Logo
Getu Temesgen
ግብፅ በማሊያዋ ላይ ያሉትን ኮከቦች እንድታነሳ ታዘዘች
#ethiopia | ​የዓለም እግር ኳስ ማኅበር (ፊፋ) የግብፅ ብሔራዊ ቡድን ለዓለም ዋንጫ ያዘጋጀውን ማሊያ ተጠቅሞ መጫወት እንደማይችል በመግለጽ አስቸኳይ እገዳ ጥሏል።

ቡድኑ ከቤልጂየም ጋር ከሚያደርገው የመክፈቻ ጨዋታ በፊት በማሊያው ደረት ላይ ያረፉትን ኮከቦች እንዲያነሳና በተጫዋቾች ስም እንዲሁም ቁጥር ላይ የተጠቀመውን የወርቅ ቀለም እንዲቀይር ጥብቅ ትዕዛዝ አስተላልፏል።

ፊፋ ይህንን ውሳኔ ያስተላለፈው የዓለም ዋንጫ ደንብ ሀገራት በደረት ላይ ኮከብ ማሳረፍ የሚችሉት የዓለም ዋንጫን ማሸነፍ ሲችሉ ብቻ በመሆኑ ሲሆን፣ ግብፅ ግን የአፍሪካ ዋንጫን ያሸነፈችበትን 7 ኮከቦች በዓለም ዋንጫ ማሊያዋ ላይ በማሳረፏ ነው።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
​#egypt #fifa #worldcup #pharaohs #footballnews #africacupofnations

4 hours ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.