2 months ago
የኢራን ነዳጅ ጫኝ መርከቦች የአሜሪካን እገዳ አለፉ
**************
ዋሽንግተን እና ቴህራን ጦርነታቸውን ለማቆም የሚያስችል ማዕቀፋዊ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ተከትሎ፣ በርካታ የኢራን ነዳጅ ጫኝ መርከቦች በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ የተጣለውን የአሜሪካ የባሕር እገዳ መስመር ጥሰው ማለፋቸው ተሰምቷል።
የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ተጨማሪ ውይይቶችን ለማድረግ እና የመግባቢያ ሰነድ ለመፈራረም ሁለት ቀናት ሲቀራቸው፣ የመርከቦችን እንቅስቃሴ የሚከታተለው “ታንከር ትራከርስ” የተባለው ድረ-ገጽ የኢራን መርከቦች እገዳውን ማለፋቸውን ይፋ አድርጓል።
ድረ-ገጹ በዲጂታል መከታተያ መረጃዎች እና በሳተላይት ምስሎች ላይ በመደገፍ፣ ኢራን ባለፉት ሁለት ወራት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የነዳጅ ምርት ወደ ውጭ መላክ መጀመሯን ዛሬ አስታውቋል።
በአሜሪካ እና በእስራኤል ጥቃት የካቲት 28 ቀን የተቀሰቀሰውን ጦርነት በዘላቂነት ለማቆም የሚደረገው የመጨረሻው የሰላም ንግግር፣ የፊታችን ዐርብ በስዊዘርላንድ ቡርገንስቶክ ተራራማ የመዝናኛ ስፍራ እንደሚጀመር ይጠበቃል።
የሆርሙዝ ወሽመጥ ዳግም ይከፈታል የሚለው ዜናም በዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ ላይ ከፍተኛ ቅናሽ እንዲታይ አድርጓል።
ታንከር ትራከርስ እንዳመለከተው፣ “ዲዮና” እና “ሄሮ 2” የተሰኙ የኢራን ብሔራዊ የነዳጅ ጫኝ መርከብ ኩባንያ መርከቦች በድምሩ 3 ነጥብ 8 ሚሊዮን በርሜል ነዳጅ በመጫን ማክሰኞ ዕለት የእገዳ ቀጣናውን አልፈዋል።
በተመሳሳይ “ስትሪም” የተሰኘችው ሌላኛዋ መርከብ ረቡዕ ዕለት ወደ ኢራን ወደቦች እያመራች የነበረች ሲሆን፣ በዚሁ ዕለት 1 ሚሊዮን በርሜል የኢራን ድፍድፍ ነዳጅ የጫነች ሦስተኛዋ የኩባንያው መርከብ በኦማን ባሕረ ሰላጤ ላይ የተጣለውን የአሜሪካ ባሕር ኃይል እገዳ አልፋ መጓዟን አልጄዚራ ዘግቧል።
#iranoiltankers #usblockade #middleeastpeacetalks #oilpricestumble #straitofhormuz
**************
ዋሽንግተን እና ቴህራን ጦርነታቸውን ለማቆም የሚያስችል ማዕቀፋዊ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ተከትሎ፣ በርካታ የኢራን ነዳጅ ጫኝ መርከቦች በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ የተጣለውን የአሜሪካ የባሕር እገዳ መስመር ጥሰው ማለፋቸው ተሰምቷል።
የሁለቱ ሀገራት መሪዎች ተጨማሪ ውይይቶችን ለማድረግ እና የመግባቢያ ሰነድ ለመፈራረም ሁለት ቀናት ሲቀራቸው፣ የመርከቦችን እንቅስቃሴ የሚከታተለው “ታንከር ትራከርስ” የተባለው ድረ-ገጽ የኢራን መርከቦች እገዳውን ማለፋቸውን ይፋ አድርጓል።
ድረ-ገጹ በዲጂታል መከታተያ መረጃዎች እና በሳተላይት ምስሎች ላይ በመደገፍ፣ ኢራን ባለፉት ሁለት ወራት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የነዳጅ ምርት ወደ ውጭ መላክ መጀመሯን ዛሬ አስታውቋል።
በአሜሪካ እና በእስራኤል ጥቃት የካቲት 28 ቀን የተቀሰቀሰውን ጦርነት በዘላቂነት ለማቆም የሚደረገው የመጨረሻው የሰላም ንግግር፣ የፊታችን ዐርብ በስዊዘርላንድ ቡርገንስቶክ ተራራማ የመዝናኛ ስፍራ እንደሚጀመር ይጠበቃል።
የሆርሙዝ ወሽመጥ ዳግም ይከፈታል የሚለው ዜናም በዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ ላይ ከፍተኛ ቅናሽ እንዲታይ አድርጓል።
ታንከር ትራከርስ እንዳመለከተው፣ “ዲዮና” እና “ሄሮ 2” የተሰኙ የኢራን ብሔራዊ የነዳጅ ጫኝ መርከብ ኩባንያ መርከቦች በድምሩ 3 ነጥብ 8 ሚሊዮን በርሜል ነዳጅ በመጫን ማክሰኞ ዕለት የእገዳ ቀጣናውን አልፈዋል።
በተመሳሳይ “ስትሪም” የተሰኘችው ሌላኛዋ መርከብ ረቡዕ ዕለት ወደ ኢራን ወደቦች እያመራች የነበረች ሲሆን፣ በዚሁ ዕለት 1 ሚሊዮን በርሜል የኢራን ድፍድፍ ነዳጅ የጫነች ሦስተኛዋ የኩባንያው መርከብ በኦማን ባሕረ ሰላጤ ላይ የተጣለውን የአሜሪካ ባሕር ኃይል እገዳ አልፋ መጓዟን አልጄዚራ ዘግቧል።
#iranoiltankers #usblockade #middleeastpeacetalks #oilpricestumble #straitofhormuz
2 months ago
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው የሰላም ስምምነት የመጨረሻ ውል ላይ ደረሰ
*************
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው የሰላም ስምምነት የመጨረሻ ሰነድ መጽደቁን በሂደቱ ላይ ቁልፍ አስታራቂ የሆኑት የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሸህባዝ ሸሪፍ አስታውቀዋል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጦርነት ለማቆም እና ወሳኙን የሆርሙዝ ወሽመጥ ድጋሚ ለመክፈት ያለመውን ይህንን ስምምነት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ሰላም እንደ አሁኑ ቀርቦ አያውቅም” ብለዋል።
ሂደቱን ለማደናቀፍ የሚነዙ የሀሰት መረጃዎችን ወደ ጎን በመተው ፓኪስታን ቀጣይ እርምጃዎችን ለማጠናቀቅ ከሁለቱም ወገኖች ጋር በቅርበት እየሰራች መሆኑን ገልጸዋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራጊቺም በበኩላቸው የጦርነቱ ማክተሚያ መቃረቡን አረጋግጠዋል።
ከሁለቱም ወገኖች ተስፋ ሰጪ መግለጫዎች ቢሰሙም፣ በአደባባይ ያላቸው የድርድር አቋም አሁንም የተራራቀ መሆኑ ይስተዋላል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን መገናኛ ብዙኃን የተናፈሰው የስምምነቱ ይዘት ከእውነታው የራቀ ነው ያሉ ሲሆን፣ ኢራናውያንን “በቅንነት ለመደራደር የማይመቹ” ሲሉ ተችተዋል።
በሌላ በኩል ኢራን አሜሪካ በዲፕሎማሲያዊ ሂደቱ ላይ በተደጋጋሚ ክህደት ፈጽማለች ስትል በመውቀስ፣ በዋሽንግተን ባህሪ ምክንያት የተገኘው መሻሻል ወደኋላ እየተመለሰ መሆኑን ገልጻለች።
ይሁን እንጂ ኢራን በአብዛኛዎቹ ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ መደረሱንና በመጨረሻው የውስጥ ግምገማ ደረጃ ላይ እንደምትገኝ አስታውቃለች።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ስምምነቱ በመጪው እሁድ መጀመሪያ ላይ ሊፈረም እንደሚችል የገለጹ ሲሆን፣ ቴህራን በበኩሏ በጊዜ ሰሌዳው ላይ ጥርጣሬ ቢኖራትም ፊርማው “በሚቀጥሉት ቀናት” ሊከናወን እንደሚችል ፍንጭ ሰጥታለች።
ስምምነቱ ከተፈረመ በኋላ የሆርሙዝ ወሽመጥ ለሁሉም ክፍት እንደሚሆንና አሜሪካም በመጨረሻ የኢራንን የኑክሌር ቁሳቁስ እንደምታገኝ ተጠቅሷል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ኢራን ማንኛውም የተኩስ አቁም ስምምነት እስከ ሊባኖስ ድረስ መዘርጋት አለበት ብላ ብታስረግጥም፣ የእስራኤል ጦር ጥቃቱን በመቀጠሉ በደቡብ ሊባኖስ በርካታ ፍንዳታዎች እየተከሰቱ ይገኛሉ ሲሉ ዘ ቴሌግራፍ እና አልጀዚራ በዘገባቸው ጠቅሰዋል።
በመሐመድ ፊጣሞ
#usiranpeacetalks #straitofhormuz #middleeastpeace #ethiopianbroadcastingcorporation
*************
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው የሰላም ስምምነት የመጨረሻ ሰነድ መጽደቁን በሂደቱ ላይ ቁልፍ አስታራቂ የሆኑት የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሸህባዝ ሸሪፍ አስታውቀዋል።
በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጦርነት ለማቆም እና ወሳኙን የሆርሙዝ ወሽመጥ ድጋሚ ለመክፈት ያለመውን ይህንን ስምምነት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ሰላም እንደ አሁኑ ቀርቦ አያውቅም” ብለዋል።
ሂደቱን ለማደናቀፍ የሚነዙ የሀሰት መረጃዎችን ወደ ጎን በመተው ፓኪስታን ቀጣይ እርምጃዎችን ለማጠናቀቅ ከሁለቱም ወገኖች ጋር በቅርበት እየሰራች መሆኑን ገልጸዋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራጊቺም በበኩላቸው የጦርነቱ ማክተሚያ መቃረቡን አረጋግጠዋል።
ከሁለቱም ወገኖች ተስፋ ሰጪ መግለጫዎች ቢሰሙም፣ በአደባባይ ያላቸው የድርድር አቋም አሁንም የተራራቀ መሆኑ ይስተዋላል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን መገናኛ ብዙኃን የተናፈሰው የስምምነቱ ይዘት ከእውነታው የራቀ ነው ያሉ ሲሆን፣ ኢራናውያንን “በቅንነት ለመደራደር የማይመቹ” ሲሉ ተችተዋል።
በሌላ በኩል ኢራን አሜሪካ በዲፕሎማሲያዊ ሂደቱ ላይ በተደጋጋሚ ክህደት ፈጽማለች ስትል በመውቀስ፣ በዋሽንግተን ባህሪ ምክንያት የተገኘው መሻሻል ወደኋላ እየተመለሰ መሆኑን ገልጻለች።
ይሁን እንጂ ኢራን በአብዛኛዎቹ ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ መደረሱንና በመጨረሻው የውስጥ ግምገማ ደረጃ ላይ እንደምትገኝ አስታውቃለች።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ስምምነቱ በመጪው እሁድ መጀመሪያ ላይ ሊፈረም እንደሚችል የገለጹ ሲሆን፣ ቴህራን በበኩሏ በጊዜ ሰሌዳው ላይ ጥርጣሬ ቢኖራትም ፊርማው “በሚቀጥሉት ቀናት” ሊከናወን እንደሚችል ፍንጭ ሰጥታለች።
ስምምነቱ ከተፈረመ በኋላ የሆርሙዝ ወሽመጥ ለሁሉም ክፍት እንደሚሆንና አሜሪካም በመጨረሻ የኢራንን የኑክሌር ቁሳቁስ እንደምታገኝ ተጠቅሷል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ኢራን ማንኛውም የተኩስ አቁም ስምምነት እስከ ሊባኖስ ድረስ መዘርጋት አለበት ብላ ብታስረግጥም፣ የእስራኤል ጦር ጥቃቱን በመቀጠሉ በደቡብ ሊባኖስ በርካታ ፍንዳታዎች እየተከሰቱ ይገኛሉ ሲሉ ዘ ቴሌግራፍ እና አልጀዚራ በዘገባቸው ጠቅሰዋል።
በመሐመድ ፊጣሞ
#usiranpeacetalks #straitofhormuz #middleeastpeace #ethiopianbroadcastingcorporation
3 months ago
የሰላም ድርድር መቋረጥ፣ የሆርሙዝ ሰርጥ አዳዲስ ክልከላዎች እና የባራካህ የኑክሌር ጣቢያ ጥቃት
**************
በመካከለኛው ምሥራቅ የሰላም ድርድር ጥረቶች፣ በሆርሙዝ ሰርጥ የባሕር ላይ መተላለፊያ ቁጥጥር እና በተመዘገቡ የጸጥታ ስጋቶች ዙሪያ አዳዲስ ክስተቶች ተመዝግበዋል።
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የነበረው ቀጥተኛ ድርድር መቋረጡን ተከትሎ ዲፕሎማሲያዊ ውጥረቱ ያሻቀበ ሲሆን፣ የንግድ መርከቦች እንቅስቃሴን ለመቆጣጠርም አዳዲስ እርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ።
የፓኪስታን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ሞህሲን ናቅቪ አስቀድሞ ያልተገለጸ የሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ቴህራን መግባታቸውን የፓኪስታኑ ‘ዶን’ ጋዜጣ ዲፕሎማቲክ ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል።
ይህ አስቸኳይ ጉብኝት የተደረገው የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራንን የቅርብ ጊዜ የሰላም አማራጭ ውድቅ ማድረጋቸውን ተከትሎ፣ የሰላም ድርድሩ ሙሉ በሙሉ እንዳይደናቀፍ ለማድረግ የተጀመረው የሽምግልና ጥረት አካል መሆኑ ተገልጿል።
የኢራኑ ‘ተስኒም’ የዜና ወኪል በበኩሉ፣ ሚኒስትሩ ከኢራን አቻቸው ኤስካንዳር ሞሜኒ እና ከፓርላማ አፈ-ጉባኤ መሐመድ ባጌር ጋሊባፍ ጋር ተገናኝተው በዋሽንግተን እና ቴህራን መካከል ያለውን የሰላም ድርድር ማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውን ጠቁሟል።
ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ እንዳስነበበው፣ ፕሬዚዳንት ትራምፕ የኢራንን የሰላም ሃሳብ ውድቅ ቢያደርጉም፤ ኢራን የኑክሌር መርሐ ግብሯን ለ20 ዓመታት እንድታግድ የሚጠይቅ አማራጭ አቅርበዋል።
ይሁን እንጂ የኢራን ባለሥልጣናት በአሜሪካ ወገን ምንም ዓይነት ተጨባጭ የዲፕሎማሲ አካሄድ ለውጥ አልታየም ሲሉ መተቸታቸውን መህር የዜና ወኪል ዘግቧል።
የሆርሙዝ ሰርጥን በተመለከተ ኢራን የባሕር ላይ መተላለፊያውን ለመቆጣጠር አዲስ “ሙያዊ የአሠራር ሥርዓት” ያለችውን የቁጥጥር ሥርዓት ይፋ እንደምታደርግ አስታውቃለች።
የኢራን ፓርላማ የብሔራዊ ደኅንነት ኮሚቴ ሰብሳቢ ኢብራሂም አዚዝን ጠቅሶ ሮይተርስ እንደዘገበው፣ አዲሱ አሠራር ከኢራን ጋር ለሚተባበሩ የንግድ መርከቦች ብቻ ቅድሚያ የሚሰጥ ሲሆን፣ የአሜሪካ ደጋፊ ለሆኑ መርከቦች ግን ዝግ ይሆናል።
በተጨማሪም ኢራን በዲጂታል እና በቢትኮይን ክፍያ የሚሠራ “ሆርሙዝ ሴፍ” የተባለ አዲስ የባሕር ላይ መድን ይፋ ማድረጓን ፋርስ የዜና ወኪል አረጋግጧል።
በሆርሙዝ ሰርጥ ያለው የባሕር ላይ ትራፊክ አሁንም እንደቀዘቀዘ መሆኑን እና አንዳንድ የአውሮፓ ሀገራት መርከቦቻቸው በሰላም እንዲያልፉ ከኢራን አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ጋር ድርድር መጀመራቸውን ብሉምበርግ ዘግቧል።
በሌላ በኩል የቀጣናውን ሰላም ይበልጥ አሳሳቢ የሚያደርግ ክስተት ተመዝግቧል። በተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች በሚገኘው የባራካህ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ የድሮን ጥቃት ደርሷል።
‘አሶሺዬትድ ፕሬስ' እንደዘገበው ጥቃቱ ከኃይል ማመንጫው የውስጠኛው አጥር ውጭ በሚገኝ የኤሌክትሪክ ጄነሬተር ላይ እሳት ቢያስነሳም፣ የኢምሬቶች ባለሥልጣናት እሳቱን በፍጥነት መቆጣጠር መቻሉን እና ምንም ዓይነት የጨረር ስጋትም ሆነ የሰው ጉዳት አለመድረሱን አረጋግጠዋል።
ዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኃይል ኤጀንሲ (IAEA) ዋና ዳይሬክተር ራፋኤል ግሮሲ ጥቃቱን “ተቀባይነት የሌለው” ሲሉ አውግዘውታል።
በመካከለኛው ምሥራቅ በአንድ በኩል ዲፕሎማሲያዊ የሰላም ጥረቶች ቢቀጥሉም፣ በሌላ በኩል እየተከሰቱ ያሉ የጸጥታ ስጋቶች ቀውሱ ወደ ከፋ ጦርነት እንዳያመራ ከፍተኛ ስጋት መፍጠራቸውን ዓለም አቀፍ የጂኦፖለቲካ ተንታኞች በማስጠንቀቅ ላይ ይገኛሉ።
በለሚ ታደሰ
#middleeastcrisis #peacetalks #straitofhormuz #diplomacy #globalenergy
**************
በመካከለኛው ምሥራቅ የሰላም ድርድር ጥረቶች፣ በሆርሙዝ ሰርጥ የባሕር ላይ መተላለፊያ ቁጥጥር እና በተመዘገቡ የጸጥታ ስጋቶች ዙሪያ አዳዲስ ክስተቶች ተመዝግበዋል።
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የነበረው ቀጥተኛ ድርድር መቋረጡን ተከትሎ ዲፕሎማሲያዊ ውጥረቱ ያሻቀበ ሲሆን፣ የንግድ መርከቦች እንቅስቃሴን ለመቆጣጠርም አዳዲስ እርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ።
የፓኪስታን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ሞህሲን ናቅቪ አስቀድሞ ያልተገለጸ የሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ቴህራን መግባታቸውን የፓኪስታኑ ‘ዶን’ ጋዜጣ ዲፕሎማቲክ ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል።
ይህ አስቸኳይ ጉብኝት የተደረገው የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራንን የቅርብ ጊዜ የሰላም አማራጭ ውድቅ ማድረጋቸውን ተከትሎ፣ የሰላም ድርድሩ ሙሉ በሙሉ እንዳይደናቀፍ ለማድረግ የተጀመረው የሽምግልና ጥረት አካል መሆኑ ተገልጿል።
የኢራኑ ‘ተስኒም’ የዜና ወኪል በበኩሉ፣ ሚኒስትሩ ከኢራን አቻቸው ኤስካንዳር ሞሜኒ እና ከፓርላማ አፈ-ጉባኤ መሐመድ ባጌር ጋሊባፍ ጋር ተገናኝተው በዋሽንግተን እና ቴህራን መካከል ያለውን የሰላም ድርድር ማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውን ጠቁሟል።
ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ እንዳስነበበው፣ ፕሬዚዳንት ትራምፕ የኢራንን የሰላም ሃሳብ ውድቅ ቢያደርጉም፤ ኢራን የኑክሌር መርሐ ግብሯን ለ20 ዓመታት እንድታግድ የሚጠይቅ አማራጭ አቅርበዋል።
ይሁን እንጂ የኢራን ባለሥልጣናት በአሜሪካ ወገን ምንም ዓይነት ተጨባጭ የዲፕሎማሲ አካሄድ ለውጥ አልታየም ሲሉ መተቸታቸውን መህር የዜና ወኪል ዘግቧል።
የሆርሙዝ ሰርጥን በተመለከተ ኢራን የባሕር ላይ መተላለፊያውን ለመቆጣጠር አዲስ “ሙያዊ የአሠራር ሥርዓት” ያለችውን የቁጥጥር ሥርዓት ይፋ እንደምታደርግ አስታውቃለች።
የኢራን ፓርላማ የብሔራዊ ደኅንነት ኮሚቴ ሰብሳቢ ኢብራሂም አዚዝን ጠቅሶ ሮይተርስ እንደዘገበው፣ አዲሱ አሠራር ከኢራን ጋር ለሚተባበሩ የንግድ መርከቦች ብቻ ቅድሚያ የሚሰጥ ሲሆን፣ የአሜሪካ ደጋፊ ለሆኑ መርከቦች ግን ዝግ ይሆናል።
በተጨማሪም ኢራን በዲጂታል እና በቢትኮይን ክፍያ የሚሠራ “ሆርሙዝ ሴፍ” የተባለ አዲስ የባሕር ላይ መድን ይፋ ማድረጓን ፋርስ የዜና ወኪል አረጋግጧል።
በሆርሙዝ ሰርጥ ያለው የባሕር ላይ ትራፊክ አሁንም እንደቀዘቀዘ መሆኑን እና አንዳንድ የአውሮፓ ሀገራት መርከቦቻቸው በሰላም እንዲያልፉ ከኢራን አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ጋር ድርድር መጀመራቸውን ብሉምበርግ ዘግቧል።
በሌላ በኩል የቀጣናውን ሰላም ይበልጥ አሳሳቢ የሚያደርግ ክስተት ተመዝግቧል። በተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች በሚገኘው የባራካህ የኑክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ የድሮን ጥቃት ደርሷል።
‘አሶሺዬትድ ፕሬስ' እንደዘገበው ጥቃቱ ከኃይል ማመንጫው የውስጠኛው አጥር ውጭ በሚገኝ የኤሌክትሪክ ጄነሬተር ላይ እሳት ቢያስነሳም፣ የኢምሬቶች ባለሥልጣናት እሳቱን በፍጥነት መቆጣጠር መቻሉን እና ምንም ዓይነት የጨረር ስጋትም ሆነ የሰው ጉዳት አለመድረሱን አረጋግጠዋል።
ዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኃይል ኤጀንሲ (IAEA) ዋና ዳይሬክተር ራፋኤል ግሮሲ ጥቃቱን “ተቀባይነት የሌለው” ሲሉ አውግዘውታል።
በመካከለኛው ምሥራቅ በአንድ በኩል ዲፕሎማሲያዊ የሰላም ጥረቶች ቢቀጥሉም፣ በሌላ በኩል እየተከሰቱ ያሉ የጸጥታ ስጋቶች ቀውሱ ወደ ከፋ ጦርነት እንዳያመራ ከፍተኛ ስጋት መፍጠራቸውን ዓለም አቀፍ የጂኦፖለቲካ ተንታኞች በማስጠንቀቅ ላይ ይገኛሉ።
በለሚ ታደሰ
#middleeastcrisis #peacetalks #straitofhormuz #diplomacy #globalenergy
3 months ago
“ኢራን ከምድር ገጽ ትጠፋለች!” — ዶናልድ ትራምፕ
#ethiopia | በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ እየተባባሰ የመጣውን ወታደራዊ ውጥረት ተከትሎ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለኢራን እጅግ አስደንጋጭ ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።
ከፎክስ ኒውስ ጋዜጠኛ ትሬይ ይንግስት ጋር ቆይታ ያደረጉት ትራምፕ፣ የንግድ መርከቦችን በማጀብ ላይ ባሉ የአሜሪካ የጦር መርከቦች ላይ የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ ማንኛውንም ዓይነት ጥቃት የምትሰነዝር ከሆነ ሀገሪቱ “ከምድር ገጽ እንድትጠፋ” ይደረጋል ሲሉ በከባድ ቃላት ዝተዋል።
ይህ የአሜሪካ ጠንካራ አቋም የመጣው ዋሽንግተን በስትሬቱ በኩል የሚያልፉ የነዳጅ እና የንግድ መርከቦችን በጦር መርከቦች የማጀብ (Project Freedom) ዘመቻ መጀመሯን ተከትሎ ነው።
ትራምፕ በንግግራቸው አሜሪካ በአሁኑ ወቅት እጅግ ዘመናዊ የጦር መሣሪያ የታጠቀች መሆኑን በመጥቀስ፣ ማንኛውንም ትንኮሳ ለመመከት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
በዛሬው ዕለት ብቻ የአሜሪካ ባህር ኃይል ስድስት የኢራን የፈጣን ጥቃት ጀልባዎችን ማውደሙ የተነገረ ሲሆን፣ ይህም አካባቢውን ወደ ቀጥተኛ ጦርነት ሊያስገባው ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል።
ምንም እንኳን ትራምፕ የኃይል እርምጃ ማስጠንቀቂያ ቢሰጡም፣ ኢራን በድርድር ረገድ የተሻለ አቋም እንድታሳይ ግፊት እያደረጉ መሆኑን ጠቁመዋል።
በአሁኑ ወቅት የፔንታጎን እና የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ሁኔታውን በቅርበት እየተከታተሉ ሲሆን፣ ተጨማሪ መግለጫዎች እንደሚሰጡ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #መናኸሪያfm #trump #iran #straitofhormuz #breakingnews #ethiopia #amharicnewsm
#ethiopia | በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ እየተባባሰ የመጣውን ወታደራዊ ውጥረት ተከትሎ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለኢራን እጅግ አስደንጋጭ ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።
ከፎክስ ኒውስ ጋዜጠኛ ትሬይ ይንግስት ጋር ቆይታ ያደረጉት ትራምፕ፣ የንግድ መርከቦችን በማጀብ ላይ ባሉ የአሜሪካ የጦር መርከቦች ላይ የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ ማንኛውንም ዓይነት ጥቃት የምትሰነዝር ከሆነ ሀገሪቱ “ከምድር ገጽ እንድትጠፋ” ይደረጋል ሲሉ በከባድ ቃላት ዝተዋል።
ይህ የአሜሪካ ጠንካራ አቋም የመጣው ዋሽንግተን በስትሬቱ በኩል የሚያልፉ የነዳጅ እና የንግድ መርከቦችን በጦር መርከቦች የማጀብ (Project Freedom) ዘመቻ መጀመሯን ተከትሎ ነው።
ትራምፕ በንግግራቸው አሜሪካ በአሁኑ ወቅት እጅግ ዘመናዊ የጦር መሣሪያ የታጠቀች መሆኑን በመጥቀስ፣ ማንኛውንም ትንኮሳ ለመመከት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
በዛሬው ዕለት ብቻ የአሜሪካ ባህር ኃይል ስድስት የኢራን የፈጣን ጥቃት ጀልባዎችን ማውደሙ የተነገረ ሲሆን፣ ይህም አካባቢውን ወደ ቀጥተኛ ጦርነት ሊያስገባው ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል።
ምንም እንኳን ትራምፕ የኃይል እርምጃ ማስጠንቀቂያ ቢሰጡም፣ ኢራን በድርድር ረገድ የተሻለ አቋም እንድታሳይ ግፊት እያደረጉ መሆኑን ጠቁመዋል።
በአሁኑ ወቅት የፔንታጎን እና የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ሁኔታውን በቅርበት እየተከታተሉ ሲሆን፣ ተጨማሪ መግለጫዎች እንደሚሰጡ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #መናኸሪያfm #trump #iran #straitofhormuz #breakingnews #ethiopia #amharicnewsm
3 months ago
የሆርሙዝ ሰርጥ ውጥረት ወደ አዲስ ምዕራፍ ተሸጋግሯል! #us #iran #straitofhormuz #projectfreedom #middleeastconflict #maritimesecurity
Sponsored by
Surafel
3 months ago
አሜሪካ በሆርሙዝ ሰርጥ የንግድ መርከቦችን ለማጀብ ማቀዷን ተከትሎ ኢራን ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ሰጠች
*****************
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሀገራቸው የጦር መርከቦች በሆርሙዝ ሰርጥ የሚያልፉ ገለልተኛ የውጭ ሀገራት የንግድ መርከቦችን የማጀብ እና ደኅንነት የማስጠበቅ ሥራ እንደሚጀምሩ አስታውቀዋል።
ፕሬዝዳንቱ ይህንን ጥረት "ሰብዓዊ ተግባር" ሲሉ የገለጹት ሲሆን፤ ርምጃው የተዘጋውን የውኃ መስመር ለሚያቋርጡ መርከቦች ከለላ ለመስጠት ያለመ መሆኑን አመላክተዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለእስራኤሉ የመገናኛ ብዙኃን ተቋም 'ካን ኒውስ' በሰጡት ቃል፣ ጦርነቱን ለማስቆም በቅርቡ ከኢራን የቀረበውን የሰላም ሀሳብ መርምረው ተቀባይነት የሌለው ሆኖ እንዳገኙት ተናግረዋል።
የኢራን ሀሳብ ውድቅ ቢደረግም፤ አሜሪካ ለቴህራኑ የ14 ነጥብ የውሳኔ ሃሳብ ምላሽ የሚሆን አዲስ የተሻሻለ ረቂቅ ስምምነት ማቅረቧ ተገልጿል።
ይህንን የአሜሪካን ውሳኔ ተከትሎ ኢራን በበኩሏ ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ሰጥታለች።
ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት ንግግር ምላሽ የሰጡት የኢራን ብሔራዊ ደኅንነት ኮሚሽን ምክትል ሰብሳቢ ኢብራሂም አዚዚ፤ ማንኛውም የአሜሪካ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት በሆርሙዝ የውኃ መስመር ላይ የተደረሰውን የተኩስ አቁም ስምምነት የሚጥስ ነው ብለዋል።
የአሜሪካው ዜና አውታር 'አክሲዮስ' በዘገባው እንዳመለከተው ኢራን የሆርሙዝ ሰርጥን መልሳ ለመክፈት አሜሪካ የባሕር ላይ ከበባዋን እንድታነሳና ጦርነቱ እንዲያበቃ የአንድ ወር የድርድር ጊዜ ገደብ አስቀምጣለች።
በሌላ በኩል የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (ሴንትኮም) በሆርሙዝ ሰርጥ ለሚያካሂደው ተልዕኮ ሚሳኤል አውዳሚ የጦር መርከቦችን፣ ከ100 በላይ የጦር አውሮፕላኖችን፣ ድሮኖችን እንዲሁም 15 ሺህ ወታደሮችን እንደሚያሰማራ አስታውቋል።
የመርከቦችን ደኅንነቱ በመጠበቅ ጉዞውን ወደ ነበረበት ለመመለስ የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ኃይሎች ከዛሬ ጀምሮ ለ'ፕሮጀክት ፍሪደም' ዘመቻ ተግባራዊነት ርምጃ መውሰድ እንደሚጀምሩም ተጠቁሟል።
የአሜሪካ የባሕር ኃይል ማዕከላዊ ዕዝ አዛዥ አድሚራል ብራድ ኩፐር አሜሪካ የባሕር ላይ ከበባዋን አጠናክራ እንደቀጠለች ጠቁመው፤ ለዚህ የመከላከያ ተልዕኮ የሚደረገው ጥረት ለቀጣናው ደኅንነት ወሳኝ መሆኑን አስምረውበታል።
በሀና ምንዳሁን
#us #iran #straitofhormuz #projectfreedom #middleeastconflict #maritimesecurity
*****************
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሀገራቸው የጦር መርከቦች በሆርሙዝ ሰርጥ የሚያልፉ ገለልተኛ የውጭ ሀገራት የንግድ መርከቦችን የማጀብ እና ደኅንነት የማስጠበቅ ሥራ እንደሚጀምሩ አስታውቀዋል።
ፕሬዝዳንቱ ይህንን ጥረት "ሰብዓዊ ተግባር" ሲሉ የገለጹት ሲሆን፤ ርምጃው የተዘጋውን የውኃ መስመር ለሚያቋርጡ መርከቦች ከለላ ለመስጠት ያለመ መሆኑን አመላክተዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለእስራኤሉ የመገናኛ ብዙኃን ተቋም 'ካን ኒውስ' በሰጡት ቃል፣ ጦርነቱን ለማስቆም በቅርቡ ከኢራን የቀረበውን የሰላም ሀሳብ መርምረው ተቀባይነት የሌለው ሆኖ እንዳገኙት ተናግረዋል።
የኢራን ሀሳብ ውድቅ ቢደረግም፤ አሜሪካ ለቴህራኑ የ14 ነጥብ የውሳኔ ሃሳብ ምላሽ የሚሆን አዲስ የተሻሻለ ረቂቅ ስምምነት ማቅረቧ ተገልጿል።
ይህንን የአሜሪካን ውሳኔ ተከትሎ ኢራን በበኩሏ ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ሰጥታለች።
ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት ንግግር ምላሽ የሰጡት የኢራን ብሔራዊ ደኅንነት ኮሚሽን ምክትል ሰብሳቢ ኢብራሂም አዚዚ፤ ማንኛውም የአሜሪካ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት በሆርሙዝ የውኃ መስመር ላይ የተደረሰውን የተኩስ አቁም ስምምነት የሚጥስ ነው ብለዋል።
የአሜሪካው ዜና አውታር 'አክሲዮስ' በዘገባው እንዳመለከተው ኢራን የሆርሙዝ ሰርጥን መልሳ ለመክፈት አሜሪካ የባሕር ላይ ከበባዋን እንድታነሳና ጦርነቱ እንዲያበቃ የአንድ ወር የድርድር ጊዜ ገደብ አስቀምጣለች።
በሌላ በኩል የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (ሴንትኮም) በሆርሙዝ ሰርጥ ለሚያካሂደው ተልዕኮ ሚሳኤል አውዳሚ የጦር መርከቦችን፣ ከ100 በላይ የጦር አውሮፕላኖችን፣ ድሮኖችን እንዲሁም 15 ሺህ ወታደሮችን እንደሚያሰማራ አስታውቋል።
የመርከቦችን ደኅንነቱ በመጠበቅ ጉዞውን ወደ ነበረበት ለመመለስ የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ኃይሎች ከዛሬ ጀምሮ ለ'ፕሮጀክት ፍሪደም' ዘመቻ ተግባራዊነት ርምጃ መውሰድ እንደሚጀምሩም ተጠቁሟል።
የአሜሪካ የባሕር ኃይል ማዕከላዊ ዕዝ አዛዥ አድሚራል ብራድ ኩፐር አሜሪካ የባሕር ላይ ከበባዋን አጠናክራ እንደቀጠለች ጠቁመው፤ ለዚህ የመከላከያ ተልዕኮ የሚደረገው ጥረት ለቀጣናው ደኅንነት ወሳኝ መሆኑን አስምረውበታል።
በሀና ምንዳሁን
#us #iran #straitofhormuz #projectfreedom #middleeastconflict #maritimesecurity
3 months ago
ትራምፕ የተኩስ አቁሙን አራዘሙ፤
ኢራን ግን መርከቦችን መጥለፍ ቀጥላለች
#ethiopia | የመካከለኛው ምስራቅ ውጥረት ባልተጠበቀ ሁኔታ አዲስ መልክ ይዟል። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሰላም ድርድሩ እንዲቀጥል የተኩስ አቁም ስምምነቱን ለማራዘም ቢወስኑም፣ በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ ግን የኢራን ባህር ኃይል እርምጃ መውሰዱን ቀጥሏል።
የኢራን አብዮታዊ ዘበኛ (IRGC) በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ ሁለት መርከቦችን በቁጥጥር ስር አውሎ ወደ ግዛቱ መውሰዱን አስታውቋል። ሶስተኛ መርከብ ደግሞ በጥቃት ምክንያት ከጥቅም ውጪ ሆና በኢራን ባህር ዳርቻ ትገኛለች።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለቴህራን የተወሰነ ጊዜ በመስጠት የተኩስ አቁሙ ድርድሩ እስኪያልቅ ድረስ እንዲቀጥል ወስነዋል። ይህ ውሳኔ በዓለም ላይ የነበረውን ከፍተኛ ስጋት ለጊዜው አርክሶታል።
ሊባኖስ ከእስራኤል ጋር ያላትን የተኩስ አቁም ለአንድ ወር እንዲራዘም የጠየቀች ቢሆንም፣ እስራኤል ግን የሂዝቦላህ ድሮን መትታ መጣሏን ገልጻለች።
ትራምፕ ለድርድር ዕድል ቢሰጡም፣ ኢራን መርከቦችን በመጥለፍ "ካርዶቿን እየመዘዘች" ትገኛለች። ይህ የድመትና አይጥ ጨዋታ በዓለም ነዳጅ ገበያና በኢኮኖሚው ላይ የሚያሳድረው ጫና በቀላሉ የሚታይ አይደለም። ድርድሩ ካልተሳካ ወደ መጠነ ሰፊ ጦርነት የመመለስ ዕድሉ አሁንም ሰፊ ነው።
ሰላምና ጦርነት በአንድ ቀጭን ክር ላይ ተንጠልጥለዋል!
#getu #breakingnews #trumpiran #straitofhormuz #ceasefireextension #middleeastconflict #oilmarket #globalsecurity #ትራምፕ #ኢራን #የሆርሙዝወሽመጥ #ጦርነት #ጌጡተመስገን #getutemesgen
ኢራን ግን መርከቦችን መጥለፍ ቀጥላለች
#ethiopia | የመካከለኛው ምስራቅ ውጥረት ባልተጠበቀ ሁኔታ አዲስ መልክ ይዟል። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሰላም ድርድሩ እንዲቀጥል የተኩስ አቁም ስምምነቱን ለማራዘም ቢወስኑም፣ በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ ግን የኢራን ባህር ኃይል እርምጃ መውሰዱን ቀጥሏል።
የኢራን አብዮታዊ ዘበኛ (IRGC) በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ ሁለት መርከቦችን በቁጥጥር ስር አውሎ ወደ ግዛቱ መውሰዱን አስታውቋል። ሶስተኛ መርከብ ደግሞ በጥቃት ምክንያት ከጥቅም ውጪ ሆና በኢራን ባህር ዳርቻ ትገኛለች።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለቴህራን የተወሰነ ጊዜ በመስጠት የተኩስ አቁሙ ድርድሩ እስኪያልቅ ድረስ እንዲቀጥል ወስነዋል። ይህ ውሳኔ በዓለም ላይ የነበረውን ከፍተኛ ስጋት ለጊዜው አርክሶታል።
ሊባኖስ ከእስራኤል ጋር ያላትን የተኩስ አቁም ለአንድ ወር እንዲራዘም የጠየቀች ቢሆንም፣ እስራኤል ግን የሂዝቦላህ ድሮን መትታ መጣሏን ገልጻለች።
ትራምፕ ለድርድር ዕድል ቢሰጡም፣ ኢራን መርከቦችን በመጥለፍ "ካርዶቿን እየመዘዘች" ትገኛለች። ይህ የድመትና አይጥ ጨዋታ በዓለም ነዳጅ ገበያና በኢኮኖሚው ላይ የሚያሳድረው ጫና በቀላሉ የሚታይ አይደለም። ድርድሩ ካልተሳካ ወደ መጠነ ሰፊ ጦርነት የመመለስ ዕድሉ አሁንም ሰፊ ነው።
ሰላምና ጦርነት በአንድ ቀጭን ክር ላይ ተንጠልጥለዋል!
#getu #breakingnews #trumpiran #straitofhormuz #ceasefireextension #middleeastconflict #oilmarket #globalsecurity #ትራምፕ #ኢራን #የሆርሙዝወሽመጥ #ጦርነት #ጌጡተመስገን #getutemesgen
4 months ago
48 ሰዓታት
ኢራን፣ የሆርሙዝ ሰርጥ እና የትራምፕ ማስጠንቀቂያ!
#ethiopia | ባለፉት 48 ሰዓታት በመካከለኛው ምስራቅ የታዩት ክስተቶች ዓለምን በስጋት አይን እንድትመለከት አድርገዋል።
በኢራንና በአሜሪካ መካከል ያለው ፍጥጫ ወደ አዲስ ምዕራፍ ተሸጋግሯል።
ኢራን የዓለም የነዳጅ ንግድ የደም ሥር የሆነውን የሆርሙዝ ሰርጥን ልትዘጋ ትችላለች የሚለው ስጋት አይሏል። ይህም በዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ ላይ ከፍተኛ መናር ሊያስከትል እንደሚችል ተገምቷል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ የአሜሪካ ጦር "በጣም በቅርብ ጊዜ" ከኢራን እንደሚወጣ ቢገልጹም፣ በሌላ በኩል ግን ማንኛውም ጥቃት ቢሰነዘር አሜሪካ "የማያዳግም ምላሽ" እንደምትሰጥ አስጠንቅቀዋል።
የኢራን ግማሽ ያህሉ የሚሳኤልና የድሮን አቅም ጥቃት ሳይደርስበት አሁንም ዝግጁ መሆኑ መገለጹ፣ አሜሪካ ጦሯን በምታወጣበት ወቅት ኢራን የበላይነቱን ለመያዝ እንድትሞክር በር ሊከፍት ይችላል ተብሏል።
የሆርሙዝ ሰርጥ መዘጋት ማለት የኢትዮጵያን ጨምሮ የበርካታ ሀገራት ኢኮኖሚ ላይ ቀጥተኛ ጫና ይፈጥራል። የነዳጅ ዋጋ መናር የኑሮ ውድነትን ይበልጥ ሊያባብሰው ይችላል።
#getu #irantension #straitofhormuz #trump #middleeastcrisis #oilprices #globalsecurity #usmilitary #geopolitics #ኢራን #ሆርሙዝሰርጥ #ትራምፕ #ነዳጅ #ኢኮኖሚ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
ኢራን፣ የሆርሙዝ ሰርጥ እና የትራምፕ ማስጠንቀቂያ!
#ethiopia | ባለፉት 48 ሰዓታት በመካከለኛው ምስራቅ የታዩት ክስተቶች ዓለምን በስጋት አይን እንድትመለከት አድርገዋል።
በኢራንና በአሜሪካ መካከል ያለው ፍጥጫ ወደ አዲስ ምዕራፍ ተሸጋግሯል።
ኢራን የዓለም የነዳጅ ንግድ የደም ሥር የሆነውን የሆርሙዝ ሰርጥን ልትዘጋ ትችላለች የሚለው ስጋት አይሏል። ይህም በዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ ላይ ከፍተኛ መናር ሊያስከትል እንደሚችል ተገምቷል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ የአሜሪካ ጦር "በጣም በቅርብ ጊዜ" ከኢራን እንደሚወጣ ቢገልጹም፣ በሌላ በኩል ግን ማንኛውም ጥቃት ቢሰነዘር አሜሪካ "የማያዳግም ምላሽ" እንደምትሰጥ አስጠንቅቀዋል።
የኢራን ግማሽ ያህሉ የሚሳኤልና የድሮን አቅም ጥቃት ሳይደርስበት አሁንም ዝግጁ መሆኑ መገለጹ፣ አሜሪካ ጦሯን በምታወጣበት ወቅት ኢራን የበላይነቱን ለመያዝ እንድትሞክር በር ሊከፍት ይችላል ተብሏል።
የሆርሙዝ ሰርጥ መዘጋት ማለት የኢትዮጵያን ጨምሮ የበርካታ ሀገራት ኢኮኖሚ ላይ ቀጥተኛ ጫና ይፈጥራል። የነዳጅ ዋጋ መናር የኑሮ ውድነትን ይበልጥ ሊያባብሰው ይችላል።
#getu #irantension #straitofhormuz #trump #middleeastcrisis #oilprices #globalsecurity #usmilitary #geopolitics #ኢራን #ሆርሙዝሰርጥ #ትራምፕ #ነዳጅ #ኢኮኖሚ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
4 months ago
ኢራን የነዳጅ መርከቦችን በ2 ሚ. ዶላር እያሳለፈች ነው
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ የኔቶ (NATO) አባላት በሆርሙዝ ወንዝ ላይ ያለውን የጸጥታ ሁኔታ ለማረጋጋትና የንግድ መስመሩን ክፍት ለማድረግ ካልተባበሩ ዓለም አቀፍ ቀውስ ሊከሰት እንደሚችል አስጠነቀቁ።
ኔቶ የሆርሙዝ ወንዝን ደህንነት በመጠበቅ ረገድ የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንዳለበትና አሜሪካ ብቻዋን ዋጋ መክፈል እንደማይገባት አሳስበዋል።
አጋር ሀገራት ድጋፍ ካልሰጡ፣ የወደፊቱ ጊዜ "እጅግ አስከፊ" ሊሆን እንደሚችልና የዓለም የንግድ ፍሰት አደጋ ላይ እንደሚወድቅ ገልጸዋል።
ይህ ማስጠንቀቂያ የመጣው በሆርሙዝ ወንዝ አካባቢ በኢራንና በአሜሪካ መካከል ያለው ውጥረት በከረረበት ወቅት መሆኑ ጉዳዩን ዓለም አቀፍ ትኩረት እንዲያገኝ አድርጎታል።
የሆርሙዝ ወንዝ የዓለም የነዳጅ ንግድ አንድ አምስተኛ የሚተላለፍበት በመሆኑ፣ ይህ ማስጠንቀቂያ በነዳጅ ዋጋ ላይ ከፍተኛ መናወጥ ሊፈጥር ይችላል ተብሎ ተሰግቷል።
የትራምፕ አስተዳደር አጋሮቹን "የድርሻችሁን ተወጡ" በማለት እያስገደደበት ያለው ይህ አቋም፣ በኔቶ አባላት መካከል አዲስ የፖለቲካ ፍጥጫ መፍጠሩን ቀጥሏል።
በተያያዘ ዜና
በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ግጭት ወደ ከፋ ኢኮኖሚያዊ ጦርነት ተሸጋግሯል። WION እንደዘገበው ከሆነ፤ አንድ የነዳጅ ጫኝ መርከብ ኦፕሬተር በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ በሰላም ለማለፍ ብቻ ለኢራን 2 ሚሊዮን ዶላር "የመሸጋገሪያ ክፍያ" መክፈሉ ተሰምቷል።
ኢራን ይህንን ስትራቴጂካዊ የባህር መስመር በመቆጣጠር፣ "ለፈቀደችላቸው" ሀገራት መርከቦች ሚሊዮኖችን እያስከፈለች ሲሆን፣ ይህም በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ ላይ ከፍተኛ ጫና ፈጥሯል።
በዚህ ሳቢያ በአንዳንድ የአሜሪካ ከተሞች የአንድ ጋሎን ነዳጅ ዋጋ 8 ዶላር ደርሷል።
ዋይት ሀውስ በባህር ላይ ታግተው የነበሩ የኢራን የነዳጅ መርከቦች ላይ የተጣለውን ማዕቀብ በማንሳት የገበያውን ንረት ለማረጋጋት እየሞከረ ቢሆንም፣ ሁኔታው ግን ከቁጥጥር ውጪ እየሆነ መጥቷል።
ይህ በኢራን፣ አሜሪካና እስራኤል መካከል እየተካሄደ ያለው ፍጥጫ የጦርነት ግንባሩን ወደ ዓለም አቀፍ ኢኮኖሚ ቀውስ የቀየረው ይመስላል።
#getu #trump #nato #straitofhormuz #globalsecurity #oilmarket #usforeignpolicy #iranus #internationaltrade #breakingnews #ትራምፕ #ኔቶ #ሆርሙዝወንዝ #ዓለምአቀፍፖለቲካ #ዜና #ጌጡተመስገን #getutemesgen
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ የኔቶ (NATO) አባላት በሆርሙዝ ወንዝ ላይ ያለውን የጸጥታ ሁኔታ ለማረጋጋትና የንግድ መስመሩን ክፍት ለማድረግ ካልተባበሩ ዓለም አቀፍ ቀውስ ሊከሰት እንደሚችል አስጠነቀቁ።
ኔቶ የሆርሙዝ ወንዝን ደህንነት በመጠበቅ ረገድ የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንዳለበትና አሜሪካ ብቻዋን ዋጋ መክፈል እንደማይገባት አሳስበዋል።
አጋር ሀገራት ድጋፍ ካልሰጡ፣ የወደፊቱ ጊዜ "እጅግ አስከፊ" ሊሆን እንደሚችልና የዓለም የንግድ ፍሰት አደጋ ላይ እንደሚወድቅ ገልጸዋል።
ይህ ማስጠንቀቂያ የመጣው በሆርሙዝ ወንዝ አካባቢ በኢራንና በአሜሪካ መካከል ያለው ውጥረት በከረረበት ወቅት መሆኑ ጉዳዩን ዓለም አቀፍ ትኩረት እንዲያገኝ አድርጎታል።
የሆርሙዝ ወንዝ የዓለም የነዳጅ ንግድ አንድ አምስተኛ የሚተላለፍበት በመሆኑ፣ ይህ ማስጠንቀቂያ በነዳጅ ዋጋ ላይ ከፍተኛ መናወጥ ሊፈጥር ይችላል ተብሎ ተሰግቷል።
የትራምፕ አስተዳደር አጋሮቹን "የድርሻችሁን ተወጡ" በማለት እያስገደደበት ያለው ይህ አቋም፣ በኔቶ አባላት መካከል አዲስ የፖለቲካ ፍጥጫ መፍጠሩን ቀጥሏል።
በተያያዘ ዜና
በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ግጭት ወደ ከፋ ኢኮኖሚያዊ ጦርነት ተሸጋግሯል። WION እንደዘገበው ከሆነ፤ አንድ የነዳጅ ጫኝ መርከብ ኦፕሬተር በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ በሰላም ለማለፍ ብቻ ለኢራን 2 ሚሊዮን ዶላር "የመሸጋገሪያ ክፍያ" መክፈሉ ተሰምቷል።
ኢራን ይህንን ስትራቴጂካዊ የባህር መስመር በመቆጣጠር፣ "ለፈቀደችላቸው" ሀገራት መርከቦች ሚሊዮኖችን እያስከፈለች ሲሆን፣ ይህም በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ ላይ ከፍተኛ ጫና ፈጥሯል።
በዚህ ሳቢያ በአንዳንድ የአሜሪካ ከተሞች የአንድ ጋሎን ነዳጅ ዋጋ 8 ዶላር ደርሷል።
ዋይት ሀውስ በባህር ላይ ታግተው የነበሩ የኢራን የነዳጅ መርከቦች ላይ የተጣለውን ማዕቀብ በማንሳት የገበያውን ንረት ለማረጋጋት እየሞከረ ቢሆንም፣ ሁኔታው ግን ከቁጥጥር ውጪ እየሆነ መጥቷል።
ይህ በኢራን፣ አሜሪካና እስራኤል መካከል እየተካሄደ ያለው ፍጥጫ የጦርነት ግንባሩን ወደ ዓለም አቀፍ ኢኮኖሚ ቀውስ የቀየረው ይመስላል።
#getu #trump #nato #straitofhormuz #globalsecurity #oilmarket #usforeignpolicy #iranus #internationaltrade #breakingnews #ትራምፕ #ኔቶ #ሆርሙዝወንዝ #ዓለምአቀፍፖለቲካ #ዜና #ጌጡተመስገን #getutemesgen
5 months ago
ባህሬንና 19 ሀገራት በኢራን ላይ ጠንካራ ጥምረት መሰረቱ
#ethiopia | የባህሬን መንግስት ከአውሮፓ እና እስያ ከተውጣጡ 19 አጋር ሀገራት ጋር በመሆን፣ ስልታዊ ጠቀሜታ ባለው የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ (Strait of Hormuz) ላይ ጥብቅ የደህንነት እርምጃ ለመውሰድ ዝግጁ መሆኑን አስታውቋል።
ይህ ሰፊ ጥምረት ዩናይትድ ኪንግደም፣ ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ ጃፓን፣ ካናዳ እና ደቡብ ኮሪያን ጨምሮ በርካታ የአውሮፓ ሀገራትን ያቀፈ ነው።
ጥምረቱ ኢራን በንግድ መርከቦች እና በሲቪል መሰረተ ልማቶች ላይ የምታደርሰውን ጥቃት እንዲሁም የባህር ላይ መስመሮች መቋረጥን በጽኑ ኮንኗል።
ቴህራን የባህር ላይ ፈንጂዎችን ከመቅበር፣ የድሮን እና የሚሳኤል ጥቃቶችን ከመሰንዘር በአስቸኳይ እንድትቆጠብ ጥሪ ቀርቧል።
ኢራን በቀጠናው መረጋጋትን ለመመለስ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ውሳኔ ቁጥር 2817ን እንድታከብር አሳስቧል።
ይህ ጥምረት መስተጓጎሉ የሚቀጥል ከሆነ በቴህራን ላይ ተጨማሪ እና ጠንካራ እርምጃዎች ሊወሰዱ እንደሚችሉ ግልጽ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል።
የዓለም የኢነርጂ ማጓጓዣ ቁልፍ በሆነው በዚህ ቀጠና ላይ የተደቀነው ስጋት የዓለምን ትኩረት ስቧል።
