16 days ago
የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ አሸናፊ ስፔን የድል ዋንጫዋን ስትረከብ - (በምሥል)
*************
ስፔን የዘንድሮውን የዓለም ዋንጫ ከማሸነፍ ባሻገር የጨዋታው ሦስት ኮከቦች ማለትም የውድድሩ ምርጥ ወጣት ተጫዋች - ፓዎ ኩባርሲ፣ የውድድሩ ኮከብ ግብ ጠባቂ - ኡናይ ሲሞን እንዲሁም የውድድሩ ምርጥ ተጫዋች - ሮድሪ የተመረጡት ከሀገሪቱ (ስፔን) ነው።
የፈረንሳዩ የፊት መስመር ተጫዋች ኪሊያን ምባፔ በ10 ግቦች የውድድሩ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል።
#ebc #sports #worldcup #worldcup2026 #spain
*************
ስፔን የዘንድሮውን የዓለም ዋንጫ ከማሸነፍ ባሻገር የጨዋታው ሦስት ኮከቦች ማለትም የውድድሩ ምርጥ ወጣት ተጫዋች - ፓዎ ኩባርሲ፣ የውድድሩ ኮከብ ግብ ጠባቂ - ኡናይ ሲሞን እንዲሁም የውድድሩ ምርጥ ተጫዋች - ሮድሪ የተመረጡት ከሀገሪቱ (ስፔን) ነው።
የፈረንሳዩ የፊት መስመር ተጫዋች ኪሊያን ምባፔ በ10 ግቦች የውድድሩ ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል።
#ebc #sports #worldcup #worldcup2026 #spain
16 days ago
ስፔን የ23ኛው ዓለም ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነች
********************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ ስፔን አርጀንቲናን 1 ለ 0 በማሸነፍ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ ሆናለች።
የጨዋታው መደበኛ ክፍለ ጊዜ ያለ ግብ በመጠናቀቁ አሸናፊውን ለመለየት 30 ደቂቃ ተጨምሯል።
በጭማሪው ክፍለ ጊዜ 106ኛው ደቂቃ ላይ ፌራን ቶሬስ ያስቆጠራት ግብ ስፔንን አሸናፊ አድርጋለች።
በዚህም ስፔን ከ16 ዓመታት በኋላ ውድድሩን አሸንፋ በታሪኳ ለሁለተኛ ጊዜ የዓለም ዋንጫ ባለቤት ሆናለች።
#worldcup #fifaworldcup #fifaworldcup2026 #argentina #spain #finalmatch #football #sports
********************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ ስፔን አርጀንቲናን 1 ለ 0 በማሸነፍ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ ሆናለች።
የጨዋታው መደበኛ ክፍለ ጊዜ ያለ ግብ በመጠናቀቁ አሸናፊውን ለመለየት 30 ደቂቃ ተጨምሯል።
በጭማሪው ክፍለ ጊዜ 106ኛው ደቂቃ ላይ ፌራን ቶሬስ ያስቆጠራት ግብ ስፔንን አሸናፊ አድርጋለች።
በዚህም ስፔን ከ16 ዓመታት በኋላ ውድድሩን አሸንፋ በታሪኳ ለሁለተኛ ጊዜ የዓለም ዋንጫ ባለቤት ሆናለች።
#worldcup #fifaworldcup #fifaworldcup2026 #argentina #spain #finalmatch #football #sports
16 days ago
ስፔን 1-0 አርጀንቲና
*********
እየተካሄደ ባለው የ23ኛው ዓለም ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ ስፔን 106ኛው ደቂቃ ላይ በፌራን ቶሬስ አማካኝነት ባስቆጠረችው ግብ 1 ለ 0 መምራት ጀምራለች።
#worldcup #fifaworldcup #fifaworldcup2026 #argentina #spain #finalmatch #football #sports
*********
እየተካሄደ ባለው የ23ኛው ዓለም ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ ስፔን 106ኛው ደቂቃ ላይ በፌራን ቶሬስ አማካኝነት ባስቆጠረችው ግብ 1 ለ 0 መምራት ጀምራለች።
#worldcup #fifaworldcup #fifaworldcup2026 #argentina #spain #finalmatch #football #sports
16 days ago
አርጀንቲና 0 - 0 ስፔን :- የመደበኛ ሰዓት ውጤት
*****************
በአርጀንቲና እና በስፔን መካከል እየተደረገ የሚገኘው የዓለም ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ መደበኛው የ90 ደቂቃ ክፍለ ጊዜ ያለምንም ግብ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።
በጨዋታው መደበኛ ክፍለ ጊዜ አሸናፊ ባለመገኘቱ፣ አሸናፊውን ለመለየት ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አምርቷል።
ኤንዞ ፈርናንዴዝ ፓብሎ ኩባርሲ ላይ በሰራው ጥፋት 90+3 ደቂቃ ላይ በሁለት ቢጫ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል።
#worldcup #fifaworldcup #fifaworldcup2026 #argentina #spain #finalmatch #football #sports
*****************
በአርጀንቲና እና በስፔን መካከል እየተደረገ የሚገኘው የዓለም ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ መደበኛው የ90 ደቂቃ ክፍለ ጊዜ ያለምንም ግብ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።
በጨዋታው መደበኛ ክፍለ ጊዜ አሸናፊ ባለመገኘቱ፣ አሸናፊውን ለመለየት ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አምርቷል።
ኤንዞ ፈርናንዴዝ ፓብሎ ኩባርሲ ላይ በሰራው ጥፋት 90+3 ደቂቃ ላይ በሁለት ቢጫ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል።
#worldcup #fifaworldcup #fifaworldcup2026 #argentina #spain #finalmatch #football #sports
17 days ago
በዓለም ዋንጫ የደረጃ ጨዋታ እንግሊዝ ፈረንሳይን አሸነፈች
**********************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ 3ኛ ደረጃን ይዞ ለማጠናቀቅ በግማሽ ፍፃሜ ተፋላሚዎቹ ሀገራት መካከል የተካሄደው የደረጃ ጨዋታ፤ በእንግሊዝ 6 ለ 4 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
አስር ግቦች በተቆጠሩበት ጨዋታ፤ ለእንግሊዝ ዲክላን ራይስ፣ ኤዝሪ ኮንሳህ፣ ጁድ ቤሊንግሃም እንዲሁም ቡካዮ ሳካ(ሦስት) አስቆጥረዋል።
የፈረንሳይን ግቦች ደግሞ ኪሊያን ምባፔ(ሁለት)፣ ብራድሊ ባርኮላ እና ኡስማን ዴምቤሌ ከመረብ አሳርፈዋል።
በዚህም 3ኛ ደረጃን ያገኘችው እንግሊዝ የነሀስ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆናለች።
በጨዋታው ሁለት ግቦችን ያስቆጠረው ኪሊያን ምባፔ ደግሞ፤ በምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት 22ኛውን በዚህ ዓለም ዋንጫ ደግሞ 10ኛውን በማስመዝገብ የወርቅ ጫማ ሽልማት ፉክክሩን ከሊዮኔል ሜሲ በመላቅ አስቀድሞ መምራት ጀምሯል።
ማይክል ኦሊሴ በዓለም ዋንጫ ሰባት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል በፔሌ ተይዞ የነበረውን ክብረወሰን አሻሽሏል።
#worldcup #fifaworldcup #fifaworldcup2026 #3rdplaceplayoff #england #france #football #sports
**********************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ 3ኛ ደረጃን ይዞ ለማጠናቀቅ በግማሽ ፍፃሜ ተፋላሚዎቹ ሀገራት መካከል የተካሄደው የደረጃ ጨዋታ፤ በእንግሊዝ 6 ለ 4 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
አስር ግቦች በተቆጠሩበት ጨዋታ፤ ለእንግሊዝ ዲክላን ራይስ፣ ኤዝሪ ኮንሳህ፣ ጁድ ቤሊንግሃም እንዲሁም ቡካዮ ሳካ(ሦስት) አስቆጥረዋል።
የፈረንሳይን ግቦች ደግሞ ኪሊያን ምባፔ(ሁለት)፣ ብራድሊ ባርኮላ እና ኡስማን ዴምቤሌ ከመረብ አሳርፈዋል።
በዚህም 3ኛ ደረጃን ያገኘችው እንግሊዝ የነሀስ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆናለች።
በጨዋታው ሁለት ግቦችን ያስቆጠረው ኪሊያን ምባፔ ደግሞ፤ በምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት 22ኛውን በዚህ ዓለም ዋንጫ ደግሞ 10ኛውን በማስመዝገብ የወርቅ ጫማ ሽልማት ፉክክሩን ከሊዮኔል ሜሲ በመላቅ አስቀድሞ መምራት ጀምሯል።
ማይክል ኦሊሴ በዓለም ዋንጫ ሰባት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል በፔሌ ተይዞ የነበረውን ክብረወሰን አሻሽሏል።
#worldcup #fifaworldcup #fifaworldcup2026 #3rdplaceplayoff #england #france #football #sports
Sponsored by
Surafel
17 days ago
ከስንብት ሐዘን ማግስት የሚደረግ የክብር ፍልሚያ
*******************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ዋዜማ ላይ ቆመናል። ዓለም ዋንጫ በግማሽ ፍፃሜ በለስ ያልቀናቸውን፣ ድል ከነርሱ ጋር ያልነበረውን እንዲሁ አያሰናብትም። ለሦስተኝነት ማዕረግ ዳግም ያፋልማል።
23ኛው ዓለም ዋንጫ ፍሎሪዳ ላይ የግማሽ ፍፃሜ ተሸናፊዎቹን ዛሬ እኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ፍሎሪዳ ሚያሚ ላይ ያፎካክራል። በእርግጥ በብዙዎች፣ በተለይም በተሸናፊ ብሔራዊ ቡድኖች ዘንድ የደረጃው ጨዋታ ለመጫወት የተመረጠ አይደለም።
የዛሬው መርኃ ግብር ግን ብሔራዊ ቡድኖቹ ከሚያደርጉት ፉክክር ባልተናነሰ፣ በኮከብ ግብ አስቆጣሪነት በመላቅ የወርቅ ኳስ ሽልማቱን ለማግኘት ባለው ፉክክር ለውጥ እንደሚያስከትል ይጠበቃል። ከሊዮኔል ሜሲ ጋር የኮከብ ግብ አስቆጣሪነት ፉክክሩን በ8 ግቦች እየመራ የሚገኘው ኪሊያን ምባፔ እንዲሁም እያንዳንዳቸው ስድስት ግቦች ያስቆጠሩት ጁድ ቤሊንግሃም እና ሀሪኬን ከባለ አምስት ግቡ የዓለም ኮከብ ኡስማን ዴምቤሌ ጋር በሚያደርጉት የኮከብ ግብ አስቆጣሪነት ፉክክር ላይ አንዳች ለውጥ ሊያስከትል የሚችል ጨዋታ እንደሚሆን ታምኗል።
በዚህ መሀል ግን ከሽንፈት ማግስት የሚደረግ፤ ከዓለም ዋንጫ ስንብት ሀዘንም ሳያገግሙ የሚመጣ መርኃ ግብር መሆኑ የተጫዋቾችን ተነሳሽነት መቀነሱ፣ የተመልካቾችን ጉጉትም ማሳነሱ አይቀርም። ቶማስ ቱሄል ይህን የሚያስረግጥ ሃሳብ ነው የሰነዘሩት። "የእኛም ሆነ የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች ይህን ጨዋታ የማድረግ ፍላጎት የላቸውም" በማለት በውድድሩ ሙሉ የለፉትና የተዘጋጁት ለዓለም ሻምፒዮንነት በመሆኑና፤ ያም ባለመሳካቱ ለዚህ ጨዋታ የሚኖራቸውን ጉጉትና ፍላጎት እንደቀነሰው ተናግረዋል።
ቱሄል ይህንን ቢሉም የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ዲዲየር ዴሻው ግን ከዚህ በአንፃራዊነት የተለየ ሃሳብ ነው የሰነዘሩት። 3ኛ ደረጃም ቢሆን የተሻለ መሆኑን በማንሳት፤ እርሱን ለማሳካት የቻሉትን ሁሉ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል። አክለውም የተፈጠረው ሀዘን የዓለም ሻምፒዮን ከመሆን ፅኑ መሻት የመጣ መሆኑን ጠቅሰው፤ የሆነውን ከመቀበል ውጪ አማራጭ የለንም ብለዋል።
በግማሽ ፍፃሜው እንግሊዝ እየመራች የነበረችውን ጨዋታ የኋላ ኋላ በአርጀንቲና 2 ለ 1 ተሸንፋ የፍፃሜ መንገዷ ሲቋረጥ፤ በአንፃሩ ፈረንሳይ ባልተጠበቀ ሁኔታ በስፔን ፍፁም ብልጫ ተወስዶባት 2 ለ 0 ተረታ ነው ከፍፃሜው የቀረችው።
የ23ኛው ዓለም ዋንጫ 103ኛው ጨዋታ በሁለት ሃሳቦች መሀል፤ የጨዋታውን አስፈላጊነት ተጠይቅ ውስጥ በሚከቱና የኮከብ ግብ አግቢነት ፉክክሩ ላይ የሚኖረውን ሚና በሚያጎሉ መሀል ሆኖ፤ እኩለ ሌሊት 6፡00 ሰዓት በሚያሚ ጋርደን ሀርድ ሮክ ስታዲየም ይካሄዳል።
በእድሪስ አህመድ
#worldcup #fifaworldcup #fifaworldcup2026 #3rdplaceplayoff #england #france #football #sports
*******************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ዋዜማ ላይ ቆመናል። ዓለም ዋንጫ በግማሽ ፍፃሜ በለስ ያልቀናቸውን፣ ድል ከነርሱ ጋር ያልነበረውን እንዲሁ አያሰናብትም። ለሦስተኝነት ማዕረግ ዳግም ያፋልማል።
23ኛው ዓለም ዋንጫ ፍሎሪዳ ላይ የግማሽ ፍፃሜ ተሸናፊዎቹን ዛሬ እኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ፍሎሪዳ ሚያሚ ላይ ያፎካክራል። በእርግጥ በብዙዎች፣ በተለይም በተሸናፊ ብሔራዊ ቡድኖች ዘንድ የደረጃው ጨዋታ ለመጫወት የተመረጠ አይደለም።
የዛሬው መርኃ ግብር ግን ብሔራዊ ቡድኖቹ ከሚያደርጉት ፉክክር ባልተናነሰ፣ በኮከብ ግብ አስቆጣሪነት በመላቅ የወርቅ ኳስ ሽልማቱን ለማግኘት ባለው ፉክክር ለውጥ እንደሚያስከትል ይጠበቃል። ከሊዮኔል ሜሲ ጋር የኮከብ ግብ አስቆጣሪነት ፉክክሩን በ8 ግቦች እየመራ የሚገኘው ኪሊያን ምባፔ እንዲሁም እያንዳንዳቸው ስድስት ግቦች ያስቆጠሩት ጁድ ቤሊንግሃም እና ሀሪኬን ከባለ አምስት ግቡ የዓለም ኮከብ ኡስማን ዴምቤሌ ጋር በሚያደርጉት የኮከብ ግብ አስቆጣሪነት ፉክክር ላይ አንዳች ለውጥ ሊያስከትል የሚችል ጨዋታ እንደሚሆን ታምኗል።
በዚህ መሀል ግን ከሽንፈት ማግስት የሚደረግ፤ ከዓለም ዋንጫ ስንብት ሀዘንም ሳያገግሙ የሚመጣ መርኃ ግብር መሆኑ የተጫዋቾችን ተነሳሽነት መቀነሱ፣ የተመልካቾችን ጉጉትም ማሳነሱ አይቀርም። ቶማስ ቱሄል ይህን የሚያስረግጥ ሃሳብ ነው የሰነዘሩት። "የእኛም ሆነ የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች ይህን ጨዋታ የማድረግ ፍላጎት የላቸውም" በማለት በውድድሩ ሙሉ የለፉትና የተዘጋጁት ለዓለም ሻምፒዮንነት በመሆኑና፤ ያም ባለመሳካቱ ለዚህ ጨዋታ የሚኖራቸውን ጉጉትና ፍላጎት እንደቀነሰው ተናግረዋል።
ቱሄል ይህንን ቢሉም የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ዲዲየር ዴሻው ግን ከዚህ በአንፃራዊነት የተለየ ሃሳብ ነው የሰነዘሩት። 3ኛ ደረጃም ቢሆን የተሻለ መሆኑን በማንሳት፤ እርሱን ለማሳካት የቻሉትን ሁሉ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል። አክለውም የተፈጠረው ሀዘን የዓለም ሻምፒዮን ከመሆን ፅኑ መሻት የመጣ መሆኑን ጠቅሰው፤ የሆነውን ከመቀበል ውጪ አማራጭ የለንም ብለዋል።
በግማሽ ፍፃሜው እንግሊዝ እየመራች የነበረችውን ጨዋታ የኋላ ኋላ በአርጀንቲና 2 ለ 1 ተሸንፋ የፍፃሜ መንገዷ ሲቋረጥ፤ በአንፃሩ ፈረንሳይ ባልተጠበቀ ሁኔታ በስፔን ፍፁም ብልጫ ተወስዶባት 2 ለ 0 ተረታ ነው ከፍፃሜው የቀረችው።
የ23ኛው ዓለም ዋንጫ 103ኛው ጨዋታ በሁለት ሃሳቦች መሀል፤ የጨዋታውን አስፈላጊነት ተጠይቅ ውስጥ በሚከቱና የኮከብ ግብ አግቢነት ፉክክሩ ላይ የሚኖረውን ሚና በሚያጎሉ መሀል ሆኖ፤ እኩለ ሌሊት 6፡00 ሰዓት በሚያሚ ጋርደን ሀርድ ሮክ ስታዲየም ይካሄዳል።
በእድሪስ አህመድ
#worldcup #fifaworldcup #fifaworldcup2026 #3rdplaceplayoff #england #france #football #sports
19 days ago
እንግሊዝ በዓለም ዋንጫ፤ ለ60 ዓመታት ያልተፈታው ህልም፣ ያልተመለሰው ጥያቄ!
**************************
እንግሊዝ የዓለም ዋንጫን ዳግም ሳታነሳ ተጨማሪ 4 ዓመታት እንደሚቆጠሩ እርግጥ ከሆነ 24 ሰዓታት አለፉ። አትላንታ ላይ “ሦስቱ አናብስት” የዓለም ሻምፒዮን የመሆን ውጥን ይዘው፣ እስከ ግማሽ ፍፃሜም ተጉዘው የጀመሩት መንገድ በሊዮኔል ሜሲ አርጀንቲና ተቋርጧል። ለተጨማሪ ዓመታት እንዲወጡት የሚያስፈልግ ሌላ ዳገት፣ ሊወርዱትም የሚገባ ሌላ ቁልቁለት ‘ተበጅቶላቸዋል’።
እነዛ 60 ዓመታት በዓለም እግር ኳስ የራሷን አሻራ ላኖረችው ሀገር ብዙ መውጣትና መውረዶች፣ በርካታ ተስፋ አስቆራጭ ደግሞም ተስፋ መልሶ የለመለመባቸው ወቅቶች አልፎባቸዋል። ዓለም ዋንጫ ግን ያዝኩት ሲሉ እያመለጠ፣ ደረስኩበት ሲሉ እየራቀ “ጉም የመዝገን” ያክል ሆኖባቸዋል።
ሐምሌ 30/ 1966 እ.አ.አ ሰር ቦቢ ሙር የእንግሊዝን የመድረኩ ብቸኛ ድል፣ የቀደመውን የጁሊየስ ሪሜትስ ዋንጫ ካነሳ በኋላ ብዙ ነገሮች ባሉበት የሉም ተቀያይረዋል። እግር ኳስም፣ ራሷ እንግሊዝም ሆነ ዓለም ትላንትን አይመስሉም።
እንግሊዝ ምዕራብ ጀርመንን 4 ለ 2 አሸንፋ የመጀመሪያ ዓለም ዋንጫዋን ካነሳች በኋላ፤ 454 ተጫዋቾች ነጩን የብሔራዊ ቡድን መለያ ለመጀመሪያ ጊዜ ለብሰዋል። ቀዳሚው በ1967 የተጫወተው 847ኛው ተጫዋች ጆን ሆሊንስ ሲሆን፤ የብሔራዊ ቡድኑን መለያ በመልበስ ደግሞ የመጨረሻ የሆነው 1300ኛው የሊቨርፑሉ ሪዮ ንጉምሃ ነው። በዓለም ዋንጫው ደግሞ ከውጤታማው የአልፍ ራምሴይ ቡድን ጀምሮ እሰከ አሁኑ ቶማስ ቱሄል ድረስ 161 ተጫዋቾች እንግሊዝን ወክለዋል።
በስድሰቱ አስርታት ዋንጫ አልባ ዓመታት 15 አሰልጣኞች በቋሚነት ብሔራዊ ቡድኑን መርተዋል። ሮን ግሪንዉድ፣ ሰቨን ጎራን ኤሪክሰን፣ ፋቢዮ ካፔሎ እና ጋሬት ሳውዝጌት ተጠቃሾች ናቸው። ሁሉም ግን የአልፍ ራምሴይን ውጤታማ መንገድ ማስቀጠል አልሆነላቸውም።
አለን ሺረር፣ ዴቪድ ቤካም፣ ስቴቨን ጄራርድ እና ሃሪ ኬን ባለፉት 60 ዓመታት በተካሄዱት ዓለም ዋንጫዎች ቡድኑን በአምበልነት ከመሩ ተጫዋቾች የሚጠቀሱ ናቸው።
እንግሊዝ ከ1966 ሻምፒዮንነቷ በኋላ ከተካሄዱት 15 የዓለም ዋንጫዎች በ12ቱ ተሳትፋለች። በሁሉም ግን ደርሶ የመመለስ፣ አግኝቶም የማጣት ምሳሌ ተደርጋ ቀጥላለች። በ1986 የዲዬጎ ማራዶና በ4 ደቂቃ ልዩነት ያሳየው “የእጅም የእግርም” ትርዒት፣ በ1990 ግማሽ ፍጻሜ የፖል ጋስኮኝ እንባ፣ በ1998 ዓለም ዋንጫ የዴቪድ ቤካም ቀይ ካርድ፣ በ2002 ዓለም ዋንጫ የሮናልዲንሆ ጎቾ ዝነኛ የቅጣት ምት “ወርቃማ ግብ”፣ በ2010 መስመሯን አልፋ የተሻረችው የፍራንክ ላምፓርድ ግብ፣ በ2022 ዓለም ዋንጫ ሀሪ ኬን ያባከናት የፍፁም ቅጣት ምት፣ በመጨረሻም 2026 ላይ በአትላንታ ምድር እየመሩ የነበረውን ጨዋታ የኋላ ኋላ ማጣት፤ እንግሊዞች በቁጭት የሚያስታውሷቸው አጋጣሚዎች ናቸው።
ከዚያ በኋላ የበርሊን ግንብ ፈርሷል፣ የሰው ልጅ ወደ ጨረቃ መጥቋል፣ ዓለም በበይነ መረብ ተሳስሯል፣ የስማርት ስልክ ዘመን የሰው ልጅን የዕለት ተዕለት ህይወት ፈጣን አድርጓል። እነዚህና መሰል ለውጦች በሰው ልጅ የምድር ቆይታ ቢስተናገዱም፤ የእንግሊዝ የዓለም ዋንጫ ሻምፒዮንነት ህልም 1966 ላይ እንደቆመ አለ።
እንግሊዝ ባስተናገደችው የ1996ቱ አውሮፓ ዋንጫ ወቅት የተዜመው “…30 የህመም ዓመታት” የሚል ሀረግ የያዘውና የ1966ቱን ዓለም ዋንጫ በማስታወስ እግር ኳስ ወደ ቤቱ እየተመለሰ እንደሆነ የሚያትተው ኅብረ ዝማሬ፣ ዛሬም አውዱን የሳተ አይመስልም። 30ዎቹ ዓመታት ሌላ 30 ዓመታትን አዋልደዋል፤ እግር ኳስም ወደ “ቤቱ” አልተመለሰም።
የብሔራዊ ቡድኑን መለያ ከለበሱት 454 ተጫዋቾች፣ በዓለም ዋንጫው ከተጫወቱት 161 እግር ኳሰኞች፣ በ15ቱ አሰልጣኞች ስር ካለፉ 7 አምበሎች የምድር ትልቁን የእግር ኳስ ሽልማት ከፍ አድርጎ ማንሳት የቻለው ቦቢ ሙር ብቻ ነው።
ትውልድ ይተካል፣ ተስፋም እየደበዘዘም ቢሆን መልሶ ይለመልማል። እንግሊዛውያንም እግር ኳሳቸው በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም በሊግ ውድድሮች በቅርቦቹ ዓመታት እንዳሳደረው ተፅእኖ፤ ብሔራዊ ቡድናቸውም ይህን የዘመናት ህልሙን እውን የሚያደርግበትን ቀን በተስፋ ይጠባበቃሉ።
የ2026ቱ የአሜሪካ ምድር መንገድ ግን ጫፍ ደርሶ ተቋርጧል። ጁድ ቤሊንግሃም “ልብ ሰባሪ ፍፃሜን ያስከተለ ውብ ጉዞ” ሲል የገለፀው የ2026 ዓለም ዋንጫ ቆይታ አብቅቷል።
በእድሪስ አህመድ
#worldcup #fifaworldcup2026 #fifaworldcup1966 #england #threelions #judebellingham #harrykane #semifinal #football #sports #ebc
**************************
እንግሊዝ የዓለም ዋንጫን ዳግም ሳታነሳ ተጨማሪ 4 ዓመታት እንደሚቆጠሩ እርግጥ ከሆነ 24 ሰዓታት አለፉ። አትላንታ ላይ “ሦስቱ አናብስት” የዓለም ሻምፒዮን የመሆን ውጥን ይዘው፣ እስከ ግማሽ ፍፃሜም ተጉዘው የጀመሩት መንገድ በሊዮኔል ሜሲ አርጀንቲና ተቋርጧል። ለተጨማሪ ዓመታት እንዲወጡት የሚያስፈልግ ሌላ ዳገት፣ ሊወርዱትም የሚገባ ሌላ ቁልቁለት ‘ተበጅቶላቸዋል’።
እነዛ 60 ዓመታት በዓለም እግር ኳስ የራሷን አሻራ ላኖረችው ሀገር ብዙ መውጣትና መውረዶች፣ በርካታ ተስፋ አስቆራጭ ደግሞም ተስፋ መልሶ የለመለመባቸው ወቅቶች አልፎባቸዋል። ዓለም ዋንጫ ግን ያዝኩት ሲሉ እያመለጠ፣ ደረስኩበት ሲሉ እየራቀ “ጉም የመዝገን” ያክል ሆኖባቸዋል።
ሐምሌ 30/ 1966 እ.አ.አ ሰር ቦቢ ሙር የእንግሊዝን የመድረኩ ብቸኛ ድል፣ የቀደመውን የጁሊየስ ሪሜትስ ዋንጫ ካነሳ በኋላ ብዙ ነገሮች ባሉበት የሉም ተቀያይረዋል። እግር ኳስም፣ ራሷ እንግሊዝም ሆነ ዓለም ትላንትን አይመስሉም።
እንግሊዝ ምዕራብ ጀርመንን 4 ለ 2 አሸንፋ የመጀመሪያ ዓለም ዋንጫዋን ካነሳች በኋላ፤ 454 ተጫዋቾች ነጩን የብሔራዊ ቡድን መለያ ለመጀመሪያ ጊዜ ለብሰዋል። ቀዳሚው በ1967 የተጫወተው 847ኛው ተጫዋች ጆን ሆሊንስ ሲሆን፤ የብሔራዊ ቡድኑን መለያ በመልበስ ደግሞ የመጨረሻ የሆነው 1300ኛው የሊቨርፑሉ ሪዮ ንጉምሃ ነው። በዓለም ዋንጫው ደግሞ ከውጤታማው የአልፍ ራምሴይ ቡድን ጀምሮ እሰከ አሁኑ ቶማስ ቱሄል ድረስ 161 ተጫዋቾች እንግሊዝን ወክለዋል።
በስድሰቱ አስርታት ዋንጫ አልባ ዓመታት 15 አሰልጣኞች በቋሚነት ብሔራዊ ቡድኑን መርተዋል። ሮን ግሪንዉድ፣ ሰቨን ጎራን ኤሪክሰን፣ ፋቢዮ ካፔሎ እና ጋሬት ሳውዝጌት ተጠቃሾች ናቸው። ሁሉም ግን የአልፍ ራምሴይን ውጤታማ መንገድ ማስቀጠል አልሆነላቸውም።
አለን ሺረር፣ ዴቪድ ቤካም፣ ስቴቨን ጄራርድ እና ሃሪ ኬን ባለፉት 60 ዓመታት በተካሄዱት ዓለም ዋንጫዎች ቡድኑን በአምበልነት ከመሩ ተጫዋቾች የሚጠቀሱ ናቸው።
እንግሊዝ ከ1966 ሻምፒዮንነቷ በኋላ ከተካሄዱት 15 የዓለም ዋንጫዎች በ12ቱ ተሳትፋለች። በሁሉም ግን ደርሶ የመመለስ፣ አግኝቶም የማጣት ምሳሌ ተደርጋ ቀጥላለች። በ1986 የዲዬጎ ማራዶና በ4 ደቂቃ ልዩነት ያሳየው “የእጅም የእግርም” ትርዒት፣ በ1990 ግማሽ ፍጻሜ የፖል ጋስኮኝ እንባ፣ በ1998 ዓለም ዋንጫ የዴቪድ ቤካም ቀይ ካርድ፣ በ2002 ዓለም ዋንጫ የሮናልዲንሆ ጎቾ ዝነኛ የቅጣት ምት “ወርቃማ ግብ”፣ በ2010 መስመሯን አልፋ የተሻረችው የፍራንክ ላምፓርድ ግብ፣ በ2022 ዓለም ዋንጫ ሀሪ ኬን ያባከናት የፍፁም ቅጣት ምት፣ በመጨረሻም 2026 ላይ በአትላንታ ምድር እየመሩ የነበረውን ጨዋታ የኋላ ኋላ ማጣት፤ እንግሊዞች በቁጭት የሚያስታውሷቸው አጋጣሚዎች ናቸው።
ከዚያ በኋላ የበርሊን ግንብ ፈርሷል፣ የሰው ልጅ ወደ ጨረቃ መጥቋል፣ ዓለም በበይነ መረብ ተሳስሯል፣ የስማርት ስልክ ዘመን የሰው ልጅን የዕለት ተዕለት ህይወት ፈጣን አድርጓል። እነዚህና መሰል ለውጦች በሰው ልጅ የምድር ቆይታ ቢስተናገዱም፤ የእንግሊዝ የዓለም ዋንጫ ሻምፒዮንነት ህልም 1966 ላይ እንደቆመ አለ።
እንግሊዝ ባስተናገደችው የ1996ቱ አውሮፓ ዋንጫ ወቅት የተዜመው “…30 የህመም ዓመታት” የሚል ሀረግ የያዘውና የ1966ቱን ዓለም ዋንጫ በማስታወስ እግር ኳስ ወደ ቤቱ እየተመለሰ እንደሆነ የሚያትተው ኅብረ ዝማሬ፣ ዛሬም አውዱን የሳተ አይመስልም። 30ዎቹ ዓመታት ሌላ 30 ዓመታትን አዋልደዋል፤ እግር ኳስም ወደ “ቤቱ” አልተመለሰም።
የብሔራዊ ቡድኑን መለያ ከለበሱት 454 ተጫዋቾች፣ በዓለም ዋንጫው ከተጫወቱት 161 እግር ኳሰኞች፣ በ15ቱ አሰልጣኞች ስር ካለፉ 7 አምበሎች የምድር ትልቁን የእግር ኳስ ሽልማት ከፍ አድርጎ ማንሳት የቻለው ቦቢ ሙር ብቻ ነው።
ትውልድ ይተካል፣ ተስፋም እየደበዘዘም ቢሆን መልሶ ይለመልማል። እንግሊዛውያንም እግር ኳሳቸው በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም በሊግ ውድድሮች በቅርቦቹ ዓመታት እንዳሳደረው ተፅእኖ፤ ብሔራዊ ቡድናቸውም ይህን የዘመናት ህልሙን እውን የሚያደርግበትን ቀን በተስፋ ይጠባበቃሉ።
የ2026ቱ የአሜሪካ ምድር መንገድ ግን ጫፍ ደርሶ ተቋርጧል። ጁድ ቤሊንግሃም “ልብ ሰባሪ ፍፃሜን ያስከተለ ውብ ጉዞ” ሲል የገለፀው የ2026 ዓለም ዋንጫ ቆይታ አብቅቷል።
በእድሪስ አህመድ
#worldcup #fifaworldcup2026 #fifaworldcup1966 #england #threelions #judebellingham #harrykane #semifinal #football #sports #ebc
19 days ago
"በሚሊዮን አንድ ጊዜ የሚከሰት ታሪክ!"
*********
ሊዮኔል ሜሲ እና ላሚን ያማል በ2026ቱ የፊፋ ዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድ ሜዳ ላይ ለመገናኘት ተዘጋጅተዋል።
ነገር ግን በመካከላቸው ያለው አስገራሚ ግንኙነት የተጀመረው ከሁለት አስርት ዓመታት ገደማ በፊት ነበር።
እ.አ.አ. በታኅሣሥ 2007 የ20 ዓመቱ ወጣት ሊዮኔል ሜሲ ለባርሴሎና ፋውንዴሽን የበጎ አድራጎት ቀን በሚዘጋጅ የፎቶ ግራፍ መርኃ ግብር ላይ ተሳትፎ ነበር።
በወቅቱ ሜሲ አምስት ወር ከሆነው ሕፃን ላሚን ያማል ጋር አብሮ ፎቶ የተነሳ ሲሆን፣ ሕፃኑን በገንዳ ውስጥ ሲያጥበውና ሲንከባከበው የሚያሳዩት እነዚህ ምስሎች ለዩኒሴፍ እና ለሌሎች በጎ አድራጎት ድርጅቶች ገቢ ማሰባሰቢያነት ታትመው ወጥተዋል።
ይህን ታሪካዊ ምስል የቀረጸው ፎቶ ግራፍ አንሺ ጆአን ሞንፎርት በሰጠው አስተያየት፤ በወቅቱ የወደፊቱን ማንም እንዳልገመተው ተናግሯል።
በዚያን ጊዜ ሜሲ የምንግዜም ታላቁ እግር ኳስ ተጫዋች ለመሆን ገና ጉዞውን የጀመረበት ወቅት የነበረ ሲሆን፣ ያማል ደግሞ በፕሮጀክቱ ላይ ከተሳተፉት በርካታ ሕፃናት መካከል አንዱ ነበር።
ይህ ታሪካዊ ፎቶ ግራፍ የመገናኛ ብዙኃንን ትኩረት የሳበው በ2024ቱ የአውሮፓ ዋንጫ ወቅት የያማል አባት በማኅበራዊ ሚዲያ ካጋሩት በኋላ ነበር።
ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ምስሉ የሁለቱን የባርሴሎና ትውልድ ኮከቦች የሚወክል የእግር ኳስ ታሪክ ተምሳሌት ሆኗል።
ያማል በ2014 የባርሴሎናውን ላማሲያ አካዳሚን የተቀላቀለ ሲሆን፣ ፈጣን ዕድገት በማሳየት ገና በ15 ዓመቱ ለዋናው ቡድን መጫወት ችሏል።
አሁን ላይ የስፔን እግር ኳስ ትልቁ ተስፋ የሆነው ያማል፣ በባርሴሎና ቤት የሜሲን ታሪካዊ የ10 ቁጥር መለያ የሚለብስ ሲሆን በብዙዎች ዘንድም የሜሲ ተተኪ ተደርጎም ይወሰዳል።
አሁን ግን የእግር ኳስ ታሪክ አስደናቂውን ምዕራፍ ሊያሳየን ተቃርቧል።
በአንድ ወቅት በሜሲ እቅፍ ውስጥ የነበረው ያ ሕፃን፣ አሁን በትልቁ መድረክ ማለትም በዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ላይ የልጅነት አርአያውን ፊት ለፊት ለመጋፈጥ እየተዘጋጀ ይገኛል።
ፎቶግራፍ አንሺው ጆአን ሞንፎርት ይህንን ታሪክ "በሚሊዮን አንድ ጊዜ ብቻ የሚከሰት" ሲል ገልጾታል።
በእሱባለው ተሾመ
#worldcup #sports #messi #lamineyamal #ebc
*********
ሊዮኔል ሜሲ እና ላሚን ያማል በ2026ቱ የፊፋ ዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድ ሜዳ ላይ ለመገናኘት ተዘጋጅተዋል።
ነገር ግን በመካከላቸው ያለው አስገራሚ ግንኙነት የተጀመረው ከሁለት አስርት ዓመታት ገደማ በፊት ነበር።
እ.አ.አ. በታኅሣሥ 2007 የ20 ዓመቱ ወጣት ሊዮኔል ሜሲ ለባርሴሎና ፋውንዴሽን የበጎ አድራጎት ቀን በሚዘጋጅ የፎቶ ግራፍ መርኃ ግብር ላይ ተሳትፎ ነበር።
በወቅቱ ሜሲ አምስት ወር ከሆነው ሕፃን ላሚን ያማል ጋር አብሮ ፎቶ የተነሳ ሲሆን፣ ሕፃኑን በገንዳ ውስጥ ሲያጥበውና ሲንከባከበው የሚያሳዩት እነዚህ ምስሎች ለዩኒሴፍ እና ለሌሎች በጎ አድራጎት ድርጅቶች ገቢ ማሰባሰቢያነት ታትመው ወጥተዋል።
ይህን ታሪካዊ ምስል የቀረጸው ፎቶ ግራፍ አንሺ ጆአን ሞንፎርት በሰጠው አስተያየት፤ በወቅቱ የወደፊቱን ማንም እንዳልገመተው ተናግሯል።
በዚያን ጊዜ ሜሲ የምንግዜም ታላቁ እግር ኳስ ተጫዋች ለመሆን ገና ጉዞውን የጀመረበት ወቅት የነበረ ሲሆን፣ ያማል ደግሞ በፕሮጀክቱ ላይ ከተሳተፉት በርካታ ሕፃናት መካከል አንዱ ነበር።
ይህ ታሪካዊ ፎቶ ግራፍ የመገናኛ ብዙኃንን ትኩረት የሳበው በ2024ቱ የአውሮፓ ዋንጫ ወቅት የያማል አባት በማኅበራዊ ሚዲያ ካጋሩት በኋላ ነበር።
ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ምስሉ የሁለቱን የባርሴሎና ትውልድ ኮከቦች የሚወክል የእግር ኳስ ታሪክ ተምሳሌት ሆኗል።
ያማል በ2014 የባርሴሎናውን ላማሲያ አካዳሚን የተቀላቀለ ሲሆን፣ ፈጣን ዕድገት በማሳየት ገና በ15 ዓመቱ ለዋናው ቡድን መጫወት ችሏል።
አሁን ላይ የስፔን እግር ኳስ ትልቁ ተስፋ የሆነው ያማል፣ በባርሴሎና ቤት የሜሲን ታሪካዊ የ10 ቁጥር መለያ የሚለብስ ሲሆን በብዙዎች ዘንድም የሜሲ ተተኪ ተደርጎም ይወሰዳል።
አሁን ግን የእግር ኳስ ታሪክ አስደናቂውን ምዕራፍ ሊያሳየን ተቃርቧል።
በአንድ ወቅት በሜሲ እቅፍ ውስጥ የነበረው ያ ሕፃን፣ አሁን በትልቁ መድረክ ማለትም በዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ላይ የልጅነት አርአያውን ፊት ለፊት ለመጋፈጥ እየተዘጋጀ ይገኛል።
ፎቶግራፍ አንሺው ጆአን ሞንፎርት ይህንን ታሪክ "በሚሊዮን አንድ ጊዜ ብቻ የሚከሰት" ሲል ገልጾታል።
በእሱባለው ተሾመ
#worldcup #sports #messi #lamineyamal #ebc
20 days ago
አርጀንቲና ወደ ዓለም ዋንጫ ፍፃሜ አለፈች
***************
በ23ኛው የዓለም ዋንጫ በአትላንታ ስታዲየም በእንግሊዝና አርጀንቲና መካከል የተካሄደው ተጠባቂ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ በአርጀንቲና 2 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
ለአርጀንቲና የአሸናፊነት ግቦቹን በ85ኛው ደቂቃ ኤንዞ ፈርናንዴዝ እንዲሁም በጭማሪ ሰዓት (90+3) ላውታሮ ማርቲኔዝ ከመረብ አሳርፈዋል። ለእንግሊዝ ብቸኛዋን ግብ በ55ኛው ደቂቃ አንቶኒ ጎርደን አስቆጥሯል።
የወቅቱ የዓለም ሻምፒዮን አርጀንቲና ለዋንጫው ክብሯን ለማስጠበቅ የፊታችን እሁድ ከስፔን ብሔራዊ ቡድን ጋር ታላቅ የፍፃሜ ጨዋታዋን ታደርጋለች።
የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታዎች ተሸናፊዎቹ ፈረንሳይና እንግሊዝ ደግሞ የፊታችን ቅዳሜ ሌሊት 3ኛ ደረጃ ይዞ ለማጠናቀቅ የሚጫወቱ ይሆናል።
#worldcup #fifaworldcup2026 #fifaworldcup #england #argentina #semifinal #football #sports
***************
በ23ኛው የዓለም ዋንጫ በአትላንታ ስታዲየም በእንግሊዝና አርጀንቲና መካከል የተካሄደው ተጠባቂ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ በአርጀንቲና 2 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
ለአርጀንቲና የአሸናፊነት ግቦቹን በ85ኛው ደቂቃ ኤንዞ ፈርናንዴዝ እንዲሁም በጭማሪ ሰዓት (90+3) ላውታሮ ማርቲኔዝ ከመረብ አሳርፈዋል። ለእንግሊዝ ብቸኛዋን ግብ በ55ኛው ደቂቃ አንቶኒ ጎርደን አስቆጥሯል።
የወቅቱ የዓለም ሻምፒዮን አርጀንቲና ለዋንጫው ክብሯን ለማስጠበቅ የፊታችን እሁድ ከስፔን ብሔራዊ ቡድን ጋር ታላቅ የፍፃሜ ጨዋታዋን ታደርጋለች።
የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታዎች ተሸናፊዎቹ ፈረንሳይና እንግሊዝ ደግሞ የፊታችን ቅዳሜ ሌሊት 3ኛ ደረጃ ይዞ ለማጠናቀቅ የሚጫወቱ ይሆናል።
#worldcup #fifaworldcup2026 #fifaworldcup #england #argentina #semifinal #football #sports
20 days ago
እንግሊዝ 0 - 0 አርጀንቲና :- የመጀመሪያ አጋማሽ ውጤት
**************
በአትላንታ ስታዲየም በእንግሊዝ እና አርጀንቲና መካከል እየተካሄደ የሚገኘው እጅግ ተጠባቂ የዓለም ዋንጫ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ የመጀመሪያው 45 ደቂቃ ያለምንም ግብ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።
#worldcup #fifaworldcup2026 #fifaworldcup #england #argentina #semifinal #football #sports
**************
በአትላንታ ስታዲየም በእንግሊዝ እና አርጀንቲና መካከል እየተካሄደ የሚገኘው እጅግ ተጠባቂ የዓለም ዋንጫ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ የመጀመሪያው 45 ደቂቃ ያለምንም ግብ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።
#worldcup #fifaworldcup2026 #fifaworldcup #england #argentina #semifinal #football #sports
24 days ago
እንግሊዝ ለግማሽ ፍፃሜው ደረሰች
*******************
በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ እንግሊዝ ኖርዌይን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለግማሽ ፍፃሜው ደርሳለች።
ከሌሊቱ 6 ሰዓት የተጀመረው የሁለቱ ብሔራዊ ቡድን ጨዋታ በደበኛው ሰዓት (በ90 ደቂቃ) 1 ለ 1 በሆነ ውጤት ነው የተጠናቀቀው።
አንድሪያስ ሼልድረፕ ኖርዌይን ቀዳሚ ያደረገችውን ግብ በ36ኛው ደቂቃ ሲያስቆጥር ጁድ ቤሊንግሃም እንግሊዝን 45+2 ደቂቃ ላይ አቻ አድርጓል።
መደበኛ ሰዓቱ በአቻ ውጤት መጠናቀቁን ተከትሎ ወደ ተጨማሪ 30 ደቂቃ ያመሩ ሲሆን ጁድ ቤሊንግሃም እንግሊዝን አሸናፊ ያደረገችውን ግብ 93ኛ ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።
በዓለም ዋንጫው ለሀገሩ የመጀመሪያ ተሳትፎ እያደረገ ያለው ጁድ ቤሊንግሃም እስካሁን ባደረጋቸው ስድስት ጨዋታዎች ስድስት ግቦችን ሲያስቆጥር አንድ ለግብ የሚሆን ኳስ አመቻችቶ ማቀበል ችሏል።
#ebc #ebcsport #worldcup #worldcup2026 #england
*******************
በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ እንግሊዝ ኖርዌይን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለግማሽ ፍፃሜው ደርሳለች።
ከሌሊቱ 6 ሰዓት የተጀመረው የሁለቱ ብሔራዊ ቡድን ጨዋታ በደበኛው ሰዓት (በ90 ደቂቃ) 1 ለ 1 በሆነ ውጤት ነው የተጠናቀቀው።
አንድሪያስ ሼልድረፕ ኖርዌይን ቀዳሚ ያደረገችውን ግብ በ36ኛው ደቂቃ ሲያስቆጥር ጁድ ቤሊንግሃም እንግሊዝን 45+2 ደቂቃ ላይ አቻ አድርጓል።
መደበኛ ሰዓቱ በአቻ ውጤት መጠናቀቁን ተከትሎ ወደ ተጨማሪ 30 ደቂቃ ያመሩ ሲሆን ጁድ ቤሊንግሃም እንግሊዝን አሸናፊ ያደረገችውን ግብ 93ኛ ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።
በዓለም ዋንጫው ለሀገሩ የመጀመሪያ ተሳትፎ እያደረገ ያለው ጁድ ቤሊንግሃም እስካሁን ባደረጋቸው ስድስት ጨዋታዎች ስድስት ግቦችን ሲያስቆጥር አንድ ለግብ የሚሆን ኳስ አመቻችቶ ማቀበል ችሏል።
#ebc #ebcsport #worldcup #worldcup2026 #england
28 days ago
ስዊዘርላንድ ስምንተኛዋ ሩብ ፍፃሜውን የተቀላቀለች ሀገር ሆናለች
************************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ16ቱ ሀገራት ጥሎ ማለፍ የመጨረሻው ጨዋታ ስዊዘርላንድ ኮሎምቢያን አሸንፋለች።
መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ እና ጭማሪው 30 ደቂቃ ያለግብ ተጠናቀው፤ አሸናፊውን ለመለየት በተሰጡ መለያ ምቶች ስዊዘርላንድ 4 ለ 3 ረታለች።
ስዊዘርላንድ በሩብ ፍፃሜው አርጀንቲናን የምትገጥም ይሆናል።
ፈረንሳይ ከ ሞሮኮ፣ ስፔን ከ ቤልጂየም እንዲሁም ኖርዌይ ከ እንግሊዝ ሌሎቹ የሩብ ፍፃሜ መርኃ ግብሮች ናቸው።
#worldcup #fifaworldcup #switzerland #colombia #quarterfinal #football #sports
************************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ16ቱ ሀገራት ጥሎ ማለፍ የመጨረሻው ጨዋታ ስዊዘርላንድ ኮሎምቢያን አሸንፋለች።
መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ እና ጭማሪው 30 ደቂቃ ያለግብ ተጠናቀው፤ አሸናፊውን ለመለየት በተሰጡ መለያ ምቶች ስዊዘርላንድ 4 ለ 3 ረታለች።
ስዊዘርላንድ በሩብ ፍፃሜው አርጀንቲናን የምትገጥም ይሆናል።
ፈረንሳይ ከ ሞሮኮ፣ ስፔን ከ ቤልጂየም እንዲሁም ኖርዌይ ከ እንግሊዝ ሌሎቹ የሩብ ፍፃሜ መርኃ ግብሮች ናቸው።
#worldcup #fifaworldcup #switzerland #colombia #quarterfinal #football #sports
Sponsored by
Surafel
29 days ago
አሜሪካ በቤልጂየም ተሸንፋ ከዓለም ዋንጫው ተሰናበተች
********************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ ከውድድሩ አዘጋጅ ሀገራት አንዷ የሆነችው አሜሪካ፤ በቤልጂየም 4 ለ 1 ተሸንፋ ከዓለም ዋንጫው ውጪ ሆናለች።
ቻርለስ ኬቴለር(ሁለት) እንዲሁም ሀንስ ቫናከን እና ሮሜሉ ሉካኩ የቤልጂየምን ማሸነፊያ ግቦች ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው።
የአሜሪካን ብቸኛ ግብ ማሊክ ቲልማን ከመረብ አሳርፏል።
ቤልጂየም በሩብ ፍፃሜው የስፔን ብሔራዊ ቡድንን የምትገጥም ይሆናል።
#worldcup #fifaworldcup #usa #belgium #knockoutstage #football #sports
********************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ ከውድድሩ አዘጋጅ ሀገራት አንዷ የሆነችው አሜሪካ፤ በቤልጂየም 4 ለ 1 ተሸንፋ ከዓለም ዋንጫው ውጪ ሆናለች።
ቻርለስ ኬቴለር(ሁለት) እንዲሁም ሀንስ ቫናከን እና ሮሜሉ ሉካኩ የቤልጂየምን ማሸነፊያ ግቦች ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው።
የአሜሪካን ብቸኛ ግብ ማሊክ ቲልማን ከመረብ አሳርፏል።
ቤልጂየም በሩብ ፍፃሜው የስፔን ብሔራዊ ቡድንን የምትገጥም ይሆናል።
#worldcup #fifaworldcup #usa #belgium #knockoutstage #football #sports
29 days ago
ስፔን 0 - 0 ፖርቹጋል፦ የመጀመሪያ አጋማሽ ውጤት
****************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ16ቱ ሀገራት ጥሎ ማለፍ ስፔን ከፖርቹጋል እያደረጉት ያለው ጨዋታ፤ የመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ግብ ተጠናቋል።
#worldcup #fifaworldcup #portugal #spain #knockoutstage #football #sports
****************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ16ቱ ሀገራት ጥሎ ማለፍ ስፔን ከፖርቹጋል እያደረጉት ያለው ጨዋታ፤ የመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ግብ ተጠናቋል።
#worldcup #fifaworldcup #portugal #spain #knockoutstage #football #sports
30 days ago
ብራዚል ከ23ኛው ዓለም ዋንጫ ተሰናበተች
**************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ16ቱ ሀገራት ጥሎ ማለፍ መርኃ ግብር ብራዚል በኖርዌይ 2 ለ 1 ተሸንፋ ከዓለም ዋንጫው ተሰናብታለች። ኖርዌይም በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሩብ ፍፃሜ አልፋለች።
የኖርዌይን የማሸነፊያ ግቦች 79ኛው እና 90ኛው ደቂቃ ላይ ኧርሊንግ ሀላንድ ከመረብ አሳርፏል። ለብራዚል ኔይማር ጁኒየር በፍፁም ቅጣት ምት 90+10 ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።
በጨዋታው በብራዚል በኩል ብሩኖ ጉማሬሽ 14ኛው ደቂቃ ላይ ያገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
ኖርዌይ በሩብ ፍፃሜው የሜክሲኮ እና እንግሊዝን አሸናፊ የምትገጥም ይሆናል።
በእድሪስ አሕመድ
#worldcup #fifaworldcup #brazil #norway #knockoutstage #football #sports
**************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ16ቱ ሀገራት ጥሎ ማለፍ መርኃ ግብር ብራዚል በኖርዌይ 2 ለ 1 ተሸንፋ ከዓለም ዋንጫው ተሰናብታለች። ኖርዌይም በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሩብ ፍፃሜ አልፋለች።
የኖርዌይን የማሸነፊያ ግቦች 79ኛው እና 90ኛው ደቂቃ ላይ ኧርሊንግ ሀላንድ ከመረብ አሳርፏል። ለብራዚል ኔይማር ጁኒየር በፍፁም ቅጣት ምት 90+10 ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።
በጨዋታው በብራዚል በኩል ብሩኖ ጉማሬሽ 14ኛው ደቂቃ ላይ ያገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
ኖርዌይ በሩብ ፍፃሜው የሜክሲኮ እና እንግሊዝን አሸናፊ የምትገጥም ይሆናል።
በእድሪስ አሕመድ
#worldcup #fifaworldcup #brazil #norway #knockoutstage #football #sports
30 days ago
ብራዚል 0 - 0 ኖርዌይ :- የመጀመሪያ አጋማሽ ውጤት
***************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ በብራዚል እና በኖርዌይ መካከል እየተደረገ ያለው ጨዋታ የመጀመሪያው 45 ደቂቃ ያለ ምንም ግብ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።
በጨዋታው በብራዚል በኩል ብሩኖ ጉማሬሽ 14ኛው ደቂቃ ላይ ያገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
#worldcup #fifaworldcup #brazil #norway #knockoutstage #football #sports
***************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ በብራዚል እና በኖርዌይ መካከል እየተደረገ ያለው ጨዋታ የመጀመሪያው 45 ደቂቃ ያለ ምንም ግብ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።
በጨዋታው በብራዚል በኩል ብሩኖ ጉማሬሽ 14ኛው ደቂቃ ላይ ያገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
#worldcup #fifaworldcup #brazil #norway #knockoutstage #football #sports
1 month ago
1 month ago
ኮሎምቢያ ጋናን በማሸነፍ ወደ 16ቱ ጥሎ ማለፍ ተሸጋገረች
**************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ32ቱ ሀገራት ጥሎ ማለፍ ኮሎምቢያ ከ ጋና ያደረጉት ጨዋታ፤ በኮሎምቢያ 1 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
ለኮሎምቢያ የማሸነፊያዋን ብቸኛ ግብ ጆን አሪያስ በ14ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።
ወደ 16ቱ ጥሎ ማለፍ የተሸጋገረችው ኮሎምቢያ በቀጣይ ጨዋታዋ ከስዊዘርላንድ ጋር ትጫወታለች።
#worldcup #fifaworldcup #colombia #ghana #football #sports #ebc
**************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ32ቱ ሀገራት ጥሎ ማለፍ ኮሎምቢያ ከ ጋና ያደረጉት ጨዋታ፤ በኮሎምቢያ 1 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
ለኮሎምቢያ የማሸነፊያዋን ብቸኛ ግብ ጆን አሪያስ በ14ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።
ወደ 16ቱ ጥሎ ማለፍ የተሸጋገረችው ኮሎምቢያ በቀጣይ ጨዋታዋ ከስዊዘርላንድ ጋር ትጫወታለች።
#worldcup #fifaworldcup #colombia #ghana #football #sports #ebc
Sponsored by
Surafel
1 month ago
አርጀንቲና ኬፕቨርዴን በማሸነፍ ወደ 16ቱ ጥሎ ማለፍ ተሸጋገረች
*********
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ32 ሀገራት ጥሎ ማለፍ መርኃ ግብር አፍሪካዊቷን ደሴት ኬፕቨርዴን የገጠመችው አርጀንቲና 3 ለ 2 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ቀጣዩን የ16 ሀገራት ጥሎ ማለፍ ዙር ተቀላቅላለች።
ሊዮኔል ሜሲ ለአርጀንቲና ዳንኤል ዱዋርቴ ደግሞ ለኬፕቨርዴ 1 አቻ በተጠናቀቀው መደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ግቦቹን ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው።
አሸናፊውን ለመለየት በተጨመሩት 90 ደቂቃዎች፤ የአርጀንቲናን የማሸነፊያ ግቦች ያስቆጠሩት ሊሳንድሮ ማርቲኔዝ እና ዲኔይ ቦርገስ(በራሱ መረብ ላይ) ሲሆን የኬፕ ቨሮዴን ግብ ሲድኒ ካብራል ከመረብ አሳርፏል።
ሻምፒዮኗ አርጀንቲና በቀጣዩ የጥሎ ማለፍ መርኃ ግብር ግብፅን የምትገጥም ይሆናል።
#worldcup #fifaworldcup #argentina #caboverde #lionelmessi #football #sports
*********
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ32 ሀገራት ጥሎ ማለፍ መርኃ ግብር አፍሪካዊቷን ደሴት ኬፕቨርዴን የገጠመችው አርጀንቲና 3 ለ 2 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ቀጣዩን የ16 ሀገራት ጥሎ ማለፍ ዙር ተቀላቅላለች።
ሊዮኔል ሜሲ ለአርጀንቲና ዳንኤል ዱዋርቴ ደግሞ ለኬፕቨርዴ 1 አቻ በተጠናቀቀው መደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ግቦቹን ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው።
አሸናፊውን ለመለየት በተጨመሩት 90 ደቂቃዎች፤ የአርጀንቲናን የማሸነፊያ ግቦች ያስቆጠሩት ሊሳንድሮ ማርቲኔዝ እና ዲኔይ ቦርገስ(በራሱ መረብ ላይ) ሲሆን የኬፕ ቨሮዴን ግብ ሲድኒ ካብራል ከመረብ አሳርፏል።
ሻምፒዮኗ አርጀንቲና በቀጣዩ የጥሎ ማለፍ መርኃ ግብር ግብፅን የምትገጥም ይሆናል።
#worldcup #fifaworldcup #argentina #caboverde #lionelmessi #football #sports
1 month ago
ግብፅ አውስትራሊያን በማሸነፍ 16ቱን ተቀላቀለች
**********************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ ግብፅ አውስትራሊያን በመርታት የ16ቱ ጥሎ ማለፍ ጉዞዋን አሳክታለች።
በጨዋታው ኢማም አሹር በ13ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ግብፅን መሪ ብታደርግም፣ በ55ኛው ደቂቃ ሞሀመድ ሀኒ በራሱ መረብ ላይ ባስቆጠራት ግብ አውስትራሊያ አቻ ሆና ነበር።
የጨዋታው መደበኛ ክፍለ ጊዜና ጭማሪው 30 ደቂቃ 1 ለ 1 ተጠናቆ ግብፅ በመለያ ምት 4 ለ 2 አሸንፋለች።
ወደ 16ቱ ጥሎ ማለፍ የተሸጋገረችው ግብፅ በቀጣይ ጨዋታዋ ከአርጀንቲና እና ኬፕ ቨርዴ አሸናፊ ጋር ትጫወታለች።
#worldcup #fifaworldcup #switzerland #algeria #embolo #football #sports #ebc
**********************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ ግብፅ አውስትራሊያን በመርታት የ16ቱ ጥሎ ማለፍ ጉዞዋን አሳክታለች።
በጨዋታው ኢማም አሹር በ13ኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ግብ ግብፅን መሪ ብታደርግም፣ በ55ኛው ደቂቃ ሞሀመድ ሀኒ በራሱ መረብ ላይ ባስቆጠራት ግብ አውስትራሊያ አቻ ሆና ነበር።
የጨዋታው መደበኛ ክፍለ ጊዜና ጭማሪው 30 ደቂቃ 1 ለ 1 ተጠናቆ ግብፅ በመለያ ምት 4 ለ 2 አሸንፋለች።
ወደ 16ቱ ጥሎ ማለፍ የተሸጋገረችው ግብፅ በቀጣይ ጨዋታዋ ከአርጀንቲና እና ኬፕ ቨርዴ አሸናፊ ጋር ትጫወታለች።
#worldcup #fifaworldcup #switzerland #algeria #embolo #football #sports #ebc
1 month ago
አውስትራሊያ 1 - 1 ግብፅ :- የመደበኛ ሰዓት ውጤት
*************************
በአውስትራሊያ እና በግብፅ መካከል የተደረገው የጥሎ ማለፍ ጨዋታ መደበኛው የ90 ደቂቃ ክፍለ ጊዜ በ 1 ለ 1 አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።
በመጀመሪያው አጋማሽ በ13ኛው ደቂቃ ላይ በኢማም አሹር ግብ መሪ የነበረችው ግብፅ፣ በ55ኛው ደቂቃ ላይ ሞሀመድ ሀኒ በራሱ መረብ ላይ ባስቆጠራት ግብ አውስትራሊያ አቻ መሆን ችላለች።
በጨዋታው በመደበኛው ሰዓት አሸናፊ ባለመገኘቱ፣ ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አምርቷል።
#worldcup #australia #egypt #football #ebc #fifa2026
*************************
በአውስትራሊያ እና በግብፅ መካከል የተደረገው የጥሎ ማለፍ ጨዋታ መደበኛው የ90 ደቂቃ ክፍለ ጊዜ በ 1 ለ 1 አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።
በመጀመሪያው አጋማሽ በ13ኛው ደቂቃ ላይ በኢማም አሹር ግብ መሪ የነበረችው ግብፅ፣ በ55ኛው ደቂቃ ላይ ሞሀመድ ሀኒ በራሱ መረብ ላይ ባስቆጠራት ግብ አውስትራሊያ አቻ መሆን ችላለች።
በጨዋታው በመደበኛው ሰዓት አሸናፊ ባለመገኘቱ፣ ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አምርቷል።
#worldcup #australia #egypt #football #ebc #fifa2026
1 month ago
ፖርቹጋል ወደ 16ቱ ጥሎ ማለፍ ተሸጋገረች
*************************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ32ቱ ሀገራት ጥሎ ማለፍ ፖርቹጋል ከ ክሮሺያ ያደረጉት ጨዋታ፣ በፖርቹጋል 2 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቋል።
ለፖርቹጋል የማሸነፊያዎቹን ግቦች ክሪስቲያኖ ሮናልዶ (በፍፁም ቅጣት ምት) እንዲሁም ጎንካሎ ራሞስ አስቆጥረዋል።
ክሪስቲያኖ ሮናልዶ በ6 የዓለም ዋንጫ ተሳትፎው 11ኛ ግቡን ነው ያስቆጠረው።
ለክሮሺያ ብቸኛዋን ግብ ኢቫን ፔሪሲች ከመረብ አሳርፏል።
ወደ 16ቱ ጥሎ ማለፍ የተሸጋገረችው ፖርቹጋል በቀጣይ ጨዋታዋ ከስፔን ጋር ትጫወታለች።
#worldcup #fifaworldcup #portugal #croatia #cr7 #football #sports
*************************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ32ቱ ሀገራት ጥሎ ማለፍ ፖርቹጋል ከ ክሮሺያ ያደረጉት ጨዋታ፣ በፖርቹጋል 2 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቋል።
ለፖርቹጋል የማሸነፊያዎቹን ግቦች ክሪስቲያኖ ሮናልዶ (በፍፁም ቅጣት ምት) እንዲሁም ጎንካሎ ራሞስ አስቆጥረዋል።
ክሪስቲያኖ ሮናልዶ በ6 የዓለም ዋንጫ ተሳትፎው 11ኛ ግቡን ነው ያስቆጠረው።
ለክሮሺያ ብቸኛዋን ግብ ኢቫን ፔሪሲች ከመረብ አሳርፏል።
ወደ 16ቱ ጥሎ ማለፍ የተሸጋገረችው ፖርቹጋል በቀጣይ ጨዋታዋ ከስፔን ጋር ትጫወታለች።
#worldcup #fifaworldcup #portugal #croatia #cr7 #football #sports
1 month ago
ስፔን ኦስትሪያን 3 ለ 0 በማሸነፍ 16ቱን ተቀላቀለች
*******************
በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ስፔን ኦስትሪያን 3 ለ 0 በመርታት ወደ 16ቱ ጥሎ ማለፍ ተሸጋግራለች።
ስፔንን ለድል ያበቋትን ሦስት ግቦች ሚኬል ኦያርዛባል በ36ኛው እና በ89ኛው ደቂቃ ላይ ሲያስቆጥር፤ ቀሪዋን አንድ ግብ ፔድሮ ፖሮ በ66ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።
ስፔን በቀጣይ ዙር ጨዋታዋ ከፖርቹጋል እና ክሮሺያ አሸናፊ ጋር የምትገናኝ ይሆናል።
#worldcup #spain #austria #sports #ebc #fifa2026
*******************
በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ስፔን ኦስትሪያን 3 ለ 0 በመርታት ወደ 16ቱ ጥሎ ማለፍ ተሸጋግራለች።
ስፔንን ለድል ያበቋትን ሦስት ግቦች ሚኬል ኦያርዛባል በ36ኛው እና በ89ኛው ደቂቃ ላይ ሲያስቆጥር፤ ቀሪዋን አንድ ግብ ፔድሮ ፖሮ በ66ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።
ስፔን በቀጣይ ዙር ጨዋታዋ ከፖርቹጋል እና ክሮሺያ አሸናፊ ጋር የምትገናኝ ይሆናል።
#worldcup #spain #austria #sports #ebc #fifa2026
Sponsored by
Surafel
1 month ago
እንግሊዝ ዲሞክራቲክ ኮንጎን 2 ለ 1 በማሸነፍ 16ቱን ተቀላቀለች
**************************
በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ እንግሊዝ ዲሞክራቲክ ኮንጎን 2 ለ 1 በመርታት ወደ 16ቱ ጥሎ ማለፍ ተሸጋግራለች።
እንግሊዝን ለድል ያበቋትን ሁለት ግቦች ሃሪ ኬን በ75ኛው እና በ86ኛው ደቂቃ ላይ ሲያስቆጥር፤ ለዲሞክራቲክ ኮንጎ ብሪያን ሲፔንጋ በ7ኛው ደቂቃ ላይ ብቸኛ ግብ አስቆጥሯል።
እንግሊዝ በቀጣይ ዙር ጨዋታዋ ከሜክሲኮ ጋር የምትገናኝ ይሆናል።
#worldcup #england #drcongo #sports #ebc #fifa2026
**************************
በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ እንግሊዝ ዲሞክራቲክ ኮንጎን 2 ለ 1 በመርታት ወደ 16ቱ ጥሎ ማለፍ ተሸጋግራለች።
እንግሊዝን ለድል ያበቋትን ሁለት ግቦች ሃሪ ኬን በ75ኛው እና በ86ኛው ደቂቃ ላይ ሲያስቆጥር፤ ለዲሞክራቲክ ኮንጎ ብሪያን ሲፔንጋ በ7ኛው ደቂቃ ላይ ብቸኛ ግብ አስቆጥሯል።
እንግሊዝ በቀጣይ ዙር ጨዋታዋ ከሜክሲኮ ጋር የምትገናኝ ይሆናል።
#worldcup #england #drcongo #sports #ebc #fifa2026
1 month ago
ብራዚል ያነባች ዕለት - የጀርመኑ ዓለም ዋንጫ ትዝታዎች
****************
ያኔ ብራዚል እንዲህ ትሆናለች፣ በመሰል ደረጃ ላይ ትገኛለች ብለው ብዙዎች አልጠበቁም። ሁለት አስርት ዓመታት አልፈው ወደ ኋላ መለስ ብለው ሲያስታውሱት የሆነው ግን እንደዚያ ነው። የ2006 ዓለም ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ የቀደመውን አሸናፊ ፈረንሳይ እና የወቅቱን ሻምፒዮን ብራዚልን አገናኝቷል።
የ21ኛው ክፍለ ዘመን የብራዚል ወርቃማ ትውልድ፣ ኳስ የጥበብ አውድማ መሆኑን ዳግም ያስመሰከሩት ጥበበኞች ስብስብ ጀርመን ምድር ለዓለም ዋንጫው ሲዘልቁ ለ6ኛ የመድረኩ አሸናፊነት፣ ለተከታታይ ሻፒዮንነት ነው የታጩት።
ሮናልዶ ሉዊስ ናዛሪዮ ዴሊማ፣ ሮናልዲንሆ ጎቾ፣ ካካ፣ ካፉ፣ ሮቤርቶ ካርሎስ፣ አድሪያኖ እና ዚ ሮቤርቶን የመሰሉ ክዋክብት እንደ ምን ይዘነጋሉ? የሰው አዕምሮ ሊዘነጋቸው ቢፈቅድ እንኳ የእግር ኳስ ታሪክ ሊረሳቸው አይቻለውም። ትዝታቸው ርቆ ያልራቀ፣ ደብዝዞ ያልጠፋ፣ ቀጥኖ ያልተበጠሰ ህልው ነው። ከመዘንጋት የራቀ ታሪክ!
የዚያች ዕለት ግን ቀን ከነርሱ በተቃራኒ የቆመች መሰለች። የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን በተለይም ዚነዲን ዚዳን በዚያች ቀን ስል፣ አስፈሪ እና ባለ ግርማ ሞገስ ሆነው ነው የቀረቡት።
ዚዳን ፀጉሩ እንደከዳው፣ የጎልማሳነት ደጃፉ ላይ እንደቆመ፣ ከእግር ኳስ የመሰናበቻ ቀናቱ እንደደረሰ ሳይሆን የ20ዎቹ አጋማሽ ላይ እንደሚገኝ ወጣት ነበር ይቦርቅ የነበረው።
በዚያ ጨዋታ ዚዳን የነበረው እንቅስቃሴ በዓለም ዋንጫ ታሪክ በግለሰብ ደረጃ ከተደረጉ እንቅስቃሴዎች ምርጡ እንደሆነ የብዙዎች እምነት ነው። የዘመን ተጋሪው ሮናልዶ ሉዊስ ናዛሪዮ ዴሊማም ያን ጨዋታ አስመልክቶ በሰጠው ቃለ-መጠይቅ “በዚያ ጨዋታ ዚዳን ያደረገው እንቅስቃሴ ያለማወላዳት በዓለም ዋንጫው ታሪክ ከታዩ ምርጥ ብቃቶች እንደ አንዱ ሊመደብ የተገባ ነው” ነበር ያለው።
ፈረንሳይ በቴሪ ሄንሪ አማካኝነት ባስቆጠረችው ግብ ጨዋታውን 1 ለ 0 አሸንፋ የወቅቱን የዓለም ሻምፒዮን ከውድድሩ አሰናበተቻት። ያኔ ብዙ አለማመኖች ነበሩ፣ የሆነው ከብዙዎቹ ጥበቃ በተቃራኒ ነው።
የ1998 ዓለም ዋንጫ አሸናፊ፣ የነ ዚነዲን ዚዳን ሀገር የወቅቱን የዓለም ሻምፒዮን ከዓለም ዋንጫ አስወጣቻት የሚለው በመጨረሻ የዳኛውን ፊሽካ ተከትሎ የተሰማው ዜና ነበር።
ያ ታሪክ በፍራንክፈርቱ ባልድ ስታዲየም የመጫወቻ ሜዳ ብቻ ተፈፅሞ ያበቃ አልሆነም። ወደ ካናሪንሀ መልበሻ ክፍልም ተከትሎ አምርቷል። በዕለቱ ልዩ የነበረው፣ ለቴሪ ሄንሪም ለግብ የምትሆነውን ኳስ አመቻችቶ ያቀበለው ዚነዲን ዚዳን ወደዚያች መልበሻ ክፍል አመራ።
አንድም ሊያፅናና አንድም በትልልቅ የእግር ኳስ መድረኮች እንደተለመደው መለያ ሊቀያየር።
‛ኤል ፌኖሜኖ’ ይህን የዚዳን ተግባር በበጎ አልተመከተውም። ሮናልዶ ከ20 ዓመታት በኋላ ሁነቱን አስመልክቶ ሲናገር “ሁላችንም ዛሬ ድረስ አብረን የቀጠልን ጓደኛሞች ነን፣ እርሱ ወደ መልበሻ ክፍል ሲገባ ግን የነበረው ድባብ አስፈሪ ነበር።
ብዙ ተጫዋቾች እያነቡ ነበር፤ እናም መለያ ለመቀያየር ወደ መልበሻ ክፍሉ የመጣበት ሰዓት ትክክለኛ እንዳልሆነና እንዲመለስ አስረግጬ ነገርኩት” ይላል።
እንደ ሮናልዶ እምነት ያች ዕለት የዓለም ዋንጫን ታሪክ ራሱን ቀይራለች። በእርግጥም በብራዚል በኩል ሆኖ ለተመለከተው ብዙ እውነት የሚመስሉ ነገሮችን የያዘ ሃሳብ ነው።
ለዓለም እግር ኳስ የስኬታማነት ናሙና የሆኑ ክዋክብትን ያበረከተችው ብራዚል ከትልቁ መድረክ አሸናፊነት እንደተናጠበች ሩብ ምዕተ ዓመታት እየተቆጠሩ ነው። እነዛን ኮከቦች ግን እግር ኳስ ሊዘነጋቸው አይቻለውም።
በእርግጥ ፈረንሳይ አስከ ፍፃሜ ብትጓዝም፣ በዚነዲን ዚዳን እና ማርኮ ማታራዚ ድራማ በታጀበው ጨዋታ፣ በነ ማርሴሎ ሊፒ እና አንድሪያ ፒርሎ ጣሊያን ተረታ ለሌላ ዓለም ዋንጫ አሸናፊነት 12 ዓመታት ለመጠበቅ ተገዳለች።
ዚዳንን የ2006ቱ ዓለም ዋንጫ ‛አንተ በእግር ኳስ ስንብትህ ደጃፍ ላይ ቆመህ በእኔ ያበራህ ኮከብ ነህ’ ብሎታል።
ዓለም ዋንጫ ትዝታ ነው። ድልና ሽንፈት፣ ደስታ እና ሀዘን፣ ሳቅ እና ለቅሶ የሚመላለስበት የስፖርት አውድማ፤ የትውስታ መቼት ነው። መንገዱ ይቀጥላል!
በእድሪስ አህመድ
#worldcup #brazil #sports #japan #ebc Ethiopian Broadcasting Corporation EBC-መዝናኛ EBC SPORT ኢቢሲ ስፖርት
****************
ያኔ ብራዚል እንዲህ ትሆናለች፣ በመሰል ደረጃ ላይ ትገኛለች ብለው ብዙዎች አልጠበቁም። ሁለት አስርት ዓመታት አልፈው ወደ ኋላ መለስ ብለው ሲያስታውሱት የሆነው ግን እንደዚያ ነው። የ2006 ዓለም ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ የቀደመውን አሸናፊ ፈረንሳይ እና የወቅቱን ሻምፒዮን ብራዚልን አገናኝቷል።
የ21ኛው ክፍለ ዘመን የብራዚል ወርቃማ ትውልድ፣ ኳስ የጥበብ አውድማ መሆኑን ዳግም ያስመሰከሩት ጥበበኞች ስብስብ ጀርመን ምድር ለዓለም ዋንጫው ሲዘልቁ ለ6ኛ የመድረኩ አሸናፊነት፣ ለተከታታይ ሻፒዮንነት ነው የታጩት።
ሮናልዶ ሉዊስ ናዛሪዮ ዴሊማ፣ ሮናልዲንሆ ጎቾ፣ ካካ፣ ካፉ፣ ሮቤርቶ ካርሎስ፣ አድሪያኖ እና ዚ ሮቤርቶን የመሰሉ ክዋክብት እንደ ምን ይዘነጋሉ? የሰው አዕምሮ ሊዘነጋቸው ቢፈቅድ እንኳ የእግር ኳስ ታሪክ ሊረሳቸው አይቻለውም። ትዝታቸው ርቆ ያልራቀ፣ ደብዝዞ ያልጠፋ፣ ቀጥኖ ያልተበጠሰ ህልው ነው። ከመዘንጋት የራቀ ታሪክ!
የዚያች ዕለት ግን ቀን ከነርሱ በተቃራኒ የቆመች መሰለች። የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን በተለይም ዚነዲን ዚዳን በዚያች ቀን ስል፣ አስፈሪ እና ባለ ግርማ ሞገስ ሆነው ነው የቀረቡት።
ዚዳን ፀጉሩ እንደከዳው፣ የጎልማሳነት ደጃፉ ላይ እንደቆመ፣ ከእግር ኳስ የመሰናበቻ ቀናቱ እንደደረሰ ሳይሆን የ20ዎቹ አጋማሽ ላይ እንደሚገኝ ወጣት ነበር ይቦርቅ የነበረው።
በዚያ ጨዋታ ዚዳን የነበረው እንቅስቃሴ በዓለም ዋንጫ ታሪክ በግለሰብ ደረጃ ከተደረጉ እንቅስቃሴዎች ምርጡ እንደሆነ የብዙዎች እምነት ነው። የዘመን ተጋሪው ሮናልዶ ሉዊስ ናዛሪዮ ዴሊማም ያን ጨዋታ አስመልክቶ በሰጠው ቃለ-መጠይቅ “በዚያ ጨዋታ ዚዳን ያደረገው እንቅስቃሴ ያለማወላዳት በዓለም ዋንጫው ታሪክ ከታዩ ምርጥ ብቃቶች እንደ አንዱ ሊመደብ የተገባ ነው” ነበር ያለው።
ፈረንሳይ በቴሪ ሄንሪ አማካኝነት ባስቆጠረችው ግብ ጨዋታውን 1 ለ 0 አሸንፋ የወቅቱን የዓለም ሻምፒዮን ከውድድሩ አሰናበተቻት። ያኔ ብዙ አለማመኖች ነበሩ፣ የሆነው ከብዙዎቹ ጥበቃ በተቃራኒ ነው።
የ1998 ዓለም ዋንጫ አሸናፊ፣ የነ ዚነዲን ዚዳን ሀገር የወቅቱን የዓለም ሻምፒዮን ከዓለም ዋንጫ አስወጣቻት የሚለው በመጨረሻ የዳኛውን ፊሽካ ተከትሎ የተሰማው ዜና ነበር።
ያ ታሪክ በፍራንክፈርቱ ባልድ ስታዲየም የመጫወቻ ሜዳ ብቻ ተፈፅሞ ያበቃ አልሆነም። ወደ ካናሪንሀ መልበሻ ክፍልም ተከትሎ አምርቷል። በዕለቱ ልዩ የነበረው፣ ለቴሪ ሄንሪም ለግብ የምትሆነውን ኳስ አመቻችቶ ያቀበለው ዚነዲን ዚዳን ወደዚያች መልበሻ ክፍል አመራ።
አንድም ሊያፅናና አንድም በትልልቅ የእግር ኳስ መድረኮች እንደተለመደው መለያ ሊቀያየር።
‛ኤል ፌኖሜኖ’ ይህን የዚዳን ተግባር በበጎ አልተመከተውም። ሮናልዶ ከ20 ዓመታት በኋላ ሁነቱን አስመልክቶ ሲናገር “ሁላችንም ዛሬ ድረስ አብረን የቀጠልን ጓደኛሞች ነን፣ እርሱ ወደ መልበሻ ክፍል ሲገባ ግን የነበረው ድባብ አስፈሪ ነበር።
ብዙ ተጫዋቾች እያነቡ ነበር፤ እናም መለያ ለመቀያየር ወደ መልበሻ ክፍሉ የመጣበት ሰዓት ትክክለኛ እንዳልሆነና እንዲመለስ አስረግጬ ነገርኩት” ይላል።
እንደ ሮናልዶ እምነት ያች ዕለት የዓለም ዋንጫን ታሪክ ራሱን ቀይራለች። በእርግጥም በብራዚል በኩል ሆኖ ለተመለከተው ብዙ እውነት የሚመስሉ ነገሮችን የያዘ ሃሳብ ነው።
ለዓለም እግር ኳስ የስኬታማነት ናሙና የሆኑ ክዋክብትን ያበረከተችው ብራዚል ከትልቁ መድረክ አሸናፊነት እንደተናጠበች ሩብ ምዕተ ዓመታት እየተቆጠሩ ነው። እነዛን ኮከቦች ግን እግር ኳስ ሊዘነጋቸው አይቻለውም።
በእርግጥ ፈረንሳይ አስከ ፍፃሜ ብትጓዝም፣ በዚነዲን ዚዳን እና ማርኮ ማታራዚ ድራማ በታጀበው ጨዋታ፣ በነ ማርሴሎ ሊፒ እና አንድሪያ ፒርሎ ጣሊያን ተረታ ለሌላ ዓለም ዋንጫ አሸናፊነት 12 ዓመታት ለመጠበቅ ተገዳለች።
ዚዳንን የ2006ቱ ዓለም ዋንጫ ‛አንተ በእግር ኳስ ስንብትህ ደጃፍ ላይ ቆመህ በእኔ ያበራህ ኮከብ ነህ’ ብሎታል።
ዓለም ዋንጫ ትዝታ ነው። ድልና ሽንፈት፣ ደስታ እና ሀዘን፣ ሳቅ እና ለቅሶ የሚመላለስበት የስፖርት አውድማ፤ የትውስታ መቼት ነው። መንገዱ ይቀጥላል!
በእድሪስ አህመድ
#worldcup #brazil #sports #japan #ebc Ethiopian Broadcasting Corporation EBC-መዝናኛ EBC SPORT ኢቢሲ ስፖርት
1 month ago
ካናዳ ደቡብ አፍሪካን አሸንፋ ወደ 16 ቡድኖች አለፈች
#ethiopia | በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ዙር ካናዳ ከደቡብ አፍሪካ ያደረገችውን ጠንካራ ጨዋታ 1 ለ0 በማሸነፍ ወደ 16 ቡድኖች ማለፏን አረጋግጣለች።
ጨዋታው በሁለቱም ቡድኖች ጠንካራ መከላከል ምክንያት እስከ 90ኛው ደቂቃ ድረስ ያለ ግብ 0-0 ቀጥሎ ነበር። ሆኖም በ90+2 ደቂቃ ላይ ስቴፈን ኢውስታኪዮ ያስቆጠረው ወሳኝ ግብ ለካናዳ ድልን አስገኝቷል።
በዚህ ውጤት ካናዳ ወደ ቀጣዩ ዙር በማለፍ በ16 ቡድኖች ውስጥ ቦታዋን ስታረጋግጥ፣ ደቡብ አፍሪካ ደግሞ ከውድድሩ ተሰናብታለች።
#worldcup #canada #southafrica #football #sports
#ethiopia | በ23ኛው የፊፋ ዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ዙር ካናዳ ከደቡብ አፍሪካ ያደረገችውን ጠንካራ ጨዋታ 1 ለ0 በማሸነፍ ወደ 16 ቡድኖች ማለፏን አረጋግጣለች።
ጨዋታው በሁለቱም ቡድኖች ጠንካራ መከላከል ምክንያት እስከ 90ኛው ደቂቃ ድረስ ያለ ግብ 0-0 ቀጥሎ ነበር። ሆኖም በ90+2 ደቂቃ ላይ ስቴፈን ኢውስታኪዮ ያስቆጠረው ወሳኝ ግብ ለካናዳ ድልን አስገኝቷል።
በዚህ ውጤት ካናዳ ወደ ቀጣዩ ዙር በማለፍ በ16 ቡድኖች ውስጥ ቦታዋን ስታረጋግጥ፣ ደቡብ አፍሪካ ደግሞ ከውድድሩ ተሰናብታለች።
#worldcup #canada #southafrica #football #sports
1 month ago
ካናዳ ደቡብ አፍሪካን 1 ለ 0 በማሸነፍ 16ቱን ተቀላቀለች
**********************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ በጥሎ ማለፍ ደቡብ አፍሪካ ከካናዳ ያደረጉት ጨዋታ በካናዳ 1 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
ጨዋታው እስከ መደበኛው 90 ደቂቃ ያለ ምንም ግብ 0 ለ 0 ቀጥሎ የነበረ ቢሆንም፣ ስቴፈን ኢውስታኪዮ በጭማሪ ደቂቃ 90+2 ላይ ባስቆጠራት ግብ ካናዳን አሸናፊ ማድረግ ችሏል።
ውጤቱን ተከትሎ ካናዳ ደቡብ አፍሪካን ከውድድሩ በማሰናበት 16ቱን መቀላቀሏን አረጋግጣለች።
#worldcup #fifaworldcup #canada #southafrica #football #sports #ebc
**********************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ በጥሎ ማለፍ ደቡብ አፍሪካ ከካናዳ ያደረጉት ጨዋታ በካናዳ 1 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
ጨዋታው እስከ መደበኛው 90 ደቂቃ ያለ ምንም ግብ 0 ለ 0 ቀጥሎ የነበረ ቢሆንም፣ ስቴፈን ኢውስታኪዮ በጭማሪ ደቂቃ 90+2 ላይ ባስቆጠራት ግብ ካናዳን አሸናፊ ማድረግ ችሏል።
ውጤቱን ተከትሎ ካናዳ ደቡብ አፍሪካን ከውድድሩ በማሰናበት 16ቱን መቀላቀሏን አረጋግጣለች።
#worldcup #fifaworldcup #canada #southafrica #football #sports #ebc
1 month ago
የምድብ ዘጠኝ የመጨረሻ ጨዋታዎች፤ ፈረንሳይ ከ ኖርዌይ እና ሴኔጋል ከ ኢራቅ
************************
በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የምድብ ዘጠኝ ተጠባቂ የመጨረሻ ጨዋታዎች በተመሳሳይ ዛሬ ምሽት 4:00 ሰዓት ላይ ሲደረጉ፣ የምድቡን መሪ ለመለየትና የምርጥ ሦስተኛ ደረጃ ዕድልን ለመጠቀም ብርቱ ፉክክር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
የዓለም ዋንጫን ሁለት ጊዜ ማንሳት የቻለችው ፈረንሳይ በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኖርዌይን ትገጥማለች፡፡
ፈረንሳይ ካደረገቻቸው ሁለት ጨዋታዎች ሁለቱንም በማሸነፍ፣ 6 ግቦችን አስቆጥራ 1 ብቻ በማስተናገድ በ6 ነጥብ የምድቡ መሪ ነች።
በአንጻሩ ኖርዌይ ካደረገቻቸው ሁለት ጨዋታዎች ሁለቱንም በማሸነፍ፣ 6 ነጥብ ይዛ በግብ ክፍያ በፈረንሳይ ተበልጣ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
ኖርዌይ በዓለም ዋንጫ ተሳትፎ ታሪኳ በ1998 እስከ ጥሎ ማለፍ ድረስ መጓዝ የቻለችበት ታሪክ ያላት ሲሆን፣ ዛሬ ከፈረንሳይ ጋር በምታደርገው ጨዋታ የምድቡን የበላይነት ለመያዝ ትጫወታለች።
ሁለቱም ብሔራዊ ቡድኖች ቀደም ብለው ባከናወኗቸው የምድብ ጨዋታዎች ላይ ባስመዘገቡት ድል ወደ ቀጣይ ዙር ማለፋቸውን ያረጋገጡ ሲሆን፣ የዛሬውን ጨዋታ ምድቡን በአንደኝነት ለማጠናቀቅ ይጫወታሉ፡፡
በሌላኛው መርኃ ግብር ሴኔጋል ከኢራቅ ጋር በምታደርገው ጨዋታ ምርጥ ሦስተኛ ሆና ወደ ጥሎ ማለፍ ለመግባት ያላት ዕድል ጠባብ ሲሆን፣ ምንም እንኳ በእርሷ ማሸነፍ ብቻ የሚወሰን ባይሆንም ብሎም በምታስመዘግባቸው ግቦች ብዛት ቢመረኮዝም፣ በዚያ ጠባብ ዕድል ለመጠቀም የሚደረግ ወሳኝ ፍልሚያ ነው።
ሴኔጋል ካደረገቻቸው ሁለት ጨዋታዎች በሁለቱም በመሸነፏ ካለምንም ነጥብ ሦስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
በ2002 የኮሪያ እና ጃፓን ዓለም ዋንጫ እስከ ሩብ ፍፃሜ ተጉዛ ታሪክ የጻፈችው ሴኔጋል፣ ዛሬ ኢራቅን በማሸነፍ ምርጥ ሦስተኛ ሆና ለማለፍ ያላትን ጠባብ ዕድል ለመጠቀም ትጫወታለች።
ኢራቅ በበኩሏ ካደረገቻቸው ሁለት ጨዋታዎች በሁለቱም በመሸነፏ፣ ከምድቡ የተሰናበተች ለመርኃ ግብር ማሟያ እና ለታሪክ ጨዋታዋን ታከናውናለች።
በአሁኑ ሰዓት ስዊድን እና ኢኳዶር በ4 ነጥብ ምርጥ ሦስተኛ ሆነው ለማለፍ ያለውን ዝርዝር እየመሩ ሲሆን፣ የዚህ ምድብ ውጤትም በምርጥ ሦስተኛነት በሚያልፉ ሀገራት ዝርዝር ላይ የራሱ ተጽዕኖ ይኖረዋል።
በዘረንቶስ ሰለሞን
Ethiopian Broadcasting Corporation EBC SPORT ኢቢሲ ስፖርት #worldcup #groupi #france #norway #senegal #iraq #football #sport
************************
በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የምድብ ዘጠኝ ተጠባቂ የመጨረሻ ጨዋታዎች በተመሳሳይ ዛሬ ምሽት 4:00 ሰዓት ላይ ሲደረጉ፣ የምድቡን መሪ ለመለየትና የምርጥ ሦስተኛ ደረጃ ዕድልን ለመጠቀም ብርቱ ፉክክር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
የዓለም ዋንጫን ሁለት ጊዜ ማንሳት የቻለችው ፈረንሳይ በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ኖርዌይን ትገጥማለች፡፡
ፈረንሳይ ካደረገቻቸው ሁለት ጨዋታዎች ሁለቱንም በማሸነፍ፣ 6 ግቦችን አስቆጥራ 1 ብቻ በማስተናገድ በ6 ነጥብ የምድቡ መሪ ነች።
በአንጻሩ ኖርዌይ ካደረገቻቸው ሁለት ጨዋታዎች ሁለቱንም በማሸነፍ፣ 6 ነጥብ ይዛ በግብ ክፍያ በፈረንሳይ ተበልጣ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
ኖርዌይ በዓለም ዋንጫ ተሳትፎ ታሪኳ በ1998 እስከ ጥሎ ማለፍ ድረስ መጓዝ የቻለችበት ታሪክ ያላት ሲሆን፣ ዛሬ ከፈረንሳይ ጋር በምታደርገው ጨዋታ የምድቡን የበላይነት ለመያዝ ትጫወታለች።
ሁለቱም ብሔራዊ ቡድኖች ቀደም ብለው ባከናወኗቸው የምድብ ጨዋታዎች ላይ ባስመዘገቡት ድል ወደ ቀጣይ ዙር ማለፋቸውን ያረጋገጡ ሲሆን፣ የዛሬውን ጨዋታ ምድቡን በአንደኝነት ለማጠናቀቅ ይጫወታሉ፡፡
በሌላኛው መርኃ ግብር ሴኔጋል ከኢራቅ ጋር በምታደርገው ጨዋታ ምርጥ ሦስተኛ ሆና ወደ ጥሎ ማለፍ ለመግባት ያላት ዕድል ጠባብ ሲሆን፣ ምንም እንኳ በእርሷ ማሸነፍ ብቻ የሚወሰን ባይሆንም ብሎም በምታስመዘግባቸው ግቦች ብዛት ቢመረኮዝም፣ በዚያ ጠባብ ዕድል ለመጠቀም የሚደረግ ወሳኝ ፍልሚያ ነው።
ሴኔጋል ካደረገቻቸው ሁለት ጨዋታዎች በሁለቱም በመሸነፏ ካለምንም ነጥብ ሦስተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
በ2002 የኮሪያ እና ጃፓን ዓለም ዋንጫ እስከ ሩብ ፍፃሜ ተጉዛ ታሪክ የጻፈችው ሴኔጋል፣ ዛሬ ኢራቅን በማሸነፍ ምርጥ ሦስተኛ ሆና ለማለፍ ያላትን ጠባብ ዕድል ለመጠቀም ትጫወታለች።
ኢራቅ በበኩሏ ካደረገቻቸው ሁለት ጨዋታዎች በሁለቱም በመሸነፏ፣ ከምድቡ የተሰናበተች ለመርኃ ግብር ማሟያ እና ለታሪክ ጨዋታዋን ታከናውናለች።
በአሁኑ ሰዓት ስዊድን እና ኢኳዶር በ4 ነጥብ ምርጥ ሦስተኛ ሆነው ለማለፍ ያለውን ዝርዝር እየመሩ ሲሆን፣ የዚህ ምድብ ውጤትም በምርጥ ሦስተኛነት በሚያልፉ ሀገራት ዝርዝር ላይ የራሱ ተጽዕኖ ይኖረዋል።
በዘረንቶስ ሰለሞን
Ethiopian Broadcasting Corporation EBC SPORT ኢቢሲ ስፖርት #worldcup #groupi #france #norway #senegal #iraq #football #sport
1 month ago
ኮት ዲቯር በዓለም ዋንጫ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ለጥሎ ማለፍ ጨዋታ ደረሰች
*********************
ዛሬ ምሽት በተደረገ የ23ኛ የዓለም ዋንጫ የምድብ E የመጨረሻ ጨዋታ ኮት ዲቯር ኩራሳዎን 2 ለ 0 በማሸነፍ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ለጥሎ ማለፍ ጨዋታ ደርሳለች።
የኮት ዲቯርን የማሸነፊያ ግቦች ኒኮላስ ፔፔ አስቆጥሯል።
በሌላ የምድቡ ጨዋታ ኢኳዶር ጀርመንን 2 ለ 1 በማሸነፍ በምርጥ 3ኛነት ወደ ጥሎ ማለፉ መሸጋገሯን አረጋግጣለች።
ኢኳዶር በምድቡ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በአይቮሪኮስት ተሸንፋ፣ ከኩራሳኦ ጋር አቻ ተለያይታ እና ጀርመንን አሸንፋ በ4 ነጥብ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፍ ችላለች።
በኢኳዶር የተሸነፈችው ጀርመን ቀደም ሲል ኩራሳዎን 7 ለ 1 እና አይቮሪ ኮስትን 2 ለ 1 አሸንፋ በሰበሰበችው ነጥብ እና ባስቆጠረችው የግብ ብዛት የምድቡ መሪ ሆና ወደ ቀጣዩ ዙር አልፋለች።
#ebc #worldcup #qualifiers #worldcup2026
*********************
ዛሬ ምሽት በተደረገ የ23ኛ የዓለም ዋንጫ የምድብ E የመጨረሻ ጨዋታ ኮት ዲቯር ኩራሳዎን 2 ለ 0 በማሸነፍ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ለጥሎ ማለፍ ጨዋታ ደርሳለች።
የኮት ዲቯርን የማሸነፊያ ግቦች ኒኮላስ ፔፔ አስቆጥሯል።
በሌላ የምድቡ ጨዋታ ኢኳዶር ጀርመንን 2 ለ 1 በማሸነፍ በምርጥ 3ኛነት ወደ ጥሎ ማለፉ መሸጋገሯን አረጋግጣለች።
ኢኳዶር በምድቡ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች በአይቮሪኮስት ተሸንፋ፣ ከኩራሳኦ ጋር አቻ ተለያይታ እና ጀርመንን አሸንፋ በ4 ነጥብ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፍ ችላለች።
በኢኳዶር የተሸነፈችው ጀርመን ቀደም ሲል ኩራሳዎን 7 ለ 1 እና አይቮሪ ኮስትን 2 ለ 1 አሸንፋ በሰበሰበችው ነጥብ እና ባስቆጠረችው የግብ ብዛት የምድቡ መሪ ሆና ወደ ቀጣዩ ዙር አልፋለች።
#ebc #worldcup #qualifiers #worldcup2026
Sponsored by
Surafel
Comments