20 hours ago
ከምርጫ በኋላ ምን ይከናወናል?
****************
1. የድምፅ ቆጠራ እና ማረጋገጥ
ከምርጫ ጣቢያዎች ጀምሮ የተሰጡ ድምፆችን በጥንቃቄ መቁጠር እና ማረጋገጥ።
2. ውጤትን ይፋ ማድረግ
ከምርጫ ጣቢያ ጀምሮ በየደረጃው ውጤት መግለጽ፣ በመጨረሻም በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በኩል የተረጋገጠውን አጠቃላይ ውጤት ለሕዝብ ይፋ ማድረግ።
3. የታዛቢዎች መግለጫ
የሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ የምርጫ ታዛቢዎች የሒደቱን አጠቃላይ ሁኔታ አስመልክቶ ሪፖርት (መግለጫ) ማቅረብ።
4. ቅሬታዎችን በሕግ መፍታት
ተፎካካሪ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች የሚያነሷቸውን አቤቶታዎች በሕገ-መንግሥታዊ መንገድ እና በሕግ አግባብ መፍትሔ መስጠት።
5. የአፈጻጸም ግምገማ
የምርጫ አስፈጻሚ አካላት በምርጫው የነበራቸውን አጠቃላይ ሒደት፣ ጥንካሬና ክፍተት መገምገም።
6. መንግሥት መመሥረት
የሕዝብን ውሳኔ (ድምፅ) መሠረት በማድረግ ሥልጣን ማስተላለፍ እና ወደ ተግባራዊ የመንግሥት ምሥረታ መቀየር።
Ethiopian Broadcasting Corporation #ምርጫ #ኢትዮጵያ
****************
1. የድምፅ ቆጠራ እና ማረጋገጥ
ከምርጫ ጣቢያዎች ጀምሮ የተሰጡ ድምፆችን በጥንቃቄ መቁጠር እና ማረጋገጥ።
2. ውጤትን ይፋ ማድረግ
ከምርጫ ጣቢያ ጀምሮ በየደረጃው ውጤት መግለጽ፣ በመጨረሻም በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በኩል የተረጋገጠውን አጠቃላይ ውጤት ለሕዝብ ይፋ ማድረግ።
3. የታዛቢዎች መግለጫ
የሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ የምርጫ ታዛቢዎች የሒደቱን አጠቃላይ ሁኔታ አስመልክቶ ሪፖርት (መግለጫ) ማቅረብ።
4. ቅሬታዎችን በሕግ መፍታት
ተፎካካሪ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች የሚያነሷቸውን አቤቶታዎች በሕገ-መንግሥታዊ መንገድ እና በሕግ አግባብ መፍትሔ መስጠት።
5. የአፈጻጸም ግምገማ
የምርጫ አስፈጻሚ አካላት በምርጫው የነበራቸውን አጠቃላይ ሒደት፣ ጥንካሬና ክፍተት መገምገም።
6. መንግሥት መመሥረት
የሕዝብን ውሳኔ (ድምፅ) መሠረት በማድረግ ሥልጣን ማስተላለፍ እና ወደ ተግባራዊ የመንግሥት ምሥረታ መቀየር።
Ethiopian Broadcasting Corporation #ምርጫ #ኢትዮጵያ
21 hours ago
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሀገር መፃኢ እድል እና ለዲሞክራሲ ግንባታ ያለው ፋይዳ የጎላ እንደሆነ መራጮች ገለጹ
*********************
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች ሰላማዊ በሆነ መልኩ የተሄደ ሲሆን የዜጎችን የፖለቲካ ንቃትና የዲሞክራሲ ፍላጎት በግልጽ ያሳየ ክስተት ነበር።
በምርጫው ሂደት ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ ዜጎች እንደገለጹት መምረጥ ማለት ተራ ተግባር ሳይሆን የሀገርን መፃኢ እድል የመወሰንና የዲሞክራሲ መሰረትን የማጠናከር ወሳኝ ሂደት ነው ብለዋል።
ዜጎች ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በነቂስ የወጡት ያለምንም አስገዳጅነትና በራሳቸው ተነሳሽነት መሆኑን ገልፀው ለዚህም ዋነኛው ምክንያት ይሆነኛል የሚሉትን እና ለሀገር እድገት ይሰራል የሚሉትን አካል በነፃነት ለመሰየም መምጣታቸውን ገልጸዋል።
ምርጫው ለሀገር ገንባታ ትልቅ መድረክ ነው የምርጫ ሂደት ኢትዮጵያ ወደተሻለ የዲሞክራሲ ምህዳር ለማሸጋገርና ለቀጣዩ ትውልድ የምትመች ሀገርን ለመገንባት የምታደርገውን ጉዞ የሚያፋጥን ነው ብለዋል።
ምርጫ ዜጎች በመረጡት መሪ የመተዳደር መብታቸውን በማስጠበቅ ለሀገራዊ አንድነትና ለዘላቂ ሰላም መሰረት ሆኖ ያገለግላል።
በቢታኒያ ሲሳይ
Ethiopian Broadcasting Corporation #ebc #ethiopia #election #democracy
*********************
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች ሰላማዊ በሆነ መልኩ የተሄደ ሲሆን የዜጎችን የፖለቲካ ንቃትና የዲሞክራሲ ፍላጎት በግልጽ ያሳየ ክስተት ነበር።
በምርጫው ሂደት ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ ዜጎች እንደገለጹት መምረጥ ማለት ተራ ተግባር ሳይሆን የሀገርን መፃኢ እድል የመወሰንና የዲሞክራሲ መሰረትን የማጠናከር ወሳኝ ሂደት ነው ብለዋል።
ዜጎች ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በነቂስ የወጡት ያለምንም አስገዳጅነትና በራሳቸው ተነሳሽነት መሆኑን ገልፀው ለዚህም ዋነኛው ምክንያት ይሆነኛል የሚሉትን እና ለሀገር እድገት ይሰራል የሚሉትን አካል በነፃነት ለመሰየም መምጣታቸውን ገልጸዋል።
ምርጫው ለሀገር ገንባታ ትልቅ መድረክ ነው የምርጫ ሂደት ኢትዮጵያ ወደተሻለ የዲሞክራሲ ምህዳር ለማሸጋገርና ለቀጣዩ ትውልድ የምትመች ሀገርን ለመገንባት የምታደርገውን ጉዞ የሚያፋጥን ነው ብለዋል።
ምርጫ ዜጎች በመረጡት መሪ የመተዳደር መብታቸውን በማስጠበቅ ለሀገራዊ አንድነትና ለዘላቂ ሰላም መሰረት ሆኖ ያገለግላል።
በቢታኒያ ሲሳይ
Ethiopian Broadcasting Corporation #ebc #ethiopia #election #democracy
1 day ago
Discover the enchanting charm of Hanoi with our exclusive 7-Nights/8-Days tour package starting at just USD 2639! Experience the perfect blend of rich traditions and stunning architecture in the historic Old Quarter. Don’t miss your chance to explore the heart of
Vietnam. Book your adventure today and let the magic of Hanoi inspire your soul!
https://www.ethiopianholid... #flyethiopian #ethiopianholidays
Vietnam. Book your adventure today and let the magic of Hanoi inspire your soul!
https://www.ethiopianholid... #flyethiopian #ethiopianholidays
1 day ago
“የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አፈፃፀምን አስመልክቶ የኢትዮጵያ ሕዝብ እና መንግሥት በራሳቸው ሊኮሩ ይገባል” - የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ
Ethiopian Broadcasting Corporation #dotstream
Ethiopian Broadcasting Corporation #dotstream
2 days ago
✨🏆 እንኳን ደስ አላችሁ፣ እንኳን ደስ አለን! 🎉 🎉
ኩባንያችን ኢትዮ ቴሌኮም በታዋቂው Brand Africa 16ኛው ዓመታዊ የብራንድ አፍሪካ 100 ሽልማት ላይ በሁለት ታላላቅ ዘርፎች አሸናፊ መሆኑን ስንገልጽ በታላቅ ኩራት ነው!
