1 hr. ago
ሕወሃት አዲስ አውዳሚ ጦርነት ሊቀሰቀስ እንደሚችል በማስጠንቀቅ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አስቸኳይ ጥሪ አቀረበ።
ህውሃት ከፊታችን አውዳሚ ጦርነት እየመጣ ይገኛል አስወግዱ ሲል ለአለማቀፍ ማህብረሰብ ባሰራጨው ደብዳቤ፣ በኢትዮጵያ ያለው የፖለቲካ ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ሲል ገልጿል።
በምርጫ ቦርድ እውቅናው የተሰረዘው ድርጅቱ ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም "ሊቀረፍ የማይችልና አውዳሚ ጦርነትን ለመከላከል የቀረበ አስቸኳይ ጥሪ" በሚል ርዕስ ለዲፕሎማሲያዊ ሚሲዮኖች እና ለዓለም አቀፍ አጋሮች ባሰራጨው የዲፕሎማሲያዊ ማስታወሻ ሀገሪቱ ወደ አዲስ የትጥቅ ግጭት እያመራች መሆኑን አስጠንቅቋል።
እንደ ሕወሃት መግለጫ ከሆነ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ የውይይት እና የስምምነት መንፈስ እየጠፋ በመምጣቱ በእርሱ ፋንታ "የአንድ ወገን ውሳኔ፣ ማስገደድ እና ወታደራዊ የኃይል እርምጃ" ፖሊሲዎች እየነገሱ መጥተዋል ብሏል። ይህ አካሄድ መቀጠሉ ደግሞ ዳግም የትጥቅ ግጭት መከሰቱ የማይቀሬ እንዲሆን እያደረገው ነው ብሏል።
ይህ ሊቀሰቀስ የሚችለው ጦርነት በኢትዮጵያ ድንበር ብቻ ተወስኖ እንደማይቀር የጠቆመው መግለጫው በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ቀጣናዊ ውጥረት እና ለጎረቤት ሀገራት የሚታየውን የጠብ አጫሪነት ዝንባሌ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ግጭቱ አጠቃላይ ቀጣናውን ሊያናጋና ሰብዓዊ ቀውሱን ሊያባብስ እንደሚችል አመልክቷል።
የፌዴራል መንግሥቱ "ግትር አቋም" ይዟል ሲል የወቀሰው ሕወሃት፣ የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ግን አሁንም ለሰላማዊ መፍትሔ ያለውን ቁርጠኝነት ገልጿል።
ከሰሞኑ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የትግራይ ወጣቶች ወደ ወታደራዊ የስልጠና ካምፖች መግባታቸውን ሪፖርቶች በተሰሙበት በዚህ ወቅት የወጣው መግለጫ ጨምሮም "ማንኛውም ማህበረሰብ ሊሸከመው የሚችለው የጽናት ገደብ አለው" በሚል በትግራይ ላይ ያለው ጫና መጥበቁን የገለጸው ድርጅቱ፣ ቢሆንም ግን ብቸኛው አማራጭ መንገድ የፖለቲካ ውይይት መሆኑን በጽኑ እንደሚያምን አስታውቋል።
በመጨረሻም ሕወሃት የችግሩን ስር የሰደዱ መንስኤዎች ለመፍታት እንዲቻል፣ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚመራና የሚደገፍ ታማኝ የፖለቲካ ሂደት እንዲጀመርና ለዚህም ዝግጁ መሆኑን በመግለጫው ገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
ህውሃት ከፊታችን አውዳሚ ጦርነት እየመጣ ይገኛል አስወግዱ ሲል ለአለማቀፍ ማህብረሰብ ባሰራጨው ደብዳቤ፣ በኢትዮጵያ ያለው የፖለቲካ ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ሲል ገልጿል።
በምርጫ ቦርድ እውቅናው የተሰረዘው ድርጅቱ ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም "ሊቀረፍ የማይችልና አውዳሚ ጦርነትን ለመከላከል የቀረበ አስቸኳይ ጥሪ" በሚል ርዕስ ለዲፕሎማሲያዊ ሚሲዮኖች እና ለዓለም አቀፍ አጋሮች ባሰራጨው የዲፕሎማሲያዊ ማስታወሻ ሀገሪቱ ወደ አዲስ የትጥቅ ግጭት እያመራች መሆኑን አስጠንቅቋል።
እንደ ሕወሃት መግለጫ ከሆነ በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ የውይይት እና የስምምነት መንፈስ እየጠፋ በመምጣቱ በእርሱ ፋንታ "የአንድ ወገን ውሳኔ፣ ማስገደድ እና ወታደራዊ የኃይል እርምጃ" ፖሊሲዎች እየነገሱ መጥተዋል ብሏል። ይህ አካሄድ መቀጠሉ ደግሞ ዳግም የትጥቅ ግጭት መከሰቱ የማይቀሬ እንዲሆን እያደረገው ነው ብሏል።
ይህ ሊቀሰቀስ የሚችለው ጦርነት በኢትዮጵያ ድንበር ብቻ ተወስኖ እንደማይቀር የጠቆመው መግለጫው በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ቀጣናዊ ውጥረት እና ለጎረቤት ሀገራት የሚታየውን የጠብ አጫሪነት ዝንባሌ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ግጭቱ አጠቃላይ ቀጣናውን ሊያናጋና ሰብዓዊ ቀውሱን ሊያባብስ እንደሚችል አመልክቷል።
የፌዴራል መንግሥቱ "ግትር አቋም" ይዟል ሲል የወቀሰው ሕወሃት፣ የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ግን አሁንም ለሰላማዊ መፍትሔ ያለውን ቁርጠኝነት ገልጿል።
ከሰሞኑ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የትግራይ ወጣቶች ወደ ወታደራዊ የስልጠና ካምፖች መግባታቸውን ሪፖርቶች በተሰሙበት በዚህ ወቅት የወጣው መግለጫ ጨምሮም "ማንኛውም ማህበረሰብ ሊሸከመው የሚችለው የጽናት ገደብ አለው" በሚል በትግራይ ላይ ያለው ጫና መጥበቁን የገለጸው ድርጅቱ፣ ቢሆንም ግን ብቸኛው አማራጭ መንገድ የፖለቲካ ውይይት መሆኑን በጽኑ እንደሚያምን አስታውቋል።
በመጨረሻም ሕወሃት የችግሩን ስር የሰደዱ መንስኤዎች ለመፍታት እንዲቻል፣ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚመራና የሚደገፍ ታማኝ የፖለቲካ ሂደት እንዲጀመርና ለዚህም ዝግጁ መሆኑን በመግለጫው ገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
2 hours ago
ኢትዮጵያና አይ ኤም ኤፍ (አይኤምኤፍ) የ468 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት ላይ ደረሱ
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት በተራዘመው የብድር አቅርቦት ፕሮግራም አምስተኛ ግምገማ ላይ በባለሙያዎች ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስታውቀዋል።
ይህ ስምምነት በሚቀጥሉት ሳምንታት በድርጅቱ ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሙሉ በሙሉ ሲጸድቅ፣ ኢትዮጵያ የ468 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ተጨማሪ የፋይናንስ ድጋፍ እንድታገኝ ያደርጋታል።
ይህም ሀገሪቱ በ4 ዓመታት ውስጥ ከምታገኘው የ3.4 ቢሊዮን ዶላር አጠቃላይ ድጋፍ ውስጥ እስካሁን የተለቀቀላትን የገንዘብ መጠን ወደ 2.65 ቢሊዮን ዶላር ከፍ የሚያደርገው ሲሆን፣ ስምምነቱ ሊደረስ የተቻለው ከአልቫሮ ፒሪስ የተመራው የድርጅቱ ልዑክ ከሚያዝያ 28 እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ባደረገው የሁለት ሳምንታት ጉብኝትና ተከታታይ የሥራ ውይይቶች ማጠናቀቂያ ላይ ነው።
በዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት መግለጫ ላይ እንደተመለከተው ፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከቀጠናዊ ቀውሶች ጋር ተያይዞ የመጣውን ትልቅ ውጫዊ ጫና በመቋቋም ረገድ ከፍተኛ ጥንካሬ አሳይቷል።
ይሁን እንጂ፣ ዓለም አቀፋዊ አለመረጋጋትና የሸቀጦች ዋጋ መዋዠቅ አሁንም እያደገ በመምጣቱ በኢኮኖሚው የወደፊት ጉዞ ላይ የሚታዩት ስጋቶች መጨመራቸውን አይ ኤም ኤፍ አስጠንቅቋል።
የሀገሪቱን የኢኮኖሚ መረጋጋት በዘላቂነት ለማስቀጠልም ድርጅቱ ለኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ቁልፍ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን የጠቆመ ሲሆን፣ ይህም የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲን አጠናክሮ መቀጠልን፣ የውጭ ምንዛሬ ገበያውን ግልጽነትና አሠራር ይበልጥ ማሻሻልን እንዲሁም የአገር ውስጥ ገቢ አሰባሰብን በማጠናከር የወጪ አያያዝን በጥንቃቄ መምራት አስፈላጊ መሆኑን አሳስቧል።
Seledadotio
Seledadotio
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት በተራዘመው የብድር አቅርቦት ፕሮግራም አምስተኛ ግምገማ ላይ በባለሙያዎች ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስታውቀዋል።
ይህ ስምምነት በሚቀጥሉት ሳምንታት በድርጅቱ ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሙሉ በሙሉ ሲጸድቅ፣ ኢትዮጵያ የ468 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ተጨማሪ የፋይናንስ ድጋፍ እንድታገኝ ያደርጋታል።
ይህም ሀገሪቱ በ4 ዓመታት ውስጥ ከምታገኘው የ3.4 ቢሊዮን ዶላር አጠቃላይ ድጋፍ ውስጥ እስካሁን የተለቀቀላትን የገንዘብ መጠን ወደ 2.65 ቢሊዮን ዶላር ከፍ የሚያደርገው ሲሆን፣ ስምምነቱ ሊደረስ የተቻለው ከአልቫሮ ፒሪስ የተመራው የድርጅቱ ልዑክ ከሚያዝያ 28 እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ባደረገው የሁለት ሳምንታት ጉብኝትና ተከታታይ የሥራ ውይይቶች ማጠናቀቂያ ላይ ነው።
በዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት መግለጫ ላይ እንደተመለከተው ፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከቀጠናዊ ቀውሶች ጋር ተያይዞ የመጣውን ትልቅ ውጫዊ ጫና በመቋቋም ረገድ ከፍተኛ ጥንካሬ አሳይቷል።
ይሁን እንጂ፣ ዓለም አቀፋዊ አለመረጋጋትና የሸቀጦች ዋጋ መዋዠቅ አሁንም እያደገ በመምጣቱ በኢኮኖሚው የወደፊት ጉዞ ላይ የሚታዩት ስጋቶች መጨመራቸውን አይ ኤም ኤፍ አስጠንቅቋል።
የሀገሪቱን የኢኮኖሚ መረጋጋት በዘላቂነት ለማስቀጠልም ድርጅቱ ለኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ቁልፍ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን የጠቆመ ሲሆን፣ ይህም የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲን አጠናክሮ መቀጠልን፣ የውጭ ምንዛሬ ገበያውን ግልጽነትና አሠራር ይበልጥ ማሻሻልን እንዲሁም የአገር ውስጥ ገቢ አሰባሰብን በማጠናከር የወጪ አያያዝን በጥንቃቄ መምራት አስፈላጊ መሆኑን አሳስቧል።
Seledadotio
Seledadotio
18 hours ago
ጅቡቲ በዳመርጆግ የነዳጅ ማከማቻ ግንባታ ላይ የኢትዮጵያን ድጋፍና ተሳትፎ እየጠበቀች መሆኑን ገለጸች
የጅቡቲ ወደቦች እና ነፃ ቀጠናዎች ባለስልጣን በሀገሪቱ ደቡብ ምስራቅ በኩል በሚገኘው አዲሱ የዳመርጆግ ፈሳሽ ጭነት ወደብ ላይ የነዳጅ ማከማቻ ዴፖ ግንባታ ለመጀመር በበጀት ዓመቱ መጀመሪያ ላይ የኢትዮጵያን ተሳትፎና የገንዘብ ድጋፍ እየጠበቀ መሆኑን አስታውቋል።
የባለስልጣኑ ሰብሳቢ አቡበከር ኦማር ሀዲ ለካፒታል እንደገለፁት ፣ ዘመናዊው የነዳጅ ወደብ ወደ ስራ እንዲገባ የነዳጅ ማራገፊያ ዴፖ ግንባታ ይቀረዋል።
ለዚህም ባለስልጣኑ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ጋር ድርድር እያደረገ ሲሆን፣ ተቋሙ ሐምሌ 1 ቀን በሚጀምረው አዲስ የበጀት አመት በጀት አፀድቆ ለስራው እንደሚመጣ ይጠበቃል ሲሉ ነው የገለፁት።
Seledadotio
Seledadotio
የጅቡቲ ወደቦች እና ነፃ ቀጠናዎች ባለስልጣን በሀገሪቱ ደቡብ ምስራቅ በኩል በሚገኘው አዲሱ የዳመርጆግ ፈሳሽ ጭነት ወደብ ላይ የነዳጅ ማከማቻ ዴፖ ግንባታ ለመጀመር በበጀት ዓመቱ መጀመሪያ ላይ የኢትዮጵያን ተሳትፎና የገንዘብ ድጋፍ እየጠበቀ መሆኑን አስታውቋል።
የባለስልጣኑ ሰብሳቢ አቡበከር ኦማር ሀዲ ለካፒታል እንደገለፁት ፣ ዘመናዊው የነዳጅ ወደብ ወደ ስራ እንዲገባ የነዳጅ ማራገፊያ ዴፖ ግንባታ ይቀረዋል።
ለዚህም ባለስልጣኑ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ጋር ድርድር እያደረገ ሲሆን፣ ተቋሙ ሐምሌ 1 ቀን በሚጀምረው አዲስ የበጀት አመት በጀት አፀድቆ ለስራው እንደሚመጣ ይጠበቃል ሲሉ ነው የገለፁት።
Seledadotio
Seledadotio
13 hours ago
በ130 ምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች መዝገብ ላይ ያልተገኙ እና ካርድ ያልያዙ መራጮች እንዲመርጡ መደረጋቸውን ኅብረት ለምርጫ ገለጸ
የኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ኅብረት ለምርጫ (CECOE / ኅብረት ለምርጫ) ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የተከናወነውን 7ኛውን ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ አስመልክቶ ዛሬ ረቡዕ ባወጣው የመጀመሪያ ደረጃ የትዝብት ሪፖርቱ፣ በ130 ምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች መዝገብ ላይ ያልተገኙ እና ካርድ ያልያዙ፣ በእያንዳንዱ ጣቢያ ከአንድ እስከ 10 የሚሆኑ መራጮች እንዲመርጡ መደረጋቸውን ገለጸ።
እንዲሁም በስምንት የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ደግሞ ከ10 በላይ ሰዎች ስማቸው በመራጮች መዝገብ ላይ ሳይገኝ እና የመራጭነት ካርድ ሳይዙ እንዲመርጡ መፈቀዱንም ኅብረቱ በምርጫ ትዝብት ጊዜያዊ ሪፖርቱ ላይ አስታውቋል።
ኅብረቱ ከታዘባቸው 2,506 የምርጫ ጣቢያዎች መካከል በ2,458 ጣቢያዎች ስማቸው በመራጮች መዝገብ ላይ ሰፍሮ ድምጽ መስጠት የተከለከለ ሰው እንዳልነበር መታዘቡን ጠቅሷል፤ ይሁንና በ46 የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ከ1 እስከ 10 ግለሰቦች ስማቸው በመራጮች መዝገብ ላይ ሰፍሮ ድምጽ መስጠት መከልከላቸው ተገልጿል።
በሁለት ድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ደግሞ ከ10 በላይ ሰዎች ስማቸው በመራጮች መዝገብ ላይ ሰፍሮ ድምጽ መስጠት መከልከላቸውን የኅብረቱ ሰብሳቢ ተናግረዋል።
Via ኢትዮጵያ ኢንሳይደር
Seledadotio
Seledadotio
የኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ኅብረት ለምርጫ (CECOE / ኅብረት ለምርጫ) ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የተከናወነውን 7ኛውን ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ አስመልክቶ ዛሬ ረቡዕ ባወጣው የመጀመሪያ ደረጃ የትዝብት ሪፖርቱ፣ በ130 ምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች መዝገብ ላይ ያልተገኙ እና ካርድ ያልያዙ፣ በእያንዳንዱ ጣቢያ ከአንድ እስከ 10 የሚሆኑ መራጮች እንዲመርጡ መደረጋቸውን ገለጸ።
እንዲሁም በስምንት የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ደግሞ ከ10 በላይ ሰዎች ስማቸው በመራጮች መዝገብ ላይ ሳይገኝ እና የመራጭነት ካርድ ሳይዙ እንዲመርጡ መፈቀዱንም ኅብረቱ በምርጫ ትዝብት ጊዜያዊ ሪፖርቱ ላይ አስታውቋል።
ኅብረቱ ከታዘባቸው 2,506 የምርጫ ጣቢያዎች መካከል በ2,458 ጣቢያዎች ስማቸው በመራጮች መዝገብ ላይ ሰፍሮ ድምጽ መስጠት የተከለከለ ሰው እንዳልነበር መታዘቡን ጠቅሷል፤ ይሁንና በ46 የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ከ1 እስከ 10 ግለሰቦች ስማቸው በመራጮች መዝገብ ላይ ሰፍሮ ድምጽ መስጠት መከልከላቸው ተገልጿል።
በሁለት ድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ደግሞ ከ10 በላይ ሰዎች ስማቸው በመራጮች መዝገብ ላይ ሰፍሮ ድምጽ መስጠት መከልከላቸውን የኅብረቱ ሰብሳቢ ተናግረዋል።
Via ኢትዮጵያ ኢንሳይደር
Seledadotio
Seledadotio
11 hours ago
"በሚሊተሪ ካምፓች እና በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ምርጫ ሰኔ 2 ይካሄዳል" - የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በሚሊተሪ ካምፓች እና በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በተመዘገቡባቸው ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ የመራጮች ምዝገባ ሰኔ 1 ቀን እንደሚያካሂድ የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን በዛሬው ዕለት በሪፖርቱ ጠቅሶት ነበር።
ይህንን አስመልክቶ ማብራሪያ እንዲሰጡበት ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበላቸው የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሚሊተሪ ካምፓች እና በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በተመዘገቡባቸው ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ምርጫው በተለየ ቀን እንደሚካሄድ አረጋግጠዋል።
ሆኖም ህብረቱ "June-8 / ሰኔ 1" ቀን እንደሚካሄድ ሪፖርቱ ቢጠቅስም፥ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ግን ምርጫው በእነዚህ ልዩ ጣቢያዎች የሚካሄደው #ሰኔ_2 መሆኑን ነው የገለጹት።
ይህ የተፈጠረበትን ምክንያትም ቦርዱ ያለበትን የተጨናነቀ ጊዜ ታሳቢ በማድረግ ውጤቶቹም "በፍጥነት ተጠቃለው መቅረብ የሚችሉ ውጤቶች በመሆናቸው " ነው ሲሉ ቦርዱ ከሌሎች ውጤቶች ጋር አብሮ የሚያቀርባቸው መሆኑን ገልጸዋል።
ከዚህ ቀደም በሀገር ውስጥ ተፈናቃይ ካምፖች 28,632 እንዲሁም በሚሊተሪ ካምፖች 126,498 ሺ መራጮች መመዝገባቸው መገለጹ ይታወሳል።
በተጨማሪም ህብረቱ የተጠናቀቀ ውጤት የሚገለጽበትን ቀን በተመለከተ ህብረቱ ሰኔ 4 መሆኑን በሪፖርቱ ጠቅሷል።
የቦርዱ ሰብሳቢ በበኩላቸው ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ቦርዱ ከገጠመው የድምጽ በይፋ የማሳወቅ ሥራ እስከ 20 ቀን የመግፋት መብት እንዳለውም ጠቁመዋል።
Seledadotio
Seledadotio
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በሚሊተሪ ካምፓች እና በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በተመዘገቡባቸው ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ የመራጮች ምዝገባ ሰኔ 1 ቀን እንደሚያካሂድ የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን በዛሬው ዕለት በሪፖርቱ ጠቅሶት ነበር።
ይህንን አስመልክቶ ማብራሪያ እንዲሰጡበት ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበላቸው የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሚሊተሪ ካምፓች እና በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በተመዘገቡባቸው ልዩ የምርጫ ጣቢያዎች ምርጫው በተለየ ቀን እንደሚካሄድ አረጋግጠዋል።
ሆኖም ህብረቱ "June-8 / ሰኔ 1" ቀን እንደሚካሄድ ሪፖርቱ ቢጠቅስም፥ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ግን ምርጫው በእነዚህ ልዩ ጣቢያዎች የሚካሄደው #ሰኔ_2 መሆኑን ነው የገለጹት።
ይህ የተፈጠረበትን ምክንያትም ቦርዱ ያለበትን የተጨናነቀ ጊዜ ታሳቢ በማድረግ ውጤቶቹም "በፍጥነት ተጠቃለው መቅረብ የሚችሉ ውጤቶች በመሆናቸው " ነው ሲሉ ቦርዱ ከሌሎች ውጤቶች ጋር አብሮ የሚያቀርባቸው መሆኑን ገልጸዋል።
ከዚህ ቀደም በሀገር ውስጥ ተፈናቃይ ካምፖች 28,632 እንዲሁም በሚሊተሪ ካምፖች 126,498 ሺ መራጮች መመዝገባቸው መገለጹ ይታወሳል።
በተጨማሪም ህብረቱ የተጠናቀቀ ውጤት የሚገለጽበትን ቀን በተመለከተ ህብረቱ ሰኔ 4 መሆኑን በሪፖርቱ ጠቅሷል።
የቦርዱ ሰብሳቢ በበኩላቸው ከአቅም በላይ የሆነ ችግር ቦርዱ ከገጠመው የድምጽ በይፋ የማሳወቅ ሥራ እስከ 20 ቀን የመግፋት መብት እንዳለውም ጠቁመዋል።
Seledadotio
Seledadotio
12 hours ago
የንፁሀን እልቂት በቃ ሊባል ይገባል!!
በኦሮሚያ ክልል በአርሲ ዞን በአሰኮ ወረዳ፣ በሺርካ ወረዳ እና ሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ ታጣቂዎች ንፁሀን የኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታዮችን በመግደል በርካቶችን ከቤት ንብረታቸው ማፈናቀላቸውን በመስማቴ እጅግ አዝኛለው::
ይህን ሰይጣናዊ የጥፋት ተግባርም በፅኑ አወግዛለሁ::
በአርሲ በተደጋጋሚ ንፁሀኖችን ኢላማ ያደረገ ጥቃት እየተበራከተ በየጊዜው ለቅሶ እና ዋይታ ብቻ እየተሰማ ያለ መፍትሄ መቀጠሉ እጅግ ያሳምማል::
ንፁሃን ዜጎች እያለቁ ያለው ከውጪ በመጣ ወራሪ ጠላት ሳይሆን ወንድም ወንድሙ ላይ እየሰነዘረው ባለው አሳዛኝ ከጭካኔ ጥቃት ነው::
በሀገሩ ምድር በድህነት ህይወቱን እየመራ ለሚገኝ ንፁህ ህዝብ ከግራ እና በቀኝ ጠብመንጃ በታጠቁ ሃይሎች በማያውቁት አጀንዳ ለሞት፣ ለእልቂት፣ ለስደት መዳረጉ ልብ ሰባሪ ነው::
ይህ የንፁሀን እልቂት በቃ ሊባል ይገባል!!
ሁሉም ኢትዮጵያዊ የዚህ መሰሉን እልቂት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማስቆም እጅ ለእጅ ተያይዞ ሊቆም ይገባል::
በአርሲ በተደጋጋሚ እየተፈፀመ በሚገኘው ጥቃት ህይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን ቤተሰቦች መፅናናትን እመኛለው::
ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖቻችንም ቶሎ ያገግሙ ዘንድ አላህ እንዲረዳቸው እንዲሁም የተፈናቀሉትም ወደቄያቸው ደህንነታቸው ተጠብቆ ባስቸኳይ ይመለሱ ዘንድ ልባዊ ምኞቴ ነው::
አላህ ሀገራችንን እና ወገኖቻችንን ይጠብቅልን::
ሰላም መግባባቱንና መተዛዘኑን በመላው ሀገራችን ሀያሉ ጌታችን አላህ(ሱ.ወ) ያስፍንልን
ኡስታዝ አቡበከር
Seledadotio
Seledadotio
በኦሮሚያ ክልል በአርሲ ዞን በአሰኮ ወረዳ፣ በሺርካ ወረዳ እና ሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ ታጣቂዎች ንፁሀን የኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታዮችን በመግደል በርካቶችን ከቤት ንብረታቸው ማፈናቀላቸውን በመስማቴ እጅግ አዝኛለው::
ይህን ሰይጣናዊ የጥፋት ተግባርም በፅኑ አወግዛለሁ::
በአርሲ በተደጋጋሚ ንፁሀኖችን ኢላማ ያደረገ ጥቃት እየተበራከተ በየጊዜው ለቅሶ እና ዋይታ ብቻ እየተሰማ ያለ መፍትሄ መቀጠሉ እጅግ ያሳምማል::
ንፁሃን ዜጎች እያለቁ ያለው ከውጪ በመጣ ወራሪ ጠላት ሳይሆን ወንድም ወንድሙ ላይ እየሰነዘረው ባለው አሳዛኝ ከጭካኔ ጥቃት ነው::
በሀገሩ ምድር በድህነት ህይወቱን እየመራ ለሚገኝ ንፁህ ህዝብ ከግራ እና በቀኝ ጠብመንጃ በታጠቁ ሃይሎች በማያውቁት አጀንዳ ለሞት፣ ለእልቂት፣ ለስደት መዳረጉ ልብ ሰባሪ ነው::
ይህ የንፁሀን እልቂት በቃ ሊባል ይገባል!!
ሁሉም ኢትዮጵያዊ የዚህ መሰሉን እልቂት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለማስቆም እጅ ለእጅ ተያይዞ ሊቆም ይገባል::
በአርሲ በተደጋጋሚ እየተፈፀመ በሚገኘው ጥቃት ህይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን ቤተሰቦች መፅናናትን እመኛለው::
ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖቻችንም ቶሎ ያገግሙ ዘንድ አላህ እንዲረዳቸው እንዲሁም የተፈናቀሉትም ወደቄያቸው ደህንነታቸው ተጠብቆ ባስቸኳይ ይመለሱ ዘንድ ልባዊ ምኞቴ ነው::
አላህ ሀገራችንን እና ወገኖቻችንን ይጠብቅልን::
ሰላም መግባባቱንና መተዛዘኑን በመላው ሀገራችን ሀያሉ ጌታችን አላህ(ሱ.ወ) ያስፍንልን
ኡስታዝ አቡበከር
Seledadotio
Seledadotio
13 hours ago
ይህንን ያውቃሉ❓❓
የሲቪል ምዝገባና ነዋሪዎች አገልግሎት ኤጀንሲ በወረዳ ጽሕፈት ቤቶቹ የሚሰጣቸውን የኩነት (የልደት፣ ጋብቻ፣ ፍቺ፣ ሞትና ጉዲፈቻ) ማስረጃዎችን የማረጋገጥ አገልግሎት ለማግኘት ተገልጋዮች ይዘው መቅረብ የሚገባቸው ቅድመ ሁኔታዎችንና ደጋፊ ሰነዶችን እንደሚከተለው ያሳውቃል።
ለእያንዳንዱ አገልግሎት የሚያስፈልጉ ልዩ ቅድመ ሁኔታዎች
1. የልደት ሰርተፍኬት ለማረጋገጥ
ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች ለሆኑ፦ በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የልደት ማስረጃ
አገልግሎቱ የሚሰጠው ከሁለቱ አንዱ ወላጅ በአካል ሲገኝ ነው (የወላጆች የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት ያስፈልጋል)።
ምዝገባው በሞግዚትነት ከሆነ የፍርድ ቤት የሞግዚትነት ውሳኔ ሰነድ መቅረብ አለበት።
ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ ለሆኑ፦ ባለጉዳዩ በአካል መቅረብ አለበት። በአካል መቅረብ ካልቻለ፣ ጉዳዩን የሚገልጽ ልዩ ውክልና ከወካይና ተወካይ የታደሰ መታወቂያ/ፓስፖርት ጋር ማቅረብ ይኖርበታል።
2. የጋብቻ ማስረጃ ለማረጋገጥ
በክፍለ ከተማ ወይም በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የጋብቻ ማስረጃ መያዝ።
ለግልባጭ ወይም ለእርማት አገልግሎት፦ የተጋቢዎች ሁለት ሁለት (2) ጉርድ ፎቶግራፍ።
በውክልና የሚጠየቅ ከሆነ (ለእርማት፣ ዕድሳትና ግልባጭ)፦ ባልና ሚስት ጉዳዩን በግልጽ የሚያሳይ ውክልና፣ የወካዮች እና የተወካይ የታደሰ መታወቂያ/ፓስፖርት ወይም የታደሰ የመኖሪያ ፈቃድ ማቅረብ አለባቸው።
3. የፍቺ ማስረጃ ለማረጋገጥ
በክፍለ ከተማ ወይም በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የፍቺ ማስረጃ
የህግ አስገዳጅነቱ የተረጋገጠ የፍርድ ቤት የፍቺ ውሳኔ ሰነድ መቅረብ አለበት።
4. የጉዲፈቻ ሰርተፍኬት ለማረጋገጥ
በወረዳ የተመዘገበ የጉዲፈቻ ሰርተፍኬት እና የፍርድ ቤት ውሳኔ ሰነድ
ጉዲፈቻ አድራጊዎች የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት በመያዝ በአካል መቅረብ አለባቸው።
ጉዳዩ በውክልና ከሆነ፣ይህንኑ የሚያስረዳ ልዩ ውክልና መቅረብ አለበት።
5. የሞት ማስረጃ ለማረጋገጥ
በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የሞት ማስረጃ የማረጋገጥ አገልግሎት ለማግኘት
ከሟች ጋር አብሮ ይኖር የነበረ ሰው፣ እርሱ ከሌለ የሟች የስጋ ወይም የጋብቻ ዘመዶች፣ እነዚህም ከሌሉ የቅርብ ጎረቤት ወይም ስለሟቹ መሞት የሚያውቅ ማንኛውም ሰው የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት በማቅረብ ማስመዝገብና ማረጋገጥ ይችላል።
ሟች የውጭ ሀገር ዜጋ ከሆነ ከሆስፒታል የተሰጠ የማሳወቂያ ወረቀት መቅረብ አለበት።
ማሳሰቢያ፡- ለሁሉም ከላይ ለተዘረዘሩት የኩነት አገልግሎቶችን ለማግኘት የሚያስፈልግ ደጋፊ ሰነድ
• የታደሰ ብሔራዊ መታወቂያ / የታደሰ ፓስፖርት / የትውልደ ኢትዮጵያ የውጭ ዜግነት መታወቂያ (የቢጫ ካርድ)።
• ከዝቅተኛው አስተዳደር ጽ/ቤት መደበኛ ነዋሪነቱን የሚገልጽ የድጋፍ ደብዳቤ / የስደተኛነት ማስረጃ / የመኖሪያ ፈቃድ።
• ከሚሰራበት መስሪያ ቤት ባልደረባነቱንና ዜግነቱን የሚገልጽ የድጋፍ ደብዳቤ ከመስሪያ ቤቱ መታወቂያ ጋር / የመከላከያ ሰራዊት ከሆነ የመከላከያ ሰራዊት መታወቂያ መያዝ
• የጠፋ ሰርተፍኬት ግልባጭ ለመውሰድ፦ ከፖሊስ የተሰጠ የጠፋ ሰነድ ማረጋገጫ ማቅረብ ግዴታ ነው።
• ከወረዳ የመጡ ማስረጃዎች፦ ከወረዳው ስለመውጣታቸው የሚገልጽ ማረጋገጫ ደብዳቤ ያስፈልጋቸዋል።
• ከክፍለ ከተማ የመጡ ማስረጃዎች፦ ከሰነዱ በስተጀርባ የማረጋገጫ ማህተም ማረፍ ይኖርበታል።
• ከውጭ ሀገር የሚመጣ ውክልና፦ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና በፌደራል ሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ ኤጀንሲ መረጋገጥ አለበት።
Seledadotio
Seledadotio
የሲቪል ምዝገባና ነዋሪዎች አገልግሎት ኤጀንሲ በወረዳ ጽሕፈት ቤቶቹ የሚሰጣቸውን የኩነት (የልደት፣ ጋብቻ፣ ፍቺ፣ ሞትና ጉዲፈቻ) ማስረጃዎችን የማረጋገጥ አገልግሎት ለማግኘት ተገልጋዮች ይዘው መቅረብ የሚገባቸው ቅድመ ሁኔታዎችንና ደጋፊ ሰነዶችን እንደሚከተለው ያሳውቃል።
ለእያንዳንዱ አገልግሎት የሚያስፈልጉ ልዩ ቅድመ ሁኔታዎች
1. የልደት ሰርተፍኬት ለማረጋገጥ
ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች ለሆኑ፦ በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የልደት ማስረጃ
አገልግሎቱ የሚሰጠው ከሁለቱ አንዱ ወላጅ በአካል ሲገኝ ነው (የወላጆች የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት ያስፈልጋል)።
ምዝገባው በሞግዚትነት ከሆነ የፍርድ ቤት የሞግዚትነት ውሳኔ ሰነድ መቅረብ አለበት።
ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ ለሆኑ፦ ባለጉዳዩ በአካል መቅረብ አለበት። በአካል መቅረብ ካልቻለ፣ ጉዳዩን የሚገልጽ ልዩ ውክልና ከወካይና ተወካይ የታደሰ መታወቂያ/ፓስፖርት ጋር ማቅረብ ይኖርበታል።
2. የጋብቻ ማስረጃ ለማረጋገጥ
በክፍለ ከተማ ወይም በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የጋብቻ ማስረጃ መያዝ።
ለግልባጭ ወይም ለእርማት አገልግሎት፦ የተጋቢዎች ሁለት ሁለት (2) ጉርድ ፎቶግራፍ።
በውክልና የሚጠየቅ ከሆነ (ለእርማት፣ ዕድሳትና ግልባጭ)፦ ባልና ሚስት ጉዳዩን በግልጽ የሚያሳይ ውክልና፣ የወካዮች እና የተወካይ የታደሰ መታወቂያ/ፓስፖርት ወይም የታደሰ የመኖሪያ ፈቃድ ማቅረብ አለባቸው።
3. የፍቺ ማስረጃ ለማረጋገጥ
በክፍለ ከተማ ወይም በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የፍቺ ማስረጃ
የህግ አስገዳጅነቱ የተረጋገጠ የፍርድ ቤት የፍቺ ውሳኔ ሰነድ መቅረብ አለበት።
4. የጉዲፈቻ ሰርተፍኬት ለማረጋገጥ
በወረዳ የተመዘገበ የጉዲፈቻ ሰርተፍኬት እና የፍርድ ቤት ውሳኔ ሰነድ
ጉዲፈቻ አድራጊዎች የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት በመያዝ በአካል መቅረብ አለባቸው።
ጉዳዩ በውክልና ከሆነ፣ይህንኑ የሚያስረዳ ልዩ ውክልና መቅረብ አለበት።
5. የሞት ማስረጃ ለማረጋገጥ
በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የሞት ማስረጃ የማረጋገጥ አገልግሎት ለማግኘት
ከሟች ጋር አብሮ ይኖር የነበረ ሰው፣ እርሱ ከሌለ የሟች የስጋ ወይም የጋብቻ ዘመዶች፣ እነዚህም ከሌሉ የቅርብ ጎረቤት ወይም ስለሟቹ መሞት የሚያውቅ ማንኛውም ሰው የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት በማቅረብ ማስመዝገብና ማረጋገጥ ይችላል።
ሟች የውጭ ሀገር ዜጋ ከሆነ ከሆስፒታል የተሰጠ የማሳወቂያ ወረቀት መቅረብ አለበት።
ማሳሰቢያ፡- ለሁሉም ከላይ ለተዘረዘሩት የኩነት አገልግሎቶችን ለማግኘት የሚያስፈልግ ደጋፊ ሰነድ
• የታደሰ ብሔራዊ መታወቂያ / የታደሰ ፓስፖርት / የትውልደ ኢትዮጵያ የውጭ ዜግነት መታወቂያ (የቢጫ ካርድ)።
• ከዝቅተኛው አስተዳደር ጽ/ቤት መደበኛ ነዋሪነቱን የሚገልጽ የድጋፍ ደብዳቤ / የስደተኛነት ማስረጃ / የመኖሪያ ፈቃድ።
• ከሚሰራበት መስሪያ ቤት ባልደረባነቱንና ዜግነቱን የሚገልጽ የድጋፍ ደብዳቤ ከመስሪያ ቤቱ መታወቂያ ጋር / የመከላከያ ሰራዊት ከሆነ የመከላከያ ሰራዊት መታወቂያ መያዝ
• የጠፋ ሰርተፍኬት ግልባጭ ለመውሰድ፦ ከፖሊስ የተሰጠ የጠፋ ሰነድ ማረጋገጫ ማቅረብ ግዴታ ነው።
• ከወረዳ የመጡ ማስረጃዎች፦ ከወረዳው ስለመውጣታቸው የሚገልጽ ማረጋገጫ ደብዳቤ ያስፈልጋቸዋል።
• ከክፍለ ከተማ የመጡ ማስረጃዎች፦ ከሰነዱ በስተጀርባ የማረጋገጫ ማህተም ማረፍ ይኖርበታል።
• ከውጭ ሀገር የሚመጣ ውክልና፦ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና በፌደራል ሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ ኤጀንሲ መረጋገጥ አለበት።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
15 hours ago
የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ነገ ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን ኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች ፦
⏰ ከጠዋቱ 2:00-12:00
👉 በአዳማ ሪጅን አዳማ ቆርቆሮ፣
⏰ ከጠዋቱ 2:00-11:00
አዳማ ፈትል ፋብሪካ፣ ሬድሬስ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ፣ አህዋን ፋብሪካ
⏰ ከጠዋቱ 2:30-9:00
👉 በአዳማ ሪጅን ከአዋሽ መልካሳ ወደ አዱላላና አሮሪቲ፣
⏰ ከጠዋቱ 2:30-7:00
👉 በሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን አስኮ ገብርኤል፣ ሳንሱሲ፣ እያሱ ምንጭ፣ ብርጭቆ ኮንዶሚኒየም፣ ከታ አፍያ ዴቄት፣
⏰ ከጠዋቱ 3:00 እስከ ምሽቱ 4:00 ድረስ
👉 በደቡብ አዲስ አበባ ሪጅን ኬኬ ብርድ ልብስ ፋብሪካ፣ ቂሊንጦ ኮንዶሚኒየም፣ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት፣ አስቱ ዩኒቨርስቲ እና ኢንዱስትሪ መንደር፣ ዋልያ ቢራ
⏰ ከጠዋቱ 6:00-9:00
👉 በምዕረብ አደስ አበባ ሪጅን ስልጤ ሰፈር፣ አጃምባ ኮንዶሚኒየም
⏰ ከቀኑ 7፡00- 11፡00
👉 በሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን ሸጎሌ አንበሳ ጋራዥ፣ ሸጎሌ መንደር-7፣ ፊናንስ፣ አበበ ቢቂላ፣ ኳስ ሜዳ፣ መሳለሚያ
⏰ ከቀኑ 7:30-10:30
👉 በሽረ ረጅን እደጋ አርቢ፣ ማይ ቐንታል
ስለሆነም በአካባቢው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻች የጥገና ሥራው ተጠናቆ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትእግስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
Seledadotio
Seledadotio
ነገ ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን ኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች ፦
⏰ ከጠዋቱ 2:00-12:00
👉 በአዳማ ሪጅን አዳማ ቆርቆሮ፣
⏰ ከጠዋቱ 2:00-11:00
አዳማ ፈትል ፋብሪካ፣ ሬድሬስ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ፣ አህዋን ፋብሪካ
⏰ ከጠዋቱ 2:30-9:00
👉 በአዳማ ሪጅን ከአዋሽ መልካሳ ወደ አዱላላና አሮሪቲ፣
⏰ ከጠዋቱ 2:30-7:00
👉 በሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን አስኮ ገብርኤል፣ ሳንሱሲ፣ እያሱ ምንጭ፣ ብርጭቆ ኮንዶሚኒየም፣ ከታ አፍያ ዴቄት፣
⏰ ከጠዋቱ 3:00 እስከ ምሽቱ 4:00 ድረስ
👉 በደቡብ አዲስ አበባ ሪጅን ኬኬ ብርድ ልብስ ፋብሪካ፣ ቂሊንጦ ኮንዶሚኒየም፣ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት፣ አስቱ ዩኒቨርስቲ እና ኢንዱስትሪ መንደር፣ ዋልያ ቢራ
⏰ ከጠዋቱ 6:00-9:00
👉 በምዕረብ አደስ አበባ ሪጅን ስልጤ ሰፈር፣ አጃምባ ኮንዶሚኒየም
⏰ ከቀኑ 7፡00- 11፡00
👉 በሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን ሸጎሌ አንበሳ ጋራዥ፣ ሸጎሌ መንደር-7፣ ፊናንስ፣ አበበ ቢቂላ፣ ኳስ ሜዳ፣ መሳለሚያ
⏰ ከቀኑ 7:30-10:30
👉 በሽረ ረጅን እደጋ አርቢ፣ ማይ ቐንታል
ስለሆነም በአካባቢው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻች የጥገና ሥራው ተጠናቆ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትእግስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
Seledadotio
Seledadotio
16 hours ago
ኢራን በጦርነቱ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተከሰተ ከፍተኛ የኑሮ ውድነት አስተናገደች
በእስራኤል - አሜሪካና እና ኢራን መካከል ያለው ጦርነት በኢራን የኑሮ ውድነቱን አንሮታል ተብሏል።
በዚህም በግንቦት ወር ብቻ የኑሮ ውድነቱ 77.2% ሆኖ መመዝገቡን አሀዛዊ መረጃዎች አመላክተዋል።
ይህም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተከሰተ ከፍተኛ የኑሮ ውድነት ሆኗል ተብሏል።
በተያያዘ፣ ኢራን በባህሬን እና ኩዌት ላይ ጥቃት ማድረሷ ተገልጿል።
ዩናይትድስቴትስ በበኩሏ የኢራን ወታደራዊ ስፍራዎችን መደብደቧ ተነግሯል።
zena_maezen
zena_maezenኢራን በጦርነቱ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተከሰተ ከፍተኛ የኑሮ ውድነት አስተናገደች
በእስራኤል - አሜሪካና እና ኢራን መካከል ያለው ጦርነት በኢራን የኑሮ ውድነቱን አንሮታል ተብሏል።
በዚህም በግንቦት ወር ብቻ የኑሮ ውድነቱ 77.2% ሆኖ መመዝገቡን አሀዛዊ መረጃዎች አመላክተዋል።
ይህም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተከሰተ ከፍተኛ የኑሮ ውድነት ሆኗል ተብሏል።
በተያያዘ፣ ኢራን በባህሬን እና ኩዌት ላይ ጥቃት ማድረሷ ተገልጿል።
ዩናይትድስቴትስ በበኩሏ የኢራን ወታደራዊ ስፍራዎችን መደብደቧ ተነግሯል።
Seledadotio
Seledadotio
በእስራኤል - አሜሪካና እና ኢራን መካከል ያለው ጦርነት በኢራን የኑሮ ውድነቱን አንሮታል ተብሏል።
በዚህም በግንቦት ወር ብቻ የኑሮ ውድነቱ 77.2% ሆኖ መመዝገቡን አሀዛዊ መረጃዎች አመላክተዋል።
ይህም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተከሰተ ከፍተኛ የኑሮ ውድነት ሆኗል ተብሏል።
በተያያዘ፣ ኢራን በባህሬን እና ኩዌት ላይ ጥቃት ማድረሷ ተገልጿል።
ዩናይትድስቴትስ በበኩሏ የኢራን ወታደራዊ ስፍራዎችን መደብደቧ ተነግሯል።
zena_maezen
zena_maezenኢራን በጦርነቱ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተከሰተ ከፍተኛ የኑሮ ውድነት አስተናገደች
በእስራኤል - አሜሪካና እና ኢራን መካከል ያለው ጦርነት በኢራን የኑሮ ውድነቱን አንሮታል ተብሏል።
በዚህም በግንቦት ወር ብቻ የኑሮ ውድነቱ 77.2% ሆኖ መመዝገቡን አሀዛዊ መረጃዎች አመላክተዋል።
ይህም ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተከሰተ ከፍተኛ የኑሮ ውድነት ሆኗል ተብሏል።
በተያያዘ፣ ኢራን በባህሬን እና ኩዌት ላይ ጥቃት ማድረሷ ተገልጿል።
ዩናይትድስቴትስ በበኩሏ የኢራን ወታደራዊ ስፍራዎችን መደብደቧ ተነግሯል።
Seledadotio
Seledadotio
17 hours ago
ኢራን የኩዌት አየር መንገድን በዚ መልኩ ነው ያወደመችው በዚህ ጥቃት 63 ሰዎች ቀላል እና ከባድ ጉዳት የደርሰባቸው ሲሆን የሞቾች ቁጥርም ከአንድ ሊበልጥ እንደሚችል እየተናገሩ ይገኛል"
Seledadotio
Seledadotio
Seledadotio
Seledadotio
18 hours ago
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት መልእክት አስተላለፉ
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያን እና በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ ::
"በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው።
ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን።
በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን::"
Seledadotio
Seledadotio
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያን እና በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ ::
"በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው።
ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን።
በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን::"
Seledadotio
Seledadotio
21 hours ago
🌟 𝗥𝗘𝗔𝗟𝗜𝗧𝗬 𝗥𝗘𝗔𝗟 𝗘𝗦𝗧𝗔𝗧𝗘: 𝗘𝗫𝗖𝗟𝗨𝗦𝗜𝗩𝗘 𝗥𝗘-𝗥𝗘𝗟𝗘𝗔𝗦𝗘! 🌟
Message To Ermiyas Realtor on Whatspp ; https://wa.me/c/2519681970...
Tellegram ; t.me/Ermihome
📞 09-68-19-70-96 ይደውሉ ።
09 19-89-03-91
✅ 100% ያለቁ የተናጠል ካርታ ያላቸዉ በቦሌ ደንበል እና በቦሌ መድሐኒያለም ( 100%) ያለቁ ይፍጠኑ ።
@@ ባለ ሁለት መኝታ 137 ካሬ ።
@@ ባለ ሶስት መኝታ 186 ፣ 199 ፣ 212 ካሬዎች።
✅ ዛሬዉኑ የሚረከቡት
📌በሳር ቤት ( ካናዳ ኤምባሲ አጠገብ )
✅ 100% ያለቁ የተናጠል ካርታ ያላቸዉ
👉ከባለ 2 - 3 መኝታ
👉ባለ 1 መኝታ - 94 ካሬ እና 98 ካሬ
👉ባለ 2 መኝታ - 104 ካሬ, 111 ካሬ ,124 ካ, 119ካሬ ።
ባለ ሶስት መኝታ 143 ካሬዎች ።
📌ቦሌ ደንበል ጀርባ
✅ ከባለ 1 - 3መኝታ ሽያጭ ጀምረናል!
✅ በ 10% ቅድመ ክፍያ
✅ እስከ 30% በሚደርስ ልዩ ቅናሽ
✅በረዥም እና ምቹ አከፋፈል
👉ባለ 1 መኝታ - 86 ካሬ
👉ባለ 2 መኝታ - 137 ካሬ እና 139 ካሬ
👉ባለ 3 መኝታ - 171 ካሬ እና 186 ካሬ
📌በአፍሪካ ህብረት ( ሳር ቤት ላይ )
👉የንግድ ሱቆች እና
👉የመኖሪያ ቤት አፓርታማ
👉ከ 10 ካሬ እሰከ 80 ካሬ ለ ሱቅና ለቢሮ የሚሆኑ ።
👉ባለ 2 መኝታ - 110 ካሬ
👉ባለ 2 መኝታ - 165 ካሬ እና 192 ካሬ
👉ባለ 3 መኝታ - 215 ካሬ
Message Ermiyas Realtor on Whatspp ; https://wa.me/c/2519681970...
Tellegram ; t.me/Ermihome
☎️ 09-68-19-70-96 ይደዉሉ ::
09-19-89-03-91
#realityrealestate #smartbuying
Message To Ermiyas Realtor on Whatspp ; https://wa.me/c/2519681970...
Tellegram ; t.me/Ermihome
📞 09-68-19-70-96 ይደውሉ ።
09 19-89-03-91
✅ 100% ያለቁ የተናጠል ካርታ ያላቸዉ በቦሌ ደንበል እና በቦሌ መድሐኒያለም ( 100%) ያለቁ ይፍጠኑ ።
@@ ባለ ሁለት መኝታ 137 ካሬ ።
@@ ባለ ሶስት መኝታ 186 ፣ 199 ፣ 212 ካሬዎች።
✅ ዛሬዉኑ የሚረከቡት
📌በሳር ቤት ( ካናዳ ኤምባሲ አጠገብ )
✅ 100% ያለቁ የተናጠል ካርታ ያላቸዉ
👉ከባለ 2 - 3 መኝታ
👉ባለ 1 መኝታ - 94 ካሬ እና 98 ካሬ
👉ባለ 2 መኝታ - 104 ካሬ, 111 ካሬ ,124 ካ, 119ካሬ ።
ባለ ሶስት መኝታ 143 ካሬዎች ።
📌ቦሌ ደንበል ጀርባ
✅ ከባለ 1 - 3መኝታ ሽያጭ ጀምረናል!
✅ በ 10% ቅድመ ክፍያ
✅ እስከ 30% በሚደርስ ልዩ ቅናሽ
✅በረዥም እና ምቹ አከፋፈል
👉ባለ 1 መኝታ - 86 ካሬ
👉ባለ 2 መኝታ - 137 ካሬ እና 139 ካሬ
👉ባለ 3 መኝታ - 171 ካሬ እና 186 ካሬ
📌በአፍሪካ ህብረት ( ሳር ቤት ላይ )
👉የንግድ ሱቆች እና
👉የመኖሪያ ቤት አፓርታማ
👉ከ 10 ካሬ እሰከ 80 ካሬ ለ ሱቅና ለቢሮ የሚሆኑ ።
👉ባለ 2 መኝታ - 110 ካሬ
👉ባለ 2 መኝታ - 165 ካሬ እና 192 ካሬ
👉ባለ 3 መኝታ - 215 ካሬ
Message Ermiyas Realtor on Whatspp ; https://wa.me/c/2519681970...
Tellegram ; t.me/Ermihome
☎️ 09-68-19-70-96 ይደዉሉ ::
09-19-89-03-91
#realityrealestate #smartbuying
21 hours ago
የምርጫ ቦርድ ይፋዊ መግለጫ እስከሚሰጥ ድረስ ማንኛውም አካል ራሱን አሸናፊ አድርጎ ከመግለጽ ይቆጠብ":-ኢሰመጉ‼️
ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ተከትሎ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) ባወጣው የምርጫ መታዘብ ቅድመ መግለጫ ላይ ያነሳቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
ጥብቅ ማሳሰቢያ፦የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ (NEBE) ይፋዊ መግለጫ እስከሚሰጥ ድረስ ማንኛውም ግለሰብ፣ የፖለቲካ ድርጅት ወይም የማኅበራዊ ሚዲያ አንቂዎች ጊዜያዊ ውጤት በማጋራት ማኅበረሰቡን ከማደናገር እንዲቆጠቡ አሳስቧል።
የምልከታ ስፋት፦ኢሰመጉ ባሰማራቸው 433 ታዛቢዎች አማካኝነት ከ800 በላይ የምርጫ ጣቢያዎችን ተከታትሏል።
⚠️ የተስተዋሉ ዋና ዋና ተግዳሮቶች፦
* የአዲሱ ዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ሥልት መጀመሩ የሚበረታታ ቢሆንም፣ የአስፈጻሚዎች ሥልጠና ማነስ ለመራጮች መጨናነቅና ለሰዓት መራዘም ምክንያት ሆኗል።
* በበርካታ አካባቢዎች የትራንስፖርት መቋረጥ፣ በአዲስ አበባ የሰልፍ አስተባባሪዎች ማነስ እና በመራጮች ላይ የደረሰ የእንግልት ሰዓት።
* በሐዋሳና አካባቢው በሚገኙ ውስን ጣቢያዎች የምርጫ አስፈጻሚዎች በሚስጥራዊ ድምፅ መስጫ ቦታ በመግባት የሥነ-ልቦና ጫና ማድረጋቸው እና ያልተመረጡ ወረቀቶችን ወደ ሳጥን ማስገባት የመሳሰሉ የነፃነት መብትን የገደቡ ክስተቶች መታየታቸው።
✅ በበጎ ጎን የተነሱ ነጥቦች፦
* የመራጮች ከፍተኛ ተነሳሽነት፣ በቂ የቁሳቁስ አቅርቦት እና በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች የጎላ የጸጥታ መደፍረስ ሳይኖር ሂደቱ መጠናቀቁ።
"ኢሰመጉ ምርጫ ቦርድ በአንጻራዊነት ስኬታማና ሰላማዊ ምርጫ ማከናወኑን በመግለጽ ዕውቅና የሰጠ ሲሆን፣ በቀጣይ ግን የተስተዋሉ ችግሮችን በዝርዝር ለይቶ እንዲያርም ጥሪ አቅርቧል።"
Seledadotio
Seledadotio
ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ተከትሎ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) ባወጣው የምርጫ መታዘብ ቅድመ መግለጫ ላይ ያነሳቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
ጥብቅ ማሳሰቢያ፦የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ (NEBE) ይፋዊ መግለጫ እስከሚሰጥ ድረስ ማንኛውም ግለሰብ፣ የፖለቲካ ድርጅት ወይም የማኅበራዊ ሚዲያ አንቂዎች ጊዜያዊ ውጤት በማጋራት ማኅበረሰቡን ከማደናገር እንዲቆጠቡ አሳስቧል።
የምልከታ ስፋት፦ኢሰመጉ ባሰማራቸው 433 ታዛቢዎች አማካኝነት ከ800 በላይ የምርጫ ጣቢያዎችን ተከታትሏል።
⚠️ የተስተዋሉ ዋና ዋና ተግዳሮቶች፦
* የአዲሱ ዲጂታል የመራጮች ምዝገባ ሥልት መጀመሩ የሚበረታታ ቢሆንም፣ የአስፈጻሚዎች ሥልጠና ማነስ ለመራጮች መጨናነቅና ለሰዓት መራዘም ምክንያት ሆኗል።
* በበርካታ አካባቢዎች የትራንስፖርት መቋረጥ፣ በአዲስ አበባ የሰልፍ አስተባባሪዎች ማነስ እና በመራጮች ላይ የደረሰ የእንግልት ሰዓት።
* በሐዋሳና አካባቢው በሚገኙ ውስን ጣቢያዎች የምርጫ አስፈጻሚዎች በሚስጥራዊ ድምፅ መስጫ ቦታ በመግባት የሥነ-ልቦና ጫና ማድረጋቸው እና ያልተመረጡ ወረቀቶችን ወደ ሳጥን ማስገባት የመሳሰሉ የነፃነት መብትን የገደቡ ክስተቶች መታየታቸው።
✅ በበጎ ጎን የተነሱ ነጥቦች፦
* የመራጮች ከፍተኛ ተነሳሽነት፣ በቂ የቁሳቁስ አቅርቦት እና በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች የጎላ የጸጥታ መደፍረስ ሳይኖር ሂደቱ መጠናቀቁ።
"ኢሰመጉ ምርጫ ቦርድ በአንጻራዊነት ስኬታማና ሰላማዊ ምርጫ ማከናወኑን በመግለጽ ዕውቅና የሰጠ ሲሆን፣ በቀጣይ ግን የተስተዋሉ ችግሮችን በዝርዝር ለይቶ እንዲያርም ጥሪ አቅርቧል።"
Seledadotio
Seledadotio
22 hours ago
⚡️ "የኢራን ድሮኖች በኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ከባድ ጥቃት ሰነዘሩ"
በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን ቀጠናዊ ጦርነት ተከትሎ፣ የኢራን ድሮኖች በኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ዋናው የመንገደኞች ተርሚናል (T1) ላይ ከባድ ጥቃት ማድረሳቸውን የኩዌት ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን እና የመከላከያ ሚኒስቴር በይፋ አስታውቀዋል። ጥቃቱ ከፍተኛ ውድመት ማድረሱንና በርካታ ሰዎችን ማቁሰሉ ተገልጿል።
📌 ጥቃቱን ተከትሎ የኩዌት ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የአደጋ ጊዜ እቅድን ያነቀሳቀሰ ሲሆን፣ ሁሉንም የንግድ በረራዎች በማቋረጥ ወደ ሀገር ውስጥ ሊገቡ የነበሩ አውሮፕላኖችን ወደ ጎረቤት ሀገራት አማራጭ አውሮፕላን ማረፊያዎች እንዲቀየሩ አድርጓል።
Seledadotio
Seledadotio
በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን ቀጠናዊ ጦርነት ተከትሎ፣ የኢራን ድሮኖች በኩዌት ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ዋናው የመንገደኞች ተርሚናል (T1) ላይ ከባድ ጥቃት ማድረሳቸውን የኩዌት ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን እና የመከላከያ ሚኒስቴር በይፋ አስታውቀዋል። ጥቃቱ ከፍተኛ ውድመት ማድረሱንና በርካታ ሰዎችን ማቁሰሉ ተገልጿል።
📌 ጥቃቱን ተከትሎ የኩዌት ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የአደጋ ጊዜ እቅድን ያነቀሳቀሰ ሲሆን፣ ሁሉንም የንግድ በረራዎች በማቋረጥ ወደ ሀገር ውስጥ ሊገቡ የነበሩ አውሮፕላኖችን ወደ ጎረቤት ሀገራት አማራጭ አውሮፕላን ማረፊያዎች እንዲቀየሩ አድርጓል።
Seledadotio
Seledadotio
23 hours ago
የአሜሪካ መንግስት በአፍሪካ የቪዛ አገልግሎት መስጫ ቦታዎችን ወደ 20 ብቻ ሊቀንስ ነው‼️
👉 አዲስ አበባ አገልግሎቷን እንደምትቀጥል ተረጋግጧል
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአፍሪካ አህጉር የሚገኙ የቪዛ ማስተናገጃ ማዕከላቱን ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ለመቀነስ መወሰኑን ይፋ አደረገ።
ይህ አዲስ መመሪያ የትራምፕ አስተዳደር በስደት ላይ የጀመረውን ጠንካራ የቁጥጥር ፖሊሲ ይበልጥ ለማጥበቅ ከሚያደርገው ጥረት ጋር የተያያዘ ነው።
እስካሁን ድረስ በአፍሪካ አህጉር ውስጥ ወደ 50 የሚጠጉ የአሜሪካ ኤምባሲዎችና ቆንስላዎች የቪዛ ማመልከቻዎችን ሲቀበሉ የነበረ ቢሆንም፣ አዲሱ እቅድ ይህንን ቁጥር ወደ 20 "ማዕከላት" ብቻ ዝቅ የሚያደርግ ይሆናል።
እንደ አሶሺየትድ ፕሬስ ዘገባ እና ከውስጥ ባለስልጣናት በተገኘ መረጃ መሠረት፣ ይሄው አሰራር በሚቀጥሉት ሳምንታት (በሰኔ ወር ውስጥ) ተግባራዊ መሆን ይጀምራል።
በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርኮ ሩቢዮ በፀደቀው በዚህ መመሪያ መሠረት፣ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ ሙሉ የቪዛ አገልግሎት መስጠቷን እንድትቀጥል ከተመረጡት 20 ጥቂት ማዕከላት መካከል አንዷ ሆናለች።
ይህም ማለት በኢትዮጵያ የሚገኙ አመልካቾች ያለምንም እንግልት መደበኛ የቪዛ አገልግሎታቸውን ከአዲስ አበባ ማግኘት ይችላሉ።
ይሁን እንጂ ይህ ውሳኔ ማዕከል ባልሆኑ ሀገራት ዜጎች ላይ ከፍተኛ የኢኮኖሚና የጉዞ ጫና ያሳድራል።
በእነዚህ ሀገራት የሚገኙ የአሜሪካ ቆንስላዎች መደበኛ የቪዛ አገልግሎት መስጠታቸውን የሚያቆሙ በመሆኑ፣ ዜጎቹ ቪዛ ለማግኘት ድንበር አቋርጠው አዲስ አበባን ወደመሳሰሉ የቪዛ ማዕከላት ለመጓዝ ይገደዳሉ። ይህም ተጨማሪ የጉዞ ወጪን እና የጊዜ መዘግየትን ያስከትላል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ አገልግሎታቸው በሚቀነስባቸው ሀገራት የሚገኙ ኤምባሲዎች ሙሉ በሙሉ የማይዘጉ ሲሆን፣ ለአሜሪካ ዜጎች የሚሰጡ ድንገተኛ ድጋፎችን እና ልዩ የዲፕሎማቲክ ጉዳዮችን ማስተናገዳቸውን ይቀጥላሉ ተብሏል።
Seledadotio
Seledadotio
👉 አዲስ አበባ አገልግሎቷን እንደምትቀጥል ተረጋግጧል
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአፍሪካ አህጉር የሚገኙ የቪዛ ማስተናገጃ ማዕከላቱን ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ለመቀነስ መወሰኑን ይፋ አደረገ።
ይህ አዲስ መመሪያ የትራምፕ አስተዳደር በስደት ላይ የጀመረውን ጠንካራ የቁጥጥር ፖሊሲ ይበልጥ ለማጥበቅ ከሚያደርገው ጥረት ጋር የተያያዘ ነው።
እስካሁን ድረስ በአፍሪካ አህጉር ውስጥ ወደ 50 የሚጠጉ የአሜሪካ ኤምባሲዎችና ቆንስላዎች የቪዛ ማመልከቻዎችን ሲቀበሉ የነበረ ቢሆንም፣ አዲሱ እቅድ ይህንን ቁጥር ወደ 20 "ማዕከላት" ብቻ ዝቅ የሚያደርግ ይሆናል።
እንደ አሶሺየትድ ፕሬስ ዘገባ እና ከውስጥ ባለስልጣናት በተገኘ መረጃ መሠረት፣ ይሄው አሰራር በሚቀጥሉት ሳምንታት (በሰኔ ወር ውስጥ) ተግባራዊ መሆን ይጀምራል።
በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርኮ ሩቢዮ በፀደቀው በዚህ መመሪያ መሠረት፣ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ ሙሉ የቪዛ አገልግሎት መስጠቷን እንድትቀጥል ከተመረጡት 20 ጥቂት ማዕከላት መካከል አንዷ ሆናለች።
ይህም ማለት በኢትዮጵያ የሚገኙ አመልካቾች ያለምንም እንግልት መደበኛ የቪዛ አገልግሎታቸውን ከአዲስ አበባ ማግኘት ይችላሉ።
ይሁን እንጂ ይህ ውሳኔ ማዕከል ባልሆኑ ሀገራት ዜጎች ላይ ከፍተኛ የኢኮኖሚና የጉዞ ጫና ያሳድራል።
በእነዚህ ሀገራት የሚገኙ የአሜሪካ ቆንስላዎች መደበኛ የቪዛ አገልግሎት መስጠታቸውን የሚያቆሙ በመሆኑ፣ ዜጎቹ ቪዛ ለማግኘት ድንበር አቋርጠው አዲስ አበባን ወደመሳሰሉ የቪዛ ማዕከላት ለመጓዝ ይገደዳሉ። ይህም ተጨማሪ የጉዞ ወጪን እና የጊዜ መዘግየትን ያስከትላል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ አገልግሎታቸው በሚቀነስባቸው ሀገራት የሚገኙ ኤምባሲዎች ሙሉ በሙሉ የማይዘጉ ሲሆን፣ ለአሜሪካ ዜጎች የሚሰጡ ድንገተኛ ድጋፎችን እና ልዩ የዲፕሎማቲክ ጉዳዮችን ማስተናገዳቸውን ይቀጥላሉ ተብሏል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
24 hours ago
አሜሪካና ኢራን ተጠቃቁ
አሜሪካ በኢራን ገ’ሽም(ቀሽም) ደሴት ላይ ጥቃት አደረሰች።
ቴህራን በበኩሏ ኩዌትን እና ባህሬንን በምላሹ ማጥቃቷን አሳውቃለች።
የአሜሪካ ጦር ራስን ለመከላከል የተሰነዘረ ጥቃት ነው ቢለውም ተኩስ አቁሙን ገደል የከተተ ዕርምጃ ነው በሚል ትችት ተሰዝሮበታል።
ኢራንም በሚሳዔል እና ሰው አልባ አውሮፕላን የአሜሪካን ዒላማዎች በኩዌትና ባህሬን መምታቷን ቀጥላለች።
ዋሽንግተን ወታደራዊ እርምጃ እየወሰደች ቢሆንም የተኩስ አቁም ድርድሩ አሁንም እንደቀጠለ ነው ብላለች።
ጥቃቱን ያደረሰው የአሜሪካው ማዕከላዊ ዕዝ (ሴንት ኮም ) እንደሆነም ተረጋግጧል።
ዕዙ ሁለት በኩዌት ላይ እንዲሁም በባህሬን ላይ ሶስት ሚሳኤሎችን ቴህራን ብታስወነጭፍም ዒላማቸውን ሳይመቱ ወድቀዋል አሊያም አየር ላይ ከሽፈዋል በሚል ሀሳብ ሰጥቷል።
የኩዌት ጦር የአየር መከላከያ ስርዓቶች ሚሳዔሎችንና ድሮኖችን በማክሸፉ ስራ ላይ ተጠመጃለሁም ብሏል።
በባህሬንም ከፍተኛ የአደጋ መጥቷል ድምፅ ሰጪ ደውሎች ማስጠንቀቂያ ሲሰጡ አድረዋል ።
አልጀዚራ እንዳስነበበው።
Seledadotio
Seledadotio
አሜሪካ በኢራን ገ’ሽም(ቀሽም) ደሴት ላይ ጥቃት አደረሰች።
ቴህራን በበኩሏ ኩዌትን እና ባህሬንን በምላሹ ማጥቃቷን አሳውቃለች።
የአሜሪካ ጦር ራስን ለመከላከል የተሰነዘረ ጥቃት ነው ቢለውም ተኩስ አቁሙን ገደል የከተተ ዕርምጃ ነው በሚል ትችት ተሰዝሮበታል።
ኢራንም በሚሳዔል እና ሰው አልባ አውሮፕላን የአሜሪካን ዒላማዎች በኩዌትና ባህሬን መምታቷን ቀጥላለች።
ዋሽንግተን ወታደራዊ እርምጃ እየወሰደች ቢሆንም የተኩስ አቁም ድርድሩ አሁንም እንደቀጠለ ነው ብላለች።
ጥቃቱን ያደረሰው የአሜሪካው ማዕከላዊ ዕዝ (ሴንት ኮም ) እንደሆነም ተረጋግጧል።
ዕዙ ሁለት በኩዌት ላይ እንዲሁም በባህሬን ላይ ሶስት ሚሳኤሎችን ቴህራን ብታስወነጭፍም ዒላማቸውን ሳይመቱ ወድቀዋል አሊያም አየር ላይ ከሽፈዋል በሚል ሀሳብ ሰጥቷል።
የኩዌት ጦር የአየር መከላከያ ስርዓቶች ሚሳዔሎችንና ድሮኖችን በማክሸፉ ስራ ላይ ተጠመጃለሁም ብሏል።
በባህሬንም ከፍተኛ የአደጋ መጥቷል ድምፅ ሰጪ ደውሎች ማስጠንቀቂያ ሲሰጡ አድረዋል ።
አልጀዚራ እንዳስነበበው።
Seledadotio
Seledadotio
1 day ago
ጎግል (Google) በሽታን ለመዋጋት 32 ሚሊዮን በቤተ ሙከራ ያደጉ ወንድ ትንኞችን ሊለቅ ነው
ጎግል በትንኞች አማካኝነት የሚመጡ ገዳይ በሽታዎችን ለመቆጣጠር 32 ሚሊዮን በቤተ ሙከራ የበለጸጉ ወንድ ትንኞችን በካሊፎርኒያ እና በፍሎሪዳ ግዛቶች ለመልቀቅ ከአሜሪካ የአካባቢ ጥበቃ ኤጀንሲ (EPA) ይፋዊ ፈቃድ እየጠየቀ መሆኑ ታውቋል።
ይህ በሁለት ዓመታት ውስጥ ተግባራዊ የሚደረገው ግዙፍ ፕሮጀክት፥ ጎግል በሽታ አምጪ ትንኞችን ለመቆጣጠር አዳዲስ የቴክኖሎጂ መፍትሄዎችን ለመቅረጽ እ.ኤ.አ. በ2016 የጀመረው “ዲበግ” (Debug) የተሰኘው ልዩ ተነሳሽነት አካል ነው። እንደ እቅዱ ከሆነ ድርጅቱ በየዓመቱ 16 ሚሊዮን ትንኞችን የሚለቅ ሲሆን፥ በአሁኑ ወቅት የፈቃድ ጥያቄው በኤጀንሲው (EPA) የምርመራ ሂደት ላይ ይገኛል።
እነዚህ በቤተ ሙከራ የተዘጋጁት ወንድ ትንኞች “ዎልባኪያ” (Wolbachia) በተሰኘ ባክቴሪያ እንዲያዙ ይደረጋል። እነዚህ ወንድ ትንኞች በተፈጥሮ ካሉ ሴት ትንኞች ጋር በሚራቡበት ወቅት የሚጣሉት እንቁላሎች ሳይፈልፈሉ እንዲቀሩ የሚያደርግ ሲሆን፥ ይህም በሽታ አምጪ የትንኝ ዝርያዎች በሂደት እንዲጠፉና ቁጥራቸው በከፍተኛ ደረጃ እንዲቀንስ ያደርጋል።
ህዝቡ ሊኖረው ስለሚችለው ስጋት ጎግል ሲያስረዳ፥ ወደ ተፈጥሮ የሚለቀቁት ወንድ ትንኞች ብቻ መሆናቸውን ገልጿል። ወንድ ትንኞች ሰውን የመንከስም ሆነ ደም የመምጠጥ ተፈጥሮ የሌላቸው በመሆኑ፥ በህዝብ ጤና ላይ ምንም ዓይነት ተጨማሪ የመነከስ ስጋትም ሆነ አደጋ እንደማይፈጥሩ ተረጋግጧል።
Seledadotio
Seledadotio
ጎግል በትንኞች አማካኝነት የሚመጡ ገዳይ በሽታዎችን ለመቆጣጠር 32 ሚሊዮን በቤተ ሙከራ የበለጸጉ ወንድ ትንኞችን በካሊፎርኒያ እና በፍሎሪዳ ግዛቶች ለመልቀቅ ከአሜሪካ የአካባቢ ጥበቃ ኤጀንሲ (EPA) ይፋዊ ፈቃድ እየጠየቀ መሆኑ ታውቋል።
ይህ በሁለት ዓመታት ውስጥ ተግባራዊ የሚደረገው ግዙፍ ፕሮጀክት፥ ጎግል በሽታ አምጪ ትንኞችን ለመቆጣጠር አዳዲስ የቴክኖሎጂ መፍትሄዎችን ለመቅረጽ እ.ኤ.አ. በ2016 የጀመረው “ዲበግ” (Debug) የተሰኘው ልዩ ተነሳሽነት አካል ነው። እንደ እቅዱ ከሆነ ድርጅቱ በየዓመቱ 16 ሚሊዮን ትንኞችን የሚለቅ ሲሆን፥ በአሁኑ ወቅት የፈቃድ ጥያቄው በኤጀንሲው (EPA) የምርመራ ሂደት ላይ ይገኛል።
እነዚህ በቤተ ሙከራ የተዘጋጁት ወንድ ትንኞች “ዎልባኪያ” (Wolbachia) በተሰኘ ባክቴሪያ እንዲያዙ ይደረጋል። እነዚህ ወንድ ትንኞች በተፈጥሮ ካሉ ሴት ትንኞች ጋር በሚራቡበት ወቅት የሚጣሉት እንቁላሎች ሳይፈልፈሉ እንዲቀሩ የሚያደርግ ሲሆን፥ ይህም በሽታ አምጪ የትንኝ ዝርያዎች በሂደት እንዲጠፉና ቁጥራቸው በከፍተኛ ደረጃ እንዲቀንስ ያደርጋል።
ህዝቡ ሊኖረው ስለሚችለው ስጋት ጎግል ሲያስረዳ፥ ወደ ተፈጥሮ የሚለቀቁት ወንድ ትንኞች ብቻ መሆናቸውን ገልጿል። ወንድ ትንኞች ሰውን የመንከስም ሆነ ደም የመምጠጥ ተፈጥሮ የሌላቸው በመሆኑ፥ በህዝብ ጤና ላይ ምንም ዓይነት ተጨማሪ የመነከስ ስጋትም ሆነ አደጋ እንደማይፈጥሩ ተረጋግጧል።
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
🌟 𝗥𝗘𝗔𝗟𝗜𝗧𝗬 𝗥𝗘𝗔𝗟 𝗘𝗦𝗧𝗔𝗧𝗘: 𝗘𝗫𝗖𝗟𝗨𝗦𝗜𝗩𝗘 𝗥𝗘-𝗥𝗘𝗟𝗘𝗔𝗦𝗘! 🌟
Message To Ermiyas Realtor on Whatspp ; https://wa.me/c/2519681970...
Tellegram ; t.me/Ermihome
📞 09-68-19-70-96 ይደውሉ ።
09 19-89-03-91
✅ 100% ያለቁ የተናጠል ካርታ ያላቸዉ በቦሌ ደንበል እና በቦሌ መድሐኒያለም ( 100%) ያለቁ ይፍጠኑ ።
@@ ባለ ሁለት መኝታ 137 ካሬ ።
@@ ባለ ሶስት መኝታ 186 ፣ 199 ፣ 212 ካሬዎች።
✅ ዛሬዉኑ የሚረከቡት
📌በሳር ቤት ( ካናዳ ኤምባሲ አጠገብ )
✅ 100% ያለቁ የተናጠል ካርታ ያላቸዉ
👉ከባለ 2 - 3 መኝታ
👉ባለ 1 መኝታ - 94 ካሬ እና 98 ካሬ
👉ባለ 2 መኝታ - 104 ካሬ, 111 ካሬ ,124 ካ, 119ካሬ ።
ባለ ሶስት መኝታ 143 ካሬዎች ።
📌ቦሌ ደንበል ጀርባ
✅ ከባለ 1 - 3መኝታ ሽያጭ ጀምረናል!
✅ በ 10% ቅድመ ክፍያ
✅ እስከ 30% በሚደርስ ልዩ ቅናሽ
✅በረዥም እና ምቹ አከፋፈል
👉ባለ 1 መኝታ - 86 ካሬ
👉ባለ 2 መኝታ - 137 ካሬ እና 139 ካሬ
👉ባለ 3 መኝታ - 171 ካሬ እና 186 ካሬ
📌በአፍሪካ ህብረት ( ሳር ቤት ላይ )
👉የንግድ ሱቆች እና
👉የመኖሪያ ቤት አፓርታማ
👉ከ 10 ካሬ እሰከ 80 ካሬ ለ ሱቅና ለቢሮ የሚሆኑ ።
👉ባለ 2 መኝታ - 110 ካሬ
👉ባለ 2 መኝታ - 165 ካሬ እና 192 ካሬ
👉ባለ 3 መኝታ - 215 ካሬ
Message Ermiyas Realtor on Whatspp ; https://wa.me/c/2519681970...
Tellegram ; t.me/Ermihome
☎️ 09-68-19-70-96 ይደዉሉ ::
09-19-89-03-91
#realityrealestate #smartbuying
Message To Ermiyas Realtor on Whatspp ; https://wa.me/c/2519681970...
Tellegram ; t.me/Ermihome
📞 09-68-19-70-96 ይደውሉ ።
09 19-89-03-91
✅ 100% ያለቁ የተናጠል ካርታ ያላቸዉ በቦሌ ደንበል እና በቦሌ መድሐኒያለም ( 100%) ያለቁ ይፍጠኑ ።
@@ ባለ ሁለት መኝታ 137 ካሬ ።
@@ ባለ ሶስት መኝታ 186 ፣ 199 ፣ 212 ካሬዎች።
✅ ዛሬዉኑ የሚረከቡት
📌በሳር ቤት ( ካናዳ ኤምባሲ አጠገብ )
✅ 100% ያለቁ የተናጠል ካርታ ያላቸዉ
👉ከባለ 2 - 3 መኝታ
👉ባለ 1 መኝታ - 94 ካሬ እና 98 ካሬ
👉ባለ 2 መኝታ - 104 ካሬ, 111 ካሬ ,124 ካ, 119ካሬ ።
ባለ ሶስት መኝታ 143 ካሬዎች ።
📌ቦሌ ደንበል ጀርባ
✅ ከባለ 1 - 3መኝታ ሽያጭ ጀምረናል!
✅ በ 10% ቅድመ ክፍያ
✅ እስከ 30% በሚደርስ ልዩ ቅናሽ
✅በረዥም እና ምቹ አከፋፈል
👉ባለ 1 መኝታ - 86 ካሬ
👉ባለ 2 መኝታ - 137 ካሬ እና 139 ካሬ
👉ባለ 3 መኝታ - 171 ካሬ እና 186 ካሬ
📌በአፍሪካ ህብረት ( ሳር ቤት ላይ )
👉የንግድ ሱቆች እና
👉የመኖሪያ ቤት አፓርታማ
👉ከ 10 ካሬ እሰከ 80 ካሬ ለ ሱቅና ለቢሮ የሚሆኑ ።
👉ባለ 2 መኝታ - 110 ካሬ
👉ባለ 2 መኝታ - 165 ካሬ እና 192 ካሬ
👉ባለ 3 መኝታ - 215 ካሬ
Message Ermiyas Realtor on Whatspp ; https://wa.me/c/2519681970...
Tellegram ; t.me/Ermihome
☎️ 09-68-19-70-96 ይደዉሉ ::
09-19-89-03-91
#realityrealestate #smartbuying
2 days ago
የምርጫ ውጤት‼️
በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የተረጋገጠ የመጨረሻ ውጤት ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ ይፋ ይደረጋል።
ይሁን እንጂ አጠቃላይ ውጤቱ ከመታወቁ በፊት፣ ከዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በየምርጫ ጣቢያዎቹ ላይ ጊዜያዊ ውጤቶች መለጠፍ ይጀምራሉ።
በተመሳሳይ ከግንቦት 25 እስከ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በምርጫ ክልሎች ደረጃ ጊዜያዊ ውጤቶች ይፋ እንደሚደረጉ ተገልጿል።
ምርጫ ቦርድ ከየምርጫ ክልሎቹ ውጤቶችን የመረከብ ሒደቱን ከግንቦት 26 እስከ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ የሚያከናውን ሲሆን፣ ከምርጫው ዕለት (ግንቦት 24) ጀምሮ እስከ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ ማንኛውንም ዓይነት ቅሬታዎችን የመቀበልና የማስተናገድ ሥራ እንደሚሠራ አመልክቷል።
Seledadotio
Seledadotio
በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የተረጋገጠ የመጨረሻ ውጤት ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ ይፋ ይደረጋል።
ይሁን እንጂ አጠቃላይ ውጤቱ ከመታወቁ በፊት፣ ከዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በየምርጫ ጣቢያዎቹ ላይ ጊዜያዊ ውጤቶች መለጠፍ ይጀምራሉ።
በተመሳሳይ ከግንቦት 25 እስከ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በምርጫ ክልሎች ደረጃ ጊዜያዊ ውጤቶች ይፋ እንደሚደረጉ ተገልጿል።
ምርጫ ቦርድ ከየምርጫ ክልሎቹ ውጤቶችን የመረከብ ሒደቱን ከግንቦት 26 እስከ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ የሚያከናውን ሲሆን፣ ከምርጫው ዕለት (ግንቦት 24) ጀምሮ እስከ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ ማንኛውንም ዓይነት ቅሬታዎችን የመቀበልና የማስተናገድ ሥራ እንደሚሠራ አመልክቷል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
1 day ago
የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በአራቱ ክልሎች በሚገኙ አንዳንድ ጣቢያዎች አሁንም የድምጽ ቆጠራው አለመጠናቀቁን ገለጸ
ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በሲዳማ፣ በአማራ፣ በጋምቤላ እና በሶማሌ ክልሎች የድምጽ ቆጠራ ሂደት እስካሁን አለመጠናቀቁን የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ ተናግረዋል።
በምርጫው እለት የቀረቡ ቅሬታዎችን በመከታተል ቦርዱ እርምጃ መውሰዱን ሰብሳቢዋ ገልጸዋል። በዚህም በተደረጉ ማጣራቶች ሁለት ሰዎች ከስራቸው መባረራቸውን ጠቁመዋል። በምርጫ ጣቢያዎች ስም የመፈለግ ሂደት ችግር የነበረበት መሆኑ እና ሂደቱን ማጓተቱም ተገልጿል።
በክትትል ክፍተት የተገኘባቸው እና ጠዋት ላይ ተቋርጠው የነበሩ ጣቢያዎች ከማጣራት በኋላ በድጋሜ ሂደቱን እንዲቀጥሉ ተደርጓል ብለዋል።
አሁን ላይ ውጤትን ከጣቢያ ወደ ምርጫ ክልል በመውሰድ የማዳመር እና የመቁጠር ስራው እየተጠናቀቀ መሆኑን ጠቁመዋል። ውጤቱንም ይፋ ለማድረግ ወደ ዋናው ማእከል የመሰብሰብ ስራ በቀጣይ የሚጠበቅ መሆኑን አስረድተዋል።
ሰብሳቢዋ አክለውም በአዲስ አበባ ከ1 ሺህ በላይ የሚሆኑ ጣቢያዎች የውጤት ማዳመር ስራን ገና አላጠናቀቁም ብለዋል።
ቦርዱ ባደረገው ማጣራት ከ50 ሺህ በላይ ጣቢያዎች በሰአቱ ተከፍተው የምርጫ ሂደቱን ማከናወናቸውን ገልጸዋል። የአለም አቀፍ ታዛቢዎችን ተሳትፎ በተመለከተም ከመጀመሪያው ሰአት እና ቀን ጀምሮ ተገኝተው ሚናቸውን መወጣታቸውን ጠቁመዋል።
ቦርዱ በነበረው ሂደት ካጋጠሙት ዋና ዋና ተግዳሮቶች መካከል በጸጥታ ምክንያት የተቋረጡ የምርጫ ጣቢያዎች መኖር፣ የምርጫ ወረቀት እና የቁሳቁስ እጥረት ማጋጠማቸው መሆናቸውን ሰብሳቢዋ አመላክተዋል።
Seledadotio
Seledadotio
ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በሲዳማ፣ በአማራ፣ በጋምቤላ እና በሶማሌ ክልሎች የድምጽ ቆጠራ ሂደት እስካሁን አለመጠናቀቁን የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ሃይሉ ተናግረዋል።
በምርጫው እለት የቀረቡ ቅሬታዎችን በመከታተል ቦርዱ እርምጃ መውሰዱን ሰብሳቢዋ ገልጸዋል። በዚህም በተደረጉ ማጣራቶች ሁለት ሰዎች ከስራቸው መባረራቸውን ጠቁመዋል። በምርጫ ጣቢያዎች ስም የመፈለግ ሂደት ችግር የነበረበት መሆኑ እና ሂደቱን ማጓተቱም ተገልጿል።
በክትትል ክፍተት የተገኘባቸው እና ጠዋት ላይ ተቋርጠው የነበሩ ጣቢያዎች ከማጣራት በኋላ በድጋሜ ሂደቱን እንዲቀጥሉ ተደርጓል ብለዋል።
አሁን ላይ ውጤትን ከጣቢያ ወደ ምርጫ ክልል በመውሰድ የማዳመር እና የመቁጠር ስራው እየተጠናቀቀ መሆኑን ጠቁመዋል። ውጤቱንም ይፋ ለማድረግ ወደ ዋናው ማእከል የመሰብሰብ ስራ በቀጣይ የሚጠበቅ መሆኑን አስረድተዋል።
ሰብሳቢዋ አክለውም በአዲስ አበባ ከ1 ሺህ በላይ የሚሆኑ ጣቢያዎች የውጤት ማዳመር ስራን ገና አላጠናቀቁም ብለዋል።
ቦርዱ ባደረገው ማጣራት ከ50 ሺህ በላይ ጣቢያዎች በሰአቱ ተከፍተው የምርጫ ሂደቱን ማከናወናቸውን ገልጸዋል። የአለም አቀፍ ታዛቢዎችን ተሳትፎ በተመለከተም ከመጀመሪያው ሰአት እና ቀን ጀምሮ ተገኝተው ሚናቸውን መወጣታቸውን ጠቁመዋል።
ቦርዱ በነበረው ሂደት ካጋጠሙት ዋና ዋና ተግዳሮቶች መካከል በጸጥታ ምክንያት የተቋረጡ የምርጫ ጣቢያዎች መኖር፣ የምርጫ ወረቀት እና የቁሳቁስ እጥረት ማጋጠማቸው መሆናቸውን ሰብሳቢዋ አመላክተዋል።
Seledadotio
Seledadotio
1 day ago
ኢዜማን ምረጥ ያለው ኢህአዴግ በእስራት ተቀጣ...
በደቡብ አሪ ወረዳ፣ ገድር ቀበሌ በምርጫ ዕለት የተከለከለ የፖለቲካ ቅስቀሳ በማድረጉ የተከሰሰው አቶ ኢህአዴግ ኃይሉ የ6 ወር ቀላል እስራት ተፈረደበት።
የዐቃቤ ህግ ክስ እንደሚያስረዳው፣ ተከሳሹ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ምርጫ ጣቢያ አቅራቢያ ድምፅ ለመስጠት ወደ ጣቢያው ይሄድ የነበረን ወጣት ለኢዜማ ድምፅ እንዲሰጥ በመገፋፋት በምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 የተደነገገውን ክልከላ ጥሷል።
ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የደቡብ አሪ ወረዳ ፍርድ ቤት፣ የዐቃቤ ህግን የሰው ምስክሮች እና የተከሳሹን የእምነት ክህደት ቃል ካዳመጠ በኋላ ተከሳሹ መከላከያ ማስረጃ ማቅረብ ባለመቻሉ ጥፋተኛ ብሎታል። ፍርድ ቤቱ ተከሳሹ የሦስት ልጆች አሳዳጊ መሆኑን እንደ ማቅለያ በመቀበል፣ በቀጣይ ለሌሎችም ማስጠንቀቂያ ይሆን ዘንድ በ6 ወር ቀላል እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አሳልፏል። ፍርዱ ለሁለት ዓመት በግልጽ ገደብ እንዲፈጸም ታዟል።
Seledadotio
Seledadotio
በደቡብ አሪ ወረዳ፣ ገድር ቀበሌ በምርጫ ዕለት የተከለከለ የፖለቲካ ቅስቀሳ በማድረጉ የተከሰሰው አቶ ኢህአዴግ ኃይሉ የ6 ወር ቀላል እስራት ተፈረደበት።
የዐቃቤ ህግ ክስ እንደሚያስረዳው፣ ተከሳሹ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ምርጫ ጣቢያ አቅራቢያ ድምፅ ለመስጠት ወደ ጣቢያው ይሄድ የነበረን ወጣት ለኢዜማ ድምፅ እንዲሰጥ በመገፋፋት በምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 የተደነገገውን ክልከላ ጥሷል።
ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የደቡብ አሪ ወረዳ ፍርድ ቤት፣ የዐቃቤ ህግን የሰው ምስክሮች እና የተከሳሹን የእምነት ክህደት ቃል ካዳመጠ በኋላ ተከሳሹ መከላከያ ማስረጃ ማቅረብ ባለመቻሉ ጥፋተኛ ብሎታል። ፍርድ ቤቱ ተከሳሹ የሦስት ልጆች አሳዳጊ መሆኑን እንደ ማቅለያ በመቀበል፣ በቀጣይ ለሌሎችም ማስጠንቀቂያ ይሆን ዘንድ በ6 ወር ቀላል እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አሳልፏል። ፍርዱ ለሁለት ዓመት በግልጽ ገደብ እንዲፈጸም ታዟል።
Seledadotio
Seledadotio
1 day ago
ቢቢሲ በአርሲ በደረሰው ጥቃት ላይ መረጃ ለመጠየቅ ለኦሮሚያ ክልል ኮሚዩኒክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ እና የክልሉ ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አራርሳ መርዳሳ በተደጋጋሚ ቢደውልም ስልካቸው ባለመነሳቱ ምላሽ ማግኘት አልቻለም።
ቢቢሲ አፋን ኦሮሞ የአርሲ ዞን ኮሚዩኒኬሽን ጽህፈት ቤት ኃላፊ የሆኑትን አቶ ሶሪ ወጊን ስለተፈጸመው ጥቃት ማክሰኞ አመሻሽ ላይ ላቀረበላቸው ጥያቄ "እስከአሁን የደረሰን መረጃ የለም፤ እናጣራለን" የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
ጥቃቱ ከተፈጸመባቸው አካበቢዎች አንዱ የሆነው የሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ አስተዳዳሪ ሐሰን መሐመድም ሰዎች ስለሞቱበት እና ንብረት ስለወደመበት ክስተት "መረጃ የለንም" የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
Seledadotio
Seledadotio
ቢቢሲ አፋን ኦሮሞ የአርሲ ዞን ኮሚዩኒኬሽን ጽህፈት ቤት ኃላፊ የሆኑትን አቶ ሶሪ ወጊን ስለተፈጸመው ጥቃት ማክሰኞ አመሻሽ ላይ ላቀረበላቸው ጥያቄ "እስከአሁን የደረሰን መረጃ የለም፤ እናጣራለን" የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
ጥቃቱ ከተፈጸመባቸው አካበቢዎች አንዱ የሆነው የሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ አስተዳዳሪ ሐሰን መሐመድም ሰዎች ስለሞቱበት እና ንብረት ስለወደመበት ክስተት "መረጃ የለንም" የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
Seledadotio
Seledadotio
1 day ago
የኢትዮጵያ መርከብ የሆርሙዝ ሰርጥን በሰላም መሻገሯ ተሰማ
በመካከለኛው ምስራቅ ቀውስ ምክንያት ከፍተኛ ስጋት በነበረበት የሆርሙዝ ሰርጥ አካባቢ፣ የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ንብረት የሆነችው “አሶሳ” መርከብ ከሆርሙዝ ሰርጥ በቅርብ ርቀት ላይ በምትገኘው ኮርፋካን ወደብ በመድረስ ወሳኝ የሕክምና እና የንግድ ጭነቶችን በተሳካ ሁኔታ ጭና ወደ ሀገሯ ተመልሳለች።
ይህ ስኬት የኢትዮጵያን ባሕረኞች ቁርጠኝነት እና የኢትዮጵያን የባሕር ሎጅስቲክስ ብቃት በተግባር ያሳየ ነው ተብሎለታለ።
Seledadotio
Seledadotio
በመካከለኛው ምስራቅ ቀውስ ምክንያት ከፍተኛ ስጋት በነበረበት የሆርሙዝ ሰርጥ አካባቢ፣ የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ንብረት የሆነችው “አሶሳ” መርከብ ከሆርሙዝ ሰርጥ በቅርብ ርቀት ላይ በምትገኘው ኮርፋካን ወደብ በመድረስ ወሳኝ የሕክምና እና የንግድ ጭነቶችን በተሳካ ሁኔታ ጭና ወደ ሀገሯ ተመልሳለች።
ይህ ስኬት የኢትዮጵያን ባሕረኞች ቁርጠኝነት እና የኢትዮጵያን የባሕር ሎጅስቲክስ ብቃት በተግባር ያሳየ ነው ተብሎለታለ።
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
🎉 ለቀናት ብቻ የወጣ ታላቅ ቅናሽ እና የኢንቨስትመንት ዕድል! 🎉
📌በካሬ 78,000 ብር ብቻ
📌100% ለከፈለ በካሬ 59,000 ብር
👉በየጊዜው ዋጋው እየጨመረ የሚሄድ ኢንቨስትመንት አሁኑኑ የራስዎ ያድርጉ!
🏡 በየዕለቱ የሪዞርት ዓይነት ቅንጦት ሕይወትን ይኑሩት❗️
📍በአፍሪካ ኮንቬሽን ሴንተር
📍 በከተማችን ትልቁና ቅንጡ Water Park አጠገብ
📍 የተባበሩት (CMC) አደባባይ
📍 ከፀሐይ ሪል ስቴት ፊት ለፊት
🏢 ከ2 ወር ጀምሮ የሚረከቡአቸው
ከ15 ካሬ ጀምሮ የንግድ ሱቆች፣
🏢ከ2 ዓመት በታች የሚረከቡአቸው መኖሪያ ቤቶችን ከ76 ካሬ ጀምሮ በማይደገም ምቹ የክፍያ አማራጮች!
🔥 ፈጥነው ይወስኑ!
ይህ ልዩ ቅናሽ የሚቆየው ለተወሰኑ ቀናት ብቻ ነው! 🔥
👉አንድ አፓርታማ ሊያሟላ የሚችለውን ሁሉንም ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ዝርጋታ የተሟላለት።
✍️ እርስዎም ይህንን ወርቃማ ዕድል በመጠቀም የዚህ ዘመናዊ መንደር ባለቤት ይሁኑ።
📌ቀድሞ ለመጣ ቅድሚያ ይስተናገዳል ።
⏱☎️ ለበለጠ መረጃ እና ለሳይት ጉብኝት አሁኑኑ በ 0944666669 አዳነ
ወይንም
👉Telegram----ADD112721
👉WhatsApp.https://wa.me/25194466666
ዛሬ ይግዙ፣ ነገን ያሸንፉ! Time is now❗️
📌በካሬ 78,000 ብር ብቻ
📌100% ለከፈለ በካሬ 59,000 ብር
👉በየጊዜው ዋጋው እየጨመረ የሚሄድ ኢንቨስትመንት አሁኑኑ የራስዎ ያድርጉ!
🏡 በየዕለቱ የሪዞርት ዓይነት ቅንጦት ሕይወትን ይኑሩት❗️
📍በአፍሪካ ኮንቬሽን ሴንተር
📍 በከተማችን ትልቁና ቅንጡ Water Park አጠገብ
📍 የተባበሩት (CMC) አደባባይ
📍 ከፀሐይ ሪል ስቴት ፊት ለፊት
🏢 ከ2 ወር ጀምሮ የሚረከቡአቸው
ከ15 ካሬ ጀምሮ የንግድ ሱቆች፣
🏢ከ2 ዓመት በታች የሚረከቡአቸው መኖሪያ ቤቶችን ከ76 ካሬ ጀምሮ በማይደገም ምቹ የክፍያ አማራጮች!
🔥 ፈጥነው ይወስኑ!
ይህ ልዩ ቅናሽ የሚቆየው ለተወሰኑ ቀናት ብቻ ነው! 🔥
👉አንድ አፓርታማ ሊያሟላ የሚችለውን ሁሉንም ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ዝርጋታ የተሟላለት።
✍️ እርስዎም ይህንን ወርቃማ ዕድል በመጠቀም የዚህ ዘመናዊ መንደር ባለቤት ይሁኑ።
📌ቀድሞ ለመጣ ቅድሚያ ይስተናገዳል ።
⏱☎️ ለበለጠ መረጃ እና ለሳይት ጉብኝት አሁኑኑ በ 0944666669 አዳነ
ወይንም
👉Telegram----ADD112721
👉WhatsApp.https://wa.me/25194466666
ዛሬ ይግዙ፣ ነገን ያሸንፉ! Time is now❗️
2 days ago
ደሴ‼️
በደሴ ከተማ የአይጥ መርዝ ለበርካታ ሰዎች ህልፈት ምክኒያት ሆኗል ተባለ።
በ2018 በጀት አመት ዘጠኝ ወራት የኬሚካል መመረዝ ጉዳት ለደረሰባቸው በርካታ ሰዎች ህክምና መስጠቱን የደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አስታውቋል።የሆስፒታሉ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች መከላከልና መቆጣጠር ባለሙያ አቶ ብርሃኑ አዱኛ ለብስራት ሬድዮ እንደገለፁት ሆስፒታሉ በዘጠኝ ወራት ውስጥ የኬሚካል መመረዝ አደጋ ለደረሰባቸው 1መቶ 72 ሰዎች የህክምና አገልግሎት ሰጥቷል።
ከእነዚህ መካከል 6.8 በመቶ የሞት ምጣኔ መመዝገቡን ገልፀው በሆስፒታሉ በተሰራው የተቀናጀ ስራ ከመመረዝ ጋር የተያያዘ የሞት ምጣኔ ከባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ 27.3 በመቶ ቀንሷል ብለዋል።የጉዳቱን የስርጭት መጠን አስመልክቶ 67 በመቶ የሚሆነው ከደሴ እንዲሁም 29 በመቶ የሚሆነው ደግሞ ከደቡብ ወሎ የተከሰተ መሆኑ ተገልጿል።
እነዚህ አካባቢዎች በኬሚካል መመረዝ በከፍተኛ ሁኔታ የተጠቁ የማህበረሰብ ክፍሎች መገኛ መሆናቸውን የጠቆሙት አቶ ብርሀኑ በሆስፒታሉ አስፈላጊውን ህክምና እንዲያገኙ ተደርጓል ብለዋል።86.5 በመቶ የሚሆኑት ራሳቸውን ለማጥፋት በሚል ህብረተሰቡ አይጥን ለመግደል የሚጠቀምባቸውን መርዞች የተጠቀሙ ናቸው።
የመርዝ ዓይነቶች ትንታኔ እንደሚያሳየው የአይጥ መመረዝ 35.9 በመቶ ፣ የመድኃኒት መመረዝ 17.6 በመቶ እንዲሁም የበረኪና መመረዝ ደግሞ 15.3 በመቶ ድርሻን ይይዛሉ።
Seledadotio
Seledadotio
በደሴ ከተማ የአይጥ መርዝ ለበርካታ ሰዎች ህልፈት ምክኒያት ሆኗል ተባለ።
በ2018 በጀት አመት ዘጠኝ ወራት የኬሚካል መመረዝ ጉዳት ለደረሰባቸው በርካታ ሰዎች ህክምና መስጠቱን የደሴ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አስታውቋል።የሆስፒታሉ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች መከላከልና መቆጣጠር ባለሙያ አቶ ብርሃኑ አዱኛ ለብስራት ሬድዮ እንደገለፁት ሆስፒታሉ በዘጠኝ ወራት ውስጥ የኬሚካል መመረዝ አደጋ ለደረሰባቸው 1መቶ 72 ሰዎች የህክምና አገልግሎት ሰጥቷል።
ከእነዚህ መካከል 6.8 በመቶ የሞት ምጣኔ መመዝገቡን ገልፀው በሆስፒታሉ በተሰራው የተቀናጀ ስራ ከመመረዝ ጋር የተያያዘ የሞት ምጣኔ ከባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ 27.3 በመቶ ቀንሷል ብለዋል።የጉዳቱን የስርጭት መጠን አስመልክቶ 67 በመቶ የሚሆነው ከደሴ እንዲሁም 29 በመቶ የሚሆነው ደግሞ ከደቡብ ወሎ የተከሰተ መሆኑ ተገልጿል።
እነዚህ አካባቢዎች በኬሚካል መመረዝ በከፍተኛ ሁኔታ የተጠቁ የማህበረሰብ ክፍሎች መገኛ መሆናቸውን የጠቆሙት አቶ ብርሀኑ በሆስፒታሉ አስፈላጊውን ህክምና እንዲያገኙ ተደርጓል ብለዋል።86.5 በመቶ የሚሆኑት ራሳቸውን ለማጥፋት በሚል ህብረተሰቡ አይጥን ለመግደል የሚጠቀምባቸውን መርዞች የተጠቀሙ ናቸው።
የመርዝ ዓይነቶች ትንታኔ እንደሚያሳየው የአይጥ መመረዝ 35.9 በመቶ ፣ የመድኃኒት መመረዝ 17.6 በመቶ እንዲሁም የበረኪና መመረዝ ደግሞ 15.3 በመቶ ድርሻን ይይዛሉ።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
2 days ago
በበሻሻ የምርጫ ጣቢያ የድምፅ ቆጠራ ውጤት
በኢትዮጵያ የተካሄደው የሰባተኛው አጠቃላይ ምርጫ የድምፅ ቆጠራ ውጤት፣ ዛሬ ማክሰኞ ከማለዳው ጀምሮ በአብዛኞቹ የምርጫ ጣቢያዎች እየተለጠፈ ይገኛል። በጅማ ከተማም ሆነ በዞኑ ስር በሚገኙ የምርጫ ክልሎች የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ሙሉ በሙሉ በሰላም መጠናቀቁን የዞኑ የምርጫ አስተባባሪ ለዶቼ ቬለ ገልጸዋል።
Seledadotio
Seledadotio
በኢትዮጵያ የተካሄደው የሰባተኛው አጠቃላይ ምርጫ የድምፅ ቆጠራ ውጤት፣ ዛሬ ማክሰኞ ከማለዳው ጀምሮ በአብዛኞቹ የምርጫ ጣቢያዎች እየተለጠፈ ይገኛል። በጅማ ከተማም ሆነ በዞኑ ስር በሚገኙ የምርጫ ክልሎች የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ሙሉ በሙሉ በሰላም መጠናቀቁን የዞኑ የምርጫ አስተባባሪ ለዶቼ ቬለ ገልጸዋል።
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
በጋና "ባሕሩን እከፍላለሁ" በማለት የሙሴን ታሪክ ለመድገም የሞከረው ግለሰብ ለትዝብት ተዳረገ
ራሱን "ነቢይ" አድርጎ የሚጠራውና በተደጋጋሚ ስለ ዓለም ፍጻሜ ትንቢት በመናገር የሚታወቀው ኤቦ ኖህ (እውነተኛ ስሙ ኢቫንስ ኢሹን) የተባለ ጋናዊ፣ በባሕር ማዕበል ተመትቶ ሲወሰድ የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል (ቪዲዮ) በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ መነጋገሪያ ሆኗል።
ሰሞኑን በጋና የባሕር ዳርቻ ላይ የተከናወነው ይህ ክስተት፣ ግለሰቡ የነቢዩ ሙሴን ታሪክ በመምሰል ሁለቱን እጆቹን ወደ ባሕሩ ዘርግቶ "ባሕሩን ለመክፈል" ሲሞክር ያሳያል።
ሆኖም ግን፣ ሳይታሰብ የመጣ ከባድ ማዕበል ክፉኛ ከመታው በኋላ በውሃው ፍሰት ተገፍቶ ሲወሰድና ሊወድቅ ሲል በምስሉ ላይ ታይቷል።
ይህ የተቀረጸ ምስል በቲክቶክ እና ኤክስ ላይ በስፋት የተሰራጨ ሲሆን፣ በርካታ የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ድርጊቱን በትዝብት እየተመለከቱት ይገኛሉ።
ኖህ ከዚህ ቀደም "እ.ኤ.አ. ታኅሣሥ 25 ቀን 2025 ዓለም ትጠፋለች" የሚል ትንቢት ተናግሮ የነበረ ሲሆን፣ የጋና ባለሥልጣናትም የሕዝብ ሽብር በመፍጠር ወንጀል ከዚህ ቀደም በቁጥጥር ስር አውለውት እንደነበር ተገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
ራሱን "ነቢይ" አድርጎ የሚጠራውና በተደጋጋሚ ስለ ዓለም ፍጻሜ ትንቢት በመናገር የሚታወቀው ኤቦ ኖህ (እውነተኛ ስሙ ኢቫንስ ኢሹን) የተባለ ጋናዊ፣ በባሕር ማዕበል ተመትቶ ሲወሰድ የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል (ቪዲዮ) በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ መነጋገሪያ ሆኗል።
ሰሞኑን በጋና የባሕር ዳርቻ ላይ የተከናወነው ይህ ክስተት፣ ግለሰቡ የነቢዩ ሙሴን ታሪክ በመምሰል ሁለቱን እጆቹን ወደ ባሕሩ ዘርግቶ "ባሕሩን ለመክፈል" ሲሞክር ያሳያል።
ሆኖም ግን፣ ሳይታሰብ የመጣ ከባድ ማዕበል ክፉኛ ከመታው በኋላ በውሃው ፍሰት ተገፍቶ ሲወሰድና ሊወድቅ ሲል በምስሉ ላይ ታይቷል።
ይህ የተቀረጸ ምስል በቲክቶክ እና ኤክስ ላይ በስፋት የተሰራጨ ሲሆን፣ በርካታ የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ድርጊቱን በትዝብት እየተመለከቱት ይገኛሉ።
ኖህ ከዚህ ቀደም "እ.ኤ.አ. ታኅሣሥ 25 ቀን 2025 ዓለም ትጠፋለች" የሚል ትንቢት ተናግሮ የነበረ ሲሆን፣ የጋና ባለሥልጣናትም የሕዝብ ሽብር በመፍጠር ወንጀል ከዚህ ቀደም በቁጥጥር ስር አውለውት እንደነበር ተገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
የሟቾቹ ቁጥር 13 ደርሷል‼️
ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የአርሲና ሶማሌ ክልል ጅግጅጋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት 13 ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸውን፣ ከ280 በላይ ምእመናን መፈናቀላቸውንና የ101 ዓመት ቤተ ክርስቲያን መቃጠሉን አሳወቁ።
ከግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ:ም ጀምሮ በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ ወረዳ; በሺርካ ወረዳና ሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ 13 ኦርቶዶክሳውያን ሲገደሉ የ101 ዓመት እድሜ ያለው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ወድሟል።
የካራ ኩፍተና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ላይም ዘረፋ የተካሄደ ሲሆን ምእመናን ጽላቱን ይዘው ተሰደዋል፤ መኖሪያ ቤታቸውም ተቃጥሏል።
የተገደሉ ሰዎች ስም ዝርዝርም
1. አቶ ደምረው አበራ የ70 ዓመት
2. ከፈለኝ ልክየለው የ56ዓመት
3. ሐይሉ ንጉሴ የ70 ዓመት
4. እሸቴ ዳመና የ42 ዓመት
5. አበባየሁ ዳኜ የ42 ዓመት
6. ሰሙ አባይነህ የ70 ዓመት
7. 1 ሚሊሻ
8. አማረ በላይነህ የ80 ዓመት
9. ተሬ ደሴ የ25 ዓመት
10. ወጣት ገነነ ጥላሁን በሽርካ ወረዳ
11. ሙርቴሳ ጥላሁን በሽርካ ወረዳ
12. አቶ ንጉሱ ማንደፍሮ በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ
13. አቶ በቀለ ኃ/ሚካኤል በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ
በአጠቃላይ የ13 ሰዎች ህይወት አልፈዋል።
በተጨማሪ በአሰኮ ወረዳ ከ280 ሰው በላይ ተፈናቅለዋል::
በመሆኑም ኦርቶዶክሳውያኑ ተወልደው ካደጉበት፣ ወልደው ከሳሙበት ቀያቸው በሃይማኖታቸው ብቻ ቤታቸው እየተለየ ተቃጥሏል፤ ንብረታቸውና ከብቶቻቸው ተዘርፈዋል።
ከጥቃቱ የተረፉት ነዋሪዎችም ይዘውት የሸሹት እምነታቸውንና ማንነታቸውን ብቻ በመሆኑ አሁን ላይ ሜዳ ላይ ወድቀው ይገኛሉ።
Seledadotio
Seledadotio
ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የአርሲና ሶማሌ ክልል ጅግጅጋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት 13 ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸውን፣ ከ280 በላይ ምእመናን መፈናቀላቸውንና የ101 ዓመት ቤተ ክርስቲያን መቃጠሉን አሳወቁ።
ከግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ:ም ጀምሮ በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ ወረዳ; በሺርካ ወረዳና ሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ 13 ኦርቶዶክሳውያን ሲገደሉ የ101 ዓመት እድሜ ያለው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ወድሟል።
የካራ ኩፍተና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ላይም ዘረፋ የተካሄደ ሲሆን ምእመናን ጽላቱን ይዘው ተሰደዋል፤ መኖሪያ ቤታቸውም ተቃጥሏል።
የተገደሉ ሰዎች ስም ዝርዝርም
1. አቶ ደምረው አበራ የ70 ዓመት
2. ከፈለኝ ልክየለው የ56ዓመት
3. ሐይሉ ንጉሴ የ70 ዓመት
4. እሸቴ ዳመና የ42 ዓመት
5. አበባየሁ ዳኜ የ42 ዓመት
6. ሰሙ አባይነህ የ70 ዓመት
7. 1 ሚሊሻ
8. አማረ በላይነህ የ80 ዓመት
9. ተሬ ደሴ የ25 ዓመት
10. ወጣት ገነነ ጥላሁን በሽርካ ወረዳ
11. ሙርቴሳ ጥላሁን በሽርካ ወረዳ
12. አቶ ንጉሱ ማንደፍሮ በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ
13. አቶ በቀለ ኃ/ሚካኤል በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ
በአጠቃላይ የ13 ሰዎች ህይወት አልፈዋል።
በተጨማሪ በአሰኮ ወረዳ ከ280 ሰው በላይ ተፈናቅለዋል::
በመሆኑም ኦርቶዶክሳውያኑ ተወልደው ካደጉበት፣ ወልደው ከሳሙበት ቀያቸው በሃይማኖታቸው ብቻ ቤታቸው እየተለየ ተቃጥሏል፤ ንብረታቸውና ከብቶቻቸው ተዘርፈዋል።
ከጥቃቱ የተረፉት ነዋሪዎችም ይዘውት የሸሹት እምነታቸውንና ማንነታቸውን ብቻ በመሆኑ አሁን ላይ ሜዳ ላይ ወድቀው ይገኛሉ።
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
⚡ "የጽምዶ ጥምረት" በርካታ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ቡድኖችን እያካተተ መሆኑ ተገለጠ
በኤርትራ እና ህወሃት መካከል የተጀመረውና "ጽምዶ" (Ximdo) በመባል የሚታወቀው አዲሱ የፖለቲካ ትስስር፣ አሁን ላይ በርካታ የኢትዮጵያ የታጠቁና የፖለቲካ ተቃዋሚ ቡድኖችን ወደማካተት እየሰፋ መሄዱን አፍሪካ ኢንተለጀንስ ዘግቧል።
📌 የአዲስ አበባውን ማዕከላዊ መንግስት የሚቃወሙት የህወሃት/ትግራይ መከላከያ ኃይል አመራሮች፣ በቅርቡ በሱዳን የወደብ ከተማ ፖርት ሱዳን ከተደረጉ የኤርትራ ከፍተኛ ባለስልጣናት እና ከሱዳን ጦር ኃይል ተወካዮች ጋር ስብሰባ ማድረጋቸው ተረጋግጧል።
ይህ በኤርትራ መንግስት አስተባባሪነት እየተመራ ያለው ጥምረት የህወሃትን "የአሮጌው ጎራ ጨምሮ፣ እንደ ፋኖ ያሉ፣ የኦብነግ የተገነጠሉ ክንፎችን እና ሌሎች ታዋቂ የፖለቲካ ተቃዋሚዎችን በአንድ ጥላ ስር ለማሰባሰብ እየሰራ እንደሆነ የደህንነት ምንጮች ጠቁመዋል።
የሰሜኑ ጦርነት ወቅት ኤርትራ እና ህወሃት እርስ በእርስ የገጠሙ ደመኛ ጠላቶች የነበሩ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን "የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው" በሚለው መርህ የአዲስ አበባውን መንግስት ለመጫንና የራሳቸውን የፖለቲካ ህልውና ለማስጠበቅ ስልታዊ ህብረት ፈጥረዋል።ይህ አዲስ የሀይሎች መሸጋሸግ በኢትዮጵያ፣ በኤርትራ እና በሱዳን መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ይበልጥ እያሻከረው ሲሆን፣ ቀጠናዊ ቀውስ ሊያስከትል ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል።
Seledadotio
Seledadotio
በኤርትራ እና ህወሃት መካከል የተጀመረውና "ጽምዶ" (Ximdo) በመባል የሚታወቀው አዲሱ የፖለቲካ ትስስር፣ አሁን ላይ በርካታ የኢትዮጵያ የታጠቁና የፖለቲካ ተቃዋሚ ቡድኖችን ወደማካተት እየሰፋ መሄዱን አፍሪካ ኢንተለጀንስ ዘግቧል።
📌 የአዲስ አበባውን ማዕከላዊ መንግስት የሚቃወሙት የህወሃት/ትግራይ መከላከያ ኃይል አመራሮች፣ በቅርቡ በሱዳን የወደብ ከተማ ፖርት ሱዳን ከተደረጉ የኤርትራ ከፍተኛ ባለስልጣናት እና ከሱዳን ጦር ኃይል ተወካዮች ጋር ስብሰባ ማድረጋቸው ተረጋግጧል።
ይህ በኤርትራ መንግስት አስተባባሪነት እየተመራ ያለው ጥምረት የህወሃትን "የአሮጌው ጎራ ጨምሮ፣ እንደ ፋኖ ያሉ፣ የኦብነግ የተገነጠሉ ክንፎችን እና ሌሎች ታዋቂ የፖለቲካ ተቃዋሚዎችን በአንድ ጥላ ስር ለማሰባሰብ እየሰራ እንደሆነ የደህንነት ምንጮች ጠቁመዋል።
የሰሜኑ ጦርነት ወቅት ኤርትራ እና ህወሃት እርስ በእርስ የገጠሙ ደመኛ ጠላቶች የነበሩ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን "የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው" በሚለው መርህ የአዲስ አበባውን መንግስት ለመጫንና የራሳቸውን የፖለቲካ ህልውና ለማስጠበቅ ስልታዊ ህብረት ፈጥረዋል።ይህ አዲስ የሀይሎች መሸጋሸግ በኢትዮጵያ፣ በኤርትራ እና በሱዳን መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ይበልጥ እያሻከረው ሲሆን፣ ቀጠናዊ ቀውስ ሊያስከትል ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል።
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
በቅርቡ ወደ ሥራ የተመለሠው የትግራይ ክልል ምክር ቤት አዳዲስ ሹመቶች አፀደቀ
ከጦርነቱ በፊት ተቃቁሞ የነበረውና በቅርቡ ወደ ሥራ የተመለሠው የትግራይ ክልል ምክር ቤት ሕወሃት ያቀረባቸውን የአዲስ የካቢኔ አባላት፣ የዞን አስተዳዳሪዎችና የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሹመት ዛሬ ማምሻውን አጸደቀ።
የሕወሃት ምክትል ሊቀመንበር አማኑኤል አሠፋ የክልሉ ምክትል ፕሬዝዳንትና የፍትሕ ቢሮ ኃላፊ ኾነው እንደተሾሙ የክልሉ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።
70 በመቶ ያህሉ የካቢኔ አባላት ከሕወሃት የተውጣጡ ሲሆኑ፣ 30 በመቶዎቹ ከተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎችና ከምሁራን የተውጣጡ እንደሆኑ ተገልጧል።
በተመሳሳይ፣ ወልደአብርሃ ገብረጻዲቅ የሰሜን ምዕራብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ፣ ሺሻይ ግርማይ የማዕከላዊ ዞን ዋና አስተዳዳሪ፣ ዝናቡ ገብረመድኅን የደቡባዊ ዞን ዋና አስተዳዳሪ፣ ግዴይ አዘናው የምዕራብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ፣ ፍስሃ ኃይላይ የምሥራቅ ዞን ዋና አስተዳዳሪ እንዲሁም ከለሊ ሐጋዚ የደቡብ ምስራቅ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኾነው እንደተሾሙ ዘገባዎቹ ጠቅሠዋል።
Seledadotio
Seledadotio
ከጦርነቱ በፊት ተቃቁሞ የነበረውና በቅርቡ ወደ ሥራ የተመለሠው የትግራይ ክልል ምክር ቤት ሕወሃት ያቀረባቸውን የአዲስ የካቢኔ አባላት፣ የዞን አስተዳዳሪዎችና የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሹመት ዛሬ ማምሻውን አጸደቀ።
የሕወሃት ምክትል ሊቀመንበር አማኑኤል አሠፋ የክልሉ ምክትል ፕሬዝዳንትና የፍትሕ ቢሮ ኃላፊ ኾነው እንደተሾሙ የክልሉ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።
70 በመቶ ያህሉ የካቢኔ አባላት ከሕወሃት የተውጣጡ ሲሆኑ፣ 30 በመቶዎቹ ከተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎችና ከምሁራን የተውጣጡ እንደሆኑ ተገልጧል።
በተመሳሳይ፣ ወልደአብርሃ ገብረጻዲቅ የሰሜን ምዕራብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ፣ ሺሻይ ግርማይ የማዕከላዊ ዞን ዋና አስተዳዳሪ፣ ዝናቡ ገብረመድኅን የደቡባዊ ዞን ዋና አስተዳዳሪ፣ ግዴይ አዘናው የምዕራብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ፣ ፍስሃ ኃይላይ የምሥራቅ ዞን ዋና አስተዳዳሪ እንዲሁም ከለሊ ሐጋዚ የደቡብ ምስራቅ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኾነው እንደተሾሙ ዘገባዎቹ ጠቅሠዋል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel