፕሮግራም ለመረዳት ተችሏል።

ለሴፕቴምበር 20 የዴንማርክ ኮፐንሃገን የአለም አቀፍ ግማሽ ማራቶን የሚያሳልፈውን ትኬት የሚያስገኘው የአዲስ አበባው ግማሽ ማራቶን ውድድርን አስመልክቶ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የፊታችን ዓርብ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሠጥ ቀይፋዊ የፌስቡክ ገፁ አሳውቋል።

✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)

Getu Temesgen
21 hours ago
ዩናይትድ ተጨዋች ለማስፈረም ተስማማ !
#ethiopia | ማንችስተር ዩናይትድ ብራዚላዊውን አማካይ ኤደርሰን ከአታላንታ ለማስፈረም ከስምምነት ደርሰዋል።

ቀያዮቹ ሰይጣኖች ተጫዋቹን ተጨማሪ ክፍያን ጨምሮ በ 4️⃣5️⃣ ሚልዮን ዩሮ ለማስፈረም ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል።

ተጨዋቹ በማንችስተር ዩናይትድ ለተጨማሪ አንድ አመት የመቆየት አማራጭ ያካተተ የአራት አመት ውል ይፈርማል።

የ 26ዓመቱ አማካይ ኤደርሰን በቀጣይ የህክምና ምርመራውን እንደሚያደርግ ተዘግቧል።

ተጨዋቹ በሌሎች ታላላቅ ክለቦች ኢላማ ቢደረግም ማንችስተር ዩናይትድን ለመቀላቀል መምረጡ ተነግሯል።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #tikvahethsport #new #ethiopia #addisababa

Getu Temesgen
22 hours ago
ቀዝቀዝ ሞቅ የሚለው የሩስያ ዩክሬን ጦርነት ዛሬ ሌላ እልቂት አስመዝግቧል
#ethiopia | ​በሩሲያ እና ዩክሬን መካከል እየተካሄደ ባለው ጦርነት፣ ሩሲያ በቅርብ ጊዜ ውስጥ በዩክሬን ላይ የሰነዘረችው እጅግ ከፍተኛ የተባለው የአየር ጥቃት የ18 ሰዎችን ህይወት ማለፉ ተረጋግጧል።

ከተጎጂዎቹ መካከል የስምንት ዓመት ህጻን እና አንዲት ሴት ከፍርስራሽ ውስጥ አስከሬናቸው የተገኘ ሲሆን፣ በጥቃቱ ሳቢያ በድኒፕሮ 12 እንዲሁም በዋና ከተማዋ ኪየቭ 6 ሰዎች መሞታቸውን የሀገሪቱ ባለስልጣናት ገልጸዋል።

​የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ እንደተናገሩት፣ የሩሲያ ኢላማዎች በመላው ዩክሬን የሚገኙ የሲቪል መሰረተ ልማቶችና የኃይል ማመንጫ ተቋማት የነበሩ ሲሆን፣ ከሟቾቹ በተጨማሪ ከ100 በላይ ሰዎች ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል።

በሌላ በኩል ሩሲያ ጥቃቱን የፈጸመችው ቀደም ሲል 21 ተማሪዎች ለተገደሉበት ጥቃት ምላሽ ለመስጠት መሆኑን አስታውቃለች።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
​#የሩሲያ_ዩክሬን_ጦርነት #የአየር_ጥቃት #ዩክሬን #ሩሲያ #ሰብአዊ_ቀውስ

Getu Temesgen
22 hours ago
"እስከ መቼ?"

📌ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያናችን እና በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ።

ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ የኀዘን መልእክት እንደሚከተለው ነው፦

መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

‹‹ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦ የአገልጋዮችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት።››
(መዝሙረ ዳዊት ፸፰፥፪)

በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው።
የእምነት ነፃነት ተደፍሮ መቶ ዓመታት ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተቃጠለበት፣ እንዲሁም የካራ ኩፍቴና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በተዘረፈበት በዚህ ክፉ ቀን፤ በርካታ ምእመናን በግፍ መሰዋታቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬአቸው መፈናቀላቸው ቤተ ክርስቲያናችንን በእጅጉ ያሳዘነ ክስተት ነው።

የሰላም፣ የፍቅርና የታሪክ ማህደር የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በምድራዊ መከራ ውስጥ ያሉትን ምእመናን በምታጽናናበት በዚህ ወቅት ራሷ በፈተና ውስጥ ሆና ከመቸገሯም በላይ በአርሲ ምድር በተደጋጋሚ የሚስተዋለው በደልና ግፍ በሁላችንም ልቡና ውስጥ "እስከ መቼ?" የሚል የቁጭት እና የኀዘን ጥያቄን ፈጥሯል።

በመሆኑም ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን።

በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

በመጨረሻም ቤተ ክርስቲያናችን ለሰላም፣ ለይቅርታና ለሰው ልጆች ክብር ሁል ጊዜ የምትቆም መሆኑን በመግለጽ ይህንን የኀዘን ሰዓት አምላካችን በምሕረቱ ያሳልፍልን፣ የሞቱትን ነፍሶቻቸውን በመንግሥቱ ይቀበልልን፣ የተጎዱትንም በቸርነቱ ያጽናናልን በማለት አባታዊ የኀዘን መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።

እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
አሜን።

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

© የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት

Getu Temesgen
21 hours ago

እጅግ በጣም ልብ ይሰብራል

የሚካኤል ወዳጆች የት ናችሁ
ይህ የምትመለከቱት በሰሜን ሸዋ ሃገረ ስብከት ስር ያለው የሞዬ አማንጉልት አጣራ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ለ20 ዓመት በመጋረጃ ውስጥ ተከልሎ በመቃብር ቤት ውስጥ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ቢሆንም በአሁኑ ሰዓት ግን አባቶች በጠና እየታመሙ የድረሱልን ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል የቅዱስ ሚካኤል ወዳጆች የት አላችሁ እጃችሁን ዘርጉልን እያሉ እየተማፀኑ ይገኛሉ እንደምትመለከቱት ዙርያውን ክፍት ስለሆነ መቅደሱ የእንስሳ መራቢያ ሆኖ አባቶች ክፉኛ ችግር ውስጥ እየከተታቸው ይገኛል ስለሆነም ኦርቶዶክሳዊያን የሆንን ሁላችን ከ200 ብር ጀምሮ ለሚካኤል ቤተክርስቲያን ማሰሪያ ለንዋየተ ቅድሳት ማሟያ የሚሆነውን አስራታችሁንም በማውጣት ካላችሁ ላይ በመስጠት አሰሩልን ተራዱን ድረሱልን እያሉ ይገኛሉ

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቁጥር

1000392881879
የሞዬ አማንጉልት አጣራ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን 🙏✨

​📞 ለበለጠ መረጃ

0952530207

(እባክዎን የክርስትና ስምዎን በቴሌግራም ወይም በዋትሳፕ በዚሁ ስልክ ይላኩላቸው በፀሎት ያስቧችኋል)

​ሼር (Share) በማድረግ ድምፅ ሁኑልኝ! 🙏⛪
Getu Temesgen
24 hours ago
ሁሉም ነገር ሲፈራርስ!
#ethiopia ሁሉም ነገር እየፈራረሰ ሲመስል፣ የወደፊት ሕይወቴም አብሮ ከሽፏል ብሎ መደምደም ቀላል ነው። ነገር ግን የከሸፈ ሙከራ፣ የከሸፈ ፕሮጀክት፣ የፈረሰ ግንኙነት ወይም የከሸፈ እቅድ ማለት ወዲያውኑ የከሸፈ ሕይወት ይሰጠናል ማለት አይደለም።

የአለምን ታሪክ መለስ ብለን ብንመለከት የማይሰሩና የተበላሹ በርካታ አማራጮችን አሟጠው ከሞከሩ በኋላ አለቀ ሲሉ እንደገና ተነስተው ስኬታማ የሆኑ ሰዎችን እናገኛለን፡፡

እነዚህ ሰዎች . . .

1. ማንነታቸውንና ውጤታቸውን አያነካኩም

አንድ ነገራቸው ወደቀ ማለት እነሱ ውዳቂ እንዳልሆኑ ያምናሉ፡፡ ስለዚህ ማንነታቸውን በስኬታማነታቸው አይመዝኑትም፡፡

2. ውድቀትን ወደ ትምህርት ይቀይሩታል

ውድቀት ዋጋ የሚኖረው አንድ ነገር ሲያስተምራቸው ብቻ እንደሆነ ገብቷቸዋል፡፡ ስለዚህ ከሁሉ ልምምዳቸው ይማራሉ፡፡

3. ራሳቸውንና እቅዶቻቸውን ሰብሰብ ያደርጋሉ

ነገሮች ሲበላሹ፣ በአንድ ጊዜ ሁሉንም የወደፊት ሕይወታቸውን መስመር ለማስያዝ መሞከር አደገኛ እንደሆነ ስለሚያውቁ በቅርብ ርቀት ላይ ባለው ነገር ላይ ያተኩራሉ፡፡

4. በስሜት ከማሰብ ይጠነቀቃሉ

ሰዎች ሲደክሙ ወይም ተስፋ ሲቆርጡ፣ ስሜታቸውን እንደ እውነት የመውሰድ ዝንባሌ እንዳላቸው ያውቃሉ፡፡ ስለዚህ ስሜታቸውን በመግራት በምክንያታዊነት ያስባሉ፡፡

5. መቆጣጠር በሚችሉት ነገር ላይ ብቻ ያተኩራሉ

ብዙ ውድቀቶች ሰዎችን የሚያደናግጧቸው ከአቅማቸው በላይ በሆኑ ነገሮች ላይ ሙሉ በሙሉ ስሚያተኩሩ እንደሆነ ያውቃሉ፡፡ ስለዚህ ከእነሱ የቁጥር ቀጠና ውጪ የሆነውን በጸሎት ለፈጣሪ በመተው እነሱ ማድረግ የሚችሉት ላይ ያተኩራ፡፡

እኛም የእነሱን ምሳሌ እንከተል!

Dr eyob mamo

Getu Temesgen
1 day ago

u12abu122du1273u12cd u12f0u122du1237u120du1363u12e8u1263u1295u12ad u1265u12f5u122du121d u1270u1218u127bu127du1277u120du1363 u1241u120du134d u1208u1218u1228u12a8u1265 u12ddu130du1301 u1296u1275?

u1260u120du134bu1275 u12ebu1348u1229u1275u1295 u1325u122au1275 u12a0u1235u1270u121bu121bu129du1293 u12a8u134du1270u129b u1275u122du134d u1260u121au12ebu1235u1308u129d u12a2u1295u1268u1235u1275u1218u1295u1275 u120bu12ed u121bu12cbu120d u1265u120du1205u1290u1275 u1290u12cdu1362 u1325u122bu1271u1295 u12e8u1320u1260u1240 u12e8u1205u120du121du12ceu1295 u1264u1275 u12a0u1320u1293u1240u1295 u12a5u1290u1206 \
Getu Temesgen
1 day ago
#ethiopia | የአርሲ ዋይታ | የአይጥ መርዝ | ግብፅ የኢትዮጵያን የባህር በር ለማደናቀፍ እያሴረች | አዲስ አበባ የአሜሪካ የቪዛ ማዕከል

" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
Getu Temesgen
1 day ago
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በድል መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ገለጸ
#ethiopia | ከፍተኛ የዕጩ ተወዳዳሪዎች ቁጥር የተመዘገበበት ሰባተኛው አገራዊ ምርጫ በስኬታማ ሁኔታ መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።

የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ እንደገለጹት በአሁኑ ወቅት በየምርጫ ጣቢያዎቹ የተሰጡ ድምጾችን የማደመርና ውጤቱን ይፋ የማድረግ ተግባር በመከናወን ላይ ይገኛል።

በየምርጫ ጣቢያው የተሰበሰበው ድምፅ በይፋ ከተለጠፈ በኋላ ውጤቱ ተጠቃሎ ወደ የምርጫ ክልሉ ይላካል። በምርጫ ክልል ደረጃም የድምፅ ማጠቃለል ሥራው ከተከናወነ በኋላ ውጤቱን በይፋ ለማወጅና ለማረጋገጥ ወደ ዋናው መሥሪያ ቤት የማረጋገጫ ማዕከል እንዲመጣ ይደረጋል።

ውጤቶቹ ወደ ማረጋገጫ ማዕከሉ በሚደርሱበት ወቅት የእያንዳንዱ ምርጫ ክልል መረጃ በተናጠል ተለይቶ የሚታይ ሲሆን ተወዳዳሪዎች ያገኙት የድምፅ መጠን በዝርዝር የማጣራት ሥራ በትኩረት ይከናወናል።

ሰብሳቢዋ አክለውም በማዕከሉ ውስጥ ከተመዘገበው አጠቃላይ የመራጭ ሕዝብ ቁጥር አንጻር ጸንተው የሚደመሩ፣ ዋጋ የሌላቸው እና ጥቅም ላይ ያልዋሉ የድምፅ መስጫ ወረቀቶችን የመለየት ተግባር በከፍተኛ ጥንቃቄ እንደሚሠራ አስታውቀዋል።

ቦርዱ ይህንን የማረጋገጥ ሒደት በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ ውስጥ ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝም ሰብሳቢዋ ሜላትወርቅ ኃይሉ ገልጸዋል።
#ምርጫቦርድ #ምርጫ #የምርጫውጤት #የኢትዮጵያምርጫ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa

Getu Temesgen
1 day ago
በአዲስ አበባ ስታዲየም :
የዊ ሻምፒዮንስ ( We Champions 2026 )
የስፖርት ፌስቲቫል እየተሰናዳ ነው
#ethiopia | የአርሰናል እግር ኳስ ክለብ ከ22 ዓመታት ረጅም የጥበቃ ጊዜ በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ማሸነፉን አስመልክቶ፣ ይህንን ታሪካዊ ድል ለማክበር የተሰናዳውና በሀገራችን የመጀመሪያው ግዙፍ የስፖርት መድረክ የሆነው የዊ ሻምፒዮንስ 2026 ( We Champions 2026 ) የእግር ኳስ ፌስቲቫል በመጪው ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ስታዲየም በታላቅ ድምቀት እንደሚከናወን ተጠቁሟል።

በጎርደን ኢንተርቴይመንት አዘጋጅነት ለሚቀርበው ለዚህ ትልቅ ሁነት አዋሽ ባንክ በአፕክስ ኖብል ፕሮግራሙ አማካኝነት ዋነኛ ስፖንሰር በመሆን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል።

ይህ ልዩ መርሃ ግብር የስፖርቱን ፍቅር፣ ታማኝነትን፣ ባህልን፣ መዝናኛንና ስፖርታዊ እሴቶችን በአንድ ላይ በማስተሳሰር ከ30 ሺህ በላይ የእግር ኳስ አፍቃሪያንን፣ የዓለም አቀፍ ስፖርት ተዋናዮችንና እውቅ ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ ላይ የሚሰበስብ ሀገራዊ ፋይዳ ያለው የደስታ መግለጫ እንደሚሆን ይጠበቃል።

ዝግጅቱ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ በበለጠ ለማስተዋወቅ መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ሲሆን፣ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ የስፖርት መገናኛ ብዙኃንንና የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎችን ትኩረት በመሳብ የሀገሪቱን የቱሪዝም ፍሰት፣ የባህል ገጽታ እንዲሁም ትላልቅ ዓለም አቀፍ ኩነቶችን የማስተናገድ ብቃት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድግ ታምኖበታል።

በዕለቱ ከሚታደሙት የክብር እንግዶች መካከል የቀድሞው የአርሰናልና የቱኒዥያ ብሔራዊ ቡድን ተከላካይ ራዲ ጃይዲ የሚገኝበት ሲሆን፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተደራሽነትና ተፅዕኖ ካላቸው የእግር ኳስ ሚዲያ አንዱ የሆነው የኤኤፍቲቪ መስራቾችና ተወካዮችም በዝግጅቱ ላይ ለመሳተፍ ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ መረጋገጡን በመግለጫው ላይ አስታውቀዋል።

ወደ ስታዲየም ለመግባት የሚያስችሉ የትኬት ሽያጮችን አስመልክቶ አዘጋጆቹ በሰጡት ማብራሪያ፣ መግቢያ ትኬቶችን ማግኘት የሚቻለው በአዋሽ ባንክ የአፕክስ ኖብል ፕሮግራም በኩል ብቻ መሆኑን ገልጸዋል።

የመዝናኛ ክፍሉን ይበልጥ ማራኪና ድምቅ ለማድረግ ከአስር በላይ ታዋቂና ወጣት የሙዚቃ አርቲስቶች የተጋበዙ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል ታደለ ሮባ፣ ልጅ ሚካኤል (ፋፍ)፣ ሳሚ ዳን፣ አስማማው እሸቱ፣ ራሄል ጌቱ፣ ሮማን ማይክ፣ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ሚካ ያኖ፣ አማኑኤል የማነ፣ አዲስ ሙላት፣ እዩ ፀጋ እና ኩሉ ሱሌ ይገኙበታል።

የአዲስ አበባ ስታዲየም ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ ለታዳሚዎች ክፍት የሚሆን በመሆኑ፣ ተመልካቾች በጊዜ በመገኘት ቦታቸውን እንዲይዙ አዘጋጆቹ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
#wechampions2026 #arsenal #awashbank #apexnoble #gordonentertainment #aftv #radhijaidi #footballfestival #ethiopiantourism #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa

Getu Temesgen
1 day ago
የግብፅን የኢትዮጵያ የባህር በር ጥረት ማደናቀፍ እንቅስቃሴ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ኮነነ
#ethiopia | የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ግብፅ ሀገሪቱ የወደብ ባለቤት እንዳትሆን እያደረገች ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ጫና እና የእንቅፋት ፈጠራ ስትራቴጂ አጥብቆ ተቃውሟል።

የቀይ ባህር ጉዳይ የሚመለከተው የባህር ዳርቻ ያላቸውን ሀገራት ብቻ ነው በማለት በግብፅ በኩል የሚሰነዘረውን አቋም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ፍጹም ተቀባይነት የሌለው ሲሉ አጣጥለውታል።

በተጨማሪም ግብፅ በቅርቡ ከኤርትራ፣ ሶማሊያ እና ሱዳን ጋር የመሰረተችው ወታደራዊ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ትብብር ኢትዮጵያን በዲፕሎማሲው መድረክ የማግለልና የመክበብ ስልት አካል ተደርጎ ተወስዷል።

ይህ አዲስ ውጥረት ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድርድር አለመግባባት ጋር የተያያዘ ቢሆንም፣ ኢትዮጵያ ግን የወደብ ባለቤት ለመሆን የጀመረችውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት በቁርጠኝነት እንደምትቀጥል አስታውቃለች።

በተለይም ከሶማሊላንድ ጋር የተፈረመውን የመግባቢያ ሰነድ ጨምሮ፣ ሀገሪቱ ያላትን የባህር በር የማግኘት ህጋዊ ፍላጎት በማናቸውም ውጫዊ ጫና ሳትበገር በሰላማዊ መንገድ እንደምታስፈጽም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በድጋሚ አረጋግጧል።
#ግብፅ #የባህርበር #የቀይባህር #የህዳሴግድብ #ዲፕሎማሲ #የአፍሪካቀንድ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa

Getu Temesgen
1 day ago
የአሜሪካ መንግሥት ከአፍሪካ ቪዛ አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን መካከል ኢትዮጵያን አልቀነሳትም
#ethiopia | የአሜሪካ መንግሥት በአፍሪካ አህጉሉአንዳ የሚሰጠውን የቪዛ አገልግሎት በከፍተኛ ደረጃ ለማሻሻል እየተዘጋጀ ነው።

በዚህ መሠረት በአፍሪካ ውስጥ የቪዛ አገልግሎት የሚሰጡ የአሜሪካ ኤምባሲዎችና ቆንስላዎች ቁጥር ከ50 ወደ 20 ብቻ ለመቀነስ ወስኗል። ይህ ለውጥ በቅርብ ጊዜያት ይጀመራል ተብሏል።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ያጸደቁት ይህ አዲስ እቅድ፣ በአፍሪካ 20 ዋና የክልል ማዕከላት (Regional Hubs) በመሾም፣ ሌሎች ቦታዎችን የቪዛ ሙሉ አገልግሎት እንዳይሰጡ ለመዝጋት ያቀደ ነው።

እነዚህ የ20 ዋና ማዕከላት የትኞቹ ናቸው ፦

° አዲስ አበባ (ኢትዮጵያ) 🇪🇹
° አክራ (ጋና) 🇬🇭
° ዳካር (ሴኔጋል) 🇸🇳
° ጅቡቲ (ጅቡቲ) 🇩🇯
° ካምፓላ (ኡጋንዳ) 🇺🇬
° ኪጋሊ (ሩዋንዳ) 🇷🇼
° ኪንሻሳ (ኮንጎ) 🇨🇩
° ላጎስ (ናይጄሪያ) 🇳🇬
° ናይሮቢ (ኬንያ) 🇰🇪
° አቢጃን (አይቮሪ ኮስት) 🇨🇮
° ዳሬሰላም (ታንዛኒያ) 🇹🇿
° ሎሜ (ቶጎ) 🇹🇬
° ሉዋአንዳ (አንጎላ) 🇦🇴
° ማላቦ (ኢኳቶሪያል ጊኒ) 🇬🇶
° ሞንሮቪያ (ላይቤሪያ) 🇱🇷
° ፖርት ሉዊስ (ሞሪሸስ) 🇲🇺
° ፕራያ (ኬፕ ቨርዴ) 🇻🇪
° ያውንዴ (ካሜሩን) 🇨🇲
° ኬፕ ታውን (ደቡብ አፍሪካ) 🇿🇦
° ጆሃንስበርግ (ደቡብ አፍሪካ) 🇿🇦

ከእንግዲህ ወዲያ በእነዚህ 20 ማዕከላት ያልተካተቱ ሀገራት ዜጎች የቪዛ ቃለ መጠይቅ፣ የጣት አሻራ እና ሌሎች ሂደቶችን ለማጠናቀቅ በራሳቸው ወጪ ወደ ቅርብ ማዕከል መጓዝ ይጠበቅባቸዋል ተብሏል ያለው ቲክቫህ ነው።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu

Getu Temesgen
2 days ago
"ኢትዮጵያ በመከፋፈል ሳይሆን በአንድነት የደመቀ... አገር ሆና እንድትቀጥል ለማየት ነው ምኞታችንና ጸሎታችን!!"
#ethiopia | የዘንድሮውን የ7ኛ ዙር አገራዊ ምርጫ ለመታዘብ የሚያስችለኝን ዕድል አግኝቼ ነበር። እናም በግልና የተለያዩ ተቋማትን ወክለን የመጣን የአገር ውስጥ ታዛቢ ቡድን አባላት ምርጫውን ለመታዘብ ከመጡ የአፍሪካ ኅብረት እና የኢጋድ የታዛቢ ቡድን አባላት ጋር በስካይ ላይት ሆቴል የትውውቅና ሰፋ ያለ የጋራ ውይይት አድርገን ነበር።

በዚህ ውይይት ላይም የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪና የቀድሞ የኡጋንዳ የቀድሞው ምክትል ፕሬዚደንት የነበሩት ዶ/ር ዋንዲራ ካዚብዌ በምክር መልኩ ለወጣቶች ያነሱት ሐሳብ ቀልቤን ገዛው። እናም ከእኚህ ጉምቱ ፖለቲከኛ አፍሪካዊ እናት ከሐሳባቸው ጥቂት ሰበዞችን ለመምዘዝ ወደድኹ።

በአገራቸው ኡጋንዳ ፖለቲካ ውስጥ የሴቶችን/የእናቶችን የፖለቲካ ተሳትፎ ትርጉም ባለው መንገድ በመቀየር ጉልህ አሻራ ያኖሩት የህክምና ሳይንስን ከሥነ-መንግሥት ትምህርት ጋር ያጣጣሙ እኚህ አፍሪካዊ ምሁር እናት በውይይታችን መካከል እንዲህ አሉን።

"When women lead, even water climbs uphill."
"ሴቶች ሲመሩ ውኃ ሳይቀር እንኳን ሽቅብ ይፈሳል፤" የሚል አፍሪካዊ አባባል አለ።

መቼም ለዚህ አባባል እናንት ኢትዮጵያውያን ሕያው ምስክሮች ናችሁ። ከኢትዮጵያዊቷ ንግሥት ሳባ፣ የዐድዋውን ጦርነት በሴትነት ብልሃት ከመሩት እቴጌ ጣይቱ ድረስ የአገራችሁ የፖለቲካ ታሪክ በሴቶች ጉልህ ተሳትፎና አሻራ የደመቀ ነው።

በእውነት በእነዚህ ጀግኖች እናቶቻችሁ ታሪክ ልትኮሩ፤ ልትደነቁ ይገባችኋል።

ዶ/ር ካዚብዌ ቁጭት በቀላቀለ ስሜት ያነሱትን ሌላኛው የሐሳባቸውን ሰበዝ ለዚህች አጭር ማስታወሻ መደምደሚያ ይሆነኝ ዘንድ መረጥኩት።

እኛ አፍሪካውያን ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን እንደ ሸቀጥ ዕቃ ሙሉ በሙሉ ከምዕራቡ ዓለም ለማስገባት የምናደርገውን ልፋት ቆም ብለን መፈተሽ ይገባናል። ከሌሎች የምንቀበለውን ያህል እኛ አፍሪካውያን ለተቀረው ዓለም ልንሰጠው የምንችላቸው በርካታ ነገሮች አሉን።

አፍሪካ ለሺህ ዓመታት የቆየ የራሷ የሆነ ግዙፍ ታሪክ፤ ገናና ሥልጣኔ፤ በዘመናት ተፈትኖ ያለፈ የዳበረ ባህላዊ የፖለቲካ ሥርዓት ያላት አህጉር ናት። እናንት ኢትዮጵያውያን ደግሞ በዚህ የአኅጉራችን የአፍሪካ የሺህ ዘመናት ታሪክና ባህል ውስጥ የአንበሳውን ድርሻ ትወስዳላችሁ።

ከአክሱም ገናና ሥልጣኔ የቅኝ ገዢዎችንና የተስፋፊዎችን ቅስም እስካንኮታኮተው የዐድዋ ድል ድረስ አኩሪ ታሪክ ያላችሁ ታላቅ ሕዝብ ናችሁ።

አብዛኛው የታሪካችሁ ምዕራፍ ሲገለጽም- የአንድነትን፤ የኅብረትን ኃይል ቀድሞ የተረዳችሁ ጠቢባን ሕዝቦች መሆናችሁን ነው የሚመስክረው። እናም ዛሬ ልዩነታችሁን በማጥበብ አንድነታችሁን አጠናከሩ፤ ኅብረታችሁን አጎልብቱ። አንድነት ኃይል ነው!!

ኢትዮጵያ በመከፋፈል ሳይሆን በአንድነት የደመቀ፤ በጦርነት ሳይሆን በሰላም ያሸበረቀ፤ በጥላቻ ሳይሆን በፍቅር የተዋበ አፍሪካዊ ተምሳሌትነቷንና እናትነቷን ያስመሰከረች አገር ሆና እንድትቀጥል ነው ምኞታችን፤ ተስፋችንና ጸሎታችን።

እግዚአብሔር አፍሪካን ይባርክ፤ አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!!

ነገርን ነገር ያነሳዋል እንዲሉ አበው፤ ጠቅላይ ሚ/ር ዶ/ር ዐብይ አሕመድ ወደ ሥልጣን በመጡ ማግሥት- ኢትዮጵያውያን እናቶች ይጸልዩልኛል፤ የእናቶቼ ጸሎታቸውና ምርቃታቸው ያግዘኛል፤ ጉልበት ይሆነኛል። የሚል ቃልን አብዝተን ከአንደበታቸው አንሰማ ነበር። ዛሬስ...?!

ታላቁ መጽሐፍ፤ "የእናት ምርቃት ቤትን ያጸናል፤" እንዲል በእናቶቻችን ምርቃትና ጸሎት የሁላችን ቤት የሆነች ኢትዮጵያ፤ አፍሪካ የአንድነት መሠረቷ ጸንቶና ሰላሟ ተጠብቆ በአንድነት ጸንታ ትኖር ዘንድ በመመኘት ልሰናበት።

ሰላም!!

በተረፈ ወርቁ (ዲ/ን)፤

Getu Temesgen
2 days ago
ምርጫው የኢትዮጵያ አሸናፊነት የተረጋገጠበት ነው፦ የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት
#ethiopia | የአዲስ አበባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደትን መጠናቀቁን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።

ምርጫው ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ ግልጽነት እና ፍትሐዊነት የተንጸባረቀበት፣ በመራጩ ሕዝብና በተፎካካሪ ፓርቲዎች ዘንድ ከፍተኛ ቅቡልነት ያገኘ መሆኑን በመግለጫው አስታውቋል።

ምክር ቤቱ በመግለጫው እንዳመለከተው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደው ይህ ምርጫ መንግሥት በከተማዋ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ላይ ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየበትና የኢትዮጵያ አሸናፊነት የተረጋገጠበት ሌላኛው ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኖ አልፏል።

ከእነዚህም መካከል እንደ ትልቅ ጅምር የሚወሰደው የዲጂታል የእጩዎች ምዝገባ ሒደት አላስፈላጊ መጉላላትን የቀነሰ እና የእጩዎችን መረጃ እና ደኅንነት ያረጋገጠ የአሰራ ግልፅነትን የፈጠረ መሆኑ በምርጫው ሂደት ከታዩ ዐበይት አዎንታዊ ሁነቶች መካከል እንደሆነ ተመላክቷል።

በምርጫው ዕለት መላው የከተማዋ ነዋሪዎች ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ ያለምንም ቀስቃሽ በነቂስ በመውጣት ድምፅ መስጠታቸውን የገለጸው ምክር ቤቱ፣ በተለይም ሴቶች፣ ወጣቶች እና አረጋውያን ያሳዩት ከፍተኛ ተነሳሽነት ሂደቱን ይበልጥ እንዳደመቀው አብራርቷል።

ከምርጫ ጣቢያዎች የሚመጡ የአሠራር ችግሮችን በጋራ በመገምገም፣ ከምርጫ ቦርድ እና ከከተማው አመራሮች ጋር በቀጥታ በመነጋገር አፋጣኝ የእርምት እርምጃ መወሰዱ በፓርቲዎች እና በአስፈፃሚ አካላት መካከል መተማመንን ማጎልበቱ ተገልጿል።

በተጨማሪም የከተማዋ የጸጥታ አካላት ያለምንም ወገንተኝነት፣ ፍጹም ገለልተኛ በሆነ መንገድ የምርጫ ጣቢያዎችን እና የመራጩን ሕዝብ ደኅንነት በመጠበቅ ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምክር ቤቱ ምስጋና አቅርቧል።

በሂደቱም ምንም ዓይነት የጸጥታ መደፍረስም ሆነ የምርጫ ሕግ መጣስ ሳይኖር መጠናቀቁ የከተማዋን ነዋሪዎችና የጸጥታ አካላት ከፍተኛ የበስለት ደረጃ ያሳየ "የአዲስ አበባ ሞዴል" መሆኑ ተነግሯል።

የድምፅ መስጠት ሂደቱ በስኬት ተጠናቅቆ ወደ ቀጣዩ የድምፅ ቆጠራ እና ውጤት ማደራጀት ምዕራፍ መሸጋገሩን የጠቀሰው ምክር ቤቱ፤ የምርጫ ቦርድ ሕጋዊ አሠራርን መሠረት አድርጎ የከተማውን ውጤት በኦፊሴላዊ መልኩ እስኪገልጽ ድረስ መላው የከተማዋ ነዋሪዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች አባላት እና ደጋፊዎች ፍጹም በሆነ ትዕግሥት እንዲጠብቁ ጥሪ አቅርቧል።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ethiopia #ethiopiaprevails #peace #ምርጫ

Getu Temesgen
2 days ago
ይቺም ሻማ ሰልችታለች‼️
#ethiopia | በአገራችን ለሚቀጥሉት ብዙ አሥርት ዓመታት ምናልባትም አሁን በሕይወት የምንገኝ ሰዎች በአጠቃላይ ሳናይ የምንሞተው ነገር የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ''ኃላፊነቴን በአግባቡ ስላልተወጣሁ ሥራዬን በፈቃዴ ለቅቄያለሁ፤ ከ'ኔ የተሻለ ሰው ይምራው'' የሚለው ነው።

በአርሲ ዞን በኦርቶዶክስ ክርስትና አማኞችና አብያተ-ክርስትያናት ላይ በተደጋጋሚ ጥቃቶች እየተሰነዘሩ ብዙ ሰው በአሰቃቂ ሁኔታ ሞተ፤ አብያተ-ክርስትያናትና ቅርሶችም ወደሙ፤ በነዋሪዎቹ ዘንድ ሥጋትና ጥርጣሬ ሰፈነ።

ይሄን ተደጋጋሚ ጥቃት ለማስቀረት የተሠራ ሥራ አለ? ሰላም ማስከበር 100% የክልሉ መንግሥት ሥራ አይደለም እንዴ? ምን አድርጓል? ሰላም ማስከበር ካቃታቸው በኢትዮጵያ ሕግ መሠረት ''አልቻልንም፤ የፌዴራል መንግሥት ጣልቃ ይግባልን'' ይባላል እኮ! መቼም ''እኔ ለዚህ ኃላፊነት ብቁ ሆኜ አልተገኘሁም፤ የተሻለ ብስለትና ልምድ ያለው ሰው ይተካኝ'' የሚሉ ኃላፊዎችን በሕይወት እያለን እንደማናይ ዕሙን ነው።

ሰው ባለቀ ቁጥር ይቺን ሻማ ብልጭ ማድረግ ምን ፋይዳ አለው? ይሰለቻል። የክልሉ መንግሥት ለዚህ ዞን ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ሕዝቡን ይጠብቅ። በጊዜ መፍትሔ ካልተሰጠው የዚህ ዳፋ የማይተርፈው ሰው የለም።

እንደ አንድ ተርታ ዜጋ በደረሰው ጉዳት ሐዘኔን ለመግለጽ እወዳለሁ።

ሐውለት አሕመድ-

Getu Temesgen
2 days ago
ዝነኛው AFTV (Arsenal Fan TV) ወደ ኢትዮጵያ ሊመጣ ነው!
#ethiopia | ​የዓለማችን ትልቁና ተፅዕኖ ፈጣሪው የክለብ ደጋፊዎች ሚዲያ AFTV፣ በኢትዮጵያ የሚገኘውን እጅግ በርካታ የአርሰናል ደጋፊ ማህበረሰብ ለመጎብኘትና ልዩ ዝግጅቶችን ለማድረግ ጉዞውን ወደ አዲስ አበባ ሊያደርግ መሆኑ ታውቋል።

ይህ ጉብኝት በኢትዮጵያ ስፖርታዊ ሚዲያና በደጋፊዎች መካከል አዲስ መነቃቃትን ይፈጥራል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ የለንደኑ ክለብ በሀገራችን ያለውን ታላቅ ተወዳጅነት ለዓለም ይበልጥ የሚያሳይ ትልቅ አጋጣሚ ይሆናል።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
​#aftv #arsenalfantv #arsenalethiopia #coyg #addisababa #gooners #ethiopiangooners #aftvinethiopia

Getu Temesgen
2 days ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ያለው የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በይፋ መርቀው ሥራ አስጀመሩ
#ethiopia | ‎ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ማግስት፣ ዛሬ ጠዋት ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ያለውን የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት መርቀው በይፋ ሥራ ማስጀመራቸውን ገልጸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጽ ባሰፈሩት መልዕክት፣ ‎ይህ ትልቅ ተነሣሽነት፤ የተራቆቱ አካባቢዎችን በዘመናዊ የአፈር ጥበቃ እና በወንዝ ማጣራት ወደ አረንጓዴ ስፍራዎች በመቀየር፣ የፍራፍሬ ፓርኮችን ከእግር ጉዞ እና ከብስክሌት መንገዶች ጋር በማቀናጀት መዲናችንን አድሷል ብለዋል።

‎በአጠቃላይ 22.25 ኪሎ ሜትር የወንዝ ዳርቻ ልማትን የሚሸፍነው ይህ ፕሮጀክት፣ የማይቆራረጥ የልማት ሥራችን ሕያው ምስክር ከመሆኑም በላይ የሀገራዊ ዕድገታችን፣ የአካባቢ ጥበቃ እና የከተማ እድሳት በተግባር የታየበት ነው ሲሉም አክለዋል።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu

Getu Temesgen
2 days ago
ተፈጸመ
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ፣ ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ካቴድራል ( አማኑኤል አጂፕ ) ከቀኑ 6:00 ሰዓት ተፈጽሟል።

ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ተከናወናል።

***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው
አጭር የህይወት ታሪክ

የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።

ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡

በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡

አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡

በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡

አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡

አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ

1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡

2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤

3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡

4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡

5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡

6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡

7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡

8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡

9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡

10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡

11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡

12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡

13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡

ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-

Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት

Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር

Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ

Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ

Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት

Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡

አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡

አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን

Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል

Ø በሚሊንየም አዳራሽ

Ø በኢግዚብሽን ማዕከል

Ø በመስቀል አደባባይ

Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም

Ø በጊዮን ሆቴል

Ø በሂልተን ሆቴል

Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡

አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦

Ø ጤና ያጣ ፍቅር

Ø ሮሚዮና ጁሌት

Ø የቀለጠው መንድር

Ø ሊስትሮ ኦፔራ

Ø ከልሺን አውልቂ

Ø ፎርፌ

Ø ኦቴሎ

Ø ቴዎድሮስ

በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-

Ø ፎርፌ

Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው

Ø ከልሽን አውልቂ

Ø ሊስትሮ ኦፔራ

Ø ሉሲ

Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡

በፊልም ትወና፡-

Ø በህይወት ዙሪያ

Ø ሔሮሽማ

አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡

Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ

Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡

አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡

ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡

ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡

አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡

የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።

የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡

የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa

Getu Temesgen
2 days ago
ካናዳ : አንጋፋዋ ዘማሪት አዲስ ለማ የዝማሬ አልበም አስመረቀች
#ethiopia | ታዋቂዋ የቤተክርስቲያን አገልጋይ ዘማሪት አዲስ ለማ በአዲስ አበባ ብሔራዊ ቴአትር ጀርባ በሚገኘው ታላቁ የቅዱስ ቂርቆስ ወኢየሉጣ ቤተክርስቲያን ውስጥ በአገልግሎት ያደገች ሲሆን ይህ ደብር በርካታ ታዋቂ ዘማርያንን በማፍራት የሚታወቅ ታሪካዊ ቦታ ነው።

ዘማሪት አዲስ ወደ ውጭ ሀገር ከመጓዟ በፊት በኢትዮጵያ ውስጥ በነበራት ሰፊ አገልግሎት ከፍተኛ አክብሮትን ያተረፈች ሲሆን በተለይም ለምኝ ድንግል ለምኝ፣ በመከራ ፅና፣ ምድረ ቀራንዮ እና ተነሺ ኢትዮጵያ የተሰኙት ዝማሬዎቿ ሁልጊዜ በምእመናን ልብ ውስጥ የሚታወሱ ተወዳጅ ሥራዎቿ ናቸው።

ከሀገር ወጥታ በደቡብ አፍሪካ በኩል አድርጋ በምዕራብ ካናዳ ሀገረ ስብከት አገልግሎቷን የቀጠለችው ዘማሪት አዲስ ለማ፣ በቅርቡ ካጋጠማት አስከፊ የመኪና አደጋ በተአምር ተርፋ ዛሬ ላይ አዲስ የዝማሬ አልበሟን በበርካታ ወንድሞችና እህቶች ታጅባ በደማቅ ሁኔታ አስመርቃለች።

በአገልግሎቷ ጥንካሬ ብቻ ሳይሆን በደግነቷ የምትታወቀው ዘማሪት አዲስ፣ ከዚህ አዲስ አልበም ምርቃት የሚገኘውን ገቢ ሙሉ በሙሉ በካናዳ ካልጋሪ ለሚገኘው የደብረ ፀሐይ ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ሕንፃ ግዢ እንዲሆን በስጦታ አበርክታለች።

ይህ በጎ ተግባር በብዙዎች ዘንድ አድናቆትን ያተረፈ ሲሆን ለአገልጋይዋም መልካም ምኞቶች እየቀረቡላት ይገኛል።
#mezmur #orthodox #ethiopianorthodox #canada #calgary #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa

Getu Temesgen
2 days ago
የህዳሴ ግድብና የቀይ ባህር ዲፕሎማሲ፡ የኢትዮጵያ አዲስ ጂኦፖለቲካዊ ምዕራፍ
#ethiopia | በ21ኛው ክፍለ ዘመን የአገራት ኃይል የሚለካው በወታደራዊ አቅም ብቻ ሳይሆን የኢኮኖሚ፣ የኢነርጂ፣ የውሃ እና የጂኦፖለቲካ ተጽዕኖ በመፍጠር ጭምር ነው።

በዚህ መሠረት ኢትዮጵያ ባለፉት አስርት ዓመታት ውስጥ በሁለት ታላላቅ ብሔራዊ አጀንዳዎች ዙሪያ የተለየ የዲፕሎማሲ ጉዞ አድርጋለች።

እነዚህም የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እና የቀይ ባህር ተደራሽነት ጉዳይ ናቸው።

ሁለቱም ጉዳዮች ከኢኮኖሚ ጥቅም ባሻገር የአገሪቱን የህልውና ጥያቄ፣ የቀጣናዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነት እና የወደፊት የልማት አቅጣጫ የሚወስኑ ናቸው።

በእነዚህ መስኮች የተመዘገቡ ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶችም ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ እና በምሥራቅ አፍሪካ እየተጠናከረ የመጣ የኃይል ማዕከል መሆኗን አመላክተዋል።

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ከፍተኛ ዓለም አቀፍ ትኩረት የሳበ ፕሮጀክት ነበር።

በተለይም የዓባይ ውሃ አጠቃቀምን በተመለከተ በታሪክ የተፈጠሩ የፖለቲካ እና የጂኦፖለቲካ አለመግባባቶች ግድቡን ከቀላል የልማት ፕሮጀክት ወደ የዲፕሎማሲ ፈተና ቀይረውት ነበር።

ሆኖም ኢትዮጵያ “ፍትሐዊና ምክንያታዊ የውሃ አጠቃቀም” እንዲሁም “በሌሎች ላይ ጉልህ ጉዳት አለማድረስ” በሚሉ ዓለም አቀፍ መርሆዎች ላይ ተመስርታ የተከተለችው የዲፕሎማሲ መንገድ ትልቅ ውጤቶችን አስመዝግቧል።

ከተመዘገቡት ታላላቅ ድሎች አንዱ የግድቡ ጉዳይ በአፍሪካ ሕብረት ማዕቀፍ እንዲመራ ማድረግ ነው።

ጉዳዩን ወደ ዓለም አቀፍ የፖለቲካ መድረኮች በመውሰድ ጫና ለመፍጠር የተደረጉ ጥረቶች ቢኖሩም፣ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ችግሮች በአፍሪካውያን መፍትሔ ሊያገኙ ይገባል የሚለውን መርህ በተግባር አስከብራለች።

