1 month ago
Fly with Ethiopian Airlines to the World Cup and seize an incredible 15% savings on your next adventure! Experience the thrill of the world’s biggest football celebration while enjoying our exclusive offer. Don’t miss out on this limited-time offer.
#flyethiopian #worldcup2026
#flyethiopian #worldcup2026
1 month ago
Fly with Ethiopian Airlines to the World Cup and seize an incredible 15% savings on your next adventure! Experience the thrill of the world’s biggest football celebration while enjoying our exclusive offer. Don’t miss out on this limited-time offer.
#flyethiopian #worldcup2026
#flyethiopian #worldcup2026
1 month ago
Fly with Ethiopian Airlines to the World Cup and seize an incredible 15% savings on your next adventure! Experience the thrill of the world’s biggest football celebration while enjoying our exclusive offer. Don’t miss out on this limited-time offer.
#flyethiopian #worldcup2026
#flyethiopian #worldcup2026
1 month ago
"ተጨዋቾቹ ይምጡ፤ አብዮታዊ ዘቡ ግን እዛው ይቆይ"
#ethiopia | አሜሪካ በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ላይ ለሚሳተፈው የኢራን ብሔራዊ ቡድን ግልጽ የሆነ የ"ይለፍ" እና የ"ክልከላ" መስመር አስመረቀች። የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርክ ሩቢዮ በሰጡት መግለጫ፣ ዋሽንግተን የኢራን ተጨዋቾች በዓለም ዋንጫው ላይ እንዳይሳተፉ የማገድ ፍላጎት እንደሌላት አስታውቀዋል።
ሚኒስትር ሩቢዮ እንደገለጹት፣ የአሜሪካ ዋነኛ ስጋት ተጨዋቾቹ ሳይሆኑ ከኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ጋር ግንኙነት ያላቸው ግለሰቦች ናቸው። "የእኛ ችግር ስፖርተኞቹ አይደሉም" ያሉት ሚኒስትሩ፣ የአብዮታዊ ዘቡ አባላት እንደ ጋዜጠኛ፣ አሰልጣኝ ወይም የቡድን አባላት ተመስለው ወደ አሜሪካ መግባት እንደማይችሉ በጠንካራ ቃላት አስገንዝበዋል።
ከሚኒስትሩ ጎን የነበሩት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ አስተዳደራቸው በፖለቲካዊ ምክንያቶች በስፖርተኞቹ ላይ ጫና ማሳደር እንደማይፈልግ ገልጸዋል። ይህ መግለጫ ባለፈው የካቲት 28 በአሜሪካ እና እስራኤል የጋራ ጥቃት የተከፈተባት ኢራን፣ በዓለም ዋንጫው ላይ ያላት ተሳትፎ አጠራጣሪ በሆነበት ወቅት የተሰጠ ነው።
ምንም እንኳን በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ውጥረት ከፍተኛ ቢሆንም፣ የኢራን መንግስት ቃል አቀባይ ፋቴሜህ ሞሃጀራኒ ሀገራቸው ለውድድሩ አስፈላጊውን ዝግጅት ማጠናቀቋን አረጋግጠዋል። የኢራን ወጣቶች እና ስፖርት ሚኒስቴር ቡድኑ በውድድሩ ላይ እንዲሳተፍ አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ መሆኑ ተገልጿል።
ኢራን በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ በምድብ ጨዋታዎቿ ከሚከተሉት ሀገራት ጋር ትፋለማለች፦
ቤልጂየም
ግብፅ
ኒውዚላንድ
ውድድሩ በፈረንጆቹ ሰኔ 11 የሚጀምር ሲሆን፣ የኢራን ብሔራዊ ቡድን አባላት ወደ አሜሪካ በሚያደርጉት ጉዞ ላይ የቪዛ እና የደህንነት ምርመራው ጥብቅ እንደሚሆን ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#worldcup2026 #usa #iran #football #internationalrelations #marcorubio #fifa
#ethiopia | አሜሪካ በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ላይ ለሚሳተፈው የኢራን ብሔራዊ ቡድን ግልጽ የሆነ የ"ይለፍ" እና የ"ክልከላ" መስመር አስመረቀች። የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርክ ሩቢዮ በሰጡት መግለጫ፣ ዋሽንግተን የኢራን ተጨዋቾች በዓለም ዋንጫው ላይ እንዳይሳተፉ የማገድ ፍላጎት እንደሌላት አስታውቀዋል።
ሚኒስትር ሩቢዮ እንደገለጹት፣ የአሜሪካ ዋነኛ ስጋት ተጨዋቾቹ ሳይሆኑ ከኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ጋር ግንኙነት ያላቸው ግለሰቦች ናቸው። "የእኛ ችግር ስፖርተኞቹ አይደሉም" ያሉት ሚኒስትሩ፣ የአብዮታዊ ዘቡ አባላት እንደ ጋዜጠኛ፣ አሰልጣኝ ወይም የቡድን አባላት ተመስለው ወደ አሜሪካ መግባት እንደማይችሉ በጠንካራ ቃላት አስገንዝበዋል።
ከሚኒስትሩ ጎን የነበሩት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ አስተዳደራቸው በፖለቲካዊ ምክንያቶች በስፖርተኞቹ ላይ ጫና ማሳደር እንደማይፈልግ ገልጸዋል። ይህ መግለጫ ባለፈው የካቲት 28 በአሜሪካ እና እስራኤል የጋራ ጥቃት የተከፈተባት ኢራን፣ በዓለም ዋንጫው ላይ ያላት ተሳትፎ አጠራጣሪ በሆነበት ወቅት የተሰጠ ነው።
ምንም እንኳን በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ውጥረት ከፍተኛ ቢሆንም፣ የኢራን መንግስት ቃል አቀባይ ፋቴሜህ ሞሃጀራኒ ሀገራቸው ለውድድሩ አስፈላጊውን ዝግጅት ማጠናቀቋን አረጋግጠዋል። የኢራን ወጣቶች እና ስፖርት ሚኒስቴር ቡድኑ በውድድሩ ላይ እንዲሳተፍ አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ መሆኑ ተገልጿል።
ኢራን በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ በምድብ ጨዋታዎቿ ከሚከተሉት ሀገራት ጋር ትፋለማለች፦
ቤልጂየም
ግብፅ
ኒውዚላንድ
ውድድሩ በፈረንጆቹ ሰኔ 11 የሚጀምር ሲሆን፣ የኢራን ብሔራዊ ቡድን አባላት ወደ አሜሪካ በሚያደርጉት ጉዞ ላይ የቪዛ እና የደህንነት ምርመራው ጥብቅ እንደሚሆን ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#worldcup2026 #usa #iran #football #internationalrelations #marcorubio #fifa
1 month ago
''ኢራንን አንተካም!" — ጣልያን
#ethiopia | ፊፋ ኢራንን ከዓለም ዋንጫ አስወግዶ በምትኳ ጣልያንን እንዲያስገባ ያቀረቡት ጥያቄ በራሷ በጣልያን መንግሥትና በስፖርት አመራሮቹ ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጠመው።
የጣልያን ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት ሉቺያኖ ቦንፊግልዮ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ጠንከር ያለ ምላሽ፣ ጣልያን በሜዳ ላይ ባላሳየችው ውጤት በፖለቲካዊ መንገድ ወደ ዓለም ዋንጫ እንድትገባ የቀረበውን ሐሳብ እንደማይቀበሉት ገልጸዋል።
"ይሄ ከተፈጠረ እንደ ስድብ ነው የምወስደው" ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ ማንኛውም ቡድን ለዓለም ዋንጫ ማለፍ ያለበት በችሎታውና በጠንካራ ሥራው መሆን እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።
የሀገሪቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችም የኦሎምፒክ ኮሚቴውን አቋም ተጋርተዋል፦
"ይሄ አስፈላጊ አይደለም፤ ሜዳ ላይ ነው ማለፍ ያለብን" በማለት በጓሮ በር ወደ ውድድሩ የመግባት ፍላጎት እንደሌላቸው አስታውቀዋል።
የኢኮኖሚ ሚኒስትር ጂዮርጌቲ፦ ዜናው በግላቸው እንዳሳፈራቸው ገልጸው፣ "በዛ መንገድ ከሄድን አፍራለሁ" ሲሉ የሐሳቡን አሳፋሪነት ገልጸዋል።
ምንም እንኳን የጣልያን ብሔራዊ ቡድን ለ2026ቱ ዓለም ዋንጫ ባለማለፉ ደጋፊዎቿ ቢያዝኑም፣ የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ግን ከውጤት ይልቅ ለስፖርታዊ ጨዋነትና ለፍትሐዊ ውድድር ቅድሚያ በመስጠት ዓለም አቀፍ አድናቆትን እያገኙ ይገኛሉ።
ጣልያን "በችሎታችን ካላለፍን በሌላው ስንብት አንገባም" የሚል ጠንካራ መልዕክት ለዓለም አስተላልፋለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#italy #fifa #worldcup2026 #iran #footballnews #sportsmanship #fairplay #azzurri #lucianobonfiglio #andreaabodi #worldcupupdate
#ethiopia | ፊፋ ኢራንን ከዓለም ዋንጫ አስወግዶ በምትኳ ጣልያንን እንዲያስገባ ያቀረቡት ጥያቄ በራሷ በጣልያን መንግሥትና በስፖርት አመራሮቹ ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጠመው።
የጣልያን ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት ሉቺያኖ ቦንፊግልዮ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ጠንከር ያለ ምላሽ፣ ጣልያን በሜዳ ላይ ባላሳየችው ውጤት በፖለቲካዊ መንገድ ወደ ዓለም ዋንጫ እንድትገባ የቀረበውን ሐሳብ እንደማይቀበሉት ገልጸዋል።
"ይሄ ከተፈጠረ እንደ ስድብ ነው የምወስደው" ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ ማንኛውም ቡድን ለዓለም ዋንጫ ማለፍ ያለበት በችሎታውና በጠንካራ ሥራው መሆን እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።
የሀገሪቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችም የኦሎምፒክ ኮሚቴውን አቋም ተጋርተዋል፦
"ይሄ አስፈላጊ አይደለም፤ ሜዳ ላይ ነው ማለፍ ያለብን" በማለት በጓሮ በር ወደ ውድድሩ የመግባት ፍላጎት እንደሌላቸው አስታውቀዋል።
የኢኮኖሚ ሚኒስትር ጂዮርጌቲ፦ ዜናው በግላቸው እንዳሳፈራቸው ገልጸው፣ "በዛ መንገድ ከሄድን አፍራለሁ" ሲሉ የሐሳቡን አሳፋሪነት ገልጸዋል።
ምንም እንኳን የጣልያን ብሔራዊ ቡድን ለ2026ቱ ዓለም ዋንጫ ባለማለፉ ደጋፊዎቿ ቢያዝኑም፣ የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ግን ከውጤት ይልቅ ለስፖርታዊ ጨዋነትና ለፍትሐዊ ውድድር ቅድሚያ በመስጠት ዓለም አቀፍ አድናቆትን እያገኙ ይገኛሉ።
ጣልያን "በችሎታችን ካላለፍን በሌላው ስንብት አንገባም" የሚል ጠንካራ መልዕክት ለዓለም አስተላልፋለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#italy #fifa #worldcup2026 #iran #footballnews #sportsmanship #fairplay #azzurri #lucianobonfiglio #andreaabodi #worldcupupdate
2 months ago
🇮🇹 የጣልያን እግር ኳስ መርዶ
አዙሪዎቹ ለ16 ዓመታት ከዓለም ዋንጫ ተለዩ
#ethiopia | በዓለም እግር ኳስ ታሪክ ስሟ በወርቅ የተጻፈው ጣልያን፣ ዛሬ የቀራት የትዝታ ማዕበል ብቻ ሆኗል።
እነ ማልዲኒ፣ ፒርሎ፣ ቡፎንና ባጂዮን ያፈራው የጣልያን ማህፀን፣ ዛሬ በታሪኩ አስከፊ የሚባለውን የውድቀት ዘመን እያሳለፈ ይገኛል።
ጣልያን ከ2018 እና ከ2022 በመቀጠል፣ አሁን ደግሞ ከ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ውጪ ሆናለች። ይህም ለአንድ ትልቅ ሀገር ለ16 ዓመታት (አራት ተከታታይ የዓለም ዋንጫዎች) ከመድረኩ መራቅ በታሪክ የመጀመሪያዋ ያደርጋታል።
በትናንትናው ወሳኝ የጥሎ ማለፍ ፍልሚያ፣ በፊፋ 71ኛ ደረጃ ላይ በምትገኘው ቦስኒያ ሄርዞጎቪና በመለያ ምት 4 ለ 1 ተሸንፋ ተሰናብታለች።
ሞይስ ኬን ጣልያንን መሪ ቢያደርግም፣ የባስቶኒ ቀይ ካርድና የቦስኒያ የአቻነት ግብ ጨዋታውን ወደ መለያ ምት ወስዶታል።
የጣልያን የመጨረሻው የዓለም ዋንጫ ትዝታ በ2014 ብራዚል ላይ ሱዋሬዝ ቺሊኒን የነከሰበትና ጣልያን በኡራጓይ ተሸንፋ ከምድብ የቀረችበት መራራ ምሽት ሆኖ ቀርቷል።
ከ2006ቱ ድል በኋላ ጣልያን በዓለም ዋንጫ መድረክ አንድም ስኬታማ ጉዞ ማድረግ አልቻለችም።
ጂናሮ ጋቱሶ የሉቺያኖ ስፓሌቲን መንበር ተረክቦ ሊታደጋት ቢሞክርም፣ እሱም እንደ ማንቺኒና ኮንቴ ሁሉ የአዙሪዎቹን ክብር ሳይመልስ አንገቱን ደፍቶ ወጥቷል።
ኩራሳኦና ጆርዳን ወደ አሜሪካ ሲያመሩ፣ አዙሪዎቹ ግን አሁንም ቤታቸው እንዲቀሩ ተፈርዶባቸዋል።
#getu #italyfootball #azzurri #worldcup2026 #gattuso #footballnews #worldcupqualifiers #italyvsbosnia #footballhistory #ጣልያን #እግርኳስ #ዓለምዋንጫ #መርዶ #ትዝታ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
አዙሪዎቹ ለ16 ዓመታት ከዓለም ዋንጫ ተለዩ
#ethiopia | በዓለም እግር ኳስ ታሪክ ስሟ በወርቅ የተጻፈው ጣልያን፣ ዛሬ የቀራት የትዝታ ማዕበል ብቻ ሆኗል።
እነ ማልዲኒ፣ ፒርሎ፣ ቡፎንና ባጂዮን ያፈራው የጣልያን ማህፀን፣ ዛሬ በታሪኩ አስከፊ የሚባለውን የውድቀት ዘመን እያሳለፈ ይገኛል።
ጣልያን ከ2018 እና ከ2022 በመቀጠል፣ አሁን ደግሞ ከ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ውጪ ሆናለች። ይህም ለአንድ ትልቅ ሀገር ለ16 ዓመታት (አራት ተከታታይ የዓለም ዋንጫዎች) ከመድረኩ መራቅ በታሪክ የመጀመሪያዋ ያደርጋታል።
በትናንትናው ወሳኝ የጥሎ ማለፍ ፍልሚያ፣ በፊፋ 71ኛ ደረጃ ላይ በምትገኘው ቦስኒያ ሄርዞጎቪና በመለያ ምት 4 ለ 1 ተሸንፋ ተሰናብታለች።
ሞይስ ኬን ጣልያንን መሪ ቢያደርግም፣ የባስቶኒ ቀይ ካርድና የቦስኒያ የአቻነት ግብ ጨዋታውን ወደ መለያ ምት ወስዶታል።
የጣልያን የመጨረሻው የዓለም ዋንጫ ትዝታ በ2014 ብራዚል ላይ ሱዋሬዝ ቺሊኒን የነከሰበትና ጣልያን በኡራጓይ ተሸንፋ ከምድብ የቀረችበት መራራ ምሽት ሆኖ ቀርቷል።
ከ2006ቱ ድል በኋላ ጣልያን በዓለም ዋንጫ መድረክ አንድም ስኬታማ ጉዞ ማድረግ አልቻለችም።
ጂናሮ ጋቱሶ የሉቺያኖ ስፓሌቲን መንበር ተረክቦ ሊታደጋት ቢሞክርም፣ እሱም እንደ ማንቺኒና ኮንቴ ሁሉ የአዙሪዎቹን ክብር ሳይመልስ አንገቱን ደፍቶ ወጥቷል።
ኩራሳኦና ጆርዳን ወደ አሜሪካ ሲያመሩ፣ አዙሪዎቹ ግን አሁንም ቤታቸው እንዲቀሩ ተፈርዶባቸዋል።
#getu #italyfootball #azzurri #worldcup2026 #gattuso #footballnews #worldcupqualifiers #italyvsbosnia #footballhistory #ጣልያን #እግርኳስ #ዓለምዋንጫ #መርዶ #ትዝታ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
2 months ago
"እኔ አሰልጣኝ እንጂ የጽዳት ሰራተኛ አይደለሁም" ማውሪሲዮ ፖቸቲኖ
#ethiopia | የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ማውሪሲዮ ፖቸቲኖ፣ ስለ 2026ቱ ዓለም ዋንጫ ዝግጅት እና ወደ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ስለመመለስ ያላቸውን ፍላጎት በተመለከተ በሰጡ አስተያየት መነጋገሪያ ሆነዋል። አርጀንቲናዊው አሰልጣኝ በተለይ "እኔ አሰልጣኝ እንጂ የጽዳት ሰራተኛ አይደለሁም" በማለት የሰጡት ምላሽ በብዙዎች ዘንድ ትኩረት ስቧል።
የ54 ዓመቱ ፖቸቲኖ እንደገለጹት፣ የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን ለ2026ቱ ዓለም ዋንጫ ራሱን በከፍተኛ ሁኔታ እያዘጋጀ ይገኛል። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን ጨምሮ መላው የአሜሪካ ሕዝብ ከቡድኑ ትልቅ ውጤት እንደሚጠብቅ እንደሚገነዘቡም ተናግረዋል። አሰልጣኙ አክለውም ለብሔራዊ ቡድኑ የሚመጥኑ ተጫዋቾችን ለመምረጥ አሁንም በቂ ጊዜ እንዳለ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
ፖቸቲኖ በአሜሪካ ያለውን ቆይታ ቢወዱትም፣ የለንደን እና የእንግሊዝ እግር ኳስ ክርክርና ፉክክር እጅግ እንደናፈቃቸው አልሸሸጉም። "ከዓለም ዋንጫው በኋላ ወደ ለንደን ብመለስ ደስ ይለኛል፤ እኔ አሰልጣኝ እንጂ የጽዳት ሰራተኛ አይደለሁም፣ ስለዚህ ነጻነቴን እፈልጋለሁ" በማለት የወደፊት እቅዳቸውን አመልክተዋል።
ፖቸቲኖ ከዓለም ዋንጫው በኋላ ወደ እንግሊዝ የመመለስ ፍላጎት እንዳላቸው መነገሩን ተከትሎ፣ የቀድሞ ክለባቸው ቶተንሃም በድጋሚ ሊቀጥራቸው እንደሚችል ጭምጭምታዎች እየተሰሙ ነው። በተለይም ቶተንሃም በሊጉ የመቆየት እድሉ ካልተመናመነ፣ አመራሮቹ አርጀንቲናዊውን አሰልጣኝ በድጋሚ ወደ ክለቡ ለመመለስ ፍላጎት እንዳላቸው እየተገለጸ ይገኛል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ብስራትኤፍ ኤም #pochettino #usmnt #worldcup2026 #premier League #tottenham #london #footballnews #mauriciopochettino
#ethiopia | የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ማውሪሲዮ ፖቸቲኖ፣ ስለ 2026ቱ ዓለም ዋንጫ ዝግጅት እና ወደ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ስለመመለስ ያላቸውን ፍላጎት በተመለከተ በሰጡ አስተያየት መነጋገሪያ ሆነዋል። አርጀንቲናዊው አሰልጣኝ በተለይ "እኔ አሰልጣኝ እንጂ የጽዳት ሰራተኛ አይደለሁም" በማለት የሰጡት ምላሽ በብዙዎች ዘንድ ትኩረት ስቧል።
የ54 ዓመቱ ፖቸቲኖ እንደገለጹት፣ የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን ለ2026ቱ ዓለም ዋንጫ ራሱን በከፍተኛ ሁኔታ እያዘጋጀ ይገኛል። ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን ጨምሮ መላው የአሜሪካ ሕዝብ ከቡድኑ ትልቅ ውጤት እንደሚጠብቅ እንደሚገነዘቡም ተናግረዋል። አሰልጣኙ አክለውም ለብሔራዊ ቡድኑ የሚመጥኑ ተጫዋቾችን ለመምረጥ አሁንም በቂ ጊዜ እንዳለ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
ፖቸቲኖ በአሜሪካ ያለውን ቆይታ ቢወዱትም፣ የለንደን እና የእንግሊዝ እግር ኳስ ክርክርና ፉክክር እጅግ እንደናፈቃቸው አልሸሸጉም። "ከዓለም ዋንጫው በኋላ ወደ ለንደን ብመለስ ደስ ይለኛል፤ እኔ አሰልጣኝ እንጂ የጽዳት ሰራተኛ አይደለሁም፣ ስለዚህ ነጻነቴን እፈልጋለሁ" በማለት የወደፊት እቅዳቸውን አመልክተዋል።
ፖቸቲኖ ከዓለም ዋንጫው በኋላ ወደ እንግሊዝ የመመለስ ፍላጎት እንዳላቸው መነገሩን ተከትሎ፣ የቀድሞ ክለባቸው ቶተንሃም በድጋሚ ሊቀጥራቸው እንደሚችል ጭምጭምታዎች እየተሰሙ ነው። በተለይም ቶተንሃም በሊጉ የመቆየት እድሉ ካልተመናመነ፣ አመራሮቹ አርጀንቲናዊውን አሰልጣኝ በድጋሚ ወደ ክለቡ ለመመለስ ፍላጎት እንዳላቸው እየተገለጸ ይገኛል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ብስራትኤፍ ኤም #pochettino #usmnt #worldcup2026 #premier League #tottenham #london #footballnews #mauriciopochettino
3 months ago
ኢራን የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎቿን ከአሜሪካ ወደ ሜክሲኮ ለማዛወር ከፊፋ ጋር እየተደራደረች ነው
#ethiopia | በፖለቲካዊ ውጥረትና በደህንነት ስጋት ምክንያት የኢራን እግር ኳስ ማህበር የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎቹን በአሜሪካ ምትክ በሜክሲኮ ለማከናወን ጥያቄ ማቅረቡ ተሰማ። የኢራን እግር ኳስ ማህበር ፕሬዝዳንት መህዲ ታጅ እንደገለጹት፣ የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ለኢራን ብሔራዊ ቡድን በቂ የደህንነት ዋስትና ለመስጠት ፈቃደኛ ባለመሆኑ ቡድኑ ወደ አሜሪካ የመጓዝ ዕቅድ የለውም።
ፕሬዝዳንቱ በኤክስ (X) ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ "ትራምፕ ለቡድናችን ደህንነት ማረጋገጫ ባልሰጡበት ሁኔታ ወደ አሜሪካ መጓዝ አንችልም" ያሉ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ጨዋታዎቹን ወደ ሜክሲኮ ለማዛወር ከዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) ጋር ንግግር እየተደረገ መሆኑን ይፋ አድርገዋል።
ይህ ውሳኔ የተሰማው የኢራን ስፖርት ሚኒስትር አሜሪካና እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት ከሰነዘሩ በኋላ በውድድሩ ላይ መሳተፍ አጠራጣሪ መሆኑን በገለጹ ማግስት ነው።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በበኩላቸው ኢራን መሳተፍ እንደምትችል ቢገልጹም፣ "ለራሳቸው ደህንነት ሲሉ ባይመጡ ይሻላል" የሚል ይዘት ያለው ማስጠንቀቂያ መስጠታቸው ይታወሳል።
እንደ መጀመሪያው መርሃ ግብር ኢራን ሁለት የምድብ ጨዋታዎቿን በሎስ አንጀለስ፣ ቀሪውን አንድ ጨዋታ ደግሞ በሲያትል ለማከናወን ተመድባ ነበር። አሁን በቀረበው ጥያቄ ላይ ፊፋ የሚሰጠው ምላሽ በጉጉት እየተጠበቀ ይገኛል::
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #worldcup2026 #fifa #iranfootball #mexico2026 #sportsnews #breakingnews #footballpolitics
#ethiopia | በፖለቲካዊ ውጥረትና በደህንነት ስጋት ምክንያት የኢራን እግር ኳስ ማህበር የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎቹን በአሜሪካ ምትክ በሜክሲኮ ለማከናወን ጥያቄ ማቅረቡ ተሰማ። የኢራን እግር ኳስ ማህበር ፕሬዝዳንት መህዲ ታጅ እንደገለጹት፣ የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ለኢራን ብሔራዊ ቡድን በቂ የደህንነት ዋስትና ለመስጠት ፈቃደኛ ባለመሆኑ ቡድኑ ወደ አሜሪካ የመጓዝ ዕቅድ የለውም።
ፕሬዝዳንቱ በኤክስ (X) ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ "ትራምፕ ለቡድናችን ደህንነት ማረጋገጫ ባልሰጡበት ሁኔታ ወደ አሜሪካ መጓዝ አንችልም" ያሉ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ጨዋታዎቹን ወደ ሜክሲኮ ለማዛወር ከዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) ጋር ንግግር እየተደረገ መሆኑን ይፋ አድርገዋል።
ይህ ውሳኔ የተሰማው የኢራን ስፖርት ሚኒስትር አሜሪካና እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት ከሰነዘሩ በኋላ በውድድሩ ላይ መሳተፍ አጠራጣሪ መሆኑን በገለጹ ማግስት ነው።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በበኩላቸው ኢራን መሳተፍ እንደምትችል ቢገልጹም፣ "ለራሳቸው ደህንነት ሲሉ ባይመጡ ይሻላል" የሚል ይዘት ያለው ማስጠንቀቂያ መስጠታቸው ይታወሳል።
እንደ መጀመሪያው መርሃ ግብር ኢራን ሁለት የምድብ ጨዋታዎቿን በሎስ አንጀለስ፣ ቀሪውን አንድ ጨዋታ ደግሞ በሲያትል ለማከናወን ተመድባ ነበር። አሁን በቀረበው ጥያቄ ላይ ፊፋ የሚሰጠው ምላሽ በጉጉት እየተጠበቀ ይገኛል::
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #worldcup2026 #fifa #iranfootball #mexico2026 #sportsnews #breakingnews #footballpolitics
3 months ago
ኔይማር ጁኒየር ወደ ብራዚል ብሔራዊ ቡድን ሊመለስ ነው!
#ethiopia | የብራዚል እግር ኳስ ደጋፊዎችን ያስፈነጠዘ ዜና ከሳምባ ምድር ተሰምቷል። ከ2023 ጀምሮ በጉዳትና በተለያዩ ምክንያቶች ከብሔራዊ ቡድኑ ርቆ የቆየው ድንቅ ተጫዋች ኔይማር ጁኒየር፣ በካርሎ አንቼሎቲ ለሚመራው የብራዚል ስብስብ ዳግም ጥሪ ሊደረግለት መሆኑ ተዘግቧል።
እንደ መረጃዎች ከሆነ፣ የኔይማር ዋና እቅድ በ2026 በሚካሄደው የዓለም ዋንጫ ላይ ሀገሩን አገልግሎ ከእግር ኳስ ዓለም በክብር መሰናበት ነው። ለዚህም ይረዳው ዘንድ ብራዚል ከፈረንሳይ እና ከክሮሺያ ጋር ለምታደርጋቸው ታላላቅ ጨዋታዎች በስብስቡ ውስጥ እንደሚካተት ይጠበቃል።
አሰልጣኝ ካርሎ አንቼሎቲ የኔይማርን ወቅታዊ አቋም ለመገምገም በሳንቶስ ቤት የሚያደርገውን ጨዋታ በስታዲየም ተገኝተው እንደሚከታተሉ የተነገረ ሲሆን፣ ሙሉው የብሔራዊ ቡድን ስብስብም በመጪው ሰኞ ይፋ ይደረጋል ተብሎ በጉጉት እየተጠበቀ ይገኛል።
የብራዚል ቁርጥ ቀን ልጅ ወደ ሜዳ መመለስ ለካናሪዎቹ አዲስ መነሳሳትን ይፈጥራል ተብሎ ታምኖበታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #neymarjr #brazil #selecao #ancelotti #worldcup2026 #footballnews #sambafootball #ኔይማር #ብራዚል #እግርኳስ
#ethiopia | የብራዚል እግር ኳስ ደጋፊዎችን ያስፈነጠዘ ዜና ከሳምባ ምድር ተሰምቷል። ከ2023 ጀምሮ በጉዳትና በተለያዩ ምክንያቶች ከብሔራዊ ቡድኑ ርቆ የቆየው ድንቅ ተጫዋች ኔይማር ጁኒየር፣ በካርሎ አንቼሎቲ ለሚመራው የብራዚል ስብስብ ዳግም ጥሪ ሊደረግለት መሆኑ ተዘግቧል።
እንደ መረጃዎች ከሆነ፣ የኔይማር ዋና እቅድ በ2026 በሚካሄደው የዓለም ዋንጫ ላይ ሀገሩን አገልግሎ ከእግር ኳስ ዓለም በክብር መሰናበት ነው። ለዚህም ይረዳው ዘንድ ብራዚል ከፈረንሳይ እና ከክሮሺያ ጋር ለምታደርጋቸው ታላላቅ ጨዋታዎች በስብስቡ ውስጥ እንደሚካተት ይጠበቃል።
አሰልጣኝ ካርሎ አንቼሎቲ የኔይማርን ወቅታዊ አቋም ለመገምገም በሳንቶስ ቤት የሚያደርገውን ጨዋታ በስታዲየም ተገኝተው እንደሚከታተሉ የተነገረ ሲሆን፣ ሙሉው የብሔራዊ ቡድን ስብስብም በመጪው ሰኞ ይፋ ይደረጋል ተብሎ በጉጉት እየተጠበቀ ይገኛል።
የብራዚል ቁርጥ ቀን ልጅ ወደ ሜዳ መመለስ ለካናሪዎቹ አዲስ መነሳሳትን ይፈጥራል ተብሎ ታምኖበታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #neymarjr #brazil #selecao #ancelotti #worldcup2026 #footballnews #sambafootball #ኔይማር #ብራዚል #እግርኳስ
Sponsored by
Surafel
4 months ago
ሜክሲኮ ለ2026ቱ የዓለም ዋንጫ "ሮቦት ውሾችን" በፀጥታ ጥበቃ ልታሰማራ ነው
#ethiopia | በቀጣዩ የ2026 የዓለም ዋንጫ አስተናጋጅ ከሆኑት አገራት አንዷ የሆነችው ሜክሲኮ፣ የውድድሩን የፀጥታ ሁኔታ ይበልጥ ለማጠናከር በቴክኖሎጂ የታገዙ "ሮቦት ውሾችን" ልታሰማራ መሆኑን አስታውቃለች።
እነዚህ አራት እግሮች ያሏቸው የሮቦት እንሰሳት፣ በተለይም የፖሊስ አባላት ወደማይደርሱባቸው ወይም አደገኛ ወደሆኑ አካባቢዎች ቀድመው በመግባት የቪዲዮ መረጃዎችን በቀጥታ ለቁጥጥር ማዕከሉ እንዲልኩ ተደርገው የተሰሩ ናቸው።
የሮቦት ውሾቹ ዋና ዋና ባህሪያት፦
* ሁለገብ እንቅስቃሴ፦ ባልተስተካከሉ መሬቶች እና አስቸጋሪ በሆኑ ስፍራዎች ላይ በቀላሉ የመንቀሳቀስ ብቃት አላቸው።
* ዘመናዊ ካሜራዎች፦ ከፍተኛ ጥራት ያላቸው ካሜራዎች የተገጠሙላቸው ሲሆን፣ የፀጥታ አካላት ስጋቶችን በሩቅ ሆነው እንዲቃኙ ይረዳሉ።
* ጥንካሬ፦ በማንኛውም የአየር ንብረትና መልክዓ ምድር ውስጥ ለመስራት የሚያስችል ጠንካራ ቁሳቁስ ተገጥሞላቸዋል።
ሜክሲኮ ይህንን ቴክኖሎጂ የምትጠቀመው የሰው ኃይል ሊገጥመው የሚችለውን አደጋ ለመቀነስ እና ለዓለም ዋንጫው የሚመጡ እንግዶችን ደህንነት በላቀ ሁኔታ ለመጠበቅ እንደሆነ የሀገሪቱ ባለስልጣናት ገልጸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #mexico2026 #worldcup2026 #robotdogs #techsecurity #fifaworldcup #mexicosafety #innovation #አለምዋንጫ #ሜክ .ሲኮ #ቴክኖሎጂ
#ethiopia | በቀጣዩ የ2026 የዓለም ዋንጫ አስተናጋጅ ከሆኑት አገራት አንዷ የሆነችው ሜክሲኮ፣ የውድድሩን የፀጥታ ሁኔታ ይበልጥ ለማጠናከር በቴክኖሎጂ የታገዙ "ሮቦት ውሾችን" ልታሰማራ መሆኑን አስታውቃለች።
እነዚህ አራት እግሮች ያሏቸው የሮቦት እንሰሳት፣ በተለይም የፖሊስ አባላት ወደማይደርሱባቸው ወይም አደገኛ ወደሆኑ አካባቢዎች ቀድመው በመግባት የቪዲዮ መረጃዎችን በቀጥታ ለቁጥጥር ማዕከሉ እንዲልኩ ተደርገው የተሰሩ ናቸው።
የሮቦት ውሾቹ ዋና ዋና ባህሪያት፦
* ሁለገብ እንቅስቃሴ፦ ባልተስተካከሉ መሬቶች እና አስቸጋሪ በሆኑ ስፍራዎች ላይ በቀላሉ የመንቀሳቀስ ብቃት አላቸው።
* ዘመናዊ ካሜራዎች፦ ከፍተኛ ጥራት ያላቸው ካሜራዎች የተገጠሙላቸው ሲሆን፣ የፀጥታ አካላት ስጋቶችን በሩቅ ሆነው እንዲቃኙ ይረዳሉ።
* ጥንካሬ፦ በማንኛውም የአየር ንብረትና መልክዓ ምድር ውስጥ ለመስራት የሚያስችል ጠንካራ ቁሳቁስ ተገጥሞላቸዋል።
ሜክሲኮ ይህንን ቴክኖሎጂ የምትጠቀመው የሰው ኃይል ሊገጥመው የሚችለውን አደጋ ለመቀነስ እና ለዓለም ዋንጫው የሚመጡ እንግዶችን ደህንነት በላቀ ሁኔታ ለመጠበቅ እንደሆነ የሀገሪቱ ባለስልጣናት ገልጸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #mexico2026 #worldcup2026 #robotdogs #techsecurity #fifaworldcup #mexicosafety #innovation #አለምዋንጫ #ሜክ .ሲኮ #ቴክኖሎጂ