1 hr. ago
በወዙና በደሙ ኢትዮጵያን ያፀና:- የጀግንነት አምባ
*****************
"የኩሩ ህዝቦች መኖሪያ የህብረ ብሄር ቡቃያ፣ የሰላም ተምሳሌት ዓርማ የቀለሞች ህብር ኢትዮጵያ!"
ይህ የክብርና የሉዓላዊነት ብሔራዊ መዝሙር ስንኝ፣ ተራ የቃላት ድርደራ ሳይሆን የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የታሪክ፣ የፅናትና የማንነት መልክ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ የህሊና ብሩህ መስታወት ነው።
የመከላከያ ሰራዊቱ የማይበገር ጥንካሬ የሚመነጨው በልቡ ውስጥ ከነደደው የማያልቅ የሀገር ፍቅር እሳትና በውስጡ ከሰረጸው ጠንካራ ወታደራዊ ዲሲፕሊን ነው።
ሰራዊቱ ሀገርን በመጠበቅና ዳር ድንበርን በማስከበር ረገድ በዓለም መድረክ ላይ ተወዳዳሪ የሌለው፣ የታሪክን ታላላቅ ፈተናዎች በትከሻው የተሸከመ የሰላም ጽኑ ዐለት ነው።
የጦር ሜዳ ውሎው ስልታዊና አስፈሪ፣ የሰላም ጊዜው ደግሞ ለህዝብ አጋዥና መከታ ነው።
ይህ ሰራዊት የሀገር ውስጥ ጋሻ ብቻ አይደለም፤ ይልቁንም በአህጉሪቱና በዓለም አቀፍ ደረጃ በተሰማራባቸው የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ሁሉ ሰብአዊነትንና የህግ የበላይነትን ያስቀደመ፣ የሌሎችን ህዝቦች ነፃነትና ክብር እንደ ራሱ አድርጎ የጠበቀ እጅግ ተወዳጅና የተከበረ ኃይል ነው። በሊቤሪያ፣ በሩዋንዳ፣ በዳርፉርና በሶማሊያ በረሃዎች ውስጥ የፈሰሰው ላቡና ደሙ፣ የኢትዮጵያን ስም በዓለም የክብር መዝገብ ላይ በደመቀ ቀለም አስፍሮታል።
የሰራዊቱ አባላት ሌሎችን ማክበርና ለተቸገሩት መድረስ ከአባቶቻቸው የወረሱት የደም እሴት በመሆኑ, በተሰማራበት አህጉርና ቀጠና ሁሉ በህዝቦች ልብ ውስጥ የማይጠፋ የፍቅርና የታማኝነት አሻራ ጥሏል። በዚህም የተነሳ በአፍሪካ ምድር ህዝቦች ዘንድ እጅግ ተወዳጅ ነው።
ከዚህም በላይ፣ ይህ የጀግኖች ስብስብ ጠመንጃ ብቻ ሳይሆን አካፋና ዶማም መያዝ የሚችል የልማት ግንባር ቀደም ኃይል ነው። በኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ ውስጥ፣ በታላላቅ የልማት ፕሮጀክቶች፣ በአረንጓዴ አሻራ፣ በታላቁ ህዳሴ ግድብና በህዝባዊ አገልግሎቶች ላይ ቀዳሚ በመሆን ድህነትን የሚዋጋ፣ ህዝቡን ከረሃብና ከችግር የሚታደግ የላብ አርበኛ ነው።
ሰላምን በደሙ፣ ልማትንና ብልጽግናን ደግሞ በላቡ እያረጋገጠ የኢትዮጵያን ትንሳኤ እውን ያደርጋል። ይህ ሰራዊት በጦር ግንባር ጀግና፣ በልማት ግንባር ደግሞ መሀንዲስ ሆኖ ሀገርን ወደ ታላቅ ከፍታ ይመራታል።
ባጠቃላይ፣ የኩሩ ህዝቦች መኖሪያ የሆነችውን ኢትዮጵያን እንደ አክሊል ደፍቶ፣ ቀለማቷን ጠብቆ፣ ታሪኳን አድሶ፣ ፈተናዎችን በብቃት ተሻግሮና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ አግዞ የሚጓዘው የመከላከያ ሰራዊታችን፣ የኢትዮጵያ ህያው ህልውና፣ የነፃነቷ ዐለት፣ የብዝሃነቷ ውበት እና የነገው ታላቅነቷ እውነተኛ ዋስትና ነው።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
Ethiopian Broadcasting Corporation #ጀግንነት #ኢትዮጵያ #ሰላም
*****************
"የኩሩ ህዝቦች መኖሪያ የህብረ ብሄር ቡቃያ፣ የሰላም ተምሳሌት ዓርማ የቀለሞች ህብር ኢትዮጵያ!"
ይህ የክብርና የሉዓላዊነት ብሔራዊ መዝሙር ስንኝ፣ ተራ የቃላት ድርደራ ሳይሆን የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የታሪክ፣ የፅናትና የማንነት መልክ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ የህሊና ብሩህ መስታወት ነው።
የመከላከያ ሰራዊቱ የማይበገር ጥንካሬ የሚመነጨው በልቡ ውስጥ ከነደደው የማያልቅ የሀገር ፍቅር እሳትና በውስጡ ከሰረጸው ጠንካራ ወታደራዊ ዲሲፕሊን ነው።
ሰራዊቱ ሀገርን በመጠበቅና ዳር ድንበርን በማስከበር ረገድ በዓለም መድረክ ላይ ተወዳዳሪ የሌለው፣ የታሪክን ታላላቅ ፈተናዎች በትከሻው የተሸከመ የሰላም ጽኑ ዐለት ነው።
የጦር ሜዳ ውሎው ስልታዊና አስፈሪ፣ የሰላም ጊዜው ደግሞ ለህዝብ አጋዥና መከታ ነው።
ይህ ሰራዊት የሀገር ውስጥ ጋሻ ብቻ አይደለም፤ ይልቁንም በአህጉሪቱና በዓለም አቀፍ ደረጃ በተሰማራባቸው የሰላም ማስከበር ተልዕኮዎች ሁሉ ሰብአዊነትንና የህግ የበላይነትን ያስቀደመ፣ የሌሎችን ህዝቦች ነፃነትና ክብር እንደ ራሱ አድርጎ የጠበቀ እጅግ ተወዳጅና የተከበረ ኃይል ነው። በሊቤሪያ፣ በሩዋንዳ፣ በዳርፉርና በሶማሊያ በረሃዎች ውስጥ የፈሰሰው ላቡና ደሙ፣ የኢትዮጵያን ስም በዓለም የክብር መዝገብ ላይ በደመቀ ቀለም አስፍሮታል።
የሰራዊቱ አባላት ሌሎችን ማክበርና ለተቸገሩት መድረስ ከአባቶቻቸው የወረሱት የደም እሴት በመሆኑ, በተሰማራበት አህጉርና ቀጠና ሁሉ በህዝቦች ልብ ውስጥ የማይጠፋ የፍቅርና የታማኝነት አሻራ ጥሏል። በዚህም የተነሳ በአፍሪካ ምድር ህዝቦች ዘንድ እጅግ ተወዳጅ ነው።
ከዚህም በላይ፣ ይህ የጀግኖች ስብስብ ጠመንጃ ብቻ ሳይሆን አካፋና ዶማም መያዝ የሚችል የልማት ግንባር ቀደም ኃይል ነው። በኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ ውስጥ፣ በታላላቅ የልማት ፕሮጀክቶች፣ በአረንጓዴ አሻራ፣ በታላቁ ህዳሴ ግድብና በህዝባዊ አገልግሎቶች ላይ ቀዳሚ በመሆን ድህነትን የሚዋጋ፣ ህዝቡን ከረሃብና ከችግር የሚታደግ የላብ አርበኛ ነው።
ሰላምን በደሙ፣ ልማትንና ብልጽግናን ደግሞ በላቡ እያረጋገጠ የኢትዮጵያን ትንሳኤ እውን ያደርጋል። ይህ ሰራዊት በጦር ግንባር ጀግና፣ በልማት ግንባር ደግሞ መሀንዲስ ሆኖ ሀገርን ወደ ታላቅ ከፍታ ይመራታል።
ባጠቃላይ፣ የኩሩ ህዝቦች መኖሪያ የሆነችውን ኢትዮጵያን እንደ አክሊል ደፍቶ፣ ቀለማቷን ጠብቆ፣ ታሪኳን አድሶ፣ ፈተናዎችን በብቃት ተሻግሮና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ አግዞ የሚጓዘው የመከላከያ ሰራዊታችን፣ የኢትዮጵያ ህያው ህልውና፣ የነፃነቷ ዐለት፣ የብዝሃነቷ ውበት እና የነገው ታላቅነቷ እውነተኛ ዋስትና ነው።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
Ethiopian Broadcasting Corporation #ጀግንነት #ኢትዮጵያ #ሰላም
2 hours ago
የኢትዮጵያ ወደ ባሕር በር መመለስ ለአፍሪካ ቀንድ ሁለንተናዊ ትብብር…
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ወደ ባሕር በር መመለስ በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ሁለንተናዊ ትብብር ይበልጥ ያጠናክራል አሉ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የደህንነት አማካሪ ሚኒስትር ዴዔታ ቀነአ ያደታ (ዶ/ር)፡፡
ቀነዓ ያደታ (ዶ/ር) እንዳሉት÷ የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ቅድሚያ የሚሰጠው የሉዓላዊነት ጉዳይ ነው።
ጥያቄው በሁሉም መመዘኛ ተገቢ መሆኑን ገልጸው÷ ኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄን ለማንሳት ጠንካራ የታሪክና የሕግ መሰረት እንዳላት አመልክተዋል።
ይህ የባሕር በር የማግኘት እንቅስቃሴ ብሔራዊ ጥቅምን የማረጋገጥ የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ብሔራዊ አጀንዳ ሆኗል ብለዋል።
ኢትዮጵያ በተለያዩ መድረኮች የባሕር በር ጥያቄ ፍትሃዊና በሰጥቶ መቀበል መርሕ ላይ የተመሰረተ መሆኑን በሰፊው የማስገንዘብ ሥራ ማከናወኗን ገልጸዋል።
በዚህም ጥያቄው በዓለም አቀፍ መድረክ ከጊዜ ወደ ጊዜ እውቅና እያገኘ መምጣቱን ነው አጽንኦት የሰጡት፡፡
ኢትዮጵያ በቀጣናው የኢኮኖሚ ዕድገትን፣ ትስስርን እና መረጋጋትን በመምራት ረገድ ታሪካዊ ሚና ያላት ሀገር መሆኑን የገለጹት ቀነዓ ያደታ (ዶ/ር)÷ የኢትዮጵያ ወደ ባሕር በር መመለስ ለቀጣናው ሠላምና መረጋጋት ቁልፍ ሚና እንዳለው አስረድተዋል።
የቀጣናው ሀገራት ትስስርን በማጠናከር ረገድም የኢትዮጵያ ወደ ባሕር በር መመለስ ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እንዳለው አስረድተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ሠላም ለጎረቤት ሀገራት ሰላም እውን መሆን ትልቅ ድርሻ እንዳለው ጠቅሰው÷ የአፍሪካ ቀንድን ፖለቲካዊና ማህበራዊ ሁኔታ መሠረታዊ በሆነ መልኩ በማረጋጋት ቀጣናዊ ብልፅግና እውን እንዲሆን አስቻይ ሁኔታ ይፈጥራል ማለታቸውንም ኢዜአ ዘግቧል።
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ወደ ባሕር በር መመለስ በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ሁለንተናዊ ትብብር ይበልጥ ያጠናክራል አሉ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የደህንነት አማካሪ ሚኒስትር ዴዔታ ቀነአ ያደታ (ዶ/ር)፡፡
ቀነዓ ያደታ (ዶ/ር) እንዳሉት÷ የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ ቅድሚያ የሚሰጠው የሉዓላዊነት ጉዳይ ነው።
ጥያቄው በሁሉም መመዘኛ ተገቢ መሆኑን ገልጸው÷ ኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄን ለማንሳት ጠንካራ የታሪክና የሕግ መሰረት እንዳላት አመልክተዋል።
ይህ የባሕር በር የማግኘት እንቅስቃሴ ብሔራዊ ጥቅምን የማረጋገጥ የህልውና ጉዳይ በመሆኑ ብሔራዊ አጀንዳ ሆኗል ብለዋል።
ኢትዮጵያ በተለያዩ መድረኮች የባሕር በር ጥያቄ ፍትሃዊና በሰጥቶ መቀበል መርሕ ላይ የተመሰረተ መሆኑን በሰፊው የማስገንዘብ ሥራ ማከናወኗን ገልጸዋል።
በዚህም ጥያቄው በዓለም አቀፍ መድረክ ከጊዜ ወደ ጊዜ እውቅና እያገኘ መምጣቱን ነው አጽንኦት የሰጡት፡፡
ኢትዮጵያ በቀጣናው የኢኮኖሚ ዕድገትን፣ ትስስርን እና መረጋጋትን በመምራት ረገድ ታሪካዊ ሚና ያላት ሀገር መሆኑን የገለጹት ቀነዓ ያደታ (ዶ/ር)÷ የኢትዮጵያ ወደ ባሕር በር መመለስ ለቀጣናው ሠላምና መረጋጋት ቁልፍ ሚና እንዳለው አስረድተዋል።
የቀጣናው ሀገራት ትስስርን በማጠናከር ረገድም የኢትዮጵያ ወደ ባሕር በር መመለስ ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እንዳለው አስረድተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ሠላም ለጎረቤት ሀገራት ሰላም እውን መሆን ትልቅ ድርሻ እንዳለው ጠቅሰው÷ የአፍሪካ ቀንድን ፖለቲካዊና ማህበራዊ ሁኔታ መሠረታዊ በሆነ መልኩ በማረጋጋት ቀጣናዊ ብልፅግና እውን እንዲሆን አስቻይ ሁኔታ ይፈጥራል ማለታቸውንም ኢዜአ ዘግቧል።
2 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት (ESL) ከ40 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የሀገሪቱን የነዳጅ እና የፔትሮሊየም ምርቶች የማጓጓዝ ስራ በይፋ መጀመሩን ዛሬ በአዲስ አበባ ታትሞ የወጣው ካፒታል እንግሊዘኛው ጋዜጣ ዘግቧል። ይህ ታሪካዊ ጅምር ኢትዮጵያ ከሱዳን ነዳጅ ማስገባት ካቆመች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከአፍሪካ (ከአህጉሪቱ) ሀገር ነዳጅ ያገኘችበትንም አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል።
በአሜሪካ በእስራኤል እና በኢራን መካከል በተፈጠረው ግጭት ምክንያት በዓለም አቀፉ የነዳጅ መተላለፊያ ላይ የተፈጠረውን መስተጓጎል ተከትሎ፣ የኢትዮጵያ መንግስት የነዳጅ ግዥ ስትራቴጂውን ወደ ምዕራብ እስያ እና ናይጄሪያ በማስፋት አማራጮችን ፈጥሯል። በዚህም መሰረት፣ በቢሊየነሩ አሊኮ ዳንጎቴ ከሚተዳደረው የናይጄሪያው 'ዳንጎቴ ፔትሮሊየም ሪፋይነሪ' 120,000 ሜትሪክ ቶን የአቪዬሽን (የአውሮፕላን) እና የናፍጣ ነዳጅ በተሳካ ሁኔታ በ3 መርከቦች ወደ ጅቡቲ ሆራይዘን ተርሚናል ተጓጉዟል። ከዚህ ውስጥ 80,000 ሜትሪክ ቶኑ የአውሮፕላን ነዳጅ ነው።
ባለፉት አራት አስርት ዓመታት የነዳጅ ማጓጓዝ ስራውን በብቸኝነት ሲያከናውን የቆየው የኢትዮጵያ የነዳጅ አቅራቢ ድርጅት (EPSE) ሲሆን፣ አሁን ግን መንግስት ዘርፉን ክፍት በማድረግ የግል ባለሀብቶች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ በራሳቸው የውጭ ምንዛሬ ነዳጅ ማስገባት የሚችሉበትን መመሪያ አውጥቷል።
ኢትዮጵያ ነዳጅ የማታመርት በመሆኗ የገቢ ንግድ በጀቷን ሩብ ያህል ለነዳጅ የምታውል ሲሆን፣ በመጪው በጀት ዓመት የነዳጅ ወጪዋ እስከ 6 ቢሊዮን ዶላር ሊደርስ እንደሚችል የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ለፓርላማው መግለጻቸውን በዘ-ሐበሻ ዜና መዘገባችን ይታወሳል። መንግስት በያዘው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ መሰረት፣ የነዳጅ ድጎማን ቀስ በቀስ ለመቀነስ በማቀድ በመጪው በጀት ዓመት ለዘርፉ 20 ቢሊዮን ብር ብቻ የድጎማ በጀት አቅርቧል፤ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ቅናሽ ያሳየ ነው።
በአሜሪካ በእስራኤል እና በኢራን መካከል በተፈጠረው ግጭት ምክንያት በዓለም አቀፉ የነዳጅ መተላለፊያ ላይ የተፈጠረውን መስተጓጎል ተከትሎ፣ የኢትዮጵያ መንግስት የነዳጅ ግዥ ስትራቴጂውን ወደ ምዕራብ እስያ እና ናይጄሪያ በማስፋት አማራጮችን ፈጥሯል። በዚህም መሰረት፣ በቢሊየነሩ አሊኮ ዳንጎቴ ከሚተዳደረው የናይጄሪያው 'ዳንጎቴ ፔትሮሊየም ሪፋይነሪ' 120,000 ሜትሪክ ቶን የአቪዬሽን (የአውሮፕላን) እና የናፍጣ ነዳጅ በተሳካ ሁኔታ በ3 መርከቦች ወደ ጅቡቲ ሆራይዘን ተርሚናል ተጓጉዟል። ከዚህ ውስጥ 80,000 ሜትሪክ ቶኑ የአውሮፕላን ነዳጅ ነው።
ባለፉት አራት አስርት ዓመታት የነዳጅ ማጓጓዝ ስራውን በብቸኝነት ሲያከናውን የቆየው የኢትዮጵያ የነዳጅ አቅራቢ ድርጅት (EPSE) ሲሆን፣ አሁን ግን መንግስት ዘርፉን ክፍት በማድረግ የግል ባለሀብቶች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ በራሳቸው የውጭ ምንዛሬ ነዳጅ ማስገባት የሚችሉበትን መመሪያ አውጥቷል።
ኢትዮጵያ ነዳጅ የማታመርት በመሆኗ የገቢ ንግድ በጀቷን ሩብ ያህል ለነዳጅ የምታውል ሲሆን፣ በመጪው በጀት ዓመት የነዳጅ ወጪዋ እስከ 6 ቢሊዮን ዶላር ሊደርስ እንደሚችል የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ለፓርላማው መግለጻቸውን በዘ-ሐበሻ ዜና መዘገባችን ይታወሳል። መንግስት በያዘው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ መሰረት፣ የነዳጅ ድጎማን ቀስ በቀስ ለመቀነስ በማቀድ በመጪው በጀት ዓመት ለዘርፉ 20 ቢሊዮን ብር ብቻ የድጎማ በጀት አቅርቧል፤ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ቅናሽ ያሳየ ነው።
5 hours ago
በዓለም ዋንጫ የአፍሪካ አህጉር ተወካዮች የሆኑት ኮትዲቯር እና ቱኒዚያ ዛሬ ወደ ሜዳ ይገባሉ
#ethiopia | በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ባለው የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ውድድር አፍሪካን ወክለው የሚሳተፉት ኮትዲቯር እና ቱኒዚያ ዛሬ ምሽት የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታቸውን ያከናውናሉ።
በዚህም መሠረት የዝሆኖቹ ሀገር ኮትዲቯር ከደቡብ አሜሪካዋ ጠንካራ ተጋጣሚ ኢኳዶር ጋር ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት ላይ ትገናኛለች።
በአውሮፓ ታዋቂ ሊጎች ውስጥ የሚጫወቱ በርካታ ባለክህሎት ተጫዋቾችን የያዘችው ኮትዲቯር ለኢኳዶር ከባድ ፈተና እንደምትሆን በስፋት ተገምቷል።
ሌላኛዋ የአፍሪካ ተወካይ ሰሜን አፍሪካዊቷ ቱኒዚያ በበኩሏ ከጠንካራዋ የአውሮፓ ሀገር ስዊድን ጋር ከሌሊቱ 11 ሰዓት ላይ ፍልሚያዋን ታደርጋለች።
ከእነዚህ ጨዋታዎች አስቀድሞ ምሽት ሁለት ሰዓት ላይ በዓለም እግር ኳስ ግዙፍ ስም ያላት ጀርመን ከካራካኦ ጋር የምታደርገው ጨዋታ በብዙዎች ዘንድ ይጠበቃል።
በተጨማሪም ኔዘርላንድ ከእስያዋ ተስፈኛ ሀገር ጃፓን ጋር የምታደርገው ጨዋታ የዛሬው ምሽት ሌላኛው አጓጊ መርሃ ግብር ነው።
ትናንት ምሽት በተከናወኑ ጨዋታዎች አውስትራሊያ ቱርኪዬን ሁለት ለባዶ ያሸነፈች ሲሆን ስኮትላንድ በበኩሏ ሃይቲን አንድ ለባዶ በሆነ ጠባብ ውጤት ማሸነፍ ችላለች።
በሌላ በኩል በአፍሪካ ኩራት የሆነችው ሞሮኮ ከዓለም እግር ኳስ ኃያሏ ብራዚል ጋር እንዲሁም ኳታር ከስዊዘርላንድ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ በተመሳሳይ አንድ ለአንድ በሆነ አቻ ውጤት አጠናቀዋል።
#worldcup2026 #africanfootball #cotedivoire #tunisia #fifaworldcup #footballnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ባለው የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ውድድር አፍሪካን ወክለው የሚሳተፉት ኮትዲቯር እና ቱኒዚያ ዛሬ ምሽት የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታቸውን ያከናውናሉ።
በዚህም መሠረት የዝሆኖቹ ሀገር ኮትዲቯር ከደቡብ አሜሪካዋ ጠንካራ ተጋጣሚ ኢኳዶር ጋር ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት ላይ ትገናኛለች።
በአውሮፓ ታዋቂ ሊጎች ውስጥ የሚጫወቱ በርካታ ባለክህሎት ተጫዋቾችን የያዘችው ኮትዲቯር ለኢኳዶር ከባድ ፈተና እንደምትሆን በስፋት ተገምቷል።
ሌላኛዋ የአፍሪካ ተወካይ ሰሜን አፍሪካዊቷ ቱኒዚያ በበኩሏ ከጠንካራዋ የአውሮፓ ሀገር ስዊድን ጋር ከሌሊቱ 11 ሰዓት ላይ ፍልሚያዋን ታደርጋለች።
ከእነዚህ ጨዋታዎች አስቀድሞ ምሽት ሁለት ሰዓት ላይ በዓለም እግር ኳስ ግዙፍ ስም ያላት ጀርመን ከካራካኦ ጋር የምታደርገው ጨዋታ በብዙዎች ዘንድ ይጠበቃል።
በተጨማሪም ኔዘርላንድ ከእስያዋ ተስፈኛ ሀገር ጃፓን ጋር የምታደርገው ጨዋታ የዛሬው ምሽት ሌላኛው አጓጊ መርሃ ግብር ነው።
ትናንት ምሽት በተከናወኑ ጨዋታዎች አውስትራሊያ ቱርኪዬን ሁለት ለባዶ ያሸነፈች ሲሆን ስኮትላንድ በበኩሏ ሃይቲን አንድ ለባዶ በሆነ ጠባብ ውጤት ማሸነፍ ችላለች።
በሌላ በኩል በአፍሪካ ኩራት የሆነችው ሞሮኮ ከዓለም እግር ኳስ ኃያሏ ብራዚል ጋር እንዲሁም ኳታር ከስዊዘርላንድ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ በተመሳሳይ አንድ ለአንድ በሆነ አቻ ውጤት አጠናቀዋል።
#worldcup2026 #africanfootball #cotedivoire #tunisia #fifaworldcup #footballnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
6 hours ago
የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት አብዲራህማን ጪሮ በሀገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ለማድረግ እስራኤል መግባታቸውን አስታወቁ። ፕሬዝዳንቱ በእስራኤሉ አቻቸው አይዛክ ኸርዞግ ደማቅ አቀባበል እንደተደረገላቸውም ገልጸዋል።
ፕሬዝዳንት ጪሮ ባወጡት ይፋዊ መግለጫ የሶማሊላንድ ህዝብ ላለፉት 35 ዓመታት ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ጠንካራ ሀገር መገንባቱን አስታውሰዋል። "ዓለምን 'ታዩናላችሁ ወይ?' ብለን ጠየቅን፤ ለእዚህ ጥያቄያችን የመጀመሪያዋ መላሽ እስራኤል ነች" በማለት እስራኤል ለሶማሊላንድ እውቅና የሰጠችበትን ታሪካዊ ክስተት አድንቀዋል። ፕሬዝዳንቱ ይህ ጉብኝት በሶማሊላንድ ጉዞ ውስጥ ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን እና በሁለቱ ሀገራት መካከል አዲስ የዲፕሎማሲ ምዕራፍ የከፈተ መሆኑን አብራርተዋል።
ለመላው የሶማሊላንድ ህዝብ ባስተላለፉት መልዕክት የህዝባቸውን ተስፋ እና ምኞት ሰንቀው እንደተጓዙ የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፣ በርካታ ትውልዶች ሀገሪቱን ወደዚህ ታሪካዊ ምዕራፍ ለማድረስ ከፍተኛ ትግል እና መስዋዕትነት መክፈላቸውን አውስተዋል። አክለውም፣ "ይህንን ታሪካዊ አጋጣሚ በልበ ሙሉነት፣ በጥበብ እና በቁርጠኝነት እንጠቀምበታለን፤ ሁሌም ቢሆን መመሪያችን የህዝባችን እና የሀገራችን ብሔራዊ ጥቅም ነው" ብለዋል።
ሶማሊላንድ ከእስራኤል ጋር በጓደኝነት፣ በትብብር እና በጋራ መከባበር ላይ የተመሰረተ የጋራ የወደፊት ተስፋን ለመገንባት ዝግጁ መሆኗንም አረጋግጠዋል። "ዛሬ አዲስ ታሪክ እየተጻፈ ነው" ሲሉም መልዕክታቸውን አጠቃልለዋል።
ይህ የፕሬዝዳንት አብዲራህማን ጪሮ የእስራኤል ጉብኝት፣ በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ውስብስብ የጂኦ-ፖለቲካዊ ውጥረት ይበልጥ ሊለውጠው እና ሊያጦፈው የሚችል ከባድ ክስተት ነው። እስራኤል ለሶማሊላንድ እውቅና መስጠቷ እና የሀገሪቱን መሪ በይፋዊ የስራ ጉብኝት ደረጃ መቀበሏ፣ ሱማሊላንድ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ለማግኘት ለምታደርገው ጥረት ትልቅ ዲፕሎማሲያዊ ስኬት ነው።
በአንጻሩ የሶማሊያ መንግስት ሶማሊላንድን እንደራሱ አካል አድርጎ ስለሚቆጥር እና እስራኤል ለሶማሊላንድ የሰጠችውን እውቅና "በታሪካችን ከታዩት የጨለማ ቀናት አንዱ ነው" በማለት አጥብቆ በማውገዝ ላይ በመሆኑ፣ ይህ ጉብኝት የሞቃዲሾን ቁጣ በእጅጉ የሚቀሰቅስ እና የቀጣናውን የፖለቲካ አሰላለፍ በአዲስ መልክ የሚቀርጽ ታሪካዊ እርምጃ ሆኖ ተመዝግቧል።
ፕሬዝዳንት ጪሮ ባወጡት ይፋዊ መግለጫ የሶማሊላንድ ህዝብ ላለፉት 35 ዓመታት ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ጠንካራ ሀገር መገንባቱን አስታውሰዋል። "ዓለምን 'ታዩናላችሁ ወይ?' ብለን ጠየቅን፤ ለእዚህ ጥያቄያችን የመጀመሪያዋ መላሽ እስራኤል ነች" በማለት እስራኤል ለሶማሊላንድ እውቅና የሰጠችበትን ታሪካዊ ክስተት አድንቀዋል። ፕሬዝዳንቱ ይህ ጉብኝት በሶማሊላንድ ጉዞ ውስጥ ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን እና በሁለቱ ሀገራት መካከል አዲስ የዲፕሎማሲ ምዕራፍ የከፈተ መሆኑን አብራርተዋል።
ለመላው የሶማሊላንድ ህዝብ ባስተላለፉት መልዕክት የህዝባቸውን ተስፋ እና ምኞት ሰንቀው እንደተጓዙ የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፣ በርካታ ትውልዶች ሀገሪቱን ወደዚህ ታሪካዊ ምዕራፍ ለማድረስ ከፍተኛ ትግል እና መስዋዕትነት መክፈላቸውን አውስተዋል። አክለውም፣ "ይህንን ታሪካዊ አጋጣሚ በልበ ሙሉነት፣ በጥበብ እና በቁርጠኝነት እንጠቀምበታለን፤ ሁሌም ቢሆን መመሪያችን የህዝባችን እና የሀገራችን ብሔራዊ ጥቅም ነው" ብለዋል።
ሶማሊላንድ ከእስራኤል ጋር በጓደኝነት፣ በትብብር እና በጋራ መከባበር ላይ የተመሰረተ የጋራ የወደፊት ተስፋን ለመገንባት ዝግጁ መሆኗንም አረጋግጠዋል። "ዛሬ አዲስ ታሪክ እየተጻፈ ነው" ሲሉም መልዕክታቸውን አጠቃልለዋል።
ይህ የፕሬዝዳንት አብዲራህማን ጪሮ የእስራኤል ጉብኝት፣ በአፍሪካ ቀንድ ያለውን ውስብስብ የጂኦ-ፖለቲካዊ ውጥረት ይበልጥ ሊለውጠው እና ሊያጦፈው የሚችል ከባድ ክስተት ነው። እስራኤል ለሶማሊላንድ እውቅና መስጠቷ እና የሀገሪቱን መሪ በይፋዊ የስራ ጉብኝት ደረጃ መቀበሏ፣ ሱማሊላንድ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ለማግኘት ለምታደርገው ጥረት ትልቅ ዲፕሎማሲያዊ ስኬት ነው።
በአንጻሩ የሶማሊያ መንግስት ሶማሊላንድን እንደራሱ አካል አድርጎ ስለሚቆጥር እና እስራኤል ለሶማሊላንድ የሰጠችውን እውቅና "በታሪካችን ከታዩት የጨለማ ቀናት አንዱ ነው" በማለት አጥብቆ በማውገዝ ላይ በመሆኑ፣ ይህ ጉብኝት የሞቃዲሾን ቁጣ በእጅጉ የሚቀሰቅስ እና የቀጣናውን የፖለቲካ አሰላለፍ በአዲስ መልክ የሚቀርጽ ታሪካዊ እርምጃ ሆኖ ተመዝግቧል።
7 hours ago
የቤተክርስቲያን የልማት ጉዳዮች ለምዕመኑ ይሰጡ ካህናት ከብረትና ሲሚንቶ ግዥ ሊወገዱ ይገባል
ካህናቱ ሁሌ በመድረክ እልል በሉ እያሉ ብር ሲሰበስቡ ማየት እንዴት ይሰቀጥጣል ?
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከጥንት ጀምሮ መንፈሳዊውን ዓለም ከሥጋዊው፣ ሰማያዊውን ከምድራዊው እያስማማች የኖረች ታሪካዊ ተቋም ናት።
ቤተክርስቲያኗ ራሷን ለመቻልና ሐዋርያዊ ተልዕኮዋን ለማስፋፋት የምታደርጋቸው የሕንፃ ግንባታዎች የሱቆች መዋቅርና የተለያዩ የልማት ሥራዎች የሚበረታቱ ናቸው።
ሆኖም ግን እነዚህን የቢዝነስና የፋይናንስ እንቅስቃሴዎች ቀጥታ በካህናትና በደብር አስተዳዳሪዎች እንዲመሩ የማድረጉ አሰራር በዘመናዊው የአደረጃጀት ሳይንስም ሆነ በተቋማዊ ውጤታማነት ረገድ ጥልቅ ምርመራና መዋቅራዊ ለውጥ ያስፈልገዋል።
የቤተክርስቲያንን ክብር ለመጠበቅና የልማት ሥራዎቿን ለማሳለጥ እነዚህን ዓለማዊና ሙያዊ ተግባራት ሙሉ በሙሉ ለምዕመኑ አሳልፎ መስጠት ወቅቱ የሚጠይቀው የማይቀረው መፍትሔ ነው።
ካህናትን ከዕለት ተዕለት የገንዘብና የግንባታ ውዝግቦች ማራቅ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባው የክህነትን ልዕልና ለመጠበቅ ሲባል ነው። የአንድ ካህን ቀዳሚ ጥሪና ስዕለት ቅዱስ ቁርባንን ማቅረብ፣ ማስተማር፣ ንስሐ ማባትና ምዕመናንን በመንፈሳዊ ሕይወት ማነጽ ነው።
ካህናቱ ቀናቸውን ሙሉ በሲሚንቶና ብረት ግዢ፣ በሱቅ ኪራይ ውል ድርድርና በገቢ አሰባሰብ ቢሮክራሲ ላይ ሲያሳልፉ ለመንፈሳዊ አገልግሎት የሚኖራቸው የጊዜና የነፍስ ዝግጁነት በእጅጉ ይሸረሸራል።
ገንዘብና ጥቅማጥቅም ባለበት ቦታ ሁሉ ደግሞ አለመግባባት ጥርጣሬና የፍርድ ቤት ክርክሮች አይጠፉም። ካህናት በእነዚህ ጉዳዮች ውስጥ ቀጥታ ተዋናይ ሲሆኑ ምዕመናን ለእነሱ ያላቸው መንፈሳዊ ፍርሃትና አክብሮት እየቀነሰ እንዲሄድ በር ይከፍታል።
በሌላ በኩል የሕንፃ ግንባታ፣ የአካውንቲንግና የፋይናንስ ሥራዎች የራሳቸው የሆነ ጥብቅ የሳይንስና የሙያ መስክ አላቸው እነዚህን ሥራዎች የሃይማኖት ዕውቀትን ብቻ መሠረት አድርጎ መምራት ለከፍተኛ የሀብት ብክነት ለጥራት መጓደልና ለፕሮጀክቶች መጓተት ይዳርጋል።
በቤተክርስቲያኗ ጥላ ሥር የሰለጠኑና በተለያዩ ዘርፎች (በኢንጂነሪንግ፣ በሕግ፣ በኦዲትና በቢዝነስ) ከፍተኛ ስኬት ያስመዘገቡ ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ምዕመናን አሉ እነዚህን ባለሙያዎች በበጎ ፈቃደኝነትም ሆነ በቅጥር ሥርዓት ውስጥ በማስገባት ሥራውን ለምዕመኑ መስጠት፣ የልማት ሥራዎቹ በሙያዊ ብቃትና በጥራት እንዲከናወኑ ያደርጋል።
ይህም በቤተክርስቲያን ውስጥ ዘመናዊ የሒሳብ አያያዝና ግልጽነት ያለው የኦዲት ሥርዓት ለመዘርጋት ብቸኛው መንገድ ነው።
ለዚህ አሰራር ውጤታማነት በዓለም አቀፍ ደረጃ ያሉ ታላላቅና ጥንታውያን አቢያተ ክርስቲያናትን እንደ ማረጋገጫ መጥቀስ ይቻላል።
ለምሳሌ በሮማን ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ውስጥ ካህናትና ጳጳሳት ትኩረታቸው ሙሉ በሙሉ በመንፈሳዊና በቀኖናዊ ጉዳዮች ላይ ብቻ የተገደበ ነው። የቅድስት መንበርን (ቫቲካንን) ጨምሮ የእያንዳንዱን ሀገረ ስብከት የህንፃ ግንባታ፣ የባንክና የኢንቨስትመንት ሥራዎች በምዕመናን እና በዘርፉ በተሰማሩ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ባለሙያዎች ቦርድ ይመራል።
በተመሳሳይ መልኩ በምሥራቅ ኦርቶዶክስ (እንደ ግሪክና ሩሲያ) እና በወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናትም መንፈሳዊው መጋቢነት ከአስተዳደራዊና ከንብረት ክፍሉ በግልጽ የተለየ ነው።
ይህ መዋቅር አብያተ ክርስቲያናቱ መንፈሳዊ ክብራቸውን ሳይለቁ በኢኮኖሚ ረገድ እጅግ ግዙፍና ስኬታማ ተቋም እንዲሆኑ አስችሏቸዋል።
ይህንን ለውጥ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ውስጥ ለመተግበር የካህናቱን ሚና ሙሉ በሙሉ ማግለል ሳይሆን የሥራ ድርሻን በግልጽ መለየት ያስፈልጋል።
ካህናቱና የደብር አስተዳዳሪዎቹ የንብረቱና የሃብቱ "የበላይ ጠባቂና ባለአደራ" ሆነው ይቀጥላሉ። ሥራዎች ከቤተክርስቲያኗ ሞራልና ቀኖና ጋር አለመጋጨታቸውን ይቆጣጠራሉ፣ ይባርካሉ።
ባለሙያ ምዕመናን ደግሞ በዕቅድ ዝግጅት፣ በግንባታ፣ በሒሳብ አያያዝና በልማት ሥራው ላይ "ቀጥተኛ ፈጻሚ" ሆነው በኃላፊነት ይሠራሉ።
ይህ አሰራር ሲዘረጋ ካህናት ከገንዘብ ንክኪና ከትችት ነፃ ይሆናሉ ምዕመናንም በዕውቀታቸውና በሙያቸው እናት ቤተክርስቲያናቸውን በታማኝነት እንዲያገለግሉ ዕድል ይፈጥራል።
በመሆኑም ቤተክርስቲያኗ ዘመኑን የዋጀ ተቋማዊ ዕድገት እንድታስመዘግብ የልማትና የፋይናንስ ሥራዎችን ሙሉ በሙሉ ለምዕመኑ አሳልፎ የመስጠቱ ጉዳይ ሊዘገይ የማይገባው አንገብጋቢ ውሳኔ ነው።
ይህንን ቅዱስ ሲኖዶስ ሊያስተካክለው አይገባም ትላላችሁ ? እስኪ ሃሳብ ስጡበት
ካህናቱ ሁሌ በመድረክ እልል በሉ እያሉ ብር ሲሰበስቡ ማየት እንዴት ይሰቀጥጣል ?
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከጥንት ጀምሮ መንፈሳዊውን ዓለም ከሥጋዊው፣ ሰማያዊውን ከምድራዊው እያስማማች የኖረች ታሪካዊ ተቋም ናት።
ቤተክርስቲያኗ ራሷን ለመቻልና ሐዋርያዊ ተልዕኮዋን ለማስፋፋት የምታደርጋቸው የሕንፃ ግንባታዎች የሱቆች መዋቅርና የተለያዩ የልማት ሥራዎች የሚበረታቱ ናቸው።
ሆኖም ግን እነዚህን የቢዝነስና የፋይናንስ እንቅስቃሴዎች ቀጥታ በካህናትና በደብር አስተዳዳሪዎች እንዲመሩ የማድረጉ አሰራር በዘመናዊው የአደረጃጀት ሳይንስም ሆነ በተቋማዊ ውጤታማነት ረገድ ጥልቅ ምርመራና መዋቅራዊ ለውጥ ያስፈልገዋል።
የቤተክርስቲያንን ክብር ለመጠበቅና የልማት ሥራዎቿን ለማሳለጥ እነዚህን ዓለማዊና ሙያዊ ተግባራት ሙሉ በሙሉ ለምዕመኑ አሳልፎ መስጠት ወቅቱ የሚጠይቀው የማይቀረው መፍትሔ ነው።
ካህናትን ከዕለት ተዕለት የገንዘብና የግንባታ ውዝግቦች ማራቅ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባው የክህነትን ልዕልና ለመጠበቅ ሲባል ነው። የአንድ ካህን ቀዳሚ ጥሪና ስዕለት ቅዱስ ቁርባንን ማቅረብ፣ ማስተማር፣ ንስሐ ማባትና ምዕመናንን በመንፈሳዊ ሕይወት ማነጽ ነው።
ካህናቱ ቀናቸውን ሙሉ በሲሚንቶና ብረት ግዢ፣ በሱቅ ኪራይ ውል ድርድርና በገቢ አሰባሰብ ቢሮክራሲ ላይ ሲያሳልፉ ለመንፈሳዊ አገልግሎት የሚኖራቸው የጊዜና የነፍስ ዝግጁነት በእጅጉ ይሸረሸራል።
ገንዘብና ጥቅማጥቅም ባለበት ቦታ ሁሉ ደግሞ አለመግባባት ጥርጣሬና የፍርድ ቤት ክርክሮች አይጠፉም። ካህናት በእነዚህ ጉዳዮች ውስጥ ቀጥታ ተዋናይ ሲሆኑ ምዕመናን ለእነሱ ያላቸው መንፈሳዊ ፍርሃትና አክብሮት እየቀነሰ እንዲሄድ በር ይከፍታል።
በሌላ በኩል የሕንፃ ግንባታ፣ የአካውንቲንግና የፋይናንስ ሥራዎች የራሳቸው የሆነ ጥብቅ የሳይንስና የሙያ መስክ አላቸው እነዚህን ሥራዎች የሃይማኖት ዕውቀትን ብቻ መሠረት አድርጎ መምራት ለከፍተኛ የሀብት ብክነት ለጥራት መጓደልና ለፕሮጀክቶች መጓተት ይዳርጋል።
በቤተክርስቲያኗ ጥላ ሥር የሰለጠኑና በተለያዩ ዘርፎች (በኢንጂነሪንግ፣ በሕግ፣ በኦዲትና በቢዝነስ) ከፍተኛ ስኬት ያስመዘገቡ ቁጥራቸው ቀላል የማይባል ምዕመናን አሉ እነዚህን ባለሙያዎች በበጎ ፈቃደኝነትም ሆነ በቅጥር ሥርዓት ውስጥ በማስገባት ሥራውን ለምዕመኑ መስጠት፣ የልማት ሥራዎቹ በሙያዊ ብቃትና በጥራት እንዲከናወኑ ያደርጋል።
ይህም በቤተክርስቲያን ውስጥ ዘመናዊ የሒሳብ አያያዝና ግልጽነት ያለው የኦዲት ሥርዓት ለመዘርጋት ብቸኛው መንገድ ነው።
ለዚህ አሰራር ውጤታማነት በዓለም አቀፍ ደረጃ ያሉ ታላላቅና ጥንታውያን አቢያተ ክርስቲያናትን እንደ ማረጋገጫ መጥቀስ ይቻላል።
ለምሳሌ በሮማን ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ውስጥ ካህናትና ጳጳሳት ትኩረታቸው ሙሉ በሙሉ በመንፈሳዊና በቀኖናዊ ጉዳዮች ላይ ብቻ የተገደበ ነው። የቅድስት መንበርን (ቫቲካንን) ጨምሮ የእያንዳንዱን ሀገረ ስብከት የህንፃ ግንባታ፣ የባንክና የኢንቨስትመንት ሥራዎች በምዕመናን እና በዘርፉ በተሰማሩ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ባለሙያዎች ቦርድ ይመራል።
በተመሳሳይ መልኩ በምሥራቅ ኦርቶዶክስ (እንደ ግሪክና ሩሲያ) እና በወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናትም መንፈሳዊው መጋቢነት ከአስተዳደራዊና ከንብረት ክፍሉ በግልጽ የተለየ ነው።
ይህ መዋቅር አብያተ ክርስቲያናቱ መንፈሳዊ ክብራቸውን ሳይለቁ በኢኮኖሚ ረገድ እጅግ ግዙፍና ስኬታማ ተቋም እንዲሆኑ አስችሏቸዋል።
ይህንን ለውጥ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ውስጥ ለመተግበር የካህናቱን ሚና ሙሉ በሙሉ ማግለል ሳይሆን የሥራ ድርሻን በግልጽ መለየት ያስፈልጋል።
ካህናቱና የደብር አስተዳዳሪዎቹ የንብረቱና የሃብቱ "የበላይ ጠባቂና ባለአደራ" ሆነው ይቀጥላሉ። ሥራዎች ከቤተክርስቲያኗ ሞራልና ቀኖና ጋር አለመጋጨታቸውን ይቆጣጠራሉ፣ ይባርካሉ።
ባለሙያ ምዕመናን ደግሞ በዕቅድ ዝግጅት፣ በግንባታ፣ በሒሳብ አያያዝና በልማት ሥራው ላይ "ቀጥተኛ ፈጻሚ" ሆነው በኃላፊነት ይሠራሉ።
ይህ አሰራር ሲዘረጋ ካህናት ከገንዘብ ንክኪና ከትችት ነፃ ይሆናሉ ምዕመናንም በዕውቀታቸውና በሙያቸው እናት ቤተክርስቲያናቸውን በታማኝነት እንዲያገለግሉ ዕድል ይፈጥራል።
በመሆኑም ቤተክርስቲያኗ ዘመኑን የዋጀ ተቋማዊ ዕድገት እንድታስመዘግብ የልማትና የፋይናንስ ሥራዎችን ሙሉ በሙሉ ለምዕመኑ አሳልፎ የመስጠቱ ጉዳይ ሊዘገይ የማይገባው አንገብጋቢ ውሳኔ ነው።
ይህንን ቅዱስ ሲኖዶስ ሊያስተካክለው አይገባም ትላላችሁ ? እስኪ ሃሳብ ስጡበት
Sponsored by
Surafel
8 hours ago
የፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች መቋቋም ስጋት የሕክምናው ዘርፍ ፈተና
#ethiopia | በተለያዩ የመድኃኒት መሸጫ ፋርማሲዎች፣ በሙያ ማህበራት፣ በጤና ተቋማትና በማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ሰሞኑን ስለ ፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች መቋቋም ወይም Antimicrobial Resistance (AMR) ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ መልዕክቶች ሲስተላለፉ ቆይተዋል።
ይህ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ ትኩረት ሊሰጠው የቻለው በየዓመቱ የሚታሰበውን ዓለም አቀፍ የባለሙያዎችና የህዝብ ንቅናቄ መድረክን ተከትሎ ነው።
የመድኃኒት መቋቋም የሚባለው ክስተት ባክቴሪያዎች፣ ፈንገሶች፣ ቫይረሶችና መሰል ጥቃቅን ተህዋሲያን እነሱን ለማጥፋት የሚታዘዙ መድኃኒቶችን የመላመድና የመቋቋም አቅም ሲያዳብሩ የሚፈጠር የጤና እክል ነው።
ይህ ሁኔታ ቀደም ሲል በቀላሉ መፈወስ የሚችሉ የጤና ችግሮችን ውስብስብ ከማድረጉም በላይ ለተጨማሪ የሕክምና ወጪና ለከፋ የህይወት መጥፋት አደጋ የሚያጋልጥ መሆኑ ይነገራል።
ችግሩ በዓለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፋ ቢገኝም አሁንም ድረስ ከብዙሃኑ ህብረተሰብ ተገቢውን ትኩረት አላገኘም።
በተለይም አንቲባዮቲክስ ወይም የፀረ-ባክቴሪያ መድኃኒቶችን ያለ ሐኪም ትዕዛዝ በራስ ፍቃድ መውሰድ፣ የተጀመረን የሕክምና ጊዜ አጠናቆ አለመጨረስና መድኃኒቶችን ያለአግባብ መጠቀም ለችግሩ መባባስ ዋነኛ መንስኤዎች ሆነዋል።
የዘርፉ ባለሙያዎች ይህንን የጤና ስጋት ዝምተኛው ወይም ቀዝቃዛው ሱናሚ ሲሉ ይጠሩታል።
እንደ ድንገተኛ ወረርሽኝ በአንድ ጊዜ ህዝብን ባያጠቃም በሂደት ግን በዝግታ እየተስፋፋ የዘመናዊ ሕክምና ስኬቶችንና መሠረቶችን ትልቅ አደጋ ላይ እየጣለ ይገኛል።
ስለሆነም መድኃኒቶችን በከፍተኛ ኃላፊነት መጠቀም፣ የሕክምና ባለሙያዎችን ምክር በአግባቡ መተግበርና ህብረተሰቡን ማስተማር የሁሉንም አካላት ርብርብ ይጠይቃል።
ዛሬ የምናሳየው ጥንቃቄና የምንወስደው እርምጃ ወደፊት ውጤታማና ፈዋሽ መድኃኒቶች እንዲኖሩን ለማድረግ ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
ሃና ልካስ
#amr #antimicrobialresistance #healthnews #publichealth #medicine #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በተለያዩ የመድኃኒት መሸጫ ፋርማሲዎች፣ በሙያ ማህበራት፣ በጤና ተቋማትና በማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ሰሞኑን ስለ ፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች መቋቋም ወይም Antimicrobial Resistance (AMR) ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ መልዕክቶች ሲስተላለፉ ቆይተዋል።
ይህ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ ትኩረት ሊሰጠው የቻለው በየዓመቱ የሚታሰበውን ዓለም አቀፍ የባለሙያዎችና የህዝብ ንቅናቄ መድረክን ተከትሎ ነው።
የመድኃኒት መቋቋም የሚባለው ክስተት ባክቴሪያዎች፣ ፈንገሶች፣ ቫይረሶችና መሰል ጥቃቅን ተህዋሲያን እነሱን ለማጥፋት የሚታዘዙ መድኃኒቶችን የመላመድና የመቋቋም አቅም ሲያዳብሩ የሚፈጠር የጤና እክል ነው።
ይህ ሁኔታ ቀደም ሲል በቀላሉ መፈወስ የሚችሉ የጤና ችግሮችን ውስብስብ ከማድረጉም በላይ ለተጨማሪ የሕክምና ወጪና ለከፋ የህይወት መጥፋት አደጋ የሚያጋልጥ መሆኑ ይነገራል።
ችግሩ በዓለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፋ ቢገኝም አሁንም ድረስ ከብዙሃኑ ህብረተሰብ ተገቢውን ትኩረት አላገኘም።
በተለይም አንቲባዮቲክስ ወይም የፀረ-ባክቴሪያ መድኃኒቶችን ያለ ሐኪም ትዕዛዝ በራስ ፍቃድ መውሰድ፣ የተጀመረን የሕክምና ጊዜ አጠናቆ አለመጨረስና መድኃኒቶችን ያለአግባብ መጠቀም ለችግሩ መባባስ ዋነኛ መንስኤዎች ሆነዋል።
የዘርፉ ባለሙያዎች ይህንን የጤና ስጋት ዝምተኛው ወይም ቀዝቃዛው ሱናሚ ሲሉ ይጠሩታል።
እንደ ድንገተኛ ወረርሽኝ በአንድ ጊዜ ህዝብን ባያጠቃም በሂደት ግን በዝግታ እየተስፋፋ የዘመናዊ ሕክምና ስኬቶችንና መሠረቶችን ትልቅ አደጋ ላይ እየጣለ ይገኛል።
ስለሆነም መድኃኒቶችን በከፍተኛ ኃላፊነት መጠቀም፣ የሕክምና ባለሙያዎችን ምክር በአግባቡ መተግበርና ህብረተሰቡን ማስተማር የሁሉንም አካላት ርብርብ ይጠይቃል።
ዛሬ የምናሳየው ጥንቃቄና የምንወስደው እርምጃ ወደፊት ውጤታማና ፈዋሽ መድኃኒቶች እንዲኖሩን ለማድረግ ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
ሃና ልካስ
#amr #antimicrobialresistance #healthnews #publichealth #medicine #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
9 hours ago
ኢትዮጵያዊው የቴክኖሎጂ ስራ ፈጣሪ በሰፊቃድ ጌታቸው በአፍሪካ ምርጥ 100 የንግድ ጀግኖች ዝርዝር ውስጥ ተካተቱ
#fastmereja | የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኩባንያ የሆነው "ኢግል ላይን ሲስተም ቴክኖሎጂ" መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ በሰፊቃድ ጌታቸው፣ በ2026ቱ "አፍሪካ ቢዝነስ ሄሮውስ" (ABH) ውድድር ከመላው አፍሪካ ከተውጣጡ ከ24 ሺህ በላይ ተወዳዳሪዎች መካከል በማለፍ፣ በምርጥ 100 የንግድ ጀግኖች ዝርዝር ውስጥ መካተታቸው ተገለጸ።
በሰፊቃድ ጌታቸው የሚመራው "ኢግል ላይን ሲስተም ቴክኖሎጂ" በተለይም በፋይናንስ፣ በግብርና፣ በዲጂታል ክፍያ እና በቱሪዝም ዘርፎች ከሁለት ደርዘን በላይ የቴክኖሎጂ መፍትሄዎችን በማዘጋጀት ይታወቃል። በዘርፉ ካበረከቷቸው ፈጠራዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ከአንድ ሚሊየን ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የግብርና ግብዓት ግዥን ያቀለለው የ"ጌትፊ ኢንተርፕራይዝ" (GetFee Enterprise) የክፍያ ስብስብ መድረክ እና የዳሽን ባንክ የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ ዋነኞቹ ናቸው።
በተጨማሪም እንደ "ካሽ ጎ" (CashGo)፣ "ኢትዮ-ዳይሬክት ኮኔክት" (Ethio-Direct Connect) እና የ"ዱቤ አለ" (DubeAle) የክፍያ መድረክ የመሳሰሉ ፈጠራዎች በኢትዮጵያ የዲጂታል ፋይናንስ ስነ-ምህዳር ውስጥ ያላቸውን ተፅእኖ አሳይተዋል። ከእነዚህም ባሻገር ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ ማሰባሰቢያ የሆነውን "ItsMyDam.com" መድረክ በማልማትም ይታወቃሉ።
የአፍሪካ ቢዝነስ ሄሮውስ (ABH) ተነሳሽነት በ2018 ዓ.ም. በአሊባባ መስራች ጃክ ማ የተጀመረ ሲሆን፣ ዓላማውም በየአመቱ በአህጉሪቱ አስር ምርጥ ስራ ፈጣሪዎችን በመለየት የገንዘብ ድጋፍ፣ ስልጠና እና የአማካሪነት አገልግሎት መስጠት ነው። ለዘንድሮው የውድድር ዘመን በአጠቃላይ 1.5 ሚሊዮን ዶላር የሽልማት በጀት ተይዞለታል።
የሰፊቃድ ጌታቸው በምርጥ 100 ዝርዝር ውስጥ መካተት፣ ኢትዮጵያውያን ስራ ፈጣሪዎች በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያላቸውን አቅም በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማሳየትና አህጉራዊ ተወዳዳሪነትን ለመቀዳጀት እንደ ትልቅ ምዕራፍ ተወስዷል። ቀደም ሲል ከነበሩት ዓመታት አንጻር፣ በውድድሩ የኢትዮጵያውያን ተሳትፎ እየጨመረ መምጣቱን መረጃዎች ይጠቁማሉ።
#fastmereja | የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኩባንያ የሆነው "ኢግል ላይን ሲስተም ቴክኖሎጂ" መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ በሰፊቃድ ጌታቸው፣ በ2026ቱ "አፍሪካ ቢዝነስ ሄሮውስ" (ABH) ውድድር ከመላው አፍሪካ ከተውጣጡ ከ24 ሺህ በላይ ተወዳዳሪዎች መካከል በማለፍ፣ በምርጥ 100 የንግድ ጀግኖች ዝርዝር ውስጥ መካተታቸው ተገለጸ።
በሰፊቃድ ጌታቸው የሚመራው "ኢግል ላይን ሲስተም ቴክኖሎጂ" በተለይም በፋይናንስ፣ በግብርና፣ በዲጂታል ክፍያ እና በቱሪዝም ዘርፎች ከሁለት ደርዘን በላይ የቴክኖሎጂ መፍትሄዎችን በማዘጋጀት ይታወቃል። በዘርፉ ካበረከቷቸው ፈጠራዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ከአንድ ሚሊየን ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የግብርና ግብዓት ግዥን ያቀለለው የ"ጌትፊ ኢንተርፕራይዝ" (GetFee Enterprise) የክፍያ ስብስብ መድረክ እና የዳሽን ባንክ የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ ዋነኞቹ ናቸው።
በተጨማሪም እንደ "ካሽ ጎ" (CashGo)፣ "ኢትዮ-ዳይሬክት ኮኔክት" (Ethio-Direct Connect) እና የ"ዱቤ አለ" (DubeAle) የክፍያ መድረክ የመሳሰሉ ፈጠራዎች በኢትዮጵያ የዲጂታል ፋይናንስ ስነ-ምህዳር ውስጥ ያላቸውን ተፅእኖ አሳይተዋል። ከእነዚህም ባሻገር ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ ማሰባሰቢያ የሆነውን "ItsMyDam.com" መድረክ በማልማትም ይታወቃሉ።
የአፍሪካ ቢዝነስ ሄሮውስ (ABH) ተነሳሽነት በ2018 ዓ.ም. በአሊባባ መስራች ጃክ ማ የተጀመረ ሲሆን፣ ዓላማውም በየአመቱ በአህጉሪቱ አስር ምርጥ ስራ ፈጣሪዎችን በመለየት የገንዘብ ድጋፍ፣ ስልጠና እና የአማካሪነት አገልግሎት መስጠት ነው። ለዘንድሮው የውድድር ዘመን በአጠቃላይ 1.5 ሚሊዮን ዶላር የሽልማት በጀት ተይዞለታል።
የሰፊቃድ ጌታቸው በምርጥ 100 ዝርዝር ውስጥ መካተት፣ ኢትዮጵያውያን ስራ ፈጣሪዎች በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያላቸውን አቅም በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማሳየትና አህጉራዊ ተወዳዳሪነትን ለመቀዳጀት እንደ ትልቅ ምዕራፍ ተወስዷል። ቀደም ሲል ከነበሩት ዓመታት አንጻር፣ በውድድሩ የኢትዮጵያውያን ተሳትፎ እየጨመረ መምጣቱን መረጃዎች ይጠቁማሉ።
11 hours ago
ጀግናዋ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ የረዳት ኮሚሽነርነት ማዕረግ አገኘች
#fastmereja I የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የስፖርት ክለብ እንዲሁም የሙዚቃና ቴአትር ቡድን የተመሠረተበት 40ኛ ዓመት ክብረ በዓል በአድዋ ድል መታሰቢያ በድምቀት ተከብሯል።
በዚሁ መድረክ ላይ በኦሎምፒክና በዓለም ሻምፒዮና ውድድሮች በርካታ ሜዳሊያዎችን በማምጣት የሀገርን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ ላደረገችው ጀግናዋ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ የተቋሙ ከፍተኛ የዕድገት እርከን የሆነው የረዳት ኮሚሽነርነት ማዕረግ ተሰጥቷታል።
በዕለቱም ለረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ፣ ለኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን፣ ለኮማንደር ፋጡማ ሮባ፣ ለኮማንደር አትሌት ሰለሞን ባረጋ እና ለምክትል ኮማንደር ሰንበሬ ተፈሪ የዕውቅናና ሽልማት ፕሮግራም ተካሂዷል።
በተጨማሪም በአሰልጣኝነት ከ30 ዓመታት በላይ በማገልገል የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱት ረዳት ኮሚሽነር ሁሴን ሸቦ የኒሻን ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን፤ በኪነ-ጥበቡ ዘርፍ ለሀገር ትልቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የሙዚቃና ቴአትር ቡድኑ አባላትም ዕውቅና ተሰጥቷል።
በክብረ በዓሉ ላይ የተገኙት የፍትሕ ሚኒስትር ሐና አርዓያሥላሴ የኮሚሽኑ የስፖርት ክለብ ባለፉት 40 ዓመታት እውቅ ጀግኖችን በማፍራት በኩል የላቀ ሚና መጫወቱን ጠቅሰው፤ ተቋሙ ይህንኑ አበረታች ሥራውን ይበልጥ ዘመናዊ በማድረግ አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል።
#fastmereja I የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የስፖርት ክለብ እንዲሁም የሙዚቃና ቴአትር ቡድን የተመሠረተበት 40ኛ ዓመት ክብረ በዓል በአድዋ ድል መታሰቢያ በድምቀት ተከብሯል።
በዚሁ መድረክ ላይ በኦሎምፒክና በዓለም ሻምፒዮና ውድድሮች በርካታ ሜዳሊያዎችን በማምጣት የሀገርን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ ላደረገችው ጀግናዋ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ የተቋሙ ከፍተኛ የዕድገት እርከን የሆነው የረዳት ኮሚሽነርነት ማዕረግ ተሰጥቷታል።
በዕለቱም ለረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ፣ ለኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን፣ ለኮማንደር ፋጡማ ሮባ፣ ለኮማንደር አትሌት ሰለሞን ባረጋ እና ለምክትል ኮማንደር ሰንበሬ ተፈሪ የዕውቅናና ሽልማት ፕሮግራም ተካሂዷል።
በተጨማሪም በአሰልጣኝነት ከ30 ዓመታት በላይ በማገልገል የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱት ረዳት ኮሚሽነር ሁሴን ሸቦ የኒሻን ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን፤ በኪነ-ጥበቡ ዘርፍ ለሀገር ትልቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የሙዚቃና ቴአትር ቡድኑ አባላትም ዕውቅና ተሰጥቷል።
በክብረ በዓሉ ላይ የተገኙት የፍትሕ ሚኒስትር ሐና አርዓያሥላሴ የኮሚሽኑ የስፖርት ክለብ ባለፉት 40 ዓመታት እውቅ ጀግኖችን በማፍራት በኩል የላቀ ሚና መጫወቱን ጠቅሰው፤ ተቋሙ ይህንኑ አበረታች ሥራውን ይበልጥ ዘመናዊ በማድረግ አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል።
11 hours ago
የተስፋው ትውልድ አሻራ፡ ከሀገራዊ ራዕይ እስከ ዓለም አቀፍ ልዕልና
**************
ሀገር ማለት የትናንት ታሪክ፣ የዛሬ ጥረት እና የነገ ተስፋ ድምር ውጤት ናት። ዛሬ የምናሳርፈው እያንዳንዱ አሻራ ለነገው ትውልድ የምናወርሰው የእድገት እና የሰላም ተሥፋ ነው።
በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መሪነት ይፋ የተደረገው የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ በአጭር ጊዜ ውስጥ አዲስ ሀገራዊ እይታ መፍጠር ችሏል። የኢትዮጵያ መንግስት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የወሰደው ቁርጠኝነት የሚመነጨው ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የ"መደመር" ዕሳቤ ነው።
ይህ ዕሳቤ በአረንጓዴ አሻራ በተግባር ሲተረጎም አካባቢን፣ ኢኮኖሚን እና ብሔራዊ ማንነትን በማዋሃድ አዲስ ዓይነት ስነ-ምህዳራዊ የመንግስት አስተዳደር እንዲፈጠር አድርጓል።
ታሪክ ሰሪው የመደመር ትውልድ ደግሞ ይህንን የሀገር ውስጥ ራዕይ ይዞ በመነሳት፣ ታላላቅ ሀገራዊና አህጉራዊ ብሎም ዓለምአቀፋዊ ጉዳዮችን በብቃት እየከወነ ይገኛል።
የአረንጓዴ አሻራ ጉዳይ አንድምታው ከችግኝ ተከላ የዘለለ መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ያለው ይህ ትውልድ፣ የራሱን አቅምና ሁለንተናዊ ብቃት በዓለም አደባባይ እያስመሰከረ ነው።
የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የትናንት የነጻነት አርበኝነታችንን በተፈጥሮ ጥበቃ የምንደግምበት የዘመናችን ድንቅ «ዓድዋ» ነው። ይህ የዘመናችን አድዋ ደግሞ የዛሬውን «የመደመር ትውልድ» የታሪክ አሻራ እና ሁለንተናዊ አቅም የሚፈትን ታላቅ አገራዊ ጥሪ ነው።
የዛሬው የመደመር ትውልድ እውቀቱን፣ ጉልበቱንና ፍቅሩን አስተባብሮ በተከታታይ ዓመታት አገሩ አረንጓዴ እያለበሳት ይገኛል። ዛሬ በእኛ (በመደመር) ትውልድ ጥረት እየተሰራ ያለ ስራ አገራችን የምግብ ዋስትናዋ በዘላቂነት የተረጋገጠና የአየር ንብረት መዛባት የማይበግራት ጽኑ እንድትሆን ያደርጋታል።
"የችግኝ ተከላ ተግባራችን ስለ ዛፎች ብቻ ሳይሆን ለወደፊቱ ለትውልድ ጥላ እና ተስፋን ስለመፍጠር ነው።" የሚለውን የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መርህ በመከተል እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ያሉ የዘመናችንን ሜጋ ፕሮጀክቶች ከደለል የሚታደግ፣ በግብርናው ዘርፍ የምግብ ሉዓላዊነትን የሚያረጋግጥ፣ በኢንዱስትሪው ለሚፈጠሩ የግብርና ማቀነባበሪያዎች ጥሬ ዕቃ የሚያቀርብ እና በአጠቃላይ በኢኮኖሚ, በልማት እና በማህበራዊ ስነ-ልቦና ላይ ጠንካራ መሠረት የሚጥል ሁለንተናዊ የብልፅግና ጉዞ ነው።
ይህም የመደመር ትውልድ የተፈጥሮ ሚዛንን ከመጠበቅ ባሻገር ሀገራዊ የልማት ምሰሶዎችን እንዴት ማፅናት እንደሚቻል ያሳየበት ህያው ማረጋገጫ ነው።
"ተስፋን እንትከል" ሲባል መሬት ላይ ችግኝ ማፅደቃችን ብቻ ሳይሆን፣ በልጆቻችን እና በቀጣዩ ትውልድ አዕምሮ ውስጥ የሀገር ፍቅርን፣ አብሮነትን እና የማይበገር ጥንካሬን መዝራታችን ነው።
የትናንት ታሪካችን የቱንም ያህል በፈተናዎች የተሞላ ቢሆንም ዛሬ የመደመር ትውልድ በእጆቹ የሚተክለው ተስፋ፣ ለነገው ትውልድ የማያልፍ ጥላ፣ የማይነጥፍ የኢኮኖሚ በረከት እና ቀና ብሎ የሚኮራባት ቅርስ ሆኖ ይፀድቃል። ስለዚህ ተስፋችንን እንትከል፤ የነገዋን ብሩህ ኢትዮጵያ ዛሬ በጋራ እንገንባ!
በበረከት ሽመልስ
Ethiopian Broadcasting Corporation #የመደመርትውልድ #ethiopia #greenliving #አረንጓዴአሻራ #ተፈጥሮ #ኢትዮጵያ
**************
ሀገር ማለት የትናንት ታሪክ፣ የዛሬ ጥረት እና የነገ ተስፋ ድምር ውጤት ናት። ዛሬ የምናሳርፈው እያንዳንዱ አሻራ ለነገው ትውልድ የምናወርሰው የእድገት እና የሰላም ተሥፋ ነው።
በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መሪነት ይፋ የተደረገው የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ በአጭር ጊዜ ውስጥ አዲስ ሀገራዊ እይታ መፍጠር ችሏል። የኢትዮጵያ መንግስት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የወሰደው ቁርጠኝነት የሚመነጨው ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የ"መደመር" ዕሳቤ ነው።
ይህ ዕሳቤ በአረንጓዴ አሻራ በተግባር ሲተረጎም አካባቢን፣ ኢኮኖሚን እና ብሔራዊ ማንነትን በማዋሃድ አዲስ ዓይነት ስነ-ምህዳራዊ የመንግስት አስተዳደር እንዲፈጠር አድርጓል።
ታሪክ ሰሪው የመደመር ትውልድ ደግሞ ይህንን የሀገር ውስጥ ራዕይ ይዞ በመነሳት፣ ታላላቅ ሀገራዊና አህጉራዊ ብሎም ዓለምአቀፋዊ ጉዳዮችን በብቃት እየከወነ ይገኛል።
የአረንጓዴ አሻራ ጉዳይ አንድምታው ከችግኝ ተከላ የዘለለ መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ያለው ይህ ትውልድ፣ የራሱን አቅምና ሁለንተናዊ ብቃት በዓለም አደባባይ እያስመሰከረ ነው።
የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የትናንት የነጻነት አርበኝነታችንን በተፈጥሮ ጥበቃ የምንደግምበት የዘመናችን ድንቅ «ዓድዋ» ነው። ይህ የዘመናችን አድዋ ደግሞ የዛሬውን «የመደመር ትውልድ» የታሪክ አሻራ እና ሁለንተናዊ አቅም የሚፈትን ታላቅ አገራዊ ጥሪ ነው።
የዛሬው የመደመር ትውልድ እውቀቱን፣ ጉልበቱንና ፍቅሩን አስተባብሮ በተከታታይ ዓመታት አገሩ አረንጓዴ እያለበሳት ይገኛል። ዛሬ በእኛ (በመደመር) ትውልድ ጥረት እየተሰራ ያለ ስራ አገራችን የምግብ ዋስትናዋ በዘላቂነት የተረጋገጠና የአየር ንብረት መዛባት የማይበግራት ጽኑ እንድትሆን ያደርጋታል።
"የችግኝ ተከላ ተግባራችን ስለ ዛፎች ብቻ ሳይሆን ለወደፊቱ ለትውልድ ጥላ እና ተስፋን ስለመፍጠር ነው።" የሚለውን የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መርህ በመከተል እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ያሉ የዘመናችንን ሜጋ ፕሮጀክቶች ከደለል የሚታደግ፣ በግብርናው ዘርፍ የምግብ ሉዓላዊነትን የሚያረጋግጥ፣ በኢንዱስትሪው ለሚፈጠሩ የግብርና ማቀነባበሪያዎች ጥሬ ዕቃ የሚያቀርብ እና በአጠቃላይ በኢኮኖሚ, በልማት እና በማህበራዊ ስነ-ልቦና ላይ ጠንካራ መሠረት የሚጥል ሁለንተናዊ የብልፅግና ጉዞ ነው።
ይህም የመደመር ትውልድ የተፈጥሮ ሚዛንን ከመጠበቅ ባሻገር ሀገራዊ የልማት ምሰሶዎችን እንዴት ማፅናት እንደሚቻል ያሳየበት ህያው ማረጋገጫ ነው።
"ተስፋን እንትከል" ሲባል መሬት ላይ ችግኝ ማፅደቃችን ብቻ ሳይሆን፣ በልጆቻችን እና በቀጣዩ ትውልድ አዕምሮ ውስጥ የሀገር ፍቅርን፣ አብሮነትን እና የማይበገር ጥንካሬን መዝራታችን ነው።
የትናንት ታሪካችን የቱንም ያህል በፈተናዎች የተሞላ ቢሆንም ዛሬ የመደመር ትውልድ በእጆቹ የሚተክለው ተስፋ፣ ለነገው ትውልድ የማያልፍ ጥላ፣ የማይነጥፍ የኢኮኖሚ በረከት እና ቀና ብሎ የሚኮራባት ቅርስ ሆኖ ይፀድቃል። ስለዚህ ተስፋችንን እንትከል፤ የነገዋን ብሩህ ኢትዮጵያ ዛሬ በጋራ እንገንባ!
በበረከት ሽመልስ
Ethiopian Broadcasting Corporation #የመደመርትውልድ #ethiopia #greenliving #አረንጓዴአሻራ #ተፈጥሮ #ኢትዮጵያ
11 hours ago
ታዋቂዋ የአትሌቶች መፍለቂያ ቦቆጂ ከተማ የልወቅሽ የኢትዮጵያ ክላሲክ 2018 የሩጫ ውድድርን በደመቀ ሁኔታ ማስተናገድ ጀመረች
#ethiopia | የበርካታ የዓለምና የኦሊምፒክ ሻምፒዮኖችን በማፍራት በዓለም አቀፍ ደረጃ በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀሰው የቦቆጂ ከተማ፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በመሆን ያዘጋጀውን ልወቅሽ የኢትዮጵያ ክላሲክ ታላቅ የሩጫ ውድድር በዛሬው ዕለት ማስተናገድ ጀምራለች።
ውድድሩ መነሻና መድረሻውን ታሪካዊው የቦቆጂ ስታዲየም ላይ ያደረገ ሲሆን፣ ከ100 በላይ አንጋፋና ፕሮፌሽናል አትሌቶች፣ ከ2 ሺህ 500 በላይ የቦቆጂ ከተማ ነዋሪዎች እንዲሁም ከአዲስ አበባ የተጓዙ ከ70 በላይ የስፖርቱ አፍቃሪያን ተሳታፊ ሆነዋል።
ይህ ትልቅ ስፖርታዊ መርሃ ግብር የአትሌቲክስ ስፖርትን ለማሳደግ ከሚኖረው ሚና ባሻገር፣ የቦቆጂን ከተማ የቱሪዝም መስህቦችና አቅሞች ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ጎብኝዎች በሰፊው ለማስተዋወቅ ታላቅ ዕድል የፈጠረ ነው።
የመጀመሪያው ምዕራፉ በደብረ ብርሃን ከተማ ተጀምሮ አሁን በቦቆጂ ይፋዊ ጉዞውን የቀጠለው ይህ መርሃ ግብር፣ በኢትዮጵያ የስፖርት ቱሪዝም ልማት ላይ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ክስተት ሆኗል።
በዚህ ደማቅ የማስጀመሪያ ዝግጅት ላይ የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እንደገና አበበ፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ መኪዩ መሀመድ፣ የአርሲ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኢብራሒም ከድር እና የቦቆጂ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ ብርሃኔ ነገሰ ተገኝተዋል።
በተጨማሪም ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የቱሪዝም ዘርፍ ተወካዮች፣ ታዋቂ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችና የብዙኃን መገናኛ ባለሙያዎች በከተማዋ በመገኘት መርሃ ግብሩን ታድመዋል።
#bekoji #ethiopianclassic #greatethiopianrun #sportstourism #tourismethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የበርካታ የዓለምና የኦሊምፒክ ሻምፒዮኖችን በማፍራት በዓለም አቀፍ ደረጃ በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀሰው የቦቆጂ ከተማ፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በመሆን ያዘጋጀውን ልወቅሽ የኢትዮጵያ ክላሲክ ታላቅ የሩጫ ውድድር በዛሬው ዕለት ማስተናገድ ጀምራለች።
ውድድሩ መነሻና መድረሻውን ታሪካዊው የቦቆጂ ስታዲየም ላይ ያደረገ ሲሆን፣ ከ100 በላይ አንጋፋና ፕሮፌሽናል አትሌቶች፣ ከ2 ሺህ 500 በላይ የቦቆጂ ከተማ ነዋሪዎች እንዲሁም ከአዲስ አበባ የተጓዙ ከ70 በላይ የስፖርቱ አፍቃሪያን ተሳታፊ ሆነዋል።
ይህ ትልቅ ስፖርታዊ መርሃ ግብር የአትሌቲክስ ስፖርትን ለማሳደግ ከሚኖረው ሚና ባሻገር፣ የቦቆጂን ከተማ የቱሪዝም መስህቦችና አቅሞች ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ጎብኝዎች በሰፊው ለማስተዋወቅ ታላቅ ዕድል የፈጠረ ነው።
የመጀመሪያው ምዕራፉ በደብረ ብርሃን ከተማ ተጀምሮ አሁን በቦቆጂ ይፋዊ ጉዞውን የቀጠለው ይህ መርሃ ግብር፣ በኢትዮጵያ የስፖርት ቱሪዝም ልማት ላይ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ክስተት ሆኗል።
በዚህ ደማቅ የማስጀመሪያ ዝግጅት ላይ የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እንደገና አበበ፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ መኪዩ መሀመድ፣ የአርሲ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኢብራሒም ከድር እና የቦቆጂ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ ብርሃኔ ነገሰ ተገኝተዋል።
በተጨማሪም ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የቱሪዝም ዘርፍ ተወካዮች፣ ታዋቂ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችና የብዙኃን መገናኛ ባለሙያዎች በከተማዋ በመገኘት መርሃ ግብሩን ታድመዋል።
#bekoji #ethiopianclassic #greatethiopianrun #sportstourism #tourismethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
18 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) በፊፋ የዓለም ደረጃ ከምርጥ 10ሩ ውስጥ በሚገኙት ብራዚል እና ሞሮኮ መካከል በከፍተኛ ጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የምድብ ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ የአቻ ውጤት ተጠናቋል። በከፍተኛ ፉክክር እና ማራኪ እንቅስቃሴ በታጀበው የዚህ ጨዋታ የመጀመሪያ አጋማሽ፣ ሁለቱም ቡድኖች ያሳዩት የጨዋታ ጥራት እጅግ አስደናቂ ነበር። በተለይም ሞሮኮዎች በኳስ ቁጥጥር እና በጉልበት ብልጫ በመውሰድ በኢስማኤል ሳይባሪ አስገራሚ የቺፕ ግብ ቀዳሚ መሆን ቢችሉም፣ የብራዚሉ ኮከብ ቪኒሽየስ ጁኒየር ብዙም ሳይቆይ ባስቆጠራት ኃይለኛ እና ማራኪ ግብ ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ 1 ለ 1 መመዝገቡ ይታወሳል።
ይሁን እንጂ ከእረፍት መልስ የታየው የጨዋታው ሁለተኛ አጋማሽ ከመጀመሪያው 45 ደቂቃ ጋር ሲነጻጸር ፍጹም ተቃራኒ ገጽታ ነበረው። የቀድሞው የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን አጥቂ አላን ሺረር እንደገመገመው በሁለተኛው አጋማሽ ሁለቱም ቡድኖች ኳስን በብዛት በማንከባለል የኳስ ቅብብሎችን ቢያደርጉም፣ በማጥቃት ሲሶ (final third) ላይ ግን በቂ የሆነ የጨዋታ ጥራት እና አደገኛ ሙከራዎችን ማሳየት አልቻሉም። ሌላኛው የቀድሞ እንግሊዛዊ አጥቂ ዲዮን ዳብሊንም በበኩሉ፣ ሁለተኛው አጋማሽ ለሁለቱም ቡድኖች ያን ያህል ማራኪ እንዳልነበር እና ሁለቱም በአንድ ነጥብ መውጣትን የመረጡ እንደሚመስሉ አስተያየቱን ሰጥቷል።
በዚህ ጨዋታ ከግቦቹ ባሻገር የስታዲየሙን ትኩረት በከፍተኛ ሁኔታ የሳበው የ18 ዓመቱ የሞሮኮ ታዳጊ አዩብ ቡአዲ ነው። ታዳጊው በእድሜው ልክ የማይመጥን አስገራሚ የጨዋታ ብልህነት እና እርጋታ በማሳየት፣ ልምድ ባካበቱት የብራዚል የመሃል ሜዳ ተጫዋቾች ላይ ብልጫ መውሰድ ችሏል። የጨዋታው ኮከብነት ክብር አብዛኛውን ጊዜ ግብ ላስቆጠሩ ተጫዋቾች የሚሰጥ ቢሆንም፣ ኳስን ደጋግሞ በማስጣል እና ቡድኑን ወደ ፊት በማሻገር ላሳየው ፍጹም የብስለት እንቅስቃሴ ቡአዲ የዚህ ክብር ዋነኛ ተፎካካሪ መሆን ይገባዋል። በአሁኑ ወቅት ለፈረንሳዩ ክለብ ሊል የሚጫወተው ይህ ድንቅ ታዳጊ፣ በዓለም ዋንጫ መድረክ በብራዚል ላይ ይህን የመሰለ ብቃት ካሳየ በአጭር ጊዜ ውስጥ በታላላቅ የአውሮፓ ክለቦች መነጠቁ አይቀርም።
ጨዋታው ወደ ማብቂያው ሲቃረብ 10 ተጨማሪ ደቂቃዎች መታየታቸው በስታዲየሙ ደጋፊዎች እና በጋዜጠኞች ማረፊያ ዘንድ ያልተጠበቀ ድንጋጤን ፈጥሮ ነበር። ይህ ሰፊ ተጨማሪ ሰዓት አሸናፊ ግብ ለማስቆጠር በቂ ጊዜ የሰጠ ሲሆን፣ ብራዚሎችም በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች የማሸነፊያዋን ግብ ፍለጋ በሞሮኮ ላይ ከፍተኛ ጫና መፍጠር ችለው ነበር። በተለይም ማቲየስ ኩንሃ ያሻማቸውን ተከታታይ እና አደገኛ የማዕዘን ምቶች የሞሮኮው ግብ ጠባቂ ያሲን ቡኑ በድንቅ ብቃት በሁለት እጆቹ በቡጢ እየገጨ ያወጣቸው ሲሆን፣ ከዳኒሎ ሳንቶስ የተሞከረውን ኳስም በሚገርም ሁኔታ አድኖታል።
የያሲን ቡኑ የጀግንነት ጥረት ታክሎበት ብራዚልን የመጨረሻ ደቂቃ ፈታኝ ጫናዎች መቋቋም የቻለችው ሞሮኮ ጨዋታውን 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት በስኬት ማጠናቀቅ ችላለች።
ይሁን እንጂ ከእረፍት መልስ የታየው የጨዋታው ሁለተኛ አጋማሽ ከመጀመሪያው 45 ደቂቃ ጋር ሲነጻጸር ፍጹም ተቃራኒ ገጽታ ነበረው። የቀድሞው የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን አጥቂ አላን ሺረር እንደገመገመው በሁለተኛው አጋማሽ ሁለቱም ቡድኖች ኳስን በብዛት በማንከባለል የኳስ ቅብብሎችን ቢያደርጉም፣ በማጥቃት ሲሶ (final third) ላይ ግን በቂ የሆነ የጨዋታ ጥራት እና አደገኛ ሙከራዎችን ማሳየት አልቻሉም። ሌላኛው የቀድሞ እንግሊዛዊ አጥቂ ዲዮን ዳብሊንም በበኩሉ፣ ሁለተኛው አጋማሽ ለሁለቱም ቡድኖች ያን ያህል ማራኪ እንዳልነበር እና ሁለቱም በአንድ ነጥብ መውጣትን የመረጡ እንደሚመስሉ አስተያየቱን ሰጥቷል።
በዚህ ጨዋታ ከግቦቹ ባሻገር የስታዲየሙን ትኩረት በከፍተኛ ሁኔታ የሳበው የ18 ዓመቱ የሞሮኮ ታዳጊ አዩብ ቡአዲ ነው። ታዳጊው በእድሜው ልክ የማይመጥን አስገራሚ የጨዋታ ብልህነት እና እርጋታ በማሳየት፣ ልምድ ባካበቱት የብራዚል የመሃል ሜዳ ተጫዋቾች ላይ ብልጫ መውሰድ ችሏል። የጨዋታው ኮከብነት ክብር አብዛኛውን ጊዜ ግብ ላስቆጠሩ ተጫዋቾች የሚሰጥ ቢሆንም፣ ኳስን ደጋግሞ በማስጣል እና ቡድኑን ወደ ፊት በማሻገር ላሳየው ፍጹም የብስለት እንቅስቃሴ ቡአዲ የዚህ ክብር ዋነኛ ተፎካካሪ መሆን ይገባዋል። በአሁኑ ወቅት ለፈረንሳዩ ክለብ ሊል የሚጫወተው ይህ ድንቅ ታዳጊ፣ በዓለም ዋንጫ መድረክ በብራዚል ላይ ይህን የመሰለ ብቃት ካሳየ በአጭር ጊዜ ውስጥ በታላላቅ የአውሮፓ ክለቦች መነጠቁ አይቀርም።
ጨዋታው ወደ ማብቂያው ሲቃረብ 10 ተጨማሪ ደቂቃዎች መታየታቸው በስታዲየሙ ደጋፊዎች እና በጋዜጠኞች ማረፊያ ዘንድ ያልተጠበቀ ድንጋጤን ፈጥሮ ነበር። ይህ ሰፊ ተጨማሪ ሰዓት አሸናፊ ግብ ለማስቆጠር በቂ ጊዜ የሰጠ ሲሆን፣ ብራዚሎችም በመጨረሻዎቹ ደቂቃዎች የማሸነፊያዋን ግብ ፍለጋ በሞሮኮ ላይ ከፍተኛ ጫና መፍጠር ችለው ነበር። በተለይም ማቲየስ ኩንሃ ያሻማቸውን ተከታታይ እና አደገኛ የማዕዘን ምቶች የሞሮኮው ግብ ጠባቂ ያሲን ቡኑ በድንቅ ብቃት በሁለት እጆቹ በቡጢ እየገጨ ያወጣቸው ሲሆን፣ ከዳኒሎ ሳንቶስ የተሞከረውን ኳስም በሚገርም ሁኔታ አድኖታል።
የያሲን ቡኑ የጀግንነት ጥረት ታክሎበት ብራዚልን የመጨረሻ ደቂቃ ፈታኝ ጫናዎች መቋቋም የቻለችው ሞሮኮ ጨዋታውን 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት በስኬት ማጠናቀቅ ችላለች።
23 hours ago
የአሜሪካዊው ፋንቱ ማንዶዬ ሞርጋን ፍሪማን በጎ ልብ
#ethiopia | በዓለም ዙሪያ በሚማርክ ድምፃቸው እና አስደናቂ የትወና ብቃታቸው የሚታወቁት አንጋፋው ተዋናይ ሞርጋን ፍሪማን፣ ትርጉም ያለው ለውጥ ለማምጣት የሚተጉ ታዋቂ የሰብዓዊ መብትና የበጎ አድራጎት አምባሳደር መሆናቸው ይነገራል።
የሳቸው ዘርፈ ብዙ የበጎ አድራጎት ስራዎች በተለያዩ ቁልፍ ዘርፎች ላይ ያተኮሩ ሲሆን፣ ይህም በማህበረሰቡ ውስጥ አዎንታዊ ተጽዕኖ ለመፍጠር ያላቸውን ጥልቅ ፍላጎት የሚያንጸባርቅ ነው።
ከእነዚህም የጎላ አስተዋፅኦዎቻቸው መካከል በተፈጥሮ አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የሚያደርጉት ድጋፍ በዋናነት ይጠቀሳል። አውዳሚ የሆኑ አውሎ ነፋሶች ባስከተሉት አደጋ የተረፉ ሰዎችን ለመደገፍ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብሮችን በግንባር ቀደምትነት አስተባብረዋል።
በተጨማሪም በዓለም አቀፍ ደረጃ በተፈጥሮ አደጋ ለሚጎዱ ሰዎች ፈጣን እርዳታ ለማድረግ "የግሬናዳ የዕርዳታ ፈንድን" የተሰኘ ኢኒሼቲቭ የነበራቸው ሲሆን፣ ይህ ተቋም አሁን ላይ “ፕላን ኢት ናው” ወደሚባል ዓለም አቀፍ ድርጅት ተሸጋግሯል።
ትምህርት የሌላኛው የበጎ አድራጎት ስራቸው የማዕዘን ድንጋይ ነው። እ.ኤ.አ. በ1991 በሚሲሲፒ ግዛት ውስጥ ለሚገኙ አቅመ ደካማ ታዳጊዎች የቅድመ መደበኛ ትምህርትን ለማስፋፋት ከልጃቸው ጋር በመሆን "የታላሃቺ ሪቨር ፋውንዴሽንን" መስርተዋል። ከዚህም ባሻገር፣ ለእንስሳት ደህንነት ልዩ ጥበቃ የሚያደርጉት ፍሪማን፤ እንደ 'ሚሲሲፒ የእንስሳት አድን ማህበር' ያሉ ድርጅቶችን በመደገፍ እና በእንስሳት ህክምና ኮሌጆች ውስጥ የጥናትና ምርምር ማዕከላትን በገንዘብ በማገዝ ላይ ይገኛሉ።
በእነዚህና መሰል ሰብዓዊ ተነሳሽነቶች፣ ሞርጋን ፍሪማን ተሰሚነታቸው እና ተጽዕኖ ፈጣሪነታቸው ከፊልም ኢንዱስትሪው መድረክ እና ከካሜራ ዕይታ ውጭ ጭምር ነው።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በዓለም ዙሪያ በሚማርክ ድምፃቸው እና አስደናቂ የትወና ብቃታቸው የሚታወቁት አንጋፋው ተዋናይ ሞርጋን ፍሪማን፣ ትርጉም ያለው ለውጥ ለማምጣት የሚተጉ ታዋቂ የሰብዓዊ መብትና የበጎ አድራጎት አምባሳደር መሆናቸው ይነገራል።
የሳቸው ዘርፈ ብዙ የበጎ አድራጎት ስራዎች በተለያዩ ቁልፍ ዘርፎች ላይ ያተኮሩ ሲሆን፣ ይህም በማህበረሰቡ ውስጥ አዎንታዊ ተጽዕኖ ለመፍጠር ያላቸውን ጥልቅ ፍላጎት የሚያንጸባርቅ ነው።
ከእነዚህም የጎላ አስተዋፅኦዎቻቸው መካከል በተፈጥሮ አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የሚያደርጉት ድጋፍ በዋናነት ይጠቀሳል። አውዳሚ የሆኑ አውሎ ነፋሶች ባስከተሉት አደጋ የተረፉ ሰዎችን ለመደገፍ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብሮችን በግንባር ቀደምትነት አስተባብረዋል።
በተጨማሪም በዓለም አቀፍ ደረጃ በተፈጥሮ አደጋ ለሚጎዱ ሰዎች ፈጣን እርዳታ ለማድረግ "የግሬናዳ የዕርዳታ ፈንድን" የተሰኘ ኢኒሼቲቭ የነበራቸው ሲሆን፣ ይህ ተቋም አሁን ላይ “ፕላን ኢት ናው” ወደሚባል ዓለም አቀፍ ድርጅት ተሸጋግሯል።
ትምህርት የሌላኛው የበጎ አድራጎት ስራቸው የማዕዘን ድንጋይ ነው። እ.ኤ.አ. በ1991 በሚሲሲፒ ግዛት ውስጥ ለሚገኙ አቅመ ደካማ ታዳጊዎች የቅድመ መደበኛ ትምህርትን ለማስፋፋት ከልጃቸው ጋር በመሆን "የታላሃቺ ሪቨር ፋውንዴሽንን" መስርተዋል። ከዚህም ባሻገር፣ ለእንስሳት ደህንነት ልዩ ጥበቃ የሚያደርጉት ፍሪማን፤ እንደ 'ሚሲሲፒ የእንስሳት አድን ማህበር' ያሉ ድርጅቶችን በመደገፍ እና በእንስሳት ህክምና ኮሌጆች ውስጥ የጥናትና ምርምር ማዕከላትን በገንዘብ በማገዝ ላይ ይገኛሉ።
በእነዚህና መሰል ሰብዓዊ ተነሳሽነቶች፣ ሞርጋን ፍሪማን ተሰሚነታቸው እና ተጽዕኖ ፈጣሪነታቸው ከፊልም ኢንዱስትሪው መድረክ እና ከካሜራ ዕይታ ውጭ ጭምር ነው።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Sponsored by
Surafel
23 hours ago
አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ የረዳት ኮሚሽነርነት ከፍተኛ የማዕረግ ዕድገት ተሰጣት
#ethiopia | ታዋቂዋ እና ተወዳጇ የረጅም ርቀት አትሌት ኮማንደር ጥሩነሽ ዲባባ የረዳት ኮሚሽነርነት ማዕረግ ተሸላሚ ሆናለች።
ይህ የሹመት መርሃ ግብር የተከናወነው የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የስፖርት ክለብ እንዲሁም የሙዚቃና ቴአትር ቡድን የተመሰረተበትን 40ኛ ዓመት በዓል ባከበረበት ወቅት ነው።
በዛሬው ዕለት ሰኔ 6 ቀን 2018 ዓ.ም በአድዋ ድል መታሰቢያ በተካሄደው የክብር ስነ ሥርዓት ላይ የፍትህ ሚኒስትሯ ሀና አርዕያ ስላሴን ጨምሮ በርካታ የሀገር መሪዎች፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም የስፖርትና የኪነጥበብ ዘርፍ ተወካዮች ታድመዋል።
ረዳት ኮሚሽነር አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ በዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች ላይ የሀገሯን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርጋ ያወለበለበች መሪ አትሌት ናት።
በአራት የኦሎምፒክ መድረኮች ላይ በመሳተፍ 3 የወርቅ እና 1 የነሀስ ሜዳሊያዎችን ያስመዘገበች ሲሆን በአጠቃላይ በተለያዩ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ከ15 በላይ የወርቅ ሜዳሊያዎችን ለሀገሯ በማበርከት ስሟ በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ ጀግና ናት።
ይህ አሁን የተሰጣት የረዳት ኮሚሽነርነት ማዕረግ በተቋሙ ውስጥ የሚሰጥ ከፍተኛ የማዕረግ ዕድገት መሆኑ ተገልጿል።
በዚሁ ታላቅ መርሃ ግብር ላይ ከጥሩነሽ ዲባባ በተጨማሪ ለሌሎች የሀገር ባለውለታ የሆኑ አንጋፋ ስፖርተኞች እና የኪነጥበብ ባለሙያዎች የዕውቅና እና የሽልማት ስነ ሥርዓት ተካሂዶላቸዋል።
በዚህም መሰረት በአትሌቲክስ ታሪክ የመጀመሪያዋ ጥቁር አፍሪካዊት የኦሎምፒክ አሸናፊ የሆነችው ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ፣ የማራቶን ጀግናዋ ኮማንደር ፋጡማ ሮባ፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዘዳንትና የሁለት ጊዜ የኦሎምፒክ እንዲሁም የሦስት ጊዜ የዓለም ሻምፒዮና የብር ሜዳሊያ ባለቤቱ አትሌት ስለሺ ስህን፣ ኮማንደር ሰለሞን ባረጋ እና ምክትል ኮሚሽነር ሰንበሬ ተፈሪ የክብር ሽልማታቸውን ተቀብለዋል።
በተጨማሪም በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ውስጥ ከሶስት አስርት ዓመታት በላይ በማሰልጠን ያገለገለው፣ በ7 ኦሎምፒክ እና በ12 የዓለም ሻምፒዮናዎች ላይ በመሳተፍ በርካታ ስኬታማ አትሌቶችን ያፈራው አዳኙ አሰልጣኝ ረዳት ኮሚሽነር ሁሴን ሸቦ የኒሻን ሽልማት ተበርክቶለታል።
በኪነጥበብ ዘርፍም የኮሚሽኑ የሙዚቃና ቴያትር ቡድን አባላት የነበሩት ድምፃዊ ደመረ ለገሰ፣ ድምፃዊ ተፈራ ነጋሽ፣ ድምፃዊ ምክትል ኮሚሽነር መላኩ እንግዳ፣ አርቲስት ፍሬህይወት ስዩም፣ ሳክስፎኒስት ዘሪሁን በለጠ እና ሌሎች ባለሙያዎች ላበረከቱት አስተዋጽኦ ተገቢው ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል።
#tiruneshdibaba #athletics #sport #ethiopianathletics #news #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ታዋቂዋ እና ተወዳጇ የረጅም ርቀት አትሌት ኮማንደር ጥሩነሽ ዲባባ የረዳት ኮሚሽነርነት ማዕረግ ተሸላሚ ሆናለች።
ይህ የሹመት መርሃ ግብር የተከናወነው የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን የስፖርት ክለብ እንዲሁም የሙዚቃና ቴአትር ቡድን የተመሰረተበትን 40ኛ ዓመት በዓል ባከበረበት ወቅት ነው።
በዛሬው ዕለት ሰኔ 6 ቀን 2018 ዓ.ም በአድዋ ድል መታሰቢያ በተካሄደው የክብር ስነ ሥርዓት ላይ የፍትህ ሚኒስትሯ ሀና አርዕያ ስላሴን ጨምሮ በርካታ የሀገር መሪዎች፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም የስፖርትና የኪነጥበብ ዘርፍ ተወካዮች ታድመዋል።
ረዳት ኮሚሽነር አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ በዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች ላይ የሀገሯን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ አድርጋ ያወለበለበች መሪ አትሌት ናት።
በአራት የኦሎምፒክ መድረኮች ላይ በመሳተፍ 3 የወርቅ እና 1 የነሀስ ሜዳሊያዎችን ያስመዘገበች ሲሆን በአጠቃላይ በተለያዩ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ከ15 በላይ የወርቅ ሜዳሊያዎችን ለሀገሯ በማበርከት ስሟ በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ ጀግና ናት።
ይህ አሁን የተሰጣት የረዳት ኮሚሽነርነት ማዕረግ በተቋሙ ውስጥ የሚሰጥ ከፍተኛ የማዕረግ ዕድገት መሆኑ ተገልጿል።
በዚሁ ታላቅ መርሃ ግብር ላይ ከጥሩነሽ ዲባባ በተጨማሪ ለሌሎች የሀገር ባለውለታ የሆኑ አንጋፋ ስፖርተኞች እና የኪነጥበብ ባለሙያዎች የዕውቅና እና የሽልማት ስነ ሥርዓት ተካሂዶላቸዋል።
በዚህም መሰረት በአትሌቲክስ ታሪክ የመጀመሪያዋ ጥቁር አፍሪካዊት የኦሎምፒክ አሸናፊ የሆነችው ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ፣ የማራቶን ጀግናዋ ኮማንደር ፋጡማ ሮባ፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዘዳንትና የሁለት ጊዜ የኦሎምፒክ እንዲሁም የሦስት ጊዜ የዓለም ሻምፒዮና የብር ሜዳሊያ ባለቤቱ አትሌት ስለሺ ስህን፣ ኮማንደር ሰለሞን ባረጋ እና ምክትል ኮሚሽነር ሰንበሬ ተፈሪ የክብር ሽልማታቸውን ተቀብለዋል።
በተጨማሪም በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ውስጥ ከሶስት አስርት ዓመታት በላይ በማሰልጠን ያገለገለው፣ በ7 ኦሎምፒክ እና በ12 የዓለም ሻምፒዮናዎች ላይ በመሳተፍ በርካታ ስኬታማ አትሌቶችን ያፈራው አዳኙ አሰልጣኝ ረዳት ኮሚሽነር ሁሴን ሸቦ የኒሻን ሽልማት ተበርክቶለታል።
በኪነጥበብ ዘርፍም የኮሚሽኑ የሙዚቃና ቴያትር ቡድን አባላት የነበሩት ድምፃዊ ደመረ ለገሰ፣ ድምፃዊ ተፈራ ነጋሽ፣ ድምፃዊ ምክትል ኮሚሽነር መላኩ እንግዳ፣ አርቲስት ፍሬህይወት ስዩም፣ ሳክስፎኒስት ዘሪሁን በለጠ እና ሌሎች ባለሙያዎች ላበረከቱት አስተዋጽኦ ተገቢው ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል።
#tiruneshdibaba #athletics #sport #ethiopianathletics #news #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 day ago
ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ2027 የሚካሄደውን የዓለም አቀፍ የፀረ-ዶፒንግ ትምህርት ጉባኤን እንድታስተናግድ በይፋ ተመረጠች
#ethiopia | ሀገራችን ኢትዮጵያ ለስፖርቱ ዘርፍ ዕድገት ለሰጠችው ልዩ ትኩረት ትልቅ ማሳያ የሚሆንና ከፍተኛ ፋይዳ ያለው ዓለም አቀፍ የባህልና የስፖርት ኩነትን የማዘጋጀት ዕድል አግኝታለች።
በዓለም አቀፉ የፀረ-ዶፒንግ ኤጀንሲ አስተናጋጅነት በየወቅቱ የሚካሄደው የዓለም አቀፍ የፀረ-ዶፒንግ ትምህርትና ሥልጠና ጉባኤ በፈረንጆቹ 2027 በኢትዮጵያ እንዲሰናዳ ተወስኗል።
ይህ ትልቅ መድረክ በፀረ-አበረታች ቅመሞች እንቅስቃሴ ላይ ሰፊ ተፅዕኖ ያለው ሲሆን ቀደም ሲል እ.ኤ.አ በ2018 በቻይና ቤጂንግ፣ በ2022 በአውስትራሊያ ሲድኒ እንዲሁም በ2024 በፈረንሳይ ፓሪስ መካሄዱ ይታወሳል።
ይህ የዓለም አቀፍ የፀረ-ዶፒንግ ትምህርት ጉባኤ በአፍሪካ አህጉር ሲካሄድ የአሁኑ የመጀመሪያው ነው። በመሆኑም መድረኩ ለሀገራችን መልካም ገጽታ ግንባታና ለስፖርት ቱሪዝም ዕድገት ከሚያበረክተው ዘርፈ ብዙ ጥቅም ባለፈ በአህጉር ደረጃ ንጹህ ስፖርትን ለማስፋፋትና የፀረ-አበረታች ቅመሞች ቁጥጥርን ይበልጥ ለማጠናከር ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
ከምንም በላይ ደግሞ ኢትዮጵያ የአበረታች ቅመሞች ወይም የዶፒንግ መከላከል ሥራዎችን በመደበኛው የትምህርት ሥርዓት ውስጥ በማካተት፣ ጠንካራ የሕግ ማዕቀፎችን በማውጣት፣ እንዲሁም አስተማማኝ የምርመራና የቁጥጥር ሥርዓቶችን በመዘርጋት ረገድ ያስመዘገበቻቸውን በርካታ ስኬቶች ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በተግባር ለማሳየትና ለማስተዋወቅ ትልቅ ዕድል ይፈጥራል።
#wada #globaleducationconference #cleansport #antidoping #sportstourism #africasports #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ሀገራችን ኢትዮጵያ ለስፖርቱ ዘርፍ ዕድገት ለሰጠችው ልዩ ትኩረት ትልቅ ማሳያ የሚሆንና ከፍተኛ ፋይዳ ያለው ዓለም አቀፍ የባህልና የስፖርት ኩነትን የማዘጋጀት ዕድል አግኝታለች።
በዓለም አቀፉ የፀረ-ዶፒንግ ኤጀንሲ አስተናጋጅነት በየወቅቱ የሚካሄደው የዓለም አቀፍ የፀረ-ዶፒንግ ትምህርትና ሥልጠና ጉባኤ በፈረንጆቹ 2027 በኢትዮጵያ እንዲሰናዳ ተወስኗል።
ይህ ትልቅ መድረክ በፀረ-አበረታች ቅመሞች እንቅስቃሴ ላይ ሰፊ ተፅዕኖ ያለው ሲሆን ቀደም ሲል እ.ኤ.አ በ2018 በቻይና ቤጂንግ፣ በ2022 በአውስትራሊያ ሲድኒ እንዲሁም በ2024 በፈረንሳይ ፓሪስ መካሄዱ ይታወሳል።
ይህ የዓለም አቀፍ የፀረ-ዶፒንግ ትምህርት ጉባኤ በአፍሪካ አህጉር ሲካሄድ የአሁኑ የመጀመሪያው ነው። በመሆኑም መድረኩ ለሀገራችን መልካም ገጽታ ግንባታና ለስፖርት ቱሪዝም ዕድገት ከሚያበረክተው ዘርፈ ብዙ ጥቅም ባለፈ በአህጉር ደረጃ ንጹህ ስፖርትን ለማስፋፋትና የፀረ-አበረታች ቅመሞች ቁጥጥርን ይበልጥ ለማጠናከር ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
ከምንም በላይ ደግሞ ኢትዮጵያ የአበረታች ቅመሞች ወይም የዶፒንግ መከላከል ሥራዎችን በመደበኛው የትምህርት ሥርዓት ውስጥ በማካተት፣ ጠንካራ የሕግ ማዕቀፎችን በማውጣት፣ እንዲሁም አስተማማኝ የምርመራና የቁጥጥር ሥርዓቶችን በመዘርጋት ረገድ ያስመዘገበቻቸውን በርካታ ስኬቶች ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በተግባር ለማሳየትና ለማስተዋወቅ ትልቅ ዕድል ይፈጥራል።
#wada #globaleducationconference #cleansport #antidoping #sportstourism #africasports #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 day ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የካርሎ አንቸሎቲ የጋዜጣዊ መግለጫ ሊጠናቀቅ ሲል.. ጣሊያናዊው አሰልጣኝ ሁሌም በሚታወቁበት የሰከነ እና ጥልቅ በሆነ መንገድ ማንም ሊያነሳው ያልደፈረውን ጉዳይ አንስተው መናገር ጀመሩ። በግንቦት ወር መገባደጃ ላይ ብራዚል ከፓናማ ጋር ለምታደርገው የወዳጅነት ጨዋታ አስቀድሞ፣ አዲሱ የብራዚል ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ አንቸሎቲ እንዲህ አሉ፡...
"ሰዎች አሁን ላይ ብራዚል ኮከብ ተጫዋች የላትም ሲሉ እሰማለሁ። ምናልባት እውነት ሊሆን ይችላል። እንደ ፔሌ፣ ሮማሪዮ ወይም ሮናልዶ አይነት ተጫዋች ላይኖረን ይችላል፤ ነገር ግን የጋራ ኃላፊነት ስሜት ሊኖረን ይችላል፣ ያ ደግሞ እጅግ ኃይለኛ መሳሪያ ነው።"
ይህ የአንቸሎቲ ንግግር የብዙዎችን ቀልብ የሳበው፣ የሪያል ማድሪዱ ኮከብ ቪኒሽየስ ጁኒየር እስካሁን ድረስ የብሔራዊ ቡድኑ የማይነካ መሪ ይሆናል ተብሎ ሲጠበቅ... በተግባር ግን ያ ባለመሆኑ ነው። በ2022ቱ የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ በክሮኤሺያ በመለያ ምት ተሸንፈው ከወጡ ከአራት ዓመታት በኋላም.... በ25 ዓመቱ አጥቂ ላይ አሁንም በርካታ ጥያቄዎች ይነሳሉ።
ይህ ጥርጣሬ ምን ያህል ከፍ እንዳለ ለማሳየት... በመጋቢት ወር ብራዚል በፈረንሳይ 2ለ1 መሸነፏን ተከትሎ፣ በሀገሪቱ የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች ላይ "ቪኒሽየስ በመጀመሪያ አሰላለፍ ውስጥ መካተት ይገባዋል ወይ?" የሚል የከረረ ክርክር እስከመክፈት ደርሷል። በክለብ ደረጃ ለቪኒሽየስ እጅግ ስኬታማ ጊዜያትን ያመጣው እና ትልቅ ተጽዕኖ የፈጠረው አንቸሎቲ ብሔራዊ ቡድኑን ቢረከብም፣ "ቪኒሽየስ በሪያል ማድሪድ የሚያሳየውን ድንቅ አቋም ለምን በብሔራዊ ቡድን መድገም አቃተው?" የሚለው ጥያቄ አሁንም እንደ ጥላ እየተከተለው ነው።
በእርግጥም ቪኒሽየስ በዚህ የዓለም ዋንጫ ዑደት ውስጥ በብሔራዊ ቡድኑ ብዙ የግብ ተሳትፎ ያደረገ ተጫዋች ነው፤ ሆኖም በ28 ጨዋታዎች 7 ግቦችን እና 6 አሲስቶችን ብቻ ማስመዝገቡ ለሱ ደረጃ አነስተኛ ነው። በ2018 እና 2022 የዓለም ዋንጫዎች የብራዚል ብሔራዊ ቡድን ምክትል አሰልጣኝ የነበረው ክሌበር ዣቪየር ይህንን ሲያብራራ "በክለብ ደረጃ የምታሳየውን አቋም በብሔራዊ ቡድን መድገም እጅግ ከባድ ነው። ክለብ ውስጥ የተለየ ልምምድ፣ የተለየ የጨዋታ መንገድ እና የዕለት ተዕለት ቆይታ አለ። ግልጹ ምሳሌ የሜሲ እና የአርጀንቲና ጉዳይ ነው። ሜሲ ሁሌም ይተች ነበር፣ ሊሳካለት የቻለው በ2022 ነው። ምክንያቱም አርጀንቲና ቡድን መገንባት ስለቻለች ነው። ለተጫዋች ተገቢውን መዋቅር መፍጠር ወሳኝ ነው" ይላል።
ቪኒሽየስም ይህንን እውነታ አይክድም። በቅርቡ ለካዜ ቲቪ በሰጠው ቃለ ምልልስ ላይ፣ "በክለብ ውስጥ በየሶስት ቀኑ አዲስ ዕድል አለ። ከ10 ጨዋታዎች ሁለቱን መጥፎ ብጫወት ማንም ብዙ አያወራም። በብሔራዊ ቡድን ግን በአንድ ጨዋታ እና በሌላኛው መካከል ያለው ጊዜ ረጅም ነው፤ ጫናውም ሁልጊዜ ከፍተኛ ነው። ሰዎች ሁሌም በምርጥ አቋሜ ላይ እንድገኝ ይጠብቃሉ። ነገር ግን ወደ ዓለም ዋንጫ ሄጄ አራት ወይም አምስት ግቦችን አግብቼ ሻምፒዮን ብንሆን፣ ታሪኩ ሙሉ በሙሉ ይቀየራል። ያኔ መጥፎ በተጫወትኩባቸው ጨዋታዎች ላይ እንኳን ለዓለም ዋንጫ እየተዘጋጀሁ እንደነበር አድርገው ያወራሉ" ብሏል።
ለብራዚል ብሔራዊ ቡድን መጫወት ለቪኒሽየስ ቀላል ሆኖ አያውቅም። አንድ የቀድሞ የብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ እንዳሉት፣ የ2024 የባሎን ዶር ሁለተኛ ደረጃን የያዘው ቪኒሽየስ፣ "ሁሌም ዋናው ተዋናይ የመሆን ከፍተኛ ጉጉት" ያጠቃዋል። ቪኒሽየስ በሙያ ዘመኑ ሁሉ የለመደውም ይሄንኑ የዋና ተዋናይነት ቦታ ነው።
ወደ ሁለተኛው የዓለም ዋንጫው ሲያቀና... ቪኒሽየስ 14 የንግድ ስምምነቶች ያሉት ሲሆን፣ ይህ ከማንኛውም ብራዚላዊ ተጫዋች የላቀ ነው። ከሜዳ ውጪ ይህ ሁሉ ስኬት ቢኖረውም፣ አሁንም ድረስ ኔማር ከብራዚል እግር ኳስ አፍቃሪ ህዝብ ጋር ያለውን አይነት ጥልቅ ስሜታዊ ቁርኝት እና ፍቅር ማግኘት አልቻለም። ይህ ሁኔታ እጅግ አስገራሚ ነው፤ አንደኛው (ኔማር) ኮከብነቱ እያለፈ ቢሆንም አሁንም በህዝቡ ልብ ውስጥ አለ፤ ሌላኛው (ቪኒሽየስ) ደግሞ በብቃቱ ጣሪያ ላይ ቢሆንም ያንን የህዝብ ፍቅር አላገኘም።
የግብይት ባለሙያ እና የቀድሞው የኔማር አማካሪ ኤድዋርዶ ሙሳ ይህንን ሲያብራራ፣ "ቪኒሽየስ በብራዚል ደጋፊዎች ይወደዳል፤ ነገር ግን እንደ ኔማር አይደለም። ኔማር አስቀድሞ በብሔራዊ ቡድኑ ግልጽ የሆነ ታሪክ (Legacy) ሰርቷል፤ የዘመናት ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። ቪኒሽየስ ግን በሪያል ማድሪድ ያሳየውን ብቃት በብሔራዊ ቡድን ገና አላሳየም። ሌላው ነጥብ፣ ኔማር በሳንቶስ ቆይታው ብራዚላውያን በየሳምንቱ አስደናቂ ብቃቱን ይመለከቱ ነበር። ቪኒሽየስ ግን በፍላሜንጎ ቋሚ ተሰላፊ እንኳ ሳይሆን ነው በልጅነቱ ሀገር ለቆ የወጣው" ይላል።
ዳታፎልሃ የተሰኘው የብራዚል የምርምር ተቋም ባወጣው መረጃ፣ አሁንም 53 በመቶ የሚሆኑ ደጋፊዎች አንጋፋው ኔማር በዓለም ዋንጫው ስኳድ ውስጥ መካተቱን ይደግፋሉ።
"አሁን ሁሉም የሚያወራው ስለእኔ ነው"
የብራዚል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ቪኒሽየስን የብሔራዊ ቡድኑ ማዕከል ለማድረግ ብዙ ጥረት አድርጓል። ባለፈው መጋቢት ወር ሮድሪጎ በጉዳት ከዓለም ዋንጫው ውጪ መሆኑ ሲረጋገጥ፣ ዝነኛዋን ቁጥር 10 ማልያ ለቪኒሽየስ ሰጥተውት ነበር። ዓላማው ግልጽ ነበር... ቪኒሽየስ የብራዚል ፊት እንዲሆን ማድረግ። ነገር ግን ኔማር ባልተጠበቀ ሁኔታ ወደ ብሔራዊ ቡድኑ ሲመለስ፣ የ34 ዓመቱ የሳንቶስ አጥቂ ዳግም የቁጥር 10 ማልያውን ተረክቧል።
ምንም እንኳን ኔማር ማልያውን ቢወስድም፣...በቅርብ ጊዜያት እያስተናገደው ያለው ተደጋጋሚ የአካል ብቃት ችግር ቀድሞ ይጣልበት የነበረውን ተስፋ አደብዝዞታል። አሁን የብዙዎች አይን ያረፈው ቪኒሽየስ ላይ ነው። ብራዚል 6ኛዋን የዓለም ዋንጫ ለማንሳት በምታደርገው ጉዞ ላይ ቪኒሽየስ የጥርጣሬ ደመናን ገፎ ደምቆ መውጣት ይኖርበታል።
ቪኒሽየስም ለዚህ የትኩረት ማዕከልነት ዝግጁ መሆኑን ይናገራል። "አሁን ሁሉም የሚያወራው ስለእኔ ነው፤ ምክንያቱም በሪያል ማድሪድ አምስት ወይም ስድስት ምርጥ የውድድር ዘመናትን አሳልፌያለሁ፣ ከዓለማችን ምርጥ ተጫዋቾች ተርታም ተሰልፌያለሁ። ይህ ደግሞ በተፈጥሮ ተጨማሪ ኃላፊነት ያመጣል። እኔም የምፈልገው ይሄንኑ ኃላፊነት ነው። አቅሜ የት ድረስ እንደሆነ አውቃለሁ፤ ምክንያቱም የኔ ጣሪያ ሁሌም በጣም ከፍተኛ ነው" በማለት ቆራጥነቱን አሳይቷል። ይህ የዓለም ዋንጫ ቪኒሽየስ የብራዚል ደጋፊዎችን ልብ ሙሉ በሙሉ የሚያሸንፍበት ይሆን? ጊዜ የሚመልሰው ይሆናል።
"ሰዎች አሁን ላይ ብራዚል ኮከብ ተጫዋች የላትም ሲሉ እሰማለሁ። ምናልባት እውነት ሊሆን ይችላል። እንደ ፔሌ፣ ሮማሪዮ ወይም ሮናልዶ አይነት ተጫዋች ላይኖረን ይችላል፤ ነገር ግን የጋራ ኃላፊነት ስሜት ሊኖረን ይችላል፣ ያ ደግሞ እጅግ ኃይለኛ መሳሪያ ነው።"
ይህ የአንቸሎቲ ንግግር የብዙዎችን ቀልብ የሳበው፣ የሪያል ማድሪዱ ኮከብ ቪኒሽየስ ጁኒየር እስካሁን ድረስ የብሔራዊ ቡድኑ የማይነካ መሪ ይሆናል ተብሎ ሲጠበቅ... በተግባር ግን ያ ባለመሆኑ ነው። በ2022ቱ የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ በክሮኤሺያ በመለያ ምት ተሸንፈው ከወጡ ከአራት ዓመታት በኋላም.... በ25 ዓመቱ አጥቂ ላይ አሁንም በርካታ ጥያቄዎች ይነሳሉ።
ይህ ጥርጣሬ ምን ያህል ከፍ እንዳለ ለማሳየት... በመጋቢት ወር ብራዚል በፈረንሳይ 2ለ1 መሸነፏን ተከትሎ፣ በሀገሪቱ የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች ላይ "ቪኒሽየስ በመጀመሪያ አሰላለፍ ውስጥ መካተት ይገባዋል ወይ?" የሚል የከረረ ክርክር እስከመክፈት ደርሷል። በክለብ ደረጃ ለቪኒሽየስ እጅግ ስኬታማ ጊዜያትን ያመጣው እና ትልቅ ተጽዕኖ የፈጠረው አንቸሎቲ ብሔራዊ ቡድኑን ቢረከብም፣ "ቪኒሽየስ በሪያል ማድሪድ የሚያሳየውን ድንቅ አቋም ለምን በብሔራዊ ቡድን መድገም አቃተው?" የሚለው ጥያቄ አሁንም እንደ ጥላ እየተከተለው ነው።
በእርግጥም ቪኒሽየስ በዚህ የዓለም ዋንጫ ዑደት ውስጥ በብሔራዊ ቡድኑ ብዙ የግብ ተሳትፎ ያደረገ ተጫዋች ነው፤ ሆኖም በ28 ጨዋታዎች 7 ግቦችን እና 6 አሲስቶችን ብቻ ማስመዝገቡ ለሱ ደረጃ አነስተኛ ነው። በ2018 እና 2022 የዓለም ዋንጫዎች የብራዚል ብሔራዊ ቡድን ምክትል አሰልጣኝ የነበረው ክሌበር ዣቪየር ይህንን ሲያብራራ "በክለብ ደረጃ የምታሳየውን አቋም በብሔራዊ ቡድን መድገም እጅግ ከባድ ነው። ክለብ ውስጥ የተለየ ልምምድ፣ የተለየ የጨዋታ መንገድ እና የዕለት ተዕለት ቆይታ አለ። ግልጹ ምሳሌ የሜሲ እና የአርጀንቲና ጉዳይ ነው። ሜሲ ሁሌም ይተች ነበር፣ ሊሳካለት የቻለው በ2022 ነው። ምክንያቱም አርጀንቲና ቡድን መገንባት ስለቻለች ነው። ለተጫዋች ተገቢውን መዋቅር መፍጠር ወሳኝ ነው" ይላል።
ቪኒሽየስም ይህንን እውነታ አይክድም። በቅርቡ ለካዜ ቲቪ በሰጠው ቃለ ምልልስ ላይ፣ "በክለብ ውስጥ በየሶስት ቀኑ አዲስ ዕድል አለ። ከ10 ጨዋታዎች ሁለቱን መጥፎ ብጫወት ማንም ብዙ አያወራም። በብሔራዊ ቡድን ግን በአንድ ጨዋታ እና በሌላኛው መካከል ያለው ጊዜ ረጅም ነው፤ ጫናውም ሁልጊዜ ከፍተኛ ነው። ሰዎች ሁሌም በምርጥ አቋሜ ላይ እንድገኝ ይጠብቃሉ። ነገር ግን ወደ ዓለም ዋንጫ ሄጄ አራት ወይም አምስት ግቦችን አግብቼ ሻምፒዮን ብንሆን፣ ታሪኩ ሙሉ በሙሉ ይቀየራል። ያኔ መጥፎ በተጫወትኩባቸው ጨዋታዎች ላይ እንኳን ለዓለም ዋንጫ እየተዘጋጀሁ እንደነበር አድርገው ያወራሉ" ብሏል።
ለብራዚል ብሔራዊ ቡድን መጫወት ለቪኒሽየስ ቀላል ሆኖ አያውቅም። አንድ የቀድሞ የብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ እንዳሉት፣ የ2024 የባሎን ዶር ሁለተኛ ደረጃን የያዘው ቪኒሽየስ፣ "ሁሌም ዋናው ተዋናይ የመሆን ከፍተኛ ጉጉት" ያጠቃዋል። ቪኒሽየስ በሙያ ዘመኑ ሁሉ የለመደውም ይሄንኑ የዋና ተዋናይነት ቦታ ነው።
ወደ ሁለተኛው የዓለም ዋንጫው ሲያቀና... ቪኒሽየስ 14 የንግድ ስምምነቶች ያሉት ሲሆን፣ ይህ ከማንኛውም ብራዚላዊ ተጫዋች የላቀ ነው። ከሜዳ ውጪ ይህ ሁሉ ስኬት ቢኖረውም፣ አሁንም ድረስ ኔማር ከብራዚል እግር ኳስ አፍቃሪ ህዝብ ጋር ያለውን አይነት ጥልቅ ስሜታዊ ቁርኝት እና ፍቅር ማግኘት አልቻለም። ይህ ሁኔታ እጅግ አስገራሚ ነው፤ አንደኛው (ኔማር) ኮከብነቱ እያለፈ ቢሆንም አሁንም በህዝቡ ልብ ውስጥ አለ፤ ሌላኛው (ቪኒሽየስ) ደግሞ በብቃቱ ጣሪያ ላይ ቢሆንም ያንን የህዝብ ፍቅር አላገኘም።
የግብይት ባለሙያ እና የቀድሞው የኔማር አማካሪ ኤድዋርዶ ሙሳ ይህንን ሲያብራራ፣ "ቪኒሽየስ በብራዚል ደጋፊዎች ይወደዳል፤ ነገር ግን እንደ ኔማር አይደለም። ኔማር አስቀድሞ በብሔራዊ ቡድኑ ግልጽ የሆነ ታሪክ (Legacy) ሰርቷል፤ የዘመናት ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ነው። ቪኒሽየስ ግን በሪያል ማድሪድ ያሳየውን ብቃት በብሔራዊ ቡድን ገና አላሳየም። ሌላው ነጥብ፣ ኔማር በሳንቶስ ቆይታው ብራዚላውያን በየሳምንቱ አስደናቂ ብቃቱን ይመለከቱ ነበር። ቪኒሽየስ ግን በፍላሜንጎ ቋሚ ተሰላፊ እንኳ ሳይሆን ነው በልጅነቱ ሀገር ለቆ የወጣው" ይላል።
ዳታፎልሃ የተሰኘው የብራዚል የምርምር ተቋም ባወጣው መረጃ፣ አሁንም 53 በመቶ የሚሆኑ ደጋፊዎች አንጋፋው ኔማር በዓለም ዋንጫው ስኳድ ውስጥ መካተቱን ይደግፋሉ።
"አሁን ሁሉም የሚያወራው ስለእኔ ነው"
የብራዚል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ቪኒሽየስን የብሔራዊ ቡድኑ ማዕከል ለማድረግ ብዙ ጥረት አድርጓል። ባለፈው መጋቢት ወር ሮድሪጎ በጉዳት ከዓለም ዋንጫው ውጪ መሆኑ ሲረጋገጥ፣ ዝነኛዋን ቁጥር 10 ማልያ ለቪኒሽየስ ሰጥተውት ነበር። ዓላማው ግልጽ ነበር... ቪኒሽየስ የብራዚል ፊት እንዲሆን ማድረግ። ነገር ግን ኔማር ባልተጠበቀ ሁኔታ ወደ ብሔራዊ ቡድኑ ሲመለስ፣ የ34 ዓመቱ የሳንቶስ አጥቂ ዳግም የቁጥር 10 ማልያውን ተረክቧል።
ምንም እንኳን ኔማር ማልያውን ቢወስድም፣...በቅርብ ጊዜያት እያስተናገደው ያለው ተደጋጋሚ የአካል ብቃት ችግር ቀድሞ ይጣልበት የነበረውን ተስፋ አደብዝዞታል። አሁን የብዙዎች አይን ያረፈው ቪኒሽየስ ላይ ነው። ብራዚል 6ኛዋን የዓለም ዋንጫ ለማንሳት በምታደርገው ጉዞ ላይ ቪኒሽየስ የጥርጣሬ ደመናን ገፎ ደምቆ መውጣት ይኖርበታል።
ቪኒሽየስም ለዚህ የትኩረት ማዕከልነት ዝግጁ መሆኑን ይናገራል። "አሁን ሁሉም የሚያወራው ስለእኔ ነው፤ ምክንያቱም በሪያል ማድሪድ አምስት ወይም ስድስት ምርጥ የውድድር ዘመናትን አሳልፌያለሁ፣ ከዓለማችን ምርጥ ተጫዋቾች ተርታም ተሰልፌያለሁ። ይህ ደግሞ በተፈጥሮ ተጨማሪ ኃላፊነት ያመጣል። እኔም የምፈልገው ይሄንኑ ኃላፊነት ነው። አቅሜ የት ድረስ እንደሆነ አውቃለሁ፤ ምክንያቱም የኔ ጣሪያ ሁሌም በጣም ከፍተኛ ነው" በማለት ቆራጥነቱን አሳይቷል። ይህ የዓለም ዋንጫ ቪኒሽየስ የብራዚል ደጋፊዎችን ልብ ሙሉ በሙሉ የሚያሸንፍበት ይሆን? ጊዜ የሚመልሰው ይሆናል።
1 day ago
ዓለም በዝምታ ቢያዘግምም ኢትዮጵያ ምድርን እያከመች ነው!
********************
በዓለማችን ላይ አሳዛኝ እና ዐይን ያወጣ ኢፍትሐዊነት ቢኖር፣ ምድራችንን በበካይ ጋዝ እያፈኗት ያሉት ኃያላን ሀገራት ሲሆኑ፣ የጥፋታቸው ገፈት ቀማሽ ደግሞ ለብክለቱ ኢምንት የማያበረክቱ ደሃ ሀገራት መሆናቸው ነው።
አስቡት፤ አጠቃላይ የዓለማችንን የበካይ ጋዝ ልቀት ከ75 እስከ 80 በመቶ የሚያመነጩት ግዙፍ ኢኮኖሚ ያላቸው የቡድን 20 ሀገራት ናቸው።
በአንጻሩ፣ 54 ሀገራትን አቅፋ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት አፍሪካ ለዚህ በካይ ጋዝ ያላት አስተዋፅኦ ከ3 እስከ 4 በመቶ ብቻ ነው። ይሁን እንጂ ኢትዮጵያን ጨምሮ አፍሪካውያን ለችግሩ ያበረከቱት አስተዋፅኦ እዚህ ግባ የሚባል ባይሆንም በድርቅ፣ በጎርፍ እና በሙቀት መጨመር ግንባር ቀደም ሰለባ ሆነው ዘመናትን አሳልፈዋል።
የፈረሱ ስምምነቶች እና የወረቀት ላይ ቃላት
የኢንዱስትሪ ባለቤቶች የሆኑት እነዚህ ኃያላን ሀገራት፣ ምድርን በካርቦን ጋዝ እያፈኗት መሆኑን አምነው፣ ልቀትን ለማስቀረትና ለችግሩ ሰለባ ለሆኑት ሀገራት ካሳ ለመክፈል በፓሪስ ታሪካዊ ስምምነት ፈረሙ።
ነገር ግን ዘመናት ተቆጠሩ፤ የወረቀት ላይ ቃላት ወደ ተግባር ሳይቀየሩ፣ ስምምነቶች የሚዲያ ፍጆታ ብቻ ሆነው ቀሩ። በኃያላኑ ቸልተኝነትና ቃል ማጠፍ ምክንያት ዓለማችን በድርቅ፣ በጎርፍ መጥለቅለቅ፣ በበረሃማነት መስፋፋት እና ባልተጠበቀ የአየር ጸባይ መዛባት ክፉኛ መታመሷን ቀጥላለች።
ከንግግር ወደ ተግባር፤ የኢትዮጵያ አረንጓዴ አብዮት
ዓለም መፍትሔ አጥቶ በየስብሰባ አዳራሹ ሲባዝን፣ ቃሉን ሲያጥፍና ከንግግር ያለፈ አንዳች መፍትሔ ማምጣት ሲሳነው፣ ኢትዮጵያ ግን እጆቿን አጣጥፋ የኃያላኑን ምፅዋት አልጠበቀችም። ይልቁንም ተፈጥሮን እና አካባቢን ለማከም ቆርጣ በመነሳት ዓለምን ያስደመመ ተዓምራዊ የድል ትርክት መፃፍ ጀመረች።
ይህ ታሪካዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ጉዞ፣ በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በይፋ ሲበሰር፣ ገና በዕለቱ 350 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር በመትከል የህንድን የዓለም ክብረ-ወሰን በታላቅ ጀግንነት በመስበር ነበር የተጀመረው።
ዓለም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ክፉኛ በተረበሸችበት በ2012 ዓ.ም እንኳን፣ ኢትዮጵያውያን ተስፋ ሳይቆርጡ 5 ቢሊዮን ችግኞችን በመትከል ጽናታቸውን አሳይተዋል። በ2013 እና 2014 ዓ.ም ከ6 ነጥብ 8 እና 7 ነጥብ 2 ቢሊዮን በላይ ችግኞች በምድሪቱ ላይ ሲያርፉ፣ እንደ ሐሮማያ ሐይቅ ያሉ ጠፍተው የነበሩ የውሃ አካላት ዳግም ህያው ሆነዋል።
የድል መዳረሻዎቻችን በዚህ አላበቁም፤ በ2015 ዓ.ም ለምግብ ዋስትና የሚሆኑ የፍራፍሬ ተክሎች ላይ በማተኮር 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች ተተከሉ። በ2016 ዓ.ም ይህ አሃዝ ወደ 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ሲሻገር፣ በአንድ ጀንበር ብቻ ከ600 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል የራሳችንን ክብረ-ወሰን ደግመን ሰበርን።
በመጨረሻም በ2017 ዓ.ም ከ8 ቢሊዮን በላይ ዐሻራዎችን በማኖር፣ በሰባት ዓመታት ጉዞ ብቻ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል ኢትዮጵያ በዓለም የደን ልማት መዝገብ ላይ ወደር የማይገኝለት የልዕልና ስፍራ ተቀመጠች። በየዓመቱ ከ25 እስከ 35 ሚሊዮን ዜጎች በፈቃደኝነት የሚሳተፉበት ይህ ግዙፍ ንቅናቄ፣ ብሔራዊ አንድነትን ያጠናከረ የአረንጓዴ ማዕበል ሆኗል።
ይህ የ7 ዓመታት ጉዞ ያመጣው ሥነ-ምህዳራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተዓምር ቃላት ከሚገልጹት በላይ ነው። አስቀድሞ ወደ 3 በመቶ አሽቆልቁሎ የነበረው የሀገራችን የደን ሽፋን፣ በማይታመን ፍጥነት አድጎ 23 ነጥብ 6 በመቶ ደርሷል።
የተተከሉት ችግኞች ከ80 እስከ 85 በመቶ በሚደርስ የፅድቀት ምጣኔ ጸድቀው፣ በአማካይ 64 ሚሊዮን በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች የሚያወጡትን በካይ ጋዝ ከከባቢ አየር ላይ በማጽዳት ዓለምን እየታደጉ ይገኛሉ።
መሬቱ ውሃን የመምጠጥ አቅሙ ከ16 ነጥብ 9 በመቶ ወደ 68 ነጥብ 9 በመቶ በከፍተኛ ደረጃ በማደጉ፣ የተፋሰስ ልማቱ ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጨምሮ የሌሎች የኃይል ማመንጫ ግድቦችን የዕድሜ ጣሪያ ቢያንስ በ50 ዓመታት እንዲራዘም አድርጓል።
ከዚህም ባሻገር በተቋቋሙ ከ120 ሺህ በላይ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ለሚበልጡ ዜጎች የስራ ዕድል ሲፈጠር፤ ተፈጥሮ በማገገሟም የሀገራችን የቡና ወጪ ንግድ ከ230 ሺህ ቶን ወደ 475 ሺህ ቶን በማደግ ትልቅ የውጭ ምንዛሪ እያስገኘ ነው።
በአጠቃላይ፣ ኃያላን ሀገራት ዛሬም ስለ አየር ንብረት ለውጥ ይነጋገራሉ፣ ስምምነት ያፈርሳሉ፣ ይከራከራሉ። ኢትዮጵያ ግን ንግግርን ወደ ተግባር ቀይራ፣ ቆስላ የነበረችውን ምድር በቢሊዮኖች አረንጓዴ ዐሻራ በተግባር እያከመች ነው።
አረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ የመትከል ዘመቻ ብቻ ሳይሆን፣ ተፈጥሮን ማዳን፣ ማክሮ-ኢኮኖሚን መገንባት እና ትውልድን ማሻገር መሆኑን አሃዞች አፍ አውጥተው እየመሰከሩ ነው።
የዓለምን የሥነ-ምህዳር ህመም ለመፈወስ እውነተኛው እና ህያው መድኃኒት ከኢትዮጵያ ተገኝቷል፤ ወደ 50 ቢሊዮን የሚያልመው የድል ትርክታችንም በብልጽግና ጎዳና ላይ አሁንም ተጠናክሮ ይቀጥላል።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #climatechange #greenlegacy #climateresilience
********************
በዓለማችን ላይ አሳዛኝ እና ዐይን ያወጣ ኢፍትሐዊነት ቢኖር፣ ምድራችንን በበካይ ጋዝ እያፈኗት ያሉት ኃያላን ሀገራት ሲሆኑ፣ የጥፋታቸው ገፈት ቀማሽ ደግሞ ለብክለቱ ኢምንት የማያበረክቱ ደሃ ሀገራት መሆናቸው ነው።
አስቡት፤ አጠቃላይ የዓለማችንን የበካይ ጋዝ ልቀት ከ75 እስከ 80 በመቶ የሚያመነጩት ግዙፍ ኢኮኖሚ ያላቸው የቡድን 20 ሀገራት ናቸው።
በአንጻሩ፣ 54 ሀገራትን አቅፋ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት አፍሪካ ለዚህ በካይ ጋዝ ያላት አስተዋፅኦ ከ3 እስከ 4 በመቶ ብቻ ነው። ይሁን እንጂ ኢትዮጵያን ጨምሮ አፍሪካውያን ለችግሩ ያበረከቱት አስተዋፅኦ እዚህ ግባ የሚባል ባይሆንም በድርቅ፣ በጎርፍ እና በሙቀት መጨመር ግንባር ቀደም ሰለባ ሆነው ዘመናትን አሳልፈዋል።
የፈረሱ ስምምነቶች እና የወረቀት ላይ ቃላት
የኢንዱስትሪ ባለቤቶች የሆኑት እነዚህ ኃያላን ሀገራት፣ ምድርን በካርቦን ጋዝ እያፈኗት መሆኑን አምነው፣ ልቀትን ለማስቀረትና ለችግሩ ሰለባ ለሆኑት ሀገራት ካሳ ለመክፈል በፓሪስ ታሪካዊ ስምምነት ፈረሙ።
ነገር ግን ዘመናት ተቆጠሩ፤ የወረቀት ላይ ቃላት ወደ ተግባር ሳይቀየሩ፣ ስምምነቶች የሚዲያ ፍጆታ ብቻ ሆነው ቀሩ። በኃያላኑ ቸልተኝነትና ቃል ማጠፍ ምክንያት ዓለማችን በድርቅ፣ በጎርፍ መጥለቅለቅ፣ በበረሃማነት መስፋፋት እና ባልተጠበቀ የአየር ጸባይ መዛባት ክፉኛ መታመሷን ቀጥላለች።
ከንግግር ወደ ተግባር፤ የኢትዮጵያ አረንጓዴ አብዮት
ዓለም መፍትሔ አጥቶ በየስብሰባ አዳራሹ ሲባዝን፣ ቃሉን ሲያጥፍና ከንግግር ያለፈ አንዳች መፍትሔ ማምጣት ሲሳነው፣ ኢትዮጵያ ግን እጆቿን አጣጥፋ የኃያላኑን ምፅዋት አልጠበቀችም። ይልቁንም ተፈጥሮን እና አካባቢን ለማከም ቆርጣ በመነሳት ዓለምን ያስደመመ ተዓምራዊ የድል ትርክት መፃፍ ጀመረች።
ይህ ታሪካዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ጉዞ፣ በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በይፋ ሲበሰር፣ ገና በዕለቱ 350 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር በመትከል የህንድን የዓለም ክብረ-ወሰን በታላቅ ጀግንነት በመስበር ነበር የተጀመረው።
ዓለም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ክፉኛ በተረበሸችበት በ2012 ዓ.ም እንኳን፣ ኢትዮጵያውያን ተስፋ ሳይቆርጡ 5 ቢሊዮን ችግኞችን በመትከል ጽናታቸውን አሳይተዋል። በ2013 እና 2014 ዓ.ም ከ6 ነጥብ 8 እና 7 ነጥብ 2 ቢሊዮን በላይ ችግኞች በምድሪቱ ላይ ሲያርፉ፣ እንደ ሐሮማያ ሐይቅ ያሉ ጠፍተው የነበሩ የውሃ አካላት ዳግም ህያው ሆነዋል።
የድል መዳረሻዎቻችን በዚህ አላበቁም፤ በ2015 ዓ.ም ለምግብ ዋስትና የሚሆኑ የፍራፍሬ ተክሎች ላይ በማተኮር 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች ተተከሉ። በ2016 ዓ.ም ይህ አሃዝ ወደ 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ሲሻገር፣ በአንድ ጀንበር ብቻ ከ600 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል የራሳችንን ክብረ-ወሰን ደግመን ሰበርን።
በመጨረሻም በ2017 ዓ.ም ከ8 ቢሊዮን በላይ ዐሻራዎችን በማኖር፣ በሰባት ዓመታት ጉዞ ብቻ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል ኢትዮጵያ በዓለም የደን ልማት መዝገብ ላይ ወደር የማይገኝለት የልዕልና ስፍራ ተቀመጠች። በየዓመቱ ከ25 እስከ 35 ሚሊዮን ዜጎች በፈቃደኝነት የሚሳተፉበት ይህ ግዙፍ ንቅናቄ፣ ብሔራዊ አንድነትን ያጠናከረ የአረንጓዴ ማዕበል ሆኗል።
ይህ የ7 ዓመታት ጉዞ ያመጣው ሥነ-ምህዳራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተዓምር ቃላት ከሚገልጹት በላይ ነው። አስቀድሞ ወደ 3 በመቶ አሽቆልቁሎ የነበረው የሀገራችን የደን ሽፋን፣ በማይታመን ፍጥነት አድጎ 23 ነጥብ 6 በመቶ ደርሷል።
የተተከሉት ችግኞች ከ80 እስከ 85 በመቶ በሚደርስ የፅድቀት ምጣኔ ጸድቀው፣ በአማካይ 64 ሚሊዮን በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች የሚያወጡትን በካይ ጋዝ ከከባቢ አየር ላይ በማጽዳት ዓለምን እየታደጉ ይገኛሉ።
መሬቱ ውሃን የመምጠጥ አቅሙ ከ16 ነጥብ 9 በመቶ ወደ 68 ነጥብ 9 በመቶ በከፍተኛ ደረጃ በማደጉ፣ የተፋሰስ ልማቱ ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጨምሮ የሌሎች የኃይል ማመንጫ ግድቦችን የዕድሜ ጣሪያ ቢያንስ በ50 ዓመታት እንዲራዘም አድርጓል።
ከዚህም ባሻገር በተቋቋሙ ከ120 ሺህ በላይ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ለሚበልጡ ዜጎች የስራ ዕድል ሲፈጠር፤ ተፈጥሮ በማገገሟም የሀገራችን የቡና ወጪ ንግድ ከ230 ሺህ ቶን ወደ 475 ሺህ ቶን በማደግ ትልቅ የውጭ ምንዛሪ እያስገኘ ነው።
በአጠቃላይ፣ ኃያላን ሀገራት ዛሬም ስለ አየር ንብረት ለውጥ ይነጋገራሉ፣ ስምምነት ያፈርሳሉ፣ ይከራከራሉ። ኢትዮጵያ ግን ንግግርን ወደ ተግባር ቀይራ፣ ቆስላ የነበረችውን ምድር በቢሊዮኖች አረንጓዴ ዐሻራ በተግባር እያከመች ነው።
አረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ የመትከል ዘመቻ ብቻ ሳይሆን፣ ተፈጥሮን ማዳን፣ ማክሮ-ኢኮኖሚን መገንባት እና ትውልድን ማሻገር መሆኑን አሃዞች አፍ አውጥተው እየመሰከሩ ነው።
የዓለምን የሥነ-ምህዳር ህመም ለመፈወስ እውነተኛው እና ህያው መድኃኒት ከኢትዮጵያ ተገኝቷል፤ ወደ 50 ቢሊዮን የሚያልመው የድል ትርክታችንም በብልጽግና ጎዳና ላይ አሁንም ተጠናክሮ ይቀጥላል።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #climatechange #greenlegacy #climateresilience
1 day ago
ግብፅ በማሊያዋ ላይ ያሉትን ኮከቦች እንድታነሳ ታዘዘች
#ethiopia | የዓለም እግር ኳስ ማኅበር (ፊፋ) የግብፅ ብሔራዊ ቡድን ለዓለም ዋንጫ ያዘጋጀውን ማሊያ ተጠቅሞ መጫወት እንደማይችል በመግለጽ አስቸኳይ እገዳ ጥሏል።
ቡድኑ ከቤልጂየም ጋር ከሚያደርገው የመክፈቻ ጨዋታ በፊት በማሊያው ደረት ላይ ያረፉትን ኮከቦች እንዲያነሳና በተጫዋቾች ስም እንዲሁም ቁጥር ላይ የተጠቀመውን የወርቅ ቀለም እንዲቀይር ጥብቅ ትዕዛዝ አስተላልፏል።
ፊፋ ይህንን ውሳኔ ያስተላለፈው የዓለም ዋንጫ ደንብ ሀገራት በደረት ላይ ኮከብ ማሳረፍ የሚችሉት የዓለም ዋንጫን ማሸነፍ ሲችሉ ብቻ በመሆኑ ሲሆን፣ ግብፅ ግን የአፍሪካ ዋንጫን ያሸነፈችበትን 7 ኮከቦች በዓለም ዋንጫ ማሊያዋ ላይ በማሳረፏ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#egypt #fifa #worldcup #pharaohs #footballnews #africacupofnations
#ethiopia | የዓለም እግር ኳስ ማኅበር (ፊፋ) የግብፅ ብሔራዊ ቡድን ለዓለም ዋንጫ ያዘጋጀውን ማሊያ ተጠቅሞ መጫወት እንደማይችል በመግለጽ አስቸኳይ እገዳ ጥሏል።
ቡድኑ ከቤልጂየም ጋር ከሚያደርገው የመክፈቻ ጨዋታ በፊት በማሊያው ደረት ላይ ያረፉትን ኮከቦች እንዲያነሳና በተጫዋቾች ስም እንዲሁም ቁጥር ላይ የተጠቀመውን የወርቅ ቀለም እንዲቀይር ጥብቅ ትዕዛዝ አስተላልፏል።
ፊፋ ይህንን ውሳኔ ያስተላለፈው የዓለም ዋንጫ ደንብ ሀገራት በደረት ላይ ኮከብ ማሳረፍ የሚችሉት የዓለም ዋንጫን ማሸነፍ ሲችሉ ብቻ በመሆኑ ሲሆን፣ ግብፅ ግን የአፍሪካ ዋንጫን ያሸነፈችበትን 7 ኮከቦች በዓለም ዋንጫ ማሊያዋ ላይ በማሳረፏ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#egypt #fifa #worldcup #pharaohs #footballnews #africacupofnations
Sponsored by
Surafel
1 day ago
የአሜሪካዋ ግዛት ምክር ቤት ለአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን ሰየመ
#fastmereja I በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት 2' በግዛቱ የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን እንዲሆን የቀረበን የውሳኔ ሐሳብ በከፍተኛ ድምጽ አፀደቀ።
ይህ 'ኤችአር 441' የተሰኘው የውሳኔ ሐሳብ የፀደቀው ባለፈው ሳምንት በግዛቲቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተደረገ የድምጽ አሰጣጥ ሥነ ሥርዓት ነው።
በአሜሪካ የግዛቶች ምክር ቤት አሠራር መሠረት፣ ይህ ውሳኔ በግዛቲቱ የሕግ መዝገብ ላይ የአድዋ ድል በይፋ ዕውቅና ያገኘበት ታሪካዊ ሰነድ ሆኖ በቋሚነት ይቀመጣል።
ይህ የውሳኔ ሐሳብ ረቂቅ፣ የአውሮፓውያኑ 'ማርች 2 ቀን 2026' የ130ኛ 'የአድዋ ድል ቀን' ሆኖ በፔንሲልቬኒያ ግዛት ዕውቅና እንዲሰጠው የሚደነግግ ነው።
ውሳኔው በሪፐብሊካን እና በዲሞክራቲክ ፓርቲ እንደራሴዎች በተሰጠ 195 ከፍተኛ የድጋፍ ድምጽ እና በ6 ተቃውሞ ብቻ ነው የፀደቀው።
ረቂቁ የቀረበው ከወራት በፊት ቢሆንም የምክር ቤቱን የውስጥ አሠራሮችን አልፎ፣ ውይይቶች ተደርገውበት ከቆየ በኋላ የውሳኔ ድምጽ የተሰጠበት ግን ባለፈው ሳምንት ነው።
''ኤችአር 441'' ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀረቡት የሰሜን ፊላደልፊያ ሜንገመሪ ካውንቲ፣ የሕዝብ ተወካይ የሆኑት ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ ናቸው።
ቢቢሲ የፀደቀውን የውሳኔ ሐሳብ አስመልክቶ ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጡት ሴናተሩን በኢሜይል ጥያቄ አቅርቦላቸው የነበረ ሲሆን፣ ይህ ዘገባ እስኪጠናቀር ድረስ ምላሽ አልሰጡም።
ሆኖም እርሳቸው ረቂቁን ባቀረቡት ዕለት በምክር ቤቱ ባደረጉት ንግግር፣ አድዋ ለአፍሪካ አሜሪካዊያን ያለውን ታላቅ ትርጉም አውስተዋል።
የምክር ቤቱ አባል ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ በዕለቱ በንባብ ባሰሙት የመክፈቻ ንግግር በዘመናዊ የዓለም ታሪክ ውስጥ አድዋ የማይናቅ ቦታ እንዳለው ካወሱ በኋላ "ኢትዮጵያዊው ንጉሥ ዳግማዊ ምንሊክ እና ባለቤታቸው ጣይቱ ብጡል በአመራር ሰጪነት አገራቸውን ከቅኝ ገዥ ተቀራማቾች" ማስጣላቸውን አብራርተዋል።
ይህም ለአፍሪካ አሜሪካዊያን፣ በአገረ ግዛቱ ውስጥ ለሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ታላቅ ኩራት ነው ብለዋል።
የፔንሲልቬኒያ ግዛት የተወካዮች ምክር ቤት በበኩሉ በድረ ገጹ ባሰፈረው ጽሑፍ አውሮፓውያን የአፍሪካ አገራትን ቅኝ ግዛት በያዙበት እና መቼም ነፃ የሚወጡ በማይመስልበት በዚያን ወቅት ኢትዮጵያ ነፃነቷን በማስከበር የአደዋ ድልን አድንቋል።
በዚህም ኢትዮጵያ ቅኝ ያልተገዛች ብቸኛዋ አፍሪካዊት አገር በመሆን በ19ኛው እና በ20ኛው ክፍለ ዘመን በነበሩ የዓለም ኃያላን ዕውቅና ማግኘቷን ገልጿል።
በመሆኑም የአውሮፓውያኑ መጋቢት 2 በፔንሲልቬኒያ ግዛት "የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን" እንዲሆን ውሳኔ ማሳለፉን አስታውቋል።
"የአድዋ ድል ቀንን በማክበር የአሜሪካን ታሪክንም እናከብራለን" ብሏል።
ምክር ቤቱ ያሳለፈውን ውሳኔ በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ ግንኙነት ላይ የሚሠራው 'አሜሪካን ኢትዮጵያን ፐብሊክ አፌርስ ኮሚቴ' አወድሶታል።
"የፔንሲልቬኒያ ምክር ቤት በውሳኔው ከአድዋ የተቀሰመው ትምህርት ዛሬም ድረስ ወሳኝ መሆኑን የሚያሳይ ትልቅ መልዕክት አስተላልፏል። በዓለም ሚሊዮኖችን ለሚያነሳሳ እና ለሚያኮራ ለዚህ ታሪካዊ ቀን ዕውቅና በመስጠቱ እናመሰግናለን" ብሏል።
ኮሚቴው ኤችአር 441 ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ ምክር ቤት ላቀረቡት የሕዝብ ተወካይ ቤንጃሚን ሳንቼዝም ምስጋናውን አቅርቧል።
በኮሎራዶ ግዛት የአውሮራ ከተማ ምክር ቤት እንደራሴ እና የሪፐብሊካን ፓርቲ አባል የሆኑት ትውልደ ኢትዮጵያዊው አቶ አምሳሉ ፀጋዬ ኤችአር 441' የተባለው ውሳኔ በምክር ቤቱ ባሉ ሁለቱም ፓርቲዎች [ ዲሞክራት እና ሪፐብሊካን] በከፍተኛ ድምጽ የጸደቀ መሆኑን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ውሳኔው የአውሮፓውያኑ መጋቢት 2 የኢትዮጵያ አርበኞች በ1896 በአድዋ ተራሮች የጣሊያንን ዘመናዊ ጦር ድል ያደረጉበትን ዕለት ለማስታወስ የተላለፈ መሆኑንም አክለዋል።
13 ሚሊዮን ሕዝብ በሚኖርባት ፔንሲልቬኒያ ግዛት በርካታ ትውልደ ኢትዮጵያን ፊላዴልፊያን ጨምሮ በሌሎች የግዛቲቱ ትልልቅ ከተሞች ውስጥ ይኖራሉ።
"የኢትዮጵያ ታሪክ በኢትዮጵያውያን ብቻ ተወስኖ የሚቀር አይደለም" ያሉት አቶ አምሳሉ፣ "ያ ታሪክ የአፍሪካውያን እና የጥቁር አሜሪካውያን ታሪክም ጭምር ነው" በማለት፣ የድል ቀኑ በፔንሲልቬኒያ ግዛት እንዲታሰብ መደረጉ ወርቃማ ዕድልን የሚፈጥር እንደሆነም ገልጸዋል።
የአድዋ ድል በተመሳሳይ እርሳቸው በተወከሉበት ኮሎራዶ ግዛት፣ አውሮራ ከተማ ምክር ቤትም ዕውቅና ተሰጥቶት 'የጥቁሮች ታሪክ ከሚዘከርበት ወር' ጋር ተጣምሮ የሚከበር በዓል እንደሆነም አስታውሰዋል።
ጉዳዩ ወደ ምክር ቤቱ ከመምጣቱ በፊት ከፍተኛ እንቅስቃሴ ሲደረግበት እንደነበር ያወሱት አቶ አምሳሉ "ይህ ታሪካዊ ድል ለኢትዮጵያውያን፣ ለአሜሪካውያን፣ ለጥቁሮች በሙሉ ትልቅ ዕድል ነው" ብለዋል።
በግዛቲቱ 'መጋቢት 2፣ 2026 'ለ130ኛው የዓድዋ በዓል' መታሰቢያ እንዲሆን ተወሰነ ሲባል ትርጉሙ ምንድነው? ለምንስ ውሳኔው ረዥም ጊዜን ሊወስድ ቻለ በሚል የተጠየቁት አቶ አምሳሉ፣ በምክር ቤት አሠራር የውሳኔ ሐሳቦች (ሪዞሉሽንስ) ብዙ ማለፍ ያለባቸው ሂደት ስላለ ነው ብለዋል።
'መጋቢት 2' የአድዋ ቀን መባሉ ደግሞ ለአንድ ጊዜና ለአንድ ዓመት ብቻ ሳይሆን ቋሚና ቀጣይ እንደሆነ አብራርተዋል።
ዕለቱ ለአድዋ ድል መሰየሙ በተግባር ምን ማለት እንደሆነ ተጠይቀው በግዛቲቱ ቀን መቁጠሪያ (ካላንደር) ውስጥ 'የአድዋ ቀን' ተብሎ ተካትቶ ታስቦ ይውላል። ይህም ትልቅ ትርጉም ያለው ተዕምርታዊ (ሲምቦሊክ) ነው' ብለዋል።
ሆኖም ውሳኔው በዚያው ግዛት ተፈፃሚ የሚሆን እንጂ ወደ ፌደራል የሚያመራ እንዳልሆነም አክለዋል።
ይሁንና አድዋ በበርካታ ግዛቶች ዕውቅና እያገኘ ከመጣ፣ ወደፊት ኢትዮ- አሜሪካውያን፣ ጥቁር አሜሪካውያን እና የተለያዩ አደረጃጀቶች ጉዳዩን በጊዜ ሂደት ወደ ፌደራል ይዘውት እንዲሄዱ አንዳች ዕድል ሊፈጥረ እንደሚችል ያላቸውን ተስፋ ተናግረዋል።
አድዋ ኢትዮጵያ በአፄ ምንሊክ እና ባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ አመራር ሰጪነት የጣሊያን ወራሪዎችን ድል በመምታት ሉዓላዊነቷን አስከብራ የቆየችበት እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የጥቁር ሕዝቦች ነፃነት እና ፀረ-ቅኝ ግዛት ትግል ምልክት የሆነ ታሪካዊ ድል ነው።
ከአድዋ ድል በኋላ በርካታ አገራት የፀረ-ቅኝ ግዛት ተጋድሏቸውን በማጠናከር ለዓመታት በዘለቀ ትግል ነፃነታቸውን መቀዳጀት ችለዋል።
በአፍሪካ ሁለት አገራት ቅኝ አለመገዛታቸውን ታሪክ የሚያስረዳ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ራሷን ያስከበረችው አርበኞቿ ባደረጉ ትግል ነው።
በአድዋ ጦርነት በሺዎች የሚቆጠሩ የጣሊያን ሠራዊት አባላት ሲገደሉ ሌሎች ሺህዎች ደግሞ ተማርከዋል። መድፎችን ጨምሮ ከፍተኛ መጠን ያለው የጦር መሳሪያዎችም መማረካቸውን ታሪክ ያስረዳል።
በተጨማሪም የጣሊያንን ሠራዊት ከመሩት መኮንኖች መካከል ጄነራል አልቤርቶኒ ሲማረክ ዋና አዛዥ ጄነራል ባራቴሪ ሸሽቶ አምልጧል።
ኢትዮጵያ ይህንን ታሪካዊ ድል የተጎናፀፈችበትን የካቲት 23 ቀንን በየዓመቱ በደማቅ ታሪካዊ ሁነቶች ታከብራለች።
ባለፈው የካቲት ወርም 130ኛው የአድዋ ድል በዓል ተከብሯል። ዘገባው የቢቢሲ አማርኛ ነው
#fastmereja I በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት 2' በግዛቱ የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን እንዲሆን የቀረበን የውሳኔ ሐሳብ በከፍተኛ ድምጽ አፀደቀ።
ይህ 'ኤችአር 441' የተሰኘው የውሳኔ ሐሳብ የፀደቀው ባለፈው ሳምንት በግዛቲቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተደረገ የድምጽ አሰጣጥ ሥነ ሥርዓት ነው።
በአሜሪካ የግዛቶች ምክር ቤት አሠራር መሠረት፣ ይህ ውሳኔ በግዛቲቱ የሕግ መዝገብ ላይ የአድዋ ድል በይፋ ዕውቅና ያገኘበት ታሪካዊ ሰነድ ሆኖ በቋሚነት ይቀመጣል።
ይህ የውሳኔ ሐሳብ ረቂቅ፣ የአውሮፓውያኑ 'ማርች 2 ቀን 2026' የ130ኛ 'የአድዋ ድል ቀን' ሆኖ በፔንሲልቬኒያ ግዛት ዕውቅና እንዲሰጠው የሚደነግግ ነው።
ውሳኔው በሪፐብሊካን እና በዲሞክራቲክ ፓርቲ እንደራሴዎች በተሰጠ 195 ከፍተኛ የድጋፍ ድምጽ እና በ6 ተቃውሞ ብቻ ነው የፀደቀው።
ረቂቁ የቀረበው ከወራት በፊት ቢሆንም የምክር ቤቱን የውስጥ አሠራሮችን አልፎ፣ ውይይቶች ተደርገውበት ከቆየ በኋላ የውሳኔ ድምጽ የተሰጠበት ግን ባለፈው ሳምንት ነው።
''ኤችአር 441'' ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀረቡት የሰሜን ፊላደልፊያ ሜንገመሪ ካውንቲ፣ የሕዝብ ተወካይ የሆኑት ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ ናቸው።
ቢቢሲ የፀደቀውን የውሳኔ ሐሳብ አስመልክቶ ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጡት ሴናተሩን በኢሜይል ጥያቄ አቅርቦላቸው የነበረ ሲሆን፣ ይህ ዘገባ እስኪጠናቀር ድረስ ምላሽ አልሰጡም።
ሆኖም እርሳቸው ረቂቁን ባቀረቡት ዕለት በምክር ቤቱ ባደረጉት ንግግር፣ አድዋ ለአፍሪካ አሜሪካዊያን ያለውን ታላቅ ትርጉም አውስተዋል።
የምክር ቤቱ አባል ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ በዕለቱ በንባብ ባሰሙት የመክፈቻ ንግግር በዘመናዊ የዓለም ታሪክ ውስጥ አድዋ የማይናቅ ቦታ እንዳለው ካወሱ በኋላ "ኢትዮጵያዊው ንጉሥ ዳግማዊ ምንሊክ እና ባለቤታቸው ጣይቱ ብጡል በአመራር ሰጪነት አገራቸውን ከቅኝ ገዥ ተቀራማቾች" ማስጣላቸውን አብራርተዋል።
ይህም ለአፍሪካ አሜሪካዊያን፣ በአገረ ግዛቱ ውስጥ ለሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ታላቅ ኩራት ነው ብለዋል።
የፔንሲልቬኒያ ግዛት የተወካዮች ምክር ቤት በበኩሉ በድረ ገጹ ባሰፈረው ጽሑፍ አውሮፓውያን የአፍሪካ አገራትን ቅኝ ግዛት በያዙበት እና መቼም ነፃ የሚወጡ በማይመስልበት በዚያን ወቅት ኢትዮጵያ ነፃነቷን በማስከበር የአደዋ ድልን አድንቋል።
በዚህም ኢትዮጵያ ቅኝ ያልተገዛች ብቸኛዋ አፍሪካዊት አገር በመሆን በ19ኛው እና በ20ኛው ክፍለ ዘመን በነበሩ የዓለም ኃያላን ዕውቅና ማግኘቷን ገልጿል።
በመሆኑም የአውሮፓውያኑ መጋቢት 2 በፔንሲልቬኒያ ግዛት "የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን" እንዲሆን ውሳኔ ማሳለፉን አስታውቋል።
"የአድዋ ድል ቀንን በማክበር የአሜሪካን ታሪክንም እናከብራለን" ብሏል።
ምክር ቤቱ ያሳለፈውን ውሳኔ በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ ግንኙነት ላይ የሚሠራው 'አሜሪካን ኢትዮጵያን ፐብሊክ አፌርስ ኮሚቴ' አወድሶታል።
"የፔንሲልቬኒያ ምክር ቤት በውሳኔው ከአድዋ የተቀሰመው ትምህርት ዛሬም ድረስ ወሳኝ መሆኑን የሚያሳይ ትልቅ መልዕክት አስተላልፏል። በዓለም ሚሊዮኖችን ለሚያነሳሳ እና ለሚያኮራ ለዚህ ታሪካዊ ቀን ዕውቅና በመስጠቱ እናመሰግናለን" ብሏል።
ኮሚቴው ኤችአር 441 ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ ምክር ቤት ላቀረቡት የሕዝብ ተወካይ ቤንጃሚን ሳንቼዝም ምስጋናውን አቅርቧል።
በኮሎራዶ ግዛት የአውሮራ ከተማ ምክር ቤት እንደራሴ እና የሪፐብሊካን ፓርቲ አባል የሆኑት ትውልደ ኢትዮጵያዊው አቶ አምሳሉ ፀጋዬ ኤችአር 441' የተባለው ውሳኔ በምክር ቤቱ ባሉ ሁለቱም ፓርቲዎች [ ዲሞክራት እና ሪፐብሊካን] በከፍተኛ ድምጽ የጸደቀ መሆኑን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ውሳኔው የአውሮፓውያኑ መጋቢት 2 የኢትዮጵያ አርበኞች በ1896 በአድዋ ተራሮች የጣሊያንን ዘመናዊ ጦር ድል ያደረጉበትን ዕለት ለማስታወስ የተላለፈ መሆኑንም አክለዋል።
13 ሚሊዮን ሕዝብ በሚኖርባት ፔንሲልቬኒያ ግዛት በርካታ ትውልደ ኢትዮጵያን ፊላዴልፊያን ጨምሮ በሌሎች የግዛቲቱ ትልልቅ ከተሞች ውስጥ ይኖራሉ።
"የኢትዮጵያ ታሪክ በኢትዮጵያውያን ብቻ ተወስኖ የሚቀር አይደለም" ያሉት አቶ አምሳሉ፣ "ያ ታሪክ የአፍሪካውያን እና የጥቁር አሜሪካውያን ታሪክም ጭምር ነው" በማለት፣ የድል ቀኑ በፔንሲልቬኒያ ግዛት እንዲታሰብ መደረጉ ወርቃማ ዕድልን የሚፈጥር እንደሆነም ገልጸዋል።
የአድዋ ድል በተመሳሳይ እርሳቸው በተወከሉበት ኮሎራዶ ግዛት፣ አውሮራ ከተማ ምክር ቤትም ዕውቅና ተሰጥቶት 'የጥቁሮች ታሪክ ከሚዘከርበት ወር' ጋር ተጣምሮ የሚከበር በዓል እንደሆነም አስታውሰዋል።
ጉዳዩ ወደ ምክር ቤቱ ከመምጣቱ በፊት ከፍተኛ እንቅስቃሴ ሲደረግበት እንደነበር ያወሱት አቶ አምሳሉ "ይህ ታሪካዊ ድል ለኢትዮጵያውያን፣ ለአሜሪካውያን፣ ለጥቁሮች በሙሉ ትልቅ ዕድል ነው" ብለዋል።
በግዛቲቱ 'መጋቢት 2፣ 2026 'ለ130ኛው የዓድዋ በዓል' መታሰቢያ እንዲሆን ተወሰነ ሲባል ትርጉሙ ምንድነው? ለምንስ ውሳኔው ረዥም ጊዜን ሊወስድ ቻለ በሚል የተጠየቁት አቶ አምሳሉ፣ በምክር ቤት አሠራር የውሳኔ ሐሳቦች (ሪዞሉሽንስ) ብዙ ማለፍ ያለባቸው ሂደት ስላለ ነው ብለዋል።
'መጋቢት 2' የአድዋ ቀን መባሉ ደግሞ ለአንድ ጊዜና ለአንድ ዓመት ብቻ ሳይሆን ቋሚና ቀጣይ እንደሆነ አብራርተዋል።
ዕለቱ ለአድዋ ድል መሰየሙ በተግባር ምን ማለት እንደሆነ ተጠይቀው በግዛቲቱ ቀን መቁጠሪያ (ካላንደር) ውስጥ 'የአድዋ ቀን' ተብሎ ተካትቶ ታስቦ ይውላል። ይህም ትልቅ ትርጉም ያለው ተዕምርታዊ (ሲምቦሊክ) ነው' ብለዋል።
ሆኖም ውሳኔው በዚያው ግዛት ተፈፃሚ የሚሆን እንጂ ወደ ፌደራል የሚያመራ እንዳልሆነም አክለዋል።
ይሁንና አድዋ በበርካታ ግዛቶች ዕውቅና እያገኘ ከመጣ፣ ወደፊት ኢትዮ- አሜሪካውያን፣ ጥቁር አሜሪካውያን እና የተለያዩ አደረጃጀቶች ጉዳዩን በጊዜ ሂደት ወደ ፌደራል ይዘውት እንዲሄዱ አንዳች ዕድል ሊፈጥረ እንደሚችል ያላቸውን ተስፋ ተናግረዋል።
አድዋ ኢትዮጵያ በአፄ ምንሊክ እና ባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ አመራር ሰጪነት የጣሊያን ወራሪዎችን ድል በመምታት ሉዓላዊነቷን አስከብራ የቆየችበት እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የጥቁር ሕዝቦች ነፃነት እና ፀረ-ቅኝ ግዛት ትግል ምልክት የሆነ ታሪካዊ ድል ነው።
ከአድዋ ድል በኋላ በርካታ አገራት የፀረ-ቅኝ ግዛት ተጋድሏቸውን በማጠናከር ለዓመታት በዘለቀ ትግል ነፃነታቸውን መቀዳጀት ችለዋል።
በአፍሪካ ሁለት አገራት ቅኝ አለመገዛታቸውን ታሪክ የሚያስረዳ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ራሷን ያስከበረችው አርበኞቿ ባደረጉ ትግል ነው።
በአድዋ ጦርነት በሺዎች የሚቆጠሩ የጣሊያን ሠራዊት አባላት ሲገደሉ ሌሎች ሺህዎች ደግሞ ተማርከዋል። መድፎችን ጨምሮ ከፍተኛ መጠን ያለው የጦር መሳሪያዎችም መማረካቸውን ታሪክ ያስረዳል።
በተጨማሪም የጣሊያንን ሠራዊት ከመሩት መኮንኖች መካከል ጄነራል አልቤርቶኒ ሲማረክ ዋና አዛዥ ጄነራል ባራቴሪ ሸሽቶ አምልጧል።
ኢትዮጵያ ይህንን ታሪካዊ ድል የተጎናፀፈችበትን የካቲት 23 ቀንን በየዓመቱ በደማቅ ታሪካዊ ሁነቶች ታከብራለች።
ባለፈው የካቲት ወርም 130ኛው የአድዋ ድል በዓል ተከብሯል። ዘገባው የቢቢሲ አማርኛ ነው
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ድባብ ሎስ አንጀለስን አድምቋታል! ታዋቂዋ ድምጻዊት ኬቲ ፔሪ፣ የደቡብ አፍሪካዊቷ ታይላ እና አሜሪካዊው ራፐር ፊውቸር ባቀረቡት ማራኪ የመክፈቻ ስነ-ስርዓት፣ እንዲሁም እንደ ዴቪድ ቤካም እና ቶም ክሩዝ ያሉ የሆሊዉድ እና የስፖርት ከዋክብት በታደሙበት ከ70,000 በላይ ተመልካች በተገኘበት የሎስ አንጀለስ ስታዲየም፣ አዘጋጇ አሜሪካ ፓራጓይን 4ለ1 በመደምሰስ የዓለም ዋንጫ ዘመቻዋን በድል ጀምራለች።
የቀድሞው የአርሰናል እና የአሁኑ የሞናኮ አጥቂ ፎላሪን ባሎገን ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የዚህ ታሪካዊ ምሽት ኮከብ ሆኖ አምሽቷል።
ጨዋታው በጀመረ በ7ኛው ደቂቃ ላይ አሜሪካውያኑ በደጋፊዎቻቸው ፊት የመጀመሪያዋን ግብ አገኙ። የዚህች ግብ ጠንሳሽ ደግሞ "ካፒቴን አሜሪካ" በመባል የሚጠራው ክርስቲያን ፑሊሲች ነበር። ፑሊሲች ሁለት የፓራጓይ ተከላካዮችን በአስገራሚ ፍጥነት አልፎ ለዌስተን ማኬኒ ያቀበለውን ኳስ፣ ማኬኒ ወደ ውስጥ ሲያሻማው የፓራጓዩ ዳሚያን ቦባዲያ በድንጋጤ በገዛ መረቡ ላይ አስቆጠረው።
በማውሪሲዮ ፖቼቲኖ የሚመራው የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን የበላይነቱን አጠናክሮ ቀጠለ። በ28ኛው ደቂቃ ላይ ባሎገን ኳስ እና መረብን ቢያገናኝም ከጨዋታ ውጭ ተብሎ ተሻረበት። ሆኖም ከሶስት ደቂቃዎች በኋላ ፑሊሲች ያቀበለውን ኳስ ባሎገን በኃይል መትቶ ከመረብ በማሳረፍ መሪነቱን ወደ 2ለ0 አሳደገው።
ባሎገን በዚህ ብቻ አላቆመም! ማሊክ ቲልማን ሰንጥቆ ያቀበለውን ኳስ ይዞ በመሮጥ፣ የሰንደርላንዱን ተከላካይ ኦማር አልዴሬቴን በቀላሉ በማለፍ ኳሷን አክርሮ በመምታት የፓራጓዩን ግብ ጠባቂ ኦርላንዶ ጊልን አቅም በማሳጣት የግብ አግዳሚውን አስላሶ 3ኛዋን ግብ አገባ!
በዚህ ድንቅ ብቃቱ የ24 ዓመቱ ባሎገን በዓለም ዋንጫ ታሪክ በአንድ ጨዋታ ከአንድ በላይ ግብ ያስቆጠረ ሁለተኛው አሜሪካዊ በመሆን ስሙን በወርቅ ቀለም ጽፏል። (የመጀመሪያው በ1930ው የዓለም ዋንጫ በዚሁ በፓራጓይ ላይ ሀትሪክ የሰራው ቤርት ፓቴናውድ ነበር)።
በሁለተኛው አጋማሽ አሜሪካውያኑ ጫናቸውን ቢያበረቱም፣ ከጨዋታው ፍሰት ውጪ ፓራጓዮች የማስተዛዘኛ ግብ አገኙ። የቀድሞው የብራይተን አጥቂ ጁሊዮ ኤንሲሶ ያቀበለውን ኳስ ትውልደ ብራዚላዊው ማውሪሲዮ የአሜሪካውን ግብ ጠባቂ ማት ፍሪስን አልፎ መረብ ላይ አሳረፈው።
ሆኖም የምሽቱ ማሳረጊያ እጅግ ማራኪ ነበር! ተቀይሮ የገባው ጂዮቫኒ ሬይና ጨዋታው ሊጠናቀቅ ሰከንዶች ሲቀሩት፣ ከ20 ያርድ ርቀት በስተቀኝ እግሩ የውጭኛው ክፍል (Outside of the boot) አክርሮ የመታው ኳስ 4ኛዋን የአሜሪካ ግብ አስገኘ። ይህች ግብ የምሽቱ ምርጥ ግብ ሆና ተመዝግባለች።
በኒውዮርክ ተወልዶ በልጅነቱ ወደ ለንደን ያቀናው ባሎገን፣ በአርሰናል አካዳሚ ያደገ ተጫዋች ነው። በ2020 ወደ ዋናው ቡድን ቢያድግም በፕሪሚየር ሊጉ የመሰለፍ ዕድል ስላላገኘ ወደ ሬምስ በውሰት አቅንቶ በፈረንሳይ ሊግ 1 በ21 ግቦች ድንቅ ብቃቱን አሳየ፤ ይህም በ2023 በ35 ሚሊዮን ፓውንድ ወደ ሞናኮ እንዲዘዋወር አድርጎታል።
ለእንግሊዝ ከ15 እስከ 21 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድኖች ተጫውቶ 13 ጨዋታዎችን ያደረገው ባሎገን፣ በመጨረሻም የትውልድ ሀገሩን አሜሪካን ለመወከል መወሰኑ ለፖቼቲኖ ቡድን ትልቅ በረከት ሆኖለታል።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በስታዲየሙ ባይገኙም፣ አሜሪካውያኑ ከ32 ዓመታት በኋላ ወደ ሀገራቸው የመጣውን የዓለም ዋንጫ እጅግ በሚያኮራ እና የላቀ ብቃት በታከለበት ድል ጀምረውታል። ይህ የ4ለ1 ውጤትም አሜሪካ በዓለም ዋንጫ ታሪክ ያስመዘገበችው ከፍተኛው የድል ልዩነት (ከ1930ው የ3ለ0 ድሎች ጋር እኩል) ሆኖ ተመዝግቧል።
የቀድሞው የአርሰናል እና የአሁኑ የሞናኮ አጥቂ ፎላሪን ባሎገን ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የዚህ ታሪካዊ ምሽት ኮከብ ሆኖ አምሽቷል።
ጨዋታው በጀመረ በ7ኛው ደቂቃ ላይ አሜሪካውያኑ በደጋፊዎቻቸው ፊት የመጀመሪያዋን ግብ አገኙ። የዚህች ግብ ጠንሳሽ ደግሞ "ካፒቴን አሜሪካ" በመባል የሚጠራው ክርስቲያን ፑሊሲች ነበር። ፑሊሲች ሁለት የፓራጓይ ተከላካዮችን በአስገራሚ ፍጥነት አልፎ ለዌስተን ማኬኒ ያቀበለውን ኳስ፣ ማኬኒ ወደ ውስጥ ሲያሻማው የፓራጓዩ ዳሚያን ቦባዲያ በድንጋጤ በገዛ መረቡ ላይ አስቆጠረው።
በማውሪሲዮ ፖቼቲኖ የሚመራው የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን የበላይነቱን አጠናክሮ ቀጠለ። በ28ኛው ደቂቃ ላይ ባሎገን ኳስ እና መረብን ቢያገናኝም ከጨዋታ ውጭ ተብሎ ተሻረበት። ሆኖም ከሶስት ደቂቃዎች በኋላ ፑሊሲች ያቀበለውን ኳስ ባሎገን በኃይል መትቶ ከመረብ በማሳረፍ መሪነቱን ወደ 2ለ0 አሳደገው።
ባሎገን በዚህ ብቻ አላቆመም! ማሊክ ቲልማን ሰንጥቆ ያቀበለውን ኳስ ይዞ በመሮጥ፣ የሰንደርላንዱን ተከላካይ ኦማር አልዴሬቴን በቀላሉ በማለፍ ኳሷን አክርሮ በመምታት የፓራጓዩን ግብ ጠባቂ ኦርላንዶ ጊልን አቅም በማሳጣት የግብ አግዳሚውን አስላሶ 3ኛዋን ግብ አገባ!
በዚህ ድንቅ ብቃቱ የ24 ዓመቱ ባሎገን በዓለም ዋንጫ ታሪክ በአንድ ጨዋታ ከአንድ በላይ ግብ ያስቆጠረ ሁለተኛው አሜሪካዊ በመሆን ስሙን በወርቅ ቀለም ጽፏል። (የመጀመሪያው በ1930ው የዓለም ዋንጫ በዚሁ በፓራጓይ ላይ ሀትሪክ የሰራው ቤርት ፓቴናውድ ነበር)።
በሁለተኛው አጋማሽ አሜሪካውያኑ ጫናቸውን ቢያበረቱም፣ ከጨዋታው ፍሰት ውጪ ፓራጓዮች የማስተዛዘኛ ግብ አገኙ። የቀድሞው የብራይተን አጥቂ ጁሊዮ ኤንሲሶ ያቀበለውን ኳስ ትውልደ ብራዚላዊው ማውሪሲዮ የአሜሪካውን ግብ ጠባቂ ማት ፍሪስን አልፎ መረብ ላይ አሳረፈው።
ሆኖም የምሽቱ ማሳረጊያ እጅግ ማራኪ ነበር! ተቀይሮ የገባው ጂዮቫኒ ሬይና ጨዋታው ሊጠናቀቅ ሰከንዶች ሲቀሩት፣ ከ20 ያርድ ርቀት በስተቀኝ እግሩ የውጭኛው ክፍል (Outside of the boot) አክርሮ የመታው ኳስ 4ኛዋን የአሜሪካ ግብ አስገኘ። ይህች ግብ የምሽቱ ምርጥ ግብ ሆና ተመዝግባለች።
በኒውዮርክ ተወልዶ በልጅነቱ ወደ ለንደን ያቀናው ባሎገን፣ በአርሰናል አካዳሚ ያደገ ተጫዋች ነው። በ2020 ወደ ዋናው ቡድን ቢያድግም በፕሪሚየር ሊጉ የመሰለፍ ዕድል ስላላገኘ ወደ ሬምስ በውሰት አቅንቶ በፈረንሳይ ሊግ 1 በ21 ግቦች ድንቅ ብቃቱን አሳየ፤ ይህም በ2023 በ35 ሚሊዮን ፓውንድ ወደ ሞናኮ እንዲዘዋወር አድርጎታል።
ለእንግሊዝ ከ15 እስከ 21 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድኖች ተጫውቶ 13 ጨዋታዎችን ያደረገው ባሎገን፣ በመጨረሻም የትውልድ ሀገሩን አሜሪካን ለመወከል መወሰኑ ለፖቼቲኖ ቡድን ትልቅ በረከት ሆኖለታል።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በስታዲየሙ ባይገኙም፣ አሜሪካውያኑ ከ32 ዓመታት በኋላ ወደ ሀገራቸው የመጣውን የዓለም ዋንጫ እጅግ በሚያኮራ እና የላቀ ብቃት በታከለበት ድል ጀምረውታል። ይህ የ4ለ1 ውጤትም አሜሪካ በዓለም ዋንጫ ታሪክ ያስመዘገበችው ከፍተኛው የድል ልዩነት (ከ1930ው የ3ለ0 ድሎች ጋር እኩል) ሆኖ ተመዝግቧል።
2 days ago
ጋና ከዩራጋይ የ2010 ዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ ጨዋታ…
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በፈረንጆቹ 2010 አፍሪካዊቷ ሀገር ደቡብ አፍሪካ የዓለም ዋንጫን ማዘጋጀቷ ይታወሳል፡፡
በ2010 ለመጀመሪያ ጊዜ በአፍሪካ አህጉር በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው ውድድር በሩብ ፍጻሜ መርሐ ግብር ጋና ከዩራጋይ ያደረጉት ጨዋታ በውድድሩ ከማይረሱ ክስተቶች መካከል አንዱ ነበር፡፡
በሶከር ሲቲ ስታዲየም አፍሪካዊቷን ሀገር ጋናን ከደቡብ አሜሪካዋ ሀገር ዩራጋይ ያገናኘው የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ በመላው አፍሪካዊያን ዘንድ በጉጉት ነበር የተጠበቀው፡፡
አፍሪካ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ባዘጋጀችው የዓለም ዋንጫ ውደድር አዲስ የዓለም ዋንጫ ታሪክ በአፍሪካ ብሔራዊ ቡድን ሊጻፍ የተቃረበበት አጋጣሚ እንደነበርም ይታወሳል፡፡
በወቅቱ የጋና ብሔራዊ ቡድን የአፍሪካን በዓለም ዋንጫ ውድድር ከሩብ ፍጻሜ መሻገር ያለመቻል ታሪክ ሊቀይር መቃረቡም አይዘነጋም፡፡
ጨዋታው የሚደረግበት ሶከር ሲቲ ስታዲየም በቩቩዜላ ድምጽ የደመቀበት አጋጣሚ ይታወሳል፡፡
ጨዋታውን ጋና ማሸነፍ ብትችል አፍሪካ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም ዋንጫን ማዘጋጀት ብቻ ሳይሆን በመድረኩ ግማሽ ፍጻሜ በመግባትም በዓለም ዋንጫ ውድድር አዲስ ምዕራፍ የምትከፍትበት ነበር፡፡
በጨዋታው ሁለቱም ብሔራዊ ቡድን ጥሩ እንቅስቃሴ ያሳዩ ሲሆን የመጀመሪያው አጋማሽ መጠናቀቂያ ላይ ሱሌ ሙንታሪ ግብ አስቆጥሮ ጋና 1 ለ 0 እየመራች ወደ መልበሻ ክፍል ማምራት ችለዋል፡፡
መላው አፍሪካውያን በሱሌ ሙንታሪ አማካኝነት ግቧ ስትቆጠር የነበራቸው ደስታ ወደር አልነበረውም፡፡
ከእረፍት መልስ 55ኛው ደቂቃ ላይ ዲያጎ ፎርላ ለዩራጋይ ብሔራዊ ቡድን ግብ በማስቆጠር ሀገሩን አቻ ማድረጉ ይታወሳል፡፡
የዩራጋይ ብሔራዊ ቡድን የፊት መስመር ተጫዋች ሉዊስ ሰዋሬዝ ኳስ በእጁ በመመለሱ ጋና የፍጹም ቅጣት ምት ብታገኝም አሳሞጂያን ሳይጠቀምበት መቅረቱ አይዘነጋም፡፡
አሳሞጂያን ሀገሩ ጋና ወደ ግማሽ ፍጻሜው የምታልፍበትን ዕድል መጠቀም ባለመቻሉ መላው አፍሪካዊያንን ያስቆጨ ክስተት ነበር፡፡
ጨዋታው 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት መጠናቀቁን ተከትሎ ወደ መለያ ምት ማምራታቸው ይታወሳል፡፡
በዚህም አሸናፊውን እና ግማሽ ፍጻሜውን የሚቀላቀለውን ብሔራዊ ቡድን ለመለየት በተሰጠው የመለያ ምት ዩራጋይ አሸናፊ ሆነች፡፡
አፍሪካም በዓለም ዋንጫ ታሪክ ግማሽ ፍጻሜ መድረስ ሳትችል በመቅረቷ መላው አፍሪካ ማዘኑ ይታወሳል፡፡
ከዚያ በኋላ ግን ሞሮኮ በ2022 የዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ በመግባት በመድረኩ ግማሽ ፍጻሜ መድረስ የቻለች ቀዳሚዋ አፍሪካዊት ሀገር መሆን ችላለች፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በፈረንጆቹ 2010 አፍሪካዊቷ ሀገር ደቡብ አፍሪካ የዓለም ዋንጫን ማዘጋጀቷ ይታወሳል፡፡
በ2010 ለመጀመሪያ ጊዜ በአፍሪካ አህጉር በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው ውድድር በሩብ ፍጻሜ መርሐ ግብር ጋና ከዩራጋይ ያደረጉት ጨዋታ በውድድሩ ከማይረሱ ክስተቶች መካከል አንዱ ነበር፡፡
በሶከር ሲቲ ስታዲየም አፍሪካዊቷን ሀገር ጋናን ከደቡብ አሜሪካዋ ሀገር ዩራጋይ ያገናኘው የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ በመላው አፍሪካዊያን ዘንድ በጉጉት ነበር የተጠበቀው፡፡
አፍሪካ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ባዘጋጀችው የዓለም ዋንጫ ውደድር አዲስ የዓለም ዋንጫ ታሪክ በአፍሪካ ብሔራዊ ቡድን ሊጻፍ የተቃረበበት አጋጣሚ እንደነበርም ይታወሳል፡፡
በወቅቱ የጋና ብሔራዊ ቡድን የአፍሪካን በዓለም ዋንጫ ውድድር ከሩብ ፍጻሜ መሻገር ያለመቻል ታሪክ ሊቀይር መቃረቡም አይዘነጋም፡፡
ጨዋታው የሚደረግበት ሶከር ሲቲ ስታዲየም በቩቩዜላ ድምጽ የደመቀበት አጋጣሚ ይታወሳል፡፡
ጨዋታውን ጋና ማሸነፍ ብትችል አፍሪካ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም ዋንጫን ማዘጋጀት ብቻ ሳይሆን በመድረኩ ግማሽ ፍጻሜ በመግባትም በዓለም ዋንጫ ውድድር አዲስ ምዕራፍ የምትከፍትበት ነበር፡፡
በጨዋታው ሁለቱም ብሔራዊ ቡድን ጥሩ እንቅስቃሴ ያሳዩ ሲሆን የመጀመሪያው አጋማሽ መጠናቀቂያ ላይ ሱሌ ሙንታሪ ግብ አስቆጥሮ ጋና 1 ለ 0 እየመራች ወደ መልበሻ ክፍል ማምራት ችለዋል፡፡
መላው አፍሪካውያን በሱሌ ሙንታሪ አማካኝነት ግቧ ስትቆጠር የነበራቸው ደስታ ወደር አልነበረውም፡፡
ከእረፍት መልስ 55ኛው ደቂቃ ላይ ዲያጎ ፎርላ ለዩራጋይ ብሔራዊ ቡድን ግብ በማስቆጠር ሀገሩን አቻ ማድረጉ ይታወሳል፡፡
የዩራጋይ ብሔራዊ ቡድን የፊት መስመር ተጫዋች ሉዊስ ሰዋሬዝ ኳስ በእጁ በመመለሱ ጋና የፍጹም ቅጣት ምት ብታገኝም አሳሞጂያን ሳይጠቀምበት መቅረቱ አይዘነጋም፡፡
አሳሞጂያን ሀገሩ ጋና ወደ ግማሽ ፍጻሜው የምታልፍበትን ዕድል መጠቀም ባለመቻሉ መላው አፍሪካዊያንን ያስቆጨ ክስተት ነበር፡፡
ጨዋታው 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት መጠናቀቁን ተከትሎ ወደ መለያ ምት ማምራታቸው ይታወሳል፡፡
በዚህም አሸናፊውን እና ግማሽ ፍጻሜውን የሚቀላቀለውን ብሔራዊ ቡድን ለመለየት በተሰጠው የመለያ ምት ዩራጋይ አሸናፊ ሆነች፡፡
አፍሪካም በዓለም ዋንጫ ታሪክ ግማሽ ፍጻሜ መድረስ ሳትችል በመቅረቷ መላው አፍሪካ ማዘኑ ይታወሳል፡፡
ከዚያ በኋላ ግን ሞሮኮ በ2022 የዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜ በመግባት በመድረኩ ግማሽ ፍጻሜ መድረስ የቻለች ቀዳሚዋ አፍሪካዊት ሀገር መሆን ችላለች፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
2 days ago
ያለ ሐኪም ትዕዛዝ አንቲባዮቲክስ መውሰድ ጀርሞችን በሰውነታችን ውስጥ ማሳደግ መሆኑን ያውቃሉ?
#fastmereja :- የጸረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች በጀርሞች መላመድን (AMR) ለመከላከል አስቸኳይና የተቀናጀ እርምጃ የማይወሰድ ከሆነ፣ እ.ኤ.አ በ2050 በዓለም አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ወደ 10 ሚሊዮን ሊያሽቆለቁል እንደሚችል የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን አስታወቀ።
ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ይህንን ያስታወቀው፤ «የፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች በጀርሞች መለመድን ለመከላከል የተቀናጀ እርምጃ፡ የአንድ ጤናን በግንዛቤ እና በትምህርት ማሳደግ» በሚል መሪ ቃል፣ በአገር አቀፍ ደረጃ ለ14ኛ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚከበረውን የግንዛቤ ማስጨበጫ ቀንን አስመልክቶ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው።
የጀርሞች መድኃኒት መላመድ (AMR) ማለት በሰውም ሆነ በእንስሳት ላይ ለሚከሰቱ ተላላፊ በሽታዎች ማከሚያ የምንወስዳቸው የፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች (ለምሳሌ፦ አንቲባዮቲክስ፣ የቲቢ፣ የኤች.አይ.ቪ ወይም የወባ መድኃኒቶች) በሽታ አምጪ ጀርሞችን መግደል ወይም መቆጣጠር ሳይችሉ ሲቀሩ ሲሆን ጀርሞቹ መድኃኒቱን የመቋቋም አቅም ስለሚያገኟቸው በሰውነት ውስጥ ተከማችተው በመኖርና በመራባት ሕመሙ በቀላሉ እንዳይድን እንደሚያደርጉት አስታውቋል።
ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ በሰጠው መግለጫ፤ ችግሩ በአሁኑ ወቅት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱንና በሰው፣ በእንስሳትና በአካባቢ ጤና እንዲሁም በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ቀውስ እያስከተለ እንደሚገኝ ጠቅሷል።
በአሁኑ ወቅት በየዓመቱ ከ750,000 በላይ ሰዎች በዚህ ምክንያት ህይወታቸውን እንደሚያጡና ወደፊት ሊደርስ የሚችለውን የሰው ህይወት መጥፋት ከመከላከል ባሻገር፣ በዓለም ኢኮኖሚ ላይ ሊደርስ የሚችለውን የ10 ትሪሊዮን ዶላር ከፍተኛ ኪሳራ (ከ2-3% የኢኮኖሚ ቅናሽ) ለመታደግ አስቸኳይ እርምጃ እንደሚያስፈልግ ግምቶች ማሳየታቸውን ባለሥልጣኑ ገልጿል።
በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ በቂ የሕክምና ተቋማት፣ የንጹህ ውሃ አቅርቦት እጥረት ባለባቸውና ውስን ሀብት ባላቸው ታዳጊ አገራት ላይ የችግሩ አሳሳቢነት ይበልጥ ጎልቶ እንደሚታይም ተመልክቷል።
ይህንን ድምፅ አልባ ወረርሽኝ ለመከላከል ህብረተሰቡ መድኃኒቶችን በባለሙያ ትዕዛዝ ብቻ መውሰድና የግል ንጽህናውን መጠበቅ እንዳለበት ያሳሰበው ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ፤ ችግሩን መከላከል ለአንድ አካል ብቻ የሚተው ባለመሆኑ መላው ህብረተሰብ፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ የጤና ባለሙያዎችና መገናኛ ብዙኃን በጋራ ሊረባረቡ እንደሚገባ ጥሪ አቅርቧል።
ዕለቱም በመጪው ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም (June 15, 2026) በልዩ ልዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅቶች በአገር አቀፍ ደረጃ እንደሚከበር ታውቋል።
#fastmereja :- የጸረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች በጀርሞች መላመድን (AMR) ለመከላከል አስቸኳይና የተቀናጀ እርምጃ የማይወሰድ ከሆነ፣ እ.ኤ.አ በ2050 በዓለም አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ወደ 10 ሚሊዮን ሊያሽቆለቁል እንደሚችል የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን አስታወቀ።
ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ይህንን ያስታወቀው፤ «የፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች በጀርሞች መለመድን ለመከላከል የተቀናጀ እርምጃ፡ የአንድ ጤናን በግንዛቤ እና በትምህርት ማሳደግ» በሚል መሪ ቃል፣ በአገር አቀፍ ደረጃ ለ14ኛ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚከበረውን የግንዛቤ ማስጨበጫ ቀንን አስመልክቶ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው።
የጀርሞች መድኃኒት መላመድ (AMR) ማለት በሰውም ሆነ በእንስሳት ላይ ለሚከሰቱ ተላላፊ በሽታዎች ማከሚያ የምንወስዳቸው የፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች (ለምሳሌ፦ አንቲባዮቲክስ፣ የቲቢ፣ የኤች.አይ.ቪ ወይም የወባ መድኃኒቶች) በሽታ አምጪ ጀርሞችን መግደል ወይም መቆጣጠር ሳይችሉ ሲቀሩ ሲሆን ጀርሞቹ መድኃኒቱን የመቋቋም አቅም ስለሚያገኟቸው በሰውነት ውስጥ ተከማችተው በመኖርና በመራባት ሕመሙ በቀላሉ እንዳይድን እንደሚያደርጉት አስታውቋል።
ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ በሰጠው መግለጫ፤ ችግሩ በአሁኑ ወቅት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱንና በሰው፣ በእንስሳትና በአካባቢ ጤና እንዲሁም በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ቀውስ እያስከተለ እንደሚገኝ ጠቅሷል።
በአሁኑ ወቅት በየዓመቱ ከ750,000 በላይ ሰዎች በዚህ ምክንያት ህይወታቸውን እንደሚያጡና ወደፊት ሊደርስ የሚችለውን የሰው ህይወት መጥፋት ከመከላከል ባሻገር፣ በዓለም ኢኮኖሚ ላይ ሊደርስ የሚችለውን የ10 ትሪሊዮን ዶላር ከፍተኛ ኪሳራ (ከ2-3% የኢኮኖሚ ቅናሽ) ለመታደግ አስቸኳይ እርምጃ እንደሚያስፈልግ ግምቶች ማሳየታቸውን ባለሥልጣኑ ገልጿል።
በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ በቂ የሕክምና ተቋማት፣ የንጹህ ውሃ አቅርቦት እጥረት ባለባቸውና ውስን ሀብት ባላቸው ታዳጊ አገራት ላይ የችግሩ አሳሳቢነት ይበልጥ ጎልቶ እንደሚታይም ተመልክቷል።
ይህንን ድምፅ አልባ ወረርሽኝ ለመከላከል ህብረተሰቡ መድኃኒቶችን በባለሙያ ትዕዛዝ ብቻ መውሰድና የግል ንጽህናውን መጠበቅ እንዳለበት ያሳሰበው ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ፤ ችግሩን መከላከል ለአንድ አካል ብቻ የሚተው ባለመሆኑ መላው ህብረተሰብ፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ የጤና ባለሙያዎችና መገናኛ ብዙኃን በጋራ ሊረባረቡ እንደሚገባ ጥሪ አቅርቧል።
ዕለቱም በመጪው ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም (June 15, 2026) በልዩ ልዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅቶች በአገር አቀፍ ደረጃ እንደሚከበር ታውቋል።
Sponsored by
Surafel
2 days ago
በስታዲየሙ የተገኘው ደጋፊ ባየው ድንቅ የእግር ኳስ ምሽት እጅግ እንደተደሰተ ምንም ጥርጥር የለውም። አንድ ቡድን በዓለም ዋንጫ የመክፈቻ ጨዋታው ሊያሳየው የሚገባውን አዎንታዊ፣ ፈጠራ የታከለበት እና ጉልበት የተሞላበት እጅግ ማራኪ እንቅስቃሴ የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን አሳይቶናል።
ተጫዋቾቹ ኳስ ሲነጠቁ መልሰው ለማግኘት የነበራቸው ትጋት እና ኳስ መስርተው ለመጫወት የነበራቸው ድፍረት በእውነት የሚያስደንቅ ነበር። ኳስ ይዘውም ሆነ ሳይዙ ያሳዩት የጨዋታ ጥራት እና ብርታት በስታዲየም ለተገኘው ተመልካች ብዙ የሚያስደስቱ እና የሚያስደንቁ ትዕይንቶችን ፈጥሯል። በተለይም በመጀመሪያው አጋማሽ በነበራቸው ፍጹም የበላይነት ጨዋታውን ገና በዕረፍት ሰዓት ነበር የጨረሱት ማለት ይቻላል።
በሁለተኛው አጋማሽ ላይ የተደረጉት የተጫዋች ቅያሬዎች የቡድኑን የጨዋታ ምት እና ጉልበት በመጠኑም ቢሆን እንዲቀንስ አድርገውታል፤ ይህ ደግሞ በእግር ኳስ የሚጠበቅ እና ለመረዳት የማያስቸግር ነው። ፓራጓዮች በሁለተኛው አጋማሽ ወደ ጨዋታው ለመመለስ መንፈራገጥ አሳይተው ግብ ማስቆጠር ቢችሉም፣ አሜሪካውያኑ የፈጠሯቸውን በርካታ ዕድሎች በሙሉ ቢጠቀሙ ኖሮ ውጤቱ በቀላሉ አምስት ወይም ስድስት ሊደርስ ይችል ነበር።
በመጨረሻም ጨዋታው በአሜሪካ 4ለ1 አሸናፊነት የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ይህ የላቀ ብቃት አሜሪካን በቀሪዎቹ የምድብ ጨዋታዎች በከፍተኛ የሞራል ስንቅ እና በራስ መተማመን እንድትጓዝ የሚያደርጋት ነው።
ተጫዋቾቹ ኳስ ሲነጠቁ መልሰው ለማግኘት የነበራቸው ትጋት እና ኳስ መስርተው ለመጫወት የነበራቸው ድፍረት በእውነት የሚያስደንቅ ነበር። ኳስ ይዘውም ሆነ ሳይዙ ያሳዩት የጨዋታ ጥራት እና ብርታት በስታዲየም ለተገኘው ተመልካች ብዙ የሚያስደስቱ እና የሚያስደንቁ ትዕይንቶችን ፈጥሯል። በተለይም በመጀመሪያው አጋማሽ በነበራቸው ፍጹም የበላይነት ጨዋታውን ገና በዕረፍት ሰዓት ነበር የጨረሱት ማለት ይቻላል።
በሁለተኛው አጋማሽ ላይ የተደረጉት የተጫዋች ቅያሬዎች የቡድኑን የጨዋታ ምት እና ጉልበት በመጠኑም ቢሆን እንዲቀንስ አድርገውታል፤ ይህ ደግሞ በእግር ኳስ የሚጠበቅ እና ለመረዳት የማያስቸግር ነው። ፓራጓዮች በሁለተኛው አጋማሽ ወደ ጨዋታው ለመመለስ መንፈራገጥ አሳይተው ግብ ማስቆጠር ቢችሉም፣ አሜሪካውያኑ የፈጠሯቸውን በርካታ ዕድሎች በሙሉ ቢጠቀሙ ኖሮ ውጤቱ በቀላሉ አምስት ወይም ስድስት ሊደርስ ይችል ነበር።
በመጨረሻም ጨዋታው በአሜሪካ 4ለ1 አሸናፊነት የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ይህ የላቀ ብቃት አሜሪካን በቀሪዎቹ የምድብ ጨዋታዎች በከፍተኛ የሞራል ስንቅ እና በራስ መተማመን እንድትጓዝ የሚያደርጋት ነው።
2 days ago
በፌስቡክ እና በሌሎች የሜታ (Meta) አገልግሎቶች ላይ መስተጓጎል አጋጠመ!
ዛሬ ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በዓለም ዙሪያ የሚገኙ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የፌስቡክ፣ የኢንስታግራም እና የሜሴንጀር ተጠቃሚዎች ከፍተኛ የአገልግሎት መቋረጥ እያጋጠማቸው መሆኑን ሪፖርት እያደረጉ ይገኛሉ።
ምን ተከሰተ?
ብዙሃኑ ተጠቃሚዎች ከበይነ-መረብ አካውንቶቻቸው በራሱ ጊዜ Log out እየሆኑባቸው ሲሆን፥ ተመልሰው ለመግባት በሚሞክሩበት ወቅትም የሚከተሉትን የስህተት መልዕክቶች እያዩ መሆናቸውን ገልጸዋል፦
- Something went wrong” የሆነ የተሳሳተ ነገር ተከስቷል) *Query error” (የጥያቄ ስህተት) ከተለመደው የፌስቡክ መተግበሪያ በተጨማሪ የ Messenger እና የInstagram አገልግሎቶችም ተመሳሳይ እክል እንደገጠማቸው ታውቋል።
ምን ማድረግ ይኖርብዎታል? ችግሩ ከእርስዎ ስልክ ወይም የኢንተርኔት ግንኙነት ጋር የተያያዘ ሳይሆን ከራሱ ከሜታ (Meta) ሰርቨር የመነጨ በመሆኑ፦
1. አይደናገጡ፦አካውንቴ ተጠለፈ (Hack ተደረገ) ብለው እንዳይሰጉ።
2. ይጠብቁ፦የሜታ የቴክኒክ ባለሙያዎች ችግሩን ቀርፈው አገልግሎቱን ወደ ነበረበት እስኪመልሱ ድረስ በትዕግስት መጠበቅ ብልህነት ነው።
Seledadotio
Seledadotio
ዛሬ ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በዓለም ዙሪያ የሚገኙ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የፌስቡክ፣ የኢንስታግራም እና የሜሴንጀር ተጠቃሚዎች ከፍተኛ የአገልግሎት መቋረጥ እያጋጠማቸው መሆኑን ሪፖርት እያደረጉ ይገኛሉ።
ምን ተከሰተ?
ብዙሃኑ ተጠቃሚዎች ከበይነ-መረብ አካውንቶቻቸው በራሱ ጊዜ Log out እየሆኑባቸው ሲሆን፥ ተመልሰው ለመግባት በሚሞክሩበት ወቅትም የሚከተሉትን የስህተት መልዕክቶች እያዩ መሆናቸውን ገልጸዋል፦
- Something went wrong” የሆነ የተሳሳተ ነገር ተከስቷል) *Query error” (የጥያቄ ስህተት) ከተለመደው የፌስቡክ መተግበሪያ በተጨማሪ የ Messenger እና የInstagram አገልግሎቶችም ተመሳሳይ እክል እንደገጠማቸው ታውቋል።
ምን ማድረግ ይኖርብዎታል? ችግሩ ከእርስዎ ስልክ ወይም የኢንተርኔት ግንኙነት ጋር የተያያዘ ሳይሆን ከራሱ ከሜታ (Meta) ሰርቨር የመነጨ በመሆኑ፦
1. አይደናገጡ፦አካውንቴ ተጠለፈ (Hack ተደረገ) ብለው እንዳይሰጉ።
2. ይጠብቁ፦የሜታ የቴክኒክ ባለሙያዎች ችግሩን ቀርፈው አገልግሎቱን ወደ ነበረበት እስኪመልሱ ድረስ በትዕግስት መጠበቅ ብልህነት ነው።
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
12ኛ ዙር የደም ልገሳ መርሃ ግብር
የዓለም የደም ለጋሾች ቀን እና
የተስፋ አዲስ ቤተሰቦች 3ኛ ዓመት በዓል ማክበር
📅 ሰኔ 6 እና 7, 2018 ዓ.ም.
📍 በኢትዮጵያ 20 + ከተሞች
አንድ የደም ልገሳ እስከ ሦስት ሰዎች ሕይወት ሊያድን ይችላል። በየቀኑ በሆስፒታሎቻችን ውስጥ ለቀዶ ሕክምና፣ ለአደጋ ተጎጂዎች፣ ለካንሰር ታማሚዎች፣ ለእናቶች እና ለሌሎች በርካታ ሕሙማን ደም በአስቸኳይ ያስፈልጋል።
ይህ 12ኛው ዙር የደም ልገሳ መርሃ ግብር የተስፋ አዲስ ቤተሰቦች ለ3 ዓመታት ሲያከናውኑት የቆየውን የሰብዓዊነት ጉዞ የሚያከብር ሲሆን፣ በዓለም የደም ለጋሾች ቀን ላይም ለሕይወት አዳኝ ለጋሾች የምስጋና መልዕክት ያስተላልፋል።
እርስዎ የሚለግሱት ደም ለአንድ ቤተሰብ ተስፋ፣
ለአንድ ታማሚ ሕይወት፣
ለአንድ እናት ፈገግታ፣
ለአንድ ልጅ ነገን ሊሰጥ ይችላል።
🤝 ሁላችንም በጎ ፈቃደኞች፣ ወጣቶች፣ ቤተሰቦች፣ ተቋማት እና ማኅበረሰቡ በአጠቃላይ በዚህ ታላቅ የሕይወት ማዳን ተግባር እንዲሳተፉ በክብር እንጋብዛለን።
🩸 ደም መለገስ ሕይወት መስጠት ነው!
ኑ! በደማችን አዲስ ታሪክ እንፃፍ! ❤️🩸
#worldblooddonorday #የደም_ልገሳ #ተስፋ_አዲስ_ቤተሰቦች #donatebloodsavelives #20ከተሞች_አንድ_ዓላማ #ሕይወትን_እናድን
የዓለም የደም ለጋሾች ቀን እና
የተስፋ አዲስ ቤተሰቦች 3ኛ ዓመት በዓል ማክበር
📅 ሰኔ 6 እና 7, 2018 ዓ.ም.
📍 በኢትዮጵያ 20 + ከተሞች
አንድ የደም ልገሳ እስከ ሦስት ሰዎች ሕይወት ሊያድን ይችላል። በየቀኑ በሆስፒታሎቻችን ውስጥ ለቀዶ ሕክምና፣ ለአደጋ ተጎጂዎች፣ ለካንሰር ታማሚዎች፣ ለእናቶች እና ለሌሎች በርካታ ሕሙማን ደም በአስቸኳይ ያስፈልጋል።
ይህ 12ኛው ዙር የደም ልገሳ መርሃ ግብር የተስፋ አዲስ ቤተሰቦች ለ3 ዓመታት ሲያከናውኑት የቆየውን የሰብዓዊነት ጉዞ የሚያከብር ሲሆን፣ በዓለም የደም ለጋሾች ቀን ላይም ለሕይወት አዳኝ ለጋሾች የምስጋና መልዕክት ያስተላልፋል።
እርስዎ የሚለግሱት ደም ለአንድ ቤተሰብ ተስፋ፣
ለአንድ ታማሚ ሕይወት፣
ለአንድ እናት ፈገግታ፣
ለአንድ ልጅ ነገን ሊሰጥ ይችላል።
🤝 ሁላችንም በጎ ፈቃደኞች፣ ወጣቶች፣ ቤተሰቦች፣ ተቋማት እና ማኅበረሰቡ በአጠቃላይ በዚህ ታላቅ የሕይወት ማዳን ተግባር እንዲሳተፉ በክብር እንጋብዛለን።
🩸 ደም መለገስ ሕይወት መስጠት ነው!
ኑ! በደማችን አዲስ ታሪክ እንፃፍ! ❤️🩸
#worldblooddonorday #የደም_ልገሳ #ተስፋ_አዲስ_ቤተሰቦች #donatebloodsavelives #20ከተሞች_አንድ_ዓላማ #ሕይወትን_እናድን
2 days ago
የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ ከወዲሁ ታወቀ? የጀርመናዊው ሊቅ አስገራሚ ግምት
#ethiopia | ባለፉት ሦስት ተከታታይ የዓለም ዋንጫዎች የጀርመንን፣ የፈረንሳይን እንዲሁም የአርጀንቲናን ድል አስቀድሞ በትክክል በመተንበይ ስሙ ናኝቶ የቆየው ምጣኔ ሀብት አዋቂና የሂሳብ ሊቅ ዮአኪም ክሌመንት ለዘንድሮው የዓለም ዋንጫ አዲስ መላምት ይዞ ብቅ ብሏል።
ባለሙያው የስፖርታዊ ብቃትን መለኪያዎች ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ስነ-ህዝባዊ መረጃዎችን ያካተተ ሳይንሳዊ የስሌት ቀመር በመጠቀም በ2026ቱ ታላቅ የኳስ መድረክ ኔዘርላንድስ ባለድል እንደምትሆን አስታውቋል።
ይህ የክሌመንት አዲስ መግለጫ እንደ አርጀንቲና፣ ፈረንሳይ፣ እንግሊዝ እና ስፔን ላሉት ግዙፍ የኳስ ሀገራት የተሰጠውን ቅድሚያ ግምት ወደ ጎን በመግፋት ለሆላንድ እውቅና በመስጠቱ በስፖርቱ ማህበረሰብ ዘንድ ሰፊ መነጋገሪያ ፈጥሯል።
በሊቁ ሳይንሳዊ ቀመር ትንተና መሰረት በሮናልድ ኪውማን የሚመራው የኔዘርላንድስ ብሔራዊ ቡድን ለፍጻሜ ደርሶ የፖርቹጋልን አቻ በመርታት በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም ሻምፒዮንነትን ክብር ይቀዳጃል።
እግር ኳስ ሁልጊዜም ባልተጠበቁ ክስተቶችና በአጋጣሚዎች የተሞላ በመሆኑ ስሌቱ መቶ በመቶ ፍጹም ሊሆን እንደማይችል ባለሙያው ቢያስገነዝብም፣ ከዚህ ቀደም በ1974፣ 1978 እና 2010 ለፍጻሜ ደርሰው ለጥቂት ዋንጫው ያመለጣቸው ብርቱካናማዎቹ ከአንድ ወር በኋላ በሚጠናቀቀው በዚህ ውድድር ታሪክ ሰርተው ግምቱን እውን ካደረጉት፣ የጀርመናዊው ምሁር የማይሳሳት የትንበያ ስም በዓለም መድረክ ላይ በድጋሚ ደምቆ የሚመዘገብ ይሆናል።#አዲስ አድማስ
#worldcup2026 #netherlands #joachimklement #footballprediction #worldcupwinners #football #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ባለፉት ሦስት ተከታታይ የዓለም ዋንጫዎች የጀርመንን፣ የፈረንሳይን እንዲሁም የአርጀንቲናን ድል አስቀድሞ በትክክል በመተንበይ ስሙ ናኝቶ የቆየው ምጣኔ ሀብት አዋቂና የሂሳብ ሊቅ ዮአኪም ክሌመንት ለዘንድሮው የዓለም ዋንጫ አዲስ መላምት ይዞ ብቅ ብሏል።
ባለሙያው የስፖርታዊ ብቃትን መለኪያዎች ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ስነ-ህዝባዊ መረጃዎችን ያካተተ ሳይንሳዊ የስሌት ቀመር በመጠቀም በ2026ቱ ታላቅ የኳስ መድረክ ኔዘርላንድስ ባለድል እንደምትሆን አስታውቋል።
ይህ የክሌመንት አዲስ መግለጫ እንደ አርጀንቲና፣ ፈረንሳይ፣ እንግሊዝ እና ስፔን ላሉት ግዙፍ የኳስ ሀገራት የተሰጠውን ቅድሚያ ግምት ወደ ጎን በመግፋት ለሆላንድ እውቅና በመስጠቱ በስፖርቱ ማህበረሰብ ዘንድ ሰፊ መነጋገሪያ ፈጥሯል።
በሊቁ ሳይንሳዊ ቀመር ትንተና መሰረት በሮናልድ ኪውማን የሚመራው የኔዘርላንድስ ብሔራዊ ቡድን ለፍጻሜ ደርሶ የፖርቹጋልን አቻ በመርታት በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም ሻምፒዮንነትን ክብር ይቀዳጃል።
እግር ኳስ ሁልጊዜም ባልተጠበቁ ክስተቶችና በአጋጣሚዎች የተሞላ በመሆኑ ስሌቱ መቶ በመቶ ፍጹም ሊሆን እንደማይችል ባለሙያው ቢያስገነዝብም፣ ከዚህ ቀደም በ1974፣ 1978 እና 2010 ለፍጻሜ ደርሰው ለጥቂት ዋንጫው ያመለጣቸው ብርቱካናማዎቹ ከአንድ ወር በኋላ በሚጠናቀቀው በዚህ ውድድር ታሪክ ሰርተው ግምቱን እውን ካደረጉት፣ የጀርመናዊው ምሁር የማይሳሳት የትንበያ ስም በዓለም መድረክ ላይ በድጋሚ ደምቆ የሚመዘገብ ይሆናል።#አዲስ አድማስ
#worldcup2026 #netherlands #joachimklement #footballprediction #worldcupwinners #football #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 days ago
የዲጂታል ኢኮኖሚ አዲስ ምዕራፍ - ከስትራቴጂ ወደ ስኬት
***********************
(የዕለቱ መልዕክት)
ዛሬ ዓለማችን በቴክኖሎጂ እና በኢኖቬሽን ፈጣን ግስጋሴ ውስጥ ትገኛለች። ኢትዮጵያም ይህንን ዓለም አቀፋዊ እውነት በውል በመገንዘብ፣ ሁለንተናዊ ኢኮኖሚዋን ከመሠረቱ የሚቀይር ታሪካዊ የዲጂታል ሽግግር እያከናወነች ትገኛለች።
በተለይም ባለፉት አምስት ዓመታት ሀገራችን ያለባትን ዘላቂ የቢሮክራሲ እና የኢኮኖሚ ፈተናዎች ለመቅረፍ ዲጂታላይዜሽንን እንደ ዋነኛ ስትራቴጂያዊ መሣሪያ በመውሰድ እየሠራችበት ትገኛለች።
ይህ ጉዞ የሀገርን የልማት ምሰሶ በጽኑ መሠረት ላይ የሚያጸና የመንግሥት የረጅም ጊዜ ቁርጠኝነት ማሳያ ነው ብለን እናምናለን።
በአንድ ወቅት የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እንደ ሩቅ ሕልም ይታይ እንደነበር አይዘነጋም፤ ባለፉት አምስት ዓመታት በተከናወኑት መሠረታዊ ሥራዎች ግን ዛሬ ላይ ሊሻር በማይችል እውነታ ላይ የቆመ መሠረት ተጥሏል።
መንግሥት ያደረጋቸው ሰፊ የፖሊሲ እና የሕግ ማሻሻያዎች “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025” ስትራቴጂን በስኬት ለማጠናቀቅ አስችለዋል።
አሁን ደግሞ የሀገራችንን የትራንስፎርሜሽን ጉዞ ይበልጥ የሚያፋጥን እና ይበልጥ ስኬታማ የሚያደርገው “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” የተሰኘው ብሔራዊ ስትራቴጂ ፀድቆ ወደ ሥራ እንዲገባ መደረጉ የሂደቱን ቀጣይነት ያረጋግጣል።
ከዚህ ጎን ለጎን የሰው ሠራሽ አስተውሎት ኢንስቲትዩት መቋቋም ለችግር ፈቺ የቴክኖሎጂ መፍትሔዎች መበልጸግ ምቹ ሁኔታን መፍጠሩ የሚበረታታ እርምጃ ነው።
በዚህ ዘመናዊ የታሪክ እጥፋት ውስጥ የ“ፋይዳ” ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም እና የ“ኢትዮኮደርስ” ኢኒሼቲቭ ሚና እጅግ የላቀ ነው።
የዲጂታል መታወቂያ ለኢኮኖሚው ግንባታ ልክ እንደ ቤት መሠረት ነው። እስከ 90 ሚሊዮን ዜጎችን በሥርዓቱ ውስጥ ለማቀፍ የታቀደው ይህ ግዙፍ መርሐ ግብር ለባንክ፣ ለፋይናንስ፣ ለንግድ እንቅስቃሴ እና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ ምሰሶ ነው።
“የቆጠሩት እህል አያልቅም” እንደሚባለው የሀገርን የሰው ኃይል በዕውቀት ሳያደራጁ ዘላቂ ስኬትን ማሰብ አይቻልም። በመሆኑም በ“ኢትዮኮደርስ” ኢኒሼቲቭ 5 ሚሊዮን ዜጎች የዲጂታል ክህሎት ሥልጠና እንዲያገኙ ማድረግ የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያ የሚረከቡ ባለሙያዎችን ለማፍራት የተጣለ ታላቅ መሠረት ነው።
የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን በሁሉም አካባቢዎች እየተገነባ ያለው “የመሶብ” የአንድ ማዕከል አገልግሎትም የተንዛዛ ቢሮክራሲን እና የዜጎችን እንግልት በማስቀረት የመንግሥትን ግልጽነት እና ተጠያቂነት በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል። ይህ ዓይነቱ አሠራር ሙስና እና ብክነትን በዘላቂነት ለመከላከል የሚያስችል አስተማማኝ ተቋማዊ አቅም ይፈጥራል።
በፋይናንስ ዘርፍም ቢሆን በ2017 በጀት ዓመት ብቻ በዲጂታል የተከናወነው የግብይት ዋጋ 16 ትሪሊዮን ብር መድረሱ የዲጂታል ኢኮኖሚው ምን ያህል ውጤታማ እና ተደራሽ እየሆነ ለመምጣቱ ሕያው ማሳያ ነው።
ይህ ስኬት ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች እና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች በቀላሉ የብድር እና የቁጠባ አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ የፋይናንስ አካታችነትን በተግባር አረጋግጧል።
ለወደፊቱም መሠረታዊ የመንግሥት አገልግሎቶችን ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ፕላትፎርሞች ተደራሽ ለማድረግ የታቀደው ዕቅድ የሀገራችንን የነገ ገጽታ በእጅጉ የሚቀይር ነው።
መንግሥት የሳይበር ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ እና የስታርትአፕ ሥነ ምኅዳርን በማጠናከር፣ የዲጂታል ሽግግር ሂደቱን አስተማማኝ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ እያደረገው ይገኛል።
በአጠቃላይ ይህ ታሪካዊ ጉዞ የዜጎችን የዕለት ተዕለት ኑሮ የሚያቀልል፣ ሀገራችንን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርግ እና የኢኮኖሚ ልማታችንን ከሕልም ወደ እውነት የለወጠ የጋራ ብሔራዊ ስኬታችን በመሆኑ ሁሉም አካላት ለስኬቱ የበኩላቸውን ድርሻ ሊወጡ ይገባል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #digitalethiopia #5millioncoders #success #𝐃𝐢𝐠𝐢𝐭𝐚𝐥𝐄𝐜𝐨𝐧𝐨𝐦𝐲
***********************
(የዕለቱ መልዕክት)
ዛሬ ዓለማችን በቴክኖሎጂ እና በኢኖቬሽን ፈጣን ግስጋሴ ውስጥ ትገኛለች። ኢትዮጵያም ይህንን ዓለም አቀፋዊ እውነት በውል በመገንዘብ፣ ሁለንተናዊ ኢኮኖሚዋን ከመሠረቱ የሚቀይር ታሪካዊ የዲጂታል ሽግግር እያከናወነች ትገኛለች።
በተለይም ባለፉት አምስት ዓመታት ሀገራችን ያለባትን ዘላቂ የቢሮክራሲ እና የኢኮኖሚ ፈተናዎች ለመቅረፍ ዲጂታላይዜሽንን እንደ ዋነኛ ስትራቴጂያዊ መሣሪያ በመውሰድ እየሠራችበት ትገኛለች።
ይህ ጉዞ የሀገርን የልማት ምሰሶ በጽኑ መሠረት ላይ የሚያጸና የመንግሥት የረጅም ጊዜ ቁርጠኝነት ማሳያ ነው ብለን እናምናለን።
በአንድ ወቅት የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ እንደ ሩቅ ሕልም ይታይ እንደነበር አይዘነጋም፤ ባለፉት አምስት ዓመታት በተከናወኑት መሠረታዊ ሥራዎች ግን ዛሬ ላይ ሊሻር በማይችል እውነታ ላይ የቆመ መሠረት ተጥሏል።
መንግሥት ያደረጋቸው ሰፊ የፖሊሲ እና የሕግ ማሻሻያዎች “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025” ስትራቴጂን በስኬት ለማጠናቀቅ አስችለዋል።
አሁን ደግሞ የሀገራችንን የትራንስፎርሜሽን ጉዞ ይበልጥ የሚያፋጥን እና ይበልጥ ስኬታማ የሚያደርገው “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” የተሰኘው ብሔራዊ ስትራቴጂ ፀድቆ ወደ ሥራ እንዲገባ መደረጉ የሂደቱን ቀጣይነት ያረጋግጣል።
ከዚህ ጎን ለጎን የሰው ሠራሽ አስተውሎት ኢንስቲትዩት መቋቋም ለችግር ፈቺ የቴክኖሎጂ መፍትሔዎች መበልጸግ ምቹ ሁኔታን መፍጠሩ የሚበረታታ እርምጃ ነው።
በዚህ ዘመናዊ የታሪክ እጥፋት ውስጥ የ“ፋይዳ” ብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም እና የ“ኢትዮኮደርስ” ኢኒሼቲቭ ሚና እጅግ የላቀ ነው።
የዲጂታል መታወቂያ ለኢኮኖሚው ግንባታ ልክ እንደ ቤት መሠረት ነው። እስከ 90 ሚሊዮን ዜጎችን በሥርዓቱ ውስጥ ለማቀፍ የታቀደው ይህ ግዙፍ መርሐ ግብር ለባንክ፣ ለፋይናንስ፣ ለንግድ እንቅስቃሴ እና ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ወሳኝ ምሰሶ ነው።
“የቆጠሩት እህል አያልቅም” እንደሚባለው የሀገርን የሰው ኃይል በዕውቀት ሳያደራጁ ዘላቂ ስኬትን ማሰብ አይቻልም። በመሆኑም በ“ኢትዮኮደርስ” ኢኒሼቲቭ 5 ሚሊዮን ዜጎች የዲጂታል ክህሎት ሥልጠና እንዲያገኙ ማድረግ የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያ የሚረከቡ ባለሙያዎችን ለማፍራት የተጣለ ታላቅ መሠረት ነው።
የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን በሁሉም አካባቢዎች እየተገነባ ያለው “የመሶብ” የአንድ ማዕከል አገልግሎትም የተንዛዛ ቢሮክራሲን እና የዜጎችን እንግልት በማስቀረት የመንግሥትን ግልጽነት እና ተጠያቂነት በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል። ይህ ዓይነቱ አሠራር ሙስና እና ብክነትን በዘላቂነት ለመከላከል የሚያስችል አስተማማኝ ተቋማዊ አቅም ይፈጥራል።
በፋይናንስ ዘርፍም ቢሆን በ2017 በጀት ዓመት ብቻ በዲጂታል የተከናወነው የግብይት ዋጋ 16 ትሪሊዮን ብር መድረሱ የዲጂታል ኢኮኖሚው ምን ያህል ውጤታማ እና ተደራሽ እየሆነ ለመምጣቱ ሕያው ማሳያ ነው።
ይህ ስኬት ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች እና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች በቀላሉ የብድር እና የቁጠባ አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ የፋይናንስ አካታችነትን በተግባር አረጋግጧል።
ለወደፊቱም መሠረታዊ የመንግሥት አገልግሎቶችን ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ፕላትፎርሞች ተደራሽ ለማድረግ የታቀደው ዕቅድ የሀገራችንን የነገ ገጽታ በእጅጉ የሚቀይር ነው።
መንግሥት የሳይበር ሉዓላዊነትን በማረጋገጥ እና የስታርትአፕ ሥነ ምኅዳርን በማጠናከር፣ የዲጂታል ሽግግር ሂደቱን አስተማማኝ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ እያደረገው ይገኛል።
በአጠቃላይ ይህ ታሪካዊ ጉዞ የዜጎችን የዕለት ተዕለት ኑሮ የሚያቀልል፣ ሀገራችንን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሚያደርግ እና የኢኮኖሚ ልማታችንን ከሕልም ወደ እውነት የለወጠ የጋራ ብሔራዊ ስኬታችን በመሆኑ ሁሉም አካላት ለስኬቱ የበኩላቸውን ድርሻ ሊወጡ ይገባል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #digitalethiopia #5millioncoders #success #𝐃𝐢𝐠𝐢𝐭𝐚𝐥𝐄𝐜𝐨𝐧𝐨𝐦𝐲
3 days ago
በሁሉም የዓለም ዋንጫ የተሳተችፈው ብራዚል…
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ብራዚል በዓለም ዋንጫ መድረክ ከምስረታው ጀምሮ በእያንዳንዱ ውድድር ላይ በመሳተፍ ቀዳሚዋ እና ብቸኛዋ ሀገር ናት፡፡
የዓለም ሕዝብ በጉጉት የሚጠብቀው ትልቁ የሀገራት ውድድር የዓለም ዋንጫ በፈረንጆቹ 1930 ነው መደረግ የጀመረው፡፡
ብራዚል ከዓለም ዋንጫ ጅማሮ አንስቶ እስካሁን ድረስ በሁሉም የዓለም ዋንጫ የተሳተፈች ሲሆን ÷ የዘንድሮው ተሳትፎዋ ደግሞ ለተከታታይ 23ኛ ጊዜ ነው፡፡
በዚህም ብራዚል በሁሉም የዓለም ዋንጫ ውድድር ላይ በመሳተፍ እና በተከታታይ ለበርካታ ጊዜ በመድረኩ በመገኘት ቀዳሚዋ ሀገር ናት፡፡
በዓለም ዋንጫ ታሪክ ብራዚል አምስት ጊዜ ሻምፒዮን በመሆን ቀዳሚ ብሔራዊ ቡድን ስትሆን ÷ ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም ዋንጫን ያሳካችው በፈረንጆቹ 1958 ነበር፡፡
በመቀጠልም በፈረንጆቹ 1962 ሻምፒዮን በመሆን በተከታታይ ዋንጫውን አሳክታለች፡፡ ከተጨማሪም በ1970፣ 1994 እና 2002 ሻምፒዮን በመሆን በመድረኩ አምስት ጊዜ ዋንጫውን በማሳካት ቀዳሚ ናት፡፡
ሆኖም ግን የአምስት ጊዜ የመድረኩ አሸናፊዋ ሀገር ብራዚል በፈረንጆቹ 2014 እራሷ ባዘጋጀችው መድረክ በጀርመን የደረሰባት ሽንፈት የሚረሳ አይደለም፡፡
በወቅቱ ብራዚል በእራሷ ድግስ በጀርመን ብሔራዊ ቡድን አስከፊ የ7 ለ 1 ሽንፈት ማስመዝገቧ ይታወሳል፡፡
ብራዚል ኔይማር ጁኒየርን በሩብ ፍጻሜው በከባድ ጉዳት ማጣቷን ተከትሎ ያለ ወሳኝ ተጫዋቿ ነበር የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታውን ያደረገችው፡፡
ብራዚል በ2014ቱ የዓለም ዋንጫ በግማሽ ፍጻሜው በጀርመን ያልጠበቀችው ሽንፈት ማስተናገዷ የሚታወስ ነው፡፡
በስታዲየሙ የታደሙ የብራዚል ብሔራዊ ቡድን ደጋፊዎች በጭንቀት ተውጠው እና በእንባ ታጅበው ተመሳስሎ የተሰራውን ዋንጫ አቅፈው ጨዋታውን መመለከታቸው አይዘነጋም፡፡
በወቅቱ ብሔራዊ ቡድኑን በአምበልነት እየመራ ወደ ሜዳ የገባው ዴቪድ ሉዊዝ በእንባ ታጅቦ ደጋፊዎቻቸውን ይቅርታ ጠይቋል፡፡
የብራዚል ብሔራዊ ቡድን ደጋፊዎችም የብሔራዊ ቡድናቸውን ማልያ መሬት ላይ በመጣል የረጋገጡ ሲሆን÷ ከዚያም አልፈው ማቃጠላቸው አይዘነጋም፡፡
ብራዚል በ2014 ዓለም ዋንጫ በግማሽ ፍጻሜው በጀርመን የደረሰባት አስከፊ ሽንፈት በዓለም ዋንጫ ወድድር ከማይረሱ ክስተቶች መካከል አንዱ ሆኖ በታሪክ ይወሳል፡፡
ለመጨረሻ ጊዜ በፈረንጆቹ 2002 የዓለም ዋንጫን ያሳካችው ብራዚል ለ6ኛ ጊዜ በመድረኩ ሻምፒዮን ለመሆን በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ የምታደርገው ጉዞ ይጠበቃል፡፡
በአሰልጣኝ ካርሎ አንቸሎቲ የሚመራው ብሔራዊ ቡድኑ ኔይማር ጁኒየርን በስብስቡ ውስጥ አካትቷል፡፡
ኦፕታ የ2026ቱን የዓለም ዋንጫ ያሳካል በሚል ባስቀመጠው ቅድመ ትንተና መሰረት ብራዚል 6ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡
ብራዚል የ2026 ዓለም ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋን የፊታችን እሑድ ከሞሮኮ ጋር የምታደርግ ይሆናል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ብራዚል በዓለም ዋንጫ መድረክ ከምስረታው ጀምሮ በእያንዳንዱ ውድድር ላይ በመሳተፍ ቀዳሚዋ እና ብቸኛዋ ሀገር ናት፡፡
የዓለም ሕዝብ በጉጉት የሚጠብቀው ትልቁ የሀገራት ውድድር የዓለም ዋንጫ በፈረንጆቹ 1930 ነው መደረግ የጀመረው፡፡
ብራዚል ከዓለም ዋንጫ ጅማሮ አንስቶ እስካሁን ድረስ በሁሉም የዓለም ዋንጫ የተሳተፈች ሲሆን ÷ የዘንድሮው ተሳትፎዋ ደግሞ ለተከታታይ 23ኛ ጊዜ ነው፡፡
በዚህም ብራዚል በሁሉም የዓለም ዋንጫ ውድድር ላይ በመሳተፍ እና በተከታታይ ለበርካታ ጊዜ በመድረኩ በመገኘት ቀዳሚዋ ሀገር ናት፡፡
በዓለም ዋንጫ ታሪክ ብራዚል አምስት ጊዜ ሻምፒዮን በመሆን ቀዳሚ ብሔራዊ ቡድን ስትሆን ÷ ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም ዋንጫን ያሳካችው በፈረንጆቹ 1958 ነበር፡፡
በመቀጠልም በፈረንጆቹ 1962 ሻምፒዮን በመሆን በተከታታይ ዋንጫውን አሳክታለች፡፡ ከተጨማሪም በ1970፣ 1994 እና 2002 ሻምፒዮን በመሆን በመድረኩ አምስት ጊዜ ዋንጫውን በማሳካት ቀዳሚ ናት፡፡
ሆኖም ግን የአምስት ጊዜ የመድረኩ አሸናፊዋ ሀገር ብራዚል በፈረንጆቹ 2014 እራሷ ባዘጋጀችው መድረክ በጀርመን የደረሰባት ሽንፈት የሚረሳ አይደለም፡፡
በወቅቱ ብራዚል በእራሷ ድግስ በጀርመን ብሔራዊ ቡድን አስከፊ የ7 ለ 1 ሽንፈት ማስመዝገቧ ይታወሳል፡፡
ብራዚል ኔይማር ጁኒየርን በሩብ ፍጻሜው በከባድ ጉዳት ማጣቷን ተከትሎ ያለ ወሳኝ ተጫዋቿ ነበር የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታውን ያደረገችው፡፡
ብራዚል በ2014ቱ የዓለም ዋንጫ በግማሽ ፍጻሜው በጀርመን ያልጠበቀችው ሽንፈት ማስተናገዷ የሚታወስ ነው፡፡
በስታዲየሙ የታደሙ የብራዚል ብሔራዊ ቡድን ደጋፊዎች በጭንቀት ተውጠው እና በእንባ ታጅበው ተመሳስሎ የተሰራውን ዋንጫ አቅፈው ጨዋታውን መመለከታቸው አይዘነጋም፡፡
በወቅቱ ብሔራዊ ቡድኑን በአምበልነት እየመራ ወደ ሜዳ የገባው ዴቪድ ሉዊዝ በእንባ ታጅቦ ደጋፊዎቻቸውን ይቅርታ ጠይቋል፡፡
የብራዚል ብሔራዊ ቡድን ደጋፊዎችም የብሔራዊ ቡድናቸውን ማልያ መሬት ላይ በመጣል የረጋገጡ ሲሆን÷ ከዚያም አልፈው ማቃጠላቸው አይዘነጋም፡፡
ብራዚል በ2014 ዓለም ዋንጫ በግማሽ ፍጻሜው በጀርመን የደረሰባት አስከፊ ሽንፈት በዓለም ዋንጫ ወድድር ከማይረሱ ክስተቶች መካከል አንዱ ሆኖ በታሪክ ይወሳል፡፡
ለመጨረሻ ጊዜ በፈረንጆቹ 2002 የዓለም ዋንጫን ያሳካችው ብራዚል ለ6ኛ ጊዜ በመድረኩ ሻምፒዮን ለመሆን በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ የምታደርገው ጉዞ ይጠበቃል፡፡
በአሰልጣኝ ካርሎ አንቸሎቲ የሚመራው ብሔራዊ ቡድኑ ኔይማር ጁኒየርን በስብስቡ ውስጥ አካትቷል፡፡
ኦፕታ የ2026ቱን የዓለም ዋንጫ ያሳካል በሚል ባስቀመጠው ቅድመ ትንተና መሰረት ብራዚል 6ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡
ብራዚል የ2026 ዓለም ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ጨዋታዋን የፊታችን እሑድ ከሞሮኮ ጋር የምታደርግ ይሆናል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
Sponsored by
Surafel
3 days ago
በዓለም ዋንጫ የመክፈቻ ጨዋታ ደቡብ አፍሪካ ተሸነፈች
*************************
23ኛው የዓለም ዋንጫ ዛሬ በይፋ ሲጀመር ሜክሲኮን የገጠመችው ደቡብ አፍሪካ 2 ለ 0 ተረታለች።
የሜክሲኮን የማሸነፊያ ግቦች ዩሊያን ኩዊኖኔስ በመጀመሪያው አጋማሽ 9ኛው ደቂቃ ላይ እንዲሁም፤ ራውል ሂሚኔዝ 68ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥረዋል።
በሁለተኛው አጋማሽ 50ኛው ደቂቃ ላይ የደቡብ አፍሪካው የተከላካይ ስፍራ ተጫዋች ስፊፎሌ ሲቶሌ ብሪያን ጉቴሬዝ ላይ በፈፀመው ጥፋት በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል።
በዚሁ ጨዋታ ሁለተኛውን ቀይ ካርድ መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሊጠናቀቅ ሰባት ደቂቃዎች እየቀሩ ቴምባ ዝዋን ተመልክቷል። ይህ በ'ባፋና ባፋና' የመድረኩ ተሳትፎ ታሪክ አራተኛ ቀይ ካርድ ሆኖ ተመዝግቧል።
በጭማሪው ሰዓት 92ኛው ደቂቃ ላይ የሜክሲኮው ሴዛር ሞንቴዝ የጨዋታውን ሦስተኛ ቀይ ካርድ ተመልክቷል።
የ23ኛው ዓለም ዋንጫ መክፈቻ፣ የታሪካዊው አዝቴክ ስታዲየም 21ኛ የዓለም ዋንጫ ጨዋታ፣ የሀገራቱ 2ኛ የእርስ በእርስ ግንኙነት በ'ትሪ ከለርስ' አሸናፊነት ተጠናቋል።
ከዓለም ዋንጫው አስተናጋጆች አንዷ ሜክሲኮም ምድብ አንድን ከወዲሁ መምራት ጀምራለች።
የምድብ አንድ ሌላኛው ጨዋታ በነገው ዕለት በደቡብ ኮሪያና ቼክ ሪፐብሊክ መካከል ይደረጋል።
*************************
23ኛው የዓለም ዋንጫ ዛሬ በይፋ ሲጀመር ሜክሲኮን የገጠመችው ደቡብ አፍሪካ 2 ለ 0 ተረታለች።
የሜክሲኮን የማሸነፊያ ግቦች ዩሊያን ኩዊኖኔስ በመጀመሪያው አጋማሽ 9ኛው ደቂቃ ላይ እንዲሁም፤ ራውል ሂሚኔዝ 68ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥረዋል።
በሁለተኛው አጋማሽ 50ኛው ደቂቃ ላይ የደቡብ አፍሪካው የተከላካይ ስፍራ ተጫዋች ስፊፎሌ ሲቶሌ ብሪያን ጉቴሬዝ ላይ በፈፀመው ጥፋት በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል።
በዚሁ ጨዋታ ሁለተኛውን ቀይ ካርድ መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ሊጠናቀቅ ሰባት ደቂቃዎች እየቀሩ ቴምባ ዝዋን ተመልክቷል። ይህ በ'ባፋና ባፋና' የመድረኩ ተሳትፎ ታሪክ አራተኛ ቀይ ካርድ ሆኖ ተመዝግቧል።
በጭማሪው ሰዓት 92ኛው ደቂቃ ላይ የሜክሲኮው ሴዛር ሞንቴዝ የጨዋታውን ሦስተኛ ቀይ ካርድ ተመልክቷል።
የ23ኛው ዓለም ዋንጫ መክፈቻ፣ የታሪካዊው አዝቴክ ስታዲየም 21ኛ የዓለም ዋንጫ ጨዋታ፣ የሀገራቱ 2ኛ የእርስ በእርስ ግንኙነት በ'ትሪ ከለርስ' አሸናፊነት ተጠናቋል።
ከዓለም ዋንጫው አስተናጋጆች አንዷ ሜክሲኮም ምድብ አንድን ከወዲሁ መምራት ጀምራለች።
የምድብ አንድ ሌላኛው ጨዋታ በነገው ዕለት በደቡብ ኮሪያና ቼክ ሪፐብሊክ መካከል ይደረጋል።
3 days ago
የ5ቱ ዓመታት ገፆች፦ መደመር ያዋለዳቸው የገበታ ፕሮጀክቶች
**************
ታሪክ በየዘመኑ የራሱን ዐሻራ ጥሎ ያልፋል። ከስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ አንስቶ ወደ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዋዜማ ስንሸጋገር የተፃፉት የአምስቱ ዓመታት ገፆች ደግሞ፣ ኢትዮጵያ ድብቅ የተፈጥሮ ውበቷንና ፀዳሏን አውጥታ ለዓለም ያሳየችባቸው የውበት አብዮት ድርሳናት ናቸው።
ለዘመናት "የ13 ወር ፀጋ" በሚለው የቱሪዝም መሪ ቃል ብቻ ስትጠራ የነበረችው ሀገራችን፣ ዛሬ ከመፈክር ባለፈ "ምድረ ቀደምት" በሚለው ከፍታዋ ልክ በተጨባጭ በዓለም አቀፍ መድረክ ደምቃ እንድትታይ ያደረጋት አስደናቂ የታሪክ እጥፋት ተፈጥሯል። የዚህ ታላቅ ሀገራዊ ትራንስፎርሜሽን የጀርባ አጥንትና ሞተር ደግሞ ከመደመር እሳቤ የተወለዱት የ"ገበታ" ፕሮጀክቶች ናቸው።
የገበታ ፕሮጀክቶች “ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ” ተራ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች አይደሉም። ይልቁንም ሃብትን አስተባብሮ ከተፈጥሮ ፀጋዎች ጋር በማዋሀድ ኢትዮጵያን ወደ ተፈጥሯዊ የቱሪዝም መስህብነት የቀየሩና ከመደመር እሳቤ የፈለቁ እውነተኛ ኢትዮጵያዊ ትርክቶች ናቸው። የመደመር ትውልድ ሀገርን ማልማት ማለት የውጭ ዕርዳታን መጠበቅ ሳይሆን፣ የራስን እምቅ አቅም፣ የተፈጥሮ ውበትና ታሪክን ወደ ኢኮኖሚያዊ እሴት መቀየር መሆኑን በተግባር አሳይቶበታል።
ይህ የገበታ ጉዞ የተጀመረው በ"ገበታ ለሸገር" ሲሆን፣ ለዘመናት በቆሻሻ ተውጠው የነበሩ የከተማ ቦታዎችንና የተተው ተራራዎችን ወደ ምድር ገነት ቀይሯቸዋል። ጫካና ገደል የነበረው የእንጦጦ ተራራ ወደ ማራኪው "እንጦጦ ፓርክ" ሲቀየር፣ የአዲስ አበባን የልብ ትርታ ያደሰው "ወዳጅነት ፓርክ" እና ታሪክን ከተፈጥሮ ጋር ያዋሀደው ግዙፉ "አንድነት ፓርክ" የዚህ ስኬት በኩር ፍሬዎች ሆነዋል።
ይህ ስኬት በመዲናዋ ብቻ አልተገታም፤ የመደመር እሳቤ "ገበታ ለሀገር" በሚል አዲስ ሀገራዊ ንቅናቄ መላዋን ኢትዮጵያ አዳረሰ። ማራኪው የ"ወንጪ" ሐይቅ ከተፈጥሮ አቀማመጡ ጋር በተዋሀደ መልኩ በዓለም አቀፍ ስታንዳርድ ለቱሪዝም ክፍት ሆነ። የጣናን ሐይቅ ሞገድ የሚያማትረው የ"ጎርጎራ" ፕሮጀክት ታሪካዊቷን ከተማ ዳግም ሲያነቃ፣ በደቡብ ምዕራብ የሚገኘው "ኮይሻ" እና የታላቁ ሸለቆ ድንቅ ስጦታ የሆነው "ሀላላ ኬላ ሎጅ" እንዲሁም በጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ የተገነባው “ጨበራ የዝሆን ዳና ሎጅ” የኢትዮጵያን የተፈጥሮ ውበትና የባህል ብዝኃነት ቁልጭ አድርገው አሳይተዋል።
በዚህ ያላቆመው የመደመር ትውልድ "ገበታ ለትውልድ" በማለት ሌላ ምዕራፍ ከፈተ። የደንዲ ሐይቅ፣ የጢስ አባይ ፏፏቴ፣ የጅማ ዞን ቦንጋ አካባቢ እና የሶፍ ኡመር ዋሻን ጨምሮ በርካታ ድንቅ የቱሪስት መዳረሻዎች በተፈጥሮ ላይ ምንም ዓይነት አሉታዊ ተፅዕኖ በማያሳድር (eco-friendly) እና ከዓለም አቀፍ ስታንዳርድ ጋር በተናበበ አኳኋን እየተገነቡ ይገኛሉ።
እነዚህ ሁሉ የገበታ ፕሮጀክቶች ስኬታማ ሊሆኑ የቻሉበት ትልቁ ምስጢር የሥራ ባህል ለውጥ ነው። ፕሮጀክቶቹ የተመሩት "ጥራትና ፍጥነት"ን ባማከለ ጽኑ መርህ ነው። ለዘመናት ሲንከባለሉና ሲጓተቱ የነበሩ የመንግሥት ፕሮጀክቶችን ልማድ በመስበር፣ የገበታ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው በጀት፣ በተቀመጠላቸው እጅግ አጭር ጊዜ እና ዓለም አቀፍ ጥራታቸውን በጠበቀ መልኩ ተጠናቅቀዋል። ፕሮጀክቶቹ ከተፈጥሮ ጋር የፈጠሩት አስደናቂ መስተጋብር ሳይነካ የአካባቢን ሥነ-ምህዳር በጠበቀ መልኩ የተከናወኑ በመሆናቸው፣ ሀገራችንን የዓለም ጎብኚዎች ተመራጭ መዳረሻ አድርገዋታል።
የገበታ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን እውነተኛ ፀዳል የገለጡ፣ የመደመር ትውልድ ሀገሩን በዓለም አቀፍ የቱሪዝም ካርታ ላይ ቀዳሚ ለማድረግ ያለውን ብቃት፣ ፍጥነትና የፈጠራ ጥበብ ያረጋገጡ ሕያው ሐውልቶች ናቸው።
ኢትዮጵያም "ምድረ ቀደምት" መሆኗን በኩራት እያወጀች፣ የተፈጥሮና የሰው ልጅ ጥበብ የተዋሀደበትን አዲሱን ገፅታዋን ለዓለም እየገለጠች ትገኛለች።
በአጠቃላይ፣ ከስድስተኛው እስከ ሰባተኛው ምርጫ የተጓዝንባቸው የአምስቱ ዓመታት ገፆች፣ የኢትዮጵያ ውበት ከግጥምና ከዘፈን ወጥቶ መሬት የነካባቸው የክብር ዘመናት ናቸው።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #tourism #ecotourism #greentourism #sustainabletourism #ebc
**************
ታሪክ በየዘመኑ የራሱን ዐሻራ ጥሎ ያልፋል። ከስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ አንስቶ ወደ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዋዜማ ስንሸጋገር የተፃፉት የአምስቱ ዓመታት ገፆች ደግሞ፣ ኢትዮጵያ ድብቅ የተፈጥሮ ውበቷንና ፀዳሏን አውጥታ ለዓለም ያሳየችባቸው የውበት አብዮት ድርሳናት ናቸው።
ለዘመናት "የ13 ወር ፀጋ" በሚለው የቱሪዝም መሪ ቃል ብቻ ስትጠራ የነበረችው ሀገራችን፣ ዛሬ ከመፈክር ባለፈ "ምድረ ቀደምት" በሚለው ከፍታዋ ልክ በተጨባጭ በዓለም አቀፍ መድረክ ደምቃ እንድትታይ ያደረጋት አስደናቂ የታሪክ እጥፋት ተፈጥሯል። የዚህ ታላቅ ሀገራዊ ትራንስፎርሜሽን የጀርባ አጥንትና ሞተር ደግሞ ከመደመር እሳቤ የተወለዱት የ"ገበታ" ፕሮጀክቶች ናቸው።
የገበታ ፕሮጀክቶች “ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ” ተራ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች አይደሉም። ይልቁንም ሃብትን አስተባብሮ ከተፈጥሮ ፀጋዎች ጋር በማዋሀድ ኢትዮጵያን ወደ ተፈጥሯዊ የቱሪዝም መስህብነት የቀየሩና ከመደመር እሳቤ የፈለቁ እውነተኛ ኢትዮጵያዊ ትርክቶች ናቸው። የመደመር ትውልድ ሀገርን ማልማት ማለት የውጭ ዕርዳታን መጠበቅ ሳይሆን፣ የራስን እምቅ አቅም፣ የተፈጥሮ ውበትና ታሪክን ወደ ኢኮኖሚያዊ እሴት መቀየር መሆኑን በተግባር አሳይቶበታል።
ይህ የገበታ ጉዞ የተጀመረው በ"ገበታ ለሸገር" ሲሆን፣ ለዘመናት በቆሻሻ ተውጠው የነበሩ የከተማ ቦታዎችንና የተተው ተራራዎችን ወደ ምድር ገነት ቀይሯቸዋል። ጫካና ገደል የነበረው የእንጦጦ ተራራ ወደ ማራኪው "እንጦጦ ፓርክ" ሲቀየር፣ የአዲስ አበባን የልብ ትርታ ያደሰው "ወዳጅነት ፓርክ" እና ታሪክን ከተፈጥሮ ጋር ያዋሀደው ግዙፉ "አንድነት ፓርክ" የዚህ ስኬት በኩር ፍሬዎች ሆነዋል።
ይህ ስኬት በመዲናዋ ብቻ አልተገታም፤ የመደመር እሳቤ "ገበታ ለሀገር" በሚል አዲስ ሀገራዊ ንቅናቄ መላዋን ኢትዮጵያ አዳረሰ። ማራኪው የ"ወንጪ" ሐይቅ ከተፈጥሮ አቀማመጡ ጋር በተዋሀደ መልኩ በዓለም አቀፍ ስታንዳርድ ለቱሪዝም ክፍት ሆነ። የጣናን ሐይቅ ሞገድ የሚያማትረው የ"ጎርጎራ" ፕሮጀክት ታሪካዊቷን ከተማ ዳግም ሲያነቃ፣ በደቡብ ምዕራብ የሚገኘው "ኮይሻ" እና የታላቁ ሸለቆ ድንቅ ስጦታ የሆነው "ሀላላ ኬላ ሎጅ" እንዲሁም በጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ የተገነባው “ጨበራ የዝሆን ዳና ሎጅ” የኢትዮጵያን የተፈጥሮ ውበትና የባህል ብዝኃነት ቁልጭ አድርገው አሳይተዋል።
በዚህ ያላቆመው የመደመር ትውልድ "ገበታ ለትውልድ" በማለት ሌላ ምዕራፍ ከፈተ። የደንዲ ሐይቅ፣ የጢስ አባይ ፏፏቴ፣ የጅማ ዞን ቦንጋ አካባቢ እና የሶፍ ኡመር ዋሻን ጨምሮ በርካታ ድንቅ የቱሪስት መዳረሻዎች በተፈጥሮ ላይ ምንም ዓይነት አሉታዊ ተፅዕኖ በማያሳድር (eco-friendly) እና ከዓለም አቀፍ ስታንዳርድ ጋር በተናበበ አኳኋን እየተገነቡ ይገኛሉ።
እነዚህ ሁሉ የገበታ ፕሮጀክቶች ስኬታማ ሊሆኑ የቻሉበት ትልቁ ምስጢር የሥራ ባህል ለውጥ ነው። ፕሮጀክቶቹ የተመሩት "ጥራትና ፍጥነት"ን ባማከለ ጽኑ መርህ ነው። ለዘመናት ሲንከባለሉና ሲጓተቱ የነበሩ የመንግሥት ፕሮጀክቶችን ልማድ በመስበር፣ የገበታ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው በጀት፣ በተቀመጠላቸው እጅግ አጭር ጊዜ እና ዓለም አቀፍ ጥራታቸውን በጠበቀ መልኩ ተጠናቅቀዋል። ፕሮጀክቶቹ ከተፈጥሮ ጋር የፈጠሩት አስደናቂ መስተጋብር ሳይነካ የአካባቢን ሥነ-ምህዳር በጠበቀ መልኩ የተከናወኑ በመሆናቸው፣ ሀገራችንን የዓለም ጎብኚዎች ተመራጭ መዳረሻ አድርገዋታል።
የገበታ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን እውነተኛ ፀዳል የገለጡ፣ የመደመር ትውልድ ሀገሩን በዓለም አቀፍ የቱሪዝም ካርታ ላይ ቀዳሚ ለማድረግ ያለውን ብቃት፣ ፍጥነትና የፈጠራ ጥበብ ያረጋገጡ ሕያው ሐውልቶች ናቸው።
ኢትዮጵያም "ምድረ ቀደምት" መሆኗን በኩራት እያወጀች፣ የተፈጥሮና የሰው ልጅ ጥበብ የተዋሀደበትን አዲሱን ገፅታዋን ለዓለም እየገለጠች ትገኛለች።
በአጠቃላይ፣ ከስድስተኛው እስከ ሰባተኛው ምርጫ የተጓዝንባቸው የአምስቱ ዓመታት ገፆች፣ የኢትዮጵያ ውበት ከግጥምና ከዘፈን ወጥቶ መሬት የነካባቸው የክብር ዘመናት ናቸው።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #tourism #ecotourism #greentourism #sustainabletourism #ebc
Comments