18 days ago
የሰላም ድርድር መቋረጥ፣ የሆርሙዝ ሰርጥ አዳዲስ ክልከላዎች እና የባራካህ የኑክሌር ጣቢያ ጥቃት
**************
በመካከለኛው ምሥራቅ የሰላም ድርድር ጥረቶች፣ በሆርሙዝ ሰርጥ የባሕር ላይ መተላለፊያ ቁጥጥር እና በተመዘገቡ የጸጥታ ስጋቶች ዙሪያ አዳዲስ ክስተቶች ተመዝግበዋል።
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የነበረው ቀጥተኛ ድርድር መቋረጡን ተከትሎ ዲፕሎማሲያዊ ውጥረቱ ያሻቀበ ሲሆን፣ የንግድ መርከቦች እንቅስቃሴን ለመቆጣጠርም አዳዲስ እርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ።
የፓኪስታን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ሞህሲን ናቅቪ አስቀድሞ ያልተገለጸ የሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ቴህራን መግባታቸውን የፓኪስታኑ ‘ዶን’ ጋዜጣ ዲፕሎማቲክ ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል።
ይህ አስቸኳይ ጉብኝት የተደረገው የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራንን የቅርብ ጊዜ የሰላም አማራጭ ውድቅ ማድረጋቸውን ተከትሎ፣ የሰላም ድርድሩ ሙሉ በሙሉ እንዳይደናቀፍ ለማድረግ የተጀመረው የሽምግልና ጥረት አካል መሆኑ ተገልጿል።
የኢራኑ ‘ተስኒም’ የዜና ወኪል በበኩሉ፣ ሚኒስትሩ ከኢራን አቻቸው ኤስካንዳር ሞሜኒ እና ከፓርላማ አፈ-ጉባኤ መሐመድ ባጌር ጋሊባፍ ጋር ተገናኝተው በዋሽንግተን እና ቴህራን መካከል ያለውን የሰላም ድርድር ማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውን ጠቁሟል።
ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ እንዳስነበበው፣ ፕሬዚዳንት ትራምፕ የኢራንን የሰላም ሃሳብ ውድቅ ቢያደርጉም፤ ኢራን የኑክሌር መርሐ ግብሯን ለ20 ዓመታት እንድታግድ የሚጠይቅ አማራጭ አቅርበዋል።
ይሁን እንጂ የኢራን ባለሥልጣናት በአሜሪካ ወገን ምንም ዓይነት ተጨባጭ የዲፕሎማሲ አካሄድ ለውጥ አልታየም ሲሉ መተቸታቸውን መህር የዜና ወኪል ዘግቧል።
የሆርሙዝ ሰርጥን በተመለከተ ኢራን የባሕር ላይ መተላለፊያውን ለመቆጣጠር አዲስ “ሙያዊ የአሠራር ሥርዓት” ያለችውን የቁጥጥር ሥርዓት ይፋ እንደምታደርግ አስታውቃለች።
የኢራን ፓርላማ የብሔራዊ ደኅንነት ኮሚቴ ሰብሳቢ ኢብራሂም አዚዝን ጠቅሶ ሮይተርስ እንደዘገበው፣ አዲሱ አሠራር ከኢራን ጋር ለሚተባበሩ የንግድ መርከቦች ብቻ ቅድሚያ የሚሰጥ ሲሆን፣ የአሜሪካ ደጋፊ ለሆኑ መርከቦች ግን ዝግ ይሆናል።
በተጨማሪም ኢራን በዲጂታል እና በቢትኮይን ክፍያ የሚሠራ “ሆርሙዝ ሴፍ” የተባለ አዲስ የባሕር ላይ መድን ይፋ ማድረጓን ፋርስ የዜና ወኪል አረጋግጧል።
በሆርሙዝ ሰርጥ ያለው የባሕር ላይ ትራፊክ አሁንም እንደቀዘቀዘ መሆኑን እና አንዳንድ የአውሮፓ ሀገራት መርከቦቻቸው በሰላም እንዲያልፉ ከኢራን አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ጋር ድርድር መጀመራቸውን ብሉምበርግ ዘግቧል።
በሌላ በኩል የቀጣናውን ሰላም ይበልጥ አሳሳቢ የሚያደርግ ክስተት ተመዝግቧል። በተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች በሚገኘው የባራካህ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ የድሮን ጥቃት ደርሷል።
‘አሶሺዬትድ ፕሬስ' እንደዘገበው ጥቃቱ ከኃይል ማመንጫው የውስጠኛው አጥር ውጭ በሚገኝ የኤሌክትሪክ ጄነሬተር ላይ እሳት ቢያስነሳም፣ የኢምሬቶች ባለሥልጣናት እሳቱን በፍጥነት መቆጣጠር መቻሉን እና ምንም ዓይነት የጨረር ስጋትም ሆነ የሰው ጉዳት አለመድረሱን አረጋግጠዋል።
ዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኃይል ኤጀንሲ (IAEA) ዋና ዳይሬክተር ራፋኤል ግሮሲ ጥቃቱን “ተቀባይነት የሌለው” ሲሉ አውግዘውታል።
በመካከለኛው ምሥራቅ በአንድ በኩል ዲፕሎማሲያዊ የሰላም ጥረቶች ቢቀጥሉም፣ በሌላ በኩል እየተከሰቱ ያሉ የጸጥታ ስጋቶች ቀውሱ ወደ ከፋ ጦርነት እንዳያመራ ከፍተኛ ስጋት መፍጠራቸውን ዓለም አቀፍ የጂኦፖለቲካ ተንታኞች በማስጠንቀቅ ላይ ይገኛሉ።
በለሚ ታደሰ
#middleeastcrisis #peacetalks #straitofhormuz #diplomacy #globalenergy
**************
በመካከለኛው ምሥራቅ የሰላም ድርድር ጥረቶች፣ በሆርሙዝ ሰርጥ የባሕር ላይ መተላለፊያ ቁጥጥር እና በተመዘገቡ የጸጥታ ስጋቶች ዙሪያ አዳዲስ ክስተቶች ተመዝግበዋል።
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የነበረው ቀጥተኛ ድርድር መቋረጡን ተከትሎ ዲፕሎማሲያዊ ውጥረቱ ያሻቀበ ሲሆን፣ የንግድ መርከቦች እንቅስቃሴን ለመቆጣጠርም አዳዲስ እርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ።
የፓኪስታን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ሞህሲን ናቅቪ አስቀድሞ ያልተገለጸ የሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ቴህራን መግባታቸውን የፓኪስታኑ ‘ዶን’ ጋዜጣ ዲፕሎማቲክ ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል።
ይህ አስቸኳይ ጉብኝት የተደረገው የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራንን የቅርብ ጊዜ የሰላም አማራጭ ውድቅ ማድረጋቸውን ተከትሎ፣ የሰላም ድርድሩ ሙሉ በሙሉ እንዳይደናቀፍ ለማድረግ የተጀመረው የሽምግልና ጥረት አካል መሆኑ ተገልጿል።
የኢራኑ ‘ተስኒም’ የዜና ወኪል በበኩሉ፣ ሚኒስትሩ ከኢራን አቻቸው ኤስካንዳር ሞሜኒ እና ከፓርላማ አፈ-ጉባኤ መሐመድ ባጌር ጋሊባፍ ጋር ተገናኝተው በዋሽንግተን እና ቴህራን መካከል ያለውን የሰላም ድርድር ማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውን ጠቁሟል።
ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ እንዳስነበበው፣ ፕሬዚዳንት ትራምፕ የኢራንን የሰላም ሃሳብ ውድቅ ቢያደርጉም፤ ኢራን የኑክሌር መርሐ ግብሯን ለ20 ዓመታት እንድታግድ የሚጠይቅ አማራጭ አቅርበዋል።
ይሁን እንጂ የኢራን ባለሥልጣናት በአሜሪካ ወገን ምንም ዓይነት ተጨባጭ የዲፕሎማሲ አካሄድ ለውጥ አልታየም ሲሉ መተቸታቸውን መህር የዜና ወኪል ዘግቧል።
የሆርሙዝ ሰርጥን በተመለከተ ኢራን የባሕር ላይ መተላለፊያውን ለመቆጣጠር አዲስ “ሙያዊ የአሠራር ሥርዓት” ያለችውን የቁጥጥር ሥርዓት ይፋ እንደምታደርግ አስታውቃለች።
የኢራን ፓርላማ የብሔራዊ ደኅንነት ኮሚቴ ሰብሳቢ ኢብራሂም አዚዝን ጠቅሶ ሮይተርስ እንደዘገበው፣ አዲሱ አሠራር ከኢራን ጋር ለሚተባበሩ የንግድ መርከቦች ብቻ ቅድሚያ የሚሰጥ ሲሆን፣ የአሜሪካ ደጋፊ ለሆኑ መርከቦች ግን ዝግ ይሆናል።
በተጨማሪም ኢራን በዲጂታል እና በቢትኮይን ክፍያ የሚሠራ “ሆርሙዝ ሴፍ” የተባለ አዲስ የባሕር ላይ መድን ይፋ ማድረጓን ፋርስ የዜና ወኪል አረጋግጧል።
በሆርሙዝ ሰርጥ ያለው የባሕር ላይ ትራፊክ አሁንም እንደቀዘቀዘ መሆኑን እና አንዳንድ የአውሮፓ ሀገራት መርከቦቻቸው በሰላም እንዲያልፉ ከኢራን አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ጋር ድርድር መጀመራቸውን ብሉምበርግ ዘግቧል።
በሌላ በኩል የቀጣናውን ሰላም ይበልጥ አሳሳቢ የሚያደርግ ክስተት ተመዝግቧል። በተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች በሚገኘው የባራካህ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ የድሮን ጥቃት ደርሷል።
‘አሶሺዬትድ ፕሬስ' እንደዘገበው ጥቃቱ ከኃይል ማመንጫው የውስጠኛው አጥር ውጭ በሚገኝ የኤሌክትሪክ ጄነሬተር ላይ እሳት ቢያስነሳም፣ የኢምሬቶች ባለሥልጣናት እሳቱን በፍጥነት መቆጣጠር መቻሉን እና ምንም ዓይነት የጨረር ስጋትም ሆነ የሰው ጉዳት አለመድረሱን አረጋግጠዋል።
ዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኃይል ኤጀንሲ (IAEA) ዋና ዳይሬክተር ራፋኤል ግሮሲ ጥቃቱን “ተቀባይነት የሌለው” ሲሉ አውግዘውታል።
በመካከለኛው ምሥራቅ በአንድ በኩል ዲፕሎማሲያዊ የሰላም ጥረቶች ቢቀጥሉም፣ በሌላ በኩል እየተከሰቱ ያሉ የጸጥታ ስጋቶች ቀውሱ ወደ ከፋ ጦርነት እንዳያመራ ከፍተኛ ስጋት መፍጠራቸውን ዓለም አቀፍ የጂኦፖለቲካ ተንታኞች በማስጠንቀቅ ላይ ይገኛሉ።
በለሚ ታደሰ
#middleeastcrisis #peacetalks #straitofhormuz #diplomacy #globalenergy
1 month ago
በሆርሙዝ ሰርጥ ያለውን ውጥረት ለማርገብ ዓለም አቀፍ የሰላም ጥረቶች ተጠናክረው ቀጥለዋል
************
በመካከለኛው ምሥራቅ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ አሁንም በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ቢገኝም፣ ቀጣናውን ለማረጋጋት የሚደረጉ ዓለም አቀፍ የሰላም ጥረቶች እና የዲፕሎማሲ መስመሮች ክፍት ሆነው ቀጥለዋል።
ሮይተርስ የዜና ወኪል ባለፉት ስድስት ሰዓታት ውስጥ ከዋሽንግተን ያወጣው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን በፓኪስታን በኩል ያቀረበችውን ባለ 14 ነጥብ አዲስ የሰላም የውሳኔ ሃሳብ "አላረካኝም" በማለት ለጊዜው ውድቅ አድርገውታል።
ምንም እንኳን ትራምፕ ከኢራን ጋር የነበረው ቀጥተኛ ወታደራዊ ግጭት በይፋዊ መግለጫ አብቅቷል ቢሉም፣ አልጀዚራ የዋይት ሃውስ ምንጮችን ጠቅሶ እንደዘገበው በሆርሙዝ ሰርጥ እና በኢራን ወደቦች ላይ ያለው የአሜሪካ የባሕር ላይ እገዳ ከመቼውም ጊዜ በላይ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ፕሬዝዳንቱ የአሜሪካ ባሕር ኃይል የኢራንን የነዳጅ መርከቦች መያዙን እና ጭነቱን መውረሱን ሲገልጹ፣ ኢራን በበኩሏ ድርጊቱን ከባሕር ላይ ወንበዴነት ጋር በማመሳሰል ከፍተኛ ቁጣዋን ገልጻለች።
ይህ ውጥረት ቢኖርም የሰላም ተስፋው ሙሉ በሙሉ አልተዘጋም። በፓኪስታን አሸማጋይነት የሚመራው የተኩስ አቁም ድርድር ጥረት አሁንም እንደቀጠለ መሆኑን የተለያዩ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ዘግበዋል።
ታዋቂው የመካከለኛው ምሥራቅ የፖለቲካ ተንታኝ ሰይድ መሐመድ አሊ ለቢቢሲ በሰጡት ማብራሪያ፣ በዋሽንግተን እና በቴህራን መካከል ያለው የቆየ ቅራኔ በአንድ ጀምበር የሚፈታ ባለመሆኑ የድርድሩ መዘግየት እንደ ውድቀት ሊወሰድ እንደማይገባ አሳስበዋል።
በተቃራኒው የኢራን መንፈሳዊ መሪ ተወካይ አብዱል መጂድ ሃኪም ኢላሂ ወቅታዊውን ሁኔታ "ጦርነትም የለም ሰላምም የለም" በማለት የገለጹት ሲሆን፣ የኢራን ወታደራዊ ባለሥልጣናት "አሜሪካ ለገባችው ቃል ታማኝ አይደለችም" በማለት ዳግም ጦርነት የመቀስቀሱ ዕድል እንዳለ እያስጠነቀቁ ይገኛሉ።
በቀጣናዊ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ዙሪያ የሊባኖስ ጦር አዛዥ ጄኔራል ሩዶልፍ ሃይካል ከአሜሪካው ጄኔራል ጆሴፍ ክሊርፊልድ ጋር በቤይሩት ተገናኝተው የሊባኖስን ደኅንነት ማስጠበቅ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል።
በተያያዘ ዜና፣ የዓለም የነዳጅ ገበያ የደም ስር የሆነው የሆርሙዝ ሰርጥ አሁንም በከፊል ዝግ ሆኖ የሚገኝ ሲሆን፣ የንግድ መርከቦች እንቅስቃሴ በ95 በመቶ በመቀነሱ የዓለም አቀፉ የነዳጅ ዋጋ እንደናረ ቀጥሏል።
የፋይናንሻል ታይምስ ዘገባ እንደሚያሳየው፣ ይህንን የዓለም አቀፉን የነዳጅ ገበያ መናጋት ተከትሎ ቻይና "አሜሪካ በኢራን ነዳጅ ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ዓለም አቀፍ ሕግን የጣሰ ነው" በማለት ውድቅ አድርገዋለች። ኩባንያዎቿም ከኢራን ነዳጅ መግዛታቸውን እንደሚቀጥሉ ማሳወቋ ሁኔታውን ይበልጥ ውስብስብ አድርጎታል።
ከሰብአዊ ቀውስ አኳያ የዓረብ ሊግ ዋና ጸሐፊ አሕመድ አቡል ገይት ለዋሽንግተን እና ለብራስልስ በላኩት ደብዳቤ፣ እስራኤል በተመድ የፍልስጤም ስደተኞች የእርዳታ እና ስራዎች ኤጀንሲ (UNRWA) ላይ የወሰደችው የክልከላ እርምጃ በቀጣናው ያለውን ሰብአዊ ቀውስ የሚያባብስ መሆኑን ጠቁመዋል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ መካከለኛው ምሥራቅ ማንም ሊቆጣጠረው ወደማይችል አደገኛ የክስተቶች ሰንሰለት ውስጥ እንዳይገባ ሁሉም ወገኖች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እና ወደ ሰላም ጠረጴዛ እንዲመለሱ ጥብቅ ጥሪ አቅርበዋል።
በአሁኑ ወቅት መካከለኛው ምሥራቅ ፈታኝ ሁኔታዎች ቢገጥሙትም፣ ክፍት በሆኑ የዲፕሎማሲያዊ መስመሮች እና በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የማያቋርጡ የሰላም ጥሪዎች ታግዞ ከሰፊ ክልላዊ ጦርነት ይልቅ ወደ መረጋጋት ሊያመራ በሚችልበት ወሳኝ ምዕራፍ ሊሸጋገር ይችላል የሚለው ተስፋ አሁንም አልተንጠፈጠፈም።
በለሚ ታደሰ
Ethiopian Broadcasting Corporation #middleeastcrisis #iranusnegotiations #hormuzstrait #worldpolitics #peaceefforts #globalenergy
************
በመካከለኛው ምሥራቅ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ አሁንም በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ቢገኝም፣ ቀጣናውን ለማረጋጋት የሚደረጉ ዓለም አቀፍ የሰላም ጥረቶች እና የዲፕሎማሲ መስመሮች ክፍት ሆነው ቀጥለዋል።
ሮይተርስ የዜና ወኪል ባለፉት ስድስት ሰዓታት ውስጥ ከዋሽንግተን ያወጣው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን በፓኪስታን በኩል ያቀረበችውን ባለ 14 ነጥብ አዲስ የሰላም የውሳኔ ሃሳብ "አላረካኝም" በማለት ለጊዜው ውድቅ አድርገውታል።
ምንም እንኳን ትራምፕ ከኢራን ጋር የነበረው ቀጥተኛ ወታደራዊ ግጭት በይፋዊ መግለጫ አብቅቷል ቢሉም፣ አልጀዚራ የዋይት ሃውስ ምንጮችን ጠቅሶ እንደዘገበው በሆርሙዝ ሰርጥ እና በኢራን ወደቦች ላይ ያለው የአሜሪካ የባሕር ላይ እገዳ ከመቼውም ጊዜ በላይ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ፕሬዝዳንቱ የአሜሪካ ባሕር ኃይል የኢራንን የነዳጅ መርከቦች መያዙን እና ጭነቱን መውረሱን ሲገልጹ፣ ኢራን በበኩሏ ድርጊቱን ከባሕር ላይ ወንበዴነት ጋር በማመሳሰል ከፍተኛ ቁጣዋን ገልጻለች።
ይህ ውጥረት ቢኖርም የሰላም ተስፋው ሙሉ በሙሉ አልተዘጋም። በፓኪስታን አሸማጋይነት የሚመራው የተኩስ አቁም ድርድር ጥረት አሁንም እንደቀጠለ መሆኑን የተለያዩ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ዘግበዋል።
ታዋቂው የመካከለኛው ምሥራቅ የፖለቲካ ተንታኝ ሰይድ መሐመድ አሊ ለቢቢሲ በሰጡት ማብራሪያ፣ በዋሽንግተን እና በቴህራን መካከል ያለው የቆየ ቅራኔ በአንድ ጀምበር የሚፈታ ባለመሆኑ የድርድሩ መዘግየት እንደ ውድቀት ሊወሰድ እንደማይገባ አሳስበዋል።
በተቃራኒው የኢራን መንፈሳዊ መሪ ተወካይ አብዱል መጂድ ሃኪም ኢላሂ ወቅታዊውን ሁኔታ "ጦርነትም የለም ሰላምም የለም" በማለት የገለጹት ሲሆን፣ የኢራን ወታደራዊ ባለሥልጣናት "አሜሪካ ለገባችው ቃል ታማኝ አይደለችም" በማለት ዳግም ጦርነት የመቀስቀሱ ዕድል እንዳለ እያስጠነቀቁ ይገኛሉ።
በቀጣናዊ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ዙሪያ የሊባኖስ ጦር አዛዥ ጄኔራል ሩዶልፍ ሃይካል ከአሜሪካው ጄኔራል ጆሴፍ ክሊርፊልድ ጋር በቤይሩት ተገናኝተው የሊባኖስን ደኅንነት ማስጠበቅ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል።
በተያያዘ ዜና፣ የዓለም የነዳጅ ገበያ የደም ስር የሆነው የሆርሙዝ ሰርጥ አሁንም በከፊል ዝግ ሆኖ የሚገኝ ሲሆን፣ የንግድ መርከቦች እንቅስቃሴ በ95 በመቶ በመቀነሱ የዓለም አቀፉ የነዳጅ ዋጋ እንደናረ ቀጥሏል።
የፋይናንሻል ታይምስ ዘገባ እንደሚያሳየው፣ ይህንን የዓለም አቀፉን የነዳጅ ገበያ መናጋት ተከትሎ ቻይና "አሜሪካ በኢራን ነዳጅ ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ዓለም አቀፍ ሕግን የጣሰ ነው" በማለት ውድቅ አድርገዋለች። ኩባንያዎቿም ከኢራን ነዳጅ መግዛታቸውን እንደሚቀጥሉ ማሳወቋ ሁኔታውን ይበልጥ ውስብስብ አድርጎታል።
ከሰብአዊ ቀውስ አኳያ የዓረብ ሊግ ዋና ጸሐፊ አሕመድ አቡል ገይት ለዋሽንግተን እና ለብራስልስ በላኩት ደብዳቤ፣ እስራኤል በተመድ የፍልስጤም ስደተኞች የእርዳታ እና ስራዎች ኤጀንሲ (UNRWA) ላይ የወሰደችው የክልከላ እርምጃ በቀጣናው ያለውን ሰብአዊ ቀውስ የሚያባብስ መሆኑን ጠቁመዋል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ መካከለኛው ምሥራቅ ማንም ሊቆጣጠረው ወደማይችል አደገኛ የክስተቶች ሰንሰለት ውስጥ እንዳይገባ ሁሉም ወገኖች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እና ወደ ሰላም ጠረጴዛ እንዲመለሱ ጥብቅ ጥሪ አቅርበዋል።
በአሁኑ ወቅት መካከለኛው ምሥራቅ ፈታኝ ሁኔታዎች ቢገጥሙትም፣ ክፍት በሆኑ የዲፕሎማሲያዊ መስመሮች እና በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የማያቋርጡ የሰላም ጥሪዎች ታግዞ ከሰፊ ክልላዊ ጦርነት ይልቅ ወደ መረጋጋት ሊያመራ በሚችልበት ወሳኝ ምዕራፍ ሊሸጋገር ይችላል የሚለው ተስፋ አሁንም አልተንጠፈጠፈም።
በለሚ ታደሰ
Ethiopian Broadcasting Corporation #middleeastcrisis #iranusnegotiations #hormuzstrait #worldpolitics #peaceefforts #globalenergy
