16 days ago
ስፔን የ23ኛው ዓለም ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነች
********************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ ስፔን አርጀንቲናን 1 ለ 0 በማሸነፍ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ ሆናለች።
የጨዋታው መደበኛ ክፍለ ጊዜ ያለ ግብ በመጠናቀቁ አሸናፊውን ለመለየት 30 ደቂቃ ተጨምሯል።
በጭማሪው ክፍለ ጊዜ 106ኛው ደቂቃ ላይ ፌራን ቶሬስ ያስቆጠራት ግብ ስፔንን አሸናፊ አድርጋለች።
በዚህም ስፔን ከ16 ዓመታት በኋላ ውድድሩን አሸንፋ በታሪኳ ለሁለተኛ ጊዜ የዓለም ዋንጫ ባለቤት ሆናለች።
#worldcup #fifaworldcup #fifaworldcup2026 #argentina #spain #finalmatch #football #sports
********************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ ስፔን አርጀንቲናን 1 ለ 0 በማሸነፍ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ ሆናለች።
የጨዋታው መደበኛ ክፍለ ጊዜ ያለ ግብ በመጠናቀቁ አሸናፊውን ለመለየት 30 ደቂቃ ተጨምሯል።
በጭማሪው ክፍለ ጊዜ 106ኛው ደቂቃ ላይ ፌራን ቶሬስ ያስቆጠራት ግብ ስፔንን አሸናፊ አድርጋለች።
በዚህም ስፔን ከ16 ዓመታት በኋላ ውድድሩን አሸንፋ በታሪኳ ለሁለተኛ ጊዜ የዓለም ዋንጫ ባለቤት ሆናለች።
#worldcup #fifaworldcup #fifaworldcup2026 #argentina #spain #finalmatch #football #sports
16 days ago
ስፔን 1-0 አርጀንቲና
*********
እየተካሄደ ባለው የ23ኛው ዓለም ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ ስፔን 106ኛው ደቂቃ ላይ በፌራን ቶሬስ አማካኝነት ባስቆጠረችው ግብ 1 ለ 0 መምራት ጀምራለች።
#worldcup #fifaworldcup #fifaworldcup2026 #argentina #spain #finalmatch #football #sports
*********
እየተካሄደ ባለው የ23ኛው ዓለም ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ ስፔን 106ኛው ደቂቃ ላይ በፌራን ቶሬስ አማካኝነት ባስቆጠረችው ግብ 1 ለ 0 መምራት ጀምራለች።
#worldcup #fifaworldcup #fifaworldcup2026 #argentina #spain #finalmatch #football #sports
16 days ago
አርጀንቲና 0 - 0 ስፔን :- የመደበኛ ሰዓት ውጤት
*****************
በአርጀንቲና እና በስፔን መካከል እየተደረገ የሚገኘው የዓለም ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ መደበኛው የ90 ደቂቃ ክፍለ ጊዜ ያለምንም ግብ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።
በጨዋታው መደበኛ ክፍለ ጊዜ አሸናፊ ባለመገኘቱ፣ አሸናፊውን ለመለየት ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አምርቷል።
ኤንዞ ፈርናንዴዝ ፓብሎ ኩባርሲ ላይ በሰራው ጥፋት 90+3 ደቂቃ ላይ በሁለት ቢጫ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል።
#worldcup #fifaworldcup #fifaworldcup2026 #argentina #spain #finalmatch #football #sports
*****************
በአርጀንቲና እና በስፔን መካከል እየተደረገ የሚገኘው የዓለም ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ መደበኛው የ90 ደቂቃ ክፍለ ጊዜ ያለምንም ግብ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።
በጨዋታው መደበኛ ክፍለ ጊዜ አሸናፊ ባለመገኘቱ፣ አሸናፊውን ለመለየት ወደ ጭማሪ 30 ደቂቃ አምርቷል።
ኤንዞ ፈርናንዴዝ ፓብሎ ኩባርሲ ላይ በሰራው ጥፋት 90+3 ደቂቃ ላይ በሁለት ቢጫ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል።
#worldcup #fifaworldcup #fifaworldcup2026 #argentina #spain #finalmatch #football #sports
17 days ago
በዓለም ዋንጫ የደረጃ ጨዋታ እንግሊዝ ፈረንሳይን አሸነፈች
**********************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ 3ኛ ደረጃን ይዞ ለማጠናቀቅ በግማሽ ፍፃሜ ተፋላሚዎቹ ሀገራት መካከል የተካሄደው የደረጃ ጨዋታ፤ በእንግሊዝ 6 ለ 4 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
አስር ግቦች በተቆጠሩበት ጨዋታ፤ ለእንግሊዝ ዲክላን ራይስ፣ ኤዝሪ ኮንሳህ፣ ጁድ ቤሊንግሃም እንዲሁም ቡካዮ ሳካ(ሦስት) አስቆጥረዋል።
የፈረንሳይን ግቦች ደግሞ ኪሊያን ምባፔ(ሁለት)፣ ብራድሊ ባርኮላ እና ኡስማን ዴምቤሌ ከመረብ አሳርፈዋል።
በዚህም 3ኛ ደረጃን ያገኘችው እንግሊዝ የነሀስ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆናለች።
በጨዋታው ሁለት ግቦችን ያስቆጠረው ኪሊያን ምባፔ ደግሞ፤ በምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት 22ኛውን በዚህ ዓለም ዋንጫ ደግሞ 10ኛውን በማስመዝገብ የወርቅ ጫማ ሽልማት ፉክክሩን ከሊዮኔል ሜሲ በመላቅ አስቀድሞ መምራት ጀምሯል።
ማይክል ኦሊሴ በዓለም ዋንጫ ሰባት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል በፔሌ ተይዞ የነበረውን ክብረወሰን አሻሽሏል።
#worldcup #fifaworldcup #fifaworldcup2026 #3rdplaceplayoff #england #france #football #sports
**********************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ 3ኛ ደረጃን ይዞ ለማጠናቀቅ በግማሽ ፍፃሜ ተፋላሚዎቹ ሀገራት መካከል የተካሄደው የደረጃ ጨዋታ፤ በእንግሊዝ 6 ለ 4 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
አስር ግቦች በተቆጠሩበት ጨዋታ፤ ለእንግሊዝ ዲክላን ራይስ፣ ኤዝሪ ኮንሳህ፣ ጁድ ቤሊንግሃም እንዲሁም ቡካዮ ሳካ(ሦስት) አስቆጥረዋል።
የፈረንሳይን ግቦች ደግሞ ኪሊያን ምባፔ(ሁለት)፣ ብራድሊ ባርኮላ እና ኡስማን ዴምቤሌ ከመረብ አሳርፈዋል።
በዚህም 3ኛ ደረጃን ያገኘችው እንግሊዝ የነሀስ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆናለች።
በጨዋታው ሁለት ግቦችን ያስቆጠረው ኪሊያን ምባፔ ደግሞ፤ በምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት 22ኛውን በዚህ ዓለም ዋንጫ ደግሞ 10ኛውን በማስመዝገብ የወርቅ ጫማ ሽልማት ፉክክሩን ከሊዮኔል ሜሲ በመላቅ አስቀድሞ መምራት ጀምሯል።
ማይክል ኦሊሴ በዓለም ዋንጫ ሰባት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል በፔሌ ተይዞ የነበረውን ክብረወሰን አሻሽሏል።
#worldcup #fifaworldcup #fifaworldcup2026 #3rdplaceplayoff #england #france #football #sports
17 days ago
ከስንብት ሐዘን ማግስት የሚደረግ የክብር ፍልሚያ
*******************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ዋዜማ ላይ ቆመናል። ዓለም ዋንጫ በግማሽ ፍፃሜ በለስ ያልቀናቸውን፣ ድል ከነርሱ ጋር ያልነበረውን እንዲሁ አያሰናብትም። ለሦስተኝነት ማዕረግ ዳግም ያፋልማል።
23ኛው ዓለም ዋንጫ ፍሎሪዳ ላይ የግማሽ ፍፃሜ ተሸናፊዎቹን ዛሬ እኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ፍሎሪዳ ሚያሚ ላይ ያፎካክራል። በእርግጥ በብዙዎች፣ በተለይም በተሸናፊ ብሔራዊ ቡድኖች ዘንድ የደረጃው ጨዋታ ለመጫወት የተመረጠ አይደለም።
የዛሬው መርኃ ግብር ግን ብሔራዊ ቡድኖቹ ከሚያደርጉት ፉክክር ባልተናነሰ፣ በኮከብ ግብ አስቆጣሪነት በመላቅ የወርቅ ኳስ ሽልማቱን ለማግኘት ባለው ፉክክር ለውጥ እንደሚያስከትል ይጠበቃል። ከሊዮኔል ሜሲ ጋር የኮከብ ግብ አስቆጣሪነት ፉክክሩን በ8 ግቦች እየመራ የሚገኘው ኪሊያን ምባፔ እንዲሁም እያንዳንዳቸው ስድስት ግቦች ያስቆጠሩት ጁድ ቤሊንግሃም እና ሀሪኬን ከባለ አምስት ግቡ የዓለም ኮከብ ኡስማን ዴምቤሌ ጋር በሚያደርጉት የኮከብ ግብ አስቆጣሪነት ፉክክር ላይ አንዳች ለውጥ ሊያስከትል የሚችል ጨዋታ እንደሚሆን ታምኗል።
በዚህ መሀል ግን ከሽንፈት ማግስት የሚደረግ፤ ከዓለም ዋንጫ ስንብት ሀዘንም ሳያገግሙ የሚመጣ መርኃ ግብር መሆኑ የተጫዋቾችን ተነሳሽነት መቀነሱ፣ የተመልካቾችን ጉጉትም ማሳነሱ አይቀርም። ቶማስ ቱሄል ይህን የሚያስረግጥ ሃሳብ ነው የሰነዘሩት። "የእኛም ሆነ የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች ይህን ጨዋታ የማድረግ ፍላጎት የላቸውም" በማለት በውድድሩ ሙሉ የለፉትና የተዘጋጁት ለዓለም ሻምፒዮንነት በመሆኑና፤ ያም ባለመሳካቱ ለዚህ ጨዋታ የሚኖራቸውን ጉጉትና ፍላጎት እንደቀነሰው ተናግረዋል።
ቱሄል ይህንን ቢሉም የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ዲዲየር ዴሻው ግን ከዚህ በአንፃራዊነት የተለየ ሃሳብ ነው የሰነዘሩት። 3ኛ ደረጃም ቢሆን የተሻለ መሆኑን በማንሳት፤ እርሱን ለማሳካት የቻሉትን ሁሉ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል። አክለውም የተፈጠረው ሀዘን የዓለም ሻምፒዮን ከመሆን ፅኑ መሻት የመጣ መሆኑን ጠቅሰው፤ የሆነውን ከመቀበል ውጪ አማራጭ የለንም ብለዋል።
በግማሽ ፍፃሜው እንግሊዝ እየመራች የነበረችውን ጨዋታ የኋላ ኋላ በአርጀንቲና 2 ለ 1 ተሸንፋ የፍፃሜ መንገዷ ሲቋረጥ፤ በአንፃሩ ፈረንሳይ ባልተጠበቀ ሁኔታ በስፔን ፍፁም ብልጫ ተወስዶባት 2 ለ 0 ተረታ ነው ከፍፃሜው የቀረችው።
የ23ኛው ዓለም ዋንጫ 103ኛው ጨዋታ በሁለት ሃሳቦች መሀል፤ የጨዋታውን አስፈላጊነት ተጠይቅ ውስጥ በሚከቱና የኮከብ ግብ አግቢነት ፉክክሩ ላይ የሚኖረውን ሚና በሚያጎሉ መሀል ሆኖ፤ እኩለ ሌሊት 6፡00 ሰዓት በሚያሚ ጋርደን ሀርድ ሮክ ስታዲየም ይካሄዳል።
በእድሪስ አህመድ
#worldcup #fifaworldcup #fifaworldcup2026 #3rdplaceplayoff #england #france #football #sports
*******************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ዋዜማ ላይ ቆመናል። ዓለም ዋንጫ በግማሽ ፍፃሜ በለስ ያልቀናቸውን፣ ድል ከነርሱ ጋር ያልነበረውን እንዲሁ አያሰናብትም። ለሦስተኝነት ማዕረግ ዳግም ያፋልማል።
23ኛው ዓለም ዋንጫ ፍሎሪዳ ላይ የግማሽ ፍፃሜ ተሸናፊዎቹን ዛሬ እኩለ ሌሊት 6 ሰዓት ፍሎሪዳ ሚያሚ ላይ ያፎካክራል። በእርግጥ በብዙዎች፣ በተለይም በተሸናፊ ብሔራዊ ቡድኖች ዘንድ የደረጃው ጨዋታ ለመጫወት የተመረጠ አይደለም።
የዛሬው መርኃ ግብር ግን ብሔራዊ ቡድኖቹ ከሚያደርጉት ፉክክር ባልተናነሰ፣ በኮከብ ግብ አስቆጣሪነት በመላቅ የወርቅ ኳስ ሽልማቱን ለማግኘት ባለው ፉክክር ለውጥ እንደሚያስከትል ይጠበቃል። ከሊዮኔል ሜሲ ጋር የኮከብ ግብ አስቆጣሪነት ፉክክሩን በ8 ግቦች እየመራ የሚገኘው ኪሊያን ምባፔ እንዲሁም እያንዳንዳቸው ስድስት ግቦች ያስቆጠሩት ጁድ ቤሊንግሃም እና ሀሪኬን ከባለ አምስት ግቡ የዓለም ኮከብ ኡስማን ዴምቤሌ ጋር በሚያደርጉት የኮከብ ግብ አስቆጣሪነት ፉክክር ላይ አንዳች ለውጥ ሊያስከትል የሚችል ጨዋታ እንደሚሆን ታምኗል።
በዚህ መሀል ግን ከሽንፈት ማግስት የሚደረግ፤ ከዓለም ዋንጫ ስንብት ሀዘንም ሳያገግሙ የሚመጣ መርኃ ግብር መሆኑ የተጫዋቾችን ተነሳሽነት መቀነሱ፣ የተመልካቾችን ጉጉትም ማሳነሱ አይቀርም። ቶማስ ቱሄል ይህን የሚያስረግጥ ሃሳብ ነው የሰነዘሩት። "የእኛም ሆነ የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች ይህን ጨዋታ የማድረግ ፍላጎት የላቸውም" በማለት በውድድሩ ሙሉ የለፉትና የተዘጋጁት ለዓለም ሻምፒዮንነት በመሆኑና፤ ያም ባለመሳካቱ ለዚህ ጨዋታ የሚኖራቸውን ጉጉትና ፍላጎት እንደቀነሰው ተናግረዋል።
ቱሄል ይህንን ቢሉም የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ዲዲየር ዴሻው ግን ከዚህ በአንፃራዊነት የተለየ ሃሳብ ነው የሰነዘሩት። 3ኛ ደረጃም ቢሆን የተሻለ መሆኑን በማንሳት፤ እርሱን ለማሳካት የቻሉትን ሁሉ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል። አክለውም የተፈጠረው ሀዘን የዓለም ሻምፒዮን ከመሆን ፅኑ መሻት የመጣ መሆኑን ጠቅሰው፤ የሆነውን ከመቀበል ውጪ አማራጭ የለንም ብለዋል።
በግማሽ ፍፃሜው እንግሊዝ እየመራች የነበረችውን ጨዋታ የኋላ ኋላ በአርጀንቲና 2 ለ 1 ተሸንፋ የፍፃሜ መንገዷ ሲቋረጥ፤ በአንፃሩ ፈረንሳይ ባልተጠበቀ ሁኔታ በስፔን ፍፁም ብልጫ ተወስዶባት 2 ለ 0 ተረታ ነው ከፍፃሜው የቀረችው።
የ23ኛው ዓለም ዋንጫ 103ኛው ጨዋታ በሁለት ሃሳቦች መሀል፤ የጨዋታውን አስፈላጊነት ተጠይቅ ውስጥ በሚከቱና የኮከብ ግብ አግቢነት ፉክክሩ ላይ የሚኖረውን ሚና በሚያጎሉ መሀል ሆኖ፤ እኩለ ሌሊት 6፡00 ሰዓት በሚያሚ ጋርደን ሀርድ ሮክ ስታዲየም ይካሄዳል።
በእድሪስ አህመድ
#worldcup #fifaworldcup #fifaworldcup2026 #3rdplaceplayoff #england #france #football #sports
19 days ago
እንግሊዝ በዓለም ዋንጫ፤ ለ60 ዓመታት ያልተፈታው ህልም፣ ያልተመለሰው ጥያቄ!
**************************
እንግሊዝ የዓለም ዋንጫን ዳግም ሳታነሳ ተጨማሪ 4 ዓመታት እንደሚቆጠሩ እርግጥ ከሆነ 24 ሰዓታት አለፉ። አትላንታ ላይ “ሦስቱ አናብስት” የዓለም ሻምፒዮን የመሆን ውጥን ይዘው፣ እስከ ግማሽ ፍፃሜም ተጉዘው የጀመሩት መንገድ በሊዮኔል ሜሲ አርጀንቲና ተቋርጧል። ለተጨማሪ ዓመታት እንዲወጡት የሚያስፈልግ ሌላ ዳገት፣ ሊወርዱትም የሚገባ ሌላ ቁልቁለት ‘ተበጅቶላቸዋል’።
እነዛ 60 ዓመታት በዓለም እግር ኳስ የራሷን አሻራ ላኖረችው ሀገር ብዙ መውጣትና መውረዶች፣ በርካታ ተስፋ አስቆራጭ ደግሞም ተስፋ መልሶ የለመለመባቸው ወቅቶች አልፎባቸዋል። ዓለም ዋንጫ ግን ያዝኩት ሲሉ እያመለጠ፣ ደረስኩበት ሲሉ እየራቀ “ጉም የመዝገን” ያክል ሆኖባቸዋል።
ሐምሌ 30/ 1966 እ.አ.አ ሰር ቦቢ ሙር የእንግሊዝን የመድረኩ ብቸኛ ድል፣ የቀደመውን የጁሊየስ ሪሜትስ ዋንጫ ካነሳ በኋላ ብዙ ነገሮች ባሉበት የሉም ተቀያይረዋል። እግር ኳስም፣ ራሷ እንግሊዝም ሆነ ዓለም ትላንትን አይመስሉም።
እንግሊዝ ምዕራብ ጀርመንን 4 ለ 2 አሸንፋ የመጀመሪያ ዓለም ዋንጫዋን ካነሳች በኋላ፤ 454 ተጫዋቾች ነጩን የብሔራዊ ቡድን መለያ ለመጀመሪያ ጊዜ ለብሰዋል። ቀዳሚው በ1967 የተጫወተው 847ኛው ተጫዋች ጆን ሆሊንስ ሲሆን፤ የብሔራዊ ቡድኑን መለያ በመልበስ ደግሞ የመጨረሻ የሆነው 1300ኛው የሊቨርፑሉ ሪዮ ንጉምሃ ነው። በዓለም ዋንጫው ደግሞ ከውጤታማው የአልፍ ራምሴይ ቡድን ጀምሮ እሰከ አሁኑ ቶማስ ቱሄል ድረስ 161 ተጫዋቾች እንግሊዝን ወክለዋል።
በስድሰቱ አስርታት ዋንጫ አልባ ዓመታት 15 አሰልጣኞች በቋሚነት ብሔራዊ ቡድኑን መርተዋል። ሮን ግሪንዉድ፣ ሰቨን ጎራን ኤሪክሰን፣ ፋቢዮ ካፔሎ እና ጋሬት ሳውዝጌት ተጠቃሾች ናቸው። ሁሉም ግን የአልፍ ራምሴይን ውጤታማ መንገድ ማስቀጠል አልሆነላቸውም።
አለን ሺረር፣ ዴቪድ ቤካም፣ ስቴቨን ጄራርድ እና ሃሪ ኬን ባለፉት 60 ዓመታት በተካሄዱት ዓለም ዋንጫዎች ቡድኑን በአምበልነት ከመሩ ተጫዋቾች የሚጠቀሱ ናቸው።
እንግሊዝ ከ1966 ሻምፒዮንነቷ በኋላ ከተካሄዱት 15 የዓለም ዋንጫዎች በ12ቱ ተሳትፋለች። በሁሉም ግን ደርሶ የመመለስ፣ አግኝቶም የማጣት ምሳሌ ተደርጋ ቀጥላለች። በ1986 የዲዬጎ ማራዶና በ4 ደቂቃ ልዩነት ያሳየው “የእጅም የእግርም” ትርዒት፣ በ1990 ግማሽ ፍጻሜ የፖል ጋስኮኝ እንባ፣ በ1998 ዓለም ዋንጫ የዴቪድ ቤካም ቀይ ካርድ፣ በ2002 ዓለም ዋንጫ የሮናልዲንሆ ጎቾ ዝነኛ የቅጣት ምት “ወርቃማ ግብ”፣ በ2010 መስመሯን አልፋ የተሻረችው የፍራንክ ላምፓርድ ግብ፣ በ2022 ዓለም ዋንጫ ሀሪ ኬን ያባከናት የፍፁም ቅጣት ምት፣ በመጨረሻም 2026 ላይ በአትላንታ ምድር እየመሩ የነበረውን ጨዋታ የኋላ ኋላ ማጣት፤ እንግሊዞች በቁጭት የሚያስታውሷቸው አጋጣሚዎች ናቸው።
ከዚያ በኋላ የበርሊን ግንብ ፈርሷል፣ የሰው ልጅ ወደ ጨረቃ መጥቋል፣ ዓለም በበይነ መረብ ተሳስሯል፣ የስማርት ስልክ ዘመን የሰው ልጅን የዕለት ተዕለት ህይወት ፈጣን አድርጓል። እነዚህና መሰል ለውጦች በሰው ልጅ የምድር ቆይታ ቢስተናገዱም፤ የእንግሊዝ የዓለም ዋንጫ ሻምፒዮንነት ህልም 1966 ላይ እንደቆመ አለ።
እንግሊዝ ባስተናገደችው የ1996ቱ አውሮፓ ዋንጫ ወቅት የተዜመው “…30 የህመም ዓመታት” የሚል ሀረግ የያዘውና የ1966ቱን ዓለም ዋንጫ በማስታወስ እግር ኳስ ወደ ቤቱ እየተመለሰ እንደሆነ የሚያትተው ኅብረ ዝማሬ፣ ዛሬም አውዱን የሳተ አይመስልም። 30ዎቹ ዓመታት ሌላ 30 ዓመታትን አዋልደዋል፤ እግር ኳስም ወደ “ቤቱ” አልተመለሰም።
የብሔራዊ ቡድኑን መለያ ከለበሱት 454 ተጫዋቾች፣ በዓለም ዋንጫው ከተጫወቱት 161 እግር ኳሰኞች፣ በ15ቱ አሰልጣኞች ስር ካለፉ 7 አምበሎች የምድር ትልቁን የእግር ኳስ ሽልማት ከፍ አድርጎ ማንሳት የቻለው ቦቢ ሙር ብቻ ነው።
ትውልድ ይተካል፣ ተስፋም እየደበዘዘም ቢሆን መልሶ ይለመልማል። እንግሊዛውያንም እግር ኳሳቸው በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም በሊግ ውድድሮች በቅርቦቹ ዓመታት እንዳሳደረው ተፅእኖ፤ ብሔራዊ ቡድናቸውም ይህን የዘመናት ህልሙን እውን የሚያደርግበትን ቀን በተስፋ ይጠባበቃሉ።
የ2026ቱ የአሜሪካ ምድር መንገድ ግን ጫፍ ደርሶ ተቋርጧል። ጁድ ቤሊንግሃም “ልብ ሰባሪ ፍፃሜን ያስከተለ ውብ ጉዞ” ሲል የገለፀው የ2026 ዓለም ዋንጫ ቆይታ አብቅቷል።
በእድሪስ አህመድ
#worldcup #fifaworldcup2026 #fifaworldcup1966 #england #threelions #judebellingham #harrykane #semifinal #football #sports #ebc
**************************
እንግሊዝ የዓለም ዋንጫን ዳግም ሳታነሳ ተጨማሪ 4 ዓመታት እንደሚቆጠሩ እርግጥ ከሆነ 24 ሰዓታት አለፉ። አትላንታ ላይ “ሦስቱ አናብስት” የዓለም ሻምፒዮን የመሆን ውጥን ይዘው፣ እስከ ግማሽ ፍፃሜም ተጉዘው የጀመሩት መንገድ በሊዮኔል ሜሲ አርጀንቲና ተቋርጧል። ለተጨማሪ ዓመታት እንዲወጡት የሚያስፈልግ ሌላ ዳገት፣ ሊወርዱትም የሚገባ ሌላ ቁልቁለት ‘ተበጅቶላቸዋል’።
እነዛ 60 ዓመታት በዓለም እግር ኳስ የራሷን አሻራ ላኖረችው ሀገር ብዙ መውጣትና መውረዶች፣ በርካታ ተስፋ አስቆራጭ ደግሞም ተስፋ መልሶ የለመለመባቸው ወቅቶች አልፎባቸዋል። ዓለም ዋንጫ ግን ያዝኩት ሲሉ እያመለጠ፣ ደረስኩበት ሲሉ እየራቀ “ጉም የመዝገን” ያክል ሆኖባቸዋል።
ሐምሌ 30/ 1966 እ.አ.አ ሰር ቦቢ ሙር የእንግሊዝን የመድረኩ ብቸኛ ድል፣ የቀደመውን የጁሊየስ ሪሜትስ ዋንጫ ካነሳ በኋላ ብዙ ነገሮች ባሉበት የሉም ተቀያይረዋል። እግር ኳስም፣ ራሷ እንግሊዝም ሆነ ዓለም ትላንትን አይመስሉም።
እንግሊዝ ምዕራብ ጀርመንን 4 ለ 2 አሸንፋ የመጀመሪያ ዓለም ዋንጫዋን ካነሳች በኋላ፤ 454 ተጫዋቾች ነጩን የብሔራዊ ቡድን መለያ ለመጀመሪያ ጊዜ ለብሰዋል። ቀዳሚው በ1967 የተጫወተው 847ኛው ተጫዋች ጆን ሆሊንስ ሲሆን፤ የብሔራዊ ቡድኑን መለያ በመልበስ ደግሞ የመጨረሻ የሆነው 1300ኛው የሊቨርፑሉ ሪዮ ንጉምሃ ነው። በዓለም ዋንጫው ደግሞ ከውጤታማው የአልፍ ራምሴይ ቡድን ጀምሮ እሰከ አሁኑ ቶማስ ቱሄል ድረስ 161 ተጫዋቾች እንግሊዝን ወክለዋል።
በስድሰቱ አስርታት ዋንጫ አልባ ዓመታት 15 አሰልጣኞች በቋሚነት ብሔራዊ ቡድኑን መርተዋል። ሮን ግሪንዉድ፣ ሰቨን ጎራን ኤሪክሰን፣ ፋቢዮ ካፔሎ እና ጋሬት ሳውዝጌት ተጠቃሾች ናቸው። ሁሉም ግን የአልፍ ራምሴይን ውጤታማ መንገድ ማስቀጠል አልሆነላቸውም።
አለን ሺረር፣ ዴቪድ ቤካም፣ ስቴቨን ጄራርድ እና ሃሪ ኬን ባለፉት 60 ዓመታት በተካሄዱት ዓለም ዋንጫዎች ቡድኑን በአምበልነት ከመሩ ተጫዋቾች የሚጠቀሱ ናቸው።
እንግሊዝ ከ1966 ሻምፒዮንነቷ በኋላ ከተካሄዱት 15 የዓለም ዋንጫዎች በ12ቱ ተሳትፋለች። በሁሉም ግን ደርሶ የመመለስ፣ አግኝቶም የማጣት ምሳሌ ተደርጋ ቀጥላለች። በ1986 የዲዬጎ ማራዶና በ4 ደቂቃ ልዩነት ያሳየው “የእጅም የእግርም” ትርዒት፣ በ1990 ግማሽ ፍጻሜ የፖል ጋስኮኝ እንባ፣ በ1998 ዓለም ዋንጫ የዴቪድ ቤካም ቀይ ካርድ፣ በ2002 ዓለም ዋንጫ የሮናልዲንሆ ጎቾ ዝነኛ የቅጣት ምት “ወርቃማ ግብ”፣ በ2010 መስመሯን አልፋ የተሻረችው የፍራንክ ላምፓርድ ግብ፣ በ2022 ዓለም ዋንጫ ሀሪ ኬን ያባከናት የፍፁም ቅጣት ምት፣ በመጨረሻም 2026 ላይ በአትላንታ ምድር እየመሩ የነበረውን ጨዋታ የኋላ ኋላ ማጣት፤ እንግሊዞች በቁጭት የሚያስታውሷቸው አጋጣሚዎች ናቸው።
ከዚያ በኋላ የበርሊን ግንብ ፈርሷል፣ የሰው ልጅ ወደ ጨረቃ መጥቋል፣ ዓለም በበይነ መረብ ተሳስሯል፣ የስማርት ስልክ ዘመን የሰው ልጅን የዕለት ተዕለት ህይወት ፈጣን አድርጓል። እነዚህና መሰል ለውጦች በሰው ልጅ የምድር ቆይታ ቢስተናገዱም፤ የእንግሊዝ የዓለም ዋንጫ ሻምፒዮንነት ህልም 1966 ላይ እንደቆመ አለ።
እንግሊዝ ባስተናገደችው የ1996ቱ አውሮፓ ዋንጫ ወቅት የተዜመው “…30 የህመም ዓመታት” የሚል ሀረግ የያዘውና የ1966ቱን ዓለም ዋንጫ በማስታወስ እግር ኳስ ወደ ቤቱ እየተመለሰ እንደሆነ የሚያትተው ኅብረ ዝማሬ፣ ዛሬም አውዱን የሳተ አይመስልም። 30ዎቹ ዓመታት ሌላ 30 ዓመታትን አዋልደዋል፤ እግር ኳስም ወደ “ቤቱ” አልተመለሰም።
የብሔራዊ ቡድኑን መለያ ከለበሱት 454 ተጫዋቾች፣ በዓለም ዋንጫው ከተጫወቱት 161 እግር ኳሰኞች፣ በ15ቱ አሰልጣኞች ስር ካለፉ 7 አምበሎች የምድር ትልቁን የእግር ኳስ ሽልማት ከፍ አድርጎ ማንሳት የቻለው ቦቢ ሙር ብቻ ነው።
ትውልድ ይተካል፣ ተስፋም እየደበዘዘም ቢሆን መልሶ ይለመልማል። እንግሊዛውያንም እግር ኳሳቸው በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለይም በሊግ ውድድሮች በቅርቦቹ ዓመታት እንዳሳደረው ተፅእኖ፤ ብሔራዊ ቡድናቸውም ይህን የዘመናት ህልሙን እውን የሚያደርግበትን ቀን በተስፋ ይጠባበቃሉ።
የ2026ቱ የአሜሪካ ምድር መንገድ ግን ጫፍ ደርሶ ተቋርጧል። ጁድ ቤሊንግሃም “ልብ ሰባሪ ፍፃሜን ያስከተለ ውብ ጉዞ” ሲል የገለፀው የ2026 ዓለም ዋንጫ ቆይታ አብቅቷል።
በእድሪስ አህመድ
#worldcup #fifaworldcup2026 #fifaworldcup1966 #england #threelions #judebellingham #harrykane #semifinal #football #sports #ebc
20 days ago
አርጀንቲና ወደ ዓለም ዋንጫ ፍፃሜ አለፈች
***************
በ23ኛው የዓለም ዋንጫ በአትላንታ ስታዲየም በእንግሊዝና አርጀንቲና መካከል የተካሄደው ተጠባቂ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ በአርጀንቲና 2 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
ለአርጀንቲና የአሸናፊነት ግቦቹን በ85ኛው ደቂቃ ኤንዞ ፈርናንዴዝ እንዲሁም በጭማሪ ሰዓት (90+3) ላውታሮ ማርቲኔዝ ከመረብ አሳርፈዋል። ለእንግሊዝ ብቸኛዋን ግብ በ55ኛው ደቂቃ አንቶኒ ጎርደን አስቆጥሯል።
የወቅቱ የዓለም ሻምፒዮን አርጀንቲና ለዋንጫው ክብሯን ለማስጠበቅ የፊታችን እሁድ ከስፔን ብሔራዊ ቡድን ጋር ታላቅ የፍፃሜ ጨዋታዋን ታደርጋለች።
የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታዎች ተሸናፊዎቹ ፈረንሳይና እንግሊዝ ደግሞ የፊታችን ቅዳሜ ሌሊት 3ኛ ደረጃ ይዞ ለማጠናቀቅ የሚጫወቱ ይሆናል።
#worldcup #fifaworldcup2026 #fifaworldcup #england #argentina #semifinal #football #sports
***************
በ23ኛው የዓለም ዋንጫ በአትላንታ ስታዲየም በእንግሊዝና አርጀንቲና መካከል የተካሄደው ተጠባቂ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ በአርጀንቲና 2 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
ለአርጀንቲና የአሸናፊነት ግቦቹን በ85ኛው ደቂቃ ኤንዞ ፈርናንዴዝ እንዲሁም በጭማሪ ሰዓት (90+3) ላውታሮ ማርቲኔዝ ከመረብ አሳርፈዋል። ለእንግሊዝ ብቸኛዋን ግብ በ55ኛው ደቂቃ አንቶኒ ጎርደን አስቆጥሯል።
የወቅቱ የዓለም ሻምፒዮን አርጀንቲና ለዋንጫው ክብሯን ለማስጠበቅ የፊታችን እሁድ ከስፔን ብሔራዊ ቡድን ጋር ታላቅ የፍፃሜ ጨዋታዋን ታደርጋለች።
የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታዎች ተሸናፊዎቹ ፈረንሳይና እንግሊዝ ደግሞ የፊታችን ቅዳሜ ሌሊት 3ኛ ደረጃ ይዞ ለማጠናቀቅ የሚጫወቱ ይሆናል።
#worldcup #fifaworldcup2026 #fifaworldcup #england #argentina #semifinal #football #sports
20 days ago
እንግሊዝ 0 - 0 አርጀንቲና :- የመጀመሪያ አጋማሽ ውጤት
**************
በአትላንታ ስታዲየም በእንግሊዝ እና አርጀንቲና መካከል እየተካሄደ የሚገኘው እጅግ ተጠባቂ የዓለም ዋንጫ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ የመጀመሪያው 45 ደቂቃ ያለምንም ግብ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።
#worldcup #fifaworldcup2026 #fifaworldcup #england #argentina #semifinal #football #sports
**************
በአትላንታ ስታዲየም በእንግሊዝ እና አርጀንቲና መካከል እየተካሄደ የሚገኘው እጅግ ተጠባቂ የዓለም ዋንጫ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ የመጀመሪያው 45 ደቂቃ ያለምንም ግብ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።
#worldcup #fifaworldcup2026 #fifaworldcup #england #argentina #semifinal #football #sports
21 days ago
ስፔን ፈረንሳይን አሸንፋ ለፍፃሜ አለፈች
***************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የግማሽ ፍፃሜ መርኃ ግብር ስፔን ከፈረንሳይ ያደረጉት ጨዋታ፤ በስፔን 2 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
ለስፔን የአሸናፊነት ግቦቹን ሚኬል ኦያርዛባል 22ኛው ደቂቃ ላይ በፍፁም ቅጣት ምት እንዲሁም ፔድሮ ፖሮ በ58ኛው ደቂቃ ከመረብ አሳርፈዋል።
በዚህም በ2010 የደቡብ አፍሪካውን ዓለም ዋንጫ ያሸነፈችው ስፔን ከ16 ዓመታት በኋላ ለውድድሩ ፍፃሜ ደርሳለች።
ወደ ፍፃሜው የተሸጋገረችው ስፔን በቀጣይ ከአርጀንቲና እና እንግሊዝ አሸናፊ ጋር እሁድ የምትጫወት ይሆናል።
#worldcup2026 #fifaworldcup2026 #fifaworldcup2026 #spain #france #semifinal #football #sports #ebc
***************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የግማሽ ፍፃሜ መርኃ ግብር ስፔን ከፈረንሳይ ያደረጉት ጨዋታ፤ በስፔን 2 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
ለስፔን የአሸናፊነት ግቦቹን ሚኬል ኦያርዛባል 22ኛው ደቂቃ ላይ በፍፁም ቅጣት ምት እንዲሁም ፔድሮ ፖሮ በ58ኛው ደቂቃ ከመረብ አሳርፈዋል።
በዚህም በ2010 የደቡብ አፍሪካውን ዓለም ዋንጫ ያሸነፈችው ስፔን ከ16 ዓመታት በኋላ ለውድድሩ ፍፃሜ ደርሳለች።
ወደ ፍፃሜው የተሸጋገረችው ስፔን በቀጣይ ከአርጀንቲና እና እንግሊዝ አሸናፊ ጋር እሁድ የምትጫወት ይሆናል።
#worldcup2026 #fifaworldcup2026 #fifaworldcup2026 #spain #france #semifinal #football #sports #ebc
22 days ago
ኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን በጀግኖች አቀባበል ወደ ሀገሩ ተመለሰ
#ethiopia | በ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ ታሪካዊ ጉዞ በማድረግ የዓለም የእግር ኳስ አፍቃሪዎችን ያስደነቀው የኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን፣ ወደ አገሩ ሲመለስ በሺዎች የሚቆጠሩ ደጋፊዎች የጀግና አቀባበል አደረጉለት።
የኖርዌይ ባንዲራዎች በየስፍራው ሲውለበለቡ፣ የድጋፍ ዝማሬና ጭብጨባ በመታጀብ ተጫዋቾቹና የአሰልጣኝ ቡድኑ ከሀገራቸው ህዝብ ልዩ ክብር ተቀበለዋል።
በኮከብ ተጫዋች ኤርሊንግ ሃላንድ የተመራው ቡድን በውድድሩ ያሳየው ጠንካራ አቋም፣ አንድነትና ጽናት በኖርዌይ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ እንደከፈተ ተገልጿል።
ይህ አቀባበል የውጤት ብቻ ሳይሆን የብሔራዊ ኩራት፣ የተስፋ እና የአንድነት ምልክት ሆኖ ተከብሯል። ብዙ ደጋፊዎችም ይህ ትውልድ ለኖርዌይ እግር ኳስ ብሩህ የወደፊት ተስፋ እንደሰጠ ገልጸዋል።
እርስዎ ምን ያስባሉ?
የ2026 የኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን በሀገሪቱ የእግር ኳስ ታሪክ ከታላላቅ ቡድኖች መካከል የቱ ይመደባል?
#norway #fifaworldcup2026 #erlinghaaland #football #norwegianfootball #getutemesgen #ethiopia
#ethiopia | በ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ ታሪካዊ ጉዞ በማድረግ የዓለም የእግር ኳስ አፍቃሪዎችን ያስደነቀው የኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን፣ ወደ አገሩ ሲመለስ በሺዎች የሚቆጠሩ ደጋፊዎች የጀግና አቀባበል አደረጉለት።
የኖርዌይ ባንዲራዎች በየስፍራው ሲውለበለቡ፣ የድጋፍ ዝማሬና ጭብጨባ በመታጀብ ተጫዋቾቹና የአሰልጣኝ ቡድኑ ከሀገራቸው ህዝብ ልዩ ክብር ተቀበለዋል።
በኮከብ ተጫዋች ኤርሊንግ ሃላንድ የተመራው ቡድን በውድድሩ ያሳየው ጠንካራ አቋም፣ አንድነትና ጽናት በኖርዌይ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ እንደከፈተ ተገልጿል።
ይህ አቀባበል የውጤት ብቻ ሳይሆን የብሔራዊ ኩራት፣ የተስፋ እና የአንድነት ምልክት ሆኖ ተከብሯል። ብዙ ደጋፊዎችም ይህ ትውልድ ለኖርዌይ እግር ኳስ ብሩህ የወደፊት ተስፋ እንደሰጠ ገልጸዋል።
እርስዎ ምን ያስባሉ?
የ2026 የኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን በሀገሪቱ የእግር ኳስ ታሪክ ከታላላቅ ቡድኖች መካከል የቱ ይመደባል?
#norway #fifaworldcup2026 #erlinghaaland #football #norwegianfootball #getutemesgen #ethiopia
Sponsored by
Surafel
25 days ago
ሚኬል ሜሪኖ በድጋሚ የስፔን ጀግና ሆነ፤ ስፔን ቤልጅየምን አሸንፋ ለግማሽ ፍፃሜ አለፈች
#ethiopia | በ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ በተደረገ ከፍተኛ ፉክክር የታየበት ጨዋታ፣ ስፔን ቤልጅየምን 2 ለ 1 በማሸነፍ ወደ ውድድሩ ግማሽ ፍፃሜ መድረስ ችላለች።
በሎስ አንጀለስ በተካሄደው ጨዋታ ስፔን በ30ኛው ደቂቃ ፋቢያን ሩይዝ ባስቆጠረው ጎል መሪ መሆን ችላ ነበር። ሆኖም ቤልጅየም በ41ኛው ደቂቃ ቻርልስ ዴ ኬቴላሬ ባስቆጠረው ጎል ጨዋታውን ወደ እኩልነት መልሳለች።
ሁለቱ ቡድኖች በሁለተኛው አጋማሽ የድል ጎል ፍለጋ ጠንካራ ፍልሚያ ቢያደርጉም፣ የስፔን ተቀይሮ የገባው ሚኬል ሜሪኖ በ88ኛው ደቂቃ የድል ጎል በማስቆጠር ቡድኑን ወደ ቀጣዩ ዙር አሳልፏል።
ሜሪኖ በዚህ ዓለም ዋንጫ ከመጨረሻ ደቂቃዎች ጋር የተያያዘ የድል ታሪክ እየፃፈ ይገኛል። በፖርቱጋል ላይ በ85ኛው ደቂቃ ገብቶ በ90+1 ደቂቃ ጎል ሲያስቆጥር፣ በቤልጅየም ላይ ደግሞ በ86ኛው ደቂቃ ገብቶ ከሁለት ደቂቃ በኋላ የድል ጎል አስመዝግቧል።
ቤልጅየም እስከ መጨረሻው ደቂቃ ድረስ ለመመለስ ብትጥርም፣ የስፔንን መከላከያ መስበር አልቻለችም። በተለይም የቡድኑ ግብ ጠባቂ ቲቦ ኩርቱዋ በጉዳት ከሜዳ መውጣቱ ለቤልጅየም ተጨማሪ ፈተና ሆኗል።
በዚህም ስፔን የ2026 ዓለም ዋንጫ የግማሽ ፍፃሜ ተሳታፊ ሆናለች፤ በቀጣዩ ዙርም ከፈረንሳይ ጋር ለዋንጫው ፍፃሜ ቦታ ትፋለማለች።
#worldcup2026 #spain #belgium #football #getutemesgen #ጌጡተመስገን
#ethiopia | በ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ በተደረገ ከፍተኛ ፉክክር የታየበት ጨዋታ፣ ስፔን ቤልጅየምን 2 ለ 1 በማሸነፍ ወደ ውድድሩ ግማሽ ፍፃሜ መድረስ ችላለች።
በሎስ አንጀለስ በተካሄደው ጨዋታ ስፔን በ30ኛው ደቂቃ ፋቢያን ሩይዝ ባስቆጠረው ጎል መሪ መሆን ችላ ነበር። ሆኖም ቤልጅየም በ41ኛው ደቂቃ ቻርልስ ዴ ኬቴላሬ ባስቆጠረው ጎል ጨዋታውን ወደ እኩልነት መልሳለች።
ሁለቱ ቡድኖች በሁለተኛው አጋማሽ የድል ጎል ፍለጋ ጠንካራ ፍልሚያ ቢያደርጉም፣ የስፔን ተቀይሮ የገባው ሚኬል ሜሪኖ በ88ኛው ደቂቃ የድል ጎል በማስቆጠር ቡድኑን ወደ ቀጣዩ ዙር አሳልፏል።
ሜሪኖ በዚህ ዓለም ዋንጫ ከመጨረሻ ደቂቃዎች ጋር የተያያዘ የድል ታሪክ እየፃፈ ይገኛል። በፖርቱጋል ላይ በ85ኛው ደቂቃ ገብቶ በ90+1 ደቂቃ ጎል ሲያስቆጥር፣ በቤልጅየም ላይ ደግሞ በ86ኛው ደቂቃ ገብቶ ከሁለት ደቂቃ በኋላ የድል ጎል አስመዝግቧል።
ቤልጅየም እስከ መጨረሻው ደቂቃ ድረስ ለመመለስ ብትጥርም፣ የስፔንን መከላከያ መስበር አልቻለችም። በተለይም የቡድኑ ግብ ጠባቂ ቲቦ ኩርቱዋ በጉዳት ከሜዳ መውጣቱ ለቤልጅየም ተጨማሪ ፈተና ሆኗል።
በዚህም ስፔን የ2026 ዓለም ዋንጫ የግማሽ ፍፃሜ ተሳታፊ ሆናለች፤ በቀጣዩ ዙርም ከፈረንሳይ ጋር ለዋንጫው ፍፃሜ ቦታ ትፋለማለች።
#worldcup2026 #spain #belgium #football #getutemesgen #ጌጡተመስገን
25 days ago
ስፔን ቤልጂየምን አሸንፋ ወደ ግማሽ ፍፃሜ አለፈች
******************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የሩብ ፍፃሜ መርኃ ግብር ስፔን ከቤልጂየም ያደረጉት ጨዋታ፤ በስፔን 2 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
ለስፔን የአሸናፊነት ግቦቹን ፋቢያን ሩይዝ በ30ኛው ደቂቃ እንዲሁም ሚኬል ሜሪኖ በ88ኛው ደቂቃ ላይ ከመረብ አሳርፈዋል።
ለቤልጂየም ብቸኛዋን ግብ ቻርለስ ዴ ኬተሌር በ41ኛው ደቂቃ አስቆጥሯል።
ወደ ግማሽ ፍፃሜው የተሸጋገረችው ስፔን በቀጣይ ጨዋታዋ ከፈረንሳይ ጋር የምትገናኝ ይሆናል።
#spain #belgium #football #sports #worldcup2026 #quarterfinals #semifinales #ebc
******************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የሩብ ፍፃሜ መርኃ ግብር ስፔን ከቤልጂየም ያደረጉት ጨዋታ፤ በስፔን 2 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
ለስፔን የአሸናፊነት ግቦቹን ፋቢያን ሩይዝ በ30ኛው ደቂቃ እንዲሁም ሚኬል ሜሪኖ በ88ኛው ደቂቃ ላይ ከመረብ አሳርፈዋል።
ለቤልጂየም ብቸኛዋን ግብ ቻርለስ ዴ ኬተሌር በ41ኛው ደቂቃ አስቆጥሯል።
ወደ ግማሽ ፍፃሜው የተሸጋገረችው ስፔን በቀጣይ ጨዋታዋ ከፈረንሳይ ጋር የምትገናኝ ይሆናል።
#spain #belgium #football #sports #worldcup2026 #quarterfinals #semifinales #ebc
25 days ago
65" ስፔን 1 - 1 ቤልጂየም
ቻርለስ ዴ ኬተላሬ በድንቅ አቋሙ ቀጥሏል! 🇧🇪🔥
#ethiopia | የቤልጂየሙ ኮከብ ተጫዋች ቻርለስ ዴ ኬተላሬ በ2026 የዓለም ዋንጫ ባደረጋቸው የመጨረሻ ሁለት ጨዋታዎች 4 የጎል ተሳትፎዎችን (ጎሎችና አሲስቶች) በማስመዝገብ ከፍተኛ ብቃቱን አሳይቷል።
በትልልቅ ግፊቶች ውስጥ የሚያበራው ዴ ኬተላሬ፣ በ2026 የዓለም ዋንጫ በስፔን መረብ ላይ ጎል ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋች በመሆንም ሌላ ታሪክ ጽፏል።
ቤልጂየም በውድድሩ ላይ በሚያሳየው ጠንካራ አቋም ውስጥ ዴ ኬተላሬ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ሲሆን፣ የቡድኑ የጥቃት ክፍል ዋነኛ መሪ ሆኖ ቀጥሏል።
#worldcup2026 #belgium #charlesdeketelaere #football #sports
ቻርለስ ዴ ኬተላሬ በድንቅ አቋሙ ቀጥሏል! 🇧🇪🔥
#ethiopia | የቤልጂየሙ ኮከብ ተጫዋች ቻርለስ ዴ ኬተላሬ በ2026 የዓለም ዋንጫ ባደረጋቸው የመጨረሻ ሁለት ጨዋታዎች 4 የጎል ተሳትፎዎችን (ጎሎችና አሲስቶች) በማስመዝገብ ከፍተኛ ብቃቱን አሳይቷል።
በትልልቅ ግፊቶች ውስጥ የሚያበራው ዴ ኬተላሬ፣ በ2026 የዓለም ዋንጫ በስፔን መረብ ላይ ጎል ያስቆጠረ የመጀመሪያው ተጫዋች በመሆንም ሌላ ታሪክ ጽፏል።
ቤልጂየም በውድድሩ ላይ በሚያሳየው ጠንካራ አቋም ውስጥ ዴ ኬተላሬ ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ሲሆን፣ የቡድኑ የጥቃት ክፍል ዋነኛ መሪ ሆኖ ቀጥሏል።
#worldcup2026 #belgium #charlesdeketelaere #football #sports
26 days ago
በክሪስቲያኖ ሮናልዶ የስልክ ጥሪ በኦልድትራፎርድ የደመቁት መንትዮች - ራፋኤል እና ፋቢዮ ዳ ሲልቫ
********************************
ቁመናቸው፣ መልካቸው እና የአጨዋወት ዘይቤያቸው እጅግ በመመሳሰሉ ምክንያት፣ ታላቁ አሰልጣኝ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን እንኳን ለመለየት እንደሚቸገሩ የሚነገርላቸው ራፋኤል እና ፋቢዮ ዳ ሲልቫ፤ በኦልድ ትራፎርድ በነበራቸው ቆይታ የማንቸስተር ዩናይትድ ደጋፊዎችን ልብ የገዙ ተጫዋቾች ናቸው።
ብራዚላውያኑ የሪዮ ዲ ጄኔሮ ተወላጅ መንትዮች ከልጅነታቸው ጀምሮ በአንድ ቡድን፣ በአንድ ክፍልና በአንድ ህልም ያደጉት መንትዮቹ፤ በ15 ዓመታቸው እ.አ.አ በ2005 በሆንግ ኮንግ በተደረገ የወጣቶች ውድድር ላይ በዩናይትድ የስካውቲንግ ቡድን አይን ውስጥ ገቡ።
በወቅቱ አርሰናልን ጨምሮ በርካታ የአውሮፓ ታላላቅ ክለቦች ተጫዋቾቹን ለማስፈረም ከፍተኛ ፉክክር ውስጥ ቢገቡም፣ የውሳኔያቸውን አቅጣጫ የቀየረው ያልተጠበቀ የስልክ ጥሪ ነበር።
በወቅቱ የዩናይትድ ኮከብ የነበረው ክርስቲያኖ ሮናልዶ በቀጥታ ደውሎ፣ "ወደ ማንቸስተር ዩናይትድ ኑ፤ በፍጹም አትቆጩም!" በማለት አበረታታቸው። ይህ ጥሪ የመንትዮቹን ውሳኔ አስቀይሮ፣ በጥር 2008 በይፋ የ"ቲያትር ኦፍ ድሪምስ" አባል እንዲሆኑ አደረጋቸው።
በወቅቱ የአውሮፓ እግር ኳስን በበላይነት ለሚመራው ማንቸስተር ዩናይትድ አዲስ ጉልበትና ተስፋ ይዘው የመጡት ታዳጊዎች፤ በአሰልጣኝ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ዘንድ "የወደፊቶቹ ኮከቦች" የሚል ታላቅ ሙገሳን አገኙ።
ሆኖም በመጀመሪያዎቹ ቀናት ሁለቱን መለየት እጅግ አስቸጋሪ ነበር። ተጫዋቾች፣ የክለቡ ሰራተኞች እና ሰር አሌክስ ራሳቸው ጭምር ብዙ ጊዜ ያሳስቷቸው ነበር።
በአንድ ወቅት በዩናይትድ ፖድካስት ላይ እንደተናገሩት፤ በአንድ ጨዋታ ላይ ራፋኤል ስህተት ይሰራል። በእረፍት ሰዓት ፈርጉሰን በቁጣ ወደ መልበሻ ክፍል በመግባት ፋቢዮን ራፋኤል መስሏቸው አጥብቀው ገሰጹት። ሪዮ ፈርዲናንድ እና ማይክል ካሪክ ግን "ያ ራፋኤል አይደለም፣ ፋቢዮ ነው" ብለው ሲነግሯቸው፤ ፈርጉሰን "ሁለቱም አንድ ናቸው!" ብለው ቁጣቸውን መቀጠላቸው እስከዛሬ በዩናይትድ ደጋፊዎች ዘንድ በፈገግታ ይታወሳል።
አንዳንድ ጊዜ ፋቢዮ ጥፋት አጥፍቶ ራፋኤል ካርድ የተቀበለበት አጋጣሚም ነበር። በልምምድ ሜዳም አሰልጣኞችን ለማደናገር ሆን ብለው ማሊያቸውንና ጫማቸውን እንደሚቀያይሩ ከዓመታት በኋላ በሳቅ ታጅበው የገለጡት የኦልድትራፎርድ ምስጢራቸው ነው።
መንትዮቹ በዩናይትድ ቆይታቸው በርካታ ስኬቶችን አስመዝግበዋል። በተለይም ራፋኤል በቀኝ ተከላካይ መስመር የጋሪ ኔቪልን ቦታ በብቃት መተካት የቻለ ድንቅ ተጫዋች ነው። 170 ጨዋታዎችን አድርጎ 5 ግቦችን አስቆጥሯል፤ 3 የፕሪሚየር ሊግ፣ 1 የሊግ ካፕ እና 1 የክለቦች ዓለም ዋንጫ አንስቷል።
በሌላ በኩል ፋቢዮ በግራ ተከላካይ መስመር ላይ ከፓትሪስ ኤቭራ ጋር ከባድ ፉክክር ነበረበት። ለዩናይትድ 56 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ 3 ግቦችን አስቆጥሯል፤ 1 የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫንም አሽንፏል። 2011 ላይ ዩናይትድ በባርሴሎና በተሸነፈበት የሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ ላይ በቋሚነት የመጀመር ዕድል አግኝቷል።
የሰር አሌክስ ፈርጉሰን ከማንቸስተር መልቀቅና የሉዊስ ቫን ሀል ወደ አሰልጣኝነት መምጣት ለመንትዮቹ የኦልድትራፎርድ ቆይታ ማብቃት ምክንያት ሆነ።
ቫን ሀል ለብራዚላውያኑ መንትዮች ዕድል የመስጠት ፍላጎት እንዳልነበራቸው ራፋኤል ከዓመታት በኋላ ለሚዲያ በግልጽ ተናግሯል።
በዚህም ምክንያት ራፋኤል በ2015 ወደ ፈረንሳዩ ሊዮን አቀና። በዚያም ለ5 ዓመታት ስኬታማ ቆይታ ካደረገ በኋላ፣ ወደ ቱርኩ ባሻክሼሂር አምርቶ በሻምፒዮንስ ሊግ የቀድሞ ክለቡ ማንቸስተር ዩናይትድን በመግጠም ጭምር አሸንፏል።
ፋቢዮ ደግሞ ከዩናይትድ በኋላ በካርዲፍ ሲቲ፣ ሚድልስብሮ እና በፈረንሳዩ ናንትስ ክለቦች ተጫውቷል።
ትላንት 36ኛ ዓመት የልደት በዓላቸውን ያከበሩት መንትዮቹ፤ በአሁኑ ሰዓት በትውልድ ሀገራቸው ብራዚል ይገኛሉ። ራፋኤል ለቦታፎጎ፣ ፋቢዮ ደግሞ በግሬሚዮ በመጫወት ላይ ናቸው።
ዛሬም ቢሆን ማንቸስተር ዩናይትድ ያላቸው ፍቅር አልቀነሰም። በቅርቡ በ"ኢንሳይድ ካሪንግተን" ፖድካስት ላይ ተገኝተው ስለ ዩናይትድ የቆይታ ዘመናቸው፣ ስለ ፈርጉሰን እና ስለ ማይክል ካሪክ በኩራት ተናግረዋል። አሁንም የዩናይትድን ውጤቶች በቅርበት እንደሚከታተሉና ልባቸው ኦልድትራፎርድ እንደሚገኝ ይገልጻሉ።
ራፋኤል እና ፋቢዮ ዳ ሲልቫ በዩናይትድ ታሪክ ውስጥ እንደ ሮናልዶ ወይም ሩኒ በግንባር ቀደምትነት ላይጠቀሱ ይችላሉ፤ ነገር ግን ባሳዩት የማይበገር የብራዚላውያን ስሜት፣ ለክለቡ በሰጡት ታማኝነትና ሜዳ ላይ በሚያሳዩት ውብ ፈገግታ በደጋፊዎች ልብ ውስጥ ምንጊዜም የማይረሳ አሻራ ጥለው ያለፉ ድንቅ መንትዮች ናቸው።
በአዲስ የሺዋስ
#manchesterunited #theatreofdreams #cr7cristianoronaldo #fabiodasilva #rafaeldasilva #twinbrothers #football #sports
********************************
ቁመናቸው፣ መልካቸው እና የአጨዋወት ዘይቤያቸው እጅግ በመመሳሰሉ ምክንያት፣ ታላቁ አሰልጣኝ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን እንኳን ለመለየት እንደሚቸገሩ የሚነገርላቸው ራፋኤል እና ፋቢዮ ዳ ሲልቫ፤ በኦልድ ትራፎርድ በነበራቸው ቆይታ የማንቸስተር ዩናይትድ ደጋፊዎችን ልብ የገዙ ተጫዋቾች ናቸው።
ብራዚላውያኑ የሪዮ ዲ ጄኔሮ ተወላጅ መንትዮች ከልጅነታቸው ጀምሮ በአንድ ቡድን፣ በአንድ ክፍልና በአንድ ህልም ያደጉት መንትዮቹ፤ በ15 ዓመታቸው እ.አ.አ በ2005 በሆንግ ኮንግ በተደረገ የወጣቶች ውድድር ላይ በዩናይትድ የስካውቲንግ ቡድን አይን ውስጥ ገቡ።
በወቅቱ አርሰናልን ጨምሮ በርካታ የአውሮፓ ታላላቅ ክለቦች ተጫዋቾቹን ለማስፈረም ከፍተኛ ፉክክር ውስጥ ቢገቡም፣ የውሳኔያቸውን አቅጣጫ የቀየረው ያልተጠበቀ የስልክ ጥሪ ነበር።
በወቅቱ የዩናይትድ ኮከብ የነበረው ክርስቲያኖ ሮናልዶ በቀጥታ ደውሎ፣ "ወደ ማንቸስተር ዩናይትድ ኑ፤ በፍጹም አትቆጩም!" በማለት አበረታታቸው። ይህ ጥሪ የመንትዮቹን ውሳኔ አስቀይሮ፣ በጥር 2008 በይፋ የ"ቲያትር ኦፍ ድሪምስ" አባል እንዲሆኑ አደረጋቸው።
በወቅቱ የአውሮፓ እግር ኳስን በበላይነት ለሚመራው ማንቸስተር ዩናይትድ አዲስ ጉልበትና ተስፋ ይዘው የመጡት ታዳጊዎች፤ በአሰልጣኝ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ዘንድ "የወደፊቶቹ ኮከቦች" የሚል ታላቅ ሙገሳን አገኙ።
ሆኖም በመጀመሪያዎቹ ቀናት ሁለቱን መለየት እጅግ አስቸጋሪ ነበር። ተጫዋቾች፣ የክለቡ ሰራተኞች እና ሰር አሌክስ ራሳቸው ጭምር ብዙ ጊዜ ያሳስቷቸው ነበር።
በአንድ ወቅት በዩናይትድ ፖድካስት ላይ እንደተናገሩት፤ በአንድ ጨዋታ ላይ ራፋኤል ስህተት ይሰራል። በእረፍት ሰዓት ፈርጉሰን በቁጣ ወደ መልበሻ ክፍል በመግባት ፋቢዮን ራፋኤል መስሏቸው አጥብቀው ገሰጹት። ሪዮ ፈርዲናንድ እና ማይክል ካሪክ ግን "ያ ራፋኤል አይደለም፣ ፋቢዮ ነው" ብለው ሲነግሯቸው፤ ፈርጉሰን "ሁለቱም አንድ ናቸው!" ብለው ቁጣቸውን መቀጠላቸው እስከዛሬ በዩናይትድ ደጋፊዎች ዘንድ በፈገግታ ይታወሳል።
አንዳንድ ጊዜ ፋቢዮ ጥፋት አጥፍቶ ራፋኤል ካርድ የተቀበለበት አጋጣሚም ነበር። በልምምድ ሜዳም አሰልጣኞችን ለማደናገር ሆን ብለው ማሊያቸውንና ጫማቸውን እንደሚቀያይሩ ከዓመታት በኋላ በሳቅ ታጅበው የገለጡት የኦልድትራፎርድ ምስጢራቸው ነው።
መንትዮቹ በዩናይትድ ቆይታቸው በርካታ ስኬቶችን አስመዝግበዋል። በተለይም ራፋኤል በቀኝ ተከላካይ መስመር የጋሪ ኔቪልን ቦታ በብቃት መተካት የቻለ ድንቅ ተጫዋች ነው። 170 ጨዋታዎችን አድርጎ 5 ግቦችን አስቆጥሯል፤ 3 የፕሪሚየር ሊግ፣ 1 የሊግ ካፕ እና 1 የክለቦች ዓለም ዋንጫ አንስቷል።
በሌላ በኩል ፋቢዮ በግራ ተከላካይ መስመር ላይ ከፓትሪስ ኤቭራ ጋር ከባድ ፉክክር ነበረበት። ለዩናይትድ 56 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ 3 ግቦችን አስቆጥሯል፤ 1 የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫንም አሽንፏል። 2011 ላይ ዩናይትድ በባርሴሎና በተሸነፈበት የሻምፒዮንስ ሊግ ፍፃሜ ላይ በቋሚነት የመጀመር ዕድል አግኝቷል።
የሰር አሌክስ ፈርጉሰን ከማንቸስተር መልቀቅና የሉዊስ ቫን ሀል ወደ አሰልጣኝነት መምጣት ለመንትዮቹ የኦልድትራፎርድ ቆይታ ማብቃት ምክንያት ሆነ።
ቫን ሀል ለብራዚላውያኑ መንትዮች ዕድል የመስጠት ፍላጎት እንዳልነበራቸው ራፋኤል ከዓመታት በኋላ ለሚዲያ በግልጽ ተናግሯል።
በዚህም ምክንያት ራፋኤል በ2015 ወደ ፈረንሳዩ ሊዮን አቀና። በዚያም ለ5 ዓመታት ስኬታማ ቆይታ ካደረገ በኋላ፣ ወደ ቱርኩ ባሻክሼሂር አምርቶ በሻምፒዮንስ ሊግ የቀድሞ ክለቡ ማንቸስተር ዩናይትድን በመግጠም ጭምር አሸንፏል።
ፋቢዮ ደግሞ ከዩናይትድ በኋላ በካርዲፍ ሲቲ፣ ሚድልስብሮ እና በፈረንሳዩ ናንትስ ክለቦች ተጫውቷል።
ትላንት 36ኛ ዓመት የልደት በዓላቸውን ያከበሩት መንትዮቹ፤ በአሁኑ ሰዓት በትውልድ ሀገራቸው ብራዚል ይገኛሉ። ራፋኤል ለቦታፎጎ፣ ፋቢዮ ደግሞ በግሬሚዮ በመጫወት ላይ ናቸው።
ዛሬም ቢሆን ማንቸስተር ዩናይትድ ያላቸው ፍቅር አልቀነሰም። በቅርቡ በ"ኢንሳይድ ካሪንግተን" ፖድካስት ላይ ተገኝተው ስለ ዩናይትድ የቆይታ ዘመናቸው፣ ስለ ፈርጉሰን እና ስለ ማይክል ካሪክ በኩራት ተናግረዋል። አሁንም የዩናይትድን ውጤቶች በቅርበት እንደሚከታተሉና ልባቸው ኦልድትራፎርድ እንደሚገኝ ይገልጻሉ።
ራፋኤል እና ፋቢዮ ዳ ሲልቫ በዩናይትድ ታሪክ ውስጥ እንደ ሮናልዶ ወይም ሩኒ በግንባር ቀደምትነት ላይጠቀሱ ይችላሉ፤ ነገር ግን ባሳዩት የማይበገር የብራዚላውያን ስሜት፣ ለክለቡ በሰጡት ታማኝነትና ሜዳ ላይ በሚያሳዩት ውብ ፈገግታ በደጋፊዎች ልብ ውስጥ ምንጊዜም የማይረሳ አሻራ ጥለው ያለፉ ድንቅ መንትዮች ናቸው።
በአዲስ የሺዋስ
#manchesterunited #theatreofdreams #cr7cristianoronaldo #fabiodasilva #rafaeldasilva #twinbrothers #football #sports
Sponsored by
Surafel
26 days ago
ፈረንሳይ ሞሮኮን አሸንፋ ለግማሽ ፍፃሜ አለፈች
*****************
በ23ኛው የዓለም ዋንጫ በፈረንሳይ እና በሞሮኮ መካከል የተደረገው የመጀመሪያው የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ፤ በፈረንሳይ 2 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
የፈረንሳይን የማሸነፊያ ግቦች 60ኛው ደቂቃ ላይ ኪሊያን ምባፔ እንዲሁም 66ኛው ደቂቃ ላይ ኡስማን ዴምቤሌ አስቆጥረዋል።
ኪሊያን ምባፔ በዓለም ዋንጫ ተሳትፎ ታሪኩ ያስቆጠራቸው ግቦች 20 የደረሱ ሲሆን፤ 29ኛው ደቂቃ ላይ ፈረንሳይ አግኝታው የነበረውን ፍፁም ቅጣት ምት ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
ፈረንሳይ በግማሽ ፍፃሜው ከስፔን እና ቤልጂየም አሸናፊ ጋር ትጫወታለች።
#france #morocco #fifaworldcup2026 #quarterfinal #football #sports #ebc
*****************
በ23ኛው የዓለም ዋንጫ በፈረንሳይ እና በሞሮኮ መካከል የተደረገው የመጀመሪያው የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ፤ በፈረንሳይ 2 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
የፈረንሳይን የማሸነፊያ ግቦች 60ኛው ደቂቃ ላይ ኪሊያን ምባፔ እንዲሁም 66ኛው ደቂቃ ላይ ኡስማን ዴምቤሌ አስቆጥረዋል።
ኪሊያን ምባፔ በዓለም ዋንጫ ተሳትፎ ታሪኩ ያስቆጠራቸው ግቦች 20 የደረሱ ሲሆን፤ 29ኛው ደቂቃ ላይ ፈረንሳይ አግኝታው የነበረውን ፍፁም ቅጣት ምት ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
ፈረንሳይ በግማሽ ፍፃሜው ከስፔን እና ቤልጂየም አሸናፊ ጋር ትጫወታለች።
#france #morocco #fifaworldcup2026 #quarterfinal #football #sports #ebc
26 days ago
ፈረንሳይ 0 - 0 ሞሮኮ :- የመጀመሪያ አጋማሽ ውጤት
**********************
በፈረንሳይ እና በሞሮኮ መካከል እየተደረገ ያለው ተጠባቂ የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ የመጀመሪያ አጋማሽ ያለምንም ግብ 0 ለ 0 በሆነ ውጤት ተጠናቅቋል።
በጨዋታው 28ኛው ደቂቃ ላይ ፈረንሳይ መሪ የምትሆንበትን ወርቃማ ዕድል አግኝታ የነበረ ቢሆንም፣ ኪሊያን ምባፔ ያገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
#france #morocco #fifaworldcup2026 #quarterfinal #football #sports #ebc
**********************
በፈረንሳይ እና በሞሮኮ መካከል እየተደረገ ያለው ተጠባቂ የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ የመጀመሪያ አጋማሽ ያለምንም ግብ 0 ለ 0 በሆነ ውጤት ተጠናቅቋል።
በጨዋታው 28ኛው ደቂቃ ላይ ፈረንሳይ መሪ የምትሆንበትን ወርቃማ ዕድል አግኝታ የነበረ ቢሆንም፣ ኪሊያን ምባፔ ያገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
#france #morocco #fifaworldcup2026 #quarterfinal #football #sports #ebc
28 days ago
ስዊዘርላንድ ስምንተኛዋ ሩብ ፍፃሜውን የተቀላቀለች ሀገር ሆናለች
************************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ16ቱ ሀገራት ጥሎ ማለፍ የመጨረሻው ጨዋታ ስዊዘርላንድ ኮሎምቢያን አሸንፋለች።
መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ እና ጭማሪው 30 ደቂቃ ያለግብ ተጠናቀው፤ አሸናፊውን ለመለየት በተሰጡ መለያ ምቶች ስዊዘርላንድ 4 ለ 3 ረታለች።
ስዊዘርላንድ በሩብ ፍፃሜው አርጀንቲናን የምትገጥም ይሆናል።
ፈረንሳይ ከ ሞሮኮ፣ ስፔን ከ ቤልጂየም እንዲሁም ኖርዌይ ከ እንግሊዝ ሌሎቹ የሩብ ፍፃሜ መርኃ ግብሮች ናቸው።
#worldcup #fifaworldcup #switzerland #colombia #quarterfinal #football #sports
************************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ16ቱ ሀገራት ጥሎ ማለፍ የመጨረሻው ጨዋታ ስዊዘርላንድ ኮሎምቢያን አሸንፋለች።
መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ እና ጭማሪው 30 ደቂቃ ያለግብ ተጠናቀው፤ አሸናፊውን ለመለየት በተሰጡ መለያ ምቶች ስዊዘርላንድ 4 ለ 3 ረታለች።
ስዊዘርላንድ በሩብ ፍፃሜው አርጀንቲናን የምትገጥም ይሆናል።
ፈረንሳይ ከ ሞሮኮ፣ ስፔን ከ ቤልጂየም እንዲሁም ኖርዌይ ከ እንግሊዝ ሌሎቹ የሩብ ፍፃሜ መርኃ ግብሮች ናቸው።
#worldcup #fifaworldcup #switzerland #colombia #quarterfinal #football #sports
28 days ago
ግብፅ አርጀንቲናን መርታ የመጀመሪያውን አጋማሽ አጠናቀቀች
*******************
እየተካሄደ በሚገኘው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ግብፅ አርጀንቲናን 1 ለ 0 በመምራት የመጀመሪያ አጋማሽ አጠናቅቃለች፡፡
በጥሎ ማለፍ ጨዋታው ግብፅን መሪ ያደረገችውን ግብ ያሲር ኢብራሂም በ15ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።
በጨዋታው 21ኛው ደቂቃ ላይ አርጀንቲና ያገኘችውን የፍፁም ቅጣት ምት ሊዮኔል ሜሲ ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
#ebc #argentina #egypt #football #sports #roundof16 #knockout
*******************
እየተካሄደ በሚገኘው የፊፋ ዓለም ዋንጫ ግብፅ አርጀንቲናን 1 ለ 0 በመምራት የመጀመሪያ አጋማሽ አጠናቅቃለች፡፡
በጥሎ ማለፍ ጨዋታው ግብፅን መሪ ያደረገችውን ግብ ያሲር ኢብራሂም በ15ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።
በጨዋታው 21ኛው ደቂቃ ላይ አርጀንቲና ያገኘችውን የፍፁም ቅጣት ምት ሊዮኔል ሜሲ ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
#ebc #argentina #egypt #football #sports #roundof16 #knockout
29 days ago
ቤልጂየም አሜሪካን 4-1 በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜን ተቀላቀለች
#ethiopia | በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የ16ቱ ሀገራት የጥሎ ማለፍ ውድድር ቤልጂየም የጣምራ አዘጋጅ አሜሪካን 4 ለ1 በማሸነፍ ወደ ሩብ ፍጻሜ ማለፍ ችላለች።
በሲያትል ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ቻርለስ ዲ ኬተላረ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የድሉ ዋና ተዋናይ ሆኗል። ሃንስ ቫኔከን እና ሮሜሉ ሉካኩም ተጨማሪ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የቤልጂየምን ድል አረጋግጠዋል።
አሜሪካ በጨዋታው ደካማ ብቃት ሲያሳይ ብቸኛ ግቧን በማሊክ ቲልማን አስቆጥራለች።
በዚህ ውጤት የ2026 ዓለም ዋንጫ ሦስቱም የጣምራ አዘጋጅ ሀገራት ማለትም ካናዳ፣ ሜክሲኮ እና አሜሪካ በ16ቱ ዙር ከውድድሩ ውጪ ሆነዋል።
ቤልጂየም በሩብ ፍጻሜ በሌላ አስደናቂ ጨዋታ ፖርቱጋልን 1 ለ0 በማሸነፍ ያለፈችውን ስፔን ትገጥማለች።
#worldcup2026 #belgium #usa #quarterfinal #football #getutemesgenmedia
#ethiopia | በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የ16ቱ ሀገራት የጥሎ ማለፍ ውድድር ቤልጂየም የጣምራ አዘጋጅ አሜሪካን 4 ለ1 በማሸነፍ ወደ ሩብ ፍጻሜ ማለፍ ችላለች።
በሲያትል ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ቻርለስ ዲ ኬተላረ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የድሉ ዋና ተዋናይ ሆኗል። ሃንስ ቫኔከን እና ሮሜሉ ሉካኩም ተጨማሪ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የቤልጂየምን ድል አረጋግጠዋል።
አሜሪካ በጨዋታው ደካማ ብቃት ሲያሳይ ብቸኛ ግቧን በማሊክ ቲልማን አስቆጥራለች።
በዚህ ውጤት የ2026 ዓለም ዋንጫ ሦስቱም የጣምራ አዘጋጅ ሀገራት ማለትም ካናዳ፣ ሜክሲኮ እና አሜሪካ በ16ቱ ዙር ከውድድሩ ውጪ ሆነዋል።
ቤልጂየም በሩብ ፍጻሜ በሌላ አስደናቂ ጨዋታ ፖርቱጋልን 1 ለ0 በማሸነፍ ያለፈችውን ስፔን ትገጥማለች።
#worldcup2026 #belgium #usa #quarterfinal #football #getutemesgenmedia
29 days ago
አሜሪካ በቤልጂየም ተሸንፋ ከዓለም ዋንጫው ተሰናበተች
********************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ ከውድድሩ አዘጋጅ ሀገራት አንዷ የሆነችው አሜሪካ፤ በቤልጂየም 4 ለ 1 ተሸንፋ ከዓለም ዋንጫው ውጪ ሆናለች።
ቻርለስ ኬቴለር(ሁለት) እንዲሁም ሀንስ ቫናከን እና ሮሜሉ ሉካኩ የቤልጂየምን ማሸነፊያ ግቦች ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው።
የአሜሪካን ብቸኛ ግብ ማሊክ ቲልማን ከመረብ አሳርፏል።
ቤልጂየም በሩብ ፍፃሜው የስፔን ብሔራዊ ቡድንን የምትገጥም ይሆናል።
#worldcup #fifaworldcup #usa #belgium #knockoutstage #football #sports
********************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ ከውድድሩ አዘጋጅ ሀገራት አንዷ የሆነችው አሜሪካ፤ በቤልጂየም 4 ለ 1 ተሸንፋ ከዓለም ዋንጫው ውጪ ሆናለች።
ቻርለስ ኬቴለር(ሁለት) እንዲሁም ሀንስ ቫናከን እና ሮሜሉ ሉካኩ የቤልጂየምን ማሸነፊያ ግቦች ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው።
የአሜሪካን ብቸኛ ግብ ማሊክ ቲልማን ከመረብ አሳርፏል።
ቤልጂየም በሩብ ፍፃሜው የስፔን ብሔራዊ ቡድንን የምትገጥም ይሆናል።
#worldcup #fifaworldcup #usa #belgium #knockoutstage #football #sports
29 days ago
ስፔን ፖርቹጋልን በማሸነፍ ወደ ሩብ ፍፃሜው ተሸጋገረች
*****************
በ16ቱ ሀገራት ጥሎ ማለፍ ስፔን ከ ፖርቹጋል ያደረጉት ጨዋታ፤ በስፔን 1 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
ለስፔን ሚኬል ሜሪኖ በጭማሪ ሰዓት (90+1 ደቂቃ) ላይ በፌራን ቶሬስ አመቻችነት ብቸኛዋን እና የማሸነፊያ ግብ አስቆጥሯል።
ወደ ሩብ ፍፃሜው የተሸጋገረችው ስፔን በቀጣይ ከአሜሪካ እና ቤልጂየም አሸናፊ ጋር ትጫወታለች።
#spain #portugal #football #sports #roundof16 #quarterfinal #ebc
*****************
በ16ቱ ሀገራት ጥሎ ማለፍ ስፔን ከ ፖርቹጋል ያደረጉት ጨዋታ፤ በስፔን 1 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
ለስፔን ሚኬል ሜሪኖ በጭማሪ ሰዓት (90+1 ደቂቃ) ላይ በፌራን ቶሬስ አመቻችነት ብቸኛዋን እና የማሸነፊያ ግብ አስቆጥሯል።
ወደ ሩብ ፍፃሜው የተሸጋገረችው ስፔን በቀጣይ ከአሜሪካ እና ቤልጂየም አሸናፊ ጋር ትጫወታለች።
#spain #portugal #football #sports #roundof16 #quarterfinal #ebc
29 days ago
50"
ስፔንና ፖርቹጋል ያለ ግብ ወደ ሁለተኛው አጋማሽ ተሸጋገሩ
#ethiopia | በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የ16 ዙር ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ስፔን እና ፖርቹጋል እያደረጉት ያለው ፍልሚያ የመጀመሪያ አጋማሹ 0–0 በሆነ ውጤት ተጠናቋል።
ሁለቱም ቡድኖች በጥንቃቄ ጨዋታቸውን ሲያካሂዱ ቢታዩም፣ ግብ ለማስቆጠር የተፈጠሩ እድሎችን ወደ መረብ መቀየር አልቻሉም። በመሆኑም ተጠባቂው ፍልሚያ ያለ ግብ ወደ ሁለተኛው አጋማሽ ተሸጋግሯል።
የዚህ ጨዋታ አሸናፊ ወደ ሩብ ፍጻሜ የሚያልፍ ሲሆን፣ ቀጣዩ 45 ደቂቃዎች የጨዋታውን ውጤት የሚወስኑ ይሆናሉ።
#fifaworldcup #spain #portugal #worldcup2026 #football #sports
ስፔንና ፖርቹጋል ያለ ግብ ወደ ሁለተኛው አጋማሽ ተሸጋገሩ
#ethiopia | በ23ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ የ16 ዙር ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ስፔን እና ፖርቹጋል እያደረጉት ያለው ፍልሚያ የመጀመሪያ አጋማሹ 0–0 በሆነ ውጤት ተጠናቋል።
ሁለቱም ቡድኖች በጥንቃቄ ጨዋታቸውን ሲያካሂዱ ቢታዩም፣ ግብ ለማስቆጠር የተፈጠሩ እድሎችን ወደ መረብ መቀየር አልቻሉም። በመሆኑም ተጠባቂው ፍልሚያ ያለ ግብ ወደ ሁለተኛው አጋማሽ ተሸጋግሯል።
የዚህ ጨዋታ አሸናፊ ወደ ሩብ ፍጻሜ የሚያልፍ ሲሆን፣ ቀጣዩ 45 ደቂቃዎች የጨዋታውን ውጤት የሚወስኑ ይሆናሉ።
#fifaworldcup #spain #portugal #worldcup2026 #football #sports
29 days ago
ስፔን 0 - 0 ፖርቹጋል፦ የመጀመሪያ አጋማሽ ውጤት
****************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ16ቱ ሀገራት ጥሎ ማለፍ ስፔን ከፖርቹጋል እያደረጉት ያለው ጨዋታ፤ የመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ግብ ተጠናቋል።
#worldcup #fifaworldcup #portugal #spain #knockoutstage #football #sports
****************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ16ቱ ሀገራት ጥሎ ማለፍ ስፔን ከፖርቹጋል እያደረጉት ያለው ጨዋታ፤ የመጀመሪያው አጋማሽ ያለ ግብ ተጠናቋል።
#worldcup #fifaworldcup #portugal #spain #knockoutstage #football #sports
1 month ago
ብራዚል ከ23ኛው ዓለም ዋንጫ ተሰናበተች
**************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ16ቱ ሀገራት ጥሎ ማለፍ መርኃ ግብር ብራዚል በኖርዌይ 2 ለ 1 ተሸንፋ ከዓለም ዋንጫው ተሰናብታለች። ኖርዌይም በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሩብ ፍፃሜ አልፋለች።
የኖርዌይን የማሸነፊያ ግቦች 79ኛው እና 90ኛው ደቂቃ ላይ ኧርሊንግ ሀላንድ ከመረብ አሳርፏል። ለብራዚል ኔይማር ጁኒየር በፍፁም ቅጣት ምት 90+10 ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።
በጨዋታው በብራዚል በኩል ብሩኖ ጉማሬሽ 14ኛው ደቂቃ ላይ ያገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
ኖርዌይ በሩብ ፍፃሜው የሜክሲኮ እና እንግሊዝን አሸናፊ የምትገጥም ይሆናል።
በእድሪስ አሕመድ
#worldcup #fifaworldcup #brazil #norway #knockoutstage #football #sports
**************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ16ቱ ሀገራት ጥሎ ማለፍ መርኃ ግብር ብራዚል በኖርዌይ 2 ለ 1 ተሸንፋ ከዓለም ዋንጫው ተሰናብታለች። ኖርዌይም በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሩብ ፍፃሜ አልፋለች።
የኖርዌይን የማሸነፊያ ግቦች 79ኛው እና 90ኛው ደቂቃ ላይ ኧርሊንግ ሀላንድ ከመረብ አሳርፏል። ለብራዚል ኔይማር ጁኒየር በፍፁም ቅጣት ምት 90+10 ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።
በጨዋታው በብራዚል በኩል ብሩኖ ጉማሬሽ 14ኛው ደቂቃ ላይ ያገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
ኖርዌይ በሩብ ፍፃሜው የሜክሲኮ እና እንግሊዝን አሸናፊ የምትገጥም ይሆናል።
በእድሪስ አሕመድ
#worldcup #fifaworldcup #brazil #norway #knockoutstage #football #sports
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ብራዚል 0 - 0 ኖርዌይ :- የመጀመሪያ አጋማሽ ውጤት
***************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ በብራዚል እና በኖርዌይ መካከል እየተደረገ ያለው ጨዋታ የመጀመሪያው 45 ደቂቃ ያለ ምንም ግብ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።
በጨዋታው በብራዚል በኩል ብሩኖ ጉማሬሽ 14ኛው ደቂቃ ላይ ያገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
#worldcup #fifaworldcup #brazil #norway #knockoutstage #football #sports
***************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ በብራዚል እና በኖርዌይ መካከል እየተደረገ ያለው ጨዋታ የመጀመሪያው 45 ደቂቃ ያለ ምንም ግብ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።
በጨዋታው በብራዚል በኩል ብሩኖ ጉማሬሽ 14ኛው ደቂቃ ላይ ያገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
#worldcup #fifaworldcup #brazil #norway #knockoutstage #football #sports
1 month ago
1 month ago
ሞሮኮ ወደ ሩብ ፍፃሜ አለፈች
*************
በ23ኛው የዓለም ዋንጫ ምሽት 2 ሰዓት በተደረገ የ16ቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ሞሮኮ ካናዳን 3 ለ 0 በማሸነፍ ወደ ሩብ ፍጻሜው መግባቷን አረጋግጣለች፡፡
ለሞሮኮ አዜዲን ኦናሂ በ50ኛው እና በ82ኛው ደቂቃ ላይ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር፣ ሱፊያን ረሂሚ በጭማሪ ሰዓት (90+8) ሦስተኛዋን ግብ አክሏል።
ወደ ሩብ ፍፃሜው የተሸጋገረችው ሞሮኮ በቀጣይ ጨዋታዋ ከፈረንሳይ እና ፓራጓይ አሸናፊ ጋር ትጫወታለች።
#morocco #canada #football #sports #roundof16 #quarterfinal #ebc
*************
በ23ኛው የዓለም ዋንጫ ምሽት 2 ሰዓት በተደረገ የ16ቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ሞሮኮ ካናዳን 3 ለ 0 በማሸነፍ ወደ ሩብ ፍጻሜው መግባቷን አረጋግጣለች፡፡
ለሞሮኮ አዜዲን ኦናሂ በ50ኛው እና በ82ኛው ደቂቃ ላይ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር፣ ሱፊያን ረሂሚ በጭማሪ ሰዓት (90+8) ሦስተኛዋን ግብ አክሏል።
ወደ ሩብ ፍፃሜው የተሸጋገረችው ሞሮኮ በቀጣይ ጨዋታዋ ከፈረንሳይ እና ፓራጓይ አሸናፊ ጋር ትጫወታለች።
#morocco #canada #football #sports #roundof16 #quarterfinal #ebc
1 month ago
ኮሎምቢያ ጋናን በማሸነፍ ወደ 16ቱ ጥሎ ማለፍ ተሸጋገረች
**************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ32ቱ ሀገራት ጥሎ ማለፍ ኮሎምቢያ ከ ጋና ያደረጉት ጨዋታ፤ በኮሎምቢያ 1 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
ለኮሎምቢያ የማሸነፊያዋን ብቸኛ ግብ ጆን አሪያስ በ14ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።
ወደ 16ቱ ጥሎ ማለፍ የተሸጋገረችው ኮሎምቢያ በቀጣይ ጨዋታዋ ከስዊዘርላንድ ጋር ትጫወታለች።
#worldcup #fifaworldcup #colombia #ghana #football #sports #ebc
**************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ32ቱ ሀገራት ጥሎ ማለፍ ኮሎምቢያ ከ ጋና ያደረጉት ጨዋታ፤ በኮሎምቢያ 1 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
ለኮሎምቢያ የማሸነፊያዋን ብቸኛ ግብ ጆን አሪያስ በ14ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል።
ወደ 16ቱ ጥሎ ማለፍ የተሸጋገረችው ኮሎምቢያ በቀጣይ ጨዋታዋ ከስዊዘርላንድ ጋር ትጫወታለች።
#worldcup #fifaworldcup #colombia #ghana #football #sports #ebc
1 month ago
አርጀንቲና ኬፕቨርዴን በማሸነፍ ወደ 16ቱ ጥሎ ማለፍ ተሸጋገረች
*********
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ32 ሀገራት ጥሎ ማለፍ መርኃ ግብር አፍሪካዊቷን ደሴት ኬፕቨርዴን የገጠመችው አርጀንቲና 3 ለ 2 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ቀጣዩን የ16 ሀገራት ጥሎ ማለፍ ዙር ተቀላቅላለች።
ሊዮኔል ሜሲ ለአርጀንቲና ዳንኤል ዱዋርቴ ደግሞ ለኬፕቨርዴ 1 አቻ በተጠናቀቀው መደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ግቦቹን ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው።
አሸናፊውን ለመለየት በተጨመሩት 90 ደቂቃዎች፤ የአርጀንቲናን የማሸነፊያ ግቦች ያስቆጠሩት ሊሳንድሮ ማርቲኔዝ እና ዲኔይ ቦርገስ(በራሱ መረብ ላይ) ሲሆን የኬፕ ቨሮዴን ግብ ሲድኒ ካብራል ከመረብ አሳርፏል።
ሻምፒዮኗ አርጀንቲና በቀጣዩ የጥሎ ማለፍ መርኃ ግብር ግብፅን የምትገጥም ይሆናል።
#worldcup #fifaworldcup #argentina #caboverde #lionelmessi #football #sports
*********
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ32 ሀገራት ጥሎ ማለፍ መርኃ ግብር አፍሪካዊቷን ደሴት ኬፕቨርዴን የገጠመችው አርጀንቲና 3 ለ 2 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ቀጣዩን የ16 ሀገራት ጥሎ ማለፍ ዙር ተቀላቅላለች።
ሊዮኔል ሜሲ ለአርጀንቲና ዳንኤል ዱዋርቴ ደግሞ ለኬፕቨርዴ 1 አቻ በተጠናቀቀው መደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ግቦቹን ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው።
አሸናፊውን ለመለየት በተጨመሩት 90 ደቂቃዎች፤ የአርጀንቲናን የማሸነፊያ ግቦች ያስቆጠሩት ሊሳንድሮ ማርቲኔዝ እና ዲኔይ ቦርገስ(በራሱ መረብ ላይ) ሲሆን የኬፕ ቨሮዴን ግብ ሲድኒ ካብራል ከመረብ አሳርፏል።
ሻምፒዮኗ አርጀንቲና በቀጣዩ የጥሎ ማለፍ መርኃ ግብር ግብፅን የምትገጥም ይሆናል።
#worldcup #fifaworldcup #argentina #caboverde #lionelmessi #football #sports
Comments