Logo
Getu Temesgen
2 hours ago

u12e8 Zadok Perth International Ministry, Ethiopia u1275u121du1205u122du1276u127du1293 u1235u1265u12a8u1276u127d! u2728
#ethiopia | u200bu1260u12a0u12cdu1235u1275u122bu120au12eb \
Getu Temesgen
4 hours ago
“የፊታችን አራት ዓመት ለመደበኛው ሕዝብ ሀብታም የመሆን የመጨረሻው ዕድሎች ናቸው” — የጉግል ዋና ሥራ አስፈጻሚ
#ethiopia | ​የጉግል ዋና ሥራ አስፈጻሚ
ሱንዳር ፒቻይ ከ2026 እስከ 2030 ያሉት ዓመታት ተራው ሕዝብ በከፍተኛ ደረጃ ሀብት ለማፍራትና የኢኮኖሚ አቅሙን ለማሳደግ የሚያገኝበት የመጨረሻው ወርቃማ አጋጣሚ መሆናቸውን ገለጹ።

ዋና ሥራ አስፈጻሚው በሰጡት ማብራሪያ በአሁኑ ወቅት እየታየ ያለው የቴክኖሎጂ እና የኢኮኖሚ ሽግግር ለብዙዎች ያልተጠበቀ የሀብት ፈጠራ ዕድል ይዞ የመጣ ቢሆንም ይህን አጋጣሚ አሁኑኑ ተፎካካሪ ሆኖ ያልተጠቀመበት የሕብረተሰብ ክፍል ግን ወደፊት የሚፈጠሩትን እድሎች ለማግኘት እጅግ እንደሚቸገር አሳስበዋል።

በመሆኑም ሰዎች አዳዲስ የስራ አዝማሚያዎችን ቀድመው በመገንዘብ አሁኑኑ ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉና ይህን አጋጣሚ ወደ እውነተኛ ስኬት እንዲቀይሩት ጥሪ የቀረበ ሲሆን ትክክለኛውን እርምጃ በአሁኑ ወቅት መውሰድ የነገውን የገንዘብ ነፃነት ለመወሰን ወሳኝ መሆኑ ገልጸዋል።

በያፌት ገ/ህይወት

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu

Getu Temesgen
4 hours ago

በአንድ ዓመት ውስጥ ከመሠረት እስከ ጉልላት የደረሰው የቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን ግንባታ ድጋፍ ተጠየቀ

ብዙ ጊዜ በየሚዲያው የምንሰማው የችግርና የቅሬታ ዜና ቢሆንም፣ ዛሬ የምናካፍላችሁ የደስታና የተስፋ ዜና ነው።

በአዲስ አበባ የካ አባዶ ደብረ ልዕልና ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን የተመለከትነው ግንባታ እጅግ አስደናቂ የሚባል ነው።

ባለፈው ዓመት በነሐሴ ወር የመሠረት ሥራ ብቻ የነበረው ይህ ግዙፍ ቤተ ክርስቲያን፣ በአንድ ዓመት ውስጥ የግንባታው ሥራ እስከ ጣሪያና ጉልላት ደርሶ መታየቱ በርካቶችን አስደንቋል።

በዚህ ዘመን ብዙ አሳዛኝ ክስተቶች በሚሰሙበት ጊዜ፣ በትጋት የሚሠራ የግንባታ ኮሚቴ፣ ሰበካ ጉባኤ እና በልግስና የሚያግዙ ምዕመናን መኖራቸው የሚያበረታታ ተግባር ነው።

የቤተ ክርስቲያኑን ግንባታ ለማጠናቀቅ አሁን የሚፈለገው ድጋፍ የፊኒሺንግ ሥራዎችን፣ በሮችና መስኮቶችን፣ አንድ መንበር (ከአራቱ መንበሮች ሦስቱ በአካባቢው ምዕመናን ተይዘዋል)፣ ምንጣፍ፣ ቅዱሳት ሥዕላት፣ የኤሌክትሪክ ሥራዎች፣ ብሎኬት፣ ጂፕሰም፣ ቀለም ሥራዎችና ንዋየ ቅድሳትን ያካትታል።

ለዚህም የገቢ ማሰባሰቢያ የቀጥታ ሥርጭት መርሐ ግብር በፊታችን ነሐሴ 1፣ 2 እና 5 ቀን ከምሽቱ 12፡00 ጀምሮ በቤተ ክርስቲያኑ ቅጽር ግቢ ይካሄዳል።

ድጋፍ ለማድረግ፦

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000635044482

ስልክ፦
0911426464

በቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን ግንባታ ላይ በመሳተፍ የታሪክ ሠሪ ትውልድ አካል እንሁን።

አድራሻ፦
የካ አባዶ መሰቀለኛው ጋር ሲደርሱ ቁልቁል ወደ ግራ በሚወስደው መንገድ መጨረሻ።
Getu Temesgen
4 hours ago
በፕሬዚዳንቱ ገደብ ውስጥ ኢትዮጵያም ተካታለች
#ethiopia | ​ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ፣ ታንዛኒያ፣ ኡጋንዳ፣ ዚምባብዌ፣ ቡሩንዲ እና ሴኔጋልን ጨምሮ የ30 የአፍሪካ ሀገራት ዜጎች ለንግድና ለጉብኝት (B1 እና B2) ወደ አሜሪካ ለመጓዝ የቪዛ ማመልከቻ በሚያስገቡበት ወቅት እስከ 20 ሺህ የአሜሪካ ዶላር የዋስትና ማስያዣ እንዲከፍሉ የሚገደዱበት አዲስ መመሪያ ተጣለ።

የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ይህ አሰራር የቪዛ ጊዜያቸውን አጠናቀው በህገ-ወጥ መንገድ የሚቀሩ ሰዎችን ቁጥር ለመቀነስ ያለመ ነው ሲል ገልጿል።

በአንጻሩ የስደተኞች እና የጉዞ መብት ተሟጋቾች ውሳኔው ህጋዊ ተጓዦችን በማስደንግጥና ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጫና በመፍጠር ህጋዊ የሆኑ ጉዞዎችን የሚያስቀር ነው ሲሉ ተችተውታል።

በያፌት ገ/ህይወት

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu

Getu Temesgen
7 hours ago
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ቡድን በሰላም ኦሪገን ደርሷል
#ethiopia | በአሜሪካ ኦሪገን ግዛት ዩጂን ከተማ ከሐምሌ 29 እስከ ነሐሴ 3፣ 2018 ዓ.ም በሚካሄደው 21ኛው የዓለም ከ20 ዓመት በታች (World Athletics U20 Championships) የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ለመሳተፍ የተጓዘው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ቡድን በሰላም ኦሪገን ደርሷል።

ሻምፒዮናው በዓለም አትሌቲክስ ታሪክ ልዩ ስፍራ ባለው የሄይዋርድ ፊልድ (Hayward Field) ስታዲየም የሚካሄድ ሲሆን፣ ይህ ስታዲየም በርካታ ዓለም አቀፍ ውድድሮችንና ታሪካዊ የአትሌቲክስ ፉክክሮችን በማስተናገድ የታወቀ ነው።

በዘንድሮው ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በ5000 ሜትር፣ 3000 ሜትር፣ 1500 ሜትር፣ 800 ሜትር (በሁለቱም ፆታዎች)፣ 3000 ሜትር መሰናክል (በሴቶች)፣ 400 ሜትር (በሴቶች) እና በርምጃ ውድድር (በሁለቱም ፆታዎች) በመሳተፍ ጠንካራ ውጤት ለማስመዝገብ በተጠናከረ ዝግጅት ቀርባለች።

ይህ ውድድር ለወጣት አትሌቶች ዓለም አቀፍ ልምድ የሚያስገኝ እና የወደፊት የኦሎምፒክና የዓለም ሻምፒዮኖች የሚፈጠሩበት አንዱ ትልቅ መድረክ በመሆኑ፣ የኢትዮጵያ ቡድንም የሀገሪቱን የረጅም ርቀት አትሌቲክስ ስኬት ለማስቀጠል ተስፋ ተጥሎበታል።

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለመላው ልዑክ ቡድን የተሳካ ውድድርና የድል ጉዞ በመመኘት መልካም ዕድል ብሏል።

መልካም ዕድል ለኢትዮጵያ ቡድን! 🇪🇹

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)

Getu Temesgen
6 hours ago
የጋዜጠኛና መምህር ዐቢይ ይልማ 5ኛ መጽሐፍ
“ደህና ነኝ – እግዚአብሔር ይመስገን” ቅዳሜ ይመረቃል
#ethiopia | የጋዜጠኛ፣ ደራሲና መምህር ዐቢይ ይልማ አምስተኛ መጽሐፍ የሆነው “ደህና ነኝ – እግዚአብሔር ይመስገን” ቅዳሜ ነሐሴ 2፣ 2018 ዓ.ም. ከጠዋቱ 4፡00 ጀምሮ በቦሌ በሚገኘው ዓለም ሲኒማ ይመረቃል።

መጽሐፉ በዘመናችን በብዙ ሰዎች የሚስተዋሉ እንደ ጭንቀት፣ ፍርሃት፣ የባዶነት ስሜት፣ ተስፋ መቁረጥ፣ ሱሰኝነት፣ የገንዘብ ችግርና ሌሎች የሕይወት ፈተናዎች ዙሪያ መንፈሳዊና ሳይንሳዊ እይታዎችን በማቀናጀት ለአንባቢያን ተስፋና መነሳሳት ለመስጠት ያለመ ሥራ መሆኑን አዘጋጆቹ ገልጸዋል።

ደራሲው ዐቢይ ይልማ በሕይወቱ ያጋጠሙትን ለ12 ዓመታት የዘለቀ ከባድ የጤናና የሕይወት ፈተና በድል ካለፉ በኋላ ያገኙትን ልምድና እውቀት በዚህ መጽሐፍ አካፍለዋል።

አዘጋጅ ኮሚቴው በዕለቱ የሚካሄደውን የመጽሐፍ ምረቃ ሥነ ሥርዓት እንዲታደሙ የደራሲውን ወዳጆች፣ የሥነ ጽሑፍ አፍቃሪዎችና መላውን ሕዝብ በክብር ጋብዟል።

ቅዳሜ ነሐሴ 2፣ 2018 ዓ.ም.
ጠዋት 4፡00 ሰዓት
ቦሌ ዓለም ሲኒማ

እንኳን ወደ መጽሐፉ ምረቃ በደህና መጡ!

Getu Temesgen
12 hours ago
ስቲቭ ሃርቪ: ለሦስት ዓመታት ያህል ቤት አልባ ነበር፤ መኪና ውስጥ ማደር ጀመረ
#ethiopia | ዛሬ በዓለም ዙሪያ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ስቲቭ ሃርቪን እንደ ስኬታማ የቴሌቪዥን አቅራቢ፣ ኮሜዲያን፣ ተዋናይ እና ደራሲ ያውቁታል።

እንደ "Family Feud" እና "Showtime at the Apollo" ያሉ ታዋቂ ፕሮግራሞችን በመምራት የሚታወቀው ሃርቪ፣ የሀብት እና የዝና ማማ ላይ ከመውጣቱ በፊት ግን እጅግ ፈታኝ የሆኑ የህይወት ምዕራፎችን አሳልፏል። የእሱ የህይወት ታሪክ ተስፋ የመቁረጥ፣ የእምነት እና የማያቋርጥ ጥረት ድንቅ ማሳያ ነው።

እንደ ዓለም አቀፍ የዜና አውታሮች ዘገባዎች፣ የስቲቭ ሃርቪ ጉዞ ሁልጊዜ አልጋ በአልጋ አልነበረም። በተለይም በ1980ዎቹ ውስጥ በኮሜዲው ዘርፍ ስራ ለመጀመር በሚጥርበት ወቅት፣ ለሦስት ዓመታት ያህል ቤት አልባ በመሆን በመኪናው ውስጥ ለመኖር ተገዷል። ይህ ጊዜ ለሃርቪ እጅግ ጨለማ እና ፈታኝ ነበር።

በኋላ ላይ ያንን ጊዜ ሲያስታውስ፣ "ስትመለከተው የሶስት ዓመት ጊዜ መሆኑን ማመን አልቻልኩም ነበር። ያኔ ትኩረቴ ሁሉ ከዛ ሁኔታ ለመውጣት ነበር። ወደፊት ለመራመድ በጣም ጠንክሬ እየሰራሁ ነበር" ብሏል። ይህ ንግግሩ ያሳለፈውን ጥልቅ ጭንቀት እና ከሁኔታው ለመውጣት የነበረውን ጽናት ያሳያል።

በተያያዘው ምስል ላይ እንደሚታየው፣ የስቲቭ ሃርቪ ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ ያገኘው በአንድ ሆቴል የህዝብ መታጠቢያ ቤት ውስጥ ነው። በአንድ ወቅት እራሱን እያጠበ እያለ፣ የህይወቱ ዝቅተኛው ደረጃ ላይ እንደደረሰ ተሰማው። በዛ የጭንቀት ወቅት፣ ለፈጣሪው ቃል ኪዳን ገባ። "ካሳካህልኝ፣ እዛ ደረጃ ላይ ስደርስ ይህን ያደረግከው አንተ እንደሆንክ ለሁሉም እናገራለሁ" አለ።

ይህ ቃል ኪዳን ሃርቪን በፈተናዎች ውስጥ እንዲጸና እና ተስፋ እንዳይቆርጥ ያደረገው መንፈሳዊ ጥንካሬ ሆነ። ምስሉ ላይ “I was homeless and living in my car. I told God, 'If You let me make it, I'm going to tell everybody it was You.' So, I'm telling you about Him.” የሚለው ጥቅስ ይህንን ቃል ኪዳን እና ዛሬም ድረስ እያከበረው መሆኑን ያሳያል።

ለፈጣሪው ቃል ከገባ ከጥቂት ጊዜ በኋላ፣ ሃርቪ የቆመ ኮሜዲ ስራ እድል የሚሰጥ የስልክ ጥሪ ደረሰው። ይህ እድል ለሌሎች ስራዎች መንገድ ከፈተለት፣ በመጨረሻም በኒውዮርክ የሚገኘው "Showtime at the Apollo" የተሰኘው ታዋቂ ፕሮግራም አቅራቢ ሆነ።

ይህ ትልቅ እመርታ "The Steve Harvey Show," "Family Feud," እና ሌሎች በርካታ ፕሮግራሞችን ያካተተ የተሳካ የስራ ህይወት እንዲጀምር አደረገው።

ዛሬ ሃርቪ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ተመልካቾች ያሉት ታዋቂ ሰው ቢሆንም፣ በዛ መታጠቢያ ቤት የገባውን ቃል ኪዳን ፈጽሞ አልረሳውም። ምንም እንኳን ስለ እምነቱ በግልፅ መናገሩ ትችት ቢያስከትልበትም፣ ሃርቪ ግን እምነቱን መግለጹን ቀጥሏል።

ከቤት አልባነት ወደ ስኬት ያደረገውን ጉዞ በማመልከት፣ "ህይወቴን ተመልከቱ። ከየት እንደመጣሁ ተመልከቱ። አሁን የት እንዳለሁ ተመልከቱ። እኔ የምጠቀመው (እምነት) እየሰራ ነው" ይላል።

የስቲቭ ሃርቪ የህይወት ታሪክ ከባድ ፈተናዎች እና ውድቀቶች መቋጫ ሳይሆኑ፣ ለትልቅ ስኬት መነሻ ሊሆኑ እንደሚችሉ ያስተምረናል።

በምስሉ ላይ እንደሚታየው፣ ሃርቪ በመኪና ውስጥ ከነበረበት ጭንቀት ወደ ስኬታማ ህይወት የተሸጋገረው በእምነት፣ በጠንካራ ስራ እና ተስፋ ባለመቁረጥ ነው። የእሱ ጉዞ ለብዙዎች ተስፋ የመስጠት እና የማበረታታት አቅም ያለው፣ እውነተኛ የጽናት ታሪክ ነው።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)

Getu Temesgen
13 hours ago
እኔ ውሸታም ወይም አታላይ አይደለሁም!
#ethiopia | የካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ የሶሺዮሎጂ ትምህርት ክፍል መምህር የሆኑት ፕሮፌሰር ጄሰን አርደይ የሌሎች ምሁራን ጽሑፎች ያለ አግባብ ተጠቅመዋል በሚል ክስ ቀረበባቸው።

ክሱ በዋናነት የተነሳው በፈረንጆቹ 2015 ባዘጋጁት የመመረቂያ ጽሑፏቸው ላይ ሲሆን በዚህ ጽሁፋቸው የምሁራን ጥናቶች በቀጥታ ያለ ምንጭ ተጠቅመዋል የሚል ነው።

ፕሮፌሰሩም በፒኤችዲ ቴሲሳቸው እና ባሳተሟቸው አካዳሚያዊ ጥናቶች ላይ የቀረበባቸውን የጽሑፍ ስርቆት ክስ አስተባብለዋል።

ፕሮፌሰሩ በጥናቶቻቸው ላይ ጥቂት የአሰራር እና የቴክኒክ ስህተቶች መከሰታቸውን አምነው እኔ ግን ውሸታም ወይም አታላይ አይደለሁም ሲሉ ራሳቸውን ተከላክለዋል።

በቀደሙት ሥራዎቼ ላይ የቴክኒክና የምንጭ አጠቃቀም ስህተቶች መኖራቸውን እቀበላለሁ ለሰራኋቸው ስህተቶችም ኃላፊነቱን እወስዳለሁ ብለዋል።

ነገር ግን አካዳሚያዊ ማጭበርበር ወይም የፁሁፍ ስርቆት ፈፅመሀል የሚለው ውንጀላ ፍፁም ከእውነት የራቀና ተቀባይነት የሌለው ነው ሲሉ ተናግረዋል።

የካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ በበኩሉ በሰጠው መግለጫ የቀረቡት አቤቱታዎች ላይ ጥልቅ ምርመራ መደረጉንና ፕሮፌሰሩ ምንም የፈፀሙት ስህተት የለም ብሏል።

ዩኒቨርሲቲው ውንጀላውን የፕሮፌሰሩን ስም ለማጠልሸት ሆን ተብሎ የተደረገ ነው ሲል ገልጾታል።

በተጨማሪም በርካታ ምሁራንና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ለፕሮፌሰሩ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል።

ክሱ በጥቁር ምሁራን ስኬት ላይ ያተኮረ ፖለቲካዊና ርዕዮተ ዓለማዊ ጫና እንደሆነ ተናግረዋል።

ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #england #cambridgeuniversity #professor

Getu Temesgen
13 hours ago
ካንተ ጋር በመስራቴ ኩራት ይሰማኛል
አንጀሊና ጆሊ
#ethiopia | አንጄሊና ጆሊ የቲፐረሪ ዓለም አቀፍ የሰላም ሽልማት ላሸነፈው የሙያ አጋሯ አድናቆቷን አቅርባለች።

የ2025 የቲፐረሪ ዓለም አቀፍ የሰላም ሽልማት ተሸላሚ ለሆነው የረጅም ጊዜ ወዳጇ እና የሙያ አጋሯ የሆነው ፎቶግራፈሯ አድናቆቷን ገልጻለች።

ጆሊ በሰጠችው አስተያየት የሙያ አጋሯ በፎቶግራፍ ሙያው በኩል ለሰላምና ለሰብአዊነት ላበረከተው አስተዋጽኦ ይህንን ታላቅ የሰላም ሽልማት በማሸነፉ መደሰቷን ገልጻ የደስታው ተካፋይ መሆኗን ገልጻለች።

አንጀሊና ጆሊ ለበርካታ ዓመታት ከሙያ አጋሯ ጋር አብራ ለመስራት በመታደሏ ኩራት እንደሚሰማትም ገልፃለች።

ሽልማቱ በስራዎቹ አማካኝነት ለዓለም አቀፍ ሰላምና ሰብአዊነት ላበረከተው የጎላ አስተዋጽኦ ውጤት ነው ስትል የተናገረችው።

የቲፐረሪ ዓለም አቀፍ የሰላም ሽልማት በየዓመቱ በዓለም ዙሪያ ለሰላም ለሰብአዊ መብት እና ለግጭቶች እልባት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ለሚያደርጉ አካላት የሚሰጥ ዓለም አቀፍ ሽልማት ነው።

ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #usa #peace #award #angelinajolly

Getu Temesgen
13 hours ago
አሳዛኝ ታሪክ- የፔቲዲን ሱስ
#ethiopia | ዶክተር ካሳ አደጋ ያጋጥመውና የእጁ አጥንት ይሰበራል። ወደ ድንገተኛ ክፍል ሲሄድ ለህመም ማስታገሻ ፔቲዲን የተባለውን መርፌ ይወጉታል። የስብራቱ ህመም ይጠፋና የደስታ ስሜት ይሰማዋል። ከስብራቱ ቢያገግምም ለህመም ማስታገሻ የወሰደው ፔቲዲን ሱስ ሆኖበት በየቀኑ ብዙ ብልቃጦች ራሱን ይወጋል።

ፔቲዲን የሚፃፈው በልዩ የመድሀኒት ማዘዣ ነው። ዶክተር ካሳ ጓደኞቹ እንዲፅፉለት ይጠይቃቸዋል። መጀመሪያ ላይ ይፅፉለት ነበር። በኋላ ግን የሚወስደው መጠን ከፍ ስላለ "አንፅፍም!" ብለው ከለከሉት። አንዳንድ ባልደረቦቹ ግን እያዘኑለት ይፅፉለታል። የሚወስደው መድሀኒት መጠን ከፍ ሲል ልዩ የመድሀኒት ማዘዣውን ይዞ እራሱ እየፃፈ መግዛት ጀመረ። መድሀኒቱ ውድ ስለሆነ ዶክተር ካሳ አብዛኛው ደሞዙን በመድሀኒት ግዢ ነው የሚያጠፋው። ከባልደረቦቹም በተለያየ ጊዜ ብሮች ተበድሯል።

ዶክተር ካሳ ሱሱን ለማቆም ሞክሮ ያውቃል። ነገር ግን ሳይወስድ ሲቀር ላብበላብ ይሆናል። ተረጋግቶ መስራት አይችልም። ይቅበጠበጣል። መድሀኒቱን ባለመውሰዱ የሚሰማውን ምቾት የሚነሳ ስሜት ለማጥፋት ውሳኔውን ሽሮ ፔቲዲን ይወጋል።

አንድ ቀን ዶክተር ካሳ ሆስፒታሉ የሰጠው ቤት ውስጥ ራሱን ስቶ ተዘርሮ ወድቋል። ክፍሉ ውስጥ የፔቲዲን ብልቃጦች አሉ። መርፌና ሲሪንጅ አጠገቡ አለ....

ዶክተር ካሳ ልቦለዳዊ ስም ይሆን እንጂ ተመሳሳይ የፔቲዲን ሱስ ውስጥ ያሉ ብዙ ሰዎች አሉ። አብዛኞቹ ደግሞ የጤና ባለሞያዎች ናቸው። ነርሶች፣ የሰመመን ባለሞያዎች፣ ሀኪሞች፣ የፋርማሲ ባለምያዎች...። ህክምና ሞያ ውስጥ ጥቂት አመታት ያሳለፍን ሰዎች በዚህ ሱስ የሚቸገር የምናውቀው ሰው ወይም ወዳጅ አለን።

በሱስ የሚቸገሩ ሰዎች ላይ ፍረጃ ከማድረግ ይልቅ ሞያዊ እገዛ እንዲያገኙ ብናደርግ ጥሩ ያልሆኑ ነገሮች እንዳይከሰቱ ማድረግ እንችላለን። ሱስ ህክምና ያለው የአእምሮ ህመም ነው።

እኔ የምወደውን ሰው በፔቲዲን ሱስ ምክኒያት አጥቻለሁ። ይመለከተኛል። ሌሎች ሰዎች ተመሳሳይ ነገር ውስጥ እንዳያልፉና ተገቢውን የአእምሮ ህክምና እንዲያገኙ የምችለውን ያህል ግንዛቤ ለመፍጠር እጥራለሁ።

ያለ አእምሮ ጤና፤ ጤና የለም!
ዶ/ር ዮናስ ላቀው

Getu Temesgen
13 hours ago
ገዳይ ሲያረፋፍድ ....
#ethiopia | የኢትዮጵያ የፊልም ኢንዱስትሪ የትረካ ጥበብ እና የካሜራ ቴክኖሎጂን አዋህዶ በዘመናዊ አቀራረብ እያደገ ባለበት በዚህ ወቅት፣ የፊልም አፍቃሪዎችን እና የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎችን ትኩረት ከሳቡ የሀገር ውስጥ የጥበብ ስራዎች መካከል «ገዳይ ሲያረፋፍድ» የተሰኘው የናኦድ ለማ ፊልም ይጠቀሳል።

ይህ ፊልም ይዘቱ፣ የገጸ-ባህሪያት አሳሳሉ እንዲሁም በፖስተሩ ላይ ከሚታየው ጥበብ የሞላበት የቀለምና የብርሃን አጠቃቀም ጀምሮ አቀራረቡ አዳዲስ የትረካ መስመሮችን የሚዳስስ ለመሆኑ ማመላከቻዎችን ያሳያል።

የፊልሙ ርዕስ፡ ገዳይ ሲያረፋፍድ (GEDAY SIYAREFAFID)

ዳይሬክተር / የፊልም አዘጋጅ፡ ናኦድ ለማ (A film by Naod Lemma)

ደራሲ - ስለሺ አምባው

ዋና ተዋንያን፡

መለስ ታደሰ

መስከረም ነጋ በበላይ

ጌታነት አዳነ

ልዑል ተፈራ

አዘጋጅ/ፕሮዳክሽን፡ ታና ኢንተርቴይንመንት (Tana Entertainment) እና አዲቃ (Adika)

የፖስተሩ ጥበባዊ ዳሰሳ እና ጭብጥ (Visual & Storyline Analysis)

የከባቢ አየር እና ድባብ (Atmosphere & Tone):

የፖስተሩ የጀርባ ቀለም (ደመናማና ብርቱካናማ የቀን መግቢያ/መውጫ ብርሃን) የጥርጣሬ፣ የጉጉት እና የድራማ ስሜትን ይፈጥራል።

በግርጌ እና በጎን የሚታዩት የሁለቱ ዋና ገጸ-ባህሪያት ፊት (መጨናነቅ፣ ቁጣ እና ጥልቅ ሀሳብ) ፊልሙ ከባድ የስነ-ልቦና ድራማ ወይም የወንጀልና የበቀል/የውጥረት (Suspense/Thriller) ታሪክ ሊኖረው እንደሚችል ያመላክታል።

ተምሳሌታዊ ምስሎች (Symbolism):

በፖስተሩ መካከለኛ ክፍል ላይ በጥቁር ጥላ (Silhouette) የሚታዩት ሁለት ሰዎች እና ትንሽ ጎጆ ቤት በፊልሙ ውስጥ ያለውን የገጠር ወይም የርቅ ቦታ ዳራ፣ እንዲሁም የሁለት ሰዎች ሚስጥራዊ ግንኙነት ወይም ግጭት ያሳያሉ።

ፊልሙ ከተለመዱት የፍቅርና የኮሜዲ መስመሮች ወጣ ባለ መልኩ የሰዎችን ጥልቅ ስነ-ልቦና እና ያልተጠበቁ ሁነቶችን (Plot Twists) በማቀናጀት የቀረበ እንደሆነ ይነገርለታል።

በተለይም የነመለስ ታደሰ እና ጌታነት አዳነ ገጸ-ባህሪያትን የማቅረብ ተፈጥሯዊ ብቃት ለፊልሙ ስኬት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱ ይገለጻል።

በምስል ጥራት፣ በድምጽ ቅንብር እና በምስል ቅንብር (Editing) በኩል የሀገር ውስጥ ፊልም ወደ አዲስ ደረጃ ለማሸጋገር የተደረገው ጥረት አዎንታዊ ግምገማዎችን አግኝቷል።

«ገዳይ ሲያረፋፍድ» የኢትዮጵያ ፊልም ኢንዱስትሪ የትረካ አቅሙን እና የቴክኒክ ብቃቱን ለማሳደግ የሚያደርገውን ጉዞ የሚያሳይ፣ የፊልም አፍቃሪያን ሊመለከቱት የሚገባ አሳቢና ውጥረት አዘል የጥበብ ሥራ ነው።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)

Getu Temesgen
13 hours ago
ጋምቤላና ደምቢዶሎ በአየር ሊገናኙ ነው
#ethiopia | የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሀገር ውስጥ የበረራ አገልግሎቱን በማስፋት ከጋምቤላ ወደ ደምቢዶሎ እና ከደምቢዶሎ ወደ ጋምቤላ የሚደረግ ቋሚ የበረራ መስመር ከነሐሴ 6 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ እንደሚጀምር አስታውቋል። ይህ አዲስ መስመር የአየር መንገዱ የሀገር ውስጥ ኔትወርኩን የማስፋትና የክልሎችን ትስስር የማጠናከር እቅድ አካል መሆኑ ተገልጿል።

አየር መንገዱ እንደገለጸው፣ አዲሱ የበረራ መስመር በጋምቤላና በደምቢዶሎ መካከል ያለውን የትራንስፖርት እንግልት በእጅጉ በመቀነስ ለንግድ፣ ለኢንቨስትመንት፣ ለመንግሥታዊ አገልግሎቶች እና ለማኅበራዊ ግንኙነቶች አመቺ ሁኔታ ይፈጥራል።

በተጨማሪም ይህ አዲስ መስመር በሁለቱ አካባቢዎች መካከል ያለውን ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ትስስር ይበልጥ እንደሚያጠናክር ተጠቁሟል። የኢትዮጵያ አየር መንገድም የዜጎችን የጉዞ ፍላጎት ለማሟላት የሀገር ውስጥ መዳረሻዎቹን በቀጣይነት እያሰፋ እንደሚቀጥል አረጋግጧል።
#ethiopianairlines #gambella #dembidolo #domesticflights #ethiopianews #aviation #ጋምቤላ #ደምቢዶሎ

Getu Temesgen
14 hours ago

ud83cudfd9ufe0f u1260u12f1u1263u12ed u12e8u1205u120du121du12ceu1295 u1264u1275 u12c8u12edu121d u12e8u12a2u1295u1268u1235u1275u1218u1295u1275 u12a5u12f5u120d u12a8 Brook Real Estate u130bu122d u12ebu130du1299! ud83cudfe1u2728
u260eufe0f Call / WhatsApp: +971 52 786 6251
u1260u12f1u1263u12ed u1264u1275 u1208u1218u130du12dbu1275u1363 u1260u122au120d u12a5u1235u1274u1275 u1208u1218u12a2u1295u1268u1235u1275 u12c8u12edu121d u12e8u12c8u12f0u134au1275u12ceu1295 u134bu12edu1293u1295u1235 u1208u121bu1228u130bu1308u1325 u12a8u1348u1208u1309u1363 Brook Real Estate u1260u1219u12ebu12ca u12a0u1308u120du130du120eu1275u1363 u1260u1273u121bu129du1290u1275 u12a5u1293 u1260u120du121du12f5 u12a8u1218u1300u1218u122au12eb u12a5u1235u12a8 u1218u1328u1228u123b u12a8u130eu1295u12ce u12edu1246u121bu120du1362

u2705 Off-Plan u12a5u1293 Ready Properties
u2705 u1240u120bu120d u12a5u1293 u1270u1208u12cbu12cbu132d u12e8u12adu134du12eb u12d5u1245u12f6u127d
u2705 u12a8u134du1270u129b u12e8u12a2u1295u1268u1235u1275u1218u1295u1275 u1275u122du134d u12a5u12f5u120eu127d
u2705 u12e8Golden Visa u12d5u12f5u120eu127d (u1260u1270u1348u120bu130a u1218u1235u1348u122du1276u127d)
u2705 u12a8u1273u1218u1291 u12e8u12f1u1263u12ed u12f2u1268u120eu1350u122eu127d u130bu122d u1240u1325u1273 u12e8u123du12ebu132d u12a0u121bu122bu132eu127d

ud83dudcde Call / WhatsApp: +971 52 786 6251

Brook Real Estate
Your Trusted Real Estate Partner in Dubai.
#brookrealestate #dubairealestate #dubaiproperty #dubaiinvestment #luxuryliving #propertyinvestment #goldenvisa #dreamhome #offplandubai #readyproperty #dubaihomes #uaerealestate #u12f1u1263u12ed #u12f1u1263u12edu1264u1275 #u12a2u1295u1268u1235u1275u1218u1295u1275 #u12a0u121bu122b ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
🏙️ በዱባይ የህልምዎን ቤት ወይም የኢንቨስትመንት እድል ከ Brook Real Estate ጋር ያግኙ! 🏡✨
☎️ Call / WhatsApp: +971 52 786 6251
በዱባይ ቤት ለመግዛት፣ በሪል እስቴት ለመኢንቨስት ወይም የወደፊትዎን ፋይናንስ ለማረጋገጥ ከፈለጉ፣ Brook Real Estate በሙያዊ አገልግሎት፣ በታማኝነት እና በልምድ ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ከጎንዎ ይቆማል።

✅ Off-Plan እና Ready Properties
✅ ቀላል እና ተለዋዋጭ የክፍያ ዕቅዶች
✅ ከፍተኛ የኢንቨስትመንት ትርፍ እድሎች
✅ የGolden Visa ዕድሎች (በተፈላጊ መስፈርቶች)
✅ ከታመኑ የዱባይ ዲቨሎፐሮች ጋር ቀጥታ የሽያጭ አማራጮች

📞 Call / WhatsApp: +971 52 786 6251

Brook Real Estate
Your Trusted Real Estate Partner in Dubai.
#brookrealestate #dubairealestate #dubaiproperty #dubaiinvestment #luxuryliving #propertyinvestment #goldenvisa #dreamhome #offplandubai #readyproperty #dubaihomes #uaerealestate #ዱባይ #ዱባይቤት #ኢንቨስትመንት #አማራ
Getu Temesgen
20 hours ago
በፖሊስ የአደን ማስታወቂያ የወጣበት ተጠርጣሪ የተሻለ የሰልፊ ፎቶውን ለፖሊስ ላከ
#ethiopia | ​ከአስር ዓመት በፊት እንዲህ ሆነ።በአሜሪካ ኦሃዮ ግዛት የሚገኘው የሊማ ፖሊስ መምሪያ በፍርድ ቤት ያልቀረበውን ዶናልድ “ቺፕ” ፑግ የተባለ ተፈላጊ ግለሰብ ለማደን በፌስቡክ ገጹ የፍለጋ ማስታወቂያ አወጣ።

ነገር ግን ተፈላጊው ግለሰብ ከመሸሸግ ይልቅ በፖሊስ የወጣው የመታወቂያ ፎቶው እንደማያምርበት በመግለጽ “ይህ የተሻለ ፎቶ ነው፤ ያኛው አስቀያሚ ነው” የሚል አጭር መልእክት ከተሻለ የሰልፊ ፎቶው ጋር ለፖሊስ ልኳል።

​የሊማ ፖሊስም መልእክቱን አይቶ እንዳላየ ከማለፍ ይልቅ ግለሰቡ ላደረገው “ትብብር” በፌስቡክ ገጹ ላይ አመስግኖ አዲሱን የሰልፊ ፎቶ የለጠፈው ሲሆን፣ እጁንም እንዲሰጥ አሳሰበ።

በሁለቱ አካላት መካከል የተደረገው ይህ ድንቅ ውይይት በማህበራዊ ሚዲያ ተሰራጭቶ ሰዎች የተጋሩት ሲሆን፣ የብዙዎችን አስገርሟል።

ዶናልድ ፑግ ከጥቂት ቀናት በኋላ በፍሎሪዳ ግዛት በቁጥጥር ስር የዋለ ቢሆንም የላከው ሰልፊ በቅርብ ዓመታት ከተመዘገቡት እጅግ አስገራሚ የፖሊስ የፍለጋ ማስታወቂያዎች አንዱ ሆኖ ተመዝግቧል።