ይህ የዲፕሎማሲ ድል ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው አፍሪካ የተቋማዊ ነጻነት እና የአህጉራዊ ትብብር ማሳያ ሆኗል።

ሌላው ታላቅ ስኬት የግድቡ ግንባታ በውጭ ጫናዎች ሳይቆም እስከ መጨረሻው የውሃ ሙሌት መድረሱ ነው።

በሕዝብ ገንዘብና በብሔራዊ አንድነት የተገነባው ግድብ የኢትዮጵያን የራስ አቅም እና የውጭ ጫናን የመቋቋም ችሎታ አሳይቷል።

ዛሬ ግድቡ የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት ለአጎራባች አገራት ለሚደረገው የኃይል ሽያጭ መሠረት ሆኗል። ይህም ግድቡ የግጭት ምንጭ ሳይሆን የቀጣናዊ ትስስርና የጋራ ልማት መሣሪያ መሆኑን በተግባር አረጋግጧል።

የህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያን ከተራ የኤሌክትሪክ አምራች ወደ የቀጣናው የኢነርጂ ማዕከል እየቀየራት ነው። ለጅቡቲ፣ ለኬንያ፣ ለሱዳን እና ለሌሎች አገራት የኃይል አቅርቦት መስፋፋቱ የኢኮኖሚ ትስስርን ከማጠናከሩም በላይ የፖለቲካ መተማመንን እየፈጠረ ነው።

ኢትዮጵያ ከ120 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላትና ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያሳየች ያለች አገር ብትሆንም፣ የባሕር በር አልባ መሆኗ ለንግድ፣ ለኢኮኖሚ እና ለብሔራዊ ደኅንነት ከፍተኛ ፈተና ሆኖ ቆይቷል።

በቅርብ ዓመታት ግን ኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄዋን ከታሪካዊ ቅሬታ ወደ ስትራቴጂካዊ ዲፕሎማሲ ቀይራለች።

ከሶማሊላንድ ጋር የተፈረመው የመግባቢያ ሰነድ (MoU) በዚህ ረገድ ታሪካዊ እርምጃ ተብሎ ይታያል። ይህ እርምጃ ኢትዮጵያ የባሕር በር ፍላጎቷን በሰላማዊ እና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለማሳካት ያላትን ቁርጠኝነት አሳይቷል።

ይህ የዲፕሎማሲ አቅጣጫ ኢትዮጵያ ከአንድ ወደብ ብቻ ጥገኛ የመሆን አደጋን ለመቀነስና የንግድ ወጪዋን ለመቆጣጠር የሚያስችል አዲስ የጂኦኢኮኖሚ አስተሳሰብ እንዳላት አሳይቷል።

ቀይ ባህር ከዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮች አንዱ እንደመሆኑ መጠን በዚህ አካባቢ የሚፈጠሩ የደኅንነት ችግሮች በቀጥታ ኢትዮጵያን ይነካሉ።

በመሆኑም ኢትዮጵያ በቀይ ባህር ጉዳይ ተመልካች ሳይሆን ንቁ ባለድርሻ መሆን እንዳለባት በዲፕሎማሲ መድረኮች ላይ በግልጽ ማስቀመጥ ችላለች። ይህም የአገሪቱን የጂኦፖለቲካ ተጽዕኖ እያሳደገ ነው።

የህዳሴ ግድብና የቀይ ባህር ዲፕሎማሲ በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ቢመስሉም፣ የጋራ ዓላማ አላቸው። ይህም ኢትዮጵያን በኢኮኖሚ፣ በኢነርጂ እና በጂኦፖለቲካ የቀጣናው የኃይል ማዕከል ማድረግ ነው።

የህዳሴ ግድብ የኢነርጂ ተጽዕኖን ሲፈጥር፣ የቀይ ባህር ዲፕሎማሲ ደግሞ የንግድና የስትራቴጂካዊ ተደራሽነትን ያጠናክራል። ሁለቱም ተደጋጋፊ ሲሆኑ የኢትዮጵያን የወደፊት ኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ኃይል ለመገንባት ወሳኝ ሚና አላቸው።

በህዳሴ ግድብና በቀይ ባህር ጉዳዮች ዙሪያ የታዩት የዲፕሎማሲ ስኬቶች ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሞቿን በውይይት፣ በጽናት እና በስትራቴጂካዊ አመራር ማስከበር እንደምትችል አረጋግጠዋል።

ይሁን እንጂ እነዚህ ድሎች ዘላቂ ውጤት እንዲያመጡ የውስጥ አንድነትን ማጠናከር፣ ከጎረቤት አገራት ጋር በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ ግንኙነት መገንባት እና የሰላም ዲፕሎማሲን ማስቀጠል አስፈላጊ ነው።

የህዳሴ ግድብ የኢነርጂ ነፃነትን ሲያመጣ፣ የቀይ ባህር ዲፕሎማሲ ደግሞ የኢትዮጵያን የጂኦፖለቲካ ተደራሽነት ያሰፋል። ሁለቱም ተደምረው ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ ተጽዕኖ ፈጣሪ አገር ወደማድረግ እየመሯት ነው።

ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር

Getu Temesgen
2 days ago
በደቡባዊ ጣሊያን የባህር ዳርቻ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ
#ethiopia | በዛሬው ዕለት በማለዳው ክፍለ ጊዜ በደቡባዊ ጣሊያን የባህር ዳርቻ አካባቢ በሬክተር ስኬል መለኪያ 6 ነጥብ 1 የደረሰ ኃይለኛ የመሬት መንቀጥቀጥ ማጋጠሙ ተገልጿል።

የጀርመን የጂኦሳይንስ ምርምር ማዕከል ይፋ ባደረገው መረጃ መሠረት ይህ የተፈጥሮ አደጋ የተከሰተው ከምድር ወለል በታች 253 ኪሎ ሜትር ጥልቀት ላይ ነው።

አደጋው በተለይ ማክሰኞ ሌሊት በፈረንጆቹ አቆጣጠር ንጋት ላይ የተመዘገበ ሲሆን ስለደረሰው ጉዳት ዝርዝር መረጃዎች እየተሰበሰቡ ይገኛሉ።
#italy #earthquake #seismic #worldnews #europe #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa