4 hours ago
ሳንቲም ፔይ እና የቅን ልቦች የ2018 የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ምርጫን በጋራ ለማካሄድ ተስማሙ
#fastmereja I ሳንቲም ፔይ እና የቅን ልቦች ድርጅት በቅርቡ የሚካሄደውን የ2018 የቅን ልቦች የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች የህዝብ ምርጫ በጋራ ለማከናወን የሚያስችላቸውን ታሪካዊ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ።
በሁለቱ ወገኖች መካከል የተደረገው ይህ ስምምነት የህዝብ ምርጫ ሂደቱን በዘመናዊ የዲጂታል ቴክኖሎጂ በመደገፍ ግልጽ እና ቀልጣፋ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል። የሳንቲም ፔይ የክፍያ እና የዲጂታል መሰረተ ልማት የምርጫውን የመምረጫ ግልጽነትና ፍጥነት ከፍ እንደሚያደርገው ከተፈረመው ስምምነት ለመረዳት ተችሏል።
#fastmereja I ሳንቲም ፔይ እና የቅን ልቦች ድርጅት በቅርቡ የሚካሄደውን የ2018 የቅን ልቦች የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች የህዝብ ምርጫ በጋራ ለማከናወን የሚያስችላቸውን ታሪካዊ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ።
በሁለቱ ወገኖች መካከል የተደረገው ይህ ስምምነት የህዝብ ምርጫ ሂደቱን በዘመናዊ የዲጂታል ቴክኖሎጂ በመደገፍ ግልጽ እና ቀልጣፋ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል። የሳንቲም ፔይ የክፍያ እና የዲጂታል መሰረተ ልማት የምርጫውን የመምረጫ ግልጽነትና ፍጥነት ከፍ እንደሚያደርገው ከተፈረመው ስምምነት ለመረዳት ተችሏል።
1 day ago
የሴዶ እና የጆኒ ታላቅ የMMA ፍልሚያ ነሐሴ 21 ይካሄዳል!
#fastmereja :-በኢትዮጵያ የማርሻል አርትስ እና የቦክስ ስፖርት ታሪክ ያልተነካውን እምቅ አቅም ለዓለም ለማሳየትና ስፖርቱን ለወጣቶች የቋሚ ገቢ ምንጭ ለማድረግ ያለመው ''አድዋ ፋይት ናይት 2" (ETFC 002) ታላቅ የውድድር ምሽት ነሀሴ 21 እንደሚካሄድ በዛሬዉ እለት ተገለፀ።
ነሀሴ 21 በሚካሄደው በዚህ ውድድር ላይ በስፖርት አፍቃሪያን ዘንድ ከፍተኛ ትኩረትን የሳበው እና በጉጉት የሚጠበቀው ዋና ፍልሚያ (Main Event) በጆኒ (Johnny) እና በሴዶ (Sedo) መካከል የሚደረገው ድብልቅ ማርሻል አርት (MMA) ግጥሚያ እንደሆነ ተገልጿል።
ዛሬ በተሰጠው የጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ተወዳዳሪዎች በፊት ለፊት ፍጥጫ (Face-to face) የተገናኙ ሲሆን እርስ በእርስ ያቀረቧቸው የተፎካካሪነት እና የስነ-ልቦና የበላይነት የመውሰጃ አስተያየቶች በስፍራው የነበረውን ስሜት ያጋገሉት ሲሆን፣ ሁለቱም ስፖርተኞች ለነሐሴ 21ዱ ታላቅ ፍልሚያ ያላቸውን ከፍተኛ ዝግጁነትና የማሸነፍ በራስ መተማመን አሳይተዋል።
የውድድሩ አዘጋጅና የስዊት ቦክስ መስራች እና ስራ አ አቶ ጌታቸው መለሰ በበኩላቸው፣ ETFC 002 የቀደመው ETFC 001 ከተካሄደበት ፍጥነትና ሁኔታ በተሻለ መልኩ በከፍተኛ ደረጃ ተዘጋጅቶ የቀረበ መሆኑን ገልጸዋል።
አዘጋጆቹ ለፕሮግራሙ መዘገየት ይቅርታ በመጠየቅ፣በተወዳዳሪዎቹ የስነ-ምግባር ጥንካሬ ላይ ሙሉ እምነት እንዳላቸውና ስፖርተኞቹ ሀገራቸውን በዓለም አቀፍ መድረክ ማስጠራት የሚችሉ መሆናቸውን አብራርተዋል።
በምሽቱ 11 የተመረጡ ፍልሚያዎች የሚካሄዱ ሲሆን፣ 4 የቦክስ (Boxing) 4 የኤምኤምኤ (MMA) 3 የሙአይ ታይ (Muay Thai) ፍልሚያዎች ናቸው።
በዝግጅቱ ላይ የሴቶች ተሳትፎ ልዩ ቦታ የተሰጠው ሲሆን፣ አትሌት አብስላት እና ዛራ በተወዳዳሪነት የሚሳተፉ ሲሆን በቀጣዩ «አድዋ ፋይት ናይት 003» ውድድር ላይ ደግሞ የሴት ተወዳዳሪዎች ቁጥር እንዲጨምርና ሰፊ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ተጠቅሷል።
በሌላ በኩል፣ በቀደሙት ዝግጅቶች የነበረውን የመቀመጫ መደራረብ ችግር ሙሉ በሙሉ ለመቅረፍ የተሰራ ሲሆን በዚህም ተመልካቾች ትኬት በሚቆርጡበት ወቅት ቀጥታ የመቀመጫ ቦታቸውን (Seat) መርጠው እንዲይዙ እንደሚደረግም ነዉ የተገለፀዉ።
አዘጋጆቹ እንዳብራሩት፣ በቅርቡ በሚካሄዱት ETFC-003 እና ETFC-004 የውድድር መድረኮች ላይ የሀገር ውስጥ ስፖርተኞች ከውጭ ሀገር ተወዳዳሪዎች ጋር እንዲጋጠሙ እንደሚደረግ የተገለፀ ሲሆን ይህም በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ውስጥ እንደ ኡሲክ (Usyk) ያሉ ታዋቂ የዓለም አቀፍ ቦክስ ውድድሮችን በኢትዮጵያ ውስጥ ለማዘጋጀት ለተያዘው ታላቅ ዕቅድ መንገድ የሚከፍት ነው ተብሏል።
ይህ ዝግጅት በአድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ፣ የስፖርት አመራሮች እንዲሁም አጋር ድርጅቶች አስተዋጽኦ የሚካሄድ ሲሆን፣ የስፖርት አፍቃሪያን የነሐሴ 21ዱን የሴዶ እና ጆኒ ፍልሚያ በከፍተኛ ጉጉት በመጠበቅ ላይ ይገኛሉ።
📷 ከበደ መክብብ
#fastmereja :-በኢትዮጵያ የማርሻል አርትስ እና የቦክስ ስፖርት ታሪክ ያልተነካውን እምቅ አቅም ለዓለም ለማሳየትና ስፖርቱን ለወጣቶች የቋሚ ገቢ ምንጭ ለማድረግ ያለመው ''አድዋ ፋይት ናይት 2" (ETFC 002) ታላቅ የውድድር ምሽት ነሀሴ 21 እንደሚካሄድ በዛሬዉ እለት ተገለፀ።
ነሀሴ 21 በሚካሄደው በዚህ ውድድር ላይ በስፖርት አፍቃሪያን ዘንድ ከፍተኛ ትኩረትን የሳበው እና በጉጉት የሚጠበቀው ዋና ፍልሚያ (Main Event) በጆኒ (Johnny) እና በሴዶ (Sedo) መካከል የሚደረገው ድብልቅ ማርሻል አርት (MMA) ግጥሚያ እንደሆነ ተገልጿል።
ዛሬ በተሰጠው የጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ተወዳዳሪዎች በፊት ለፊት ፍጥጫ (Face-to face) የተገናኙ ሲሆን እርስ በእርስ ያቀረቧቸው የተፎካካሪነት እና የስነ-ልቦና የበላይነት የመውሰጃ አስተያየቶች በስፍራው የነበረውን ስሜት ያጋገሉት ሲሆን፣ ሁለቱም ስፖርተኞች ለነሐሴ 21ዱ ታላቅ ፍልሚያ ያላቸውን ከፍተኛ ዝግጁነትና የማሸነፍ በራስ መተማመን አሳይተዋል።
የውድድሩ አዘጋጅና የስዊት ቦክስ መስራች እና ስራ አ አቶ ጌታቸው መለሰ በበኩላቸው፣ ETFC 002 የቀደመው ETFC 001 ከተካሄደበት ፍጥነትና ሁኔታ በተሻለ መልኩ በከፍተኛ ደረጃ ተዘጋጅቶ የቀረበ መሆኑን ገልጸዋል።
አዘጋጆቹ ለፕሮግራሙ መዘገየት ይቅርታ በመጠየቅ፣በተወዳዳሪዎቹ የስነ-ምግባር ጥንካሬ ላይ ሙሉ እምነት እንዳላቸውና ስፖርተኞቹ ሀገራቸውን በዓለም አቀፍ መድረክ ማስጠራት የሚችሉ መሆናቸውን አብራርተዋል።
በምሽቱ 11 የተመረጡ ፍልሚያዎች የሚካሄዱ ሲሆን፣ 4 የቦክስ (Boxing) 4 የኤምኤምኤ (MMA) 3 የሙአይ ታይ (Muay Thai) ፍልሚያዎች ናቸው።
በዝግጅቱ ላይ የሴቶች ተሳትፎ ልዩ ቦታ የተሰጠው ሲሆን፣ አትሌት አብስላት እና ዛራ በተወዳዳሪነት የሚሳተፉ ሲሆን በቀጣዩ «አድዋ ፋይት ናይት 003» ውድድር ላይ ደግሞ የሴት ተወዳዳሪዎች ቁጥር እንዲጨምርና ሰፊ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ተጠቅሷል።
በሌላ በኩል፣ በቀደሙት ዝግጅቶች የነበረውን የመቀመጫ መደራረብ ችግር ሙሉ በሙሉ ለመቅረፍ የተሰራ ሲሆን በዚህም ተመልካቾች ትኬት በሚቆርጡበት ወቅት ቀጥታ የመቀመጫ ቦታቸውን (Seat) መርጠው እንዲይዙ እንደሚደረግም ነዉ የተገለፀዉ።
አዘጋጆቹ እንዳብራሩት፣ በቅርቡ በሚካሄዱት ETFC-003 እና ETFC-004 የውድድር መድረኮች ላይ የሀገር ውስጥ ስፖርተኞች ከውጭ ሀገር ተወዳዳሪዎች ጋር እንዲጋጠሙ እንደሚደረግ የተገለፀ ሲሆን ይህም በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ውስጥ እንደ ኡሲክ (Usyk) ያሉ ታዋቂ የዓለም አቀፍ ቦክስ ውድድሮችን በኢትዮጵያ ውስጥ ለማዘጋጀት ለተያዘው ታላቅ ዕቅድ መንገድ የሚከፍት ነው ተብሏል።
ይህ ዝግጅት በአድዋ ድል መታሰቢያ፣ በአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ፣ የስፖርት አመራሮች እንዲሁም አጋር ድርጅቶች አስተዋጽኦ የሚካሄድ ሲሆን፣ የስፖርት አፍቃሪያን የነሐሴ 21ዱን የሴዶ እና ጆኒ ፍልሚያ በከፍተኛ ጉጉት በመጠበቅ ላይ ይገኛሉ።
📷 ከበደ መክብብ
1 day ago
በጅማ ዞን «ተስፋን እንትከል» በሚል መርህ የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተካሄደ
#fastmereja I በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን፣ ሰቃ ወረዳ ቡዬ ቀጨማ ቀበሌ ዛሬ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም «ተስፋን እንትከል» በሚል መርህ የመላው ኢትዮጵያውያንን ጥሪ ያቀናጀ ታላቅ የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በተሳካ ሁኔታ ተከናውኗል። ይህ በአገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር ከ800 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ለመትከል በተያዘው አገራዊ ግብ መሠረት የተከናወነ ሲሆን፣ የአረንጓዴ አሻራን በማሳረፍ ረገድ የትውልድ ሀላፊነትን ለመወጣት ያለመ አገራዊ ጥረት አካል እንደሆነ ተገልጿል።
ይህ ሀገር አቀፍ አቅጣጫን መሠረት ያደረገ ታላቅ መርሃ ግብር በግሪን ዌቭ አሊያንስ ሀገር በቀል ግብረ-ሰናይ ድርጅት፣ ከኢፌድሪ ግብርና ሚኒስቴር እና ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ነው። በተጨማሪም የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ አስፈላጊውን የቴክኒክ ድጋፍ በማድረግ ለዝግጅቱ ስኬት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
በዕለቱ በተካሄደው የችግኝ ተከላ ስነ-ስርዓት ላይ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶችን ጨምሮ በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ከታደሙት የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች መካከል የግብርና ሚኒስቴር ደኤታ ዶክተር ኢፋ ሙለታ፣ የጅማ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር፣ የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ደኤታ ነፊሳ አልመሃዲ፣ የግሪን ዌቭ አሊያንስ መስራች አምባሳደር ሚካኤል ነጋሳ እንዲሁም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ መልካሙ ዴሲሳ ይገኙበታል።
በተጨማሪም የአካባቢው ነዋሪዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ አርቲስቶች፣ ጋዜጠኞች እና የቲክቶክ ይዘት ፈጣሪዎች በስፍራው በመገኘት አረንጓዴ አሻራቸውን በማሳረፍ ንቁ ተሳትፎ አድርገዋል።
መርሃ ግብሩ የተፈጥሮ ሀብት እንክብካቤን ለማጠናከር እና የወደፊት ትውልድን የወደፊት እጣ ፈንታ በተግባር ለመገንባት ያለመ መሆኑን አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።
#fastmereja I በኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን፣ ሰቃ ወረዳ ቡዬ ቀጨማ ቀበሌ ዛሬ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም «ተስፋን እንትከል» በሚል መርህ የመላው ኢትዮጵያውያንን ጥሪ ያቀናጀ ታላቅ የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በተሳካ ሁኔታ ተከናውኗል። ይህ በአገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር ከ800 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን ለመትከል በተያዘው አገራዊ ግብ መሠረት የተከናወነ ሲሆን፣ የአረንጓዴ አሻራን በማሳረፍ ረገድ የትውልድ ሀላፊነትን ለመወጣት ያለመ አገራዊ ጥረት አካል እንደሆነ ተገልጿል።
ይህ ሀገር አቀፍ አቅጣጫን መሠረት ያደረገ ታላቅ መርሃ ግብር በግሪን ዌቭ አሊያንስ ሀገር በቀል ግብረ-ሰናይ ድርጅት፣ ከኢፌድሪ ግብርና ሚኒስቴር እና ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ነው። በተጨማሪም የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እና የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ አስፈላጊውን የቴክኒክ ድጋፍ በማድረግ ለዝግጅቱ ስኬት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
በዕለቱ በተካሄደው የችግኝ ተከላ ስነ-ስርዓት ላይ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶችን ጨምሮ በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ከታደሙት የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች መካከል የግብርና ሚኒስቴር ደኤታ ዶክተር ኢፋ ሙለታ፣ የጅማ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ቲጃኒ ናስር፣ የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ደኤታ ነፊሳ አልመሃዲ፣ የግሪን ዌቭ አሊያንስ መስራች አምባሳደር ሚካኤል ነጋሳ እንዲሁም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ መልካሙ ዴሲሳ ይገኙበታል።
በተጨማሪም የአካባቢው ነዋሪዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ አርቲስቶች፣ ጋዜጠኞች እና የቲክቶክ ይዘት ፈጣሪዎች በስፍራው በመገኘት አረንጓዴ አሻራቸውን በማሳረፍ ንቁ ተሳትፎ አድርገዋል።
መርሃ ግብሩ የተፈጥሮ ሀብት እንክብካቤን ለማጠናከር እና የወደፊት ትውልድን የወደፊት እጣ ፈንታ በተግባር ለመገንባት ያለመ መሆኑን አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።
3 days ago
«ገነርስ» የተሰኘው የአርሰናል ደጋፊዎች ማህበር በይፋ ስራ ጀመረ!
#fastmereja :-በኢትዮጵያ የሚገኙ የእንግሊዝ ፕሪሚየርሊግ ክለብ የአርሰናል ደጋፊዎችን በአንድ ማህበር ስር በማሰባሰብ በኢኮኖሚ፣ በሙያ እና በማህበራዊ ዘርፎች ለማስተሳሰር ያለመው «ገነርስ» የተሰኘ ማህበር በይፋ ሥራ መጀመሩን አስታወቀ።
ማህበሩ በይፋ ሥራ መጀመሩን ባበሰረበት መድረክ ላይ እንደተገለጸው፤ የማህበሩ ዋና ዓላማ የስፖርት ደጋፊነትን ከተለመደው ስፖርታዊ መዝናናት ባሻገር፣ ለአባላቱ ተጨባጭ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ወደ ሚያስገኙ ዕድሎች ማሸጋገር መሆኑ ተገልጿል።
የ«ገነርስ» ማህበር ዋነኛ ትኩረት ደጋፊዎችን በአንድ ሁለንተናዊ መድረክ ስር ማገናኘት ሲሆን፣ ለዚህም ስኬት ከመንግስታዊ እና ከግል ተቋማት ጋር ስትራቴጂካዊ አጋርነቶችን ለመመስረት ማቀዱ ተጠቅሷል።
በተለይም የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ለአባላት የሙያ ክህሎት ማሳደጊያ ሥልጠናዎች፣ የሥራ ዕድሎች እና የንግድ አማራጮች እንደሚመቻቹ የተገለፀ ሲሆን አባላት እርስ በእርስ እንዲቀራረቡ እና ልምድ እንዲለዋወጡ የሚያስችሉ ልዩ ልዩ የአባልነት ፕሮግራሞችን በማዘጋጀት ጠንካራ የማህበረሰብ መድረክ ለመገንባት መታቀዱ ይፋ ሆኗል።
በተጨማሪም ማህበሩ አባላቱን የሚያዝናኑ፣ ጠቃሚ መረጃዎችን የሚያጋሩ እና ትምህርታዊ ይዘት ያላቸውን የዲጂታል ሚዲያ ውጤቶች በማዘጋጀት የማህበረሰብ ትስስሩን ይበልጥ ለማጠናከር ማቀዱ በመድረኩ ላይ ተመላክቷል።
«ገነርስ» ማህበር በኢትዮጵያ የስፖርት ደጋፊነት ባህል ላይ አዲስ አሠራር በማስተዋወቅ፣ ደጋፊዎች ስፖርታዊ ፍቅራቸውን ወደ የጋራ ዕድገት እና ማህበራዊ ተፅዕኖ የሚቀይሩበትን አቅጣጫ እንደሚያመቻች ይጠበቃል።
#fastmereja :-በኢትዮጵያ የሚገኙ የእንግሊዝ ፕሪሚየርሊግ ክለብ የአርሰናል ደጋፊዎችን በአንድ ማህበር ስር በማሰባሰብ በኢኮኖሚ፣ በሙያ እና በማህበራዊ ዘርፎች ለማስተሳሰር ያለመው «ገነርስ» የተሰኘ ማህበር በይፋ ሥራ መጀመሩን አስታወቀ።
ማህበሩ በይፋ ሥራ መጀመሩን ባበሰረበት መድረክ ላይ እንደተገለጸው፤ የማህበሩ ዋና ዓላማ የስፖርት ደጋፊነትን ከተለመደው ስፖርታዊ መዝናናት ባሻገር፣ ለአባላቱ ተጨባጭ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ወደ ሚያስገኙ ዕድሎች ማሸጋገር መሆኑ ተገልጿል።
የ«ገነርስ» ማህበር ዋነኛ ትኩረት ደጋፊዎችን በአንድ ሁለንተናዊ መድረክ ስር ማገናኘት ሲሆን፣ ለዚህም ስኬት ከመንግስታዊ እና ከግል ተቋማት ጋር ስትራቴጂካዊ አጋርነቶችን ለመመስረት ማቀዱ ተጠቅሷል።
በተለይም የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ለአባላት የሙያ ክህሎት ማሳደጊያ ሥልጠናዎች፣ የሥራ ዕድሎች እና የንግድ አማራጮች እንደሚመቻቹ የተገለፀ ሲሆን አባላት እርስ በእርስ እንዲቀራረቡ እና ልምድ እንዲለዋወጡ የሚያስችሉ ልዩ ልዩ የአባልነት ፕሮግራሞችን በማዘጋጀት ጠንካራ የማህበረሰብ መድረክ ለመገንባት መታቀዱ ይፋ ሆኗል።
በተጨማሪም ማህበሩ አባላቱን የሚያዝናኑ፣ ጠቃሚ መረጃዎችን የሚያጋሩ እና ትምህርታዊ ይዘት ያላቸውን የዲጂታል ሚዲያ ውጤቶች በማዘጋጀት የማህበረሰብ ትስስሩን ይበልጥ ለማጠናከር ማቀዱ በመድረኩ ላይ ተመላክቷል።
«ገነርስ» ማህበር በኢትዮጵያ የስፖርት ደጋፊነት ባህል ላይ አዲስ አሠራር በማስተዋወቅ፣ ደጋፊዎች ስፖርታዊ ፍቅራቸውን ወደ የጋራ ዕድገት እና ማህበራዊ ተፅዕኖ የሚቀይሩበትን አቅጣጫ እንደሚያመቻች ይጠበቃል።
3 days ago
አሜሪካ የቪዛ ዋስትና ክፍያን ቋሚ አደረገች፣ ተጓዦች እስከ 20 ሺህ ዶላር ይጠየቃሉ!
#fastmereja I የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ እና ከሌሎች 30 የአፍሪካ ሀገራት ጨምሮ የ50 ሀገራት ዜጎች ወደ ሀገሪቱ ለንግድና ለጉብኝት (B1/B2) ቪዛ ሲያመልክቱ እስከ 20 ሺህ የአሜሪካ ዶላር የቪዛ ዋስትና (Visa Bond) ማስያዝ የሚያስገድደውን መመሪያ በቋሚነት ማጽደቁን አስታወቀ።
ቀን፦ ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. (August 1, 2026)
እንደ አዲሱ መመሪያ አሰራር፣ ተጓዦች የተሰጣቸውን የቪዛ ጊዜ ሳያሳልፉ እና የሀገሪቱን ህግ አክብረው ከተመለሱ ያስያዙት ገንዘብ ሙሉ በሙሉ ተመላሽ ይደረግላቸዋል። ነገር ግን ከተፈቀደላቸው ጊዜ በላይ የሚቆዩ ወይም የቪዛ ደንብ የሚጥሱ ከሆነ ያስያዙት ገንዘብ ለመንግስት ገቢ እንደሚሆን ተገልጻል።
ይህ አሰራር ቀደም ሲል ለሙከራ ትግበራ ተዘርግቶ የነበረ ሲሆን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባደረገው ግምገማ ከቪዛ ጊዜ በላይ የመቆየት ችግርን በመቀነስ ረገድ ውጤታማ ሆኖ በመገኘቱ በቋሚነት ስራ ላይ እንዲውል ተወስኗል። የቆንስላ ክፍሎች እንደ አመልካቾቹ ሁኔታ ከ10 ሺህ፣ 15 ሺህ እስከ 20 ሺህ ዶላር የሚደርስ ገንዘብ በዋስትና መልክ እንዲያዝ የመወሰን ስልጣን ተሰጥቷቸዋል።
በዚህ መመሪያ ውስጥ የተካተቱት የአፍሪካ ሀገራት ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ፣ አልጄሪያ፣ አንጎላ፣ ቤኒን፣ ቦትስዋና፣ ቡሩንዲ፣ ኬፕ ቨርዴ፣ ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ኮትዲቯር፣ ጅቡቲ፣ ጋቦን፣ ጋምቢያ፣ ጊኒ፣ ጊኒ ቢሳው፣ ሌሶቶ፣ ማላዊ፣ ሞሪታኒያ፣ ሞሪሸስ፣ ሞዛምቢክ፣ ናሚቢያ፣ ሳኦ ቶሜ እና ፕሪንሲፔ፣ ሴኔጋል፣ ሲሼልስ፣ ታንዛኒያ፣ ቶጎ፣ ቱኒዚያ፣ ኡጋንዳ፣ ዛምቢያ እና ዚምባብዌ ናቸው።
የአሜሪካ ባለስልጣናት እርምጃው የህገ-ወጥ ስደተኞችን ቁጥር እና የቪዛ ጊዜ ማለፍን ለመግታት ያለመ ነው ሲሉ ቢገልጹም፣ የስደት ህግ አዋቂዎችና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ግን አሰራሩ ህጋዊ ተጓዦችን እንደሚያሰናክልና ከፍተኛ የፋይናንስ ጫና እንደሚፈጥር በመግለጽ ላይ ይገኛሉ።
#fastmereja I የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ እና ከሌሎች 30 የአፍሪካ ሀገራት ጨምሮ የ50 ሀገራት ዜጎች ወደ ሀገሪቱ ለንግድና ለጉብኝት (B1/B2) ቪዛ ሲያመልክቱ እስከ 20 ሺህ የአሜሪካ ዶላር የቪዛ ዋስትና (Visa Bond) ማስያዝ የሚያስገድደውን መመሪያ በቋሚነት ማጽደቁን አስታወቀ።
ቀን፦ ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. (August 1, 2026)
እንደ አዲሱ መመሪያ አሰራር፣ ተጓዦች የተሰጣቸውን የቪዛ ጊዜ ሳያሳልፉ እና የሀገሪቱን ህግ አክብረው ከተመለሱ ያስያዙት ገንዘብ ሙሉ በሙሉ ተመላሽ ይደረግላቸዋል። ነገር ግን ከተፈቀደላቸው ጊዜ በላይ የሚቆዩ ወይም የቪዛ ደንብ የሚጥሱ ከሆነ ያስያዙት ገንዘብ ለመንግስት ገቢ እንደሚሆን ተገልጻል።
ይህ አሰራር ቀደም ሲል ለሙከራ ትግበራ ተዘርግቶ የነበረ ሲሆን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባደረገው ግምገማ ከቪዛ ጊዜ በላይ የመቆየት ችግርን በመቀነስ ረገድ ውጤታማ ሆኖ በመገኘቱ በቋሚነት ስራ ላይ እንዲውል ተወስኗል። የቆንስላ ክፍሎች እንደ አመልካቾቹ ሁኔታ ከ10 ሺህ፣ 15 ሺህ እስከ 20 ሺህ ዶላር የሚደርስ ገንዘብ በዋስትና መልክ እንዲያዝ የመወሰን ስልጣን ተሰጥቷቸዋል።
በዚህ መመሪያ ውስጥ የተካተቱት የአፍሪካ ሀገራት ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ፣ አልጄሪያ፣ አንጎላ፣ ቤኒን፣ ቦትስዋና፣ ቡሩንዲ፣ ኬፕ ቨርዴ፣ ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ኮትዲቯር፣ ጅቡቲ፣ ጋቦን፣ ጋምቢያ፣ ጊኒ፣ ጊኒ ቢሳው፣ ሌሶቶ፣ ማላዊ፣ ሞሪታኒያ፣ ሞሪሸስ፣ ሞዛምቢክ፣ ናሚቢያ፣ ሳኦ ቶሜ እና ፕሪንሲፔ፣ ሴኔጋል፣ ሲሼልስ፣ ታንዛኒያ፣ ቶጎ፣ ቱኒዚያ፣ ኡጋንዳ፣ ዛምቢያ እና ዚምባብዌ ናቸው።
የአሜሪካ ባለስልጣናት እርምጃው የህገ-ወጥ ስደተኞችን ቁጥር እና የቪዛ ጊዜ ማለፍን ለመግታት ያለመ ነው ሲሉ ቢገልጹም፣ የስደት ህግ አዋቂዎችና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ግን አሰራሩ ህጋዊ ተጓዦችን እንደሚያሰናክልና ከፍተኛ የፋይናንስ ጫና እንደሚፈጥር በመግለጽ ላይ ይገኛሉ።
3 days ago
በጎሮ ጉሊት አካባቢ መንገድ ላይ ተደጋጋሚ የትራፊክ አደጋዎች እየደረሱ መሆናቸው ተገለጸ
#fastmereja I በጎሮ ጉሊት አካባቢ በሚገኘው የአስፋልት መንገድ ላይ በተደጋጋሚ በሚከሰቱ የትራፊክ አደጋዎች ምክንያት የሰው ህይወት አልፎ በንብረት ላይም ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ። ነዋሪዎቹ የሚመለከተው አካል በአስቸኳይ በፍጥነት መቀነሻ (Speed Breaker) በመስራት የሰዎችን ህይወት እንዲታደግ ጥሪ አቅርበዋል።
በተለቀቀው ተንቀሳቃሽ ምስል ላይ አንዲት የአካባቢው ነዋሪ በስሜት ውስጥ ሆና እያለቀሰች እንደገለጸችው፤ ጉዳዩ ምንም ዓይነት ድራማ ወይም ማጋነን የሌለበትና በአካባቢው የሚኖሩ ነዋሪዎች በሙሉ የሚያውቁት እውነተኛ ስቃይ ነው ብላለች። ነዋሪዋ ወደ ሰፈሩ ከገባችበት ጊዜ አንስቶ እስከ አሁን ድረስ በተደጋጋሚ ጊዜያት አስቃቂ የመኪና አደጋዎች ሲከሰቱ መመልከቷን ተናግራለች።
አደጋው በየጊዜው የበርካታ ወገኖችን ህይወት እየቀጠፈና አካል እያጎደለ የሚገኝ በመሆኑ ጉዳዩ የሚመለከተው የመንግስት አካል ወይም የሚመለከታቸው አካላት በአስፋልቱ ላይ ፍጥነት መቀነሻ በመስራት ተጨማሪ አደጋዎችን እንዲከላከሉ ተጠይቋል። በተጨማሪም ህብረተሰቡና አሽከርካሪዎች በአካባቢው በሚያሽከረክሩበት ወቅት አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ጥሪዋን አስተላልፋለች።
#fastmereja I በጎሮ ጉሊት አካባቢ በሚገኘው የአስፋልት መንገድ ላይ በተደጋጋሚ በሚከሰቱ የትራፊክ አደጋዎች ምክንያት የሰው ህይወት አልፎ በንብረት ላይም ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ። ነዋሪዎቹ የሚመለከተው አካል በአስቸኳይ በፍጥነት መቀነሻ (Speed Breaker) በመስራት የሰዎችን ህይወት እንዲታደግ ጥሪ አቅርበዋል።
በተለቀቀው ተንቀሳቃሽ ምስል ላይ አንዲት የአካባቢው ነዋሪ በስሜት ውስጥ ሆና እያለቀሰች እንደገለጸችው፤ ጉዳዩ ምንም ዓይነት ድራማ ወይም ማጋነን የሌለበትና በአካባቢው የሚኖሩ ነዋሪዎች በሙሉ የሚያውቁት እውነተኛ ስቃይ ነው ብላለች። ነዋሪዋ ወደ ሰፈሩ ከገባችበት ጊዜ አንስቶ እስከ አሁን ድረስ በተደጋጋሚ ጊዜያት አስቃቂ የመኪና አደጋዎች ሲከሰቱ መመልከቷን ተናግራለች።
አደጋው በየጊዜው የበርካታ ወገኖችን ህይወት እየቀጠፈና አካል እያጎደለ የሚገኝ በመሆኑ ጉዳዩ የሚመለከተው የመንግስት አካል ወይም የሚመለከታቸው አካላት በአስፋልቱ ላይ ፍጥነት መቀነሻ በመስራት ተጨማሪ አደጋዎችን እንዲከላከሉ ተጠይቋል። በተጨማሪም ህብረተሰቡና አሽከርካሪዎች በአካባቢው በሚያሽከረክሩበት ወቅት አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ጥሪዋን አስተላልፋለች።
Sponsored by
Surafel
3 days ago
ጄጄ ግሩፕ በኡራኤል ባለ 12 ወለል ህንፃ ግንባታ ከ700 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ አስጀመረ!
#fastmereja :- በኮንስትራክሽን እና ሪል እስቴት ዘርፍ የተሰማራው ጄጄ ግሩፕ (JJ Group)፣ በኡራኤል አደባባይ አካባቢ ከ700 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚጠይቅ ባለ 12 ወለል ባለብዙ አገልግሎት ህንፃ ግንባታ በይፋ ማስጀመሩን በዛሬዉ እለት አስታወቀ።
ህንፃው ለንግድ፣ ለቢሮ እና ለመኖሪያ አገልግሎት የሚውል ሲሆን እስከ ሁለት የከርሰ-ምድር (Basement) እና 12 ወለሎችን (G + 12) የያዘው ይህ ህንፃ፣ ከ10 እስከ 47 ካሬ ሜትር ስፋት ያላቸው ከ60 እስከ 70 የሚደርሱ የንግድ ሱቆች፣ በ4ኛው ወለል ላይ የተዘጋጁ የቢሮ ቦታዎች እንዲሁም 31 ባለ ሁለት መኝታ የመኖሪያ አፓርትመንቶችን ያካተተ እንደሆነ ተገልጿል።
ህንፃው ለተረጋጋ የመኖሪያ alalar™ ሲባል ለንግድና ለመኖሪያ ክፍሎቹ የተለያየ መግቢያና መውጫ እንዲኖረው ተደርጎ የተዋቀረ እንደሆነም ነዉ የተገለፀዉ።
የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ እና የኢትዮጵያ ሪል እስቴት አልሚዎች ማህበር ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ጀበል ጀማል እንደገለፁት ድርጅታቸው ባለፉት 13 ዓመታት በዘርፉ በነበረው ልምድ ከ4ዐ በላይ ህንፃዎችንና ፋብሪካዎችን ገንብቶ ማስረከቡን ጠቁመው፣ በቅርቡ ይፋ የሚሆነው የሪል እስቴት አዋጅና ደንብ የገዢዎችንና የአልሚዎችን መብት የሚያስከብር መሆኑን ተናግረዋል።
እንደ ስራ አስፈፃሚው ገለጻ፣ የንግድ ሱቆቹን በ8 ወራት፣ የመኖሪያ አፓርትመንቶቹን ደግሞ በ2 ዓመታት ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለደንበኞች ለማስረከብ ማቀዱንም ገልፀዋል።
አቶ ጀበል አክለውም "ገንዘብ በዝግ አካውንት ተቀምጦ በስራው እድገት ልክ በባንክና በባለሙያ እየተረጋገጠ የሚለቀቅበት አሰራር መዘርጋቱ በዘርፉ ላይ ታማኝነትን ይፈጥራል" ብለዋል።
በተጨማሪም የፕሮጀክቱን መበሰር ምክንያት በማድረግ በቅድመ-ሽያጭ (Pre-sale) ደረጃ 10 አፓርትመንቶች ብቻ በልዩ ቅናሽ ለገዢዎች መቅረባቸው ተገልጿል።
#fastmereja :- በኮንስትራክሽን እና ሪል እስቴት ዘርፍ የተሰማራው ጄጄ ግሩፕ (JJ Group)፣ በኡራኤል አደባባይ አካባቢ ከ700 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚጠይቅ ባለ 12 ወለል ባለብዙ አገልግሎት ህንፃ ግንባታ በይፋ ማስጀመሩን በዛሬዉ እለት አስታወቀ።
ህንፃው ለንግድ፣ ለቢሮ እና ለመኖሪያ አገልግሎት የሚውል ሲሆን እስከ ሁለት የከርሰ-ምድር (Basement) እና 12 ወለሎችን (G + 12) የያዘው ይህ ህንፃ፣ ከ10 እስከ 47 ካሬ ሜትር ስፋት ያላቸው ከ60 እስከ 70 የሚደርሱ የንግድ ሱቆች፣ በ4ኛው ወለል ላይ የተዘጋጁ የቢሮ ቦታዎች እንዲሁም 31 ባለ ሁለት መኝታ የመኖሪያ አፓርትመንቶችን ያካተተ እንደሆነ ተገልጿል።
ህንፃው ለተረጋጋ የመኖሪያ alalar™ ሲባል ለንግድና ለመኖሪያ ክፍሎቹ የተለያየ መግቢያና መውጫ እንዲኖረው ተደርጎ የተዋቀረ እንደሆነም ነዉ የተገለፀዉ።
የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ እና የኢትዮጵያ ሪል እስቴት አልሚዎች ማህበር ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ጀበል ጀማል እንደገለፁት ድርጅታቸው ባለፉት 13 ዓመታት በዘርፉ በነበረው ልምድ ከ4ዐ በላይ ህንፃዎችንና ፋብሪካዎችን ገንብቶ ማስረከቡን ጠቁመው፣ በቅርቡ ይፋ የሚሆነው የሪል እስቴት አዋጅና ደንብ የገዢዎችንና የአልሚዎችን መብት የሚያስከብር መሆኑን ተናግረዋል።
እንደ ስራ አስፈፃሚው ገለጻ፣ የንግድ ሱቆቹን በ8 ወራት፣ የመኖሪያ አፓርትመንቶቹን ደግሞ በ2 ዓመታት ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለደንበኞች ለማስረከብ ማቀዱንም ገልፀዋል።
አቶ ጀበል አክለውም "ገንዘብ በዝግ አካውንት ተቀምጦ በስራው እድገት ልክ በባንክና በባለሙያ እየተረጋገጠ የሚለቀቅበት አሰራር መዘርጋቱ በዘርፉ ላይ ታማኝነትን ይፈጥራል" ብለዋል።
በተጨማሪም የፕሮጀክቱን መበሰር ምክንያት በማድረግ በቅድመ-ሽያጭ (Pre-sale) ደረጃ 10 አፓርትመንቶች ብቻ በልዩ ቅናሽ ለገዢዎች መቅረባቸው ተገልጿል።
3 days ago
የቅዱሳን ይርጋለም እህት ሩት ይርጋለም የፖሊስን እርምጃ አደነቀች
#fastmereja I በቅርቡ በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወቷ ያለፈው የቅዱሳን ይርጋለም እህት ሩት ይርጋለም፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ የተጠረጠሩትን ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ለማዋል ባደረገው ፈጣንና የተቀናጀ ክትትል የተሰማትን ከፍተኛ ምስጋና ገለጸች።
ሩት በማህበራዊ ሚዲያ ባስተላለፈችው መልዕክት፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ባደረገው የጠበቀ ክትትል ተጠርጣሪዎቹ ሳይበተኑ እና ልብሳቸውንም ሳይቀይሩ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልጻለች። ይህ ክስተት የአንድ ቤተሰብ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የጠቅላላው ህብረተሰብ ጉዳይ መሆኑን ያመለከተችው ሩት፣ መሰል አስቃቂ ድርጊቶች በሌሎች ቤተሰቦች ላይ እንዳይደገሙ ሲባል ለቅዱሳን ትክክለኛና ተመጣጣኝ ፍትህ እንዲሰጥ ጠይቃለች።
ህዝቡም ለጉዳዩ የሰጠውን ትኩረትና ያሳየውን አጋርነት በማመስገን፣ ፍትህ እስኪረጋገጥ ድረስ ህዝቡ ከጎናቸው እንዲቆም ጥሪዋን አስተላልፋለች።
#fastmereja I በቅርቡ በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወቷ ያለፈው የቅዱሳን ይርጋለም እህት ሩት ይርጋለም፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ የተጠረጠሩትን ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ለማዋል ባደረገው ፈጣንና የተቀናጀ ክትትል የተሰማትን ከፍተኛ ምስጋና ገለጸች።
ሩት በማህበራዊ ሚዲያ ባስተላለፈችው መልዕክት፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ባደረገው የጠበቀ ክትትል ተጠርጣሪዎቹ ሳይበተኑ እና ልብሳቸውንም ሳይቀይሩ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልጻለች። ይህ ክስተት የአንድ ቤተሰብ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የጠቅላላው ህብረተሰብ ጉዳይ መሆኑን ያመለከተችው ሩት፣ መሰል አስቃቂ ድርጊቶች በሌሎች ቤተሰቦች ላይ እንዳይደገሙ ሲባል ለቅዱሳን ትክክለኛና ተመጣጣኝ ፍትህ እንዲሰጥ ጠይቃለች።
ህዝቡም ለጉዳዩ የሰጠውን ትኩረትና ያሳየውን አጋርነት በማመስገን፣ ፍትህ እስኪረጋገጥ ድረስ ህዝቡ ከጎናቸው እንዲቆም ጥሪዋን አስተላልፋለች።
4 days ago
ሼፍ ሄኖክ ዘርይሁን የምስራቅ አፍሪካ ሼፎች ማህበር ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ
📌 ኢትዮጵያ የ2027ቱን አህጉራዊ ፌስቲቫል እንድታዘጋጅ ተወሰነ
#fastmereja I የኢትዮጵያ ሼፎች ማህበር ፕሬዝዳንት ሼፍ ሄኖክ ዘርይሁን የምስራቅ አፍሪካ ሼፎች ማህበር ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ። በደቡብ አፍሪካ እና በስዋቲኒ በተካሄደው የ2026 የአፍሪካ ሼፎች ፌስቲቫል ላይ ኢትዮጵያን ወክለው የተሳተፉት ሼፍ ሄኖክ ይህን ከፍተኛ ኃላፊነት ከመጨበጣቸውም በላይ፣ ሀገራችን ኢትዮጵያ የ2027ቱን የመላው አፍሪካ የሼፎች ፌስቲቫል በጋራ እንድታዘጋጅ ውሳኔ ተላላፏል።
በደቡብ አፍሪካ እና በስዋቲኒ አስተናጋጅነት በተካሄደው በዚህ አህጉራዊ መድረክ የአፍሪካ የምግብ ግብአቶች፣ የአዘገጃጀት እና የአመጋገብ ታሪክ በሰፊው የተዳሰሰ ሲሆን፣ ዘርፉን የሚያጎለብቱ የተለያዩ አለም አቀፋዊ ስልጠናዎችም ተሰጥተዋል። ኢትዮጵያ እጅግ በርካታ የተፈጥሮ የምግብ ግብአቶች እና ሀብታም የአመጋገብ ባህል ያላት ሀገር እንደመሆኗ መጠን፣ ይህ ታሪካዊ አጋጣሚ ሀገሪቱ ያላትን እምቅ ሀብት ለመላው አለም ለማስተዋወቅና በገበያ ላይ በማቅረብ ከዘርፉ ማግኘት የሚገባትን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እንድታገኝ ትልቅ መንገድ የሚከፍት መሆኑ ተገልጿል።
ይህንን ተከትሎ ኢትዮጵያ የ2027ቱን አህጉራዊ የሼፎች ፌስቲቫል እንድታዘጋጅ መመረጧ በምግብ ቱሪዝም እና በባህል ልውውጥ ዘርፍ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ሲሆን፣ የሀገሪቱን ገጽታ በበጎ መልኩ በመገንባት ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል።
📌 ኢትዮጵያ የ2027ቱን አህጉራዊ ፌስቲቫል እንድታዘጋጅ ተወሰነ
#fastmereja I የኢትዮጵያ ሼፎች ማህበር ፕሬዝዳንት ሼፍ ሄኖክ ዘርይሁን የምስራቅ አፍሪካ ሼፎች ማህበር ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ። በደቡብ አፍሪካ እና በስዋቲኒ በተካሄደው የ2026 የአፍሪካ ሼፎች ፌስቲቫል ላይ ኢትዮጵያን ወክለው የተሳተፉት ሼፍ ሄኖክ ይህን ከፍተኛ ኃላፊነት ከመጨበጣቸውም በላይ፣ ሀገራችን ኢትዮጵያ የ2027ቱን የመላው አፍሪካ የሼፎች ፌስቲቫል በጋራ እንድታዘጋጅ ውሳኔ ተላላፏል።
በደቡብ አፍሪካ እና በስዋቲኒ አስተናጋጅነት በተካሄደው በዚህ አህጉራዊ መድረክ የአፍሪካ የምግብ ግብአቶች፣ የአዘገጃጀት እና የአመጋገብ ታሪክ በሰፊው የተዳሰሰ ሲሆን፣ ዘርፉን የሚያጎለብቱ የተለያዩ አለም አቀፋዊ ስልጠናዎችም ተሰጥተዋል። ኢትዮጵያ እጅግ በርካታ የተፈጥሮ የምግብ ግብአቶች እና ሀብታም የአመጋገብ ባህል ያላት ሀገር እንደመሆኗ መጠን፣ ይህ ታሪካዊ አጋጣሚ ሀገሪቱ ያላትን እምቅ ሀብት ለመላው አለም ለማስተዋወቅና በገበያ ላይ በማቅረብ ከዘርፉ ማግኘት የሚገባትን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እንድታገኝ ትልቅ መንገድ የሚከፍት መሆኑ ተገልጿል።
ይህንን ተከትሎ ኢትዮጵያ የ2027ቱን አህጉራዊ የሼፎች ፌስቲቫል እንድታዘጋጅ መመረጧ በምግብ ቱሪዝም እና በባህል ልውውጥ ዘርፍ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት ሲሆን፣ የሀገሪቱን ገጽታ በበጎ መልኩ በመገንባት ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል።
4 days ago
በኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ ዘርፍ የሚታዩ የክህሎትና የመዋቅር ችግሮችን ለመቅረፍ አዲስ የጋራ ስምምነት ተደረገ!
#fastmereja :-በኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ ዘርፍ የሚታዩ መዋቅራዊና የክህሎት ችግሮችን ለመቅረፍ የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት እና የአባ ለታ አክቲንግ አካዳሚ በጋራ ለመስራት በዛሬዉ እለት ተፈራረሙ።
በአዲሱ አስተዳደራዊ መዋቅር ስር የሚገኙትን ብሔራዊ ቴአትር፣ ሀገርፍቅር ቴአትር፣ የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም (ባህል አዳራሽ)፣ ራስ ቴአትር እና የሕፃናትና ወጣቶች ቴአትርን የሚያስተዳድረው ተቋሙ፤ ከግል ዘርፍ አጋሮች ጋር አብሮ ለመሥራት ባቀደው መሠረት ይፋዊ ስምምነቱን አድርጓል።
በስምምነቱ መሠረት የአስተዳደሩን የዘመናት የታሪክና የልምድ ክምችት ከአካዳሚው ዘመናዊና ፈጠራ የታከለበት የአሰልጠና ዘዴ ጋር በማዋሃድ በቴአትር፣ በሙዚቃ፣ በፊልምና ተዛማጅ የኪነ-ጥበብ ዘርፎች ሰፊ ስልጠናዎች በጋራ እንደሚሰጡ ተገልጿል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያን ባህል፣ ታሪክና ወግ የሚያንፀባርቁ ጥበባዊ ሁነቶችንና ትላልቅ ፕሮዳክሽኖችን በጋራ በማዘጋጀት ለሕዝብ ለማቅረብ፣ እንዲሁም ከግጥም ምሽቶች እስከ ታላላቅ የኪነ-ጥበብ ፌስቲቫሎች ድረስ ያሉ መድረኮችን ለማስፋፋት መታቀዱም ነዉ የተገለፀዉ።
የአባ ለታ አክቲንግ አካዳሚ ዋና መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሌንጮ ፍቅሩ በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት እንደገለጹት፤ አካዳሚው ከተመሠረተበት ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ በርካታ ወጣትና ህጻናት
ተማሪዎችን አብቅቶ ያስመረቀ ሲሆን፣ በተለይም በልጆች አክቲንግ ዘርፍ አበራች አስተዋጽኦ አበርክቷል ሲሉ ተናግረዋል።
አቶ ሌንጮ አክለው እንደገለጹት፣ አካዳሚው እስካሁን በነበረው ጉዞ የቦታ፣ የሎኬሽን እና የትወና ቁሳቁሶች (Props) እጥረት ዋና ዋና ማነቆዎች እንደነበሩበት አስታውሰዋል።
ሆኖም ከአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት ጋር የተደረገው ይህ ይፋዊ ስምምነት እነዚህን የሎጅስቲክስና የቦታ ችግሮች በዘላቂነት በመቅረፍ፣ የሰለጠኑ አዳዲስ ከዋክብትን ወደ ታሪካዊ የቴአትር መድረኮች ለማውጣት ትልቅ እድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።
#fastmereja :-በኢትዮጵያ የኪነ-ጥበብ ዘርፍ የሚታዩ መዋቅራዊና የክህሎት ችግሮችን ለመቅረፍ የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት እና የአባ ለታ አክቲንግ አካዳሚ በጋራ ለመስራት በዛሬዉ እለት ተፈራረሙ።
በአዲሱ አስተዳደራዊ መዋቅር ስር የሚገኙትን ብሔራዊ ቴአትር፣ ሀገርፍቅር ቴአትር፣ የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም (ባህል አዳራሽ)፣ ራስ ቴአትር እና የሕፃናትና ወጣቶች ቴአትርን የሚያስተዳድረው ተቋሙ፤ ከግል ዘርፍ አጋሮች ጋር አብሮ ለመሥራት ባቀደው መሠረት ይፋዊ ስምምነቱን አድርጓል።
በስምምነቱ መሠረት የአስተዳደሩን የዘመናት የታሪክና የልምድ ክምችት ከአካዳሚው ዘመናዊና ፈጠራ የታከለበት የአሰልጠና ዘዴ ጋር በማዋሃድ በቴአትር፣ በሙዚቃ፣ በፊልምና ተዛማጅ የኪነ-ጥበብ ዘርፎች ሰፊ ስልጠናዎች በጋራ እንደሚሰጡ ተገልጿል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያን ባህል፣ ታሪክና ወግ የሚያንፀባርቁ ጥበባዊ ሁነቶችንና ትላልቅ ፕሮዳክሽኖችን በጋራ በማዘጋጀት ለሕዝብ ለማቅረብ፣ እንዲሁም ከግጥም ምሽቶች እስከ ታላላቅ የኪነ-ጥበብ ፌስቲቫሎች ድረስ ያሉ መድረኮችን ለማስፋፋት መታቀዱም ነዉ የተገለፀዉ።
የአባ ለታ አክቲንግ አካዳሚ ዋና መስራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሌንጮ ፍቅሩ በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት እንደገለጹት፤ አካዳሚው ከተመሠረተበት ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ በርካታ ወጣትና ህጻናት
ተማሪዎችን አብቅቶ ያስመረቀ ሲሆን፣ በተለይም በልጆች አክቲንግ ዘርፍ አበራች አስተዋጽኦ አበርክቷል ሲሉ ተናግረዋል።
አቶ ሌንጮ አክለው እንደገለጹት፣ አካዳሚው እስካሁን በነበረው ጉዞ የቦታ፣ የሎኬሽን እና የትወና ቁሳቁሶች (Props) እጥረት ዋና ዋና ማነቆዎች እንደነበሩበት አስታውሰዋል።
ሆኖም ከአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት ጋር የተደረገው ይህ ይፋዊ ስምምነት እነዚህን የሎጅስቲክስና የቦታ ችግሮች በዘላቂነት በመቅረፍ፣ የሰለጠኑ አዳዲስ ከዋክብትን ወደ ታሪካዊ የቴአትር መድረኮች ለማውጣት ትልቅ እድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።
5 days ago
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ከአማራ ክልል ጋር በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ
#fastmereja | የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት እና የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የባህል፣ ኪነ-ጥበብና ዝክረ ታሪክ ጽህፈት ቤት በባህል፣ ኪነ-ጥበብ እና ታሪክ ዘርፎች በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ታሪካዊ የመግባቢያ ሰነድ ዛሬ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም በታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተፈራርመዋል።
ይህ አዲስ የትብብር ስምምነት ቀደም ሲል በባለሙያዎች ደረጃ በተናጠል ይደረጉ የነበሩ የቴአትርና ሙዚቃ ዝግጅቶችን ወደ ተደራጀና ተቋማዊ አጋርነት የሚያሸጋግር ሲሆን፣ ሀገራዊ የታሪክና የባህል እሴቶችን ለአዲሱ ትውልድ በተሻለ ጥራትና ተደራሽነት ለማስተላለፍ ያለመ ነው ተብሏል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት ተደራሽነቱን ለማስፋትና ህዝባዊነቱን ለማፅናት ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገራት ጋር የሚደርጋቸው ስትራቴጂካዊ ጥረቶች አካል የሆነው ይህ ስምምነት ከተፈረመ በኋላ፣ በአማራ ክልል ባህል ኪነ-ጥበብና ዝክረ ታሪክ ጽህፈት ቤት የተዘጋጀው "እንዛታ" የተሰኘው ትውፊታዊ ቴአትር ጥሪ ለተደረገላቸው የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎችና እንግዶች ቀርቧል።
#fastmereja | የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት እና የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የባህል፣ ኪነ-ጥበብና ዝክረ ታሪክ ጽህፈት ቤት በባህል፣ ኪነ-ጥበብ እና ታሪክ ዘርፎች በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ታሪካዊ የመግባቢያ ሰነድ ዛሬ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም በታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተፈራርመዋል።
ይህ አዲስ የትብብር ስምምነት ቀደም ሲል በባለሙያዎች ደረጃ በተናጠል ይደረጉ የነበሩ የቴአትርና ሙዚቃ ዝግጅቶችን ወደ ተደራጀና ተቋማዊ አጋርነት የሚያሸጋግር ሲሆን፣ ሀገራዊ የታሪክና የባህል እሴቶችን ለአዲሱ ትውልድ በተሻለ ጥራትና ተደራሽነት ለማስተላለፍ ያለመ ነው ተብሏል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት ተደራሽነቱን ለማስፋትና ህዝባዊነቱን ለማፅናት ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገራት ጋር የሚደርጋቸው ስትራቴጂካዊ ጥረቶች አካል የሆነው ይህ ስምምነት ከተፈረመ በኋላ፣ በአማራ ክልል ባህል ኪነ-ጥበብና ዝክረ ታሪክ ጽህፈት ቤት የተዘጋጀው "እንዛታ" የተሰኘው ትውፊታዊ ቴአትር ጥሪ ለተደረገላቸው የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎችና እንግዶች ቀርቧል።
5 days ago
በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነው "ወርልድ ፐብሊክ ሰሚት አፍሪካ" ጉባኤ በአዲስ አበባ ተካሄደ!
#fastmereja I የአፍሪካ ሕዝቦችን ቁርኝትና አህጉራዊ ትብብር ለማጠናከር ያለመውና በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነው "ወርልድ ፐብሊክ ሰሚት አፍሪካ" (World Public Summit Africa) ጉባኤ በዛሬዉ እለት በአዲስ አበባ ተካሄደ።
«አዲስ ዓለም አፍሪካ የጋራ መፃኢ እድልን በመቅረጽ ረገድ» በሚል መሪ ቃል በተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ECA) አዳራሽ በተካሄደው በዚህ ታላቅ መድረክ ላይ ከ700 በላይ የመንግሥት ከፍተኛ ኃላፊዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የቢዝነስ ባለሀብቶች፣ የሲቪል ማህበራት ተወካዮች፣ ምሁራንና ወጣቶች ከመላው አፍሪካና ከሌሎች የዓለም ክፍሎች ተሳትፈዋል።
ጉባኤው በስፖርት፣ በባህልና በትምህርት ዘርፎች ሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነትን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ ባተኮሩ አምስት የፓናል ውይይቶች የተከናወነ ሲሆን፤ አፍሪካ አዲስ በሚፈጠረው ዘብዙኃን ዓለም አቀፍ ሥርዓት (Multipolar World) ውስጥ ያላትን ማዕከላዊ ሚና የሚያንፀባርቅና በ"ኡቡንቱ" የፍልስፍና መርህ ላይ ያተኮረ ምክክር ተደርጎበታል።
በስብሰባው ማጠቃለያ ላይ የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063ን ለማሳካት የሚረዳ “የአፍሪካ ኮሙኒኬ” (African Communiqué) የጸደቀ ሲሆን፣ ሶስት ዋና ዋና አህጉራዊ ፕሮጀክቶችም ይፋ ሆነዋል።
ከእነዚህም መካከል አንጎላ፣ ዚምባብዌ፣ ዛምቢያ፣ ናሚቢያ፣ ቦትስዋና እና ሞዛምቢክን የሚያስተሳስረው «የዛምቤዚ ወንዝ፡ ኢኮኖሚ፣ ማህበረሰብ እና መንፈስ» በሚል ርዕስ የቀረበው ሳይንሳዊ ጥናት ይገኝበታል። በተጨማሪም በሕዝብ ዲፕሎማሲ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ 10 አፍሪካውያን ልዩ እውቅናና ሽልማት ተሰጥቷል።
ጉባኤው የእውነተኛ አንድነትን በማሳየት ለሁሉም የዓለም ሕዝቦች የሚሰራ አዲስ ዓለም ለመገንባት መንገድ የሚጠርግ ሲሆን የአዲስ አበባው ጉባኤ በመጪው መስከረም ወር በሞስኮ ለሚካሄደው ሁለተኛው የዓለም የህዝብ ለህዝብ ጉባኤ የአፍሪካን አቋም ያዘጋጀበት መድረክ መሆኑ ተገልጿል።
የጉባኤው አካል የሆነውና ከ16 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ ታዋቂ አርቲስቶች ሥራዎቻቸውን የሚያቀርቡበት «አንድነት» (Unity) የተሰኘ ዓለም አቀፍ የኪነ-ጥበብ ኤግዚቢሽን በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም መከፈቱ ታውቋል።
ይህ አህጉራዊ መድረክ መቀመጫውን በሩሲያ ሞስኮ ባደረገው "ወርልድ ፒፕልስ አሴምብሊ" (World Peoples Assembly) ከአገር በቀልና ዓለም አቀፍ አጋሮቹ ሰርቨ ግሎባል እና ግሎባል ብላክ ሴንተር ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ነው።
#fastmereja I የአፍሪካ ሕዝቦችን ቁርኝትና አህጉራዊ ትብብር ለማጠናከር ያለመውና በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነው "ወርልድ ፐብሊክ ሰሚት አፍሪካ" (World Public Summit Africa) ጉባኤ በዛሬዉ እለት በአዲስ አበባ ተካሄደ።
«አዲስ ዓለም አፍሪካ የጋራ መፃኢ እድልን በመቅረጽ ረገድ» በሚል መሪ ቃል በተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (ECA) አዳራሽ በተካሄደው በዚህ ታላቅ መድረክ ላይ ከ700 በላይ የመንግሥት ከፍተኛ ኃላፊዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የቢዝነስ ባለሀብቶች፣ የሲቪል ማህበራት ተወካዮች፣ ምሁራንና ወጣቶች ከመላው አፍሪካና ከሌሎች የዓለም ክፍሎች ተሳትፈዋል።
ጉባኤው በስፖርት፣ በባህልና በትምህርት ዘርፎች ሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነትን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ ባተኮሩ አምስት የፓናል ውይይቶች የተከናወነ ሲሆን፤ አፍሪካ አዲስ በሚፈጠረው ዘብዙኃን ዓለም አቀፍ ሥርዓት (Multipolar World) ውስጥ ያላትን ማዕከላዊ ሚና የሚያንፀባርቅና በ"ኡቡንቱ" የፍልስፍና መርህ ላይ ያተኮረ ምክክር ተደርጎበታል።
በስብሰባው ማጠቃለያ ላይ የአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063ን ለማሳካት የሚረዳ “የአፍሪካ ኮሙኒኬ” (African Communiqué) የጸደቀ ሲሆን፣ ሶስት ዋና ዋና አህጉራዊ ፕሮጀክቶችም ይፋ ሆነዋል።
ከእነዚህም መካከል አንጎላ፣ ዚምባብዌ፣ ዛምቢያ፣ ናሚቢያ፣ ቦትስዋና እና ሞዛምቢክን የሚያስተሳስረው «የዛምቤዚ ወንዝ፡ ኢኮኖሚ፣ ማህበረሰብ እና መንፈስ» በሚል ርዕስ የቀረበው ሳይንሳዊ ጥናት ይገኝበታል። በተጨማሪም በሕዝብ ዲፕሎማሲ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ 10 አፍሪካውያን ልዩ እውቅናና ሽልማት ተሰጥቷል።
ጉባኤው የእውነተኛ አንድነትን በማሳየት ለሁሉም የዓለም ሕዝቦች የሚሰራ አዲስ ዓለም ለመገንባት መንገድ የሚጠርግ ሲሆን የአዲስ አበባው ጉባኤ በመጪው መስከረም ወር በሞስኮ ለሚካሄደው ሁለተኛው የዓለም የህዝብ ለህዝብ ጉባኤ የአፍሪካን አቋም ያዘጋጀበት መድረክ መሆኑ ተገልጿል።
የጉባኤው አካል የሆነውና ከ16 የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ ታዋቂ አርቲስቶች ሥራዎቻቸውን የሚያቀርቡበት «አንድነት» (Unity) የተሰኘ ዓለም አቀፍ የኪነ-ጥበብ ኤግዚቢሽን በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም መከፈቱ ታውቋል።
ይህ አህጉራዊ መድረክ መቀመጫውን በሩሲያ ሞስኮ ባደረገው "ወርልድ ፒፕልስ አሴምብሊ" (World Peoples Assembly) ከአገር በቀልና ዓለም አቀፍ አጋሮቹ ሰርቨ ግሎባል እና ግሎባል ብላክ ሴንተር ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ነው።
Sponsored by
Surafel
5 days ago
“አደይ አዲስ ዓመት ታላቅ የንግድ ኤክስፖ እና ፌስቲቫል” ይፋ ሆነ
#fastmereja I የ2019 አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ በአዲስ ኮንቬንሽን ሴንተር ሊካሄድ የታቀደው “አደይ አዲስ ዓመት ታላቅ የንግድ ኤክስፖ እና ፌስቲቫል” ይፋ ተደርጓል። ኤክስፖው ከነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜን 05 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለ15 ቀናት እንደሚቆይ አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።
ይህ ታላቅ የንግድ እና የፌስቲቫል መድረክ በማስተር ፒስ ትሬዲንግ እና ራይት ኤቨንትስ ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን፣ አዘጋጆቹ ለሚዲያ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳመለከቱት ዝግጅቱ ለስሚት እና ለአካባቢው ነዋሪዎች የገበያ አማራጮችን በቅርበት የሚያቀርብ ነው። በኤክስፖው ላይ ከ200 በላይ የሀገር ውስጥ አምራቾች፣ አስመጪዎች፣ የዕደ-ጥበብ ባለሙያዎች እና የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ምርትና አገልግሎታቸውን በተፎካካሪ እና በተመጣጣኝ ዋጋ እንደሚያቀርቡ ተገልጿል።
ከንግድ እንቅስቃሴው ጎን ለጎን ፌስቲቫሉ በየቀኑ 15 አርቲስቶች የሚሳተፉበት የቀጥታ የሙዚቃ ኮንሰርት፣ የፋሽን ሾው፣ የህፃናት መጫወቻዎች እና የበጎ አድራጎት ስራዎችን ያካተተ እንደሚሆን ተጠቅሷል። በተጨማሪም የኪነ-ጥበብ መድረኮችን ጨምሮ የመጽሐፍት አውደ ርዕይ እና ሽያጭ ይካሄዳል።
በ15 ቀናቱ የፌስቲቫል ቆይታ ከ80,000 በላይ ጎብኚዎች እና ደንበኞች ይገበያያሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ አዘጋጆቹ ቅድመ ዝግጅታቸውን አጠናቀው የኤግዚቢሽን ቦታዎችን በመሸጥ ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።
#ኹነት
#fastmereja I የ2019 አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ በአዲስ ኮንቬንሽን ሴንተር ሊካሄድ የታቀደው “አደይ አዲስ ዓመት ታላቅ የንግድ ኤክስፖ እና ፌስቲቫል” ይፋ ተደርጓል። ኤክስፖው ከነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜን 05 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለ15 ቀናት እንደሚቆይ አዘጋጆቹ አስታውቀዋል።
ይህ ታላቅ የንግድ እና የፌስቲቫል መድረክ በማስተር ፒስ ትሬዲንግ እና ራይት ኤቨንትስ ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን፣ አዘጋጆቹ ለሚዲያ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳመለከቱት ዝግጅቱ ለስሚት እና ለአካባቢው ነዋሪዎች የገበያ አማራጮችን በቅርበት የሚያቀርብ ነው። በኤክስፖው ላይ ከ200 በላይ የሀገር ውስጥ አምራቾች፣ አስመጪዎች፣ የዕደ-ጥበብ ባለሙያዎች እና የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ምርትና አገልግሎታቸውን በተፎካካሪ እና በተመጣጣኝ ዋጋ እንደሚያቀርቡ ተገልጿል።
ከንግድ እንቅስቃሴው ጎን ለጎን ፌስቲቫሉ በየቀኑ 15 አርቲስቶች የሚሳተፉበት የቀጥታ የሙዚቃ ኮንሰርት፣ የፋሽን ሾው፣ የህፃናት መጫወቻዎች እና የበጎ አድራጎት ስራዎችን ያካተተ እንደሚሆን ተጠቅሷል። በተጨማሪም የኪነ-ጥበብ መድረኮችን ጨምሮ የመጽሐፍት አውደ ርዕይ እና ሽያጭ ይካሄዳል።
በ15 ቀናቱ የፌስቲቫል ቆይታ ከ80,000 በላይ ጎብኚዎች እና ደንበኞች ይገበያያሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ አዘጋጆቹ ቅድመ ዝግጅታቸውን አጠናቀው የኤግዚቢሽን ቦታዎችን በመሸጥ ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።
#ኹነት
6 days ago
በስዊድን የጎቲያ ካፕ ላይ የተሳተፉ 20 ያህል ኢትዮጵያውያን የቡድን አባላት መጥፋታቸው ተገለጸ
#fastmereja | በስዊድን ጎተንበርግ ከተማ በተካሄደው የጎቲያ ታዳጊዎች ውድድር (Gothia Cup) ላይ ለመሳተፍ የተጓዙ 20 ያህል ኢትዮጵያውያን ተጫዋቾች እና የቡድን መሪዎች ደብዛቸው መጥፋቱን የስዊድን ፖሊስ እና የውድድሩ አዘጋጆች አስታወቁ።
በየዓመቱ በስዊድን በሚካሄደው ዓለም አቀፍ የታዳጊዎች እግር ኳስ ውድድር ላይ ከተሳተፉ አራት የኢትዮጵያ ቡድኖች መካከል የአንዱ ቡድን አባላት የሆኑት እነዚህ 20 ያህል ግለሰቦች፣ ውድድሩ በተጠናቀቀበት የመጨረሻ ቀን ያረፉበት ትምህርት ቤት ሳይሰናበቱ መውጣታቸው ተሰምቷል። የቡድኑ አባላት እድሜያቸው ከ14 እስከ 17 ዓመት የሆኑ ታዳጊ ተጫዋቾችን እና ከአሰልጣኞች ወይም መሪዎች መካከል የተወሰኑትን ያካተተ መሆኑ ተመልክቷል።
የውድድሩ አዘጋጆች የቡድኑን መጥፋት እንደተረዱ ለአካባቢው ፖሊስ ጥቆማ ያቀረቡ ሲሆን፣ ቡድኑ ወደ ዋና ከተማዋ ስቶክሆልም አቅጣጫ ተጓዥ መሆናቸውን ጠቁመዋል። የስዊድን ፖሊስ ባደረገው ማጣራት እነዚህ ግለሰቦች ወደ ኢትዮጵያ እንዳልተመለሱ ያረጋገጠ ሲሆን፣ ክስተቱ በራሳቸው ፍላጎት የተደረገ መሰወር ወይም ህገ-ወጥ የፍልሰት እንቅስቃሴ እንደሆነ መገመቱን ገልጻል።
የስዊድን የምዕራብ ክልል ፖሊስ የጠፉ ሰዎች ክፍል ተወካይ ኤሊኖር ሃልዲን እንደገለጹት፣ በጉዳዩ ላይ የሰዎች ዝውውር ወይም የወንጀል ድርጊት መኖሩን የሚያሳይ ፍንጭ እስካሁን አልተገኘም። ሆኖም የስዊድን ፖሊስ ከአገሪቱ የኢሚግሬሽን መሥሪያ ቤት፣ ከድንበር ጠባቂዎች እና ከአለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመተባበር የቡድኑን አባላት የመፈለግ ሥራ አጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቋል።
#fastmereja | በስዊድን ጎተንበርግ ከተማ በተካሄደው የጎቲያ ታዳጊዎች ውድድር (Gothia Cup) ላይ ለመሳተፍ የተጓዙ 20 ያህል ኢትዮጵያውያን ተጫዋቾች እና የቡድን መሪዎች ደብዛቸው መጥፋቱን የስዊድን ፖሊስ እና የውድድሩ አዘጋጆች አስታወቁ።
በየዓመቱ በስዊድን በሚካሄደው ዓለም አቀፍ የታዳጊዎች እግር ኳስ ውድድር ላይ ከተሳተፉ አራት የኢትዮጵያ ቡድኖች መካከል የአንዱ ቡድን አባላት የሆኑት እነዚህ 20 ያህል ግለሰቦች፣ ውድድሩ በተጠናቀቀበት የመጨረሻ ቀን ያረፉበት ትምህርት ቤት ሳይሰናበቱ መውጣታቸው ተሰምቷል። የቡድኑ አባላት እድሜያቸው ከ14 እስከ 17 ዓመት የሆኑ ታዳጊ ተጫዋቾችን እና ከአሰልጣኞች ወይም መሪዎች መካከል የተወሰኑትን ያካተተ መሆኑ ተመልክቷል።
የውድድሩ አዘጋጆች የቡድኑን መጥፋት እንደተረዱ ለአካባቢው ፖሊስ ጥቆማ ያቀረቡ ሲሆን፣ ቡድኑ ወደ ዋና ከተማዋ ስቶክሆልም አቅጣጫ ተጓዥ መሆናቸውን ጠቁመዋል። የስዊድን ፖሊስ ባደረገው ማጣራት እነዚህ ግለሰቦች ወደ ኢትዮጵያ እንዳልተመለሱ ያረጋገጠ ሲሆን፣ ክስተቱ በራሳቸው ፍላጎት የተደረገ መሰወር ወይም ህገ-ወጥ የፍልሰት እንቅስቃሴ እንደሆነ መገመቱን ገልጻል።
የስዊድን የምዕራብ ክልል ፖሊስ የጠፉ ሰዎች ክፍል ተወካይ ኤሊኖር ሃልዲን እንደገለጹት፣ በጉዳዩ ላይ የሰዎች ዝውውር ወይም የወንጀል ድርጊት መኖሩን የሚያሳይ ፍንጭ እስካሁን አልተገኘም። ሆኖም የስዊድን ፖሊስ ከአገሪቱ የኢሚግሬሽን መሥሪያ ቤት፣ ከድንበር ጠባቂዎች እና ከአለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመተባበር የቡድኑን አባላት የመፈለግ ሥራ አጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቋል።
6 days ago
በቴሌብር ዲጂታል ብድር ውዝፍ ዕዳ ያለባቸው ተበዳሪዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ እና ክስ እየተወሰደ መሆኑ ተገለጸ
#fastmereja I ዳሸን ባንክ እና ኢትዮ ቴሌኮም በቴሌብር መተግበሪያ አማካኝነት የወሰዱትን የዲጂታል ፋይናንሲንግ ብድር በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ባልከፈሉ ተበዳሪዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ መውሰድ መጀመራቸውን እና በተለያዩ ፍርድ ቤቶች ክስ እየመሰረቱ እንደሚገኙ ይፋ አደረጉ።
እ.ኤ.አ. ጁላይ 29 ቀን 2026 የወጣው የባንኩ መግለጫ እንደሚያመለክተው፡ ተበዳሪዎች ያለባቸውን ውዝፍ ዕዳ እንዲከፍሉ በተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ሲሰጥ የቆየ ሲሆን፡ ከዚህ ቀደም የተደረገውን የቅጣት ክፍያ ምሕረት ተጠቅመው ዕዳቸውን ያልከፈሉ ወገኖች ላይ የህግ አካሄድ ተጀምሯል። አስቀድመው ለቀረበላቸው ጥሪ ምላሽ ያልሰጡ ተበዳሪዎች ላይ በፍርድ ቤት ክስ ተመስርቶ ከዋናው ዕዳ በተጨማሪ ባንኩ ለክስ ያወጣቸውን ልዩ ልዩ ወጪዎች እንዲሸፍኑ ውሳኔ እየተሰጠ ይገኛል።
ዳሸን ባንክ አክሲዮን ማህበር የህዝብ ገንዘብ ለማስመለስ የጀመረውን ህጋዊ እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል በመጠቆም፡ እስካሁን የክስ መጥሪያ ያልደረሳቸው ተበዳሪዎች ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት ከመሄዱ በፊት እና ተጨማሪ አላስፈላጊ እንግልት እንዲሁም ወጪ ሳይደርስባቸው ያለባቸውን ዕዳ በአስቸኳይ እንዲከፍሉ ጥብቅ ማሳሰቢያ አስተላልፏል።
#fastmereja I ዳሸን ባንክ እና ኢትዮ ቴሌኮም በቴሌብር መተግበሪያ አማካኝነት የወሰዱትን የዲጂታል ፋይናንሲንግ ብድር በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ባልከፈሉ ተበዳሪዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ መውሰድ መጀመራቸውን እና በተለያዩ ፍርድ ቤቶች ክስ እየመሰረቱ እንደሚገኙ ይፋ አደረጉ።
እ.ኤ.አ. ጁላይ 29 ቀን 2026 የወጣው የባንኩ መግለጫ እንደሚያመለክተው፡ ተበዳሪዎች ያለባቸውን ውዝፍ ዕዳ እንዲከፍሉ በተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ሲሰጥ የቆየ ሲሆን፡ ከዚህ ቀደም የተደረገውን የቅጣት ክፍያ ምሕረት ተጠቅመው ዕዳቸውን ያልከፈሉ ወገኖች ላይ የህግ አካሄድ ተጀምሯል። አስቀድመው ለቀረበላቸው ጥሪ ምላሽ ያልሰጡ ተበዳሪዎች ላይ በፍርድ ቤት ክስ ተመስርቶ ከዋናው ዕዳ በተጨማሪ ባንኩ ለክስ ያወጣቸውን ልዩ ልዩ ወጪዎች እንዲሸፍኑ ውሳኔ እየተሰጠ ይገኛል።
ዳሸን ባንክ አክሲዮን ማህበር የህዝብ ገንዘብ ለማስመለስ የጀመረውን ህጋዊ እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል በመጠቆም፡ እስካሁን የክስ መጥሪያ ያልደረሳቸው ተበዳሪዎች ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት ከመሄዱ በፊት እና ተጨማሪ አላስፈላጊ እንግልት እንዲሁም ወጪ ሳይደርስባቸው ያለባቸውን ዕዳ በአስቸኳይ እንዲከፍሉ ጥብቅ ማሳሰቢያ አስተላልፏል።
6 days ago
በምስራቅ አርሲ ዞን በታጣቂዎች የተፈጸሙ ከባድ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ይፋ ሆኑ
#fastmereja I የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ አርሲ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች ከ2014 ዓ.ም እስከ ግንቦት 2018 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ በታጣቂ ቡድኖች በተፈጸሙ ጥቃቶች ላይ ያከናወነውን የምርመራ ግኝት የያዘ 158ኛ ልዩ መግለጫውን ይፋ አድርጓል። በዞኑ በሚገኙ ሽርካ፣ ሮቤ፣ ጀጁ፣ መርቲ፣ ጉና፣ ሆንቆሎ ዋቤ፣ አርሲ ሲሬ፣ ሙኒሳ እና አሰኮ ወረዳዎች በተፈጸሙት ጥቃቶች በሃይማኖትና ማንነት ላይ ያነጣጠሩ የሰዎች ግ ድያ፣ አካል ጉዳት፣ እገታ፣ መፈናቀል እና የንብረት ውድመት መከሰታቸው ተረጋገጧል።
ኢሰመጉ ከመጋቢት 3 እስከ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረገው የመስክ ምርመራና ከሟች ቤተሰቦች፣ ተጎጂዎች፣ የዓይን እማኞች እና የአርሲ ሀገረ ስብከት ቤተክህነት ጽሕፈት ቤቶች ባሰበሰባቸው መረጃዎች መሰረት በጥቃቱ በርካታ ንጹሃን ዜጎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። ከ2014 ዓ.ም እስከ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ዓ.ም የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች የምርመራ ስራን አከናውኗል፡፡ በተሰበሰበው መረጃ መሰረት:-
📌 በሽርካ ወረዳ 116፣
📌 በመርቲ ወረዳ 117፣
📌 በጀጁ ወረዳ 101፣
📌 በሮቤ ወረዳ 47፣
📌 በጉና ወረዳ 26፣
📌 በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ 20፣
📌 በሙኒሳ ወረዳ 19፣
📌 በአሰኮ ወረዳ 5 ንጹሃን እና 4 የጸጥታ አካላት (ሚሊሻዎች) እንዲሁም
📌 በሲሬ ወረዳ 3 ሰዎች ተገ ድለዋል።
ከግድ ያው በተጨማሪ ከፍተኛ የእገታ ወንጀል የተፈጸመ ሲሆን፣
📍በሮቤ ወረዳ 156 ሰዎች፣
📍በጀጁ ወረዳ 182 ሰዎች፣
📍በመርቲ ወረዳ 29 ሰዎች
📍በሽርካ ወረዳ 39 ሰዎች ታግተው በርካቶቹ በካሳ ክፍያ የተለቀቁ ቢሆንም የበርካታ ታጋቾች የደረሱበት ሁኔታ እስከ አሁን አይታወቅም። እንዲሁም በሕፃናትና አዛውንቶች ላይ የቆሰሉና አካል ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ከቀያቸው ተፈናቅለዋል። የአሰኮ ወረዳ የጠለታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያንን ጨምሮ በርካታ አብያተ ክርስቲያናት መዘረፋቸውና መቃጠላቸው፣ የመኖሪያ ቤቶች መፍረሳቸው እና የቀንድና የጋማ ከብቶች መዘረፋቸው በምርመራው ተረጋግጧል።
ኢሰመጉ መንግስት የዜጎችን በሕይወት የመኖርና የንብረት ጥበቃ የማድረግ ሕገ-መንግሥታዊ ግዴታውን እንዲወጣ፣ በጥሰቱ የተሳተፉ አካላት በሕግ እንዲጠየቁ እና ለተፈናቀሉት ዘላቂ መፍትሔ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል።
#fastmereja I የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ አርሲ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች ከ2014 ዓ.ም እስከ ግንቦት 2018 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ በታጣቂ ቡድኖች በተፈጸሙ ጥቃቶች ላይ ያከናወነውን የምርመራ ግኝት የያዘ 158ኛ ልዩ መግለጫውን ይፋ አድርጓል። በዞኑ በሚገኙ ሽርካ፣ ሮቤ፣ ጀጁ፣ መርቲ፣ ጉና፣ ሆንቆሎ ዋቤ፣ አርሲ ሲሬ፣ ሙኒሳ እና አሰኮ ወረዳዎች በተፈጸሙት ጥቃቶች በሃይማኖትና ማንነት ላይ ያነጣጠሩ የሰዎች ግ ድያ፣ አካል ጉዳት፣ እገታ፣ መፈናቀል እና የንብረት ውድመት መከሰታቸው ተረጋገጧል።
ኢሰመጉ ከመጋቢት 3 እስከ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረገው የመስክ ምርመራና ከሟች ቤተሰቦች፣ ተጎጂዎች፣ የዓይን እማኞች እና የአርሲ ሀገረ ስብከት ቤተክህነት ጽሕፈት ቤቶች ባሰበሰባቸው መረጃዎች መሰረት በጥቃቱ በርካታ ንጹሃን ዜጎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። ከ2014 ዓ.ም እስከ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ዓ.ም የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች የምርመራ ስራን አከናውኗል፡፡ በተሰበሰበው መረጃ መሰረት:-
📌 በሽርካ ወረዳ 116፣
📌 በመርቲ ወረዳ 117፣
📌 በጀጁ ወረዳ 101፣
📌 በሮቤ ወረዳ 47፣
📌 በጉና ወረዳ 26፣
📌 በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ 20፣
📌 በሙኒሳ ወረዳ 19፣
📌 በአሰኮ ወረዳ 5 ንጹሃን እና 4 የጸጥታ አካላት (ሚሊሻዎች) እንዲሁም
📌 በሲሬ ወረዳ 3 ሰዎች ተገ ድለዋል።
ከግድ ያው በተጨማሪ ከፍተኛ የእገታ ወንጀል የተፈጸመ ሲሆን፣
📍በሮቤ ወረዳ 156 ሰዎች፣
📍በጀጁ ወረዳ 182 ሰዎች፣
📍በመርቲ ወረዳ 29 ሰዎች
📍በሽርካ ወረዳ 39 ሰዎች ታግተው በርካቶቹ በካሳ ክፍያ የተለቀቁ ቢሆንም የበርካታ ታጋቾች የደረሱበት ሁኔታ እስከ አሁን አይታወቅም። እንዲሁም በሕፃናትና አዛውንቶች ላይ የቆሰሉና አካል ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ከቀያቸው ተፈናቅለዋል። የአሰኮ ወረዳ የጠለታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያንን ጨምሮ በርካታ አብያተ ክርስቲያናት መዘረፋቸውና መቃጠላቸው፣ የመኖሪያ ቤቶች መፍረሳቸው እና የቀንድና የጋማ ከብቶች መዘረፋቸው በምርመራው ተረጋግጧል።
ኢሰመጉ መንግስት የዜጎችን በሕይወት የመኖርና የንብረት ጥበቃ የማድረግ ሕገ-መንግሥታዊ ግዴታውን እንዲወጣ፣ በጥሰቱ የተሳተፉ አካላት በሕግ እንዲጠየቁ እና ለተፈናቀሉት ዘላቂ መፍትሔ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል።
7 days ago
የደጃዝማች ባልቻ አባ ነፍሶ ታሪክ በትውልድ ቦታቸው ወሊሶ በቴአትር ሊዘከር ነው
#fastmereja | የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች ኢንተርፕራይዝ ከወሊሶ ከተማ አስተዳደር ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን ታሪካዊ የስራ ስምምነት ተፈራረመ። የስምምነቱ ዋና ዓላማ የዓድዋው ተጋድሎ ጀግና የደጃዝማች ባልቻ አባ ነፍሶን ታሪክ እና አኩሪ ገድል የሚያወሳውን ታሪካዊ የመድረክ ቴአትር በጀግናው የትውልድ ስፍራ በሆነችው ወሊሶ ከተማ ለህዝብ እይታ ለማቅረብ ነው።
ከክቡር ደጃዝማች ባልቻ አባ ነፍሶ ቤተሰቦች ጋር በተደረገ የጠበቀ ቅንጅት እና ትብብር እውን የሆነው ይህ ስምምነት፣ ቴአትሩን በስፍራው ለመድረክ ለማብቃት ከማስቻሉም በላይ በወሊሶ ከተማና አካባቢው የኪነ-ጥበብ ዘርፍን በስፋት ለማስተዋወቅ እና ለማሳደግ ትልቅ መሰረት ይጥላል። ሁለቱ አካላት በተደረሰው ስምምነት መሰረት በጉጉት የሚጠበቀውን ይህንን ታላቅ ቴአትር በቅርቡ ለከተማዋ ነዋሪዎች የሚያቀርቡ ሲሆን፣ የጀግኖችን አገራዊ ውሎ በኪነ-ጥበብ ህያው በማድረግ ለተካኪው ትውልድ የማስተላለፍ ስራቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።
#fastmereja | የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች ኢንተርፕራይዝ ከወሊሶ ከተማ አስተዳደር ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን ታሪካዊ የስራ ስምምነት ተፈራረመ። የስምምነቱ ዋና ዓላማ የዓድዋው ተጋድሎ ጀግና የደጃዝማች ባልቻ አባ ነፍሶን ታሪክ እና አኩሪ ገድል የሚያወሳውን ታሪካዊ የመድረክ ቴአትር በጀግናው የትውልድ ስፍራ በሆነችው ወሊሶ ከተማ ለህዝብ እይታ ለማቅረብ ነው።
ከክቡር ደጃዝማች ባልቻ አባ ነፍሶ ቤተሰቦች ጋር በተደረገ የጠበቀ ቅንጅት እና ትብብር እውን የሆነው ይህ ስምምነት፣ ቴአትሩን በስፍራው ለመድረክ ለማብቃት ከማስቻሉም በላይ በወሊሶ ከተማና አካባቢው የኪነ-ጥበብ ዘርፍን በስፋት ለማስተዋወቅ እና ለማሳደግ ትልቅ መሰረት ይጥላል። ሁለቱ አካላት በተደረሰው ስምምነት መሰረት በጉጉት የሚጠበቀውን ይህንን ታላቅ ቴአትር በቅርቡ ለከተማዋ ነዋሪዎች የሚያቀርቡ ሲሆን፣ የጀግኖችን አገራዊ ውሎ በኪነ-ጥበብ ህያው በማድረግ ለተካኪው ትውልድ የማስተላለፍ ስራቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።
8 days ago
የቀድሞ የሲዳማ ክልል የፀጥታ አመራሮች በጽኑ እስራት ተቀጡ
#fastmereja I የቀድሞው የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ በ10 ዓመት ከአምስት ወር ጽኑ እስራት፣ የቀድሞው የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽነር ሽመልስ ቶማስ ደግሞ በአንድ ዓመት ከስድስት ወር ጽኑ እስራት እንዲቀጡ የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዛሬ ውሳኔ አስተላለፈ።
የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በዛሬው ዕለት ባዋለው ችሎት በሰጠው ውሳኔ፣ በክልሉ ፍትህ ቢሮ ከሳሽነት የተመሰረተባቸውን ክስ መነሻ በማድረግ የቀረቡ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን መመዘኑን ገልጻል። ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ ስልጣናቸውን አላግባብ በመገልገል "የሲዳማ ነፃነት ሠራዊት (ሲነሠ)" የተባለ ታጣቂ ቡድን በማደራጀትና ተደራራቢ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በመፈጸም ጥፋተኛ ሆነው አግኝቷቸዋል።
በዚህም መሰረት አንደኛ ተከሳሽ አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ በ10 ዓመት ከአምስት ወር ጽኑ እስራት እና በ4,000 ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ተወስኗል። ሁለተኛ ተከሳሽ የቀድሞው የፖሊስ ኮሚሽነር ሽመልስ ቶማስ በበኩላቸው በአንድ ዓመት ከስድስት ወር ጽኑ እስራት እና በ1,000 ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ ብይን ሰጥቷል።
#fastmereja I የቀድሞው የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ በ10 ዓመት ከአምስት ወር ጽኑ እስራት፣ የቀድሞው የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽነር ሽመልስ ቶማስ ደግሞ በአንድ ዓመት ከስድስት ወር ጽኑ እስራት እንዲቀጡ የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዛሬ ውሳኔ አስተላለፈ።
የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በዛሬው ዕለት ባዋለው ችሎት በሰጠው ውሳኔ፣ በክልሉ ፍትህ ቢሮ ከሳሽነት የተመሰረተባቸውን ክስ መነሻ በማድረግ የቀረቡ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን መመዘኑን ገልጻል። ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ ስልጣናቸውን አላግባብ በመገልገል "የሲዳማ ነፃነት ሠራዊት (ሲነሠ)" የተባለ ታጣቂ ቡድን በማደራጀትና ተደራራቢ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በመፈጸም ጥፋተኛ ሆነው አግኝቷቸዋል።
በዚህም መሰረት አንደኛ ተከሳሽ አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ በ10 ዓመት ከአምስት ወር ጽኑ እስራት እና በ4,000 ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ተወስኗል። ሁለተኛ ተከሳሽ የቀድሞው የፖሊስ ኮሚሽነር ሽመልስ ቶማስ በበኩላቸው በአንድ ዓመት ከስድስት ወር ጽኑ እስራት እና በ1,000 ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ ብይን ሰጥቷል።
Sponsored by
Surafel
9 days ago
አድማስ ዩኒቨርሲቲ ከ5,000 በላይ ተማሪዎችን አስመረቀ!
#fastmereja :-አድማስ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ፣ በርቀት እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ መርሃ-ግብሮች ያሰለጠናቸውን ከ5,000 በላይ ተማሪዎች በደመቀ ሁኔታ አስመረቀ።
ከተመራቂዎቹ መካከል 73.16 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች ሲሆኑ ይህም ተቋሙ ለሴቶች የከፍተኛ ትምህርት ተሳትፎ እያደረገ ያለውን አዎንታዊ አስተዋጽኦ የሚያሳይ መሆኑ ተመልክቷል።
በዕለቱ በክብር እንግድነት የተገኙት አምባሳደር ዶ/ር የሺመብራት መርሻ ካሳ፣ የዩኒቨርሲቲው ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ይብራህ ግርማይ፣ የሠኔት አባላት፣ መምህራንና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
ተቋሙ ላለፉት 27 ዓመታት ከ100,000 በላይ ተማሪዎችን አሰልጥኖ ለሀገር ልማት ማበቃቱን የገለፀ ሲሆን ከአንድ አነስተኛ የማሰልጠኛ ማዕከል የተነሳው አድማስ ዩኒቨርሲቲ፣ በአሁኑ ወቅት በሀገር ውስጥ 10 ካምፓሶችንና በርካታ የርቀት ማዕከላትን የከፈተ እና በሶማሊላንድና በፑንትላንድም ተመራጭ ተቋም ሆኖ አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ነዉ የተገለፀዉ።
አድማስ ዩኒቨርሲቲ በትምህርት ጥራትና በስታንዳርድ ኢንስፔክሽን ምዘናዎች በርካታ አገር አቀፍ ዕውቅናዎችን ያገኘ ሲሆን፣ በቅርቡም በትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የዳግም ምዝገባ መስፈርትን ካሟሉ ጥቂት የግል ተቋማት አንዱ መሆኑ ተገልጿል።
ከመማር ማስተማሩ ጎን ለጎን ተቋሙ 18ኛውን ዓመታዊ ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ በመጪው ጳጉሜ ወር እንደሚያካሂድ ተገልፆ ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ የነፃ ትምህርት ዕድል (ስኮላርሺፕ) ለማህበረሰቡ መስጠቱ ተገልጿል።
በመጨረሻም፣ ሁለተኛና ሦስተኛ ዲግሪያቸውን ለመቀጠል ለሚፈልጉ ተመራቂዎች ለሚጠብቃቸው ሀገርአቀፍ የመግቢያ ፈተና ዩኒቨርሲቲው ነፃ የማጠናከሪያ ድጋፍ እንደሚሰጥ የገለጹት ፕሬዚደንቱ፣ ለተመራቂዎችና ለቤተሰቦቻቸው መልካም የምረቃ በዓል እንዲሆንላቸው ተመኝተዋል።
#fastmereja :-አድማስ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ፣ በርቀት እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ መርሃ-ግብሮች ያሰለጠናቸውን ከ5,000 በላይ ተማሪዎች በደመቀ ሁኔታ አስመረቀ።
ከተመራቂዎቹ መካከል 73.16 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች ሲሆኑ ይህም ተቋሙ ለሴቶች የከፍተኛ ትምህርት ተሳትፎ እያደረገ ያለውን አዎንታዊ አስተዋጽኦ የሚያሳይ መሆኑ ተመልክቷል።
በዕለቱ በክብር እንግድነት የተገኙት አምባሳደር ዶ/ር የሺመብራት መርሻ ካሳ፣ የዩኒቨርሲቲው ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ይብራህ ግርማይ፣ የሠኔት አባላት፣ መምህራንና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
ተቋሙ ላለፉት 27 ዓመታት ከ100,000 በላይ ተማሪዎችን አሰልጥኖ ለሀገር ልማት ማበቃቱን የገለፀ ሲሆን ከአንድ አነስተኛ የማሰልጠኛ ማዕከል የተነሳው አድማስ ዩኒቨርሲቲ፣ በአሁኑ ወቅት በሀገር ውስጥ 10 ካምፓሶችንና በርካታ የርቀት ማዕከላትን የከፈተ እና በሶማሊላንድና በፑንትላንድም ተመራጭ ተቋም ሆኖ አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ነዉ የተገለፀዉ።
አድማስ ዩኒቨርሲቲ በትምህርት ጥራትና በስታንዳርድ ኢንስፔክሽን ምዘናዎች በርካታ አገር አቀፍ ዕውቅናዎችን ያገኘ ሲሆን፣ በቅርቡም በትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የዳግም ምዝገባ መስፈርትን ካሟሉ ጥቂት የግል ተቋማት አንዱ መሆኑ ተገልጿል።
ከመማር ማስተማሩ ጎን ለጎን ተቋሙ 18ኛውን ዓመታዊ ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ በመጪው ጳጉሜ ወር እንደሚያካሂድ ተገልፆ ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ የነፃ ትምህርት ዕድል (ስኮላርሺፕ) ለማህበረሰቡ መስጠቱ ተገልጿል።
በመጨረሻም፣ ሁለተኛና ሦስተኛ ዲግሪያቸውን ለመቀጠል ለሚፈልጉ ተመራቂዎች ለሚጠብቃቸው ሀገርአቀፍ የመግቢያ ፈተና ዩኒቨርሲቲው ነፃ የማጠናከሪያ ድጋፍ እንደሚሰጥ የገለጹት ፕሬዚደንቱ፣ ለተመራቂዎችና ለቤተሰቦቻቸው መልካም የምረቃ በዓል እንዲሆንላቸው ተመኝተዋል።
9 days ago
የሀዋሳው የቅዱስ ገብርኤል በዓል በድምቀት ተከበረ፤ ከንቲባው ለእንግዶች ጥሪ አቀረቡ
#fastmereja I በሀዋሳ ከተማ የዘንድሮው የቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል በከፍተኛ ድምቀት፣ በሰላምና በተዋበ ሥነ ሥርዓት መከበሩን የከተማዋ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገለጹ።
ከንቲባ ጥራቱ በየነ ለበዓሉ የታደሙትን ምዕመናንና እንግዶች እንኳን አደረሳችሁ ያሉ ሲሆን፣ ከሩቅና ከቅርብ የመጡ በርካታ እንግዶች በከተማዋ መገኘታቸው ለበዓሉ ልዩ ድምቀት መስጠቱን ገልጸዋል።
ከንቲባው አክለውም እንግዶች በዓሉ ካበቃ በኋላም ቢሆን ቆይታቸውን በማራዘም የሀዋሳ ሐይቅን፣ የከተማዋን ንጹሕ አየርና የሕዝቡን እንግዳ ተቀባይነት እየተለማመዱ መልካም ጊዜ እንዲያሳልፉ ጥሪ አቅርበዋል።
በመጨረሻም በዓሉ በሰላምና በውበት እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላደረጉ የቤተ ክርስቲያን አባቶች፣ የጸጥታ አካላት፣ የመንግሥት አመራሮች፣ ባለሀብቶች፣ የሆቴል ባለቤቶች፣ በጎ ፈቃደኞችና የመላው የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች የከበረ ምስጋናቸውን አስተላልፈዋል።
#fastmereja I በሀዋሳ ከተማ የዘንድሮው የቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል በከፍተኛ ድምቀት፣ በሰላምና በተዋበ ሥነ ሥርዓት መከበሩን የከተማዋ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገለጹ።
ከንቲባ ጥራቱ በየነ ለበዓሉ የታደሙትን ምዕመናንና እንግዶች እንኳን አደረሳችሁ ያሉ ሲሆን፣ ከሩቅና ከቅርብ የመጡ በርካታ እንግዶች በከተማዋ መገኘታቸው ለበዓሉ ልዩ ድምቀት መስጠቱን ገልጸዋል።
ከንቲባው አክለውም እንግዶች በዓሉ ካበቃ በኋላም ቢሆን ቆይታቸውን በማራዘም የሀዋሳ ሐይቅን፣ የከተማዋን ንጹሕ አየርና የሕዝቡን እንግዳ ተቀባይነት እየተለማመዱ መልካም ጊዜ እንዲያሳልፉ ጥሪ አቅርበዋል።
በመጨረሻም በዓሉ በሰላምና በውበት እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላደረጉ የቤተ ክርስቲያን አባቶች፣ የጸጥታ አካላት፣ የመንግሥት አመራሮች፣ ባለሀብቶች፣ የሆቴል ባለቤቶች፣ በጎ ፈቃደኞችና የመላው የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች የከበረ ምስጋናቸውን አስተላልፈዋል።
10 days ago
ዘማሪት ኢየሩሳሌም አየለ «የጄሪ ጩኮ»ን ጨምሮ ባህላዊ ምግቦችን ለኤክስፖርት አቀረበች!
#fastmereja I ታዋቂዋ ዘማሪ ኢየሩሳሌም አየለ (ጄሪ) የኢትዮጵያ ባህላዊ ምግቦችን(ጩኮ) እና የቅመማ ቅመም ምርቶችን ለውጭ ሀገር ገበያ (Export) ለማቅረብ ያዘጋጀችውን አዲስ የንግድ ስራ እና የምርት አይነቶች በይፋ አስተዋወቀች።
በእናትና አባቷ የሼፍነት ሙያ እና በቤተሰብ የሙያ ውርስ ላይ ተመስርቶ የተጀመረው ይህ የንግድ ስራ፤ በዋናነት «ጄሪ»በሚል የምርት ስም የሚታወቅ ሲሆን፣ የቦቆጂን የሳር እና የጦስኝ ለጋ ቅቤ በመጠቀም የተዘጋጀውን «የጄሪ ጩኮ» ጨምሮ አነባበሮ፣ በቅቤ የታሸገ ቆሎ፣ ዳጣ እና ሚጥሚጣን ለገበያ አቅርቧል።
ዘማሪ ኢየሩሳሌም እንደገለፀችው፣ ምርቶቹ ሙሉ በሙሉ በቤት ውስጥ በከፍተኛ ንፅህና እና ጥንቃቄ በራሳቸው እጅ የሚዘጋጁ መሆናቸዉን ገልፃለች።
ዘማሪ እየሩሳሌም አክላም ምርቶቹ አለም አቀፍ የኤክስፖርት መስፈርትን (Export Standard) አሟልተው የተሰሩ በመሆናቸው ቀዝቃዛ ቦታ ላይ በመጠበቅ ከ1 ወር እስከ 1 ዓመት ድረስ ሳይበላሹ መቆየት እንደሚችሉ ገልፃ በተለይም በቅቤ የታሸገው ቆሎ የምርቱን ትኩስነት እና ጥራት ለመጠበቅ ሲባል በልዩ ትዕዛዝ ብቻ የሚዘጋጅ መሆኑ ገልፃለች።
የምርቱ"ዋና አላማ ከሀገር ውስጥ አልፎ የኢትዮጵያን ባህላዊ ጣዕሞች በዓለም አቀፍ ደረጃ ማስተዋወቅ ነው" ስትል የተናገረችው ዘማሪ ኢየሩሳሌም፤ በአሁኑ ወቅት ወደ ካናዳ፣ አሜሪካ፣ አውስትራሊያ እና ጀርመን ምርቶቹን ለመላክ የሚያስችሉ ቅድመ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን ገልጻለች።
በአሁኑ ወቅት በቤተሰብ ደረጃ እየተከናወነ የሚገኘው ይህ ኢንተርፕራይዝ፣ ስራው ከፍተኛ ጥንቃቄ እና ድካም የሚይዝ ቢሆንም ምርቶቹን ለተጠቃሚው በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ መታቀዱ ተገልጿል።
በመጨረሻም ድርጅቱ ወደፊት አቅሙን በማስፋፋት ለበርካታ ዜጎች ተጨማሪ የሥራ ዕድል የመፍጠር እና አዳዲስ ባህላዊ ምርቶችን ወደ ገበያ የማስገባት እቅድ እንዳለው ነዉ የተገለፀዉ።
#fastmereja I ታዋቂዋ ዘማሪ ኢየሩሳሌም አየለ (ጄሪ) የኢትዮጵያ ባህላዊ ምግቦችን(ጩኮ) እና የቅመማ ቅመም ምርቶችን ለውጭ ሀገር ገበያ (Export) ለማቅረብ ያዘጋጀችውን አዲስ የንግድ ስራ እና የምርት አይነቶች በይፋ አስተዋወቀች።
በእናትና አባቷ የሼፍነት ሙያ እና በቤተሰብ የሙያ ውርስ ላይ ተመስርቶ የተጀመረው ይህ የንግድ ስራ፤ በዋናነት «ጄሪ»በሚል የምርት ስም የሚታወቅ ሲሆን፣ የቦቆጂን የሳር እና የጦስኝ ለጋ ቅቤ በመጠቀም የተዘጋጀውን «የጄሪ ጩኮ» ጨምሮ አነባበሮ፣ በቅቤ የታሸገ ቆሎ፣ ዳጣ እና ሚጥሚጣን ለገበያ አቅርቧል።
ዘማሪ ኢየሩሳሌም እንደገለፀችው፣ ምርቶቹ ሙሉ በሙሉ በቤት ውስጥ በከፍተኛ ንፅህና እና ጥንቃቄ በራሳቸው እጅ የሚዘጋጁ መሆናቸዉን ገልፃለች።
ዘማሪ እየሩሳሌም አክላም ምርቶቹ አለም አቀፍ የኤክስፖርት መስፈርትን (Export Standard) አሟልተው የተሰሩ በመሆናቸው ቀዝቃዛ ቦታ ላይ በመጠበቅ ከ1 ወር እስከ 1 ዓመት ድረስ ሳይበላሹ መቆየት እንደሚችሉ ገልፃ በተለይም በቅቤ የታሸገው ቆሎ የምርቱን ትኩስነት እና ጥራት ለመጠበቅ ሲባል በልዩ ትዕዛዝ ብቻ የሚዘጋጅ መሆኑ ገልፃለች።
የምርቱ"ዋና አላማ ከሀገር ውስጥ አልፎ የኢትዮጵያን ባህላዊ ጣዕሞች በዓለም አቀፍ ደረጃ ማስተዋወቅ ነው" ስትል የተናገረችው ዘማሪ ኢየሩሳሌም፤ በአሁኑ ወቅት ወደ ካናዳ፣ አሜሪካ፣ አውስትራሊያ እና ጀርመን ምርቶቹን ለመላክ የሚያስችሉ ቅድመ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን ገልጻለች።
በአሁኑ ወቅት በቤተሰብ ደረጃ እየተከናወነ የሚገኘው ይህ ኢንተርፕራይዝ፣ ስራው ከፍተኛ ጥንቃቄ እና ድካም የሚይዝ ቢሆንም ምርቶቹን ለተጠቃሚው በተመጣጣኝ ዋጋ ለማቅረብ መታቀዱ ተገልጿል።
በመጨረሻም ድርጅቱ ወደፊት አቅሙን በማስፋፋት ለበርካታ ዜጎች ተጨማሪ የሥራ ዕድል የመፍጠር እና አዳዲስ ባህላዊ ምርቶችን ወደ ገበያ የማስገባት እቅድ እንዳለው ነዉ የተገለፀዉ።
10 days ago
ጊፍት ትሬዲንግ 35ኛ ዓመት የምስረታ ኢዮቤልዩውን አከበረ!
#fastmereja :- በኢትዮጵያ በገቢና ወጪ ንግድ ዘርፍ አንጋፋ ከሆኑ ኩባንያዎች አንዱ የሆነው ጊፍት ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር፣ የተመሰረተበትን 35ኛ ዓመት የምስረታ ኢዮቤልዩ በዓል በዛሬዉ እለት አክብሯል።
በንግድ ማህበረሰቡ፣ በመንግስት የስራ ሃላፊዎች እና በድርጅቱ አመራሮች በተገኙበት በዚህ መርሃ-ግብር ላይ ኩባንያው ባለፉት ሶስት አስርት ዓመታት ከግማሽ ያስመዘገባቸውን ስኬቶች ያቀረበ ሲሆን፣ በቀጣይም ወደ አግሮ-ኢንዱስትሪ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለመሸጋገር ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ይፋ አድርጓል።
ድርጅቱ ይፋ ባደረገው እቅድ መሠረት በአዳማ እና ሞጆ ከተሞች መካከል በሚገኘው የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ፍሪ ዞን ውስጥ 7,527.54 ካሬ ሜትር ቦታ መረከቡን ገልፀዉ ቦታው ከጅቡቲ ኮሪደር እና ከሞጆ ደረቅ ወደብ አቅራቢያ የሚገኝ በመሆኑ፣ የገቢና ወጪ ንግድ እንቅስቃሴውን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳልጠው የተገለጸ ሲሆን፤ የአካባቢው የዲዛይን ስራ ተጠናቆ ወደ ግንባታ ምዕራፍ መሸጋገሩ ተመልክቷል።
ከዚህ በተጨማሪም ኩባንያው እሴት በተጨመረባቸው የግብርና ምርቶች ዘርፍ መሰማራት የጀመረ ሲሆን፣ በተለይም በድፍድፍ የአቮካዶ ዘይት ማምረት እና በከባድ የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች አስመጪነት ዘርፍ ለመግባት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል።
የውጭ ምንዛሪ ግኝቱን ለማሳደግ እና የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማጠናከር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ በቤንች ሸኮ ዞን የጥቁር አዝሙድ እርሻ መጀመሩን የጠቆመው ጊፍት ትሬዲንግ፤ በቀጣይ ስድስት ወራት ውስጥ 300 ሄክታርየቡና እርሻ መሬት ተረክቦ ወደ ምርት እንደሚገባ አስታውቋል።
ከ50 ዓመታት በፊት በመርካቶ በታዋቂው የቢዝነስ ሰው በአቶ ገብረኢየሱስ ኢጋታ ሲማ በትንሽ የችርቻሮ ሱቅ የተጀመረው ይህ የንግድ እንቅስቃሴ፣ በ1980ዎቹ መጀመሪያ ወደ ገቢና ወጪ ንግድ በማደግ ለዛሬው ግዙፉ ጊፍት ቢዝነስ ግሩፕ (ጊፍት ሪል እስቴት፣ ጊፍት ኮንስትራክሽን፣ ጊፍት ብረታ ብረት፣ ጊፍት ፕሮፐርቲ እና ጊፍት ቱር ኤንድ ትራቭል) መፈጠር መሰረት መሆኑ ተገልጿል።
በተጨማሪም B-29 የልብስ ሳሙና፣ የሮድ ስቶን የተሽከርካሪ ጎማዎች፣ የጂንዳል ቆርቆሮዎች፣ የብረትና የኬሚካል ምርቶችን ጨምሮ በርካታ ጥራት ያላቸውን ምርቶች ለሀገር ውስጥ ገበያ በማስተዋወቅ ረገድ ኩባንያው የነበረው ሚና ከፍተኛ እንደነበር ተገልጿል።
ኩባንያው እ.ኤ.አ በ2030 በኢትዮጵያ በቡና፣ ቅባት እህሎች፣ ጥራጥሬ እና ቅመማ ቅመም ላኪነት ከግንባርቀደም 5 ኩባንያዎች አንዱ የመሆን ራዕይ ሰንቋል።
#fastmereja :- በኢትዮጵያ በገቢና ወጪ ንግድ ዘርፍ አንጋፋ ከሆኑ ኩባንያዎች አንዱ የሆነው ጊፍት ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር፣ የተመሰረተበትን 35ኛ ዓመት የምስረታ ኢዮቤልዩ በዓል በዛሬዉ እለት አክብሯል።
በንግድ ማህበረሰቡ፣ በመንግስት የስራ ሃላፊዎች እና በድርጅቱ አመራሮች በተገኙበት በዚህ መርሃ-ግብር ላይ ኩባንያው ባለፉት ሶስት አስርት ዓመታት ከግማሽ ያስመዘገባቸውን ስኬቶች ያቀረበ ሲሆን፣ በቀጣይም ወደ አግሮ-ኢንዱስትሪ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለመሸጋገር ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ይፋ አድርጓል።
ድርጅቱ ይፋ ባደረገው እቅድ መሠረት በአዳማ እና ሞጆ ከተሞች መካከል በሚገኘው የገዳ ልዩ ኢኮኖሚ ፍሪ ዞን ውስጥ 7,527.54 ካሬ ሜትር ቦታ መረከቡን ገልፀዉ ቦታው ከጅቡቲ ኮሪደር እና ከሞጆ ደረቅ ወደብ አቅራቢያ የሚገኝ በመሆኑ፣ የገቢና ወጪ ንግድ እንቅስቃሴውን በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳልጠው የተገለጸ ሲሆን፤ የአካባቢው የዲዛይን ስራ ተጠናቆ ወደ ግንባታ ምዕራፍ መሸጋገሩ ተመልክቷል።
ከዚህ በተጨማሪም ኩባንያው እሴት በተጨመረባቸው የግብርና ምርቶች ዘርፍ መሰማራት የጀመረ ሲሆን፣ በተለይም በድፍድፍ የአቮካዶ ዘይት ማምረት እና በከባድ የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች አስመጪነት ዘርፍ ለመግባት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል።
የውጭ ምንዛሪ ግኝቱን ለማሳደግ እና የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማጠናከር በማዕከላዊ ኢትዮጵያ በቤንች ሸኮ ዞን የጥቁር አዝሙድ እርሻ መጀመሩን የጠቆመው ጊፍት ትሬዲንግ፤ በቀጣይ ስድስት ወራት ውስጥ 300 ሄክታርየቡና እርሻ መሬት ተረክቦ ወደ ምርት እንደሚገባ አስታውቋል።
ከ50 ዓመታት በፊት በመርካቶ በታዋቂው የቢዝነስ ሰው በአቶ ገብረኢየሱስ ኢጋታ ሲማ በትንሽ የችርቻሮ ሱቅ የተጀመረው ይህ የንግድ እንቅስቃሴ፣ በ1980ዎቹ መጀመሪያ ወደ ገቢና ወጪ ንግድ በማደግ ለዛሬው ግዙፉ ጊፍት ቢዝነስ ግሩፕ (ጊፍት ሪል እስቴት፣ ጊፍት ኮንስትራክሽን፣ ጊፍት ብረታ ብረት፣ ጊፍት ፕሮፐርቲ እና ጊፍት ቱር ኤንድ ትራቭል) መፈጠር መሰረት መሆኑ ተገልጿል።
በተጨማሪም B-29 የልብስ ሳሙና፣ የሮድ ስቶን የተሽከርካሪ ጎማዎች፣ የጂንዳል ቆርቆሮዎች፣ የብረትና የኬሚካል ምርቶችን ጨምሮ በርካታ ጥራት ያላቸውን ምርቶች ለሀገር ውስጥ ገበያ በማስተዋወቅ ረገድ ኩባንያው የነበረው ሚና ከፍተኛ እንደነበር ተገልጿል።
ኩባንያው እ.ኤ.አ በ2030 በኢትዮጵያ በቡና፣ ቅባት እህሎች፣ ጥራጥሬ እና ቅመማ ቅመም ላኪነት ከግንባርቀደም 5 ኩባንያዎች አንዱ የመሆን ራዕይ ሰንቋል።
10 days ago
በኢትዮጵያ የግሉን ሴክተርና የኢንቨስትመንት ትስስር ለማጠናከር ያለመ የንግድ ዎርክሾፕ ተካሄደ!
#fastmereja I አሎሃ ቪስታ ኃ.የተ.የግ.ማ የመንግሥትና የግሉን ሴክተር ተዋናዮች፣ የዲፕሎማቲክ ኮር አባላትን እንዲሁም አገር በቀልና ዓለም አቀፍ ባለሀብቶችን ያገናኘ ከፍተኛ የንግድ ለንግድ (B2B) ትስስርና የዎርክሾፕ መድረክ በዛሬዉ እለት በካፒታል ሆቴል ተካሂዷል።
ዝግጅቱ በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ልማት፣ የኢንቨስትመንት ማስፋፋት እና የግሉ ሴክተር ማጠናከር ላይ የሚሰሩ የመንግሥት ሚኒስትሮችን፣ የንግድ ምክር ቤቶችን፣ ባለሀብቶችንና የዘርፉን ባለሙያዎች በአንድ መድረክ ያሰባሰበ ነበር።
መርሀ-ግብሩ የመንግሥት አመራሮች በኢኮኖሚ ማሻሻያዎች፣ በኢንቨስትመንት ፖሊሲና በንግድ አካባቢ ሁኔታዎች ላይ ሰፊ የሃሳብ ልውውጥ አድርገዋል።
መርሀ-ግብሩ በግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ሪል እስቴት፣ ማዕድን እና ቴክኖሎጂ ዘርፎች ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ በዘርፎቹ ያሉ የገበያ እድሎች፣ የኢንቨስትመንት አቅጣጫዎች እና ዋና ዋና ተግዳሮቶች በባለሙያዎች ቀርበው የፓናል ውይይት ተካሂዶባቸዋል።
የአሎሃ ቪስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሄለና ንጉሳይ እንደገለፁት፤ "ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት የሚገነባው በጠንካራ ሽርክና፣ በእውቀት ልውውጥ እና በተግባራዊ የንግድ ትስስር ነው"ካሉ በኋላ፣ አሎሃ ቪስታ በቀጣይም ተጨባጭ የንግድ እድሎችን የሚፈጥሩ መድረኮችን በማዘጋጀት ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ወደፊት ጉዞ አስተዋጽኦ ማድረጉን እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
በዕለቱ ከተደመጡት የክብሩ እንግዶች መካከል አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በበኩላቸዉ አፍሪካ ከፖለቲካ ነፃነት ባሻገር ኢኮኖሚያዊ ራሷን የመቻል ጉዞ ላይመሆኗን ጠቁመው፣ ሀገራት የተፈጥሮ ሀብታቸውን በአግባቡ በመጠቀምና በመንግስትና በንግዱ ማህበረሰብ መካከል ቀጣይነት ያለው ውይይት በማድረግ ድህነትን ማሸነፍ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የመድረኩ ዋና አካል በነበረው የንግድ ለንግድ ትስስር ክፍለ-ጊዜ፣ ተሳታፊዎች በቀጥታ በመገናኘት አዳዲስ የንግድ እድሎችን መለዋወጣቸውና ለወደፊት የሚሆኑ ስልታዊ ሽርክናዎችን መመሥረታቸው ተገልጿል።
#fastmereja I አሎሃ ቪስታ ኃ.የተ.የግ.ማ የመንግሥትና የግሉን ሴክተር ተዋናዮች፣ የዲፕሎማቲክ ኮር አባላትን እንዲሁም አገር በቀልና ዓለም አቀፍ ባለሀብቶችን ያገናኘ ከፍተኛ የንግድ ለንግድ (B2B) ትስስርና የዎርክሾፕ መድረክ በዛሬዉ እለት በካፒታል ሆቴል ተካሂዷል።
ዝግጅቱ በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ልማት፣ የኢንቨስትመንት ማስፋፋት እና የግሉ ሴክተር ማጠናከር ላይ የሚሰሩ የመንግሥት ሚኒስትሮችን፣ የንግድ ምክር ቤቶችን፣ ባለሀብቶችንና የዘርፉን ባለሙያዎች በአንድ መድረክ ያሰባሰበ ነበር።
መርሀ-ግብሩ የመንግሥት አመራሮች በኢኮኖሚ ማሻሻያዎች፣ በኢንቨስትመንት ፖሊሲና በንግድ አካባቢ ሁኔታዎች ላይ ሰፊ የሃሳብ ልውውጥ አድርገዋል።
መርሀ-ግብሩ በግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ሪል እስቴት፣ ማዕድን እና ቴክኖሎጂ ዘርፎች ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ በዘርፎቹ ያሉ የገበያ እድሎች፣ የኢንቨስትመንት አቅጣጫዎች እና ዋና ዋና ተግዳሮቶች በባለሙያዎች ቀርበው የፓናል ውይይት ተካሂዶባቸዋል።
የአሎሃ ቪስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሄለና ንጉሳይ እንደገለፁት፤ "ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት የሚገነባው በጠንካራ ሽርክና፣ በእውቀት ልውውጥ እና በተግባራዊ የንግድ ትስስር ነው"ካሉ በኋላ፣ አሎሃ ቪስታ በቀጣይም ተጨባጭ የንግድ እድሎችን የሚፈጥሩ መድረኮችን በማዘጋጀት ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ወደፊት ጉዞ አስተዋጽኦ ማድረጉን እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
በዕለቱ ከተደመጡት የክብሩ እንግዶች መካከል አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በበኩላቸዉ አፍሪካ ከፖለቲካ ነፃነት ባሻገር ኢኮኖሚያዊ ራሷን የመቻል ጉዞ ላይመሆኗን ጠቁመው፣ ሀገራት የተፈጥሮ ሀብታቸውን በአግባቡ በመጠቀምና በመንግስትና በንግዱ ማህበረሰብ መካከል ቀጣይነት ያለው ውይይት በማድረግ ድህነትን ማሸነፍ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የመድረኩ ዋና አካል በነበረው የንግድ ለንግድ ትስስር ክፍለ-ጊዜ፣ ተሳታፊዎች በቀጥታ በመገናኘት አዳዲስ የንግድ እድሎችን መለዋወጣቸውና ለወደፊት የሚሆኑ ስልታዊ ሽርክናዎችን መመሥረታቸው ተገልጿል።
11 days ago
ከ700 በላይ የዓለም መሪዎችንና ፈጣሪዎችን የሚያሰባስበው ጉባኤ በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው!
#fastmereja :- ታሪካዊው «የዓለም አቀፍ የሕዝቦች ጉባኤ አፍሪካ» (World Public Summit Africa) ከሐምሌ 22 እስከ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. በዲፕሎማሲያዊቷ መዲና አዲስ አበባ በደመቀ ሁኔታ እንደሚካሄድ በዛሬዉ እለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቁ።
«አዲስ ዓለም አፍሪካ የጋራ መፃኢ እድልን በመቅረጽ ረገድ» በሚል መሪ ቃል በሚካሄደው በዚህ ጉባኤ ላይ ከ700 በላይ የመንግሥት መሪዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የቢዝነስ ባለሀብቶች፣ የፈጠራ አውጪዎች፣ ምሁራን፣ የሲቪል ማህበራት ተወካዮች፣ የብዙሃን መገናኛ ባለሙያዎች እና የባህል መሪዎች ከመላው አፍሪካና ከሌሎች የዓለም ክፍሎች ይሳተፋሉ።
ጉባኤው በስፖርት አማካኝነት በቢሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ከሚያቀራርበው የዓለም ዋንጫ ጋር በሚመሳሰል መልኩ፡ የተለያዩ ዓለም አቀፍ አካላትን በማሰባሰብ በጋራ ሀሳብ የመለዋወጥ፣ ጠንካራ አጋርነቶችን የመፍጠር እና ለዓለማችን መሠረታዊ ኢኮኖሚያዊ፣ ቴክኖሎጂያዊ፣ ማህበራዊ እና የልማት ጉዳዮች መፍትሔ የመፈለግ ዓላማን ማሰናዳቱን ተገልጿል።
ይህ ታላቅ መድረክ በአፍሪካ አህጉር ሲካሄድ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን፣ ይህም አፍሪካ በዓለም አቀፍ የንግድ፣የፈጠራ፣ የዘላቂ ልማት፣ የሕዝብ ዲፕሎማሲ እና የሁለገብ ትብብር ውይይቶች ላይ ያላትን እየጎለበተ የመጣ ማዕከላዊ ሚና የሚያንፀባርቅ እንደሆነ በመግለጫው ወቅት ተመላክቷል።
የጉባኤው ዋና ማዕከል ከሆኑት ዝግጅቶች አንዱ «አንድነት» (Unity) የተሰኘው ዓለም አቀፍ ዘመናዊ የኪነ-ጥበብ ኤግዚቢሽን መሆኑን አዘጋጆቹ ጠቁመዋል።
ኤግዚቢሽኑ ከ16 የአፍሪካ ሀገራት (ኢትዮጵያ፣ ካሜሩን፣ ኮንጎ ዲ/ሪ፣ ጋና፣ ኬንያ፣ ማዳጋስካር፣ ናሚቢያ፣ ናይጄሪያ፣ ሩዋንዳ፣ ሴኔጋል፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሱዳን፣ ታንዛኒያ፣ ቱኒዚያ፣ ዛምቢያ እና ዚምባብዌ) የተጣጣሙ ታዋቂ አርቲስቶችን እንዲሁም የአፍሪካና የዳያስፖራውን ታሪካዊ ቁርኝት የሚያሳይ አፍሮ-ብራዚላዊ አርቲስትን ያሰባስባል።
በተጨማሪም «የዛምቤዚ ወንዝ፡ ኢኮኖሚ፣ ማህበረሰብ እና መንፈስ» በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሳይንሳዊ ጥናት የሚቀርብ ሲሆን፣ ጥናቱ ወንዙ በስድስት የአፍሪካ ሀገራት (አንጎላ፣ ዚምባብዌ፣ ዛምቢያ፣ ናሚቢያ፣ ቦትስዋና እና ሞዛምቢክ) እድገት ላይ ያለውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ በስፋት እንደሚመረምር ነዉ የተገለፀዉ።
የጠቅላላው ምክር ቤት ሊቀመንበር አማካሪ ያኒና ዱቤይኮቭስካያ እንደገለፁት «አንድነት ማለት ወጥ መሆን ማለት አይደለም፤ ይልቁንም ለባህል ብዝሃነት ከሚሰጥ አክብሮት፣ ከእርስ በእርስ እምነት፣ ክፍትነት እና ለመደማመጥ ከሚኖር ፈቃደኝነት የሚወለድ መሆኑን ገልፀዉ ስለዚህም ጥበብ ልክ እንደ ስፖርት ሁሉ የሰው ልጅ የጋራ ቋንቋ እና የሕዝብ ዲፕሎማሲ መሣሪያ ነው። ቃላት ብቻቸውን ማሳካት በማይችሉበት ቦታ ሰዎችን ያቀራርባል።» ብለዋል።
የሰርቭ ግሎባል (Serve Global) ምክትል የሀገርውስጥ ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ነጋሽ እንደገለፁት«ጉባኤው በንግድ ድርድር ላይ ሳይሆን አልሞ የተነሳና የእውነተኛ አንድነትን በማሳየት ለሁሉም የዓለም ሕዝቦች የሚሰራ አዲስ ዓለም ለመገንባት መንገድ ይጠርጋል።» ሲሉ ገልጸዋል።
ይህ በአዲስ አበባ የሚካሄደው የአፍሪካ ጉባኤ ዓመቱን ሙሉ የሚቀጥል ዓለም አቀፍ የትብብር መድረክ አካል ሲሆን፣ ቀጣዩ ዓለም አቀፍ መድረክ በመስከረም ወር በሩሲያ ሞስኮ እንደሚካሄድ ያኒና ዱቤይኮቭስካያ እና ታሪኩ ነጋሽ ጨምረው አስታውቀዋል።
#fastmereja :- ታሪካዊው «የዓለም አቀፍ የሕዝቦች ጉባኤ አፍሪካ» (World Public Summit Africa) ከሐምሌ 22 እስከ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. በዲፕሎማሲያዊቷ መዲና አዲስ አበባ በደመቀ ሁኔታ እንደሚካሄድ በዛሬዉ እለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቁ።
«አዲስ ዓለም አፍሪካ የጋራ መፃኢ እድልን በመቅረጽ ረገድ» በሚል መሪ ቃል በሚካሄደው በዚህ ጉባኤ ላይ ከ700 በላይ የመንግሥት መሪዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የቢዝነስ ባለሀብቶች፣ የፈጠራ አውጪዎች፣ ምሁራን፣ የሲቪል ማህበራት ተወካዮች፣ የብዙሃን መገናኛ ባለሙያዎች እና የባህል መሪዎች ከመላው አፍሪካና ከሌሎች የዓለም ክፍሎች ይሳተፋሉ።
ጉባኤው በስፖርት አማካኝነት በቢሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ከሚያቀራርበው የዓለም ዋንጫ ጋር በሚመሳሰል መልኩ፡ የተለያዩ ዓለም አቀፍ አካላትን በማሰባሰብ በጋራ ሀሳብ የመለዋወጥ፣ ጠንካራ አጋርነቶችን የመፍጠር እና ለዓለማችን መሠረታዊ ኢኮኖሚያዊ፣ ቴክኖሎጂያዊ፣ ማህበራዊ እና የልማት ጉዳዮች መፍትሔ የመፈለግ ዓላማን ማሰናዳቱን ተገልጿል።
ይህ ታላቅ መድረክ በአፍሪካ አህጉር ሲካሄድ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን፣ ይህም አፍሪካ በዓለም አቀፍ የንግድ፣የፈጠራ፣ የዘላቂ ልማት፣ የሕዝብ ዲፕሎማሲ እና የሁለገብ ትብብር ውይይቶች ላይ ያላትን እየጎለበተ የመጣ ማዕከላዊ ሚና የሚያንፀባርቅ እንደሆነ በመግለጫው ወቅት ተመላክቷል።
የጉባኤው ዋና ማዕከል ከሆኑት ዝግጅቶች አንዱ «አንድነት» (Unity) የተሰኘው ዓለም አቀፍ ዘመናዊ የኪነ-ጥበብ ኤግዚቢሽን መሆኑን አዘጋጆቹ ጠቁመዋል።
ኤግዚቢሽኑ ከ16 የአፍሪካ ሀገራት (ኢትዮጵያ፣ ካሜሩን፣ ኮንጎ ዲ/ሪ፣ ጋና፣ ኬንያ፣ ማዳጋስካር፣ ናሚቢያ፣ ናይጄሪያ፣ ሩዋንዳ፣ ሴኔጋል፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሱዳን፣ ታንዛኒያ፣ ቱኒዚያ፣ ዛምቢያ እና ዚምባብዌ) የተጣጣሙ ታዋቂ አርቲስቶችን እንዲሁም የአፍሪካና የዳያስፖራውን ታሪካዊ ቁርኝት የሚያሳይ አፍሮ-ብራዚላዊ አርቲስትን ያሰባስባል።
በተጨማሪም «የዛምቤዚ ወንዝ፡ ኢኮኖሚ፣ ማህበረሰብ እና መንፈስ» በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሳይንሳዊ ጥናት የሚቀርብ ሲሆን፣ ጥናቱ ወንዙ በስድስት የአፍሪካ ሀገራት (አንጎላ፣ ዚምባብዌ፣ ዛምቢያ፣ ናሚቢያ፣ ቦትስዋና እና ሞዛምቢክ) እድገት ላይ ያለውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ በስፋት እንደሚመረምር ነዉ የተገለፀዉ።
የጠቅላላው ምክር ቤት ሊቀመንበር አማካሪ ያኒና ዱቤይኮቭስካያ እንደገለፁት «አንድነት ማለት ወጥ መሆን ማለት አይደለም፤ ይልቁንም ለባህል ብዝሃነት ከሚሰጥ አክብሮት፣ ከእርስ በእርስ እምነት፣ ክፍትነት እና ለመደማመጥ ከሚኖር ፈቃደኝነት የሚወለድ መሆኑን ገልፀዉ ስለዚህም ጥበብ ልክ እንደ ስፖርት ሁሉ የሰው ልጅ የጋራ ቋንቋ እና የሕዝብ ዲፕሎማሲ መሣሪያ ነው። ቃላት ብቻቸውን ማሳካት በማይችሉበት ቦታ ሰዎችን ያቀራርባል።» ብለዋል።
የሰርቭ ግሎባል (Serve Global) ምክትል የሀገርውስጥ ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ነጋሽ እንደገለፁት«ጉባኤው በንግድ ድርድር ላይ ሳይሆን አልሞ የተነሳና የእውነተኛ አንድነትን በማሳየት ለሁሉም የዓለም ሕዝቦች የሚሰራ አዲስ ዓለም ለመገንባት መንገድ ይጠርጋል።» ሲሉ ገልጸዋል።
ይህ በአዲስ አበባ የሚካሄደው የአፍሪካ ጉባኤ ዓመቱን ሙሉ የሚቀጥል ዓለም አቀፍ የትብብር መድረክ አካል ሲሆን፣ ቀጣዩ ዓለም አቀፍ መድረክ በመስከረም ወር በሩሲያ ሞስኮ እንደሚካሄድ ያኒና ዱቤይኮቭስካያ እና ታሪኩ ነጋሽ ጨምረው አስታውቀዋል።
12 days ago
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ውጣ ውረዶችን የሚዳስስ «ጽናት» የተሰኘ መጽሐፍ ሊመረቅ ነው
#fastmereja I የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ያለፈባቸውን የታሪክ ውጣ ውረዶች እና ተቋማዊ የለውጥ ጉዞ የሚያስነብብ «ጽናት፡ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ታሪካዊ የለውጥ ጉዞ» የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በማዕከላዊ ጎንደር ዞን አስተዳደር የመሰብሰቢያ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ እንደሚመረቅ ተገለጸ።
መጽሐፉ በዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት በዶክተር አሥራት ዓፀደወይን የተጻፈ ሲሆን፣ ተቋሙ በረጅም ዘመን ጉዞው ያሳለፋቸውን ፈተናዎች፣ ያመጣቸውን ተቋማዊ ለውጦች እና ያስመዘገባቸውን ስኬቶች በሰፊው የሚዳስስ ታሪካዊ ሰነድ እንደሆነ ታውቋል።
በዕለቱ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በሚካሄደው የይፋዊ ምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ ጥሪ የተደረገላቸው ልዩ ልዩ እንግዶች፣ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች እና የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላት እንደሚታደሙ ከተቋሙ የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
#fastmereja I የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ያለፈባቸውን የታሪክ ውጣ ውረዶች እና ተቋማዊ የለውጥ ጉዞ የሚያስነብብ «ጽናት፡ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ታሪካዊ የለውጥ ጉዞ» የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በማዕከላዊ ጎንደር ዞን አስተዳደር የመሰብሰቢያ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ እንደሚመረቅ ተገለጸ።
መጽሐፉ በዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት በዶክተር አሥራት ዓፀደወይን የተጻፈ ሲሆን፣ ተቋሙ በረጅም ዘመን ጉዞው ያሳለፋቸውን ፈተናዎች፣ ያመጣቸውን ተቋማዊ ለውጦች እና ያስመዘገባቸውን ስኬቶች በሰፊው የሚዳስስ ታሪካዊ ሰነድ እንደሆነ ታውቋል።
በዕለቱ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በሚካሄደው የይፋዊ ምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ ጥሪ የተደረገላቸው ልዩ ልዩ እንግዶች፣ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች እና የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላት እንደሚታደሙ ከተቋሙ የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
12 days ago
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ውጣ ውረዶችን የሚዳስስ «ጽናት» የተሰኘ መጽሐፍ ሊመረቅ ነው
#fastmereja I የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ያለፈባቸውን የታሪክ ውጣ ውረዶች እና ተቋማዊ የለውጥ ጉዞ የሚያስነብብ «ጽናት፡ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ታሪካዊ የለውጥ ጉዞ» የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በማዕከላዊ ጎንደር ዞን አስተዳደር የመሰብሰቢያ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ እንደሚመረቅ ተገለጸ።
መጽሐፉ በዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት በዶክተር አሥራት ዓፀደወይን የተጻፈ ሲሆን፣ ተቋሙ በረጅም ዘመን ጉዞው ያሳለፋቸውን ፈተናዎች፣ ያመጣቸውን ተቋማዊ ለውጦች እና ያስመዘገባቸውን ስኬቶች በሰፊው የሚዳስስ ታሪካዊ ሰነድ እንደሆነ ታውቋል።
በዕለቱ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በሚካሄደው የይፋዊ ምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ ጥሪ የተደረገላቸው ልዩ ልዩ እንግዶች፣ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች እና የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላት እንደሚታደሙ ከተቋሙ የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
#fastmereja I የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ያለፈባቸውን የታሪክ ውጣ ውረዶች እና ተቋማዊ የለውጥ ጉዞ የሚያስነብብ «ጽናት፡ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ታሪካዊ የለውጥ ጉዞ» የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በማዕከላዊ ጎንደር ዞን አስተዳደር የመሰብሰቢያ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ እንደሚመረቅ ተገለጸ።
መጽሐፉ በዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት በዶክተር አሥራት ዓፀደወይን የተጻፈ ሲሆን፣ ተቋሙ በረጅም ዘመን ጉዞው ያሳለፋቸውን ፈተናዎች፣ ያመጣቸውን ተቋማዊ ለውጦች እና ያስመዘገባቸውን ስኬቶች በሰፊው የሚዳስስ ታሪካዊ ሰነድ እንደሆነ ታውቋል።
በዕለቱ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በሚካሄደው የይፋዊ ምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ ጥሪ የተደረገላቸው ልዩ ልዩ እንግዶች፣ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች እና የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላት እንደሚታደሙ ከተቋሙ የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
Sponsored by
Surafel
12 days ago
የኢትዮጵያን የሪል እስቴት ገበያ ለአለም አቀፍ ኢንቨስተሮች የሚያስተዋውቅ አዲስ ስምምነት ተፈረመ!
#fastmereja I የኢትዮጵያ ሪል እስቴት አልሚዎች ማህበር (EREDA) እና ዶክሳ ቢዝነስ ትሬዲንግ ኃ.የተ.የግ.ማ. በኢትዮጵያ የሪል እስቴት ዘርፍን በሀገር ውስጥ እና በአለም አቀፍ ደረጃ ለማጠናከር የሚያስችሉ ሁለት ስትራቴጂካዊ የመግባቢያ ሰነዶችን በዛሬዉ እለት ተፈራረሙ፡፡
ስምምነቱ የሪል እስቴት ዘርፉን ትብብር ለማሳደግ፣ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስፋፋት እንዲሁም የዲያስፖራውን ተሳትፎ ለማሳደግ ያለመ መሆኑ ተገልጻል፡፡
በስምምነቱ መሠረት በሀገር ውስጥ የኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበርን ተቋማዊ አቅም ማጠናከር፣ የአባልነት መስፋፋትን መደገፍ፣ በመንግስት እና በግል ዘርፍ መካከል ያለውን ትብብር ማሳደግ እና የዕውቀት ልውውጥ መድረኮችን በጋራ ማዘጋጀት ዋና ዋና ትኩረቶች ሲሆኑ በዚህም ዶክሳ ቢዝነስ ትሬዲንግ ለተመረጡ መርሃግብሮች የኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር (EREDA) ተመራጭ የኢቨንት አስተባባሪ አጋር ሆኖ እንደሚሰራም ነዉ የተገለፀዉ።
በሌላ በኩል ስምምነቱ የዲያስፖራ ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት እና የውጭ ምንዛሬ ገቢን ለማሳደግ ያለመ ሲሆን፣ የመጀመሪያዎቹ አለም አቀፍ የሪል እስቴትና ኢንቨስትመንት ትስስር ፕሮግራሞች በሪያድ (ሳውዲ አረቢያ)፣ በጆሃንስበርግ (ደቡብ አፍሪካ) እና በእስራኤል እንደሚካሄዱ ተጠቅሷል፡፡
ሁለቱ ተቋማት ቀደም ሲል እንደ "Addis Africa Real Estate Expo 2026" ያሉ ትልልቅ መድረኮችን በጋራ ማዘጋጀታቸው የሚታወስ ሲሆን፣ በቀጣይም የሚተገበሩ ፕሮጀክቶች በግልጽነት እና በተጠያቂነት መመሪያዎች የሚመሩ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡
ዶክሳ ቢዝነስ ትሬዲንግ ኃ.የተ.የግ.ማ. በቢዝነስ ልማት፣ በስትራቴጂካዊ ግንኙነት፣ በኢቨንት ማስተባበር፣ በማርኬቲንግ ኮሙኒኬሽን እና በባለድርሻ አካላት ትስስር ላይ የተሰማራ ድርጅት ሲሆን፣ ቢዝነሶችን፣ ባለሀብቶችን፣ መንግስታዊ ተቋማትን እና ማህበረሰቡን የሚያገናኙ ዘላቂና ፈጠራ ያላቸው መድረኮችን በመፍጠር ለኢኮኖሚያዊና ለኢንዱስትሪ ልማት አስተዋፅኦ ያደርጋል::
#fastmereja I የኢትዮጵያ ሪል እስቴት አልሚዎች ማህበር (EREDA) እና ዶክሳ ቢዝነስ ትሬዲንግ ኃ.የተ.የግ.ማ. በኢትዮጵያ የሪል እስቴት ዘርፍን በሀገር ውስጥ እና በአለም አቀፍ ደረጃ ለማጠናከር የሚያስችሉ ሁለት ስትራቴጂካዊ የመግባቢያ ሰነዶችን በዛሬዉ እለት ተፈራረሙ፡፡
ስምምነቱ የሪል እስቴት ዘርፉን ትብብር ለማሳደግ፣ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስፋፋት እንዲሁም የዲያስፖራውን ተሳትፎ ለማሳደግ ያለመ መሆኑ ተገልጻል፡፡
በስምምነቱ መሠረት በሀገር ውስጥ የኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበርን ተቋማዊ አቅም ማጠናከር፣ የአባልነት መስፋፋትን መደገፍ፣ በመንግስት እና በግል ዘርፍ መካከል ያለውን ትብብር ማሳደግ እና የዕውቀት ልውውጥ መድረኮችን በጋራ ማዘጋጀት ዋና ዋና ትኩረቶች ሲሆኑ በዚህም ዶክሳ ቢዝነስ ትሬዲንግ ለተመረጡ መርሃግብሮች የኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር (EREDA) ተመራጭ የኢቨንት አስተባባሪ አጋር ሆኖ እንደሚሰራም ነዉ የተገለፀዉ።
በሌላ በኩል ስምምነቱ የዲያስፖራ ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት እና የውጭ ምንዛሬ ገቢን ለማሳደግ ያለመ ሲሆን፣ የመጀመሪያዎቹ አለም አቀፍ የሪል እስቴትና ኢንቨስትመንት ትስስር ፕሮግራሞች በሪያድ (ሳውዲ አረቢያ)፣ በጆሃንስበርግ (ደቡብ አፍሪካ) እና በእስራኤል እንደሚካሄዱ ተጠቅሷል፡፡
ሁለቱ ተቋማት ቀደም ሲል እንደ "Addis Africa Real Estate Expo 2026" ያሉ ትልልቅ መድረኮችን በጋራ ማዘጋጀታቸው የሚታወስ ሲሆን፣ በቀጣይም የሚተገበሩ ፕሮጀክቶች በግልጽነት እና በተጠያቂነት መመሪያዎች የሚመሩ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡
ዶክሳ ቢዝነስ ትሬዲንግ ኃ.የተ.የግ.ማ. በቢዝነስ ልማት፣ በስትራቴጂካዊ ግንኙነት፣ በኢቨንት ማስተባበር፣ በማርኬቲንግ ኮሙኒኬሽን እና በባለድርሻ አካላት ትስስር ላይ የተሰማራ ድርጅት ሲሆን፣ ቢዝነሶችን፣ ባለሀብቶችን፣ መንግስታዊ ተቋማትን እና ማህበረሰቡን የሚያገናኙ ዘላቂና ፈጠራ ያላቸው መድረኮችን በመፍጠር ለኢኮኖሚያዊና ለኢንዱስትሪ ልማት አስተዋፅኦ ያደርጋል::
14 days ago
ድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ «Waa'ee Jireenya Koo!» የተሰኘ አዲስ የሙዚቃ ሊለቅ መሆኑ ታወቀ
#fastmereja I ታዋቂው ድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ «Waa'ee Jireenya Koo!» በሚል ርዕስ ያዘጋጀውን አዲስ የሙዚቃ በቅርብ ቀን ለአድናቂዎቹ እንደሚያቀርብ ታወቀ።
ድምጻዊው የህይወቱን ጉዞ እና ገጠመኝ የሚያንጸባርቅበት እንደሆነ የሚጠበቀውን ይህንን አዲስ የሙዚቃ ሥራውን አስመልክቶ ይፋዊ የማስተዋወቂያ ፖስተር ባሰራጨበት ወቅት፣ ሥራው በቅርቡ እንደሚለቀቅ አረጋግጧል።
#fastmereja I ታዋቂው ድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ «Waa'ee Jireenya Koo!» በሚል ርዕስ ያዘጋጀውን አዲስ የሙዚቃ በቅርብ ቀን ለአድናቂዎቹ እንደሚያቀርብ ታወቀ።
ድምጻዊው የህይወቱን ጉዞ እና ገጠመኝ የሚያንጸባርቅበት እንደሆነ የሚጠበቀውን ይህንን አዲስ የሙዚቃ ሥራውን አስመልክቶ ይፋዊ የማስተዋወቂያ ፖስተር ባሰራጨበት ወቅት፣ ሥራው በቅርቡ እንደሚለቀቅ አረጋግጧል።
14 days ago
ድምጻዊ ጎሳዬ ተስፋዬ ምን አጋጠመው?
#fastmereja I ከለንደን ወደ አዲስ አበባ የተመለሰው ታዋቂው ድምጻዊ ጎሳዬ ተስፋዬ «ታምሜ ገባሁ» ሲል በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባሰራጨው መረጃ አድናቂዎቹን ስጋት ውስጥ ጥሎ የነበረ ቢሆንም አደጋው አሳሳቢ እንዳልሆነ ታውቋል።
ድምጻዊው ከለንደን ወደ ኢትዮጵያ በመመለስ ላይ ሳለ በአየር መንገድ ውስጥ እርጥበት የነካው ሴራሚክ አዳልጦት የወደቀ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ጉዳዩን በተመለከተ ወደ ድምጻዊው ያቀናው ጋዜጠኛ ሰይፉ ፋንታሁን ከጎሳዬ ጋር በመሆን በሰጠው ማብራሪያ፣ ያጋጠመው ክስተት ከፍተኛ የሚባል የጤና አደጋ እንዳልሆነና አድናቂዎቹ ስጋት እንዳይገባቸው መልዕክት አስተላልፏል።
#fastmereja I ከለንደን ወደ አዲስ አበባ የተመለሰው ታዋቂው ድምጻዊ ጎሳዬ ተስፋዬ «ታምሜ ገባሁ» ሲል በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባሰራጨው መረጃ አድናቂዎቹን ስጋት ውስጥ ጥሎ የነበረ ቢሆንም አደጋው አሳሳቢ እንዳልሆነ ታውቋል።
ድምጻዊው ከለንደን ወደ ኢትዮጵያ በመመለስ ላይ ሳለ በአየር መንገድ ውስጥ እርጥበት የነካው ሴራሚክ አዳልጦት የወደቀ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ጉዳዩን በተመለከተ ወደ ድምጻዊው ያቀናው ጋዜጠኛ ሰይፉ ፋንታሁን ከጎሳዬ ጋር በመሆን በሰጠው ማብራሪያ፣ ያጋጠመው ክስተት ከፍተኛ የሚባል የጤና አደጋ እንዳልሆነና አድናቂዎቹ ስጋት እንዳይገባቸው መልዕክት አስተላልፏል።
14 days ago
በሳዑዲ አረቢያ 34 ኪሎ ግራም ሀሺሽ ወደ ሀገሪቷ ሊያስገቡ ሲሉ 4 ኢትዮጵያውያን በቁጥጥር ስር ዋሉ
#fastmereja | የሳዑዲ አረቢያ የድንበር ጠባቂ ኃይል በአሲር ክልል 34 ኪሎ ግራም የሐሺሽ አደንዛዥ ዕፅ ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት ሲሞክሩ የነበሩ አራት ኢትዮጵያውያንን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ።
የሀገሪቱ የድንበር ጠባቂ የመሬት ላይ ጥበቃ አባላት በአሲር ክልል ስር በሚገኘው የራቡአ ቀጠና ተጠርጣሪዎቹ የድንበር ደህንነት ህግን ጥሰው አደንዛዥ ዕፁን ለማስገባት ሲሞክሩ እጅ ከፍንጅ መያዛቸው ተገልጿል።
የሳዑዲ አረቢያ የሚመለከታቸው አካላት እንደገለጹት፣ በተጠርጣሪዎቹ ከተያዘው ዕፅ ጋር ወደሚመለከተው የፍትህ አካል እንዲተላለፉ ተደርጓል።
#fastmereja | የሳዑዲ አረቢያ የድንበር ጠባቂ ኃይል በአሲር ክልል 34 ኪሎ ግራም የሐሺሽ አደንዛዥ ዕፅ ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት ሲሞክሩ የነበሩ አራት ኢትዮጵያውያንን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ።
የሀገሪቱ የድንበር ጠባቂ የመሬት ላይ ጥበቃ አባላት በአሲር ክልል ስር በሚገኘው የራቡአ ቀጠና ተጠርጣሪዎቹ የድንበር ደህንነት ህግን ጥሰው አደንዛዥ ዕፁን ለማስገባት ሲሞክሩ እጅ ከፍንጅ መያዛቸው ተገልጿል።
የሳዑዲ አረቢያ የሚመለከታቸው አካላት እንደገለጹት፣ በተጠርጣሪዎቹ ከተያዘው ዕፅ ጋር ወደሚመለከተው የፍትህ አካል እንዲተላለፉ ተደርጓል።
Comments