1 month ago
ቀውሱ ከ30 ሚሊዮን በላይ ሰዎችን ወደ ድህነት መቀመቅ ያወርዳል ተባለ
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣው ግጭት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ30 ሚሊዮን በላይ ሰዎችን ለከፋ ድህነት ሊዳርግ እንደሚችል የተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) አስጠነቀቀ።
ጦርነቱ በአፋጣኝ ቢቆም እንኳ፣ ቀውሱ ያስከተለው ኢኮኖሚያዊ ጠባሳ በቀላሉ የማይሻር መሆኑን ድርጅቱ ገልጿል።
የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም ኃላፊ አሌክሳንደር ዴ ክሮ ለሮይተርስ እንደገለጹት፣ ቀውሱ በተለይም በግብርናው ዘርፍ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድሯል።
አርሶ አደሮች ሰብል በሚዘሩበት ወቅት ያጋጠመው የነዳጅ እና የማዳበሪያ አቅርቦት መቋረጥ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎችን ወደ ድህነት አዘቅት ውስጥ ሊከታቸው እንደሚችል ጠቁመዋል።
ለዚህ ችግር ዋነኛ መንስኤ ተብሎ የተጠቀሰው በሆርሙዝ ሰርጥ በኩል የሚያልፉ የጭነት መርከቦች መታገድ ነው። ይህም ለግብርና ምርታማነት ወሳኝ የሆነው የማዳበሪያ እጥረት እንዲከሰትና የምርት መጠን እንዲቀንስ አድርጓል።
ሁኔታው በዓመቱ መጨረሻ በሚሰበሰበው የሰብል ምርት ላይ አሉታዊ ጥላውን እንደሚያሳርፍ የገለጹት ባለስልጣኑ፣ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለችግሩ ትኩረት እንዲሰጥ አሳስበዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#middleeastcrisis #globaleconomy #undp #agriculture #povertyalert #breakingnews #leadtheplot
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣው ግጭት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ30 ሚሊዮን በላይ ሰዎችን ለከፋ ድህነት ሊዳርግ እንደሚችል የተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) አስጠነቀቀ።
ጦርነቱ በአፋጣኝ ቢቆም እንኳ፣ ቀውሱ ያስከተለው ኢኮኖሚያዊ ጠባሳ በቀላሉ የማይሻር መሆኑን ድርጅቱ ገልጿል።
የተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም ኃላፊ አሌክሳንደር ዴ ክሮ ለሮይተርስ እንደገለጹት፣ ቀውሱ በተለይም በግብርናው ዘርፍ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድሯል።
አርሶ አደሮች ሰብል በሚዘሩበት ወቅት ያጋጠመው የነዳጅ እና የማዳበሪያ አቅርቦት መቋረጥ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎችን ወደ ድህነት አዘቅት ውስጥ ሊከታቸው እንደሚችል ጠቁመዋል።
ለዚህ ችግር ዋነኛ መንስኤ ተብሎ የተጠቀሰው በሆርሙዝ ሰርጥ በኩል የሚያልፉ የጭነት መርከቦች መታገድ ነው። ይህም ለግብርና ምርታማነት ወሳኝ የሆነው የማዳበሪያ እጥረት እንዲከሰትና የምርት መጠን እንዲቀንስ አድርጓል።
ሁኔታው በዓመቱ መጨረሻ በሚሰበሰበው የሰብል ምርት ላይ አሉታዊ ጥላውን እንደሚያሳርፍ የገለጹት ባለስልጣኑ፣ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለችግሩ ትኩረት እንዲሰጥ አሳስበዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#middleeastcrisis #globaleconomy #undp #agriculture #povertyalert #breakingnews #leadtheplot
2 months ago
የኢስላማባዱ ድርድር ያለ ስምምነት ተበተነ
#ethiopia | ዓለም ትንፋሿን ውጣ ስትጠባበቀው የነበረው የአሜሪካና የኢራን የሰላም ድርድር "ውጤት አልባ" ሆኖ መጠናቀቁን ምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ አሁን አስታወቁ።
ምን ተፈጠረ?
ለ 21 ሰዓታት በተከታታይ የተካሄደውና የፓኪስታን ባለስልጣናት ሲያደራድሩት የቆየው ንግግር፣ በዋና ዋና ጉዳዮች ላይ መስማማት ባለመቻሉ ያለምንም ስምምነት (No Deal) ተጠናቋል።
እንቅፋት የሆኑት ነጥቦች፦
አሜሪካ በኢራን የዩራኒየም ማበልጸግና በሚሳይል ክምችት ላይ የያዘችው ጠንካራ አቋም
ኢራን ሁሉም ማዕቀቦች በአስቸኳይ እንዲነሱና የአሜሪካ ጦር ቀጠናውን ለቆ እንዲወጣ ያቀረበችው ጥያቄ
የድርድሩ መፍረስ በቀጠናው ያለውን ወታደራዊ ፍጥጫ ወደ ከፋ ደረጃ ሊያሸጋግረው እንደሚችል ስጋት ተፈጥሯል።
የሰላሙ ተስፋ በድቅድቅ ጨለማ ተተክቷል!
#getu #breakingnews #jdvance #iranusa #nodeal #islamabadtalks #middleeastcrisis #globalsecurity #peacetalkscollapse #ሰበርዜና #ድርድር #አሜሪካ #ኢራን #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | ዓለም ትንፋሿን ውጣ ስትጠባበቀው የነበረው የአሜሪካና የኢራን የሰላም ድርድር "ውጤት አልባ" ሆኖ መጠናቀቁን ምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ አሁን አስታወቁ።
ምን ተፈጠረ?
ለ 21 ሰዓታት በተከታታይ የተካሄደውና የፓኪስታን ባለስልጣናት ሲያደራድሩት የቆየው ንግግር፣ በዋና ዋና ጉዳዮች ላይ መስማማት ባለመቻሉ ያለምንም ስምምነት (No Deal) ተጠናቋል።
እንቅፋት የሆኑት ነጥቦች፦
አሜሪካ በኢራን የዩራኒየም ማበልጸግና በሚሳይል ክምችት ላይ የያዘችው ጠንካራ አቋም
ኢራን ሁሉም ማዕቀቦች በአስቸኳይ እንዲነሱና የአሜሪካ ጦር ቀጠናውን ለቆ እንዲወጣ ያቀረበችው ጥያቄ
የድርድሩ መፍረስ በቀጠናው ያለውን ወታደራዊ ፍጥጫ ወደ ከፋ ደረጃ ሊያሸጋግረው እንደሚችል ስጋት ተፈጥሯል።
የሰላሙ ተስፋ በድቅድቅ ጨለማ ተተክቷል!
#getu #breakingnews #jdvance #iranusa #nodeal #islamabadtalks #middleeastcrisis #globalsecurity #peacetalkscollapse #ሰበርዜና #ድርድር #አሜሪካ #ኢራን #ጌጡተመስገን #getutemesgen
2 months ago
በ40 ቀኑ ጦርነት ኢራን 145 ቢሊዮን ዶላር አጣች
#ethiopia | በኢራን፣ በአሜሪካና በእስራኤል መካከል ለ40 ቀናት የዘለቀው አስከፊ ጦርነት በኢራን ላይ ታሪክ የማይረሳው ውድመት ጥሎ አልፏል።
የወጡ ሪፖርቶች እንደሚያመለክቱት፣ ሀገሪቱ ከአስርተ ዓመታት በኋላ ወደማታውቀው የኢኮኖሚና የወታደራዊ ቀውስ ውስጥ ገብታለች።
ከ140 እስከ 145 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ሀብት ወድሟል።
የመኖሪያ ቤቶች፦ 100,000 ቤቶች ፈርሰዋል።
857 ትምህርት ቤቶችና ዩኒቨርሲቲዎች እንዲሁም 339 የህክምና ተቋማት ጉዳት ደርሶባቸዋል።
23,500 የንግድ ድርጅቶች በመውደማቸው ከፍተኛ የሥራ አጥነት ስጋት ተፈጥሯል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) እንደገለጸው፣ የኢራን ሚሳይል ማምረቻዎችና ወታደራዊ መሠረቶች ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ወድመዋል።
በተለይ 4 ዋና ዋና የባሊስቲክ ሚሳይል ማምረቻዎች በመውደማቸው፣ ኢራን ያላትን የመከላከል አቅም ለጊዜው አጥታለች ተብሏል።
"ከዚህ ግዙፍ ውድመት ለማገገም ኢራን ረጅም ዓመታት ይፈጅባታል!" — የፖለቲካ ተንታኞች
#getu #iranwar #middleeastcrisis #economicloss #breakingnews #militaryupdate #globalpolitics #usa #israel #iran #peacetalks #ኢራን #ጦርነት #ኢኮኖሚ #መካከለኛውምስራቅ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | በኢራን፣ በአሜሪካና በእስራኤል መካከል ለ40 ቀናት የዘለቀው አስከፊ ጦርነት በኢራን ላይ ታሪክ የማይረሳው ውድመት ጥሎ አልፏል።
የወጡ ሪፖርቶች እንደሚያመለክቱት፣ ሀገሪቱ ከአስርተ ዓመታት በኋላ ወደማታውቀው የኢኮኖሚና የወታደራዊ ቀውስ ውስጥ ገብታለች።
ከ140 እስከ 145 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ሀብት ወድሟል።
የመኖሪያ ቤቶች፦ 100,000 ቤቶች ፈርሰዋል።
857 ትምህርት ቤቶችና ዩኒቨርሲቲዎች እንዲሁም 339 የህክምና ተቋማት ጉዳት ደርሶባቸዋል።
23,500 የንግድ ድርጅቶች በመውደማቸው ከፍተኛ የሥራ አጥነት ስጋት ተፈጥሯል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) እንደገለጸው፣ የኢራን ሚሳይል ማምረቻዎችና ወታደራዊ መሠረቶች ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ወድመዋል።
በተለይ 4 ዋና ዋና የባሊስቲክ ሚሳይል ማምረቻዎች በመውደማቸው፣ ኢራን ያላትን የመከላከል አቅም ለጊዜው አጥታለች ተብሏል።
"ከዚህ ግዙፍ ውድመት ለማገገም ኢራን ረጅም ዓመታት ይፈጅባታል!" — የፖለቲካ ተንታኞች
#getu #iranwar #middleeastcrisis #economicloss #breakingnews #militaryupdate #globalpolitics #usa #israel #iran #peacetalks #ኢራን #ጦርነት #ኢኮኖሚ #መካከለኛውምስራቅ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
Sponsored by
Surafel
2 months ago
አሜሪካ የቢሊዮን ዶላር "ድብቅ" ሚሳኤሎችን ማንቀሳቀስ ጀመረች
#ethiopia | ብሉምበርግ (Bloomberg) ምንጮቹን ጠቅሶ እንደዘገበው፣ አሜሪካ እጅግ ዘመናዊና ረጅም ርቀት ተጓዥ የሆኑትን JASSM-ER ክሩዝ ሚሳኤሎች በኢራን ዙሪያ በከፍተኛ ሁኔታ እያከማቸች ትገኛለች።
እያንዳንዳቸው 1.5 ሚሊዮን ዶላር የሚገመቱት እነዚህ ሚሳኤሎች፣ የጠላትን የራዳር መከላከያ ሰብረው በመግባት ኢላማን በከፍተኛ ጥንቃቄ የመምታት "ድብቅ" (Stealth) ብቃት አላቸው።
ሚሳኤሎቹ ከፓስፊክ ውቅያኖስ፣ ከመካከለኛው አሜሪካና ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች ተሰብስበው ወደ አሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) እና በእንግሊዝ ወደሚገኘው የፌርፎርድ የአየር ኃይል ጣቢያ እየተጓጓዙ ነው።
ይህ ግዙፍ ክምችት በአንድ አካባቢ መሰብሰቡ፣ በኢራን ላይ ሊሰነዘር ለሚችል መጠነ ሰፊና "የማያዳግም" ጥቃት እንደ ቅድመ ዝግጅት እየታየ ነው።
ትዕዛዙ የተሰጠው በመጋቢት ወር መጨረሻ ላይ ሲሆን፣ ይህም ፕሬዝዳንት ትራምፕ ጦራቸውን እንደሚያወጡ ከገለጹበት ንግግር በተቃራኒ ወታደራዊ ዝግጁነቱ እየጠነከረ መሄዱን ያሳያል።
#getu #usmilitary #jassmer #irantension #bloombergreport #missiledefense #globalsecurity #middleeastcrisis #trumpadmin #stealthmissiles #አሜሪካ #ኢራን #ሚሳኤል #ጦርነት #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | ብሉምበርግ (Bloomberg) ምንጮቹን ጠቅሶ እንደዘገበው፣ አሜሪካ እጅግ ዘመናዊና ረጅም ርቀት ተጓዥ የሆኑትን JASSM-ER ክሩዝ ሚሳኤሎች በኢራን ዙሪያ በከፍተኛ ሁኔታ እያከማቸች ትገኛለች።
እያንዳንዳቸው 1.5 ሚሊዮን ዶላር የሚገመቱት እነዚህ ሚሳኤሎች፣ የጠላትን የራዳር መከላከያ ሰብረው በመግባት ኢላማን በከፍተኛ ጥንቃቄ የመምታት "ድብቅ" (Stealth) ብቃት አላቸው።
ሚሳኤሎቹ ከፓስፊክ ውቅያኖስ፣ ከመካከለኛው አሜሪካና ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች ተሰብስበው ወደ አሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) እና በእንግሊዝ ወደሚገኘው የፌርፎርድ የአየር ኃይል ጣቢያ እየተጓጓዙ ነው።
ይህ ግዙፍ ክምችት በአንድ አካባቢ መሰብሰቡ፣ በኢራን ላይ ሊሰነዘር ለሚችል መጠነ ሰፊና "የማያዳግም" ጥቃት እንደ ቅድመ ዝግጅት እየታየ ነው።
ትዕዛዙ የተሰጠው በመጋቢት ወር መጨረሻ ላይ ሲሆን፣ ይህም ፕሬዝዳንት ትራምፕ ጦራቸውን እንደሚያወጡ ከገለጹበት ንግግር በተቃራኒ ወታደራዊ ዝግጁነቱ እየጠነከረ መሄዱን ያሳያል።
#getu #usmilitary #jassmer #irantension #bloombergreport #missiledefense #globalsecurity #middleeastcrisis #trumpadmin #stealthmissiles #አሜሪካ #ኢራን #ሚሳኤል #ጦርነት #ጌጡተመስገን #getutemesgen
2 months ago
48 ሰዓታት
ኢራን፣ የሆርሙዝ ሰርጥ እና የትራምፕ ማስጠንቀቂያ!
#ethiopia | ባለፉት 48 ሰዓታት በመካከለኛው ምስራቅ የታዩት ክስተቶች ዓለምን በስጋት አይን እንድትመለከት አድርገዋል።
በኢራንና በአሜሪካ መካከል ያለው ፍጥጫ ወደ አዲስ ምዕራፍ ተሸጋግሯል።
ኢራን የዓለም የነዳጅ ንግድ የደም ሥር የሆነውን የሆርሙዝ ሰርጥን ልትዘጋ ትችላለች የሚለው ስጋት አይሏል። ይህም በዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ ላይ ከፍተኛ መናር ሊያስከትል እንደሚችል ተገምቷል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ የአሜሪካ ጦር "በጣም በቅርብ ጊዜ" ከኢራን እንደሚወጣ ቢገልጹም፣ በሌላ በኩል ግን ማንኛውም ጥቃት ቢሰነዘር አሜሪካ "የማያዳግም ምላሽ" እንደምትሰጥ አስጠንቅቀዋል።
የኢራን ግማሽ ያህሉ የሚሳኤልና የድሮን አቅም ጥቃት ሳይደርስበት አሁንም ዝግጁ መሆኑ መገለጹ፣ አሜሪካ ጦሯን በምታወጣበት ወቅት ኢራን የበላይነቱን ለመያዝ እንድትሞክር በር ሊከፍት ይችላል ተብሏል።
የሆርሙዝ ሰርጥ መዘጋት ማለት የኢትዮጵያን ጨምሮ የበርካታ ሀገራት ኢኮኖሚ ላይ ቀጥተኛ ጫና ይፈጥራል። የነዳጅ ዋጋ መናር የኑሮ ውድነትን ይበልጥ ሊያባብሰው ይችላል።
#getu #irantension #straitofhormuz #trump #middleeastcrisis #oilprices #globalsecurity #usmilitary #geopolitics #ኢራን #ሆርሙዝሰርጥ #ትራምፕ #ነዳጅ #ኢኮኖሚ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
ኢራን፣ የሆርሙዝ ሰርጥ እና የትራምፕ ማስጠንቀቂያ!
#ethiopia | ባለፉት 48 ሰዓታት በመካከለኛው ምስራቅ የታዩት ክስተቶች ዓለምን በስጋት አይን እንድትመለከት አድርገዋል።
በኢራንና በአሜሪካ መካከል ያለው ፍጥጫ ወደ አዲስ ምዕራፍ ተሸጋግሯል።
ኢራን የዓለም የነዳጅ ንግድ የደም ሥር የሆነውን የሆርሙዝ ሰርጥን ልትዘጋ ትችላለች የሚለው ስጋት አይሏል። ይህም በዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ ላይ ከፍተኛ መናር ሊያስከትል እንደሚችል ተገምቷል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ የአሜሪካ ጦር "በጣም በቅርብ ጊዜ" ከኢራን እንደሚወጣ ቢገልጹም፣ በሌላ በኩል ግን ማንኛውም ጥቃት ቢሰነዘር አሜሪካ "የማያዳግም ምላሽ" እንደምትሰጥ አስጠንቅቀዋል።
የኢራን ግማሽ ያህሉ የሚሳኤልና የድሮን አቅም ጥቃት ሳይደርስበት አሁንም ዝግጁ መሆኑ መገለጹ፣ አሜሪካ ጦሯን በምታወጣበት ወቅት ኢራን የበላይነቱን ለመያዝ እንድትሞክር በር ሊከፍት ይችላል ተብሏል።
የሆርሙዝ ሰርጥ መዘጋት ማለት የኢትዮጵያን ጨምሮ የበርካታ ሀገራት ኢኮኖሚ ላይ ቀጥተኛ ጫና ይፈጥራል። የነዳጅ ዋጋ መናር የኑሮ ውድነትን ይበልጥ ሊያባብሰው ይችላል።
#getu #irantension #straitofhormuz #trump #middleeastcrisis #oilprices #globalsecurity #usmilitary #geopolitics #ኢራን #ሆርሙዝሰርጥ #ትራምፕ #ነዳጅ #ኢኮኖሚ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
2 months ago
ስጋቱ አልቀነሰም
ግማሹ የኢራን ሚሳኤልና ድሮን አቅም አሁንም አልተነካም!
#ethiopia | ከአንድ ወር በላይ ከተካሄደው የአሜሪካና እስራኤል የተቀናጀ ጥቃት በኋላም፣ የኢራን ስትራቴጂካዊ የጦር መሣሪያዎች አሁንም ለጥቃት ዝግጁ መሆናቸውን የአሜሪካ የስለላ መረጃዎች ጠቁመዋል።
50 በመቶ የሚሆኑት የባለስቲክ ሚሳኤል ተኳሾችና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰው አልባ ድሮኖች ምንም ዓይነት ጉዳት አልደረሰባቸውም።
ከመሬት በታች የተደበቁት "የሚሳኤል ከተሞች" ለጥቃቱ ምላሽ ለመስጠት አሁንም በከፍተኛ ዝግጁነት ላይ ይገኛሉ።
የኢራን የባህር ዳርቻ ተከላካይ ክሩዝ ሚሳኤሎች በአብዛኛው ሳይነኩ የቀሩ ሲሆን፣ ይህም ለባህር ትራንስፖርት ትልቅ ስጋት ነው።
እስከ አውሮፓ መድረስ የሚችለው የ"ኮራምሻህር" አይነት ሚሳኤል አሁንም የኢራን ዋነኛ የመከላከያና የማጥቂያ አቅም ሆኖ ቀጥሏል።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ጦር በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ከኢራን እንደሚወጣና "ሰላም ሰፍኗል" ባሉበት ወቅት፣ ይህ ሪፖርት መውጣቱ ብዙዎችን እያነጋገረ ነው።
ትራምፕ ዘመቻው ተሳክቷል ቢሉም፣ የስለላ መረጃው ግን የኢራን አቅም በቀላሉ ሊደመሰስ አለመቻሉን ያሳያል።
#getu #irantension #middleeastcrisis #usmilitary #trump #cnnreport #ballisticmissiles #dronewarfare #geopolitics #globalsecurity #ኢራን #አሜሪካ #ሚሳኤል #ትራምፕ #መካከለኛውምስራቅ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
ግማሹ የኢራን ሚሳኤልና ድሮን አቅም አሁንም አልተነካም!
#ethiopia | ከአንድ ወር በላይ ከተካሄደው የአሜሪካና እስራኤል የተቀናጀ ጥቃት በኋላም፣ የኢራን ስትራቴጂካዊ የጦር መሣሪያዎች አሁንም ለጥቃት ዝግጁ መሆናቸውን የአሜሪካ የስለላ መረጃዎች ጠቁመዋል።
50 በመቶ የሚሆኑት የባለስቲክ ሚሳኤል ተኳሾችና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰው አልባ ድሮኖች ምንም ዓይነት ጉዳት አልደረሰባቸውም።
ከመሬት በታች የተደበቁት "የሚሳኤል ከተሞች" ለጥቃቱ ምላሽ ለመስጠት አሁንም በከፍተኛ ዝግጁነት ላይ ይገኛሉ።
የኢራን የባህር ዳርቻ ተከላካይ ክሩዝ ሚሳኤሎች በአብዛኛው ሳይነኩ የቀሩ ሲሆን፣ ይህም ለባህር ትራንስፖርት ትልቅ ስጋት ነው።
እስከ አውሮፓ መድረስ የሚችለው የ"ኮራምሻህር" አይነት ሚሳኤል አሁንም የኢራን ዋነኛ የመከላከያና የማጥቂያ አቅም ሆኖ ቀጥሏል።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ጦር በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ከኢራን እንደሚወጣና "ሰላም ሰፍኗል" ባሉበት ወቅት፣ ይህ ሪፖርት መውጣቱ ብዙዎችን እያነጋገረ ነው።
ትራምፕ ዘመቻው ተሳክቷል ቢሉም፣ የስለላ መረጃው ግን የኢራን አቅም በቀላሉ ሊደመሰስ አለመቻሉን ያሳያል።
#getu #irantension #middleeastcrisis #usmilitary #trump #cnnreport #ballisticmissiles #dronewarfare #geopolitics #globalsecurity #ኢራን #አሜሪካ #ሚሳኤል #ትራምፕ #መካከለኛውምስራቅ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
2 months ago
🚨 1,900 መርከቦች በሆርሙዝ ሰርጥ ቆመዋል
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ የተቀሰቀሰው ወታደራዊ ውጥረት በዓለም አቀፍ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ቀውስ እየፈጠረ ይገኛል። ከየካቲት 21/2018 ዓ.ም ጀምሮ በአሜሪካ፣ በእስራኤል እና በኢራን መካከል የተከፈተውን መጠነ-ሰፊ ጥቃት ተከትሎ የባህር ላይ ትራንስፖርት ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ቆሟል።
ወደ 1,900 የሚጠጉ የንግድ መርከቦች በሆርሙዝ ሰርጥ እና በፋርስ ባህረ ሰላጤ አካባቢ መንቀሳቀስ አቅቷቸው ቆመዋል።
ኢራን "ከጥቃት አድራሾቹ አገራት ጋር ንክኪ ያላቸው መርከቦች በወሳኙ የሆርሙዝ ሰርጥ እንዳያልፉ" መከልከሏ ለቀውሱ ዋነኛ መንስኤ ሆኗል።
እንቅስቃሴያቸው ከተገታው መርከቦች መካከል ግዙፍ የነዳጅ ጫኝ፣ የኬሚካል እና የተለያዩ የንግድ ዕቃዎችን የያዙ መርከቦች ይገኙበታል።
ይህ እገዳ በዓለም አቀፍ ደረጃ የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ እንዲንር ከማድረጉም በላይ፣ ዓለም አቀፍ የአቅርቦት ሰንሰለት (Supply Chain) ላይ ከፍተኛ መስተጓጎል እየፈጠረ ይገኛል። ሁኔታው ካልረገበ የዓለም ኢኮኖሚ የከፋ ጉዳት ሊገጥመው እንደሚችል ስጋቶች እየጨመሩ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #middleeastcrisis #globaltrade #oilprice #hormuzstrait #breakingnews #shippingindustry #internationalrelations #energysecurity
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ የተቀሰቀሰው ወታደራዊ ውጥረት በዓለም አቀፍ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ቀውስ እየፈጠረ ይገኛል። ከየካቲት 21/2018 ዓ.ም ጀምሮ በአሜሪካ፣ በእስራኤል እና በኢራን መካከል የተከፈተውን መጠነ-ሰፊ ጥቃት ተከትሎ የባህር ላይ ትራንስፖርት ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ቆሟል።
ወደ 1,900 የሚጠጉ የንግድ መርከቦች በሆርሙዝ ሰርጥ እና በፋርስ ባህረ ሰላጤ አካባቢ መንቀሳቀስ አቅቷቸው ቆመዋል።
ኢራን "ከጥቃት አድራሾቹ አገራት ጋር ንክኪ ያላቸው መርከቦች በወሳኙ የሆርሙዝ ሰርጥ እንዳያልፉ" መከልከሏ ለቀውሱ ዋነኛ መንስኤ ሆኗል።
እንቅስቃሴያቸው ከተገታው መርከቦች መካከል ግዙፍ የነዳጅ ጫኝ፣ የኬሚካል እና የተለያዩ የንግድ ዕቃዎችን የያዙ መርከቦች ይገኙበታል።
ይህ እገዳ በዓለም አቀፍ ደረጃ የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ እንዲንር ከማድረጉም በላይ፣ ዓለም አቀፍ የአቅርቦት ሰንሰለት (Supply Chain) ላይ ከፍተኛ መስተጓጎል እየፈጠረ ይገኛል። ሁኔታው ካልረገበ የዓለም ኢኮኖሚ የከፋ ጉዳት ሊገጥመው እንደሚችል ስጋቶች እየጨመሩ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #middleeastcrisis #globaltrade #oilprice #hormuzstrait #breakingnews #shippingindustry #internationalrelations #energysecurity
Sponsored by
Surafel
3 months ago
የመካከለኛው ምስራቅ ውጥረት ለኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ የገበያ ዕድል ፈጠረ
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣው ጂኦፖለቲካዊ አለመረጋጋት ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተጠበቀ የገበያ ዕድል ይዞ መጥቷል። በእስራኤል፣ አሜሪካ እና ኢራን መካከል ያለው ግጭት በባህረ ሰላጤው አገራት የአየር ትራንስፖርት ላይ መስተጓጎል በመፍጠሩ፣ በርካታ የደቡብ አፍሪካ መንገደኞች አዲስ አበባን እንደ ዋነኛ የመሸጋገሪያ (Hub) ማዕከል መጠቀም ጀምረዋል።
የኢንዱስትሪ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ ከመጋቢት ወር መጀመሪያ ጀምሮ በኢትዮጵያ አየር መንገድ በኩል የሚደረጉ የቦታ ማስያዝ (Bookings) መጠኖች የ110% ድንገተኛ ጭማሪ አሳይተዋል። የFlight Centre South Africa የሥራ ኃላፊ ሱ ጋሬት እንደገለጹት፤ ይህ ለውጥ የመጣው በተለመዱት የበረራ መስመሮች ላይ በተፈጠሩ ስረዛዎችና የአየር ክልል ገደቦች ምክንያት ነው።
የዓለም አቀፉ የአየር ትራንስፖርት ማህበር (IATA) መረጃዎች እንደሚያሳዩት፣ አየር መንገዱ አሁን ካለው ቀውስ በፊትም ቢሆን በቁልፍ የጉዞ መስመሮች ላይ የበላይነቱን እያጠናከረ ቆይቷል፦
* ወደ ሕንድ፦ በ2025 በጆሃንስበርግ-ሙምባይ መስመር በአዲስ አበባ በኩል ከ69,000 በላይ መንገደኞችን በማጓጓዝ ቀዳሚው ምርጫ ሆኗል።
* ወደ ብሪታንያ፦ በደቡብ አፍሪካ እና በእንግሊዝ መካከል ባለው መስመር ኤምሬትስን በ39,000 መንገደኞች በመብለጥ ትልቁ ቀጥተኛ ያልሆነ አጓጓዥ ለመሆን በቅቷል።
* ወደ አሜሪካ፦ በደቡብ አፍሪካ እና በአሜሪካ መካከል በሚደረግ ጉዞ ከዩናይትድ እና ከዴልታ በመቀጠል በሦስተኛ ደረጃ ላይ በመቀመጥ ጠንካራ ተወዳዳሪነቱን አስመስክሯል።
ይህ ወቅታዊ ክስተት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካና በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን ስትራቴጂካዊ ተመራጭነት ይበልጥ እያሳደገው ይገኛል ያለው ካፒታል ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiopianairlines #aviationnews #middleeastcrisis #ethiopia #addisababahub #globaltravel #businessnews #africarising
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣው ጂኦፖለቲካዊ አለመረጋጋት ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ያልተጠበቀ የገበያ ዕድል ይዞ መጥቷል። በእስራኤል፣ አሜሪካ እና ኢራን መካከል ያለው ግጭት በባህረ ሰላጤው አገራት የአየር ትራንስፖርት ላይ መስተጓጎል በመፍጠሩ፣ በርካታ የደቡብ አፍሪካ መንገደኞች አዲስ አበባን እንደ ዋነኛ የመሸጋገሪያ (Hub) ማዕከል መጠቀም ጀምረዋል።
የኢንዱስትሪ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ ከመጋቢት ወር መጀመሪያ ጀምሮ በኢትዮጵያ አየር መንገድ በኩል የሚደረጉ የቦታ ማስያዝ (Bookings) መጠኖች የ110% ድንገተኛ ጭማሪ አሳይተዋል። የFlight Centre South Africa የሥራ ኃላፊ ሱ ጋሬት እንደገለጹት፤ ይህ ለውጥ የመጣው በተለመዱት የበረራ መስመሮች ላይ በተፈጠሩ ስረዛዎችና የአየር ክልል ገደቦች ምክንያት ነው።
የዓለም አቀፉ የአየር ትራንስፖርት ማህበር (IATA) መረጃዎች እንደሚያሳዩት፣ አየር መንገዱ አሁን ካለው ቀውስ በፊትም ቢሆን በቁልፍ የጉዞ መስመሮች ላይ የበላይነቱን እያጠናከረ ቆይቷል፦
* ወደ ሕንድ፦ በ2025 በጆሃንስበርግ-ሙምባይ መስመር በአዲስ አበባ በኩል ከ69,000 በላይ መንገደኞችን በማጓጓዝ ቀዳሚው ምርጫ ሆኗል።
* ወደ ብሪታንያ፦ በደቡብ አፍሪካ እና በእንግሊዝ መካከል ባለው መስመር ኤምሬትስን በ39,000 መንገደኞች በመብለጥ ትልቁ ቀጥተኛ ያልሆነ አጓጓዥ ለመሆን በቅቷል።
* ወደ አሜሪካ፦ በደቡብ አፍሪካ እና በአሜሪካ መካከል በሚደረግ ጉዞ ከዩናይትድ እና ከዴልታ በመቀጠል በሦስተኛ ደረጃ ላይ በመቀመጥ ጠንካራ ተወዳዳሪነቱን አስመስክሯል።
ይህ ወቅታዊ ክስተት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካና በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን ስትራቴጂካዊ ተመራጭነት ይበልጥ እያሳደገው ይገኛል ያለው ካፒታል ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiopianairlines #aviationnews #middleeastcrisis #ethiopia #addisababahub #globaltravel #businessnews #africarising
3 months ago
‹‹ኢራን 50 ሰሜን ኮሪያዎችን ትሆናለች›› የኔታንያሁ
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ያለው ወታደራዊ ፍጥጫ አዲስና አደገኛ ምዕራፍ ላይ መድረሱ ተሰምቷል። የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ እና የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን እርስ በእርስ የሚወራወሯቸው ጠንካራ ቃላት፣ ዓለምን ለከፋ ስጋት ዳርገዋል።
ኔታንያሁ ለምን ኢራንን ከሰሜን ኮሪያ ጋር አነጻጸሩ?
ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ ባስተላለፉት የቪዲዮ መልዕክት፣ ኢራን ለዓለም ሰላም ካላት አደገኝነት አንጻር "50 ሰሜን ኮሪያዎችን ትሆናለች" ሲሉ ገልጸዋል። እንደ ኔታንያሁ ገለጻ፣ ሰሜን ኮሪያ የኒውክሌር እና የባለስቲክ ሚሳኤል አቅም ቢኖራትም፣ እንደ ኢራን ግን "ሞት ለአሜሪካ" የሚል ግልጽ የጥፋት ርዕዮተ ዓለም አትከተልም።
"ኢራን የአሜሪካን እና የእስራኤልን መጥፋት እንደ ዋና ግብ ይዛ የተነሳች በመሆኗ፣ አጥፊነቷ ከሰሜን ኮሪያ በብዙ እጥፍ ይበልጣል" — ቤንያሚን ኔታንያሁ
የሰሜን ኮሪያው ምላሽ፦ "እስራኤልን ለማጥፋት አንድ ሚሳኤል ይበቃል"
የኔታንያሁ ንግግር ያልተዋጠላቸው የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን፣ ለቴህራን ያላቸውን ወታደራዊ ድጋፍ በይፋ አረጋግጠዋል። እስራኤልን ከዓለም ካርታ ላይ ለማጥፋት "አንድ ሚሳኤል ብቻ" በቂ እንደሆነ የገለጹት መሪው፣ አስፈላጊ ከሆነም የላቁ ሚሳኤሎችን ለኢራን ለማቅረብ ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
ይህ የፒዮንግያንግ መግለጫ የወጣው በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች መሆኑ ይነገራል፡-
* አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የከፈቱት "ኦፕሬሽን ኤፒክ ፉሪ" (Operation Epic Fury) መጠናከሩ።
* የኢራኑ የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ መገደላቸው መረጋገጡ።
አዲሱ የኃይል አሰላለፍ እና የዓለም ስጋት
በኢራን፣ ሩሲያ፣ ቻይና እና ሰሜን ኮሪያ መካከል እየተፈጠረ ያለው ወታደራዊ ጥምረት፣ ግጭቱን ከቀጣናዊነት አልፎ ዓለም አቀፍ ጦርነት ሊያደርገው ይችላል የሚል ስጋት አንዣብቧል።
* የቻይና ሚና፦ ቻይና ለኢራን የላቁ ሚሳኤሎችን እያቀረበች ነው የሚሉ ዘገባዎች ቢወጡም፣ ቤጂንግ ግን ውንጀላውን አስተባብላለች።
* የትራምፕ ማስጠንቀቂያ፦ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቀደም ሲል "ትልቁ ጦርነት ሊመጣ ይችላል" ሲሉ የሰጡት ማስጠንቀቂያ አሁን ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር እየተገጣጠመ ይገኛል።
ይህ ወታደራዊ ውጥረት በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ ላይ ከፍተኛ መናወጥን የፈጠረ ሲሆን፣ የጂኦ-ፖለቲካዊ መረጋጋትንም ጥያቄ ምልክት ውስጥ ከትቶታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiofm #middleeastcrisis #israeliranconflict #netanyahu #kimjongun #globalsecurity #operationepic Fury #breakingnews
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ያለው ወታደራዊ ፍጥጫ አዲስና አደገኛ ምዕራፍ ላይ መድረሱ ተሰምቷል። የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ እና የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን እርስ በእርስ የሚወራወሯቸው ጠንካራ ቃላት፣ ዓለምን ለከፋ ስጋት ዳርገዋል።
ኔታንያሁ ለምን ኢራንን ከሰሜን ኮሪያ ጋር አነጻጸሩ?
ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ ባስተላለፉት የቪዲዮ መልዕክት፣ ኢራን ለዓለም ሰላም ካላት አደገኝነት አንጻር "50 ሰሜን ኮሪያዎችን ትሆናለች" ሲሉ ገልጸዋል። እንደ ኔታንያሁ ገለጻ፣ ሰሜን ኮሪያ የኒውክሌር እና የባለስቲክ ሚሳኤል አቅም ቢኖራትም፣ እንደ ኢራን ግን "ሞት ለአሜሪካ" የሚል ግልጽ የጥፋት ርዕዮተ ዓለም አትከተልም።
"ኢራን የአሜሪካን እና የእስራኤልን መጥፋት እንደ ዋና ግብ ይዛ የተነሳች በመሆኗ፣ አጥፊነቷ ከሰሜን ኮሪያ በብዙ እጥፍ ይበልጣል" — ቤንያሚን ኔታንያሁ
የሰሜን ኮሪያው ምላሽ፦ "እስራኤልን ለማጥፋት አንድ ሚሳኤል ይበቃል"
የኔታንያሁ ንግግር ያልተዋጠላቸው የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን፣ ለቴህራን ያላቸውን ወታደራዊ ድጋፍ በይፋ አረጋግጠዋል። እስራኤልን ከዓለም ካርታ ላይ ለማጥፋት "አንድ ሚሳኤል ብቻ" በቂ እንደሆነ የገለጹት መሪው፣ አስፈላጊ ከሆነም የላቁ ሚሳኤሎችን ለኢራን ለማቅረብ ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
ይህ የፒዮንግያንግ መግለጫ የወጣው በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች መሆኑ ይነገራል፡-
* አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የከፈቱት "ኦፕሬሽን ኤፒክ ፉሪ" (Operation Epic Fury) መጠናከሩ።
* የኢራኑ የበላይ መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ መገደላቸው መረጋገጡ።
አዲሱ የኃይል አሰላለፍ እና የዓለም ስጋት
በኢራን፣ ሩሲያ፣ ቻይና እና ሰሜን ኮሪያ መካከል እየተፈጠረ ያለው ወታደራዊ ጥምረት፣ ግጭቱን ከቀጣናዊነት አልፎ ዓለም አቀፍ ጦርነት ሊያደርገው ይችላል የሚል ስጋት አንዣብቧል።
* የቻይና ሚና፦ ቻይና ለኢራን የላቁ ሚሳኤሎችን እያቀረበች ነው የሚሉ ዘገባዎች ቢወጡም፣ ቤጂንግ ግን ውንጀላውን አስተባብላለች።
* የትራምፕ ማስጠንቀቂያ፦ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቀደም ሲል "ትልቁ ጦርነት ሊመጣ ይችላል" ሲሉ የሰጡት ማስጠንቀቂያ አሁን ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር እየተገጣጠመ ይገኛል።
ይህ ወታደራዊ ውጥረት በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ ላይ ከፍተኛ መናወጥን የፈጠረ ሲሆን፣ የጂኦ-ፖለቲካዊ መረጋጋትንም ጥያቄ ምልክት ውስጥ ከትቶታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiofm #middleeastcrisis #israeliranconflict #netanyahu #kimjongun #globalsecurity #operationepic Fury #breakingnews