በያፌት ገ/ህይወት

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu

Getu Temesgen
20 hours ago
ዛሬ የምንተክለው ችግኝ የነገው ጥላችን ነው፦ዋረን ቡፌት

*ዛሬ ጥላ ስር የተቀመጥነው ከአመታት በፊት ሌላ ሰው በተከለው ችግኝ ነው፦ ዋረን ቡፌት
#ethiopia | ታዋቂው ባለሀብትና ኢንቨስተር ዋረን ባፌት ዛሬ ጥላ ስር የተቀመጥነው ከአመታት በፊት ሌላ ሰው በተከለው ችግኝ ነው ሲል የተናገረው አነቃቂ አባባል የረዥም ጊዜ እይታን ጥቅም ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።

በስኬት መንገድ ላይ የቆሙ ተቋማት ያደጉ ሀገራትም ሆኑ ውጤታማ ግለሰቦች ያገኙት ፍሬ የስኬታቸው መጀመሪያ ሳይሆን ከዓመታት በፊት የተዘራው ዘር ውጤት መሆኑን ዋረን ቡፌት የተናገረው።

ዛሬ የምንዘራው በጎ ዘርና ጥረት ለራሳችን ብቻ ሳይሆን ለቀጣዩ ትውልድ የሚተርፍ ጥላና ዕረፍት ይሆናል።

የዛሬን ጊዜያዊ ጥቅም ብቻ ከማየት ይልቅ ዘላቂ ለሆነ ነገር ትኩረት መስጠትና መዋዕለ ነዋያችንን ጊዜያችንን እንዲሁም እውቀታችንን በጥበብ ማዋል ያስፈልጋል ሲሉ ገልጸዋል።

ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #warrenbuffett #plantingtree #investment

Getu Temesgen
19 hours ago
ፋሻ ላውንጅ ሀዋሳ
– የመዝናኛዎ አዲሱ መዳረሻ!

ሀዋሳን በልዩ መንገድ ለመዝናናት ይፈልጋሉ?

ፋሻ ላውንጅ ሀዋሳ ለከተማው ነዋሪዎች ብቻ ሳይሆን ከየትኛውም ስፍራ ለሚመጡ እንግዶች የተለየ የመዝናኛ ልምድ ያቀርባል።

🌴 ነፋሻማና ዘመናዊ አካባቢ
🎧 በምርጥ ዲጄዎች የተሞላ አስደሳች ሙዚቃ
🍽️ ጣፋጭ ምግቦችና የተለያዩ መጠጦች
🤝 ፈጣንና ሙያዊ አገልግሎት
✨ ለወዳጅ ስብሰባ፣ ለቤተሰብ መዝናኛ እና ለልዩ ዝግጅቶች ተስማሚ

ደማቅ ቀንም ሆነ አስደሳች ምሽት በሀዋሳ ማሳለፍ ከፈለጉ፣ ፋሻ ላውንጅ የመጀመሪያ ምርጫዎ ነው።

አድራሻ: ሀዋሳ 05፣ ከጉዱማሌ ፊት ለፊት

ስልክ +251-916-860330

ፋሻ ላውንጅ ሀዋሳ
ይምጡ... ይዝናኑ... የማይረሳ ትዝታ ይዘው ይመለሱ!

Getu Temesgen
18 hours ago
በየዓመቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ60 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ህይወታቸውን ያጣሉ
#ethiopia | በየዓመቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ60 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በተለያዩ ምክንያቶች ህይወታቸውን እንደሚያጡ መረጃዎች ጠቁመዋል።

የሞት ምጣኔ በሀገራት መካከል በከፍተኛ ሁኔታ የሚለያይ ሲሆን ዋና ዋና ምክንያቶቹ የዕድሜ ስብጥር የአረጋውያን ቁጥር መብዛት ደካማ የጤና ስርዓት ጦርነትና ግጭት ዋነኞቹ ናቸው።

ከሰሀራ በታች ባሉ ሀገራት እንደ ድህነት ያሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖዎች ለሞት ምጣኔው ከፍተኛ መሆን እንደምክንያትነት ይጠቀሳሉ።

በተጨማሪም በሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት ደግሞ በቂ የህክምና አቅርቦት አለመኖር ተላላፊ በሽታዎች እና የእናቶችና ህፃናት ሞት ምጣኔ ከፍተኛ መሆን ዋና ምክንያቶች ናቸው።

በጦርነት ውስጥ ባሉ ሀገራት የሰው ህይወት ማጣት እና የጤና ተቋማት መውደም የሞት ምጣኔውን ከፍተኛ አድርጎታል።

በምስራቅ አውሮፓ እንደ ቡልጋሪያ እና ላቲቪያ ያለው የሞት ምጣኔ በቁጥር ከፍ ብሎ የሚታየው አረጋውያን በመብዛታቸው ምክንያት ነው ተብሏል።

ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #worldpopulation #deathrate #europe #africa

Getu Temesgen
20 hours ago
በአሜሪካ በሳይክሎስፖሪያሲስ (Cyclosporiasis) ወረርሽኝ የመጀመሪያ ሞት ተመዘገበ
#ethiopia | አሜሪካ ውስጥ በCyclospora cayetanensis ተውሳክ የሚከሰተው የሳይክሎስፖሪያሲስ (Cyclosporiasis) ወረርሽኝ ከተጀመረ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከዚህ በሽታ ጋር በተያያዘ ሁለት ሰዎች በሚሺጋን ግዛት መሞታቸውን የግዛቱ የጤና ባለሥልጣናት አስታውቀዋል። ይህ በአሜሪካ ታሪክ ከዚህ ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ የተመዘገበ የመጀመሪያው የሞት ክስተት ነው።

ባለሥልጣናቱ እንደገለጹት፣ ሁለቱም ሟቾች ከዚህ ቀደም ከባድ የጤና ችግሮች የነበሯቸው ሲሆን፣ በተደጋጋሚ ተቅማጥና በውኃ እጥረት (dehydration) ምክንያት የነበራቸው ሁኔታ ተባብሶ ለሞት እንዳደረሳቸው ተገልጿል። የግል መረጃቸው አልተገለጸም።

በሚሺጋን ግዛት ብቻ እስካሁን ከ11,000 በላይ ተጠርጣሪ ወይም የተመዘገቡ ኬሶች ሲኖሩ፣ 193 ሰዎች ሆስፒታል ገብተዋል። በመላው አሜሪካ ደግሞ ከ6,700 በላይ በላብራቶሪ የተረጋገጡ ኬሶች ተመዝግበዋል፣ ተጨማሪ ብዙ ሺህ ጉዳዮችም እየተመረመሩ ይገኛሉ።

የበሽታው ምንጭ ምንድን ነው?

የአሜሪካ የበሽታ መከላከልና መቆጣጠሪያ ማዕከል (CDC) እና የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን (FDA) እያካሄዱት ባለው ምርመራ፣ ወረርሽኙ በዋነኝነት ከተበከለ የአይስበርግ ሰላጣ (iceberg lettuce) ጋር የተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ተጠርጥሯል። ሆኖም ምርመራው አሁንም በመቀጠል ላይ ሲሆን የመጨረሻ ማረጋገጫ አልተሰጠም።

የበሽታው ምልክቶች

ከባድ የውኃ ተቅማጥ

የሆድ ህመም

ማቅለሽለሽ

ድካም

የምግብ ፍላጎት መቀነስ

አንዳንድ ጊዜ ትኩሳት

በጤናማ ሰዎች ላይ በአብዛኛው ሕክምና በመውሰድ ይድናል፤ ነገር ግን አረጋውያን፣ የበሽታ መከላከያ አቅማቸው ዝቅተኛ የሆኑ ሰዎች እና ሌሎች ከባድ የጤና ችግሮች ያሉባቸው ሰዎች ለከፍተኛ አደጋ ሊጋለጡ ይችላሉ።

የጤና ባለሥልጣናት የሰጡት ምክር

ጥሬ አትክልቶችንና ፍራፍሬዎችን በደንብ በማጠብ ይጠቀሙ።

የተጠረጠሩ የሰላጣ ምርቶችን አይጠቀሙ።

ተቅማጥ ከቀጠለ ወይም የውኃ እጥረት ምልክቶች ከታዩ በፍጥነት ወደ ጤና ተቋም ይሂዱ።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)

Getu Temesgen
20 hours ago
"ሁለተኛው የስልጣን ዘመኔ ልክ እንደ ኢየሱስ መመለስ ነው!"

– የፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ንግግር በኬንያ አነጋጋሪ ሆነ

አዲስ አበባ – የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ሁለተኛ የስልጣን ዘመንን ከኢየሱስ ክርስቶስ ሁለተኛ መምጣት ጋር በማያያዝ የተናገሩት ንግግር በኬንያ የፖለቲካ እና የሃይማኖት ውይይቶችን አቀጣጥሏል።

ፕሬዚዳንቱ በናይሮቢ ጊኮምባ በተካሄደ የቤተ ክርስቲያን መርሃ ግብር ላይ ለደጋፊዎቻቸው የፖለቲካ መፈክር የሆነውን "Tutam" በመጥቀስ፣ "ኢየሱስ ለሁለተኛ ጊዜ ይመጣል፤ ስለዚህ 'Tutam' ስትሉ ለዚያም ዝግጁ ሁኑ" በማለት ንግግር አድርገዋል።

እንዲሁም "ምድራዊ Tutam አለ፣ ሰማያዊ Tutam አለ" በማለት የፖለቲካ መፈክሩን ከክርስቲያናዊ ትምህርት ጋር ለማገናኘት ሞክረዋል።

ይህ ንግግር በማኅበራዊ ሚዲያ ፈጣን ምላሽ አስከትሏል። አንዳንዶች ፕሬዚዳንቱ የመንፈሳዊ መልእክት ለማስተላለፍ እንደሞከሩ ሲገልጹ፣ ሌሎች ግን የሃይማኖት ምሳሌዎችን ለፖለቲካ ዘመቻ መጠቀም ተገቢ አይደለም ሲሉ ተችተዋል።

"Tutam" የሚለው ቃል በሩቶ ደጋፊዎች መካከል "ሁለተኛ ዘመን እናሸንፋለን" የሚል የፖለቲካ መፈክር ሲሆን፣ ተቃዋሚዎቹ ደግሞ "Wantam" (አንድ ዘመን ብቻ) በሚል መፈክር ለ2027 ምርጫ ዘመቻቸውን እያጠናከሩ ነው። ይህም በኬንያ ፖለቲካ ውስጥ በጣም አነጋጋሪ የሆኑ መፈክሮች ሆነዋል።

የ2027 ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ እየተቃረበ በመምጣቱ፣ ሩቶ ሁለተኛ ዘመን ለማሸነፍ በግልጽ እየዘመቱ ሲሆን፣ ተቃዋሚዎቻቸውም "Wantam" በሚል መፈክር የስልጣን ለውጥ እየጠየቁ ነው። የፖለቲካ ውድድሩ ቀድሞውኑ ወደ ከፍተኛ ሙቀት ገብቷል።

የሩቶ የቅርብ ጊዜ ንግግር ደግሞ በኬንያ ውስጥ የፖለቲካና የሃይማኖት ግንኙነት እንደገና የውይይት ርዕስ እንዲሆን አድርጎታል።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)

Getu Temesgen
23 hours ago
በእንግሊዝኛ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ትምህርት የተማሩ ከ100 በላይ ታዳጊዎች ተመረቁ
#ethiopia | አዲስ አበባ – የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት በቦሌ ኆኀተ ብርሃን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን ላለፉት አምስት ሳምንታት በእንግሊዝኛ ቋንቋ መሠረታዊ የቤተክርስቲያን ትምህርት ሲከታተሉ የቆዩ ከ100 በላይ ታዳጊዎችን ሐምሌ 26 ቀን 2018 ዓ.ም. አስመርቋል።

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ፣ የመገናኛ ብዙኃኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ቀሲስ አካልወልድ ተሰማ እና የተመራቂዎቹ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።

ተማሪዎቹ በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቤተክርስቲያን ዶግማ፣ ቀኖና፣ ታሪክ እና የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የተማሩ ሲሆን፣ መርሐ ግብሩ እምነቱን ለወጣቶች ዓለም አቀፍ ተደራሽነት ባለው መልኩ ለማስተላለፍ በማሰብ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት፣ ታዳጊዎች የእምነታቸውን ትምህርት በእንግሊዝኛ መማራቸው ወደፊት በውጭ ሀገራት ቢኖሩም እምነታቸውን በቀላሉ እንዲረዱና እንዲያስተምሩ እንደሚያግዛቸው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅትም የወንጌል ትምህርቶችን በተለያዩ ቋንቋዎች ተደራሽ የማድረግ ሥራውን በቀጣይነት እንደሚያጠናክር አስታውቋል።

Getu Temesgen
22 hours ago
በሰሜን ሸዋ ጻድቃኔ ማርያም ገዳም በመሬት መንሸራተት 14 ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ
#ethiopia | አዲስ አበባ – በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ስር በሚገኘው ታሪካዊው የጻድቃኔ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም በደረሰ ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ 14 ሰዎች ሕይወታቸውን ሲያጡ፣ 5 ሰዎች ደግሞ የከባድና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል።

እንደ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት መረጃ፣ አደጋው በክረምቱ ወቅት በጣለው ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት የተከሰተ ሲሆን፣ በወቅቱ ለጸበል፣ ለሱባኤ እና ለንግሥ በገዳሙ የተገኙ ምዕመናን ላይ ጉዳቱ ደርሷል።

የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በአደጋው ስፍራ በመገኘት ለሕይወታቸው ላለፉት የፍትሐት ጸሎት አድርገው፣ ለተጎዱትና ለተጨነቁት ምዕመናን አባታዊ ቃለ በረከትና የማጽናኛ ትምህርት ሰጥተዋል።

ሀገረ ስብከቱ በመግለጫው በአደጋው ጥልቅ ሀዘን እንደተሰማው ገልጾ፣ ለሞቱት ዕረፍተ ነፍስ፣ ለተጎዱት ፈጣን ፈውስ፣ ለቤተሰቦቻቸውም መጽናናት ተመኝቷል።

የአደጋው መንስኤ ከከፍተኛ ዝናብ ጋር የተያያዘ የመሬት መንሸራተት መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ በቦታው ያሉ አስፈላጊ የድጋፍና የእርዳታ ሥራዎች መቀጠላቸው ተጠቁሟል።

የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት አቡ ቀለምሲስ ሚዲያ

Getu Temesgen
1 day ago
የዳሸን ባንክ ክሬቲቭ ቻሌንጅ የ6 ሚሊዮን ብሩ አሸናፊዎች ታውቀዋል!

እንኳን ደስ ያላችሁ!

ለሙሉ ተወዳዳሪዎቻች ውድድሩን በከፍተኛ የይዘት ጥራት፣ በጥበብ እና በማራኪ የቪዲዮ አሰራር ስላደመቃችሁት ከልብ እናመሰግናለን።
#dashenbank #dashencreativeaward #dashen #dashensuperapp #የዳሸንክሬቲቭቻሌንጅ

Getu Temesgen
1 day ago
እነሆ ''ተስፋን እንትከል'''
#ethiopia | ​​​"ዛፍ ለመትከል የተሻለው ጊዜ ከ20 ዓመታት በፊት ነበር፤ ሁለተኛው የተሻለው ጊዜ ደግሞ አሁን ነው" እንደሚባለው ሁሉ፣ ዛፍ መትከል ተስፋን መትከል በመሆኑና ሕይወታችንን ሰናይ ለማድረግ ደኖቻችንን ማልማት አስፈላጊ ነው።

በዓለም አቀፍ ደረጃ የምድራችን 31 ከመቶ የሚሆነው አካል በደን የተሸፈነ ቢሆንም፣ የደን ሽፋን በየጊዜው እያቆለቆለ በመምጣቱ እስከ እ.ኤ.አ 2030 ድረስ 1 ትሪሊዮን ዛፎችን ለመትከልና ለመንከባከብ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል።

በሀገራችን በ20ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ 40 ከመቶ የነበረው የደን ሽፋን ለእርሻ መሬት መስፋፋት ሲባል ተመንጥሮ ወደ 2 ከመቶ ወርዶ የነበረ ቢሆንም፣ ባለፉት አምስት ዓመታት በተደረገው ከፍተኛ ጥረት የደን ሽፋኑ በ2023 ወደ 23.6 ከመቶ ማደግ ችሏል።

በዚህ መነሻም የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆሳዕና ከተማ የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆኑ ሀገራዊና ማህበራዊ ልማቶችን አከናውኗል።

በኢንስቲትዩቱ "ተስፋን እንተክላለን" በሚል ሀገራዊ ራዕይ የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በማካሄድ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመተባበር በቦቢቾ ቀበሌ ለምግብነትና ለአካባቢ ጥበቃ የሚውሉ 5 ሺህ ችግኞችን ተክሏል።

ከችግኝ ተከላው ጎን ለጎንም በጀሎ ናረሞ ቀበሌ "የዛሬ ህፃናት የነገ ተስፋ ናቸው" በሚል መሪ ቃል የነገ ሀገር ተረካቢ ህፃናትን አእምሯዊ እድገት ለመደገፍ የሚያስችል ዘመናዊ የመዋዕለ ህፃናት ግንባታ መሠረት ድንጋይ አኖሯል።

​በዚሁ መርሃ ግብር ላይ ኢንስቲትዩቱ ከግንባታው ባሻገር ለአንድ ሺህ ተማሪዎች የሚሆን የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ለሆሳዕና ከተማ ከንቲባ ለአቶ ሳሙኤል ሽጉጤ እና ለትምህርት ጽሕፈት ቤት ሃላፊው አስረክቧል።

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ነጋሽ የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሀገራዊ አንድነትን እንደሚያጠናክር ገልጸው፣ ደረጃውን የጠበቀ እና በቴክኖሎጂ የታገዘ የትምህርት ቁሳቁስ የሚሟላለት ይህ መዋዕለ ህፃናት በአጭር ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ ለአገልግሎት እንዲበቃ አስፈላጊው ክትትል እንደሚደረግ አረጋግጠዋል።

የሆሳዕና ከተማ ከንቲባ አቶ ሳሙኤል ሽጉጤ እና የአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎች ለተከናወኑት የልማትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች ለኢንስቲትዩቱ አመራሮችና ሠራተኞች ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ለ Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) ሚዲያና ኮሙኒኬሽን

ያፌት ገ/ህይወት

ከሀዲያ ዞን ፤ ሆሳዕና

Getu Temesgen
1 day ago
የጤናው ዘርፍ የአረንጓዴ አሻራ ተሳትፎ

‎📌 ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል

‎#ethiopia | ​በሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች እንዲሁም ሰራተኞች ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ከገፈርሳ ጉጄ ክፍለ ከተማ ጋር በመተባበር በዛሬ እለት በገፈርሳ ሰው ሰራሽ ሀይቅ ዳርቻ ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል።

‎በሸገር ከተማ በገፈርሳ ጉጄ አካባቢ በተካሄደው በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች እና የየደረጃው የአካባቢው አመራሮች እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላትና የማህበረሰብ ክፍሎች ከማለዳው 1 ሰዓት ጀምሮ በመገኘት ችግኝ ተክለዋል።

‎​የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ አረንጓዴ አሻራ እና የጤና ዘርፍ የማይለያዩ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። ችግኝ ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን ለህብረተሰብ ጤና፣ ለንጹህ አየር እና ለምግብ ዋስትና ማሻሻያ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፣ በተለይም ለአዲስ አበባ እና ለአካባቢው ህዝብ የንጹህ ውሃ ምንጭ የሆነውን የገፈርሳ አካባቢን መንከባከብ የሁላችንም ህብረ-ብሄራዊ ሀገራዊ ኃላፊነት እንደሆነ አስገንዝበዋል።

‎​በዕለቱ በቦታው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ አካባቢዋን ለመጠበቅ የምታደርገው ጥረት በንግግር ሳይሆን በተግባር የሚገለጽ መሆኑን አብራርተዋል።

‎በዕለቱ ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን ከ30 ሺህ በላይ ችግኞችን የተከለ ሲሆን፣ በክረምቱ የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ-ግብር ደግሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ እስከ 250 ሺህ ችግኞችን ለመትከል እና ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ነጻ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ሚኒስትሯ ገልጸዋል።

‎​በመጨረሻም ክብርት ሚኒስትሯ፣ የጤና ባለሙያዎች እና መላው የሀገራችን ህዝብ ቀኑ ሳያልቅ እና ጀምበር ሳትጠልቅ የድርሻቸውን ችግኝ በመትከል የዚህ ታሪካዊ ኩነት አካል እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።

‎ከችግኝ ተከላው መርሐግብር ባሻገር የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በሸገር ከተማ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።

‎በጌትነት ተመስገን
‎📷 ከበደ መክብብ

‎#ministryofhealth ​#treeplanting
‎​#climateaction ​#publichealth
‎​#environmentalhealth ​#gefersa ​#cleanenvironment ​#greenethiopia
‎​#communitysupport

Getu Temesgen
1 day ago
እስራኤል ፍልስጤማውያን ታሳሪዎችን በአዞዎችን ለመክበብ የማሠቧ ነገር ውድቅ ሆኗል
#ethiopia | ​የእስራኤል ፍርድ ቤት የብሔራዊ ደህንነት ሚኒስትሩ ኢታማር ቤን-ግቪር ፍልስጤማውያን እስረኞች በሚገኙበት የኬትዚኦት እስር ቤት ዙሪያ አዞዎችን ለማስቀመጥ አስበው የነበረውን አወዛጋቢ እቅድ በጊዜያዊነት አገደ።

ፍርድ ቤቱ ይህንን ውሳኔ ያሳለፈው 'ሌት ዘ ኤኒማልስ ሊቭ' የተሰኘው የእንስሳት መብት ተሟጋች ቡድን ያቀረበውን አቤቱታ ተከትሎ ነው።

ጉዳዩን የተመለከቱት ዳኛ የታቀደው አሰራር በእንስሳቱ ላይ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል ተብሎ የቀረበው ስጋት በደንብ ሊመረመርና ሊፈተሽ እንደሚገባ በማሳሰብ እቅዱ እንዳይፈጸም እግድ ጥለውበታል።

የተገበረውን የሰው ልጅ በአውሬ ከቦ ማሠር ከሰብዓዊ መብት አንጻር ምን አንድምታ እንዳለው ግን የተባለ ነገር የለም።

በያፌት ገ/ህይወት

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu

Getu Temesgen
1 day ago
ብዕሩም እንደ አንደበቱ የሰላ ነው
#ethiopia | የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ በተለየ የጽሁፍ ዘይቤአቸው እና ጥልቅ በሆነ ሃሳባቸው ይታወቃሉ።

ከጻፏቸው መጻሕፍት መካከል በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ አድናቆት ያገኙት እና ከፍተኛ ተነባቢ ከሚባሉት መካከል እነዚህ ተጠቃሽ ናቸው።

በፈረንጆቹ 2020 ላይ ተፅፎ ለንባብ የበቃው A promised Land ወይም የተስፋይቱ ምድር የተሰኘው መፅሐፋቸው እጅግ ተነባቢ ከሆኑት መካከል ይጠቀሳል።

ይህ መጽሐፍ የአሜሪካ ፕሬዝዳንትነት ትዝታዎች የመጀመሪያ ክፍል ሲሆን የኦባማ በጣም ታዋቂው እና በስፋት የተነበበው ሥራ ነው።

መፅሐፉ ከለጋ የፖለቲካ ህይወቱ ጀምሮ በ2008 የነበረውን ታሪካዊ የምርጫ ድል እና የመጀመሪያውን የስልጣን ዘመን እስከ ኦሳማ ቢን ላደን መገደል ይተርካል።

በተጨማሪም ከዋና ዋና ታሪካዊ ውሳኔዎች ጀርባ የነበረውን ውስጣዊ ስሜት የፖለቲካ ውጥረቶች እና የስልጣን ፈተናዎችን ግልጽ በሆነ መንገድ ያቀርባል።

ሌላው ኦባማ ወደ ፖለቲካው ዓለም ከመግባታቸው በፊት የጻፉት እና የብዙዎችን ትኩረት የሳበ ግላዊ ታሪካቸው የሆነው መፅፍ ደግሞ "Dreams from my Father"ይሰኛል።

መፅሐፉ በዋናነት ማንነትን ፍለጋ ስለ ዘር ሐረጋቸው እና ስለ አባታቸው ታሪክ ለመረዳት ያደረጉትን ጉዞ ያብራራል።

ስሜት ቀስቃሽ እና ፍልስፍናዊ በሆነ የጽሁፍ ውበት የተዋቀረ በመሆኑ በብዙዎች ዘንድ ከምርጥ ግላዊ ታሪክ መጻሕፍት መካከል ተመራጭ አድርጎታል።

ሶስተኛው የኦባማ ተመራጭ መፅሐፍ
The Audacity of Hope ይሰኛል።

ይህ መጽሐፋቸው የአሜሪካ ፖለቲካዊ ክፍፍል እንዴት ማስተካከል እንደሚቻል የፖለቲካ እሴቶች እና ለወደፊት አሜሪካ ያለውን ተስፋና ራዕይ ያቀርባል።

የኦባማን የፖለቲካ ፍልስፍና እና የኋለኛውን የፕሬዝዳንትነት ዘመናቸው መሪ ሃሳብ በጥሩ ሁኔታ የሚያሳይ መፅሐፍ ነው።

ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #barackobama #apromisedland #theaudacityofhope #dreamsfrommyfather

Getu Temesgen
1 day ago
#ethiopia | "ኢትዮጵያውያን ዝቅ ብለው ለመሬት አደራ ይሰጣሉ፤ ምድርም የተሰጣትን አደራ እጥፍ አድርጋ ትመልሳለች፡፡"

- የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር
እናት አለም መለሰ

***
በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የተዘጋጀው ታሪካዊ ሀገራዊ መርሐ ግብር በይፋ ተጀመረ

ኢትዮጵያ በአንድ ቀን 800 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል አዲስ ታሪክ ለመጻፍ ያቀደችውን ሀገራዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ዛሬ በይፋ ጀምራለች።

የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰ በሰጡት መግለጫ፣ መላው ኢትዮጵያውያን የተጎሳቀለችውን ምድር ለመመለስና ለቀጣይ ትውልድ ዘላቂ አሻራ ለማኖር በአንድነት መነሳታቸውን ገልጸዋል።

ሚኒስትሯ፣ “ኢትዮጵያውያን ዝቅ ብለው ለምድር አደራ ይሰጣሉ፤ ምድርም የተሰጣትን አደራ እጥፍ አድርጋ ትመልሳለች” በማለት የሕዝቡን የአንድነት መንፈስና ለተፈጥሮ ያለውን ቁርጠኝነት አድንቀዋል።