#getu #ethiopia #breakingnews #middleeast #straitofhormuz #bahrain #iran #globalsecurity #news #ሰበርዜና #ባህሬን #ኢራን #የባህርላይደህንነት #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | የባህሬን መንግስት ከአውሮፓ እና እስያ ከተውጣጡ 19 አጋር ሀገራት ጋር በመሆን፣ ስልታዊ ጠቀሜታ ባለው የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ (Strait of Hormuz) ላይ ጥብቅ የደህንነት እርምጃ ለመውሰድ ዝግጁ መሆኑን አስታውቋል።
ይህ ሰፊ ጥምረት ዩናይትድ ኪንግደም፣ ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ ጃፓን፣ ካናዳ እና ደቡብ ኮሪያን ጨምሮ በርካታ የአውሮፓ ሀገራትን ያቀፈ ነው።
ጥምረቱ ኢራን በንግድ መርከቦች እና በሲቪል መሰረተ ልማቶች ላይ የምታደርሰውን ጥቃት እንዲሁም የባህር ላይ መስመሮች መቋረጥን በጽኑ ኮንኗል።
ቴህራን የባህር ላይ ፈንጂዎችን ከመቅበር፣ የድሮን እና የሚሳኤል ጥቃቶችን ከመሰንዘር በአስቸኳይ እንድትቆጠብ ጥሪ ቀርቧል።
ኢራን በቀጠናው መረጋጋትን ለመመለስ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት ውሳኔ ቁጥር 2817ን እንድታከብር አሳስቧል።
ይህ ጥምረት መስተጓጎሉ የሚቀጥል ከሆነ በቴህራን ላይ ተጨማሪ እና ጠንካራ እርምጃዎች ሊወሰዱ እንደሚችሉ ግልጽ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል።
የዓለም የኢነርጂ ማጓጓዣ ቁልፍ በሆነው በዚህ ቀጠና ላይ የተደቀነው ስጋት የዓለምን ትኩረት ስቧል።
#getu #ethiopia #breakingnews #middleeast #straitofhormuz #bahrain #iran #globalsecurity #news #ሰበርዜና #ባህሬን #ኢራን #የባህርላይደህንነት #ጌጡተመስገን #getutemesgen
5 months ago
የሆርሙዝ ወሽመጥ መዘዝ የግብፅን ጉሮሮ የሚዘጋ ነው
#ethiopia | የግብፁ ፕሬዝዳንት አብደል ፋታህ አል-ሲሲ፣ በዓለም አቀፉ የንግድና የነዳጅ መስመር የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ (Strait of Hormuz) ላይ ሊፈጠር የሚችል ማንኛውም መስተጓጎል በግብፅ ኢኮኖሚ ላይ “ከባድ አደጋ” እንደሚጋርጥ አስጠነቀቁ።
ፕሬዝዳንቱ ይህንን መልዕክት ያስተላለፉት፣ የ10ኛው ረመዳን የድል በዓልን ምክንያት በማድረግ የሀገሪቱ የጦር ኃይሎች ባዘጋጁት ዓመታዊ የኢፍጣር መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር ነው።
ቁልፍ ስጋቶችና የተነሱ ነጥቦች፦
* የነዳጅ ዋጋ ንረት፦ የሆርሙዝ ወሽመጥ ለዓለም አቀፍ የኃይል አቅርቦት ወሳኝ መተላለፊያ መሆኑን የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፣ የመስመሩ መዘጋት የነዳጅ ዋጋን ሰማይ በማድረስ በዓለም አቀፍ ደረጃ የዋጋ ንረትን እንደሚቀሰቅስ ገልጸዋል።
* በስዊዝ ካናል ላይ የሚደርስ ኪሳራ፦ ለግብፅ የውጭ ምንዛሬ ዋነኛ የጀርባ አጥንት የሆነው የስዊዝ ካናል (Suez Canal)፣ ከንግድ ፍሰት መቆረጥ ጋር ተያይዞ ከፍተኛ የገቢ ቅናሽ ሊገጥመው እንደሚችል አል-ሲሲ አሳስበዋል።
* አጠቃላይ የኢኮኖሚ ጫና፦ የነዳጅ ዋጋ መጨመር በግብፅ የውስጥ ኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ ተጨማሪ ጫና በመፍጠር የዜጎችን የመግዛት አቅም ሊፈትን እንደሚችል ጠቁመዋል።
ፕሬዝዳንት አል-ሲሲ አክለውም፣ ግብፅ ከቀጠናዊና ከዓለም አቀፋዊ የደህንነት ስጋቶች ጋር ተያይዘው የሚመጡ ኢኮኖሚያዊ ትንኮሳዎችን በንቃት መከታተልና መመከት እንዳለባት ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
ይህ ማስጠንቀቂያ የመጣው በቀጠናው ያለው የጂኦ-ፖለቲካ ውጥረት በዓለም አቀፍ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ስጋት እየፈጠረ ባለበት ወቅት መሆኑ ጉዳዩን ይበልጥ አሳሳቢ ያደርገዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #egypt #suezcanal #straitofhormuz #alsisi #globaleconomy #energysecurity #ግብፅ #ኢኮኖሚ
#ethiopia | የግብፁ ፕሬዝዳንት አብደል ፋታህ አል-ሲሲ፣ በዓለም አቀፉ የንግድና የነዳጅ መስመር የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ (Strait of Hormuz) ላይ ሊፈጠር የሚችል ማንኛውም መስተጓጎል በግብፅ ኢኮኖሚ ላይ “ከባድ አደጋ” እንደሚጋርጥ አስጠነቀቁ።
ፕሬዝዳንቱ ይህንን መልዕክት ያስተላለፉት፣ የ10ኛው ረመዳን የድል በዓልን ምክንያት በማድረግ የሀገሪቱ የጦር ኃይሎች ባዘጋጁት ዓመታዊ የኢፍጣር መርሃ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር ነው።
ቁልፍ ስጋቶችና የተነሱ ነጥቦች፦
* የነዳጅ ዋጋ ንረት፦ የሆርሙዝ ወሽመጥ ለዓለም አቀፍ የኃይል አቅርቦት ወሳኝ መተላለፊያ መሆኑን የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፣ የመስመሩ መዘጋት የነዳጅ ዋጋን ሰማይ በማድረስ በዓለም አቀፍ ደረጃ የዋጋ ንረትን እንደሚቀሰቅስ ገልጸዋል።
* በስዊዝ ካናል ላይ የሚደርስ ኪሳራ፦ ለግብፅ የውጭ ምንዛሬ ዋነኛ የጀርባ አጥንት የሆነው የስዊዝ ካናል (Suez Canal)፣ ከንግድ ፍሰት መቆረጥ ጋር ተያይዞ ከፍተኛ የገቢ ቅናሽ ሊገጥመው እንደሚችል አል-ሲሲ አሳስበዋል።
* አጠቃላይ የኢኮኖሚ ጫና፦ የነዳጅ ዋጋ መጨመር በግብፅ የውስጥ ኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ ተጨማሪ ጫና በመፍጠር የዜጎችን የመግዛት አቅም ሊፈትን እንደሚችል ጠቁመዋል።
ፕሬዝዳንት አል-ሲሲ አክለውም፣ ግብፅ ከቀጠናዊና ከዓለም አቀፋዊ የደህንነት ስጋቶች ጋር ተያይዘው የሚመጡ ኢኮኖሚያዊ ትንኮሳዎችን በንቃት መከታተልና መመከት እንዳለባት ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
ይህ ማስጠንቀቂያ የመጣው በቀጠናው ያለው የጂኦ-ፖለቲካ ውጥረት በዓለም አቀፍ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ስጋት እየፈጠረ ባለበት ወቅት መሆኑ ጉዳዩን ይበልጥ አሳሳቢ ያደርገዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #egypt #suezcanal #straitofhormuz #alsisi #globaleconomy #energysecurity #ግብፅ #ኢኮኖሚ
Sponsored by
Surafel
Comments