1️⃣ እጅግ ተወዳጅ የኢትዮጵያ ብራንድ
2️⃣ ለማኅበረሰቡና ለአካባቢ ጥበቃ በጎ አስተዋጽኦ በማድረግ እጅግ ተወዳጅ የኢትዮጵያ ብራንድ
ይህ ስኬት የእናንተ የደንበኞቻችን ዘላቂ እምነት፣ የአጋሮቻችንና የሠራተኞቻችን የሥራ ውጤት በመሆኑ ሁልጊዜም ከልብ እናመሰግናለን!
Congratulations to you, and congratulations to us all!
We are thrilled and deeply honored to announce that Ethio telecom has emerged victorious in two major categories at the prestigious 16th Annual Brand Africa 100.
1️⃣ Most Admired Ethiopian Brand in Telecommunications
2️⃣ Most Admired Ethiopian Brand Doing Good for Society and the Environment
This milestone is a testament to your unwavering trust as our valued customers and the dedication of our partners and employees.
Thank you for walking this journey with us!
#ethiotelecom #brandafrica100 #mostadmiredbrand
ኩባንያችን ኢትዮ ቴሌኮም በታዋቂው Brand Africa 16ኛው ዓመታዊ የብራንድ አፍሪካ 100 ሽልማት ላይ በሁለት ታላላቅ ዘርፎች አሸናፊ መሆኑን ስንገልጽ በታላቅ ኩራት ነው!
1️⃣ እጅግ ተወዳጅ የኢትዮጵያ ብራንድ
2️⃣ ለማኅበረሰቡና ለአካባቢ ጥበቃ በጎ አስተዋጽኦ በማድረግ እጅግ ተወዳጅ የኢትዮጵያ ብራንድ
ይህ ስኬት የእናንተ የደንበኞቻችን ዘላቂ እምነት፣ የአጋሮቻችንና የሠራተኞቻችን የሥራ ውጤት በመሆኑ ሁልጊዜም ከልብ እናመሰግናለን!
Congratulations to you, and congratulations to us all!
We are thrilled and deeply honored to announce that Ethio telecom has emerged victorious in two major categories at the prestigious 16th Annual Brand Africa 100.
1️⃣ Most Admired Ethiopian Brand in Telecommunications
2️⃣ Most Admired Ethiopian Brand Doing Good for Society and the Environment
This milestone is a testament to your unwavering trust as our valued customers and the dedication of our partners and employees.
Thank you for walking this journey with us!
#ethiotelecom #brandafrica100 #mostadmiredbrand
2 days ago
✨🏆 እንኳን ደስ አላችሁ፣ እንኳን ደስ አለን! 🎉 🎉
ኩባንያችን ኢትዮ ቴሌኮም በታዋቂው Brand Africa 16ኛው ዓመታዊ የብራንድ አፍሪካ 100 ሽልማት ላይ በሁለት ታላላቅ ዘርፎች አሸናፊ መሆኑን ስንገልጽ በታላቅ ኩራት ነው!
1️⃣ እጅግ ተወዳጅ የኢትዮጵያ ብራንድ
2️⃣ ለማኅበረሰቡና ለአካባቢ ጥበቃ በጎ አስተዋጽኦ በማድረግ እጅግ ተወዳጅ የኢትዮጵያ ብራንድ
ይህ ስኬት የእናንተ የደንበኞቻችን ዘላቂ እምነት፣ የአጋሮቻችንና የሠራተኞቻችን የሥራ ውጤት በመሆኑ ሁልጊዜም ከልብ እናመሰግናለን!
Congratulations to you, and congratulations to us all!
We are thrilled and deeply honored to announce that Ethio telecom has emerged victorious in two major categories at the prestigious 16th Annual Brand Africa 100.
1️⃣ Most Admired Ethiopian Brand in Telecommunications
2️⃣ Most Admired Ethiopian Brand Doing Good for Society and the Environment
This milestone is a testament to your unwavering trust as our valued customers and the dedication of our partners and employees.
Thank you for walking this journey with us!
#ethiotelecom #brandafrica100 #mostadmiredbrand
ኩባንያችን ኢትዮ ቴሌኮም በታዋቂው Brand Africa 16ኛው ዓመታዊ የብራንድ አፍሪካ 100 ሽልማት ላይ በሁለት ታላላቅ ዘርፎች አሸናፊ መሆኑን ስንገልጽ በታላቅ ኩራት ነው!
1️⃣ እጅግ ተወዳጅ የኢትዮጵያ ብራንድ
2️⃣ ለማኅበረሰቡና ለአካባቢ ጥበቃ በጎ አስተዋጽኦ በማድረግ እጅግ ተወዳጅ የኢትዮጵያ ብራንድ
ይህ ስኬት የእናንተ የደንበኞቻችን ዘላቂ እምነት፣ የአጋሮቻችንና የሠራተኞቻችን የሥራ ውጤት በመሆኑ ሁልጊዜም ከልብ እናመሰግናለን!
Congratulations to you, and congratulations to us all!
We are thrilled and deeply honored to announce that Ethio telecom has emerged victorious in two major categories at the prestigious 16th Annual Brand Africa 100.
1️⃣ Most Admired Ethiopian Brand in Telecommunications
2️⃣ Most Admired Ethiopian Brand Doing Good for Society and the Environment
This milestone is a testament to your unwavering trust as our valued customers and the dedication of our partners and employees.
Thank you for walking this journey with us!
#ethiotelecom #brandafrica100 #mostadmiredbrand
2 days ago
ቴክቦል (Teqball)፦ ተወዳጅነትን እያገኘ የመጣው አዲሱ የኳስ ስፖርት
*****************
ቴክቦል የእግር ኳስ ክህሎትን ከጠረጴዛ ቴኒስ ሕግጋት ጋር አጣምሮ የያዘ፣ ኳሱ በእጅ ሳይነካ በታጠፈ ጠረጴዛ ላይ የሚጫወቱት አስደሳች ስፖርት ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በመላው ዓለም ተወዳጅነትን እያገኘ የመጣ የስፖርት አይነት ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት በይፋ ያስመረቁት ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ያለው የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ይህንን የስፖርት ዓይነት ያካተተ ነው።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ይህ ስፖርት ለመጀመሪያ ጊዜ እ.አ.አ በ2012 በሃንጋሪ የተዋወቀ የስፖርት አይነት ሲሆን፣ ጋቦር ቦርሳኒ፣ ቪክቶር ሁሳር እና ጂዮርጂ ጋትያን በተባሉ ሦስት ግለሰቦች አማካኝነት እንደተጀመረ ይገለፃል።
የቴክቦል ዋነኛው መለያ ባህሪ "ቴክቦርድ" (Teqboard) ተብሎ የሚጠራውና መሃሉ ከፍ ብሎ ጫፎቹ ወደ ታች የታጠፈ ልዩ ጠረጴዛ መሆኑ ነው። ይህ የጠረጴዛው ቅርጽ ኳሱ በየትኛውም አቅጣጫ እንዲነጥርና ጨዋታው ፍጥነትና ከፍተኛ ክህሎት እንዲኖረው ያደርጋል።
የስፖርቱ ሕጎች በጣም ቀላልና ለማንም ሰው ለመረዳት ምቹ ሲሆኑ፣ በሁለት ተቃራኒ ተጫዋቾች (አንድ ለአንድ) ወይም በቡድን (ሁለት ለሁለት) ሊጫወቱት የሚችሉት ስፖርት ነው።
ልክ እንደ እግር ኳስ ሁሉ፣ ኳሱን በእጅ መንካት በጥብቅ የተከለከለ ሲሆን፤ ተጫዋቾች ኳሱን በጭንቅላታቸው፣ በደረታቸው፣ በትከሻቸው ወይም በእግራቸው መምታት ይችላሉ።
አንድ ተጫዋች ወይም ቡድን ኳሱ ወደ ተቃራኒው ወገን ከመሻገሩ በፊት ቢበዛ ሦስት ጊዜ ብቻ የመንካት መብት አለው።
በአንድ የሰውነት ክፍል (በእግር ብቻ፣ በደረት ብቻ አልያም በጭንቅላት ብቻ) በተከታታይ ሁለትጊዜ ኳሱን መንካት አይፈቀድም። ይህም ተጫዋቾች የተለያዩ የሰውነት ክፍሎቻቸውን እንዲጠቀሙና የተለየ ብቃት እንዲያሳዩ ያስገድዳቸዋል።
በአሁኑ ወቅት ቴክቦል በዓለም አቀፍ ደረጃ በፌዴሬሽን የሚመራ ሲሆን፣ ወደ ኦሎምፒክ ስፖርቶች እንዲካተትም ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል። እንደ ሮናልዲንሆ ያሉ ታዋቂ የዓለም እግር ኳስ ተጫዋቾች የስፖርቱ አምባሳደር በመሆን እያስተዋወቁት ይገኛሉ።
ስፖርቱ ምንም ዓይነት የአካል ንክኪ ስለሌለውና በትንሽ ቦታ ላይ ሊከናወን ስለሚችል ጉዳትን የሚቀንስ ከመሆኑም በላይ ለተጫዋቾች ትኩረትን፣ ቅልጥፍናን እና የኳስ ቁጥጥርን ለማሻሻል ትልቅ አስተዋጽኦ አለው።
በተጨማሪም የልብ ጤናን የሚያሻሽል፣ አእምሮን የሚያነቃቃ እንዲሁም የአይን፣ የእግር እና የአእምሮ ቅንጅትን በማሳደግ ፈጣን ውሳኔ የመስጠት ብቃትን የሚያዳብር ስፖርት ነው፤ ዕድሜና ጾታ ሳይለይ ሁሉም ሰው ሊጫወተው ስለሚችል፣ የአእምሮ ውጥረትን ለመቀነስና ማኅበራዊ ግንኙነትን ለማጠናከር ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው።
በዘረንቶስ ሰለሞን
Ethiopian Broadcasting Corporation #teqboard #teqball
*****************
ቴክቦል የእግር ኳስ ክህሎትን ከጠረጴዛ ቴኒስ ሕግጋት ጋር አጣምሮ የያዘ፣ ኳሱ በእጅ ሳይነካ በታጠፈ ጠረጴዛ ላይ የሚጫወቱት አስደሳች ስፖርት ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በመላው ዓለም ተወዳጅነትን እያገኘ የመጣ የስፖርት አይነት ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት በይፋ ያስመረቁት ከእንጦጦ እስከ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ያለው የመልሶ ማልማት እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ይህንን የስፖርት ዓይነት ያካተተ ነው።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ይህ ስፖርት ለመጀመሪያ ጊዜ እ.አ.አ በ2012 በሃንጋሪ የተዋወቀ የስፖርት አይነት ሲሆን፣ ጋቦር ቦርሳኒ፣ ቪክቶር ሁሳር እና ጂዮርጂ ጋትያን በተባሉ ሦስት ግለሰቦች አማካኝነት እንደተጀመረ ይገለፃል።
የቴክቦል ዋነኛው መለያ ባህሪ "ቴክቦርድ" (Teqboard) ተብሎ የሚጠራውና መሃሉ ከፍ ብሎ ጫፎቹ ወደ ታች የታጠፈ ልዩ ጠረጴዛ መሆኑ ነው። ይህ የጠረጴዛው ቅርጽ ኳሱ በየትኛውም አቅጣጫ እንዲነጥርና ጨዋታው ፍጥነትና ከፍተኛ ክህሎት እንዲኖረው ያደርጋል።
የስፖርቱ ሕጎች በጣም ቀላልና ለማንም ሰው ለመረዳት ምቹ ሲሆኑ፣ በሁለት ተቃራኒ ተጫዋቾች (አንድ ለአንድ) ወይም በቡድን (ሁለት ለሁለት) ሊጫወቱት የሚችሉት ስፖርት ነው።
ልክ እንደ እግር ኳስ ሁሉ፣ ኳሱን በእጅ መንካት በጥብቅ የተከለከለ ሲሆን፤ ተጫዋቾች ኳሱን በጭንቅላታቸው፣ በደረታቸው፣ በትከሻቸው ወይም በእግራቸው መምታት ይችላሉ።
አንድ ተጫዋች ወይም ቡድን ኳሱ ወደ ተቃራኒው ወገን ከመሻገሩ በፊት ቢበዛ ሦስት ጊዜ ብቻ የመንካት መብት አለው።
በአንድ የሰውነት ክፍል (በእግር ብቻ፣ በደረት ብቻ አልያም በጭንቅላት ብቻ) በተከታታይ ሁለትጊዜ ኳሱን መንካት አይፈቀድም። ይህም ተጫዋቾች የተለያዩ የሰውነት ክፍሎቻቸውን እንዲጠቀሙና የተለየ ብቃት እንዲያሳዩ ያስገድዳቸዋል።
በአሁኑ ወቅት ቴክቦል በዓለም አቀፍ ደረጃ በፌዴሬሽን የሚመራ ሲሆን፣ ወደ ኦሎምፒክ ስፖርቶች እንዲካተትም ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል። እንደ ሮናልዲንሆ ያሉ ታዋቂ የዓለም እግር ኳስ ተጫዋቾች የስፖርቱ አምባሳደር በመሆን እያስተዋወቁት ይገኛሉ።
ስፖርቱ ምንም ዓይነት የአካል ንክኪ ስለሌለውና በትንሽ ቦታ ላይ ሊከናወን ስለሚችል ጉዳትን የሚቀንስ ከመሆኑም በላይ ለተጫዋቾች ትኩረትን፣ ቅልጥፍናን እና የኳስ ቁጥጥርን ለማሻሻል ትልቅ አስተዋጽኦ አለው።
በተጨማሪም የልብ ጤናን የሚያሻሽል፣ አእምሮን የሚያነቃቃ እንዲሁም የአይን፣ የእግር እና የአእምሮ ቅንጅትን በማሳደግ ፈጣን ውሳኔ የመስጠት ብቃትን የሚያዳብር ስፖርት ነው፤ ዕድሜና ጾታ ሳይለይ ሁሉም ሰው ሊጫወተው ስለሚችል፣ የአእምሮ ውጥረትን ለመቀነስና ማኅበራዊ ግንኙነትን ለማጠናከር ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው።
በዘረንቶስ ሰለሞን
Ethiopian Broadcasting Corporation #teqboard #teqball
2 days ago
Experience the wonders of Istanbul with our exclusive 8-night,9-day package starting at USD 2,915! From breathtaking landscapes to rich history, your adventure awaits. Click the link below for more details! #flyethiopian #istanbul
https://www.ethiopianholid...
https://www.ethiopianholid...
2 days ago
Experience the wonders of Istanbul with our exclusive 8-night,9-day package starting at USD 2,915! From breathtaking landscapes to rich history, your adventure awaits. Click the link below for more details! #flyethiopian #istanbul
https://www.ethiopianholid...
https://www.ethiopianholid...
2 days ago
Experience the wonders of Istanbul with our exclusive 8-night,9-day package starting at USD 2,915! From breathtaking landscapes to rich history, your adventure awaits. Click the link below for more details! #flyethiopian #istanbul
https://www.ethiopianholid...
https://www.ethiopianholid...
Sponsored by
Surafel
3 days ago
Mauritius is joining the vast Ethiopian network! We are excited to announce that starting from July 12, 2026, Ethiopian will commence a thrice weekly passenger service to Port Louis. Book your flight today and be part of the journey to the bustling capital of Mauritius. #flyethiopian #mauritius
3 days ago
አስከሬን በቤት አስቀምጠው ለምርጫ የወጡት የቤተሰብ አባላት - የላቀ የዜግነት ቁርጠኝነት ተምሳሌት!
*************
በሰሜን ሽዋ ዞን ሲያደብርና ዋዩ ወረዳ፣ አባያ ቀበሌ (ሳክላ ምርጫ ጣቢያ) እጅግ ልብ የሚነካ እና ታላቅ የዜግነት ኃላፊነት የታየበት ክሥተት ተመዝግቧል።
ልጃቸው በሞት የተለየባቸው ቤተሰቦች፣ አስከሬን በቤት አስቀምጠው 7 የቤተሰቡ አባላት በማለዳ ወደ ምርጫ ጣቢያ አምርተዋል። በቦታው የነበረው ማኅበረሰብም ለኀዘናቸው ጥልቅ ክብር በመስጠት፤ ሰልፍ ሳይጠብቁ ቅድሚያ ሰጥተዋቸው ድምፃቸውን ከሰጡ በኋላ ወደ ልቅሶ ቤታቸው ተመልሰዋል።
ይህ ተግባር ሕዝባችን በምርጫው ሂደት ላይ ያለውን ጽኑ እምነት እና ለሀገሩ ያለውን የላቀ ክብር በተግባር ያረጋገጠበት ህያው ምስክር ነው ሲሉ አስተያየታቸውን የሰጡት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ናቸው።
Ethiopian Broadcasting Corporation #ምርጫ #አማራ #ክልል
*************
በሰሜን ሽዋ ዞን ሲያደብርና ዋዩ ወረዳ፣ አባያ ቀበሌ (ሳክላ ምርጫ ጣቢያ) እጅግ ልብ የሚነካ እና ታላቅ የዜግነት ኃላፊነት የታየበት ክሥተት ተመዝግቧል።
ልጃቸው በሞት የተለየባቸው ቤተሰቦች፣ አስከሬን በቤት አስቀምጠው 7 የቤተሰቡ አባላት በማለዳ ወደ ምርጫ ጣቢያ አምርተዋል። በቦታው የነበረው ማኅበረሰብም ለኀዘናቸው ጥልቅ ክብር በመስጠት፤ ሰልፍ ሳይጠብቁ ቅድሚያ ሰጥተዋቸው ድምፃቸውን ከሰጡ በኋላ ወደ ልቅሶ ቤታቸው ተመልሰዋል።
ይህ ተግባር ሕዝባችን በምርጫው ሂደት ላይ ያለውን ጽኑ እምነት እና ለሀገሩ ያለውን የላቀ ክብር በተግባር ያረጋገጠበት ህያው ምስክር ነው ሲሉ አስተያየታቸውን የሰጡት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ናቸው።
Ethiopian Broadcasting Corporation #ምርጫ #አማራ #ክልል
4 days ago
ራይድ ትራንስፖርት ተሸለመ
RIDE በAfrica's Best Brands Award ላይ Most Admired Ethiopian Brand በመሆን ለከፍተኛ ሽልማት በቅቷል::
በአዲስ አበባ United Nations Economic Commission for Africa (ECA) በተደረገው የሽልማት ስነ-ስርዓት ላይ ድርጅታችን ይህንን ታላቅ ክብርና ሽልማት በማግኘቱ የተሰማን ደስታ እየገለፅን ÷ በመላው የራይድ ቤተሰብ ስም ለማመስገን እንወዳለን::
ድርጅታችን በ2006 ዓ.ም RIDE የተሰኘውን የንግድ ስም እና ምልክት በኢትዮዽያ አዕምሮ ንብረት ጥበቃ በማስመዝገብ በኢትዮዽያ የመጀመርያውን የኤሌክትሮኒክ ታክሲ አገልግሎት ዘርፍ ፈር - ቀዳጅ ሲሆን በአሁን ወቅት በስፋት አገልግሎቱን እያቀረበ ይገኛል:: በተጨማሪም በFood Delivery እና ተዛማች አገልግሎቶች ላይ በመሪነት እያገለገለ ይገኛል::
ይህንን ትልቅ ብራንድ ስንገነባ በነበረው ሂደት ከጎናችን ለነበራችሁ አሽከርካሪዎች ÷ ደንበኞቻችን እና መላው የራይድ ቤተሰቦች በቀጣይም ከኢትዮዽያ አልፎ በአፍሪካ በምናደርገው ጉዞ አብረውን በዘላቂነት እንደሚወዳጁን እንተማመናለን::
ከRIDE ጋር ወደፊት💛!
RIDE በAfrica's Best Brands Award ላይ Most Admired Ethiopian Brand በመሆን ለከፍተኛ ሽልማት በቅቷል::
በአዲስ አበባ United Nations Economic Commission for Africa (ECA) በተደረገው የሽልማት ስነ-ስርዓት ላይ ድርጅታችን ይህንን ታላቅ ክብርና ሽልማት በማግኘቱ የተሰማን ደስታ እየገለፅን ÷ በመላው የራይድ ቤተሰብ ስም ለማመስገን እንወዳለን::
ድርጅታችን በ2006 ዓ.ም RIDE የተሰኘውን የንግድ ስም እና ምልክት በኢትዮዽያ አዕምሮ ንብረት ጥበቃ በማስመዝገብ በኢትዮዽያ የመጀመርያውን የኤሌክትሮኒክ ታክሲ አገልግሎት ዘርፍ ፈር - ቀዳጅ ሲሆን በአሁን ወቅት በስፋት አገልግሎቱን እያቀረበ ይገኛል:: በተጨማሪም በFood Delivery እና ተዛማች አገልግሎቶች ላይ በመሪነት እያገለገለ ይገኛል::
ይህንን ትልቅ ብራንድ ስንገነባ በነበረው ሂደት ከጎናችን ለነበራችሁ አሽከርካሪዎች ÷ ደንበኞቻችን እና መላው የራይድ ቤተሰቦች በቀጣይም ከኢትዮዽያ አልፎ በአፍሪካ በምናደርገው ጉዞ አብረውን በዘላቂነት እንደሚወዳጁን እንተማመናለን::
ከRIDE ጋር ወደፊት💛!
Sponsored by
Surafel
5 days ago
የ54 ሚሊዮን ዜጎች ድምጽ፤ የኢትዮጵያ ፖለቲካ አዲሱ አቅጣጫ
*******************
(የዕለቱ መልዕክት)
ለዘመናት የኢትዮጵያ ፖለቲካ በጥርጣሬ ዉስጥ መኖሩ የአደባባይ ምስጢር ነው። ዛሬ ግን ያ የድሮው መንገድ አክትሞለታል። የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዋዜማ አዲስ ተስፋ ይዞልን መጥቷል፤ ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች የተመዘገቡበት፣ በተለይ ደግሞ ከእነዚህም ዉስጥ ከ5.5 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ደግሞ በ“ምርጫዬ” ዲጂታል መድረክ ስማቸውን ያሰፈሩበት ይህ ሂደት፣ ሀገራችን ከጎዳና ጫጫታ ወደ ውይይት መድረክ፣ ከስሜት ወደ ዴሞክራሲያዊ ፉክክር መሸጋገሯን በግልጽ ያሳያል።
በዚህ ምርጫ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ከ10 ሺህ በላይ እጩዎችና 80 የግል ተወዳዳሪዎች በአንድ የህግ ጥላ ስር ቆመው፣ በምርጫ ስነ-ምግባር ሕግ ተሳስረው ለመወዳደር መዘጋጀታቸው የአዲሲቷ ኢትዮጵያ መለያ ነው።
ይህ ምርጫ የአንድ ቀን የድምፅ መስጠት ተግባር ብቻ አይደለም፤ ይልቁንም የዴሞክራሲ ትርጉም ከፖለቲካ ልሂቃን ጠባብ አዳራሾች ወጥቶ ወደ ህዝብ ልብና ህሊና እየገባ መሆኑን የሚያበስር ብሔራዊ ንቅናቄ ነው።
ውድድሩ ከብሽሽቅ ወደ ፖሊሲ ክርክር አድጓል። በርካታ የሕዝብ ውይይት መድረኮች በአምስት የሀገር ውስጥ ቋንቋዎች ተዘጋጅተው መቅረባቸው አካታችነትን በተግባር ያሳየ፣ የተፎካካሪና የገዢ ፓርቲዎችን እኩልነት በገሃድ ያረጋገጠ፤ የተቋማዊ ብስለት የታየበት እርምጃ ነው።
ዓለም አቀፍ እና የሀገር ውስጥ ታዛቢዎችን በኩራት ጋብዞ፣ የአፍሪካ ህብረትንና የኢጋድን ታዛቢዎችን በማሳተፍ አፍሪካ የራሷን ጉዳዮች በራስ አቅም የመመልከት አቅሟን ያሳየችበት እንዲሁም በሰላማዊ መንገድ ምርጫን ለማካሄድ መነሳት ራሱ ትልቅ ታሪካዊ ድል ነው። እንደ ኡሁሩ ኬንያታ ያሉ የአህጉሪቱ አንጋፋ መሪዎች የታዛቢ ቡድኖችን ይዘው መግባታቸው የኢትዮጵያን የዲሞክራሲ ጥረት በአፍሪካ መድረክ ከፍ አድርጎታል።
መልዕክቱ ግልጽ ነው፤ ፖለቲካ በሀይል ሳይሆን በህዝብ ድምፅ፣ በስሜት ሳይሆን በውይይት፣ በመገለል ሳይሆን በብሔራዊ ተሳትፎ ሊመራ እንደሚችል በተግባር እያሳየን ነው።
የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ትልቁ ድል የትኛው ፓርቲ አሸነፈ የሚለው ሳይሆን የኢትዮጵያ ህዝብና ተቋማት በዴሞክራሲያዊ ብስለት ማሸነፋቸው ነው።
ይህ የዲጂታል ዘመን ትውልድ የሀገሩን እጣ ፈንታ በራሱ እጅ እየጻፈ ነው። የነገዋን የበለፀገችና የተረጋጋች ኢትዮጵያን ለመገንባት ሁላችንም በሰላም፣ በህግና በውይይት መስመር ላይ እናጽና፤ ምክንያቱም የነጻነትና የፍትህ መሠረቱ የህዝብ ድምፅ ብቻ ነውና።
ኢትዮጵያ ትመርጣለች!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #ethiopiavotes #democracy #ethiopia
*******************
(የዕለቱ መልዕክት)
ለዘመናት የኢትዮጵያ ፖለቲካ በጥርጣሬ ዉስጥ መኖሩ የአደባባይ ምስጢር ነው። ዛሬ ግን ያ የድሮው መንገድ አክትሞለታል። የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዋዜማ አዲስ ተስፋ ይዞልን መጥቷል፤ ከ54 ሚሊዮን በላይ መራጮች የተመዘገቡበት፣ በተለይ ደግሞ ከእነዚህም ዉስጥ ከ5.5 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ደግሞ በ“ምርጫዬ” ዲጂታል መድረክ ስማቸውን ያሰፈሩበት ይህ ሂደት፣ ሀገራችን ከጎዳና ጫጫታ ወደ ውይይት መድረክ፣ ከስሜት ወደ ዴሞክራሲያዊ ፉክክር መሸጋገሯን በግልጽ ያሳያል።
በዚህ ምርጫ 42 የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ከ10 ሺህ በላይ እጩዎችና 80 የግል ተወዳዳሪዎች በአንድ የህግ ጥላ ስር ቆመው፣ በምርጫ ስነ-ምግባር ሕግ ተሳስረው ለመወዳደር መዘጋጀታቸው የአዲሲቷ ኢትዮጵያ መለያ ነው።
ይህ ምርጫ የአንድ ቀን የድምፅ መስጠት ተግባር ብቻ አይደለም፤ ይልቁንም የዴሞክራሲ ትርጉም ከፖለቲካ ልሂቃን ጠባብ አዳራሾች ወጥቶ ወደ ህዝብ ልብና ህሊና እየገባ መሆኑን የሚያበስር ብሔራዊ ንቅናቄ ነው።
ውድድሩ ከብሽሽቅ ወደ ፖሊሲ ክርክር አድጓል። በርካታ የሕዝብ ውይይት መድረኮች በአምስት የሀገር ውስጥ ቋንቋዎች ተዘጋጅተው መቅረባቸው አካታችነትን በተግባር ያሳየ፣ የተፎካካሪና የገዢ ፓርቲዎችን እኩልነት በገሃድ ያረጋገጠ፤ የተቋማዊ ብስለት የታየበት እርምጃ ነው።
ዓለም አቀፍ እና የሀገር ውስጥ ታዛቢዎችን በኩራት ጋብዞ፣ የአፍሪካ ህብረትንና የኢጋድን ታዛቢዎችን በማሳተፍ አፍሪካ የራሷን ጉዳዮች በራስ አቅም የመመልከት አቅሟን ያሳየችበት እንዲሁም በሰላማዊ መንገድ ምርጫን ለማካሄድ መነሳት ራሱ ትልቅ ታሪካዊ ድል ነው። እንደ ኡሁሩ ኬንያታ ያሉ የአህጉሪቱ አንጋፋ መሪዎች የታዛቢ ቡድኖችን ይዘው መግባታቸው የኢትዮጵያን የዲሞክራሲ ጥረት በአፍሪካ መድረክ ከፍ አድርጎታል።
መልዕክቱ ግልጽ ነው፤ ፖለቲካ በሀይል ሳይሆን በህዝብ ድምፅ፣ በስሜት ሳይሆን በውይይት፣ በመገለል ሳይሆን በብሔራዊ ተሳትፎ ሊመራ እንደሚችል በተግባር እያሳየን ነው።
የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ትልቁ ድል የትኛው ፓርቲ አሸነፈ የሚለው ሳይሆን የኢትዮጵያ ህዝብና ተቋማት በዴሞክራሲያዊ ብስለት ማሸነፋቸው ነው።
ይህ የዲጂታል ዘመን ትውልድ የሀገሩን እጣ ፈንታ በራሱ እጅ እየጻፈ ነው። የነገዋን የበለፀገችና የተረጋጋች ኢትዮጵያን ለመገንባት ሁላችንም በሰላም፣ በህግና በውይይት መስመር ላይ እናጽና፤ ምክንያቱም የነጻነትና የፍትህ መሠረቱ የህዝብ ድምፅ ብቻ ነውና።
ኢትዮጵያ ትመርጣለች!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #ethiopiavotes #democracy #ethiopia
5 days ago
ነገ ኢትዮጵያ ትመርጣለች
ታሪካዊውን 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለማከናወን የመጨረሻው ቀን ላይ እንገኛለን
ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመላው አገሪቱ ይከናወናል
በዚህ ታሪካዊ ቀን ድምፅዎን ሰጥተው ኃላፊነትዎን ለመወጣት እና አሻራዎን ለማሳረፍ ዝግጁ ነዎት?
ነገ በጠዋት ወጥተን በተመዘገብንበት ምርጫ ጣቢያ ድምፅ እንሰጣለን።
Ethiopian Broadcasting Corporation #ኢትዮጵያ #ምርጫ #ebc #democracy #በምርጫብቻn #ኢትዮጵያ #ምርጫ #ebc #democracy #በምርጫብቻ
ታሪካዊውን 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለማከናወን የመጨረሻው ቀን ላይ እንገኛለን
ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመላው አገሪቱ ይከናወናል
በዚህ ታሪካዊ ቀን ድምፅዎን ሰጥተው ኃላፊነትዎን ለመወጣት እና አሻራዎን ለማሳረፍ ዝግጁ ነዎት?
ነገ በጠዋት ወጥተን በተመዘገብንበት ምርጫ ጣቢያ ድምፅ እንሰጣለን።
Ethiopian Broadcasting Corporation #ኢትዮጵያ #ምርጫ #ebc #democracy #በምርጫብቻn #ኢትዮጵያ #ምርጫ #ebc #democracy #በምርጫብቻ
5 days ago
Enjoy your meal at Ethiopian Skylight Hotel and EarnMiles.
Present your ShebaMiles card or your ShebaMiles numberto get Miles.
Present your ShebaMiles card or your ShebaMiles numberto get Miles.
8 days ago
Ethiopian Airlines domestic destination is further expanding! Today, we proudly inaugurated Negele Borena Geda Airport and commenced a new passenger service in a grand ceremony attended by the Prime Minister of the Federal Democratic Republic of Ethiopia His Excellency Dr. Abiy Ahmed, the President of the Oromia Regional State His Excellency Shimelis Abdisa, Ethiopian Airlines Group CEO Mr. Mesfin Tasew, high level government officials, the airlines’ executives, local community representatives, and various stakeholders.
The ceremony unveiled a new airport and marked the beginning of a new thrice weekly service to Negele Borena, growing the airlines’ domestic destination to 24. #ethiopianairlines
The ceremony unveiled a new airport and marked the beginning of a new thrice weekly service to Negele Borena, growing the airlines’ domestic destination to 24. #ethiopianairlines
8 days ago
9 days ago
ለኢትዮጵያችን የዴሞክራሲ ጉዞ አንድ ወሳኝ ምዕራፍ ሊከፈት... 5 ቀናት ብቻ ቀሩት
ዛሬ ግንቦት 19 ነው
ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመላው አገሪቱ በይፋ ይካሄዳል።
የእርስዎ አንድ ድምፅ የአገርን አቅጣጫ የመወሰን ትልቅ አቅም አለው።
በዚህ ታሪካዊ ቀን ድምፅዎን ሰጥተው ኃላፊነትዎን ለመወጣት እና አሻራዎን ለማሳረፍ ዝግጁ ነዎት?
Ethiopian Broadcasting Corporation #ኢትዮጵያ #ምርጫ #ebc #democracy #በምርጫብቻ
ዛሬ ግንቦት 19 ነው
ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በመላው አገሪቱ በይፋ ይካሄዳል።
የእርስዎ አንድ ድምፅ የአገርን አቅጣጫ የመወሰን ትልቅ አቅም አለው።
በዚህ ታሪካዊ ቀን ድምፅዎን ሰጥተው ኃላፊነትዎን ለመወጣት እና አሻራዎን ለማሳረፍ ዝግጁ ነዎት?
Ethiopian Broadcasting Corporation #ኢትዮጵያ #ምርጫ #ebc #democracy #በምርጫብቻ
Sponsored by
Surafel
9 days ago
የመደመር አንቀጽ
ትዕይንታዊ ሀብቶቻችንም ለብዙ ዘመናት ባህላዊና ሃይማኖታዊ በሆነ መንገድ ሲከወኑ የኖሩ የኢትዮጵያ የቱሪስት መስሕቦች ናቸው። የሕዝቦችን ትውውቅና ትሥሥር ለሚያሳድጉ፣ ባህልንና ቅርስን ለመጠበቅ የሚረዱ እንደ የዘመን መለወጫዎች፤ የጥምቀት፣ የኢሬቻ፥ የአረፋ፤ የአዊ የፈረሰኞች ትርዒት፣ ዓይነቶቹን የያዘ ነው። ከኪነ ጥበባዊ ቅርሶችም አኳያ ሀገራችን የሙዚቃ፣ የሥዕል፣ የቅርጻ ቅርጽ፣ ሀብታም ናት።
ኢትዮጵያ ከዋሻ ላይ ሥዕሎች ጀምሮ እስከ ዘመናዊ ሥዕሎች ድረስ ከ5ሺ ዘመን የበለጠ የሥነ ሥዕል ታሪክ አላት። የተቀመረና በኖታ የተገለጠ ዜማ በማዘጋጀት ከዓለም ቀደምቶቹ ተራ የሚያሰልፋት የቅዱስ ያሬድ ዜማ ባለቤት ናት።
በየብሔረሰቡ ዘንድ ልዩ ልዩ የጭፈራ፣ የዜማ ስልትና የሙዚቃ መሣሪያዎች ይገኛሉ። ኢትዮጵያ በየአርኬዎሎጂው ቦታ ከተገኙት ቅርጻ ቅርጾች አንሥቶ በየብሔረሰቡ እስካሎት የቅርጽ ጥበቦች የተሞላች ናት።
የመደመር መንግስት
ገጽ 263
Ethiopian Broadcasting Corporation #medemer #ethiopia #አረፋ #መደመር #ኢትዮጵያ
ትዕይንታዊ ሀብቶቻችንም ለብዙ ዘመናት ባህላዊና ሃይማኖታዊ በሆነ መንገድ ሲከወኑ የኖሩ የኢትዮጵያ የቱሪስት መስሕቦች ናቸው። የሕዝቦችን ትውውቅና ትሥሥር ለሚያሳድጉ፣ ባህልንና ቅርስን ለመጠበቅ የሚረዱ እንደ የዘመን መለወጫዎች፤ የጥምቀት፣ የኢሬቻ፥ የአረፋ፤ የአዊ የፈረሰኞች ትርዒት፣ ዓይነቶቹን የያዘ ነው። ከኪነ ጥበባዊ ቅርሶችም አኳያ ሀገራችን የሙዚቃ፣ የሥዕል፣ የቅርጻ ቅርጽ፣ ሀብታም ናት።
ኢትዮጵያ ከዋሻ ላይ ሥዕሎች ጀምሮ እስከ ዘመናዊ ሥዕሎች ድረስ ከ5ሺ ዘመን የበለጠ የሥነ ሥዕል ታሪክ አላት። የተቀመረና በኖታ የተገለጠ ዜማ በማዘጋጀት ከዓለም ቀደምቶቹ ተራ የሚያሰልፋት የቅዱስ ያሬድ ዜማ ባለቤት ናት።
በየብሔረሰቡ ዘንድ ልዩ ልዩ የጭፈራ፣ የዜማ ስልትና የሙዚቃ መሣሪያዎች ይገኛሉ። ኢትዮጵያ በየአርኬዎሎጂው ቦታ ከተገኙት ቅርጻ ቅርጾች አንሥቶ በየብሔረሰቡ እስካሎት የቅርጽ ጥበቦች የተሞላች ናት።
የመደመር መንግስት
ገጽ 263
Ethiopian Broadcasting Corporation #medemer #ethiopia #አረፋ #መደመር #ኢትዮጵያ
9 days ago
Ethiopian Airlines is proud to be part of one of the leading global trade fairs in the travel, tourism, and hospitality industry, ITB China. From highlighting our rich cultural heritage and exceptional tourism attractions to building meaningful connections with global partners, it was truly an inspiring experience.
#flyethiopian #itbchina #visitethiopia #landoforigins
#flyethiopian #itbchina #visitethiopia #landoforigins
10 days ago
የመደመር አንቀጽ
የመደመር ዕሳቤ ደግሞ መፈራረስና መጠፋፋትን ሳይሆን መገንባትንና አብሮነትን፤ ሥርዓት አልበኝነትንና ዝብርቅርቅነትን ሳይሆን ሥርዓታዊ መያያዝን፤ ብሎም ወደ ጋራ ግብ አብሮ መፍሰስንና መገሥገሥን የሚያስተምር ነው።
በቀውስ መሐል ፈውስ፣ በመፈራረስ ውስጥ መታደስ፣ ተበታትኖ በመጥፋት መካከል ተሰባስቦና ተጣምሮ በአዲስ ጉልበት መነሣት የመደመር መንገድ ነው። ሀገራችንም በዚህ የመደመር መንገድ እንድትጓዝና ከገባንበት አፍራሽና በታታኝ አካሄድ ነጻ እንድትወጣ ያስፈልጋል።
ከዚህ ተላቅቃ ወዳለምንላት የብልጽግና ማማ እንድትወጣ ወደ አዎንታዊ ተጓዳኝነትና ብዝኃነትን ወደማይጨፈልቅ አንድነት መሻገር ይገባናል።
የመደመር መንግስት
ገፅ 66
Ethiopian Broadcasting Corporation #ኢትዮጵያ #መደመር #ebc #ethiopia #መንግስት
የመደመር ዕሳቤ ደግሞ መፈራረስና መጠፋፋትን ሳይሆን መገንባትንና አብሮነትን፤ ሥርዓት አልበኝነትንና ዝብርቅርቅነትን ሳይሆን ሥርዓታዊ መያያዝን፤ ብሎም ወደ ጋራ ግብ አብሮ መፍሰስንና መገሥገሥን የሚያስተምር ነው።
በቀውስ መሐል ፈውስ፣ በመፈራረስ ውስጥ መታደስ፣ ተበታትኖ በመጥፋት መካከል ተሰባስቦና ተጣምሮ በአዲስ ጉልበት መነሣት የመደመር መንገድ ነው። ሀገራችንም በዚህ የመደመር መንገድ እንድትጓዝና ከገባንበት አፍራሽና በታታኝ አካሄድ ነጻ እንድትወጣ ያስፈልጋል።
ከዚህ ተላቅቃ ወዳለምንላት የብልጽግና ማማ እንድትወጣ ወደ አዎንታዊ ተጓዳኝነትና ብዝኃነትን ወደማይጨፈልቅ አንድነት መሻገር ይገባናል።
የመደመር መንግስት
ገፅ 66
Ethiopian Broadcasting Corporation #ኢትዮጵያ #መደመር #ebc #ethiopia #መንግስት
10 days ago
11 days ago
መላው የአፍሪካ ወንድም እህቶቻችን እንኳን ለአፍሪካ ቀን አደረሳችሁ ፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
***********
HAPPY AFRICA DAY TO ALL OUR AFRICAN BROTHERS AND SISTERS!
63 years ago, our forefathers gathered right here in Addis Ababa and dared to dream of a free, united Africa, and that dream still burns bright.
Today, as the proud home of the African Union, Ethiopia stands shoulder to shoulder with every African nation in that same spirit of unity.The work is far from over. Let us move from words to action, from promises to progress.
Africa's greatest resource has always been her people, and together, WE RISE!
Ethiopian Broadcasting Corporation #africaday #africa #ethiopia
***********
HAPPY AFRICA DAY TO ALL OUR AFRICAN BROTHERS AND SISTERS!
63 years ago, our forefathers gathered right here in Addis Ababa and dared to dream of a free, united Africa, and that dream still burns bright.
Today, as the proud home of the African Union, Ethiopia stands shoulder to shoulder with every African nation in that same spirit of unity.The work is far from over. Let us move from words to action, from promises to progress.
Africa's greatest resource has always been her people, and together, WE RISE!
Ethiopian Broadcasting Corporation #africaday #africa #ethiopia
11 days ago
የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ነገ ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን በአዲስ አበባ እና ሸገር ከተሞች የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው ቦታዎች ፦
✅ከጠዋቱ 2:00 እስከ 9:30
👉በኤሞሌስ ፋብሪካ፣ በካሰዴ፣ በጣፎ፣ በ44 ማዞሪያ ፣ በሰንዳፋ ጫፍ፣ በለገጣፎ፣ በሲዲሲ ፣ በኮሰሮ፤
✅ከጠዋቱ 3:00 እስከ 9:00
👉በላዘዘሪስት የጋራ መኖሪያ ቤቶች፣ በማርቆስ መጋዘን፣ በእ/አብ ሰፈር ከማርቆስ ከፍ ብሎ፣ በጸሐይ ጮራ ት/ቤት ፣ በስፓኒሽ ኤምባሲ፣ በስብሰባ ማዕከል፣ በተፈሪ መኮንን ውኃ ልማት ቢሮ፤
✅ከጠዋቱ 3:00 እስከ 12:00
👉በታጠቅ ሙገር ሲሚንት ፋብሪካ እና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ይቋረጣል፡፡
ስለሆነም በአካባቢው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻች የጥገና ሥራው ተጠናቆአገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትእግስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እናሳስባለን፡፡
EthiopianElectricUtility
ነገ ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን በአዲስ አበባ እና ሸገር ከተሞች የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው ቦታዎች ፦
✅ከጠዋቱ 2:00 እስከ 9:30
👉በኤሞሌስ ፋብሪካ፣ በካሰዴ፣ በጣፎ፣ በ44 ማዞሪያ ፣ በሰንዳፋ ጫፍ፣ በለገጣፎ፣ በሲዲሲ ፣ በኮሰሮ፤
✅ከጠዋቱ 3:00 እስከ 9:00
👉በላዘዘሪስት የጋራ መኖሪያ ቤቶች፣ በማርቆስ መጋዘን፣ በእ/አብ ሰፈር ከማርቆስ ከፍ ብሎ፣ በጸሐይ ጮራ ት/ቤት ፣ በስፓኒሽ ኤምባሲ፣ በስብሰባ ማዕከል፣ በተፈሪ መኮንን ውኃ ልማት ቢሮ፤
✅ከጠዋቱ 3:00 እስከ 12:00
👉በታጠቅ ሙገር ሲሚንት ፋብሪካ እና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ይቋረጣል፡፡
ስለሆነም በአካባቢው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻች የጥገና ሥራው ተጠናቆአገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትእግስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እናሳስባለን፡፡
EthiopianElectricUtility
12 days ago
የማዕድን ዘርፍ እና አዲስ የኢኮኖሚ ምዕራፍ
******************
(የዕለቱ መልዕክት)
በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ትንሳኤ ውስጥ ለዓመታት ተኝቶ የነበረው የማዕድን ሀብታችን አሁን ለሀገር ኢኮኖሚ ትከሻውን እየሰጠ ይገኛል። ከባህላዊ የግብርና አጥር ወጥተን አገራችንን ወደ አፍሪካ የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማሸጋገር በሚደረገው ጥረት ኢትዮጵያ ያሏትን የሀብት ክምችት በዕውቀትና በቴክኖሎጂ አቀነባብራ መጠቀም ጀምራለች። በዚህም የከርሰ ምድርና ገጸ ምድር ሀብቷን ወደ ብሔራዊ ምርታማነት የመቀየር አዲስ ምዕራፍ ከፍታለች።
የማምረቻው ዘርፍ እንደ ወንዝ ውሃ የኢኮኖሚውን አቅጣጫ የሚቀይር ከሆነ ማዕድን ደግሞ የዚያ ወንዝ ምንጭ ነው። አገራችንን የኢንዱስትሪ ፋና ለማድረግ የጀመርነው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፣ የማዕድን ዘርፉን ከምድር ውስጥ አውጥቶ ወደ ፋብሪካዎች ግብዓትነት የመቀየር ግዴታ አለበት።
የኢንዱስትሪ ፓርኮቻችን እያሳዩት ባለው አቅም የማዕድን ዘርፉን በቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ጥገኝነታችንን መቀነስ የምንችለው አሁን ነው። በገዛ መሬታችን ያለውን ሀብት በጥራትና በክህሎት ተጠቅመን የውጭ ገበያን በዋጋና በጥራት መፎካከር የሚችል አቅም መገንባትም አለብን።
ከውጥን ወደ እውነታ እየተሸጋገርን ባለበት በዚህ ወቅት የማዕድን ልማታችን ከጥሬ ዕቃ ሽያጭ አልፎ እሴት በተጨመረባቸው ምርቶች መደገፍ አለበት። የወርቅ፣ የኦፓል፣ የታንታለም እና የሌሎች ማዕድናት ፍሰት ለሀገር ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት መሆን የሚችለው፣ የማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች በፓርኮቻችን ውስጥ ሲጠናከሩ ብቻ ነው።
የኢኮኖሚ ነፃነት ማለት በውጭ ምንዛሪ መግዛት ሳይሆን በእጅ ያለን ሀብት በአገር አቅም አምርቶ ለዓለም ማቅረብ ነው። ይህ ጉዞ በሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል ጥያቄ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ የሉዓላዊነትና የብልጽግና መለኪያ ነው።
የማዕድን ዘርፉን ወደ ኢንዱስትሪ ማቀናጀት ማለት የአገርን የቴክኖሎጂ አቅም መፈተን ማለት ነው። ዘመናዊ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለዓለም አቀፍ ደረጃ ያላቸው ማዕድናት ማቀነባበሪያ ማዕከላት ሲሆኑ ኢትዮጵያ ከጥሬ ዕቃ ላኪነት ወደ ምርት አምራችነት ትሸጋገራለች።
ይህ ሽግግር በተለይም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን፣ የፀሐይ ኃይል መሣሪያዎችን እና የሕክምና መሣሪያዎችን ለማምረት ወሳኝ የሆኑ ማዕድናትን በአገር ውስጥ መጠቀምን ይጠይቃል።
"ውኃ ካልጠራ አይጠጣም፣ ሰው ካልተማረ አይጠቅም" እንደተባለው የምንፈልገውን የኢንዱስትሪ ለውጥ የምናመጣው በትምህርት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በዘርፉ በሰለጠነ የሰው ኃይል ብቻ ነው።
የኢትዮጵያ ትንሳኤ በወረቀት ላይ የተጻፈ ራዕይ ሳይሆን በየፋብሪካው መጋዘን የሚከማች ምርት፣ በየኢንዱስትሪ ፓርኩ የሚሰማ የቴክኖሎጂ ምት እና በምድር የተገኙ ማዕድናት በኢትዮጵያዊ ክህሎት ሲቀረጹ የሚታይ እውነት ነው።
በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪ ፓርኮቻችን እየሳቡት ያለው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት፣ የማዕድን ዘርፉን እንደ ታላቅ የኢኮኖሚ ምንጭ ለመጠቀም ያለንን አቅም ያሳያል። የልዩ ኢኮኖሚ ዞን አዋጁም ለዚህ ዘርፍ የሚሰጠው የግብርና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች፣ ባለሀብቶች ወደ ማዕድን ልማት እንዲገቡ ትልቅ ማበረታቻ ሆኗል።
የማዕድን ሀብታችንን በዘመናዊ አሠራር ፈትሸን፣ የኢንዱስትሪው ዘርፍ እንዲያንሰራራ ማድረጉ የጊዜው ትልቁ አገራዊ ጥሪ ነው።
ኢትዮጵያ በምርቷ ትከበራለች፤ በምድሯ የተከማቸው ሀብትም ለቀጣዩ ትውልድ የብልጽግና ፋና ሆኖ ይደምቃል። ይህ የኢንዱስትሪ አብዮት የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ከፍ የሚያደርግ፣ የኢኮኖሚ መዋቅራችንን ለዘመናት የሚያጸና የትንሳኤ ብሥራት ነው።
በየደረጃው ያለው የማዕድን ምርታችን ሲጎለብት ኢትዮጵያ የራሷን የኢንዱስትሪ ሉዓላዊነት ታውጃለች። ነገ የምናያት ኢትዮጵያ በምርቷ የምትኩራራ፣ በሀብቷ የምትበለጽግ እና ለአፍሪካ የብልጽግና ፋና የምትሆን አገር ናት።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #ebcdotstream #ethiopia #ebc #ማዕድን #ኢኮኖሚ
******************
(የዕለቱ መልዕክት)
በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ትንሳኤ ውስጥ ለዓመታት ተኝቶ የነበረው የማዕድን ሀብታችን አሁን ለሀገር ኢኮኖሚ ትከሻውን እየሰጠ ይገኛል። ከባህላዊ የግብርና አጥር ወጥተን አገራችንን ወደ አፍሪካ የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማሸጋገር በሚደረገው ጥረት ኢትዮጵያ ያሏትን የሀብት ክምችት በዕውቀትና በቴክኖሎጂ አቀነባብራ መጠቀም ጀምራለች። በዚህም የከርሰ ምድርና ገጸ ምድር ሀብቷን ወደ ብሔራዊ ምርታማነት የመቀየር አዲስ ምዕራፍ ከፍታለች።
የማምረቻው ዘርፍ እንደ ወንዝ ውሃ የኢኮኖሚውን አቅጣጫ የሚቀይር ከሆነ ማዕድን ደግሞ የዚያ ወንዝ ምንጭ ነው። አገራችንን የኢንዱስትሪ ፋና ለማድረግ የጀመርነው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፣ የማዕድን ዘርፉን ከምድር ውስጥ አውጥቶ ወደ ፋብሪካዎች ግብዓትነት የመቀየር ግዴታ አለበት።
የኢንዱስትሪ ፓርኮቻችን እያሳዩት ባለው አቅም የማዕድን ዘርፉን በቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ጥገኝነታችንን መቀነስ የምንችለው አሁን ነው። በገዛ መሬታችን ያለውን ሀብት በጥራትና በክህሎት ተጠቅመን የውጭ ገበያን በዋጋና በጥራት መፎካከር የሚችል አቅም መገንባትም አለብን።
ከውጥን ወደ እውነታ እየተሸጋገርን ባለበት በዚህ ወቅት የማዕድን ልማታችን ከጥሬ ዕቃ ሽያጭ አልፎ እሴት በተጨመረባቸው ምርቶች መደገፍ አለበት። የወርቅ፣ የኦፓል፣ የታንታለም እና የሌሎች ማዕድናት ፍሰት ለሀገር ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት መሆን የሚችለው፣ የማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች በፓርኮቻችን ውስጥ ሲጠናከሩ ብቻ ነው።
የኢኮኖሚ ነፃነት ማለት በውጭ ምንዛሪ መግዛት ሳይሆን በእጅ ያለን ሀብት በአገር አቅም አምርቶ ለዓለም ማቅረብ ነው። ይህ ጉዞ በሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል ጥያቄ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ የሉዓላዊነትና የብልጽግና መለኪያ ነው።
የማዕድን ዘርፉን ወደ ኢንዱስትሪ ማቀናጀት ማለት የአገርን የቴክኖሎጂ አቅም መፈተን ማለት ነው። ዘመናዊ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለዓለም አቀፍ ደረጃ ያላቸው ማዕድናት ማቀነባበሪያ ማዕከላት ሲሆኑ ኢትዮጵያ ከጥሬ ዕቃ ላኪነት ወደ ምርት አምራችነት ትሸጋገራለች።
ይህ ሽግግር በተለይም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን፣ የፀሐይ ኃይል መሣሪያዎችን እና የሕክምና መሣሪያዎችን ለማምረት ወሳኝ የሆኑ ማዕድናትን በአገር ውስጥ መጠቀምን ይጠይቃል።
"ውኃ ካልጠራ አይጠጣም፣ ሰው ካልተማረ አይጠቅም" እንደተባለው የምንፈልገውን የኢንዱስትሪ ለውጥ የምናመጣው በትምህርት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በዘርፉ በሰለጠነ የሰው ኃይል ብቻ ነው።
የኢትዮጵያ ትንሳኤ በወረቀት ላይ የተጻፈ ራዕይ ሳይሆን በየፋብሪካው መጋዘን የሚከማች ምርት፣ በየኢንዱስትሪ ፓርኩ የሚሰማ የቴክኖሎጂ ምት እና በምድር የተገኙ ማዕድናት በኢትዮጵያዊ ክህሎት ሲቀረጹ የሚታይ እውነት ነው።
በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪ ፓርኮቻችን እየሳቡት ያለው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት፣ የማዕድን ዘርፉን እንደ ታላቅ የኢኮኖሚ ምንጭ ለመጠቀም ያለንን አቅም ያሳያል። የልዩ ኢኮኖሚ ዞን አዋጁም ለዚህ ዘርፍ የሚሰጠው የግብርና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች፣ ባለሀብቶች ወደ ማዕድን ልማት እንዲገቡ ትልቅ ማበረታቻ ሆኗል።
የማዕድን ሀብታችንን በዘመናዊ አሠራር ፈትሸን፣ የኢንዱስትሪው ዘርፍ እንዲያንሰራራ ማድረጉ የጊዜው ትልቁ አገራዊ ጥሪ ነው።
ኢትዮጵያ በምርቷ ትከበራለች፤ በምድሯ የተከማቸው ሀብትም ለቀጣዩ ትውልድ የብልጽግና ፋና ሆኖ ይደምቃል። ይህ የኢንዱስትሪ አብዮት የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ከፍ የሚያደርግ፣ የኢኮኖሚ መዋቅራችንን ለዘመናት የሚያጸና የትንሳኤ ብሥራት ነው።
በየደረጃው ያለው የማዕድን ምርታችን ሲጎለብት ኢትዮጵያ የራሷን የኢንዱስትሪ ሉዓላዊነት ታውጃለች። ነገ የምናያት ኢትዮጵያ በምርቷ የምትኩራራ፣ በሀብቷ የምትበለጽግ እና ለአፍሪካ የብልጽግና ፋና የምትሆን አገር ናት።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #ebcdotstream #ethiopia #ebc #ማዕድን #ኢኮኖሚ
Sponsored by
Surafel