14 days ago
ምፅዓተ ጂኦ-ፖለቲካ እና የባሕር በር አጀንዳችን
****************
ዓለማችን ከአንድ ዋልታ ወደ ብዝኃ-ዓለማዊ ሥርዓት የኃይል ሽግግር እያደረገች ባለችበት በአሁኑ ዘመን፣ የጂኦ-ፖለቲካው ዐውሎ ነፋስ በድጋሚ እያንሰራራ ይገኛል።
ከቀዝቃዛው ጦርነት ማብቃት በኋላ ተቀዛቅዞ የነበረው የኃያላን ሀገራት የእርስ በርስ የጂኦ-ፖለቲካዊ ሽኩቻ በማገርሸቱ፣ የቀይ ባሕር እና የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ዳግም የዓለም አቀፍ ትኩረት ማዕከል ሆኗል።
ሀገራት ጥቅማቸውን ለማስከበር እና የዓለም መሪ ለመሆን በሚያደርጉት ፉክክር፣ የዓለም ኃይል እና ሀብት የተከማቸባቸውን ቦታዎች ለመቆጣጠር የሚደረገው ጥድፊያ "ምፅዓተ ጂኦ-ፖለቲካን" በይፋ አውጇል።
በአሁኑ ወቅት የኃያላኑ ግብግብ በተለይም የንግድ መስመሮችን እና ስትራቴጂያዊ የባሕር ሰርጦችን መቆጣጠር ላይ ያነጣጠረ ነው።
በታሪክ የምድርን ማዕከላዊ መሬት እና የባሕር ዳርቻን መቆጣጠር ዓለምን መቆጣጠር ነው የሚሉት የሀልፎርድ ማኪንደር እና የኒኮላስ ስፓይክማን ክላሲካል ፅንሰ-ሐሳቦች በድጋሚ የዓለም መድረክ ላይ ተግባራዊ እየሆኑ ይገኛሉ።
በዚህ ፉክክር መካከል ቀይ ባሕር፥ አፍሪካን፣ አውሮፓን እና እስያን የሚያገናኝ ድልድይ በመሆኑ የጂኦ-ፖለቲካ ፉክክር ማዕከል ሆኗል።
በዚህ ውስብስብ የጂኦ-ፖለቲካ ፍጥጫ ውስጥ፣ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላት ምሰሶነት ልዩ ትኩረት የሚሻ ነው። ትልቅ የሕዝብ ቁጥር ያላት እና በነፃነት ታሪኳ የምትታወቀው ኢትዮጵያ፣ በቀጣናው ፖለቲካ የላቀ አቅም ያላት ዋልታ ናት።
ይሁን እንጂ 97 በመቶ የሚጠጋ ምርቷን ለማስገባት በአንድ ሀገር ላይ ብቻ ጥገኛ መሆኗ፣ ሀገራችን በስትራቴጂያዊ የባሕር በር እጦት እንድትፈተን አድርጓታል።
ስለሆነም፣ ኢትዮጵያ ከታሪካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ገናንነቷ አኳያ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስከበር አስተማማኝ የባሕር በር ማግኘት የግድ ይላታል።
ስንት ሺሕ ኪሎሜትር አቋርጠው የመጡ የውጭ ኃይሎች አፍንጫችን ሥር ወታደራዊ የጦር ሰፈር በገነቡበት በዚህ ዘመን፣ ቀጣናዊ ዋልታ የሆነችው ሀገራችን የራሷን የባሕር ኃይል እና ወታደራዊ ቤዝ ለማደራጀት መመኘቷ ሉዓላዊ መብት ከመሆኑም ባሻገር ለቀጣናው ሰላም እና አንድነት መጠበቅ ወሳኝ እርምጃ ነው።
ከዚህ ሁሉ አዙሪት እና የኃያላን የእጅ አዙር ጦርነት ለመውጣት የሚያስችለው ስትራቴጂያዊ መንገድ "መደመር" ነው። ኢትዮጵያ ያላት ሰፊ ገበያ እና የውኃ ሀብት፣ የጎረቤት ሀገራት ካላቸው የባሕር በር ጋር ተቀናጅቶ አካባቢውን በጋራ የማልማት ትልቅ አቅም አለው።
የአፍሪካ ቀንድ ሀገራት በታሪክ፣ በባህል እና በሃይማኖት የተሣሠሩ ወንድማማች ሕዝቦች በመሆናቸው፣ አብሮነታቸውን ድንበር ሊገድበው አይገባም።
ጥላቻን አስወግዶ፣ ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ ትሥሥር በመፍጠር፣ ወሰን ተሻጋሪ የንግድ ግንኙነትን ማጠናከር የውዴታ ግዴታ ነው።
የቀጣናው ሀገራት እርስ በርስ ከመጋጨት ይልቅ ቢተባበሩ እና የሌሎችን ኃይሎች ጣልቃ ገብነት በመረዳት ቢደጋገፉ፣ ቀጣናውን ከግጭት የፀዳ በማድረግ ወደ ላቀ ብልጽግና ማሸጋገር ይችላሉ።
የኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ ብሔራዊ ጥቅም የሚረጋገጠውም ሆነ የቀጣናው ዕጣ ፈንታ ብሩህ የሚሆነው ይህ የትብብር እና የመደመር መንፈስ በተግባር ሲመነዘር ብቻ ነው።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ebc #ethiopia #medemer #redsea #nationalinterest
****************
ዓለማችን ከአንድ ዋልታ ወደ ብዝኃ-ዓለማዊ ሥርዓት የኃይል ሽግግር እያደረገች ባለችበት በአሁኑ ዘመን፣ የጂኦ-ፖለቲካው ዐውሎ ነፋስ በድጋሚ እያንሰራራ ይገኛል።
ከቀዝቃዛው ጦርነት ማብቃት በኋላ ተቀዛቅዞ የነበረው የኃያላን ሀገራት የእርስ በርስ የጂኦ-ፖለቲካዊ ሽኩቻ በማገርሸቱ፣ የቀይ ባሕር እና የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ዳግም የዓለም አቀፍ ትኩረት ማዕከል ሆኗል።
ሀገራት ጥቅማቸውን ለማስከበር እና የዓለም መሪ ለመሆን በሚያደርጉት ፉክክር፣ የዓለም ኃይል እና ሀብት የተከማቸባቸውን ቦታዎች ለመቆጣጠር የሚደረገው ጥድፊያ "ምፅዓተ ጂኦ-ፖለቲካን" በይፋ አውጇል።
በአሁኑ ወቅት የኃያላኑ ግብግብ በተለይም የንግድ መስመሮችን እና ስትራቴጂያዊ የባሕር ሰርጦችን መቆጣጠር ላይ ያነጣጠረ ነው።
በታሪክ የምድርን ማዕከላዊ መሬት እና የባሕር ዳርቻን መቆጣጠር ዓለምን መቆጣጠር ነው የሚሉት የሀልፎርድ ማኪንደር እና የኒኮላስ ስፓይክማን ክላሲካል ፅንሰ-ሐሳቦች በድጋሚ የዓለም መድረክ ላይ ተግባራዊ እየሆኑ ይገኛሉ።
በዚህ ፉክክር መካከል ቀይ ባሕር፥ አፍሪካን፣ አውሮፓን እና እስያን የሚያገናኝ ድልድይ በመሆኑ የጂኦ-ፖለቲካ ፉክክር ማዕከል ሆኗል።
በዚህ ውስብስብ የጂኦ-ፖለቲካ ፍጥጫ ውስጥ፣ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላት ምሰሶነት ልዩ ትኩረት የሚሻ ነው። ትልቅ የሕዝብ ቁጥር ያላት እና በነፃነት ታሪኳ የምትታወቀው ኢትዮጵያ፣ በቀጣናው ፖለቲካ የላቀ አቅም ያላት ዋልታ ናት።
ይሁን እንጂ 97 በመቶ የሚጠጋ ምርቷን ለማስገባት በአንድ ሀገር ላይ ብቻ ጥገኛ መሆኗ፣ ሀገራችን በስትራቴጂያዊ የባሕር በር እጦት እንድትፈተን አድርጓታል።
ስለሆነም፣ ኢትዮጵያ ከታሪካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ገናንነቷ አኳያ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስከበር አስተማማኝ የባሕር በር ማግኘት የግድ ይላታል።
ስንት ሺሕ ኪሎሜትር አቋርጠው የመጡ የውጭ ኃይሎች አፍንጫችን ሥር ወታደራዊ የጦር ሰፈር በገነቡበት በዚህ ዘመን፣ ቀጣናዊ ዋልታ የሆነችው ሀገራችን የራሷን የባሕር ኃይል እና ወታደራዊ ቤዝ ለማደራጀት መመኘቷ ሉዓላዊ መብት ከመሆኑም ባሻገር ለቀጣናው ሰላም እና አንድነት መጠበቅ ወሳኝ እርምጃ ነው።
ከዚህ ሁሉ አዙሪት እና የኃያላን የእጅ አዙር ጦርነት ለመውጣት የሚያስችለው ስትራቴጂያዊ መንገድ "መደመር" ነው። ኢትዮጵያ ያላት ሰፊ ገበያ እና የውኃ ሀብት፣ የጎረቤት ሀገራት ካላቸው የባሕር በር ጋር ተቀናጅቶ አካባቢውን በጋራ የማልማት ትልቅ አቅም አለው።
የአፍሪካ ቀንድ ሀገራት በታሪክ፣ በባህል እና በሃይማኖት የተሣሠሩ ወንድማማች ሕዝቦች በመሆናቸው፣ አብሮነታቸውን ድንበር ሊገድበው አይገባም።
ጥላቻን አስወግዶ፣ ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ ትሥሥር በመፍጠር፣ ወሰን ተሻጋሪ የንግድ ግንኙነትን ማጠናከር የውዴታ ግዴታ ነው።
የቀጣናው ሀገራት እርስ በርስ ከመጋጨት ይልቅ ቢተባበሩ እና የሌሎችን ኃይሎች ጣልቃ ገብነት በመረዳት ቢደጋገፉ፣ ቀጣናውን ከግጭት የፀዳ በማድረግ ወደ ላቀ ብልጽግና ማሸጋገር ይችላሉ።
የኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ ብሔራዊ ጥቅም የሚረጋገጠውም ሆነ የቀጣናው ዕጣ ፈንታ ብሩህ የሚሆነው ይህ የትብብር እና የመደመር መንፈስ በተግባር ሲመነዘር ብቻ ነው።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ebc #ethiopia #medemer #redsea #nationalinterest
15 days ago
u1275u1265u1265u122d u1232u1263u1209 u1326u122du1290u1275 u12e8u121au1209 u12e8u1240u1323u1293u12cd u1283u12edu120eu127du2026 u1260u1302u130du1302u130b u12e8u1270u1230u1260u1230u1261u1275 u12e8u12a0u134du122au12ab u1240u1295u12f5 u1203u1308u122bu1275 u12a8u134du1270u129b u1263u1208u1225u120du1323u1293u1275u1293 u121du1201u122bu1295 Horn Dialogue | JIGJIGA Forum | Red Sea | Gulf Politics and Regional Security |
#jigjigaforum #redsea #gulfpoliticsandregionalsecurity #u12e8u1200u1308u122du1309u12f3u12ed ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ትብብር ሲባሉ ጦርነት የሚሉ የቀጣናው ኃይሎች… በጂግጂጋ የተሰበሰቡት የአፍሪካ ቀንድ ሃገራት ከፍተኛ ባለሥልጣናትና ምሁራን Horn Dialogue | JIGJIGA Forum | Red Sea | Gulf Politics and Regional Security |
#jigjigaforum #redsea #gulfpoliticsandregionalsecurity #የሀገርጉዳይ
15 days ago
ከሀገር ውስጥ ተቋማዊ ግንባታ እስከ ቀይ ባሕር ሕጋዊ መብት፤ አሰባሳቢው ሀገራዊ ትርክት
******************
ኢትዮጵያ በታሪኳ የብዙ ማንነቶችና የግዙፍ ታሪኮች ማህደር ብትሆንም፣ ላለፉት ዓመታት በፖለቲካው ምህዳር የነገሱት ትርክቶች እንደ አስተሳሳሪ ሳይሆን በሁለት ጎራ ተከፍለው ሀገራችንን ሲያዳክሙ ቆይተዋል።
ይህ በሁለት ጽንፎች መካከል የነበረ የጥላቻ ፖለቲካና የነጣጣይ ትርክቶች አዙሪት ግን አሁን በአዲሱ “የመደመር” እሳቤ ተሰብሯል። አዲሱ እሳቤ እነዚህን የቆዩ የፖለቲካ፣ የዴሞክራሲና የተቋማት ግንባታ ስብራቶች በመጠገን ሀገራዊ ህብርብሔራዊ አንድነትንና የጋራ ተስፋን ሰንቆ ብቅ ብሏል።
መደመር ያለፈውን ታሪክ በጭፍን ሳይቀበልና ሳይቃወም፣ መልካሙን ወርሶ ግድፈቶቹን ደግሞ ተምረንባቸው የምናልፍበት ድልድይ መሆኑን እና እሳቤው ከሀገር ውስጥ ፖለቲካ አልፎ የሀገራችንን ስልታዊ ጥቅሞች ማስከበር ላይ ያተኮረ ስለመሆኑ ምሁራን ገልጸዋል።
የታሪካዊ ጠላቶች ሴራ መነሻው ኢትዮጵያ በዓባይ እና በቀይ ባሕር ላይ ያላትን መብት ለማዳከም መሆኑን የጠቀሱት ምሁራኑ፣ የህዳሴ ግድብ በጸጥታ ኃይሎቻችን መስዋዕትነት የተገነባ የድላችን አምድ እንደሆነና የቀይ ባሕርን ህጋዊ መብት መጠየቅም የሉዓላዊነትና የህልውና ጉዳይ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
አዲሱ ሀገራዊ ትርክት የውክልና ጦርነቶችን በመመከት ግጭትን ወደ ስምምነት፣ ልዩነትን ደግሞ ወደ ውበት እየቀየረ ኢትዮጵያን ወደ ብልፅግና ማማ የማውጣት ታሪካዊ ተልዕኮውን እያሳካ ይገኛል።
የመደመር እሳቤ የሀገራችንን ዘላቂ ስልታዊ ጥቅሞች፣ ተቋማዊ ብቃትንና የአህጉራዊ ፋይዳውን እንዴት እያስከበረ እንደሚገኝ የቀረበውን ሙሉ ማብራሪያና ሰፊ ትንታኔ አስተያየት መስጫው ውስጥ ያለውን ማስፈንጠሪያ ተጭነው ያንብቡ።
በላሉ ኢታላ
#ethiopia #medemer #nationalnarrative #redsea #africanunity #ethiopianbroadcastingcorporation
******************
ኢትዮጵያ በታሪኳ የብዙ ማንነቶችና የግዙፍ ታሪኮች ማህደር ብትሆንም፣ ላለፉት ዓመታት በፖለቲካው ምህዳር የነገሱት ትርክቶች እንደ አስተሳሳሪ ሳይሆን በሁለት ጎራ ተከፍለው ሀገራችንን ሲያዳክሙ ቆይተዋል።
ይህ በሁለት ጽንፎች መካከል የነበረ የጥላቻ ፖለቲካና የነጣጣይ ትርክቶች አዙሪት ግን አሁን በአዲሱ “የመደመር” እሳቤ ተሰብሯል። አዲሱ እሳቤ እነዚህን የቆዩ የፖለቲካ፣ የዴሞክራሲና የተቋማት ግንባታ ስብራቶች በመጠገን ሀገራዊ ህብርብሔራዊ አንድነትንና የጋራ ተስፋን ሰንቆ ብቅ ብሏል።
መደመር ያለፈውን ታሪክ በጭፍን ሳይቀበልና ሳይቃወም፣ መልካሙን ወርሶ ግድፈቶቹን ደግሞ ተምረንባቸው የምናልፍበት ድልድይ መሆኑን እና እሳቤው ከሀገር ውስጥ ፖለቲካ አልፎ የሀገራችንን ስልታዊ ጥቅሞች ማስከበር ላይ ያተኮረ ስለመሆኑ ምሁራን ገልጸዋል።
የታሪካዊ ጠላቶች ሴራ መነሻው ኢትዮጵያ በዓባይ እና በቀይ ባሕር ላይ ያላትን መብት ለማዳከም መሆኑን የጠቀሱት ምሁራኑ፣ የህዳሴ ግድብ በጸጥታ ኃይሎቻችን መስዋዕትነት የተገነባ የድላችን አምድ እንደሆነና የቀይ ባሕርን ህጋዊ መብት መጠየቅም የሉዓላዊነትና የህልውና ጉዳይ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
አዲሱ ሀገራዊ ትርክት የውክልና ጦርነቶችን በመመከት ግጭትን ወደ ስምምነት፣ ልዩነትን ደግሞ ወደ ውበት እየቀየረ ኢትዮጵያን ወደ ብልፅግና ማማ የማውጣት ታሪካዊ ተልዕኮውን እያሳካ ይገኛል።
የመደመር እሳቤ የሀገራችንን ዘላቂ ስልታዊ ጥቅሞች፣ ተቋማዊ ብቃትንና የአህጉራዊ ፋይዳውን እንዴት እያስከበረ እንደሚገኝ የቀረበውን ሙሉ ማብራሪያና ሰፊ ትንታኔ አስተያየት መስጫው ውስጥ ያለውን ማስፈንጠሪያ ተጭነው ያንብቡ።
በላሉ ኢታላ
#ethiopia #medemer #nationalnarrative #redsea #africanunity #ethiopianbroadcastingcorporation
16 days ago
u12a2u1275u12eeu1335u12ebu1295 u12a8u1240u12ed u1263u1215u122d u1290u1325u120e u121bu1246u12e8u1275 u12a0u12edu127bu120du121d
#ethiopia #redsea #ethiopiannavy #assab ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ኢትዮጵያን ከቀይ ባሕር ነጥሎ ማቆየት አይቻልም
#ethiopia #redsea #ethiopiannavy #assab
17 days ago
የኢትዮጵያ የቀይ ባህር ባለቤትነት ጥያቄ ከሀገራዊ ህልውና ጋር የተቆራኘ ነው :- የቀድሞው የአሰብ ከንቲባ አቶ ዳንኤል ሊበን
*******
የኢትዮጵያ የቀይ ባህር ባለቤትነት ጥያቄ በስሜት የሚነዳ ሳይሆን የታሪክ መሠረት ያለውና ከሀገራዊ ህልውና ጋር የተቆራኘ መሆኑን የቀድሞው የአሰብ ከተማ ከንቲባ አቶ ዳንኤል ሊበን ገለጹ።
አሰብ ከተማ የኢትዮጵያ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ደም ስር ከመሆኗም ባለፈ፣ የኢትዮጵያ የሉዓላዊነት ምልክት እንደሆነች ይነገራል።
ዛሬ ላይ በይፋ የቀረበው የኢትዮጵያ የቀይ ባህር ባለቤትነት ጥያቄ፣ ከወቅታዊ ስሜት ይልቅ ተጨባጭ የታሪክ መረጃዎችንና የህልውና አጀንዳን መሠረት ያደረገ ነው።
የቀድሞው የአሰብ ከተማ ከንቲባ አቶ ዳንኤል ሊበን ከኢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ የአሰብ የባህር በር ጥያቄ ታሪካዊ እውነታን የተመረኮዘ መሆኑን አብራርተዋል።
እንደ አቶ ዳንኤል ገለጻ፣ አሰብ በወቅቱ በኢትዮጵያ ውስጥ ከነበሩ ግንባር ቀደም ከተሞች አንዷ ከመሆኗም በላይ የሀገሪቱ ዋንኛ የገቢና ወጪ ንግድ ማዕከል በመሆን ለኢኮኖሚ እድገቱ እንደ ጀርባ አጥንት ታገለግል ነበር።
አቶ ዳንኤል የአሰብ ጥያቄ ዛሬ የተፈጠረ ሳይሆን ጥልቅ የታሪክ መሠረት ያለው መሆኑን ሲያስረዱም፤ አሰብ "የአሰብ ራስ-ገዝ አስተዳደር" (Assab Regional Autonomous) ተብላ ትጠራ እንደነበር አስታውሰዋል። ይህ መዋቅር አሰብን ከኤርትራ ራስ-ገዝ አስተዳደር ነጥሎ በቀጥታ ለማዕከላዊ መንግስት ተጠሪ የሚያደርግ ነበር።
የዚህ ራስ-ገዝ አስተዳደር ስፋትም ከምጽዋ አቅራቢያ ጀምሮ እስከ ጅቡቲ ጠረፍ ድረስ ያለውን ሰፊ የባህር ዳርቻ የሚያጠቃልል ነበር ይላሉ።
በ1983 ዓ.ም የመንግስት ለውጥ ሲመጣ የነበረውን ሁኔታ ያስታወሱት አቶ ዳንኤል፤ የከተማዋ ማህበራዊ ሕይወት፣ የትምህርት ሥርዓት እና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ከኢትዮጵያ መሃል ሀገር ጋር ፍጹም የተቆራኘ እንደነበር ገልጸዋል።
በወቅቱ አስመራ የነበሩ ነዋሪዎችም ቢሆኑ "አሰብ ለኢትዮጵያ አገልግሎት ካልሰጠች ለእኛም ፋይዳዋ አነስተኛ ነው" የሚል እምነት እንደነበራቸው ጠቅሰዋል።
በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤት እንድትሆን የሚቀርበው ጥያቄ ወቅታዊና ተገቢ መሆኑ አጠያያቂ አይደለም ብለዋል።
ከተማዋ የኢትዮጵያ የነዳጅ ማጣሪያ እና የትራንስፖርት ደም-ስር ሆና ለዓመታት ማገልገሏ፣ ዛሬ ለሚነሳው ጥያቄ ትልቅ የሞራልና የታሪክ አስረጂ ነው። ይህም የባህር በር ጥያቄው ህጋዊነት፣ ተገቢነት እና ወቅታዊነት የማይናወጥ መሠረት እንዳለው ያረጋግጣል።
በላሉ ኢታላ
#ethiopia #assab #redsea #addisababa #ethiopiannews #history
*******
የኢትዮጵያ የቀይ ባህር ባለቤትነት ጥያቄ በስሜት የሚነዳ ሳይሆን የታሪክ መሠረት ያለውና ከሀገራዊ ህልውና ጋር የተቆራኘ መሆኑን የቀድሞው የአሰብ ከተማ ከንቲባ አቶ ዳንኤል ሊበን ገለጹ።
አሰብ ከተማ የኢትዮጵያ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ደም ስር ከመሆኗም ባለፈ፣ የኢትዮጵያ የሉዓላዊነት ምልክት እንደሆነች ይነገራል።
ዛሬ ላይ በይፋ የቀረበው የኢትዮጵያ የቀይ ባህር ባለቤትነት ጥያቄ፣ ከወቅታዊ ስሜት ይልቅ ተጨባጭ የታሪክ መረጃዎችንና የህልውና አጀንዳን መሠረት ያደረገ ነው።
የቀድሞው የአሰብ ከተማ ከንቲባ አቶ ዳንኤል ሊበን ከኢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ የአሰብ የባህር በር ጥያቄ ታሪካዊ እውነታን የተመረኮዘ መሆኑን አብራርተዋል።
እንደ አቶ ዳንኤል ገለጻ፣ አሰብ በወቅቱ በኢትዮጵያ ውስጥ ከነበሩ ግንባር ቀደም ከተሞች አንዷ ከመሆኗም በላይ የሀገሪቱ ዋንኛ የገቢና ወጪ ንግድ ማዕከል በመሆን ለኢኮኖሚ እድገቱ እንደ ጀርባ አጥንት ታገለግል ነበር።
አቶ ዳንኤል የአሰብ ጥያቄ ዛሬ የተፈጠረ ሳይሆን ጥልቅ የታሪክ መሠረት ያለው መሆኑን ሲያስረዱም፤ አሰብ "የአሰብ ራስ-ገዝ አስተዳደር" (Assab Regional Autonomous) ተብላ ትጠራ እንደነበር አስታውሰዋል። ይህ መዋቅር አሰብን ከኤርትራ ራስ-ገዝ አስተዳደር ነጥሎ በቀጥታ ለማዕከላዊ መንግስት ተጠሪ የሚያደርግ ነበር።
የዚህ ራስ-ገዝ አስተዳደር ስፋትም ከምጽዋ አቅራቢያ ጀምሮ እስከ ጅቡቲ ጠረፍ ድረስ ያለውን ሰፊ የባህር ዳርቻ የሚያጠቃልል ነበር ይላሉ።
በ1983 ዓ.ም የመንግስት ለውጥ ሲመጣ የነበረውን ሁኔታ ያስታወሱት አቶ ዳንኤል፤ የከተማዋ ማህበራዊ ሕይወት፣ የትምህርት ሥርዓት እና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ከኢትዮጵያ መሃል ሀገር ጋር ፍጹም የተቆራኘ እንደነበር ገልጸዋል።
በወቅቱ አስመራ የነበሩ ነዋሪዎችም ቢሆኑ "አሰብ ለኢትዮጵያ አገልግሎት ካልሰጠች ለእኛም ፋይዳዋ አነስተኛ ነው" የሚል እምነት እንደነበራቸው ጠቅሰዋል።
በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤት እንድትሆን የሚቀርበው ጥያቄ ወቅታዊና ተገቢ መሆኑ አጠያያቂ አይደለም ብለዋል።
ከተማዋ የኢትዮጵያ የነዳጅ ማጣሪያ እና የትራንስፖርት ደም-ስር ሆና ለዓመታት ማገልገሏ፣ ዛሬ ለሚነሳው ጥያቄ ትልቅ የሞራልና የታሪክ አስረጂ ነው። ይህም የባህር በር ጥያቄው ህጋዊነት፣ ተገቢነት እና ወቅታዊነት የማይናወጥ መሠረት እንዳለው ያረጋግጣል።
በላሉ ኢታላ
#ethiopia #assab #redsea #addisababa #ethiopiannews #history
18 days ago
የሁለቱ ውኃዎች አዲስ የታሪክ ምዕራፍ
*************
ኢትዮጵያ - የጥቁር ሕዝቦች ኩራት፣ የሥልጣኔ መነሻና የነፃነት ተምሳሌት ናት።
ኢትዮጵያ በዘመኗ የቀይ ባሕርን የንግድ መስመር የምትቆጣጠር ታላቅ የባሕር ኃያል ነበረች።
ይህች ጥንታዊት ሀገር በታሪክ ማኅደር ውስጥ የነበራትን ገናናነት ዳግም ለማግኘት በምታደርገው ጉዞ፣ ከፊቷ የተጋረጡት ፈተናዎች ቀላል አይደሉም።
በተለይም የሀገራችን የሕልውና መሠረት ከሆኑት "ሁለቱ ውኃዎች" ማለትም ከታላቁ ዓባይ ወንዝ እና ከቀይ ባሕር ጋር ያላትን ተፈጥሯዊ ትሥሥር ለመበጠስ ለዘመናት የተጎነጎኑ ሴራዎች ዛሬም እንደ አዲስ አቆጥቁጠው ይታያሉ።
ኢትዮጵያን ከቀይ ባሕርና ከዓባይ ለመነጠል የሚደረጉ ጥረቶች ሁሉ ግባቸው አንድ ነው፤ እርሱም ሀገራችን ያላትን የተፈጥሮ ጸጋ ተጠቅማ የቀጣናው ልዕለ-ኃያል እንዳትሆን ማሰናከል!
ይሁን እንጂ የሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ፣ የባሕር ኃይሉ ዳግም መደራጀት እና ወደ ቀይ ባህር ባለቤትነታችን ለመመለስ እያደረግናቸው ያሉ አስደናቂ የዲፕሎማሲ ጥረቶች ኢትዮጵያ ይህን የዘመናት የከበባ ሰንሰለት ሰብራ ለመውጣት ያላትን ጽኑ ቁርጠኝነት የሚያሳዩ ድሎች ናቸው።
ኢትዮጵያን ከእነዚህ ሁለት ውኃዎች ነጥሎ ማቆየት ለቀጣናው ሰላም የማይበጅና በታሪክም ሊቀጥል የማይችል መሆኑን የሀገራችን ወቅታዊ ስትራቴጂያዊ አቅጣጫዎች በተግባር እያረጋገጡ ነው።
ኢትዮጵያ የባሕር በሯን አስከብራ፣ በዓባይ ወንዝ ላይ ያላትን መብት አረጋግጣ፣ ለምሥራቅ አፍሪካ ብልጽግና ዋስትና የምትሆንበት ጊዜ ሩቅ አይደለም።
ዝርዝር ትንታኔው በአስተያየት መስጫው ካጋራነው ሊንክ ይገኛል።
#ethiopia #abbayriver #bluenile #redsea #ebc
*************
ኢትዮጵያ - የጥቁር ሕዝቦች ኩራት፣ የሥልጣኔ መነሻና የነፃነት ተምሳሌት ናት።
ኢትዮጵያ በዘመኗ የቀይ ባሕርን የንግድ መስመር የምትቆጣጠር ታላቅ የባሕር ኃያል ነበረች።
ይህች ጥንታዊት ሀገር በታሪክ ማኅደር ውስጥ የነበራትን ገናናነት ዳግም ለማግኘት በምታደርገው ጉዞ፣ ከፊቷ የተጋረጡት ፈተናዎች ቀላል አይደሉም።
በተለይም የሀገራችን የሕልውና መሠረት ከሆኑት "ሁለቱ ውኃዎች" ማለትም ከታላቁ ዓባይ ወንዝ እና ከቀይ ባሕር ጋር ያላትን ተፈጥሯዊ ትሥሥር ለመበጠስ ለዘመናት የተጎነጎኑ ሴራዎች ዛሬም እንደ አዲስ አቆጥቁጠው ይታያሉ።
ኢትዮጵያን ከቀይ ባሕርና ከዓባይ ለመነጠል የሚደረጉ ጥረቶች ሁሉ ግባቸው አንድ ነው፤ እርሱም ሀገራችን ያላትን የተፈጥሮ ጸጋ ተጠቅማ የቀጣናው ልዕለ-ኃያል እንዳትሆን ማሰናከል!
ይሁን እንጂ የሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ፣ የባሕር ኃይሉ ዳግም መደራጀት እና ወደ ቀይ ባህር ባለቤትነታችን ለመመለስ እያደረግናቸው ያሉ አስደናቂ የዲፕሎማሲ ጥረቶች ኢትዮጵያ ይህን የዘመናት የከበባ ሰንሰለት ሰብራ ለመውጣት ያላትን ጽኑ ቁርጠኝነት የሚያሳዩ ድሎች ናቸው።
ኢትዮጵያን ከእነዚህ ሁለት ውኃዎች ነጥሎ ማቆየት ለቀጣናው ሰላም የማይበጅና በታሪክም ሊቀጥል የማይችል መሆኑን የሀገራችን ወቅታዊ ስትራቴጂያዊ አቅጣጫዎች በተግባር እያረጋገጡ ነው።
ኢትዮጵያ የባሕር በሯን አስከብራ፣ በዓባይ ወንዝ ላይ ያላትን መብት አረጋግጣ፣ ለምሥራቅ አፍሪካ ብልጽግና ዋስትና የምትሆንበት ጊዜ ሩቅ አይደለም።
ዝርዝር ትንታኔው በአስተያየት መስጫው ካጋራነው ሊንክ ይገኛል።
#ethiopia #abbayriver #bluenile #redsea #ebc
20 days ago
የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ትንሣኤ
***************
ኢትዮጵያ በታሪኳ ለዘመናት ከባሕር ጋር የነበራት ቁርኝት ከጂኦግራፊያዊ መሳ ለመሳነት በዘለለ የሀገራችን የሉዓላዊነት፣ የኢኮኖሚ ጥንካሬ እና የቀጣናዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነት መሠረት ሆኖ ኖሯል።
በጥንታዊው የአክሱም ሥልጣኔ ወቅት የአዱሊስ ወደብ የዓለም የንግድ ማዕከል ሆኖ ሲያገለግል፣ ኢትዮጵያውያን እ.ኤ.አ በ518 ወደ የመን ባሕር ተሻግረው ወታደራዊ ዘመቻዎችን ለማካሄድ የሚያስችሉ ከ70 በላይ የጦር መርከቦችን በአገር ውስጥ የመገንባት ጥበብ ነበራቸው።
ይህ ጥንታዊ የባሕር ግርማ በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የኦቶማን ቱርኮች ምጽዋን እስከተቆጣጠሩበት ጊዜ ድረስ የኢትዮጵያን የባሕር ሉዓላዊነት ሲያስከብር ቆይቷል።
የባሕር ኃይሉ መሥራችና ታሪካዊው ምዕራፍ ...
የዚህን መረጃ ሙሉ ሐሳብ አስተያየት መስጫው ውስጥ ካለው ሊንክ ያገኛሉ፦
#ebc #ethiopia #seaaccess #redsea
***************
ኢትዮጵያ በታሪኳ ለዘመናት ከባሕር ጋር የነበራት ቁርኝት ከጂኦግራፊያዊ መሳ ለመሳነት በዘለለ የሀገራችን የሉዓላዊነት፣ የኢኮኖሚ ጥንካሬ እና የቀጣናዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነት መሠረት ሆኖ ኖሯል።
በጥንታዊው የአክሱም ሥልጣኔ ወቅት የአዱሊስ ወደብ የዓለም የንግድ ማዕከል ሆኖ ሲያገለግል፣ ኢትዮጵያውያን እ.ኤ.አ በ518 ወደ የመን ባሕር ተሻግረው ወታደራዊ ዘመቻዎችን ለማካሄድ የሚያስችሉ ከ70 በላይ የጦር መርከቦችን በአገር ውስጥ የመገንባት ጥበብ ነበራቸው።
ይህ ጥንታዊ የባሕር ግርማ በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የኦቶማን ቱርኮች ምጽዋን እስከተቆጣጠሩበት ጊዜ ድረስ የኢትዮጵያን የባሕር ሉዓላዊነት ሲያስከብር ቆይቷል።
የባሕር ኃይሉ መሥራችና ታሪካዊው ምዕራፍ ...
የዚህን መረጃ ሙሉ ሐሳብ አስተያየት መስጫው ውስጥ ካለው ሊንክ ያገኛሉ፦
#ebc #ethiopia #seaaccess #redsea
Sponsored by
Surafel
21 days ago
u1355u122cu12ddu12f3u1295u1275 u121bu12adu122eu1295 u12ebu1230u1219u1275 u12e8u12a2u1275u12eeu1335u12eb u121du1235u122bu127eu127d | u12a2u1275u12ee u1218u120du1215u1245 | ETHIO MELHIK ETV | EBC | #ethiopia #france #ethiofrance #maritimesecurity #redsea #geopolitics #breakingnews #ethiomelhiq ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ፕሬዝዳንት ማክሮን ያሰሙት የኢትዮጵያ ምስራቾች | ኢትዮ መልሕቅ | ETHIO MELHIK ETV | EBC | #ethiopia #france #ethiofrance #maritimesecurity #redsea #geopolitics #breakingnews #ethiomelhiq
22 days ago
እንከባበር! - ኢራን
#ethiopia | ኢራን በኩዌት የታሰሩ ዜጎቿን በተመለከተ የአጸፋ እርምጃ የመውሰድ መብት እንዳለት አስታወቀች
በፋርስ ባሕረ ሰላጤ አቅራቢያ አራት ኢራናውያን በኩዌት የጸጥታ ኃይሎች መታሰራቸውን ተከትሎ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሀገራቸው ተመጣጣኝ ምላሽ የመስጠት መብት እንዳላት አስታውቃለችል፡፡
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቅቺ በሰጡት መግለጫ ኩዌት በሕገወጥ መንገድ በኢራን የባሕር ጓዝ ላይ ጥቃት መፈጸሟንና ዜጎቿን ማሰሯን ገልጸው የታሰሩት ግለሰቦች በአስቸኳይ እንዲፈቱ ጠይቀዋል፡፡
በሌላ በኩል የኩዌት የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ በባሕር በኩል ወደ ሀገር ውስጥ ለመግባት ሲሞክሩ የተያዙት አራት ግለሰቦች የኢራን አብዮታዊ ዘበኛ አባላት መሆናቸውን እንዳመኑ ይፋ አድርጓል፡፡
ይህንን ድርጊት ተከትሎ ዮርዳኖስ የኩዌትን ሉዓላዊነት የሚጋፋ ተግባር ነው ስትል ድርጊቱን ያወገዘች ሲሆን ለኩዌት ያላትን ሙሉ ድጋፍ ገልጻለች፡፡
ኢራን ግን ግለሰቦቹ ከአብዮታዊ ዘበኛው ጋር ግንኙነት አላቸው መባሉን አስተባብላለች፡፡
#iran #kuwait #middleeast #diplomacy #jordan #redsea #internationalnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ኢራን በኩዌት የታሰሩ ዜጎቿን በተመለከተ የአጸፋ እርምጃ የመውሰድ መብት እንዳለት አስታወቀች
በፋርስ ባሕረ ሰላጤ አቅራቢያ አራት ኢራናውያን በኩዌት የጸጥታ ኃይሎች መታሰራቸውን ተከትሎ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሀገራቸው ተመጣጣኝ ምላሽ የመስጠት መብት እንዳላት አስታውቃለችል፡፡
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቅቺ በሰጡት መግለጫ ኩዌት በሕገወጥ መንገድ በኢራን የባሕር ጓዝ ላይ ጥቃት መፈጸሟንና ዜጎቿን ማሰሯን ገልጸው የታሰሩት ግለሰቦች በአስቸኳይ እንዲፈቱ ጠይቀዋል፡፡
በሌላ በኩል የኩዌት የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ በባሕር በኩል ወደ ሀገር ውስጥ ለመግባት ሲሞክሩ የተያዙት አራት ግለሰቦች የኢራን አብዮታዊ ዘበኛ አባላት መሆናቸውን እንዳመኑ ይፋ አድርጓል፡፡
ይህንን ድርጊት ተከትሎ ዮርዳኖስ የኩዌትን ሉዓላዊነት የሚጋፋ ተግባር ነው ስትል ድርጊቱን ያወገዘች ሲሆን ለኩዌት ያላትን ሙሉ ድጋፍ ገልጻለች፡፡
ኢራን ግን ግለሰቦቹ ከአብዮታዊ ዘበኛው ጋር ግንኙነት አላቸው መባሉን አስተባብላለች፡፡
#iran #kuwait #middleeast #diplomacy #jordan #redsea #internationalnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
22 days ago
u12a2u1275u12eeu1335u12eb u1320u120bu1276u127fu1295 u12a8u1263u1215u1229 u12a5u1295u12f4u1275 u1273u1295u133b? | u12a2u1275u12ee u1218u120du1215u1245 | ETHIO MELHIK | #ethiopia #redsea #seaaccess #asseb #egypt #eritrea #nomorelandlocked #accesstothesea #ebc #etv #ebcdotstream ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ኢትዮጵያ ጠላቶቿን ከባሕሩ እንዴት ታንጻ? | ኢትዮ መልሕቅ | ETHIO MELHIK | #ethiopia #redsea #seaaccess #asseb #egypt #eritrea #nomorelandlocked #accesstothesea #ebc #etv #ebcdotstream
23 days ago
u12a2u1275u12eeu1335u12eb u1320u120bu1276u127fu1295 u12a8u1263u1215u1229 u12a5u1295u12f4u1275 u1273u1295u133b? | u12a2u1275u12ee u1218u120du1215u1245 | ETHIO MELHIK | #ethiopia #redsea #seaaccess #asseb #egypt #eritrea #nomorelandlocked #accesstothesea #ebc #etv #ebcdotstream ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ኢትዮጵያ ጠላቶቿን ከባሕሩ እንዴት ታንጻ? | ኢትዮ መልሕቅ | ETHIO MELHIK | #ethiopia #redsea #seaaccess #asseb #egypt #eritrea #nomorelandlocked #accesstothesea #ebc #etv #ebcdotstream
25 days ago
ቀይ ባሕር - ኢትዮጵያ ወደ ተፈጥሯዊ ቤቷ ትመለሳለች!
*****************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ በታሪክ ማኅደር ውስጥ ስሟ በገዘፈው ልክ፣ በመልክዓ-ምድራዊ እስር ውስጥ እንድትማቅቅ የተፈረደባት ሀገር ሆና እንድትቆይ የተደረገው በድንገቴ የታሪክ አጋጣሚ ሳይሆን በረቀቀ የባዕዳን ሴራ እና በውስጥ ባንዳዎች የታሪክ ክህደት ጭምር መሆኑ የአደባባይ ምስጢር ነው።
“ውኃ ሲወስድ እያሳሳቀ ነው” እንደሚባለው ሀገራችን የባሕር በሯን ስታጣ እና የየብስ እስረኛ ስትሆን ጉዳቱ የገባቸው ጥቂቶች ነበሩ። ዛሬ ግን ያ የታፈነ ታሪክ ትንፋሽ አግኝቶ ወደ ዓለም አቀፍ አጀንዳነት ተሸጋግሯል።
የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የቅንጦት ወይም የፍላጎት ጥያቄ ሳይሆን፣ ከሕልውና ጋር የተቆራኘ የሞት እና የሽረት ጉዳይ መሆኑን መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ እና መንግሥት በአንድ ድምፅ እያስተጋቡት ይገኛሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቁርጠኝነት እንደገለጹት ኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤት ካልሆነች ልማቷ ብቻ ሳይሆን ሰላሟም አደጋ ላይ ይወድቃል።
130 ሚሊዮን ሕዝብ ያቀፈች ግዙፍ ሀገር፣ የዓለም የንግድ መስመር በሆነው ቀይ ባሕር ላይ ተሳትፎ እና ባለቤትነት ሳይኖራት መቅረቷ ለቀጣናውም ቢሆን ዘላቂ ሰላምን አያመጣም። ትናንሽ ሀገራት ግዙፉን የንግድ ወሽመጥ የመጠበቅ አቅም ስለሌላቸው፣ እንደ ኢትዮጵያ ያሉ ሀገራት ከጉዳዩ መራቃቸው ለባሕር ላይ ወንበዴነት እና ለሽብርተኝነት በር የሚከፍት ነው። ስለሆነም የባሕር በር ጥያቄያችን ከስሜታዊነት በራቀ፣ በታሪክ፣ በሕግ እና በፍትሕ ላይ የተመሠረተ መሆኑን አሁን ዓለም ሊገነዘበው ይገባል።
ኢትዮጵያ የሌላውን ሉዓላዊነት የመንካት ፍላጎት ሳይኖራት፣ የራሷን የተፈጥሮ እና የታሪክ መብት ማስከበር ላይ ትኩረት ማድረጓ ፍጹም ምክንያታዊ ነው። የሌለንን ሳይሆን የነበረንን እና የሚገባንን ነው የምንጠይቀው።
ከኢኮኖሚ አኳያ ስንመለከተው፣ የባሕር በር ማጣት ለሀገራችን ትልቅ የደም ሥር መቋረጥ ነው። ዛሬ ላይ በዓመት እስከ 20 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን የሚደርስ የገቢ እና ወጪ ንግድ የምናስተናግድ ሲሆን ይህም በ2030 ወደ 35 ሚሊዮን ከፍ እንደሚል ይገመታል። ለወደብ አገልግሎት በየዓመቱ የምንከፍለው በቢሊዮን የሚቆጠሩ ዶላሮች የሀገራችንን ካዝና ከማድረቅ ባለፈ፣ ለልማት የሚውል ሀብታችንን አሳልፎ እየሰጠ ይገኛል።
የባሕር በር ማጣት ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ ነው።
“ጀግና ካልወደቀ አይነሣም” እንደሚባለው፣ ኢትዮጵያ ካለፈችባቸው የታሪክ ስብራቶች ታላቅ ትምህርት ቀስማለች። የባሕር በሯን ያጣችበት መንገድ ሕጋዊነት የጎደለው፣ በሕዝብ ውሳኔም ሆነ በተቋማት ዕውቅና ያልተደገፈ መሆኑ ዛሬ ላይ ለጥያቄያችን የሞራል እና የሕግ ልዕልናን ሰጥቶታል።
ጎረቤቶቻችን ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን የኢኮኖሚ ትሥሥር ቢያጠናክሩ የሁላችንም ተጠቃሚነት ይረጋገጣል። የኢትዮጵያ በባሕር ላይ መገኘት ለቀጣናው ደኅንነት ዋስትና እንጂ ስጋት አይደለም።
የራሷ የባሕር ኃይል እና የወደብ ይዞታ የነባራት ኢትዮጵያ፣ በቀይ ባሕር እና በኤደን ባሕረ ሰላጤ ያለውን የጂኦ-ፖለቲካዊ ውጥረት ለማርገብ እና ዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮችን ለመጠበቅ የሚኖራት ሚና ከፍተኛ ነው።
ይህ የትውልድ ጥያቄ እና የታሪክ አደራ ነው። ኢትዮጵያ “የመልክዓ-ምድር እስረኛ” ሆና የምትቆይበት ዘመን ማክተም አለበት።
የባሕር በር ጥያቄ ከስሜታዊነት የፀዳ፣ በፍትሕ ላይ የተመሠረተ እና ለዘላቂ ሰላም የሚቆም ነው። ኢትዮጵያ ከጂኦግራፊ እስረኝነት የምትላቀቅበት ቀን ሩቅ አይሆንም።
በደም እና በአጥንት ሀገራቸውን ጠብቀው ያቆዩልን አባቶቻችን የባሕር ላይ ጀግንነት ታሪክ ዛሬም በልባችን ታትሞ ይገኛል።
የሕዳሴው ግድብ የኤሌክትሪክ ብርሃናችንን እንዳረጋገጠልን ሁሉ፣ የወደብ ባለቤትነታችንም የባሕር ላይ ክብራችንን ዳግም የሚያበስር መሆኑ አይቀሬ ነው።
መጪው ትውልድ በየብስ የታጠረች ሳይሆን አድማስ ተሻጋሪ እና የባሕር ላይ ክብር ያላት ሀገር እንደሚረከብ ጽኑ እምነታችን ነው።
ዛሬ የምንዘራው የዲፕሎማሲ ዘር ነገ ለሀገራችን የብልፅግና ፍሬ ሆኖ ይበቅላል። ኢትዮጵያ በክብር ወደ ባሕሯ ትመለሳለች!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ebc #ethiopia #seaaccess #redsea #diplomacy
*****************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ በታሪክ ማኅደር ውስጥ ስሟ በገዘፈው ልክ፣ በመልክዓ-ምድራዊ እስር ውስጥ እንድትማቅቅ የተፈረደባት ሀገር ሆና እንድትቆይ የተደረገው በድንገቴ የታሪክ አጋጣሚ ሳይሆን በረቀቀ የባዕዳን ሴራ እና በውስጥ ባንዳዎች የታሪክ ክህደት ጭምር መሆኑ የአደባባይ ምስጢር ነው።
“ውኃ ሲወስድ እያሳሳቀ ነው” እንደሚባለው ሀገራችን የባሕር በሯን ስታጣ እና የየብስ እስረኛ ስትሆን ጉዳቱ የገባቸው ጥቂቶች ነበሩ። ዛሬ ግን ያ የታፈነ ታሪክ ትንፋሽ አግኝቶ ወደ ዓለም አቀፍ አጀንዳነት ተሸጋግሯል።
የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የቅንጦት ወይም የፍላጎት ጥያቄ ሳይሆን፣ ከሕልውና ጋር የተቆራኘ የሞት እና የሽረት ጉዳይ መሆኑን መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ እና መንግሥት በአንድ ድምፅ እያስተጋቡት ይገኛሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቁርጠኝነት እንደገለጹት ኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤት ካልሆነች ልማቷ ብቻ ሳይሆን ሰላሟም አደጋ ላይ ይወድቃል።
130 ሚሊዮን ሕዝብ ያቀፈች ግዙፍ ሀገር፣ የዓለም የንግድ መስመር በሆነው ቀይ ባሕር ላይ ተሳትፎ እና ባለቤትነት ሳይኖራት መቅረቷ ለቀጣናውም ቢሆን ዘላቂ ሰላምን አያመጣም። ትናንሽ ሀገራት ግዙፉን የንግድ ወሽመጥ የመጠበቅ አቅም ስለሌላቸው፣ እንደ ኢትዮጵያ ያሉ ሀገራት ከጉዳዩ መራቃቸው ለባሕር ላይ ወንበዴነት እና ለሽብርተኝነት በር የሚከፍት ነው። ስለሆነም የባሕር በር ጥያቄያችን ከስሜታዊነት በራቀ፣ በታሪክ፣ በሕግ እና በፍትሕ ላይ የተመሠረተ መሆኑን አሁን ዓለም ሊገነዘበው ይገባል።
ኢትዮጵያ የሌላውን ሉዓላዊነት የመንካት ፍላጎት ሳይኖራት፣ የራሷን የተፈጥሮ እና የታሪክ መብት ማስከበር ላይ ትኩረት ማድረጓ ፍጹም ምክንያታዊ ነው። የሌለንን ሳይሆን የነበረንን እና የሚገባንን ነው የምንጠይቀው።
ከኢኮኖሚ አኳያ ስንመለከተው፣ የባሕር በር ማጣት ለሀገራችን ትልቅ የደም ሥር መቋረጥ ነው። ዛሬ ላይ በዓመት እስከ 20 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን የሚደርስ የገቢ እና ወጪ ንግድ የምናስተናግድ ሲሆን ይህም በ2030 ወደ 35 ሚሊዮን ከፍ እንደሚል ይገመታል። ለወደብ አገልግሎት በየዓመቱ የምንከፍለው በቢሊዮን የሚቆጠሩ ዶላሮች የሀገራችንን ካዝና ከማድረቅ ባለፈ፣ ለልማት የሚውል ሀብታችንን አሳልፎ እየሰጠ ይገኛል።
የባሕር በር ማጣት ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ ነው።
“ጀግና ካልወደቀ አይነሣም” እንደሚባለው፣ ኢትዮጵያ ካለፈችባቸው የታሪክ ስብራቶች ታላቅ ትምህርት ቀስማለች። የባሕር በሯን ያጣችበት መንገድ ሕጋዊነት የጎደለው፣ በሕዝብ ውሳኔም ሆነ በተቋማት ዕውቅና ያልተደገፈ መሆኑ ዛሬ ላይ ለጥያቄያችን የሞራል እና የሕግ ልዕልናን ሰጥቶታል።
ጎረቤቶቻችን ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን የኢኮኖሚ ትሥሥር ቢያጠናክሩ የሁላችንም ተጠቃሚነት ይረጋገጣል። የኢትዮጵያ በባሕር ላይ መገኘት ለቀጣናው ደኅንነት ዋስትና እንጂ ስጋት አይደለም።
የራሷ የባሕር ኃይል እና የወደብ ይዞታ የነባራት ኢትዮጵያ፣ በቀይ ባሕር እና በኤደን ባሕረ ሰላጤ ያለውን የጂኦ-ፖለቲካዊ ውጥረት ለማርገብ እና ዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮችን ለመጠበቅ የሚኖራት ሚና ከፍተኛ ነው።
ይህ የትውልድ ጥያቄ እና የታሪክ አደራ ነው። ኢትዮጵያ “የመልክዓ-ምድር እስረኛ” ሆና የምትቆይበት ዘመን ማክተም አለበት።
የባሕር በር ጥያቄ ከስሜታዊነት የፀዳ፣ በፍትሕ ላይ የተመሠረተ እና ለዘላቂ ሰላም የሚቆም ነው። ኢትዮጵያ ከጂኦግራፊ እስረኝነት የምትላቀቅበት ቀን ሩቅ አይሆንም።
በደም እና በአጥንት ሀገራቸውን ጠብቀው ያቆዩልን አባቶቻችን የባሕር ላይ ጀግንነት ታሪክ ዛሬም በልባችን ታትሞ ይገኛል።
የሕዳሴው ግድብ የኤሌክትሪክ ብርሃናችንን እንዳረጋገጠልን ሁሉ፣ የወደብ ባለቤትነታችንም የባሕር ላይ ክብራችንን ዳግም የሚያበስር መሆኑ አይቀሬ ነው።
መጪው ትውልድ በየብስ የታጠረች ሳይሆን አድማስ ተሻጋሪ እና የባሕር ላይ ክብር ያላት ሀገር እንደሚረከብ ጽኑ እምነታችን ነው።
ዛሬ የምንዘራው የዲፕሎማሲ ዘር ነገ ለሀገራችን የብልፅግና ፍሬ ሆኖ ይበቅላል። ኢትዮጵያ በክብር ወደ ባሕሯ ትመለሳለች!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ebc #ethiopia #seaaccess #redsea #diplomacy
26 days ago
ሰማያዊ ኢኮኖሚ፡ ኢትዮጵያ ወደ ባሕር እየተመለሰች ነው #ebcdotstream #blueeconomy #gerd #የሕዳሴ_ግድብ #ethiopiannews #redsea
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
Sponsored by
Surafel
27 days ago
u12e8u12a2u1275u12eeu1335u12eb u1209u12a0u120bu12cau1290u1275 u12e8u121bu1235u12a8u1260u122d u12d8u1218u127bu12ceu127d | u12a2u1275u12ee_u1218u120du1205u1245 | Ethio-melik #pmabiyahimed #ethiopia #u12a2u1275u12eeu1335u12eb #sovereignty #u1209u12d3u120bu12cau1290u1275 #ethiopianpolitics #u12a2u1275u12ee_u1218u120du1205u1245 #redsea #seagateway #u12e8u1263u1205u122d_u1260u122d #hornofafrica #geopolitics #nationalinterest #strategy ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
የኢትዮጵያ ሉአላዊነት የማስከበር ዘመቻዎች | ኢትዮ_መልህቅ | Ethio-melik #pmabiyahimed #ethiopia #ኢትዮጵያ #sovereignty #ሉዓላዊነት #ethiopianpolitics #ኢትዮ_መልህቅ #redsea #seagateway #የባህር_በር #hornofafrica #geopolitics #nationalinterest #strategy
28 days ago
u12e8u12a2u1275u12eeu1335u12eb u1209u12a0u120bu12cau1290u1275 u12e8u121bu1235u12a8u1260u122d u12d8u1218u127bu12ceu127d | u12a2u1275u12ee_u1218u120du1205u1245 | Ethio-melik
#pmabiyahimed #ethiopia #u12a2u1275u12eeu1335u12eb #sovereignty #u1209u12d3u120bu12cau1290u1275 #ethiopianpolitics #u12a2u1275u12ee_u1218u120du1205u1245 #redsea #seagateway #u12e8u1263u1205u122d_u1260u122d #hornofafrica #geopolitics #nationalinterest #strategy ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
የኢትዮጵያ ሉአላዊነት የማስከበር ዘመቻዎች | ኢትዮ_መልህቅ | Ethio-melik
#pmabiyahimed #ethiopia #ኢትዮጵያ #sovereignty #ሉዓላዊነት #ethiopianpolitics #ኢትዮ_መልህቅ #redsea #seagateway #የባህር_በር #hornofafrica #geopolitics #nationalinterest #strategy
1 month ago
የባሕር በር ዋና ጉዳይ የሆነበት የፓርቲዎች ክርክር
ዛሬ ምሽት 2:30 ይጠብቁን! #ethiopiabroadcastingcorporation #ethiopia #nationalinterest #redsea #seaaccess
2 months ago
ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ጉዳይ 'ለሁሉም አሸናፊ' የሆነ ስትራቴጂካዊ መፍትሔ አስፈላጊነትን አሳሰበች
#ethiopia | ኢትዮጵያ ወደ ቀይ ባሕር ሉዓላዊ መዳረሻ ለማግኘት የምታደርገው ጥረት ለቀጣናው አገራት የጋራ ብልጽግና እና ለቀጣናዊ ውህደት ወሳኝ መሆኑን የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል አስታወቀ።
በአዲስ አበባ በተካሄደው 4ኛው ዓመታዊ የቀይ ባሕር እና የኤደን ባሕረ ሰላጤ ውይይት ላይ የተገኙት የባሕር ኃይል ዋና አዛዥ **ሪር አድሚራል ክንዱ ገዙ ፣ የኢትዮጵያ የባሕር በር ፍላጎት ከብሔራዊ ምኞት ባለፈ የአፍሪካ ኅብረት የ2063 አጀንዳን መሠረት ያደረገ ስትራቴጂካዊ ራዕይ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። አዛዡ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ላይ የምትፈልገው ሚና ሁሉንም ወገኖች ተጠቃሚ የሚያደርግ "ለሁሉም አሸናፊ" (Win-Win) መፍትሔ ነው።
በተጨማሪም በቀጣናው ላይ እያያንዣበቡ ያሉ የጸጥታ ስጋቶችን በተመለከተ የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች አንስተዋል
* የባሕር ላይ ወንጀሎችና ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያ ዝውውር መስፋፋት።
* *መደበኛ ያልሆነ ስደት እና በጂኦፖለቲካዊ ፉክክር የሚመጡ ውስብስብ ፈተናዎች።
* እነዚህን ችግሮች ለመፍታትም የቀጣናው አገራት በትብብር እና በስትራቴጂካዊ ውይይት መስራት እንዳለባቸው ጥሪ አቅርበዋል።
ይህ የኢትዮጵያ አቋም የቀይ ባሕር ቀጣናን ሰላምና ደኅንነት ከማረጋገጥ ባለፈ፣ የንግድና የኢኮኖሚ ትስስርን ለማጠናከር ፋይዳው የጎላ መሆኑ ተመላክቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ቅዳሜገበያ #etbusinessview #ethiopia #redsea
#ethiopia | ኢትዮጵያ ወደ ቀይ ባሕር ሉዓላዊ መዳረሻ ለማግኘት የምታደርገው ጥረት ለቀጣናው አገራት የጋራ ብልጽግና እና ለቀጣናዊ ውህደት ወሳኝ መሆኑን የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል አስታወቀ።
በአዲስ አበባ በተካሄደው 4ኛው ዓመታዊ የቀይ ባሕር እና የኤደን ባሕረ ሰላጤ ውይይት ላይ የተገኙት የባሕር ኃይል ዋና አዛዥ **ሪር አድሚራል ክንዱ ገዙ ፣ የኢትዮጵያ የባሕር በር ፍላጎት ከብሔራዊ ምኞት ባለፈ የአፍሪካ ኅብረት የ2063 አጀንዳን መሠረት ያደረገ ስትራቴጂካዊ ራዕይ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። አዛዡ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ላይ የምትፈልገው ሚና ሁሉንም ወገኖች ተጠቃሚ የሚያደርግ "ለሁሉም አሸናፊ" (Win-Win) መፍትሔ ነው።
በተጨማሪም በቀጣናው ላይ እያያንዣበቡ ያሉ የጸጥታ ስጋቶችን በተመለከተ የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች አንስተዋል
* የባሕር ላይ ወንጀሎችና ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያ ዝውውር መስፋፋት።
* *መደበኛ ያልሆነ ስደት እና በጂኦፖለቲካዊ ፉክክር የሚመጡ ውስብስብ ፈተናዎች።
* እነዚህን ችግሮች ለመፍታትም የቀጣናው አገራት በትብብር እና በስትራቴጂካዊ ውይይት መስራት እንዳለባቸው ጥሪ አቅርበዋል።
ይህ የኢትዮጵያ አቋም የቀይ ባሕር ቀጣናን ሰላምና ደኅንነት ከማረጋገጥ ባለፈ፣ የንግድና የኢኮኖሚ ትስስርን ለማጠናከር ፋይዳው የጎላ መሆኑ ተመላክቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ቅዳሜገበያ #etbusinessview #ethiopia #redsea
2 months ago
''ቀይ ባሕር ቢታመስም ለኢትዮጵያ ጭነቶች ቅድሚያ እሰጣለሁ'' ጅቡቲ
#ethiopia | በቀይ ባሕርና በፋርስ ባህረ ሰላጤ አካባቢ እየተባባሰ የመጣው የጸጥታ ቀውስ በዓለም አቀፉ የንግድ መርከቦች ፍሰት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ እያሳደረ ባለበት በዚህ ወቅት፣ ጅቡቲ ለኢትዮጵያ የሚገቡ የጭነት ምርቶች ቀዳሚ ትኩረት እንደምትሰጥ አስታወቀች።
የጅቡቲ ወደቦችና ነፃ ቀጠናዎች ባለሥልጣን ሰብሳቢ አቡበከር ዑመር ሃዲ ለካፒታል ጋዜጣ በሰጡት ቃለ ምልልስ እንዳረጋገጡት፣ በቀጠናው ባለው ግጭት ምክንያት ቀደም ሲል ወደ ዱባይ (ጀበል አሊ) ያመሩ የነበሩ በርካታ መርከቦች አሁን ላይ መዳረሻቸውን ወደ ጅቡቲ በመቀየር ላይ ይገኛሉ።
የወደቦች አቅም እና የመርከቦች ፍሰት
ይህ ድንገተኛ የመርከቦች ፍሰት መጨመር በወደቦች ላይ የሥራ ጫና እና መጨናነቅ ሊፈጥር ይችላል የሚል ስጋት ቢኖርም፣ ጅቡቲ ያሏት ስድስት ዘመናዊና ጥልቅ የባሕር ወደቦች ይህንን ጫና የመቋቋም ሙሉ ብቃት እንዳላቸው ሰብሳቢው ገልጸዋል።
በመሬት ትራንስፖርት ላይ ሊፈጠር የሚችለውን መጨናነቅ ለመቀነስም፣ ጭነቶችን ከመርከብ ወደ መርከብ የማሸጋገር (Transshipment) ስልት ጥቅም ላይ እንደሚውል ተጠቁሟል።
ለኢትዮጵያ የተሰጠው "ልዩ መስመር"
የጅቡቲ መንግሥት ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ስትራቴጂካዊ የሆኑ ምርቶች በተለይም እንደ ማዳበሪያ ያሉ የግብርና ግብዓቶች ያለምንም መስተጓጎልና መዘግየት እንዲስተናገዱ ልዩ መመሪያ ማውረዱን አቶ አቡበከር አረጋግጠዋል።
ይህም የክልሉ የጸጥታ ሁኔታ ቢዋዥቅም የኢትዮጵያ የንግድ መስመር እንዳይስተጓጎል ለማድረግ ታስቦ የተወሰደ እርምጃ መሆኑ ተገልጿል።
የጸጥታ ስጋትና የጅቡቲ አቋም
የየመኑ አንሳሩላህ (ሁቲ) አማፅያን በቀይ ባሕር ላይ በሚንቀሳቀሱ መርከቦች ላይ የሚሰነዝሩትን ጥቃት በተመለከተ፣ ጅቡቲ የጥቃቱ ኢላማ እንደማትሆን ባለሥልጣኑ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል። ለዚህም እንደ ምክንያት ያቀረቡት፦
* የጅቡቲ ወደቦች መገኛ ከባቢል መንደብ በስተደቡብ መሆኑ።
* ወደቦቹ በቀይ ባሕር መግቢያና በሕንድ ውቅያኖስ ደጃፍ ላይ የሚገኙ በመሆናቸው ከቀጥተኛ የጦርነት ቀጠና ነፃ መሆናቸውን ነው።
በአጠቃላይ፣ ጅቡቲ የቀጠናውን የጸጥታ ቀውስ ተቋቁማ ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የወደብ አገልግሎት በታማኝነትና በቅድሚያ እንደምትቀጥል አረጋግጣለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ቅዳሜ_ገበያ #ኢትዮጵያ #ጅቡቲ #የቀይባሕር #ንግድ #ወደብ #logistics #ethiopia #djibouti #redsea
#ethiopia | በቀይ ባሕርና በፋርስ ባህረ ሰላጤ አካባቢ እየተባባሰ የመጣው የጸጥታ ቀውስ በዓለም አቀፉ የንግድ መርከቦች ፍሰት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ እያሳደረ ባለበት በዚህ ወቅት፣ ጅቡቲ ለኢትዮጵያ የሚገቡ የጭነት ምርቶች ቀዳሚ ትኩረት እንደምትሰጥ አስታወቀች።
የጅቡቲ ወደቦችና ነፃ ቀጠናዎች ባለሥልጣን ሰብሳቢ አቡበከር ዑመር ሃዲ ለካፒታል ጋዜጣ በሰጡት ቃለ ምልልስ እንዳረጋገጡት፣ በቀጠናው ባለው ግጭት ምክንያት ቀደም ሲል ወደ ዱባይ (ጀበል አሊ) ያመሩ የነበሩ በርካታ መርከቦች አሁን ላይ መዳረሻቸውን ወደ ጅቡቲ በመቀየር ላይ ይገኛሉ።
የወደቦች አቅም እና የመርከቦች ፍሰት
ይህ ድንገተኛ የመርከቦች ፍሰት መጨመር በወደቦች ላይ የሥራ ጫና እና መጨናነቅ ሊፈጥር ይችላል የሚል ስጋት ቢኖርም፣ ጅቡቲ ያሏት ስድስት ዘመናዊና ጥልቅ የባሕር ወደቦች ይህንን ጫና የመቋቋም ሙሉ ብቃት እንዳላቸው ሰብሳቢው ገልጸዋል።
በመሬት ትራንስፖርት ላይ ሊፈጠር የሚችለውን መጨናነቅ ለመቀነስም፣ ጭነቶችን ከመርከብ ወደ መርከብ የማሸጋገር (Transshipment) ስልት ጥቅም ላይ እንደሚውል ተጠቁሟል።
ለኢትዮጵያ የተሰጠው "ልዩ መስመር"
የጅቡቲ መንግሥት ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ስትራቴጂካዊ የሆኑ ምርቶች በተለይም እንደ ማዳበሪያ ያሉ የግብርና ግብዓቶች ያለምንም መስተጓጎልና መዘግየት እንዲስተናገዱ ልዩ መመሪያ ማውረዱን አቶ አቡበከር አረጋግጠዋል።
ይህም የክልሉ የጸጥታ ሁኔታ ቢዋዥቅም የኢትዮጵያ የንግድ መስመር እንዳይስተጓጎል ለማድረግ ታስቦ የተወሰደ እርምጃ መሆኑ ተገልጿል።
የጸጥታ ስጋትና የጅቡቲ አቋም
የየመኑ አንሳሩላህ (ሁቲ) አማፅያን በቀይ ባሕር ላይ በሚንቀሳቀሱ መርከቦች ላይ የሚሰነዝሩትን ጥቃት በተመለከተ፣ ጅቡቲ የጥቃቱ ኢላማ እንደማትሆን ባለሥልጣኑ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል። ለዚህም እንደ ምክንያት ያቀረቡት፦
* የጅቡቲ ወደቦች መገኛ ከባቢል መንደብ በስተደቡብ መሆኑ።
* ወደቦቹ በቀይ ባሕር መግቢያና በሕንድ ውቅያኖስ ደጃፍ ላይ የሚገኙ በመሆናቸው ከቀጥተኛ የጦርነት ቀጠና ነፃ መሆናቸውን ነው።
በአጠቃላይ፣ ጅቡቲ የቀጠናውን የጸጥታ ቀውስ ተቋቁማ ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የወደብ አገልግሎት በታማኝነትና በቅድሚያ እንደምትቀጥል አረጋግጣለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ቅዳሜ_ገበያ #ኢትዮጵያ #ጅቡቲ #የቀይባሕር #ንግድ #ወደብ #logistics #ethiopia #djibouti #redsea
2 months ago
በቀይ ባሕር ላይ ውጥረት ነግሷል
#ethiopia | የብሉምበርግ ዘገባ የዜና ምንጮቹን ዋቢ አድርጎ እንደገለጸው፣ ኢራን በየመን የሚገኙት የሁቲ አማፂያን በንግድ መርከቦች ላይ የሚያደርሱትን ጥቃት እንዲቀጥሉ ግፊት እያደረገች ነው።
ይህ የኢራን ፍላጎት የመነጨው አሜሪካ በኢራን ላይ የምታደርገውን ወታደራዊ ጫና ለመቀልበስና በንግድ መስመሩ ላይ መስተጓጎል በመፍጠር አጸፋዊ ተፅዕኖ ለማሳረፍ ካለ እቅድ መሆኑ ተመላክቷል።
በሁቲዎች መካከል ያለው የሐሳብ ልዩነት
ምንም እንኳን ሁቲዎች በቅርቡ ወደ እስራኤል በቀጥታ ሚሳኤሎችን በመተኮስ ግጭቱ ውስጥ ቢገቡም፣ በቀይ ባሕር ላይ የሚደረገውን የባሕር ላይ ጥቃት በድጋሚ ስለመጀመር ግን በቡድኑ አመራሮች መካከል መከፋፈል መኖሩ ተገልጿል።
ከዚህ ቀደም በጋዛ እየተካሄደ ያለውን ጦርነት ለማስቆም በሚል በንግድ መርከቦች ላይ የተሰነዘሩ ጥቃቶች በዓለም አቀፍ የንግድ ፍሰት ላይ ከፍተኛ ቀውስ አስከትሎ እንደነበር ይታወሳል። አሁን የተጀመረው አዲስ እንቅስቃሴ ቀጠናውን ወደ ከፋ የጸጥታ ስጋት ሊከተው እንደሚችል ተሰግቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #redsea #breakingnews #middleeastconflict #houthi #iran #internationaltrade #maritimesecurity
#ethiopia | የብሉምበርግ ዘገባ የዜና ምንጮቹን ዋቢ አድርጎ እንደገለጸው፣ ኢራን በየመን የሚገኙት የሁቲ አማፂያን በንግድ መርከቦች ላይ የሚያደርሱትን ጥቃት እንዲቀጥሉ ግፊት እያደረገች ነው።
ይህ የኢራን ፍላጎት የመነጨው አሜሪካ በኢራን ላይ የምታደርገውን ወታደራዊ ጫና ለመቀልበስና በንግድ መስመሩ ላይ መስተጓጎል በመፍጠር አጸፋዊ ተፅዕኖ ለማሳረፍ ካለ እቅድ መሆኑ ተመላክቷል።
በሁቲዎች መካከል ያለው የሐሳብ ልዩነት
ምንም እንኳን ሁቲዎች በቅርቡ ወደ እስራኤል በቀጥታ ሚሳኤሎችን በመተኮስ ግጭቱ ውስጥ ቢገቡም፣ በቀይ ባሕር ላይ የሚደረገውን የባሕር ላይ ጥቃት በድጋሚ ስለመጀመር ግን በቡድኑ አመራሮች መካከል መከፋፈል መኖሩ ተገልጿል።
ከዚህ ቀደም በጋዛ እየተካሄደ ያለውን ጦርነት ለማስቆም በሚል በንግድ መርከቦች ላይ የተሰነዘሩ ጥቃቶች በዓለም አቀፍ የንግድ ፍሰት ላይ ከፍተኛ ቀውስ አስከትሎ እንደነበር ይታወሳል። አሁን የተጀመረው አዲስ እንቅስቃሴ ቀጠናውን ወደ ከፋ የጸጥታ ስጋት ሊከተው እንደሚችል ተሰግቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #redsea #breakingnews #middleeastconflict #houthi #iran #internationaltrade #maritimesecurity
3 months ago
የአሜሪካ ግዙፍ የጦር መርከቦች ከኢራን እያፈገፈጉ ነው
#ethiopia | ኢራንን ኢላማ አድርገው ተሰማርተው የነበሩ የዩናይትድ ስቴትስ ግዙፍ የጦር መርከቦች፣ ተዋጊ ጄቶችና የሚሳኤል መከላከያ ሬዳሮች ቀደም ሲል ከነበሩበት ይዞታ ማፈግፈጋቸው ተሰማ። የጀርመኑ ARD ቴሌቪዥንና የተለያዩ የዜና ምንጮች የአሜሪካ ባለሥልጣናትን ጠቅሰው እንደዘገቡት፣ የኃይል ሚዛኑን በከፍተኛ ሁኔታ የሚቀይር እርምጃ ተወስዷል።
ዋና ዋና የዜና ነጥቦች፦
* የUSS ጄራርድ ፎርድ መቃጠል፦ በቀይ ባሕር ጂዳ አቅራቢያ መሽጎ የነበረው ይህ ግዙፍ መርከብ በደረሰበት የቃጠሎ አደጋ ምክንያት ወደ ግሪክ ሶውዳ ቤይ እያመራ መሆኑ ተገልጿል። የቃጠሎው መንስኤ በውል ባይታወቅም ከየመን የተተኮሰ ሚሳኤል ወይም ከመርከቡ ውስጣዊ ብልሽት ሊሆን እንደሚችል ግምቶች አሉ።
* የUSS አብርሃም ሊንከን ማፈግፈግ፦ የሳተላይት መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ ይህ አውሮፕላን ተሸካሚ መርከብ ከኢራን ድንበር በ400 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ግን ከ1,000 ኪሎ ሜትር በላይ ወደሚርቅ ደቡባዊ አካባቢ ሸሽቷል።
* የፕሬዝዳንት ትራምፕ ቁጣ፦ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሆርሙስ ወሽመጥን ከኢራን ጥቃት ለመከላከል እንዲተባበሩ ያቀረቡትን ጥያቄ ውድቅ ያደረጉ የኔቶ (NATO) አባል ሀገራትን "ሞኞች" ሲሉ ወርፈዋል።
* ዲፕሎማሲያዊ ውጥረት፦ ትራምፕ የብሪታንያውን ጠቅላይ ሚኒስትር ኪር ስታርመርን "ታላቅ ስህተት ሰርተዋል" በማለት የሰነዘሩ ሲሆን፣ ከዚህ ጋር ተያይዞም ወደ ቻይና ሊያደርጉት የነበረውን ጉዞ ሰርዘዋል።
ይህ የአሜሪካ የጦር መርከቦች እንቅስቃሴ በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ወታደራዊ ስትራቴጂ ሊቀይረው እንደሚችል ተገምቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #usa #iran #ussnavy #donaldtrump #nato #redsea #militarynews #globalpolitics #breakingnews
#ethiopia | ኢራንን ኢላማ አድርገው ተሰማርተው የነበሩ የዩናይትድ ስቴትስ ግዙፍ የጦር መርከቦች፣ ተዋጊ ጄቶችና የሚሳኤል መከላከያ ሬዳሮች ቀደም ሲል ከነበሩበት ይዞታ ማፈግፈጋቸው ተሰማ። የጀርመኑ ARD ቴሌቪዥንና የተለያዩ የዜና ምንጮች የአሜሪካ ባለሥልጣናትን ጠቅሰው እንደዘገቡት፣ የኃይል ሚዛኑን በከፍተኛ ሁኔታ የሚቀይር እርምጃ ተወስዷል።
ዋና ዋና የዜና ነጥቦች፦
* የUSS ጄራርድ ፎርድ መቃጠል፦ በቀይ ባሕር ጂዳ አቅራቢያ መሽጎ የነበረው ይህ ግዙፍ መርከብ በደረሰበት የቃጠሎ አደጋ ምክንያት ወደ ግሪክ ሶውዳ ቤይ እያመራ መሆኑ ተገልጿል። የቃጠሎው መንስኤ በውል ባይታወቅም ከየመን የተተኮሰ ሚሳኤል ወይም ከመርከቡ ውስጣዊ ብልሽት ሊሆን እንደሚችል ግምቶች አሉ።
* የUSS አብርሃም ሊንከን ማፈግፈግ፦ የሳተላይት መረጃዎች እንደሚያመለክቱት፣ ይህ አውሮፕላን ተሸካሚ መርከብ ከኢራን ድንበር በ400 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ግን ከ1,000 ኪሎ ሜትር በላይ ወደሚርቅ ደቡባዊ አካባቢ ሸሽቷል።
* የፕሬዝዳንት ትራምፕ ቁጣ፦ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሆርሙስ ወሽመጥን ከኢራን ጥቃት ለመከላከል እንዲተባበሩ ያቀረቡትን ጥያቄ ውድቅ ያደረጉ የኔቶ (NATO) አባል ሀገራትን "ሞኞች" ሲሉ ወርፈዋል።
* ዲፕሎማሲያዊ ውጥረት፦ ትራምፕ የብሪታንያውን ጠቅላይ ሚኒስትር ኪር ስታርመርን "ታላቅ ስህተት ሰርተዋል" በማለት የሰነዘሩ ሲሆን፣ ከዚህ ጋር ተያይዞም ወደ ቻይና ሊያደርጉት የነበረውን ጉዞ ሰርዘዋል።
ይህ የአሜሪካ የጦር መርከቦች እንቅስቃሴ በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ወታደራዊ ስትራቴጂ ሊቀይረው እንደሚችል ተገምቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #usa #iran #ussnavy #donaldtrump #nato #redsea #militarynews #globalpolitics #breakingnews
4 months ago
🌊 "የባህር በር ተደራሽነት ለኢትዮጵያ የህልውና ጉዳይ ነው!"
— ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ 🇪🇹📢
#ethiopia | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአዲስ አበባ እየተካሄደ በሚገኘው 39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ በድጋሚ በዓለም አቀፍ መድረክ አጽንኦት ሰጥተውበታል።
ቁልፍ መልዕክቶች፦
⚓️ የህልውና ጉዳይ፦
ኢትዮጵያ በሰላማዊ አማራጮች አስተማማኝ የባህር በር ተደራሽነትን ማረጋገጥ መሠረታዊ እና የማይታለፍ ጉዳይ መሆኑን በጽኑ ገልጸዋል።
📈 መሰረተ ልማት እና ብልጽግና፦
ሀገሪቱ በአየር መንገድ፣ በቴሌኮምና በመንገድ ዘርፎች የገነባቻቸው ግዙፍ መሰረተ ልማቶች ሙሉ ትርጉም እንዲኖራቸው የባህር በር ተደራሽነት ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።
🤝 ሰላማዊ አማራጭ፦
የባህር በር ጥያቄው ከጎረቤት ሀገራት ጋር በሰላማዊ መንገድ እና በጋራ ተጠቃሚነት (Win-Win) መርህ ላይ ተመስርቶ ሊፈታ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
🌍 ቀጣናዊ ትስስር፦
ይህ ስኬት ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለቀጣናዊ ትስስርና ለጋራ ዕድገት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው አብራርተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም፣ ይህ ጥረት አህጉራዊውን ‘አጀንዳ 2063’ ግቦችን ለማሳካት ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ገልጸዋል።
#pmabiyahmed #ethiopia #africanunion #ausummit #seaport #redsea #regionalintegration #agenda2063 #addisababa #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
— ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ 🇪🇹📢
#ethiopia | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአዲስ አበባ እየተካሄደ በሚገኘው 39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ የኢትዮጵያን የባህር በር ጥያቄ በድጋሚ በዓለም አቀፍ መድረክ አጽንኦት ሰጥተውበታል።
ቁልፍ መልዕክቶች፦
⚓️ የህልውና ጉዳይ፦
ኢትዮጵያ በሰላማዊ አማራጮች አስተማማኝ የባህር በር ተደራሽነትን ማረጋገጥ መሠረታዊ እና የማይታለፍ ጉዳይ መሆኑን በጽኑ ገልጸዋል።
📈 መሰረተ ልማት እና ብልጽግና፦
ሀገሪቱ በአየር መንገድ፣ በቴሌኮምና በመንገድ ዘርፎች የገነባቻቸው ግዙፍ መሰረተ ልማቶች ሙሉ ትርጉም እንዲኖራቸው የባህር በር ተደራሽነት ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል።
🤝 ሰላማዊ አማራጭ፦
የባህር በር ጥያቄው ከጎረቤት ሀገራት ጋር በሰላማዊ መንገድ እና በጋራ ተጠቃሚነት (Win-Win) መርህ ላይ ተመስርቶ ሊፈታ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
🌍 ቀጣናዊ ትስስር፦
ይህ ስኬት ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለቀጣናዊ ትስስርና ለጋራ ዕድገት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው አብራርተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም፣ ይህ ጥረት አህጉራዊውን ‘አጀንዳ 2063’ ግቦችን ለማሳካት ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ገልጸዋል።
#pmabiyahmed #ethiopia #africanunion #ausummit #seaport #redsea #regionalintegration #agenda2063 #addisababa #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
Sponsored by
Surafel
4 months ago
🎬 በኢህአዴግ ባለሥልጣናት ታግዶ የነበረው የጥላሁን ጉግሳ "የባሕር በር" ፊልም ለዕይታ ሊቀርብ ነው!
#ethiopia | "ቤቶች ድራማ ከ13 ዓመታት በኋላ በክብር ሊሰናበት ነው"
አርቲስት፣ ደራሲ እና ዳይሬክተር ጥላሁን ጉግሳ (ዘለቀ) ሁለት ዓበይት ዜናዎችን አሰምቷል።
1️⃣ "ቤቶች" ሊያበቃ ነው!
ለ13 ተከታታይ ዓመታት ያለማቋረጥ በመተላለፍ ከዓለም 3ኛ፣ ከአፍሪካ ደግሞ 2ኛ ደረጃን የያዘውና የሁላችንም የሳሎን ትዝታ የሆነው "ቤቶች" የሲትኮም ድራማ፤ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ለተመልካች በክብር እንደሚሰናበት ተገልጿል።
2️⃣ ታግዶ የነበረው ፊልም ሊለቀቅ ነው!
ከዓመታት በፊት ተሠርቶ ለጥቂት ጊዜ እንደታየ በኢህአዴግ ባለስልጣናት "ስለ አሰብ የባሕር በር ያወራል" በሚል የታገደውና አርቲስቱንም ለዛቻ እና ማስፈራሪያ ዳርጎት የነበረው "የባሕር በር" ፊልም በቅርቡ ለዕይታ ይበቃል።
ለምን አሁን?
ጥላሁን እንደገለጸው፤ ከዚህ ቀደም የኢትዮ-ኤርትራን ግንኙነት ላለማበላሸት ታግሶ የነበረ ቢሆንም፤ አሁን ላይ የባሕር በር ጉዳይ እንደ አዲስ እየተጠየቀ በመሆኑ ፊልሙን ለመልቀቅ መወሰኑን ተናግሯል።
በተጨማሪም ከሁለተኛ ሴት ልጁ ጋር በመሆን አዲስ ረጅም ተከታታይ ፊልም ይዞ ለመምጣት ዝግጅቱን ጨርሷል።
የቤቶች ድራማን ምን ያህል ይወዱት ነበር? እስኪ ትዝታችሁን አካፍሉን።
#betochdrama #tilahungugsa #yebahirber #ethiopianfilm #artnews #redsea #ethiopia
#ethiopia | "ቤቶች ድራማ ከ13 ዓመታት በኋላ በክብር ሊሰናበት ነው"
አርቲስት፣ ደራሲ እና ዳይሬክተር ጥላሁን ጉግሳ (ዘለቀ) ሁለት ዓበይት ዜናዎችን አሰምቷል።
1️⃣ "ቤቶች" ሊያበቃ ነው!
ለ13 ተከታታይ ዓመታት ያለማቋረጥ በመተላለፍ ከዓለም 3ኛ፣ ከአፍሪካ ደግሞ 2ኛ ደረጃን የያዘውና የሁላችንም የሳሎን ትዝታ የሆነው "ቤቶች" የሲትኮም ድራማ፤ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ለተመልካች በክብር እንደሚሰናበት ተገልጿል።
2️⃣ ታግዶ የነበረው ፊልም ሊለቀቅ ነው!
ከዓመታት በፊት ተሠርቶ ለጥቂት ጊዜ እንደታየ በኢህአዴግ ባለስልጣናት "ስለ አሰብ የባሕር በር ያወራል" በሚል የታገደውና አርቲስቱንም ለዛቻ እና ማስፈራሪያ ዳርጎት የነበረው "የባሕር በር" ፊልም በቅርቡ ለዕይታ ይበቃል።
ለምን አሁን?
ጥላሁን እንደገለጸው፤ ከዚህ ቀደም የኢትዮ-ኤርትራን ግንኙነት ላለማበላሸት ታግሶ የነበረ ቢሆንም፤ አሁን ላይ የባሕር በር ጉዳይ እንደ አዲስ እየተጠየቀ በመሆኑ ፊልሙን ለመልቀቅ መወሰኑን ተናግሯል።
በተጨማሪም ከሁለተኛ ሴት ልጁ ጋር በመሆን አዲስ ረጅም ተከታታይ ፊልም ይዞ ለመምጣት ዝግጅቱን ጨርሷል።
የቤቶች ድራማን ምን ያህል ይወዱት ነበር? እስኪ ትዝታችሁን አካፍሉን።
#betochdrama #tilahungugsa #yebahirber #ethiopianfilm #artnews #redsea #ethiopia
5 months ago
🌊 "ከኢኮኖሚ ጥያቄ ባለፈ የህልውና ጉዳይ ነው" — የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች
#ethiopia | የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ የትውልዱ የማይታጠፍ አጀንዳ እና የሀገር ህልውና ጉዳይ መሆኑን የተለያዩ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች በጽኑ አቋም ገለጹ።
🇪🇹 የታሪክ ቁጭት እና የትውልድ ጥያቄ
ለዘመናት የባህር በር ባለቤት የነበረችው ኢትዮጵያ፣ በአሁኑ ወቅት ከ120 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ይዛ የወደብ አልባ ሀገር መሆኗ አግባብ እንዳልሆነ አመራሮቹ አንስተዋል። የሲዳማ አርነት ንቅናቄ (ሲአን) አመራር አቶ ደምሴ ሱካሬ፣ ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት ሁኔታ ግልጽነት የጎደለውና ቁጭት የፈጠረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ጥያቄው አሁን ላይ የብሔራዊ ደህንነት እና የቀጣናዊ ትስስር ዋነኛ ጉዳይ ሆኖ መውጣቱን ገልጸዋል።
🌍 የዲፕሎማሲ ስኬት እና የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ግንዛቤ
የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ኢሶዴፓ) ተወካይ አቶ በለጠ ሲጌቦ በበኩላቸው፣ የባህር በር ጉዳይ በአደባባይ መነሳቱ ብቻ ሳይሆን ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጉዳዩን እንዲገነዘበው መደረጉ ትልቅ የዲፕሎማሲ ስኬት መሆኑን አብራርተዋል። ይህም ለፍትሃዊ የባህር በር አጠቃቀም የሚደረገውን ትግል እንደሚያጠናክረው ገልጸዋል።
🏗️ "የቅንጦት ሳይሆን የመሰረታዊ ፍላጎት ጥያቄ"
የብልጽግና ፓርቲ አመራር አቶ ተስፋዬ ኤርሚያስ እንዳሉት፣ የባህር በር ጥያቄ እያደገ የመጣውን የሀገሪቱን ህዝብ ለመመገብና በዓለም አቀፍ የንግድ መድረክ ተወዳዳሪ ለመሆን ወሳኝ ነው። "ኢትዮጵያ የባህር በር ተቆልፎባት መኖር የማትችል መሆኑን ዓለም ሊገነዘበው ይገባል" ሲሉም አክለዋል።
ቁልፍ ነጥቦች፦
* የባህር በር ጥያቄ ከፖለቲካ ልዩነት በላይ የሆነ የሀገር የህልውና ጉዳይ ነው።
* ለወደፊት ትውልድ የሚተላለፍ ብሔራዊ አጀንዳ ነው።
* ጉዳዩ ከኢኮኖሚ ባለፈ ከብሔራዊ ደህንነት ጋር ቀጥተኛ ትስስር አለው።
* ዲፕሎማሲያዊ ጥረቱ በሁሉም ወገኖች ዘንድ ተቀባይነት እያገኘ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ኢትዮጵያ #የባህርበር #ብሔራዊጥቅም #የባህርበርባለቤትነት #ዲፕሎማሲ #ምስራቅአፍሪካ #የህልውናጉዳይ #ethiopia #seaaccess #redsea #portaccess
#ethiopia | የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ የትውልዱ የማይታጠፍ አጀንዳ እና የሀገር ህልውና ጉዳይ መሆኑን የተለያዩ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች በጽኑ አቋም ገለጹ።
🇪🇹 የታሪክ ቁጭት እና የትውልድ ጥያቄ
ለዘመናት የባህር በር ባለቤት የነበረችው ኢትዮጵያ፣ በአሁኑ ወቅት ከ120 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ይዛ የወደብ አልባ ሀገር መሆኗ አግባብ እንዳልሆነ አመራሮቹ አንስተዋል። የሲዳማ አርነት ንቅናቄ (ሲአን) አመራር አቶ ደምሴ ሱካሬ፣ ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት ሁኔታ ግልጽነት የጎደለውና ቁጭት የፈጠረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ጥያቄው አሁን ላይ የብሔራዊ ደህንነት እና የቀጣናዊ ትስስር ዋነኛ ጉዳይ ሆኖ መውጣቱን ገልጸዋል።
🌍 የዲፕሎማሲ ስኬት እና የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ግንዛቤ
የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ኢሶዴፓ) ተወካይ አቶ በለጠ ሲጌቦ በበኩላቸው፣ የባህር በር ጉዳይ በአደባባይ መነሳቱ ብቻ ሳይሆን ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጉዳዩን እንዲገነዘበው መደረጉ ትልቅ የዲፕሎማሲ ስኬት መሆኑን አብራርተዋል። ይህም ለፍትሃዊ የባህር በር አጠቃቀም የሚደረገውን ትግል እንደሚያጠናክረው ገልጸዋል።
🏗️ "የቅንጦት ሳይሆን የመሰረታዊ ፍላጎት ጥያቄ"
የብልጽግና ፓርቲ አመራር አቶ ተስፋዬ ኤርሚያስ እንዳሉት፣ የባህር በር ጥያቄ እያደገ የመጣውን የሀገሪቱን ህዝብ ለመመገብና በዓለም አቀፍ የንግድ መድረክ ተወዳዳሪ ለመሆን ወሳኝ ነው። "ኢትዮጵያ የባህር በር ተቆልፎባት መኖር የማትችል መሆኑን ዓለም ሊገነዘበው ይገባል" ሲሉም አክለዋል።
ቁልፍ ነጥቦች፦
* የባህር በር ጥያቄ ከፖለቲካ ልዩነት በላይ የሆነ የሀገር የህልውና ጉዳይ ነው።
* ለወደፊት ትውልድ የሚተላለፍ ብሔራዊ አጀንዳ ነው።
* ጉዳዩ ከኢኮኖሚ ባለፈ ከብሔራዊ ደህንነት ጋር ቀጥተኛ ትስስር አለው።
* ዲፕሎማሲያዊ ጥረቱ በሁሉም ወገኖች ዘንድ ተቀባይነት እያገኘ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ኢትዮጵያ #የባህርበር #ብሔራዊጥቅም #የባህርበርባለቤትነት #ዲፕሎማሲ #ምስራቅአፍሪካ #የህልውናጉዳይ #ethiopia #seaaccess #redsea #portaccess
8 months ago
" በአፍሪካ ቀንድ ፣ በቀይ ባህር ፣ በናይል ተፋሰስ ዙሪያ ትርጉም ያለው ውይይት ለማድረግ ዝግጁ ነኝ " - ኤርትራ
በአሜሪካ የስቴት ዲፓርትመንት መሥሪያ ቤት የፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከፍተኛ አማካሪ የሆኑት ማሳድ ቡሎስ አሜሪካ ኒውዮርክ በተባበሩት መንግሥታት (UN) ጉባኤ ላይ የሚገኙ ሲሆን ከተለያዩ ሀገራት ተወካዮች ጋር እየመከሩ ነው።
ትላንትና ከኤርትራው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳሌህ ጋር ውይይት አደርገዋል።
ከትላንቱ ውይይት አንዱ #ኢትዮጵያ ወደ አደባባይ ይዛው የወጣችውና ዓለም አቀፍ አጀንዳ ያደረገችው የቀይ ባህር ጉዳይ ይገኝበታል።
የኤርትራው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፤ ሀገራቸው ብሔራዊ ሉዓላዊነቷን በጠበቀ ሁኔታ በጋራ ጉዳዮች ላይ በተለም በአፍሪካ ቀንድ ፣ በናይል ተፋሰስ፣ #በቀይ_ባህር ዙሪያ ትርጉም ያለው ውይይት ለማድረግ ዝግጁ እንደሆነች ተናግረዋል።
ኤርትራ ለቀጠናዊ ሰላምና ዘላቂ ልማት ቁርጠኛ መሆኗን የገለጹት ሳሌህ ከአሜሪካ ጋር ትብብር ለማድረግ የተፈጠረውን እድል ሀገራቸው በደስታ እንደምትቀበለ አመልክተዋል።
የአሜሪካው ከፍተኛ ባለስልጣን ማሳድ ቦሎስ ሀገራቸው አሜሪካ ለዓለም አቀፍ ንግድ፣ ደህንነት እና ፀረ-ሽብርተኝነት ጥረቶች ወሳኝ በሆነ ቀጠና ውስጥ ውይይት እና መግባባትን ለመፍጠር ፅኑ ፍላጎት እንዳላት አስምረውበታል።
ውይይቱ በአሜሪካ እና ኤርትራ ግንኙነት ላይ አዲስ ምዕራፍ ለመክፈት መንገድ የሚጠርግ እንደሆነና ይህም በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በመሠረተ ልማት፣ በትራንስፖርት፣ ግንኙነት እና ደህንነት አጋርነት ላይ ለውይይት በር ሊከፍት የሚችል እንደሆነ አመልክተዋል።
የቆዩ ችግሮችን ገንቢ በሆነ ማዕቀፍ ውስጥ ለመፍታት እንደሚያስችልም ጠቁመዋል።
ሁለቱም ወገኖች በሚቀጥሉት ወራት ግንኙነታቸው ለመቀጠል በመስማማት ውይይታቸውን ቋጭተዋል።
በአሜሪካ የስቴት ዲፓርትመንት መሥሪያ ቤት የፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከፍተኛ አማካሪ የሆኑት ማሳድ ቡሎስ ከቀናት በፊት እዚህ #ኢትዮጵያ ነበሩ።
በጠቅላይ ሚኒስትር በጽሕፈት ቤት ተገኝተውም ከጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር በበርካታ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አደርገው ነው የሄዱት።
#ቀይ_ባህር #redsea
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#tikvahethiopiafamilyaa
tikvahethiopia
በአሜሪካ የስቴት ዲፓርትመንት መሥሪያ ቤት የፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከፍተኛ አማካሪ የሆኑት ማሳድ ቡሎስ አሜሪካ ኒውዮርክ በተባበሩት መንግሥታት (UN) ጉባኤ ላይ የሚገኙ ሲሆን ከተለያዩ ሀገራት ተወካዮች ጋር እየመከሩ ነው።
ትላንትና ከኤርትራው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳሌህ ጋር ውይይት አደርገዋል።
ከትላንቱ ውይይት አንዱ #ኢትዮጵያ ወደ አደባባይ ይዛው የወጣችውና ዓለም አቀፍ አጀንዳ ያደረገችው የቀይ ባህር ጉዳይ ይገኝበታል።
የኤርትራው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፤ ሀገራቸው ብሔራዊ ሉዓላዊነቷን በጠበቀ ሁኔታ በጋራ ጉዳዮች ላይ በተለም በአፍሪካ ቀንድ ፣ በናይል ተፋሰስ፣ #በቀይ_ባህር ዙሪያ ትርጉም ያለው ውይይት ለማድረግ ዝግጁ እንደሆነች ተናግረዋል።
ኤርትራ ለቀጠናዊ ሰላምና ዘላቂ ልማት ቁርጠኛ መሆኗን የገለጹት ሳሌህ ከአሜሪካ ጋር ትብብር ለማድረግ የተፈጠረውን እድል ሀገራቸው በደስታ እንደምትቀበለ አመልክተዋል።
የአሜሪካው ከፍተኛ ባለስልጣን ማሳድ ቦሎስ ሀገራቸው አሜሪካ ለዓለም አቀፍ ንግድ፣ ደህንነት እና ፀረ-ሽብርተኝነት ጥረቶች ወሳኝ በሆነ ቀጠና ውስጥ ውይይት እና መግባባትን ለመፍጠር ፅኑ ፍላጎት እንዳላት አስምረውበታል።
ውይይቱ በአሜሪካ እና ኤርትራ ግንኙነት ላይ አዲስ ምዕራፍ ለመክፈት መንገድ የሚጠርግ እንደሆነና ይህም በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በመሠረተ ልማት፣ በትራንስፖርት፣ ግንኙነት እና ደህንነት አጋርነት ላይ ለውይይት በር ሊከፍት የሚችል እንደሆነ አመልክተዋል።
የቆዩ ችግሮችን ገንቢ በሆነ ማዕቀፍ ውስጥ ለመፍታት እንደሚያስችልም ጠቁመዋል።
ሁለቱም ወገኖች በሚቀጥሉት ወራት ግንኙነታቸው ለመቀጠል በመስማማት ውይይታቸውን ቋጭተዋል።
በአሜሪካ የስቴት ዲፓርትመንት መሥሪያ ቤት የፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከፍተኛ አማካሪ የሆኑት ማሳድ ቡሎስ ከቀናት በፊት እዚህ #ኢትዮጵያ ነበሩ።
በጠቅላይ ሚኒስትር በጽሕፈት ቤት ተገኝተውም ከጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር በበርካታ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አደርገው ነው የሄዱት።
#ቀይ_ባህር #redsea
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#tikvahethiopiafamilyaa
tikvahethiopia