በ“ኑ ተስፋን እንትከል” በሚል መሪ ሐሳብ የሚካሄደው የዘንድሮው ዘመቻ፣ በመደመር መርህ ሁሉም የማኅበረሰብ ክፍሎች በንቃት እንዲሳተፉና 800 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ቀን የመትከል ግብ እንዲሳካ ጥሪ ቀርቧል።

መርሐ ግብሩ ዛሬ ሐምሌ 27/2018 ዓ.ም. እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ድረስ በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ ሁሉም ክልሎችና የማኅበረሰብ ክፍሎች ተሳትፎ በሰፊው እንደሚከናወን ተገልጿል።

ይህ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በአካባቢ ጥበቃ፣ የደን ሽፋን መጨመር፣ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም እና ለቀጣዩ ትውልድ አረንጓዴ ኢትዮጵያን ለማስረከብ ከሚደረጉ ሀገራዊ ጥረቶች መካከል ቁልፍ ተነሳሽነት መሆኑ ተጠቅሷል።
#አረንጓዴአሻራ #greenlegacy #ethiopia #planttrees #climateaction #ጌጡተመስገን #getutemesgen

Getu Temesgen
2 days ago
የኤሎን ማስክን የሳለችው ደጋፊ በራሱ ታገደች? ከ11 ሚሊዮን በላይ እይታ አግኝታለች
#ethiopia | በElon Musk ዙሪያ የተነሳ አዲስ የማኅበራዊ ሚዲያ ጉዳይ በዓለም አቀፍ የዲጂታል ማኅበረሰብ ውስጥ ሰፊ ውይይት አስነስቷል።

አንዲት የማስክ ደጋፊ በእርሳስ የሳለችውን የማስክ ምስል በማኅበራዊ ሚዲያ በማጋራት "ለእርስዎ ብቻ የተሰራ ስጦታ ነው" ስትል ገልጻለች።

በ24 ሰዓታት ውስጥ ምስሉ 11 ሚሊዮን ያህል እይታ እንዳገኘ ተነግሯል። አንዳንዶች ሥዕሉ ማስክን በትክክል እንደሚመስል ሲገልጹ፣ ሌሎች ግን ተመሳሳይነቱን ተቃውመዋል።

በዚህ መካከል ብዙ ተጠቃሚዎች ማስክ ሥዕሉን እንዲያይ በተደጋጋሚ መለያውን (tag) ማድረግ ጀመሩ።

ይሁን እንጂ ማስክ በይፋ ምንም አስተያየት አልሰጠም ተብሏል። ከዚህ ይልቅ ሥዕሉን ያጋራችውን ተጠቃሚ ከመለያው ላይ አግዶታል የሚል ምስል (screenshot) በመስመር ላይ ተሰራጭቷል። ይህ የእገዳ ምስል ከመጀመሪያው ሥዕል የበለጠ ትኩረት መሳቡ ተነግሯል።

ሆኖም ይህን ክስተት በተመለከተ ጥርጣሬዎችም ተነስተዋል። አንዳንድ ተጠቃሚዎች የተሰራጨው ሥዕል ከቀድሞ የተወሰደ ሊሆን እንደሚችል እና የእገዳው ማስረጃም የተረጋገጠ እንዳልሆነ ጠቁመዋል። እስካሁን ድረስ ከማስክ ወይም ከX ድርጅት ይፋዊ ማረጋገጫ አልተሰጠም።

በአጠቃላይ ይህ ጉዳይ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የታዋቂ ሰዎች ከደጋፊዎቻቸው ጋር ያላቸውን ግንኙነት፣ የመለያ እገዳ (blocking) አጠቃቀም እና የቫይራል ይዘቶች እንዴት በፍጥነት እንደሚሰራጩ ዳግም ወደ ውይይት አምጥቶታል።

በአሁኑ ጊዜ ማስክ ለምን ይህን እርምጃ እንደወሰደ የሚያረጋግጥ ይፋዊ ምክንያት የለም።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)

Getu Temesgen
2 days ago
መልካም ጉዞ...

ተፃፈ በመሐሪ ነጋሽ
(የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ኮሚኒኬሽን )
#ethiopia | ዛሬ ማምሻውን የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ልዑክ ቡድናችንን በከፍተኛ ኩራትና በመልካም ምኞት ወደ አሜሪካ ኦሪገን ሸኝተናል።

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አትሌቶቻችን በተሟላ ዝግጅት ወደ ሻምፒዮናው እንዲያቀኑ ሱሉልታ በሚገኘው የጀግናው ኦሊምፒያን አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ሆቴል በማሳረፍ አስፈላጊውን ድጋፍ፣ ክትትልና ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቷል።

የቀነኒሳ በቀለ ሆቴልም አትሌቶቻችንን እንደቤተሰቦቹ በመቀበል፣ በፍቅር፣ በአክብሮትና በልዩ እንክብካቤ እስከ ሽኝታቸው ድረስ አግዟቸዋል።

ለዚህ ውድ አስተዋፅኦ ከልብ የመነጨ ምስጋና ተቀበሉ

ዓለም የሚጠብቀው ሻምፒዮና 21ኛው የዓለም ከ20 ዓመት በታች (World Athletics U20 Championships) ሻምፒዮና ....

በአሜሪካ ኦሪገን ግዛት ዩጂን ከተማ በሚገኘው ታሪካዊው ሄይዋርድ ፊልድ ከሐምሌ 29 እስከ ነሐሴ 3 ይካሄዳል።

ከ1,700 በላይ ወጣት አትሌቶች ከ190 የሚጠጉ አገራት በ44 የውድድር ዓይነቶች ላይ ይፎካከራሉ።

ዩጂን ከተማ በግምት 180,000 የሚጠጋ ህዝብ ያላት ብትሆንም፣ በዓለም ላይ "Track Town USA" በሚል ስም የምትታወቅ የአትሌቲክስ ዋና መዲና ናት።

የሻምፒዮናው ትኬቶች በፍጥነት እየተሸጡ እንደሆነ አዘጋጆቹ ገልጸዋል፣ ውድድሩም በብዙ የዓለም አቀፍ የቴሌቪዥን ኔትወርኮች፣ ዲጂታል መድረኮች እና በመቶዎች የሚቆጠሩ የስፖርት ጋዜጠኞች ይሸፈናል። የዚህ ውድድር ቀደምት እትሞች በ140 በላይ አገራት በቴሌቪዥን ተሰራጭተው 16 ሚሊዮን በላይ የተጠራቀመ የቲቪ ተመልካች ደርሰው ነበር።

በ2024 በፔሩ ሊማ በተካሄደው 20ኛው ሻምፒዮና ኢትዮጵያ 6 የወርቅ፣ 1 የብር እና 2 የነሐስ ሜዳሊያዎችን በማሸነፍ በአጠቃላይ 9 ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ በዓለም 2ኛ ደረጃን ማስመዝገቧ ይታወሳል።

ዘንድሮም አትሌቶቻችን በ5000 ሜትር፣ 3000 ሜትር፣ 1500 ሜትር፣ 800 ሜትር፣ 3000 ሜትር መሰናክል፣ 400 ሜትር እና በርምጃ ውድድሮች ላይ የኢትዮጵያን ስም በክብር ለማስጠራት ዝግጁ ናቸው።

ለጀግኖቻችን...
ውድ አትሌቶቻችን!
ከእናንተ ጋር የሚጓዘው የኢትዮጵያ 60 ዓመታትን ያስቆጠረ የድል ታሪክ ነው፤ የአበበ ቢቂላ ጨምሮ
የብዙ ጀግኖች የድል አሻራ ነው።

ኢትዮጵያውያን ልብ ከእናንተ ጋር ነው። በእግራችሁ የምትሮጡት ለራሳችሁ ብቻ ሳይሆን ለሀገራችሁ፣ ለሕዝባችሁ እና ለመጪው ትውልድ ነው።

መልካም ጉዞ!
መልካም ውድድር!

መልካም ዕድል! 🇪🇹❤️

Getu Temesgen
2 days ago
በዚህ ዓመት ቼልሲን ነው ማየት
#ethiopia | ​አርጀንቲናዊው አማካይ ቫለንቲን ‘ኮሎ’ ባርኮ ከፈረንሳዩ አርሲ ስትራስቡርግ በቋሚ ዝውውር ወደ ቼልሲ ለማቀናት የሚያስችለውን ስምምነት በይፋ ማጠናቀቁ ተረጋገጠ።

በዚህ ወር አዲሱን ክለቡን የሚቀላቀለው ይህ ወጣት ተጫዋች ወደ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ለመመለስ ሙሉ ዝግጅቱን ያጠናቀቀ ሲሆን ሁሉም አስፈላጊ የውል ስምምነቶችም በይፋ ተፈራርመዋል።

የአሰልጣኝ ሻቢ አሎንሶን ሙሉ ይሁኝታ ያገኘው የባርኮ ዝውውር የቼልሲን የአማካይ ክፍል በከፍተኛ ሁኔታ ያጠናክራል ተብሎ ተስፋ ተጥሎበታል።

በያፌት ገ/ህይወት

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu