3 days ago
ከታላቁ የለሚ ስሚንቶ እስከ ጎርጎራ በአማራ ክልል የተመዘገቡት ግዙፍ የኢንዱስትሪና የቱሪዝም እመርታዎች
**************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንዳብራሩት በለውጡ ዓመታት በአማራ ክልል ከፍተኛ የኢኮኖሚ መነቃቃትን የፈጠሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል።
ከእነዚህም መካከል በኢትዮጵያ ትልቁ የሆነው የለሚ ስሚንቶ ፋብሪካ በከፍተኛ የመንግሥት ድጋፍ ተገንብቶ ለአገልግሎት በቅቷል።
ከዚህም ባሻገር በባሕር ዳር፣ ደብረ ብርሃን እና አረርቲ አዳዲስ የኢንዱስትሪ ፓርኮች የተገነቡ ሲሆን፣ የጣና በለስ ስኳር ፋብሪካም በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።
በተለይም በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የሆነው ግዙፉ የሴራሚክ ፋብሪካ በደብረ ብርሃን መገንባቱ እንዲሁም በርካታ የዘይትና ሌሎች የግል ኢንዱስትሪዎች በስፋት መሠራታቸው ክልሉን ወደ አዲስ የኢንዱስትሪ ማዕከልነት እያሸጋገረው ይገኛል።
በቱሪዝሙ ዘርፍም ቢሆን ከዚህ ቀደም የነበረውን የመዳረሻ እና የማረፊያ ችግር በመፍታት ታሪካዊ ዐሻራዎች እየተቀመጡ መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል።
ለትውልድ የሚሻገረው የጎርጎራ ፕሮጀክት፣ በመፍረስ ላይ የነበረው የፋሲለደስ ቤተመንግሥት አስደናቂ ዕድሳት እና ከኤርፖርት እስከ ፒያሳ የተሠሩት የመሠረተ ልማት ሥራዎች የጎንደርን ውበት ይበልጥ አጉልተውታል።
ከፈረንሳይ መንግሥት ጋር በመተባበር የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን የማደስ ሰፊ ሥራ የተከናወነ ሲሆን፣ እጅግ ማራኪ የሆነው የሎጎ ሀይቅ ሪዞርትም የውጭ ዜጎችን ጭምር ለዓለም አቀፍ ስብሰባዎች እየሳበ ይገኛል።
ወደ ደባርቅ የሚወስዱ መንገዶችን ጨምሮ በቱሪዝም መሠረተ ልማት ላይ የተሠሩት እነዚህ የማይናቁ ሥራዎች የክልሉን ገጽታ በብዙ እጥፍ የቀየሩ ታላላቅ ስኬቶች ናቸው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopia #amhararegion #lemicement #tourismethiopia #industrialdevelopment
**************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንዳብራሩት በለውጡ ዓመታት በአማራ ክልል ከፍተኛ የኢኮኖሚ መነቃቃትን የፈጠሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል።
ከእነዚህም መካከል በኢትዮጵያ ትልቁ የሆነው የለሚ ስሚንቶ ፋብሪካ በከፍተኛ የመንግሥት ድጋፍ ተገንብቶ ለአገልግሎት በቅቷል።
ከዚህም ባሻገር በባሕር ዳር፣ ደብረ ብርሃን እና አረርቲ አዳዲስ የኢንዱስትሪ ፓርኮች የተገነቡ ሲሆን፣ የጣና በለስ ስኳር ፋብሪካም በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።
በተለይም በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የሆነው ግዙፉ የሴራሚክ ፋብሪካ በደብረ ብርሃን መገንባቱ እንዲሁም በርካታ የዘይትና ሌሎች የግል ኢንዱስትሪዎች በስፋት መሠራታቸው ክልሉን ወደ አዲስ የኢንዱስትሪ ማዕከልነት እያሸጋገረው ይገኛል።
በቱሪዝሙ ዘርፍም ቢሆን ከዚህ ቀደም የነበረውን የመዳረሻ እና የማረፊያ ችግር በመፍታት ታሪካዊ ዐሻራዎች እየተቀመጡ መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል።
ለትውልድ የሚሻገረው የጎርጎራ ፕሮጀክት፣ በመፍረስ ላይ የነበረው የፋሲለደስ ቤተመንግሥት አስደናቂ ዕድሳት እና ከኤርፖርት እስከ ፒያሳ የተሠሩት የመሠረተ ልማት ሥራዎች የጎንደርን ውበት ይበልጥ አጉልተውታል።
ከፈረንሳይ መንግሥት ጋር በመተባበር የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን የማደስ ሰፊ ሥራ የተከናወነ ሲሆን፣ እጅግ ማራኪ የሆነው የሎጎ ሀይቅ ሪዞርትም የውጭ ዜጎችን ጭምር ለዓለም አቀፍ ስብሰባዎች እየሳበ ይገኛል።
ወደ ደባርቅ የሚወስዱ መንገዶችን ጨምሮ በቱሪዝም መሠረተ ልማት ላይ የተሠሩት እነዚህ የማይናቁ ሥራዎች የክልሉን ገጽታ በብዙ እጥፍ የቀየሩ ታላላቅ ስኬቶች ናቸው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopia #amhararegion #lemicement #tourismethiopia #industrialdevelopment
8 days ago
u12a2u1275u12eeu1335u12eb u12e8u1271u122au12ddu121d u12d8u122du134fu1295 u12a5u1295u12f4u1275 u12a5u12e8u1240u12e8u1228u127d u1290u12cd? | u1308u1260u1273 u1208u1200u1308u122d u12a5u1293 u12a0u12f3u12f2u1236u1279 u12e8u1271u122au1235u1275 u1218u12f3u1228u123bu12ceu127d
#ethiopia #tourismethiopia #landoforigins ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፏን እንዴት እየቀየረች ነው? | ገበታ ለሀገር እና አዳዲሶቹ የቱሪስት መዳረሻዎች
#ethiopia #tourismethiopia #landoforigins
15 days ago
የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ አዲስ ዕይታና ዕድሎች
**********************
ኢትዮጵያ በታሪክ፣ በባህልና በተፈጥሮ ሀብት የታደለች፣ የበርካታ የዓለም ቅርሶች ባለቤት የሆነች ሀገር ናት። ይሁን እንጂ ይህን እምቅ አቅም ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ጥቅም ከመቀየር አንጻር ዘርፉ ለብዙ ዓመታት በርካታ ተግዳሮቶች ሲገጥሙት ቆይቷል።
በአሁኑ ወቅት ግን፣ የመደመር መንግሥት በሰጠው ልዩ ትኩረት የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ አሮጌውን አካሄድ በመቀየር፣ በአዳዲስ ስትራቴጂዎችና ሜጋ ፕሮጀክቶች የታገዘ አዲስ የዕድገት ምዕራፍ ላይ ይገኛል።
ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ቱሪዝም በአብዛኛው የታሪክና የሃይማኖት ቅርሶችን ብቻ ማዕከል ያደረገ ነበር። አሁን ላይ ይህ አካሄድ ተቀይሮ የቱሪስት መዳረሻዎች ብዝኃነትን እንዲያካትቱ ተደርጓል።
በአዲስ አበባ በ“ገበታ ለሸገር” ፕሮጀክት የተገነቡት እንደ አንድነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የወዳጅነት አደባባይ ያሉ ፕሮጀክቶች ዋና ከተማዋን የቱሪስት ማረፊያና መስኅብ አድርገዋታል።
አንዲሁም በገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች የተገነቡት የቱሪዝም መስኅቦች የሀገራችን የተፈጥሮ ውበት እና ሥነ-ምህዳር ለዓለም አቀፍ ጎብኝዎች በአዲስ መልክ እያስተዋወቁ ይገኛሉ።
በሌላ በኩል የቱሪዝም ዕድገት ያለ አስተማማኝ መሠረተ-ልማት ሊታሰብ የማይችል ሲሆን፣ በዚህ ረገድ የተሠሩ ሥራዎችም ለዘርፉ መነቃቃት ትልቅ አስተዋጽዖ አበርክተዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዳዲስ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎችን በመጨመር እና የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ-ልማቶችን በሀገር ውስጥ በማስፋፋት ተጓዦችን ከዓለም ዙሪያ በቀላሉ የማገናኘት ሚናውን እየተወጣ ይገኛል።
በተጨማሪም የኢ-ቪዛ አሰጣጥ መዘርጋት እና የኦንላይን የክፍያ ሥርዓቶች መዘመን የጎብኝዎችን እንግልት በመቀነስ የጉዞ ሂደቱን ቀላልና ፈጣን በማድረግ ሀገራችን ከዘርፉ ተጠቃሚ እንድትሆን እያስቻላት ነው።
የቱሪዝም ዕድገት ስትራቴጂ ትኩረት የነዋሪውን ማኅበረሰብ ሕይወት መለወጥ ላይ ነው። በአዳዲስ መዳረሻዎች አካባቢ የሚኖሩ ማኅበረሰቦች በዕደ-ጥበብ፣ በቅርስ ጥበቃ፣ በሎጅና በእንግዳ ተቀባይነት ዘርፍ ቀጥተኛ ተጠቃሚ እየሆኑ ነው። ይህም ቅርሶችና ተፈጥሯዊ ሀብቶችን በባለቤትነት ስሜት እንዲጠበቁ አድርጓቸዋል።
የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ ካለበት "የማይነካ እምቅ አቅም" ተሻግሮ ወደ ተግባራዊ የኢኮኖሚ ምሰሶነት እየተቀየረ ይገኛል። አዳዲስ መዳረሻዎችን ማልማት፣ ጥራትን ማሻሻል እና ዲጂታል ስትራቴጂዎችን በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ፣ ቱሪዝም ለሀገራችን የውጭ ምንዛሪ ግኝትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ቀዳሚው አንቀሳቃሽ ኃይል መሆኑ አይቀሬ ነው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopianbroadcastingcorporation #tourismethiopia #landoforigins #visitethiopia
**********************
ኢትዮጵያ በታሪክ፣ በባህልና በተፈጥሮ ሀብት የታደለች፣ የበርካታ የዓለም ቅርሶች ባለቤት የሆነች ሀገር ናት። ይሁን እንጂ ይህን እምቅ አቅም ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ጥቅም ከመቀየር አንጻር ዘርፉ ለብዙ ዓመታት በርካታ ተግዳሮቶች ሲገጥሙት ቆይቷል።
በአሁኑ ወቅት ግን፣ የመደመር መንግሥት በሰጠው ልዩ ትኩረት የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ አሮጌውን አካሄድ በመቀየር፣ በአዳዲስ ስትራቴጂዎችና ሜጋ ፕሮጀክቶች የታገዘ አዲስ የዕድገት ምዕራፍ ላይ ይገኛል።
ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ቱሪዝም በአብዛኛው የታሪክና የሃይማኖት ቅርሶችን ብቻ ማዕከል ያደረገ ነበር። አሁን ላይ ይህ አካሄድ ተቀይሮ የቱሪስት መዳረሻዎች ብዝኃነትን እንዲያካትቱ ተደርጓል።
በአዲስ አበባ በ“ገበታ ለሸገር” ፕሮጀክት የተገነቡት እንደ አንድነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የወዳጅነት አደባባይ ያሉ ፕሮጀክቶች ዋና ከተማዋን የቱሪስት ማረፊያና መስኅብ አድርገዋታል።
አንዲሁም በገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች የተገነቡት የቱሪዝም መስኅቦች የሀገራችን የተፈጥሮ ውበት እና ሥነ-ምህዳር ለዓለም አቀፍ ጎብኝዎች በአዲስ መልክ እያስተዋወቁ ይገኛሉ።
በሌላ በኩል የቱሪዝም ዕድገት ያለ አስተማማኝ መሠረተ-ልማት ሊታሰብ የማይችል ሲሆን፣ በዚህ ረገድ የተሠሩ ሥራዎችም ለዘርፉ መነቃቃት ትልቅ አስተዋጽዖ አበርክተዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዳዲስ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎችን በመጨመር እና የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ-ልማቶችን በሀገር ውስጥ በማስፋፋት ተጓዦችን ከዓለም ዙሪያ በቀላሉ የማገናኘት ሚናውን እየተወጣ ይገኛል።
በተጨማሪም የኢ-ቪዛ አሰጣጥ መዘርጋት እና የኦንላይን የክፍያ ሥርዓቶች መዘመን የጎብኝዎችን እንግልት በመቀነስ የጉዞ ሂደቱን ቀላልና ፈጣን በማድረግ ሀገራችን ከዘርፉ ተጠቃሚ እንድትሆን እያስቻላት ነው።
የቱሪዝም ዕድገት ስትራቴጂ ትኩረት የነዋሪውን ማኅበረሰብ ሕይወት መለወጥ ላይ ነው። በአዳዲስ መዳረሻዎች አካባቢ የሚኖሩ ማኅበረሰቦች በዕደ-ጥበብ፣ በቅርስ ጥበቃ፣ በሎጅና በእንግዳ ተቀባይነት ዘርፍ ቀጥተኛ ተጠቃሚ እየሆኑ ነው። ይህም ቅርሶችና ተፈጥሯዊ ሀብቶችን በባለቤትነት ስሜት እንዲጠበቁ አድርጓቸዋል።
የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ ካለበት "የማይነካ እምቅ አቅም" ተሻግሮ ወደ ተግባራዊ የኢኮኖሚ ምሰሶነት እየተቀየረ ይገኛል። አዳዲስ መዳረሻዎችን ማልማት፣ ጥራትን ማሻሻል እና ዲጂታል ስትራቴጂዎችን በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ፣ ቱሪዝም ለሀገራችን የውጭ ምንዛሪ ግኝትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ቀዳሚው አንቀሳቃሽ ኃይል መሆኑ አይቀሬ ነው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopianbroadcastingcorporation #tourismethiopia #landoforigins #visitethiopia
24 days ago
ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ከሰኞ ጀምሮ ለአገልግሎት ክፍት ይሆናል
#ethiopia | እጅግ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ከፊታችን ሰኞ ሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በይፋ ለጎብኚዎች እና ለተገልጋዮች ክፍት እንደሚሆን ተገልጿል።
ሪዞርቱ ከደሴ ከተማ በ30 ኪሎ ሜትር ርቀት የሚገኝ ሲሆን፣ በ“ገበታ ለሀገር” ፕሮጀክት ማዕቀፍ የተገነባ ዘመናዊ የቱሪዝም መዳረሻ ነው። በተፈጥሯዊ ውበቱና በመዝናኛ አገልግሎቶቹ በቅርብም በሩቅም የብዙዎችን ትኩረት ሲስብ ቆይቷል።
ከሰኞ ጀምሮ ሪዞርቱ በይፋ ስራ በመጀመሩ፣ የአገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎች የተፈጥሮ ውበቱን በመጎብኘት የተለያዩ የመዝናኛና የመስተንግዶ አገልግሎቶችን ማግኘት ይችላሉ።
በሪዞርቱ ዙሪያ ያሉ አገልግሎቶችና መስህቦችን በተመለከተ ተጨማሪ መረጃዎች በቀጣይ እንደሚቀርቡም ተገልጿል።
የወሎ አዲሱ የቱሪዝም ፈርጥ - ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት!
በ13.3 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው እና የወሎን ተፈጥሮ ከዘመናዊ የቱሪዝም አገልግሎት ጋር ያሰናኘው ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት፤ ኢትዮጵያ በቱሪዝም ዘርፍ ያላትን እምቅ አቅም የሚያሳይ አዲስ መዳረሻ ሆኗል።
ሪዞርቱ ምን ይዟል?
✅ ዓለም አቀፍ ደረጃ:
ዘመናዊ ምግብ ቤቶች እና መኝታ ክፍሎች።
✅ መዝናኛ:
የመዋኛ ገንዳዎች እና ለዓይን የሚማርኩ አረንጓዴ ስፍራዎች።
✅ መሰረተ ልማት:
የውስጥ ለውስጥ አስፋልት መንገዶች እና የሄሊኮፕተር ማረፊያ (Helipad)።
✅ ተፈጥሮ:
በተለያዩ የፍራፍሬ ዞኖች እና በደን የተከበበ መሆኑ ልዩ ትውስታን ይፈጥራል።
ይህ ፕሮጀክት የወሎን ህዝብ ባህላዊ እና ተፈጥሯዊ እሴቶች ለዓለም በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ ሚና ይጫወታል።
#logolakeresort #wollo #tourismethiopia #dineforgenerations #gebetaletewled #pmabiy #ethiopia #nature #resort #getutemesgen #ጌጡተመስገን #getutemesgen #ethiopia #logohaykresort #tourism #ገበታለሀገር
#ethiopia | እጅግ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ከፊታችን ሰኞ ሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በይፋ ለጎብኚዎች እና ለተገልጋዮች ክፍት እንደሚሆን ተገልጿል።
ሪዞርቱ ከደሴ ከተማ በ30 ኪሎ ሜትር ርቀት የሚገኝ ሲሆን፣ በ“ገበታ ለሀገር” ፕሮጀክት ማዕቀፍ የተገነባ ዘመናዊ የቱሪዝም መዳረሻ ነው። በተፈጥሯዊ ውበቱና በመዝናኛ አገልግሎቶቹ በቅርብም በሩቅም የብዙዎችን ትኩረት ሲስብ ቆይቷል።
ከሰኞ ጀምሮ ሪዞርቱ በይፋ ስራ በመጀመሩ፣ የአገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎች የተፈጥሮ ውበቱን በመጎብኘት የተለያዩ የመዝናኛና የመስተንግዶ አገልግሎቶችን ማግኘት ይችላሉ።
በሪዞርቱ ዙሪያ ያሉ አገልግሎቶችና መስህቦችን በተመለከተ ተጨማሪ መረጃዎች በቀጣይ እንደሚቀርቡም ተገልጿል።
የወሎ አዲሱ የቱሪዝም ፈርጥ - ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት!
በ13.3 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው እና የወሎን ተፈጥሮ ከዘመናዊ የቱሪዝም አገልግሎት ጋር ያሰናኘው ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት፤ ኢትዮጵያ በቱሪዝም ዘርፍ ያላትን እምቅ አቅም የሚያሳይ አዲስ መዳረሻ ሆኗል።
ሪዞርቱ ምን ይዟል?
✅ ዓለም አቀፍ ደረጃ:
ዘመናዊ ምግብ ቤቶች እና መኝታ ክፍሎች።
✅ መዝናኛ:
የመዋኛ ገንዳዎች እና ለዓይን የሚማርኩ አረንጓዴ ስፍራዎች።
✅ መሰረተ ልማት:
የውስጥ ለውስጥ አስፋልት መንገዶች እና የሄሊኮፕተር ማረፊያ (Helipad)።
✅ ተፈጥሮ:
በተለያዩ የፍራፍሬ ዞኖች እና በደን የተከበበ መሆኑ ልዩ ትውስታን ይፈጥራል።
ይህ ፕሮጀክት የወሎን ህዝብ ባህላዊ እና ተፈጥሯዊ እሴቶች ለዓለም በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ ሚና ይጫወታል።
#logolakeresort #wollo #tourismethiopia #dineforgenerations #gebetaletewled #pmabiy #ethiopia #nature #resort #getutemesgen #ጌጡተመስገን #getutemesgen #ethiopia #logohaykresort #tourism #ገበታለሀገር
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሐይቅ ላይ የተገነባ ልዩ ተንሳፋፊ ሬስቶራንት ያለው የአርባምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት ጎብኚዎች እንዲጎበኙት ጥሪ አቀረቡ
************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመዲናችን ባሻገር የኮንፈረንስ ቱሪዝምን በማስፋፋት ኢትዮጵያን የዓለም አቀፍ መድረኮች ማዕከል የማድረግ ርዕይን የሚያጠናክረውን ዘመናዊውን "የአርባምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት" መርቀዋል።
የ‘ገበታ ለትውልድ’ መርሃ-ግብር ታላቅ ስኬት የሆነው ይህ ሪዞርት፣ ከ1 ሺህ 300 በላይ ሰዎችን የሚያስተናግድ ሰፊ የስብሰባ አዳራሽ እና በሐይቅ ላይ የተገነባ ልዩ ተንሳፋፊ ሬስቶራንትን በውስጡ ያካተተ ነው።
ፕሮጀክቱ ሀገራዊ የኮንፈረንስ ቱሪዝም አቅምን ከማሳደጉም ባሻገር ለአካባቢው ማኅበረሰብ ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠሩን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፤ መላው የሀገራችን ሕዝብ፣ የዳያስፖራው አባላት እና የዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ይህንን አዲስ የሀገራችንን ዕንቁ ስፍራ በመጎብኘትና በመጠቀም የተከፈተውን አዲስ የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ምዕራፍ በጋራ እንዲቋደሱ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
#ethiopia #arbaminch #pmabiyahmed #tourismethiopia #visitethiopia #conferenceresort
************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመዲናችን ባሻገር የኮንፈረንስ ቱሪዝምን በማስፋፋት ኢትዮጵያን የዓለም አቀፍ መድረኮች ማዕከል የማድረግ ርዕይን የሚያጠናክረውን ዘመናዊውን "የአርባምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት" መርቀዋል።
የ‘ገበታ ለትውልድ’ መርሃ-ግብር ታላቅ ስኬት የሆነው ይህ ሪዞርት፣ ከ1 ሺህ 300 በላይ ሰዎችን የሚያስተናግድ ሰፊ የስብሰባ አዳራሽ እና በሐይቅ ላይ የተገነባ ልዩ ተንሳፋፊ ሬስቶራንትን በውስጡ ያካተተ ነው።
ፕሮጀክቱ ሀገራዊ የኮንፈረንስ ቱሪዝም አቅምን ከማሳደጉም ባሻገር ለአካባቢው ማኅበረሰብ ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠሩን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፤ መላው የሀገራችን ሕዝብ፣ የዳያስፖራው አባላት እና የዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ይህንን አዲስ የሀገራችንን ዕንቁ ስፍራ በመጎብኘትና በመጠቀም የተከፈተውን አዲስ የቱሪዝምና የኮንፈረንስ ምዕራፍ በጋራ እንዲቋደሱ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
#ethiopia #arbaminch #pmabiyahmed #tourismethiopia #visitethiopia #conferenceresort
1 month ago
u12e8u12f5u122eu1295 u1275u122du12d2u1275
u12a8u1308u1260u1273 u1208u1275u12cdu120du12f5 u12e8u12a0u122du1263u121du1295u132d u12aeu1295u1348u1228u1295u1235 u122au12deu122du1275 #ebc #tourismethiopia #ethiopiamegaprojects #beautifulethiopia #u12a0u122du1263u121du1295u132d ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
የድሮን ትርዒት
ከገበታ ለትውልድ የአርባምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት #ebc #tourismethiopia #ethiopiamegaprojects #beautifulethiopia #አርባምንጭ
1 month ago
የ40 ሀገራት አምባሳደሮች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች ላሊበላ ከተማ ገቡ
#ethiopia | ከአርባ በላይ ሀገራት እና ከአሥር በላይ ዓለም አቀፍ ተቋማት የተወከሉ ዲፕሎማቶች ታሪካዊቷን የላሊበላ ከተማና ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ለመጎብኘት ላሊበላ ገቡ።
የዲፕሎማቲክ ልዑካን ቡድኑ ላሊበላ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ ደማቅ ባህላዊ አቀባበል ተደርጎለታል፡፡
ጉዞው በቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ስለሺ ግርማ እና በኢትዮጵያ የዩኔስኮ ላይያዘን ኦፊስ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሪታ ቢሱናት የተመራ ነው።
ይህ ከፍተኛ የዲፕሎማቶች ልዑክ በቆይታው ከ800 ዓመታት በላይ ዕድሜ ያስቆጠሩትን፣ የሕንጻ ጥበብ እና የኢንጂነሪንግ ጥበብ ማስተርፒስ እንዲሁም የሃይማኖትና የታሪክ ሕያው ምስክር የሆኑትን የዓለም ቅርስ የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ይጎበኛል።
የዲፕሎማቶቹ ጉብኝት የተከናወነው ላሊበላ በዓለም አቀፍ ደረጃ በስፋት በተጓዙ አካላት በተደረገ ጥናት እና በዩሮኒውስ በተዘገበው መረጃ መሠረት፣ በዓለም ካሉ የዩኔስኮ የዓለም ቅርስ መዳረሻዎች መካከል ቀዳሚ ከሆኑ አምስት ምርጥ ስፍራዎች አንዷ ተብላ በተመረጠችበት ወቅት መሆኑ ለጉብኝቱ ልዩ ትርጉም ሰጥቶታል።
የቱሪዝም ሚኒስቴር እንዳመለከተው፣ ይህ ዓለም አቀፍ ዕውቅና የኢትዮጵያን የጥንታዊ ሥልጣኔ እና የባህል ውርስ ማረጋገጫ ከመሆኑም በላይ ሀገራችን በባህላዊ ቱሪዝም ያላትን ቀዳሚ መዳረሻነት በይበልጥ ያጠናክራል።
የልዑካን ቡድኑ በቆይታው የቅርሶቹን ድንቅ የታሪክ እና የጥበብ ሥራዎች ከመመልከት ባለፈ፣ ከቤተክርስቲያን አባቶች እና ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር የውይይት መድረክ ይኖረዋል።
በተጨማሪም ከ"ዘላቂ ላሊበላ ፕሮጀክት" ተወካዮች እንዲሁም ከፈረንሳይ ኤምባሲ ጋር በመሆን ቅርሶቹን ከተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ለመጠበቅ እንዲሁም በዘላቂ ልማት ዙሪያ ሰፊ ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።
በአሁኑ ወቅት መንግሥት የላሊበላን ቅርሶች ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ የጥበቃ ሥራዎችን ከማጠናከር ባለፈ የቱሪዝም መሠረተ ልማቶችን የማሻሻል ሥራ በስፋት እያከናወነ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተደጋጋሚ ጊዜ ቱሪዝም ጎብኝዎችን መሳብ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ማንነት ማሳያ፣ ቅርሶቿን መጠበቂያና በባህልና በተፈጥሮ ጸጋዎቿ አማካኝነት ብልጽግናን መገንቢያ መሆኑን ማሳሰባቸው ይታወሳል።
መንግሥት ዘርፉን ቁልፍ የኢኮኖሚ ዕድገት ምንጭ አድርጎ በወሰደው መሠረት፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ አዳዲስ የቱሪዝም ኮሪደሮችና መዳረሻዎች በስፋት እየለሙ ይገኛሉ።
በዚህም ሳቢያ በዘንድሮው ዓመት ብቻ እስካሁን 1.4 ሚሊዮን ያህል ዓለም አቀፍ ጎብኝዎች ወደ ኢትዮጵያ መምጣታቸውንና ይህም ለዘርፉ ማደግ ትልቅ ማሳያ መሆኑ ተገልጿል።
ይህ የዲፕሎማቶች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት ኃላፊዎች ታሪካዊ ጉብኝት የላሊበላን ቅርሶች በዓለም አቀፍ ደረጃ በበለጠ ለማስተዋወቅ፣ የኢትዮጵያን ገጽታ ለመገንባት እና የቱሪዝም ዘርፉን ይበልጥ ለማነቃቃት ያለው ፋይዳ የጎላ መሆኑ ተጠቁሟል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia #ebc #lalibela #unesco #tourismethiopia #landoforigins #diplomatictour #heritageconservation
#ethiopia | ከአርባ በላይ ሀገራት እና ከአሥር በላይ ዓለም አቀፍ ተቋማት የተወከሉ ዲፕሎማቶች ታሪካዊቷን የላሊበላ ከተማና ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ለመጎብኘት ላሊበላ ገቡ።
የዲፕሎማቲክ ልዑካን ቡድኑ ላሊበላ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ ደማቅ ባህላዊ አቀባበል ተደርጎለታል፡፡
ጉዞው በቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ስለሺ ግርማ እና በኢትዮጵያ የዩኔስኮ ላይያዘን ኦፊስ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሪታ ቢሱናት የተመራ ነው።
ይህ ከፍተኛ የዲፕሎማቶች ልዑክ በቆይታው ከ800 ዓመታት በላይ ዕድሜ ያስቆጠሩትን፣ የሕንጻ ጥበብ እና የኢንጂነሪንግ ጥበብ ማስተርፒስ እንዲሁም የሃይማኖትና የታሪክ ሕያው ምስክር የሆኑትን የዓለም ቅርስ የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ይጎበኛል።
የዲፕሎማቶቹ ጉብኝት የተከናወነው ላሊበላ በዓለም አቀፍ ደረጃ በስፋት በተጓዙ አካላት በተደረገ ጥናት እና በዩሮኒውስ በተዘገበው መረጃ መሠረት፣ በዓለም ካሉ የዩኔስኮ የዓለም ቅርስ መዳረሻዎች መካከል ቀዳሚ ከሆኑ አምስት ምርጥ ስፍራዎች አንዷ ተብላ በተመረጠችበት ወቅት መሆኑ ለጉብኝቱ ልዩ ትርጉም ሰጥቶታል።
የቱሪዝም ሚኒስቴር እንዳመለከተው፣ ይህ ዓለም አቀፍ ዕውቅና የኢትዮጵያን የጥንታዊ ሥልጣኔ እና የባህል ውርስ ማረጋገጫ ከመሆኑም በላይ ሀገራችን በባህላዊ ቱሪዝም ያላትን ቀዳሚ መዳረሻነት በይበልጥ ያጠናክራል።
የልዑካን ቡድኑ በቆይታው የቅርሶቹን ድንቅ የታሪክ እና የጥበብ ሥራዎች ከመመልከት ባለፈ፣ ከቤተክርስቲያን አባቶች እና ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር የውይይት መድረክ ይኖረዋል።
በተጨማሪም ከ"ዘላቂ ላሊበላ ፕሮጀክት" ተወካዮች እንዲሁም ከፈረንሳይ ኤምባሲ ጋር በመሆን ቅርሶቹን ከተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ለመጠበቅ እንዲሁም በዘላቂ ልማት ዙሪያ ሰፊ ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።
በአሁኑ ወቅት መንግሥት የላሊበላን ቅርሶች ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ የጥበቃ ሥራዎችን ከማጠናከር ባለፈ የቱሪዝም መሠረተ ልማቶችን የማሻሻል ሥራ በስፋት እያከናወነ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተደጋጋሚ ጊዜ ቱሪዝም ጎብኝዎችን መሳብ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ማንነት ማሳያ፣ ቅርሶቿን መጠበቂያና በባህልና በተፈጥሮ ጸጋዎቿ አማካኝነት ብልጽግናን መገንቢያ መሆኑን ማሳሰባቸው ይታወሳል።
መንግሥት ዘርፉን ቁልፍ የኢኮኖሚ ዕድገት ምንጭ አድርጎ በወሰደው መሠረት፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ አዳዲስ የቱሪዝም ኮሪደሮችና መዳረሻዎች በስፋት እየለሙ ይገኛሉ።
በዚህም ሳቢያ በዘንድሮው ዓመት ብቻ እስካሁን 1.4 ሚሊዮን ያህል ዓለም አቀፍ ጎብኝዎች ወደ ኢትዮጵያ መምጣታቸውንና ይህም ለዘርፉ ማደግ ትልቅ ማሳያ መሆኑ ተገልጿል።
ይህ የዲፕሎማቶች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት ኃላፊዎች ታሪካዊ ጉብኝት የላሊበላን ቅርሶች በዓለም አቀፍ ደረጃ በበለጠ ለማስተዋወቅ፣ የኢትዮጵያን ገጽታ ለመገንባት እና የቱሪዝም ዘርፉን ይበልጥ ለማነቃቃት ያለው ፋይዳ የጎላ መሆኑ ተጠቁሟል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia #ebc #lalibela #unesco #tourismethiopia #landoforigins #diplomatictour #heritageconservation
1 month ago
የተሳኩ የኢትዮጵያ ሕልሞች
#tourismethiopia #balezone #pmabiyahmed #balemountains #sofomarcave #tourismethiopia
Sponsored by
Surafel
1 month ago
በልማት ሥራዎች 'ቅርሶች ይጠፋሉ' የሚለው ወቀሳ የፖለቲካ ፍጆታ እንጂ እውነተኛ የሕዝብ ስጋት አይደለም - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
******************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መንግሥት እያከናወናቸው ባሉ ሰፊ የልማትና የእድሳት ሥራዎች “ቅርሶች ይጠፋሉ” በሚል የሚነሳው ወቀሳ የፖለቲካ ፍጆታ እንጂ እውነተኛ የሕዝብ ስጋት አለመሆኑን ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ መንግሥት የሀገራችንን ቅርሶች በከፍተኛ ጥራትና ጥንቃቄ የሚጠብቅ፣ የሚያስውብ እና ለቀጣዩ ትውልድ የሚያሻግር እንጂ የሚያፈርስ አለመሆኑን በተግባር የተሠሩ ሥራዎችን በማንሳት አብራርተዋል።
በፖለቲካ ልምምድ ድክመት ምክንያት የሚሰሩ ሥራዎችን ሁሉ የመቃወም አዝማሚያ መኖሩን የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በጎንደር የፋሲል ግንብ ላይ የነበረውን እውነታ በምሳሌነት አንስተዋል።
የፋሲል ግንብ ለመቶ ዓመታት ያህል ምንም ዓይነት እድሳት ሳይደረግለት በቁሙ እየፈረሰ እንደነበር አስታውሰው፣ መንግሥት ይህንን ታሪካዊ ቅርስ ለማዳን ሥራ ሲጀምር የተሳሳተ ቅስቀሳ ቢፈጠርም፣ ዛሬ ላይ በተሠራው የእድሳት ሥራ ግን ሕዝቡን ጨምሮ ማንም ኢትዮጵያዊና የውጭ ዜጋ የሚኮራበት ማራኪ ቅርስ መሆን መቻሉን ተናግረዋል።
በተመሳሳይ በላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፣ በጅማ የአባ ጅፋር ቤተመንግሥት፣ በሐረር ጀጎል ግንብ እና በሶፍ ዑመር ዋሻ የተከናወኑት የጥገና እና የመሠረተ ልማት ሥራዎች ቅርሶቹን በከፍተኛ ጥንቃቄ የጠበቁ መሆናቸውን የአካባቢው ነዋሪዎችና አባቶች ጭምር የሚመሰክሩት ሀቅ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከዚህ ቀደም እንክብካቤ ተነፍጓቸው ፈርሰውና ተበላሽተው የነበሩት እንደ ብሔራዊ ቤተመንግሥት ያሉ ስፍራዎችም፣ ከፍተኛ ጥንቃቄ በተሞላበት አግባብ ታድሰው ዛሬ ላይ በሚሊዮኖች የሚጎበኙ ውብ የቱሪዝም መዳረሻዎች መሆናቸውን ለአብነት አንስተዋል።
መንግሥት ያሉትን ታሪካዊ ቅርሶች ከማስዋብና ከመጠበቅ ባለፈ፣ ባለፉት ዓመታት በተለያዩ ዘመናት ከሀገር የተዘረፉና የጠፉ ከ35 በላይ ታሪካዊ ቅርሶችን ማስመለስ መቻሉንም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስረድተዋል።
አሁንም በድርድር ሂደት ላይ ያሉ በርካታ ቅርሶች እንዳሉ ጠቁመው፣ እጅግ ማራኪ የሆነው የግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ ዙፋን (የመቀመጫ ወንበር) በቅርቡ ወደ ሀገር ቤት እንደሚመለስም ተናግረዋል።
መንግሥት የሁሉንም አካባቢዎችና ሃይማኖቶች ታሪክ ባካተተ እንዲሁም የኢትዮጵያን አጠቃላይ ገጽታ በሚያሳይ መልኩ የቅርሶችን ትክክለኛነትና ዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃ በጠበቀ አግባብ እየሠራ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በስሜትና በፖለቲካ ፍላጎት ብቻ የሚነሱ መሠረተ ቢስ ትችቶች መንግሥትን ወደ ኋላ እንደማይጎትቱት የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ መንግሥት የኢትዮጵያን እምቅ የቱሪዝም አቅም ለዓለም አውጥቶ በማሳየት የቅርስ ጠባቂነትና አሻጋሪነት ታሪካዊ ኃላፊነቱን መወጣቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
#heritageconservation #tourismethiopia #pmabiyahmed #preservinghistory #ethiopianbroadcastingcorporation
******************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መንግሥት እያከናወናቸው ባሉ ሰፊ የልማትና የእድሳት ሥራዎች “ቅርሶች ይጠፋሉ” በሚል የሚነሳው ወቀሳ የፖለቲካ ፍጆታ እንጂ እውነተኛ የሕዝብ ስጋት አለመሆኑን ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ መንግሥት የሀገራችንን ቅርሶች በከፍተኛ ጥራትና ጥንቃቄ የሚጠብቅ፣ የሚያስውብ እና ለቀጣዩ ትውልድ የሚያሻግር እንጂ የሚያፈርስ አለመሆኑን በተግባር የተሠሩ ሥራዎችን በማንሳት አብራርተዋል።
በፖለቲካ ልምምድ ድክመት ምክንያት የሚሰሩ ሥራዎችን ሁሉ የመቃወም አዝማሚያ መኖሩን የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በጎንደር የፋሲል ግንብ ላይ የነበረውን እውነታ በምሳሌነት አንስተዋል።
የፋሲል ግንብ ለመቶ ዓመታት ያህል ምንም ዓይነት እድሳት ሳይደረግለት በቁሙ እየፈረሰ እንደነበር አስታውሰው፣ መንግሥት ይህንን ታሪካዊ ቅርስ ለማዳን ሥራ ሲጀምር የተሳሳተ ቅስቀሳ ቢፈጠርም፣ ዛሬ ላይ በተሠራው የእድሳት ሥራ ግን ሕዝቡን ጨምሮ ማንም ኢትዮጵያዊና የውጭ ዜጋ የሚኮራበት ማራኪ ቅርስ መሆን መቻሉን ተናግረዋል።
በተመሳሳይ በላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፣ በጅማ የአባ ጅፋር ቤተመንግሥት፣ በሐረር ጀጎል ግንብ እና በሶፍ ዑመር ዋሻ የተከናወኑት የጥገና እና የመሠረተ ልማት ሥራዎች ቅርሶቹን በከፍተኛ ጥንቃቄ የጠበቁ መሆናቸውን የአካባቢው ነዋሪዎችና አባቶች ጭምር የሚመሰክሩት ሀቅ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከዚህ ቀደም እንክብካቤ ተነፍጓቸው ፈርሰውና ተበላሽተው የነበሩት እንደ ብሔራዊ ቤተመንግሥት ያሉ ስፍራዎችም፣ ከፍተኛ ጥንቃቄ በተሞላበት አግባብ ታድሰው ዛሬ ላይ በሚሊዮኖች የሚጎበኙ ውብ የቱሪዝም መዳረሻዎች መሆናቸውን ለአብነት አንስተዋል።
መንግሥት ያሉትን ታሪካዊ ቅርሶች ከማስዋብና ከመጠበቅ ባለፈ፣ ባለፉት ዓመታት በተለያዩ ዘመናት ከሀገር የተዘረፉና የጠፉ ከ35 በላይ ታሪካዊ ቅርሶችን ማስመለስ መቻሉንም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስረድተዋል።
አሁንም በድርድር ሂደት ላይ ያሉ በርካታ ቅርሶች እንዳሉ ጠቁመው፣ እጅግ ማራኪ የሆነው የግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ ዙፋን (የመቀመጫ ወንበር) በቅርቡ ወደ ሀገር ቤት እንደሚመለስም ተናግረዋል።
መንግሥት የሁሉንም አካባቢዎችና ሃይማኖቶች ታሪክ ባካተተ እንዲሁም የኢትዮጵያን አጠቃላይ ገጽታ በሚያሳይ መልኩ የቅርሶችን ትክክለኛነትና ዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃ በጠበቀ አግባብ እየሠራ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በስሜትና በፖለቲካ ፍላጎት ብቻ የሚነሱ መሠረተ ቢስ ትችቶች መንግሥትን ወደ ኋላ እንደማይጎትቱት የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ መንግሥት የኢትዮጵያን እምቅ የቱሪዝም አቅም ለዓለም አውጥቶ በማሳየት የቅርስ ጠባቂነትና አሻጋሪነት ታሪካዊ ኃላፊነቱን መወጣቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
#heritageconservation #tourismethiopia #pmabiyahmed #preservinghistory #ethiopianbroadcastingcorporation
1 month ago
ኢትዮጵያን የማስተዋወቅ 4 ቁልፍ ስልቶች
***************
✅የዲያስፖራ ጥሪ፦ የሁለተኛው ትውልድ ዲያስፖራዎች መጥተው የኢትዮጵያን እውነተኛ ገጽታ እንዲረዱ ማድረግ።
✅ዓለም አቀፍ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፦ ከተለያዩ ሀገራት መጥተው ኢትዮጵያን በመጎብኘትና በማሳየት በሚሊዮን ለሚቆጠር ሕዝብ መልካም ገጽታን ማስተዋወቅ።
✅የኮንፈረንስ ቱሪዝም ፦ ሰፋፊ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎችን በሀገር ውስጥ በማዘጋጀት ሰርቪሱን ማስተዋወቅና ጎብኚዎችን ደጋግሞ መሳብ።
✅የመሪዎች ጉብኝት፦ ወደ ሀገር የሚመጡ የውጭ መሪዎችና አብረዋቸው የሚመጡ የሚዲያ አካላት ከቢሮ ስብሰባ ባለፈ የኢትዮጵያን አዳዲስ መዳረሻዎች እንዲያዩ ማድረግ።
#visitethiopia #tourismethiopia #pmabiyahmed #landoforigins #ethiopianbroadcastingcorporation
***************
✅የዲያስፖራ ጥሪ፦ የሁለተኛው ትውልድ ዲያስፖራዎች መጥተው የኢትዮጵያን እውነተኛ ገጽታ እንዲረዱ ማድረግ።
✅ዓለም አቀፍ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፦ ከተለያዩ ሀገራት መጥተው ኢትዮጵያን በመጎብኘትና በማሳየት በሚሊዮን ለሚቆጠር ሕዝብ መልካም ገጽታን ማስተዋወቅ።
✅የኮንፈረንስ ቱሪዝም ፦ ሰፋፊ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎችን በሀገር ውስጥ በማዘጋጀት ሰርቪሱን ማስተዋወቅና ጎብኚዎችን ደጋግሞ መሳብ።
✅የመሪዎች ጉብኝት፦ ወደ ሀገር የሚመጡ የውጭ መሪዎችና አብረዋቸው የሚመጡ የሚዲያ አካላት ከቢሮ ስብሰባ ባለፈ የኢትዮጵያን አዳዲስ መዳረሻዎች እንዲያዩ ማድረግ።
#visitethiopia #tourismethiopia #pmabiyahmed #landoforigins #ethiopianbroadcastingcorporation
1 month ago
ቱሪዝምን ሕይወት የዘራበት የመደመር መንግሥት
***********
ኢትዮጵያ የበርካታ ታሪካዊ ተፈጥሯዊና የባህል ቅርሶች ማህደር ብትሆንም ይህን ዕምቅ ፀጋ ወደ ሀገር ከፍታና ብልፅግና ቀይራ መጠቀም ሳትችል ዘመናት ተቆጥረዋል።
ሆኖም በምናብ ከፍታ ነገን አሻግሮ በመመልከት ቃልን በተግባር የመኖር ባህልን በተቋማዊ መሰረት የገነባው የመደመር እሳቤ የቱሪዝም ዘርፉን የሀገር ምሰሶ አድርጎ ተነስቷል።
የመደመር ፍልስፍና ዳራው ትናንትን ከነክብሩ ጠብቆ፣ የተበታተኑ ሀገራዊ ፀጋዎቻችንን በማሰባሰብና እሴትን በመጨመር ወደ ላቀ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጥቅም መቀየር ነው።
በዚህም መነሻነት የመደመር መንግሥት አዲስ አበባን ከጥልቅ ጉስቁልና በማውጣት ወደ ሚመጥናት የውበት ከፍታ እያሸጋገራት ይገኛል።
ይህ ጥረት በዋና ከተማዋ ብቻ ሳይገደብ ላለፉት አምስት ዓመታት በመላ የሀገራችን ክፍሎች የተመዘገቡት ስኬቶች የዚህን ዕሳቤ ጥልቀትና ተግባራዊነት ቁልጭ አድርገው የሚያሳዩ ናቸው።
ሀገራችን ለዘመናት ተዘንግተውና አቧራ ጠጥተው የቆዩ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ ቅርሶቿን ደረጃቸውን በጠበቀና በጥናት ላይ በመመስረት በማደስና በመንከባከብ በቱሪዝም ዘርፍ አስደናቂ ውጤት አስመዝግባለች።
ታሪካዊ ገፅታቸውን ሳያጡ በዘመናዊ አቀራረብ ሕይወት ዘርተው ከተነሱት ሜጋ ፕሮጀክቶች መካከል ብሔራዊ ቤተ መንግሥትን፣ የሐረር ጀጎል ግንብን፣ የጎንደር አብያተ መንግሥታትን፣ የጅማ አባ ጅፋር ቤተ መንግሥትንና የሶፍ ኡመር ዋሻን ጨምሮ በርካታ ድንቅ ቅርሶች ይገኙበታል።
የእነዚህ የቅርስ ዕድሳት ፕሮጀክቶች ፋይዳ የቱሪዝም መዳረሻዎችን ከማስፋትና ማራኪ ከማድረግም በእጅጉ የዘለለ ነው።
በዘርፉ አዲስ መነቃቃትን በመፍጠር የግሉ ዘርፍ በኢንቨስትመንት በስፋት እንዲሳተፍና ተወዳዳሪነቱ እንዲጠናከር ምቹ መደላድል ፈጥረዋል።
አዳዲስ የቱሪዝም ማዕከላት መበራከታቸው የጎብኚዎችን የቆይታ ጊዜ ከማራዘሙም ባሻገር ከዘርፉ የሚገኘው የውጭ ምንዛሬና አጠቃላይ ገቢ በከፍተኛ ደረጃ እንዲያድግ አስችሏል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነትና የቅርብ ክትትል የተተገበሩት እነዚህ የቅርስ ልማትና ጥበቃ ስራዎች የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ጎብኚዎችን ቁጥር በከፍተኛ መጠን እንዲጨምር አድርገዋል።
መንግሥት በቅርስ ጥበቃና ልማት ላይ የፈጠረው ይህ አዲስ ዕይታ የሀገራችንን የካበተ የታሪክ ሃብት በአግባቡ ጠብቆ ወደ ትልቅ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም መቀየር እንደሚቻል አረጋግጧል።
በአዶኒያስ ወ/አረጋይ
#ethiopianbroadcastingcorporation #medemergovernment #tourismethiopia #visitethiopia #landoforigins #abiyahmed
***********
ኢትዮጵያ የበርካታ ታሪካዊ ተፈጥሯዊና የባህል ቅርሶች ማህደር ብትሆንም ይህን ዕምቅ ፀጋ ወደ ሀገር ከፍታና ብልፅግና ቀይራ መጠቀም ሳትችል ዘመናት ተቆጥረዋል።
ሆኖም በምናብ ከፍታ ነገን አሻግሮ በመመልከት ቃልን በተግባር የመኖር ባህልን በተቋማዊ መሰረት የገነባው የመደመር እሳቤ የቱሪዝም ዘርፉን የሀገር ምሰሶ አድርጎ ተነስቷል።
የመደመር ፍልስፍና ዳራው ትናንትን ከነክብሩ ጠብቆ፣ የተበታተኑ ሀገራዊ ፀጋዎቻችንን በማሰባሰብና እሴትን በመጨመር ወደ ላቀ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጥቅም መቀየር ነው።
በዚህም መነሻነት የመደመር መንግሥት አዲስ አበባን ከጥልቅ ጉስቁልና በማውጣት ወደ ሚመጥናት የውበት ከፍታ እያሸጋገራት ይገኛል።
ይህ ጥረት በዋና ከተማዋ ብቻ ሳይገደብ ላለፉት አምስት ዓመታት በመላ የሀገራችን ክፍሎች የተመዘገቡት ስኬቶች የዚህን ዕሳቤ ጥልቀትና ተግባራዊነት ቁልጭ አድርገው የሚያሳዩ ናቸው።
ሀገራችን ለዘመናት ተዘንግተውና አቧራ ጠጥተው የቆዩ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ ቅርሶቿን ደረጃቸውን በጠበቀና በጥናት ላይ በመመስረት በማደስና በመንከባከብ በቱሪዝም ዘርፍ አስደናቂ ውጤት አስመዝግባለች።
ታሪካዊ ገፅታቸውን ሳያጡ በዘመናዊ አቀራረብ ሕይወት ዘርተው ከተነሱት ሜጋ ፕሮጀክቶች መካከል ብሔራዊ ቤተ መንግሥትን፣ የሐረር ጀጎል ግንብን፣ የጎንደር አብያተ መንግሥታትን፣ የጅማ አባ ጅፋር ቤተ መንግሥትንና የሶፍ ኡመር ዋሻን ጨምሮ በርካታ ድንቅ ቅርሶች ይገኙበታል።
የእነዚህ የቅርስ ዕድሳት ፕሮጀክቶች ፋይዳ የቱሪዝም መዳረሻዎችን ከማስፋትና ማራኪ ከማድረግም በእጅጉ የዘለለ ነው።
በዘርፉ አዲስ መነቃቃትን በመፍጠር የግሉ ዘርፍ በኢንቨስትመንት በስፋት እንዲሳተፍና ተወዳዳሪነቱ እንዲጠናከር ምቹ መደላድል ፈጥረዋል።
አዳዲስ የቱሪዝም ማዕከላት መበራከታቸው የጎብኚዎችን የቆይታ ጊዜ ከማራዘሙም ባሻገር ከዘርፉ የሚገኘው የውጭ ምንዛሬና አጠቃላይ ገቢ በከፍተኛ ደረጃ እንዲያድግ አስችሏል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነትና የቅርብ ክትትል የተተገበሩት እነዚህ የቅርስ ልማትና ጥበቃ ስራዎች የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ጎብኚዎችን ቁጥር በከፍተኛ መጠን እንዲጨምር አድርገዋል።
መንግሥት በቅርስ ጥበቃና ልማት ላይ የፈጠረው ይህ አዲስ ዕይታ የሀገራችንን የካበተ የታሪክ ሃብት በአግባቡ ጠብቆ ወደ ትልቅ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም መቀየር እንደሚቻል አረጋግጧል።
በአዶኒያስ ወ/አረጋይ
#ethiopianbroadcastingcorporation #medemergovernment #tourismethiopia #visitethiopia #landoforigins #abiyahmed
1 month ago
የሸገር ወንዞች ሲፈውሱ፡- ከብክለት ወደ ሕዝብ መዝናኛነት
********************
አዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ያስመዘገበችው ግዙፍ የከተማ ገጽታ ለውጥ ከመሠረተ ልማት ዝርጋታ ባሻገር የከተማዋን ነዋሪዎች አኗኗር፣ ማኅበራዊ መስተጋብርና የኢኮኖሚ አቅጣጫ የቀየረ ጥልቅ ስትራቴጂካዊ ሽግግር ነው።
ለረጅም ዘመናት አዲስ አበባ በከፍተኛ የሕዝብ ቁጥር ማደግ፣ በኮንክሪት ሕንጻዎች መበራከትና በአረንጓዴ ሥፍራዎች መመናመን ትታወቅ የነበረች ቢሆንም በቅርቡ የተከናወኑት የተቀናጁ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት ሥራዎች ግን ከተማዋን ወደ አዲስ የዕድገትና የውበት ምዕራፍ አሸጋግረዋታል።
ይህ ዘመናዊ ለውጥ በተለይም ቀደም ሲል የብክለት፣ የቸልተኝነትና የከተማዋ የጀርባ ገጽታ መገለጫ የነበሩትን የውሃ አካላትና ተፋሰሶች ወደ ሕያው፣ ማራኪና ሥነ-ምህዳራዊ ጠቀሜታ ወደላቸው የሕዝብ መጠቀሚያዎች በመለወጥ ረገድ ያተመዘገበው ስኬት የከተማዋን ታሪክና ገጽታ ሙሉ በሙሉ ቀይሮታል።
ይህ ዓይነቱ ትራንስፎርሜሽን የከተማዋን ነዋሪዎች የኑሮ ጥራት ከማሻሻሉም በላይ አዲስ አበባ በዓለም አቀፍና በአህጉራዊ መድረኮች ያላትን የላቀ አቋምና የቱሪስት መዳረሻነት በከፍተኛ ደረጃ እያሳደገው ይገኛል።
ለዚህም በዋና ማሳያነት የሚጠቀሰው ከእንጦጦ ጋራ ተነስቶ እስከ ቀበና የሚዘልቀው የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ነው። ይህ ሰፊ ኮሪደር ቀደም ሲል ለደህንነት አስጊና በቆሻሻ መጣያነት ያገለግል የነበረ አካባቢን ወደ ዘመናዊ የሕዝብ መዝናኛ፣ የእግር ጉዞ መንገዶችና የአረንጓዴ ልማት ማዕከልነት እንዴት መቀየር እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ታላቅ ስኬት ነው።
በእንጦጦ እና በቀበና ተፋሰስ መካከል በተገነቡት ዘመናዊ የሕዝብ መጠቀሚያ ሥፍራዎች ውስጥ የሚገኙት ውብ የእግር ጉዞ መስመሮች፣ የተፈጥሮን ሚዛን የጠበቁ የአትክልትና የዛፍ ዝርያዎች እንዲሁም ለዕረፍትና ለንባብ የተዘጋጁ ምቹ መቀመጫዎች ተፈጥሮንና ዘመናዊነትን በአንድ ጥላ ሥር ያቀናጁ ናቸው።
ነዋሪዎችና ጎብኚዎች ከከተማዋ የዕለት ተዕለት ጫጫታና ውጥረት ወጥተው ንጹህ አየር የሚተነፍሱበት አካላዊና አዕምሯዊ ጤንነታቸውን የሚያድሱበት ሰላማዊ ምኅዳር ተፈጥሯል።
ይህ መሠረተ ልማት በከተማ ፕላን ውስጥ ለሰዎች ቅድሚያ የመስጠትን መርህ ያረጋገጠ ከመሆኑም በላይ ወንዞች የከተማዋ የጀርባ አጥንትና የውበት መገለጫ መሆን እንደሚችሉ ያስመሰከረ አብነት ነው።
የዚህ የገጽታ መቀየር ዘላቂ ፋይዳ በዋናነት በሦስት ታላላቅ ዘርፎች ጎልቶ ይታያል። የመጀመሪያውና ግዙፉ ተጽዕኖ በቱሪዝም ዘርፍ ላይ የታየው አስደናቂ መነቃቃት ነው። አዲስ አበባ ቀደም ሲል የዓለም አቀፍ ስብሰባዎችና የትራንዚት መንገደኞች ጊዜያዊ ማረፊያ ብቻ ሆና የምትታወቅበትን የቆየ ገጽታ በመቀየር አሁን ላይ ጎብኚዎች ቀናትን አሳልፈው የሚዝናኑባትና የሚጎበኟት እውነተኛ የመዳረሻ ከተማ እየሆነች ነው።
የወንዝ ዳርቻዎቹ ውበት፣ ማራኪ የውሃ ፏፏቴዎችና በምሽት በደማቅና ውብ መብራቶች የሚዋቡት ፓርኮች ለምሽት ቱሪዝም አዲስ በር ከፍተዋል። ይህም የፎቶግራፍ አፍቃሪዎችንና ማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎችን የሚስቡ በርካታ ማራኪ ቦታዎችን በመፍጠር የከተማዋን ዓለም አቀፍ ገጽታ በከፍተኛ ደረጃ ገንብቶታል።
ሁለተኛው ከኢኮኖሚ ዕድገትና ከሥራ ዕድል ፈጠራ ጋር የተያያዘ ነው። በእነዚህ የተገነቡ የሕዝብ መጠቀሚያዎች ዙሪያ የሚንቀሳቀሱ አነስተኛና መካከለኛ የንግድ ተቋማት፣ ባህላዊ የምግብና የመጠጥ አቅራቢዎች እንዲሁም የዕደ-ጥበብ ውጤቶች መሸጫዎች ለበርካታ ዜጎች ዘላቂ የገቢ ምንጭና የሥራ ዕድል መፍጠር ችለዋል። ይህ ሁኔታ የከተማዋን የምጣኔ ሀብት እንቅስቃሴ በማነቃቃት የቱሪዝም ኢኮኖሚው በቀጥታ ወደ ማኅበረሰቡ እንዲደርስ አድርጓል።
ሶስተኛውና ትልቁ ስኬት የአካባቢ ጥበቃና የስነ-ምህዳር ሚዛንን ከመጠበቅ አንጻር የተመዘገበው ዘላቂ ውጤት ነው። ወንዞችን ከኢንዱስትሪና ከቤት ውስጥ ብክለት መታደግ መቻሉ፣ በዳርቻዎቻቸው ላይ የተተከሉ አረንጓዴ ተክሎችና ዛፎች የከተማዋን የካርቦን ልቀትን ለመቀነስና ብዝሃ ሕይወትን መልሶ ለማደስ ያላቸው ሚና ወደር የለውም።
በአጠቃላይ ሲታይ በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የተመዘገበው የወንዝ ዳርቻ ልማትና የውበት ስራ ከተማዋን ይበልጥ ለኑሮ ተስማሚ፣ ለዐይን ማራኪና በኢኮኖሚ ረገድ እራሷን የቻለች ማዕከል እያደረጋት ይገኛል።
ይህ ዓይነቱ የተቀናጀ የልማት አካሄድ አዲስ አበባ በአፍሪካ አህጉር ያላትን ተወዳዳሪነት ይበልጥ የሚያጠናክር ከመሆኑም በላይ ለቀጣይ ትውልድ የሚሻገር ታላቅ የታሪክና የውበት ዐሻራ ነው።
በበረከት ሽመልስ
#addisababa #riversidedevelopment #greenlegacy #tourismethiopia #ethiopianbroadcastingcorporation
********************
አዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ያስመዘገበችው ግዙፍ የከተማ ገጽታ ለውጥ ከመሠረተ ልማት ዝርጋታ ባሻገር የከተማዋን ነዋሪዎች አኗኗር፣ ማኅበራዊ መስተጋብርና የኢኮኖሚ አቅጣጫ የቀየረ ጥልቅ ስትራቴጂካዊ ሽግግር ነው።
ለረጅም ዘመናት አዲስ አበባ በከፍተኛ የሕዝብ ቁጥር ማደግ፣ በኮንክሪት ሕንጻዎች መበራከትና በአረንጓዴ ሥፍራዎች መመናመን ትታወቅ የነበረች ቢሆንም በቅርቡ የተከናወኑት የተቀናጁ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት ሥራዎች ግን ከተማዋን ወደ አዲስ የዕድገትና የውበት ምዕራፍ አሸጋግረዋታል።
ይህ ዘመናዊ ለውጥ በተለይም ቀደም ሲል የብክለት፣ የቸልተኝነትና የከተማዋ የጀርባ ገጽታ መገለጫ የነበሩትን የውሃ አካላትና ተፋሰሶች ወደ ሕያው፣ ማራኪና ሥነ-ምህዳራዊ ጠቀሜታ ወደላቸው የሕዝብ መጠቀሚያዎች በመለወጥ ረገድ ያተመዘገበው ስኬት የከተማዋን ታሪክና ገጽታ ሙሉ በሙሉ ቀይሮታል።
ይህ ዓይነቱ ትራንስፎርሜሽን የከተማዋን ነዋሪዎች የኑሮ ጥራት ከማሻሻሉም በላይ አዲስ አበባ በዓለም አቀፍና በአህጉራዊ መድረኮች ያላትን የላቀ አቋምና የቱሪስት መዳረሻነት በከፍተኛ ደረጃ እያሳደገው ይገኛል።
ለዚህም በዋና ማሳያነት የሚጠቀሰው ከእንጦጦ ጋራ ተነስቶ እስከ ቀበና የሚዘልቀው የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ነው። ይህ ሰፊ ኮሪደር ቀደም ሲል ለደህንነት አስጊና በቆሻሻ መጣያነት ያገለግል የነበረ አካባቢን ወደ ዘመናዊ የሕዝብ መዝናኛ፣ የእግር ጉዞ መንገዶችና የአረንጓዴ ልማት ማዕከልነት እንዴት መቀየር እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ታላቅ ስኬት ነው።
በእንጦጦ እና በቀበና ተፋሰስ መካከል በተገነቡት ዘመናዊ የሕዝብ መጠቀሚያ ሥፍራዎች ውስጥ የሚገኙት ውብ የእግር ጉዞ መስመሮች፣ የተፈጥሮን ሚዛን የጠበቁ የአትክልትና የዛፍ ዝርያዎች እንዲሁም ለዕረፍትና ለንባብ የተዘጋጁ ምቹ መቀመጫዎች ተፈጥሮንና ዘመናዊነትን በአንድ ጥላ ሥር ያቀናጁ ናቸው።
ነዋሪዎችና ጎብኚዎች ከከተማዋ የዕለት ተዕለት ጫጫታና ውጥረት ወጥተው ንጹህ አየር የሚተነፍሱበት አካላዊና አዕምሯዊ ጤንነታቸውን የሚያድሱበት ሰላማዊ ምኅዳር ተፈጥሯል።
ይህ መሠረተ ልማት በከተማ ፕላን ውስጥ ለሰዎች ቅድሚያ የመስጠትን መርህ ያረጋገጠ ከመሆኑም በላይ ወንዞች የከተማዋ የጀርባ አጥንትና የውበት መገለጫ መሆን እንደሚችሉ ያስመሰከረ አብነት ነው።
የዚህ የገጽታ መቀየር ዘላቂ ፋይዳ በዋናነት በሦስት ታላላቅ ዘርፎች ጎልቶ ይታያል። የመጀመሪያውና ግዙፉ ተጽዕኖ በቱሪዝም ዘርፍ ላይ የታየው አስደናቂ መነቃቃት ነው። አዲስ አበባ ቀደም ሲል የዓለም አቀፍ ስብሰባዎችና የትራንዚት መንገደኞች ጊዜያዊ ማረፊያ ብቻ ሆና የምትታወቅበትን የቆየ ገጽታ በመቀየር አሁን ላይ ጎብኚዎች ቀናትን አሳልፈው የሚዝናኑባትና የሚጎበኟት እውነተኛ የመዳረሻ ከተማ እየሆነች ነው።
የወንዝ ዳርቻዎቹ ውበት፣ ማራኪ የውሃ ፏፏቴዎችና በምሽት በደማቅና ውብ መብራቶች የሚዋቡት ፓርኮች ለምሽት ቱሪዝም አዲስ በር ከፍተዋል። ይህም የፎቶግራፍ አፍቃሪዎችንና ማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎችን የሚስቡ በርካታ ማራኪ ቦታዎችን በመፍጠር የከተማዋን ዓለም አቀፍ ገጽታ በከፍተኛ ደረጃ ገንብቶታል።
ሁለተኛው ከኢኮኖሚ ዕድገትና ከሥራ ዕድል ፈጠራ ጋር የተያያዘ ነው። በእነዚህ የተገነቡ የሕዝብ መጠቀሚያዎች ዙሪያ የሚንቀሳቀሱ አነስተኛና መካከለኛ የንግድ ተቋማት፣ ባህላዊ የምግብና የመጠጥ አቅራቢዎች እንዲሁም የዕደ-ጥበብ ውጤቶች መሸጫዎች ለበርካታ ዜጎች ዘላቂ የገቢ ምንጭና የሥራ ዕድል መፍጠር ችለዋል። ይህ ሁኔታ የከተማዋን የምጣኔ ሀብት እንቅስቃሴ በማነቃቃት የቱሪዝም ኢኮኖሚው በቀጥታ ወደ ማኅበረሰቡ እንዲደርስ አድርጓል።
ሶስተኛውና ትልቁ ስኬት የአካባቢ ጥበቃና የስነ-ምህዳር ሚዛንን ከመጠበቅ አንጻር የተመዘገበው ዘላቂ ውጤት ነው። ወንዞችን ከኢንዱስትሪና ከቤት ውስጥ ብክለት መታደግ መቻሉ፣ በዳርቻዎቻቸው ላይ የተተከሉ አረንጓዴ ተክሎችና ዛፎች የከተማዋን የካርቦን ልቀትን ለመቀነስና ብዝሃ ሕይወትን መልሶ ለማደስ ያላቸው ሚና ወደር የለውም።
በአጠቃላይ ሲታይ በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የተመዘገበው የወንዝ ዳርቻ ልማትና የውበት ስራ ከተማዋን ይበልጥ ለኑሮ ተስማሚ፣ ለዐይን ማራኪና በኢኮኖሚ ረገድ እራሷን የቻለች ማዕከል እያደረጋት ይገኛል።
ይህ ዓይነቱ የተቀናጀ የልማት አካሄድ አዲስ አበባ በአፍሪካ አህጉር ያላትን ተወዳዳሪነት ይበልጥ የሚያጠናክር ከመሆኑም በላይ ለቀጣይ ትውልድ የሚሻገር ታላቅ የታሪክና የውበት ዐሻራ ነው።
በበረከት ሽመልስ
#addisababa #riversidedevelopment #greenlegacy #tourismethiopia #ethiopianbroadcastingcorporation
2 months ago
ፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ እና ፋሜ ባይ ሺራዝ የሀገርን ገጽታ በጥቅል ለማስተዋወቅ በጋራ ለመስራት ተስማሙ
#ethiopia | የፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በዲጂታል ሚዲያና ብራንድ ማስተዋወቅ ላይ የሚንቀሳቀሰው ፋሜ ባይ ሺራዝ የተሰኘው ተቋም የሀገርን ገጽታ የመገንባት ስራ ላይ በትብብር ለመስራት መስማማታቸውን በጋራ ገለጹ።
የዚሁ ዓለም አቀፍ ተቋም መስራች የሆኑት ሺራዝ ሀሰን እና የስራ ባልደረቦቻቸው በፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ ተገኝተው የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን፣ ከዚሁ ጎን ለጎንም ከሚዲያው የማኔጅመንት አመራሮች ጋር በጋራ መስራት በሚቻልባቸው ዘርፎች ዙሪያ ሰፊ ውይይት አድርገዋል።
በውይይቱ ወቅት ሁለቱም ተቋማት ያላቸውን ልምድና የዲጂታል ሚዲያ አቅም በማስተባበር፣ በሀገር ገጽታ ግንባታ ስራዎች ላይ ተቀናጅተው ለመስራት የሚያስችላቸው ስምምነት ላይ ደርሰዋል።
ይህ ትብብር የሀገርን ገጽታ የማስተዋወቅ ተግባራትን በዘመናዊና ስልታዊ በሆኑ የዲጂታል መንገዶች በተደራጀ መልኩ ለመደገፍ ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ ከቱሪዝም ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
#digitalmedia #brandpromotion #tourismethiopia #mediapartnership #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በዲጂታል ሚዲያና ብራንድ ማስተዋወቅ ላይ የሚንቀሳቀሰው ፋሜ ባይ ሺራዝ የተሰኘው ተቋም የሀገርን ገጽታ የመገንባት ስራ ላይ በትብብር ለመስራት መስማማታቸውን በጋራ ገለጹ።
የዚሁ ዓለም አቀፍ ተቋም መስራች የሆኑት ሺራዝ ሀሰን እና የስራ ባልደረቦቻቸው በፐልስ ኦፍ አፍሪካ ሚዲያ ተገኝተው የስራ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን፣ ከዚሁ ጎን ለጎንም ከሚዲያው የማኔጅመንት አመራሮች ጋር በጋራ መስራት በሚቻልባቸው ዘርፎች ዙሪያ ሰፊ ውይይት አድርገዋል።
በውይይቱ ወቅት ሁለቱም ተቋማት ያላቸውን ልምድና የዲጂታል ሚዲያ አቅም በማስተባበር፣ በሀገር ገጽታ ግንባታ ስራዎች ላይ ተቀናጅተው ለመስራት የሚያስችላቸው ስምምነት ላይ ደርሰዋል።
ይህ ትብብር የሀገርን ገጽታ የማስተዋወቅ ተግባራትን በዘመናዊና ስልታዊ በሆኑ የዲጂታል መንገዶች በተደራጀ መልኩ ለመደገፍ ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ ከቱሪዝም ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
#digitalmedia #brandpromotion #tourismethiopia #mediapartnership #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
ታዋቂዋ የአትሌቶች መፍለቂያ ቦቆጂ ከተማ የልወቅሽ የኢትዮጵያ ክላሲክ 2018 የሩጫ ውድድርን በደመቀ ሁኔታ ማስተናገድ ጀመረች
#ethiopia | የበርካታ የዓለምና የኦሊምፒክ ሻምፒዮኖችን በማፍራት በዓለም አቀፍ ደረጃ በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀሰው የቦቆጂ ከተማ፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በመሆን ያዘጋጀውን ልወቅሽ የኢትዮጵያ ክላሲክ ታላቅ የሩጫ ውድድር በዛሬው ዕለት ማስተናገድ ጀምራለች።
ውድድሩ መነሻና መድረሻውን ታሪካዊው የቦቆጂ ስታዲየም ላይ ያደረገ ሲሆን፣ ከ100 በላይ አንጋፋና ፕሮፌሽናል አትሌቶች፣ ከ2 ሺህ 500 በላይ የቦቆጂ ከተማ ነዋሪዎች እንዲሁም ከአዲስ አበባ የተጓዙ ከ70 በላይ የስፖርቱ አፍቃሪያን ተሳታፊ ሆነዋል።
ይህ ትልቅ ስፖርታዊ መርሃ ግብር የአትሌቲክስ ስፖርትን ለማሳደግ ከሚኖረው ሚና ባሻገር፣ የቦቆጂን ከተማ የቱሪዝም መስህቦችና አቅሞች ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ጎብኝዎች በሰፊው ለማስተዋወቅ ታላቅ ዕድል የፈጠረ ነው።
የመጀመሪያው ምዕራፉ በደብረ ብርሃን ከተማ ተጀምሮ አሁን በቦቆጂ ይፋዊ ጉዞውን የቀጠለው ይህ መርሃ ግብር፣ በኢትዮጵያ የስፖርት ቱሪዝም ልማት ላይ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ክስተት ሆኗል።
በዚህ ደማቅ የማስጀመሪያ ዝግጅት ላይ የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እንደገና አበበ፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ መኪዩ መሀመድ፣ የአርሲ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኢብራሒም ከድር እና የቦቆጂ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ ብርሃኔ ነገሰ ተገኝተዋል።
በተጨማሪም ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የቱሪዝም ዘርፍ ተወካዮች፣ ታዋቂ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችና የብዙኃን መገናኛ ባለሙያዎች በከተማዋ በመገኘት መርሃ ግብሩን ታድመዋል።
#bekoji #ethiopianclassic #greatethiopianrun #sportstourism #tourismethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የበርካታ የዓለምና የኦሊምፒክ ሻምፒዮኖችን በማፍራት በዓለም አቀፍ ደረጃ በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀሰው የቦቆጂ ከተማ፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በመሆን ያዘጋጀውን ልወቅሽ የኢትዮጵያ ክላሲክ ታላቅ የሩጫ ውድድር በዛሬው ዕለት ማስተናገድ ጀምራለች።
ውድድሩ መነሻና መድረሻውን ታሪካዊው የቦቆጂ ስታዲየም ላይ ያደረገ ሲሆን፣ ከ100 በላይ አንጋፋና ፕሮፌሽናል አትሌቶች፣ ከ2 ሺህ 500 በላይ የቦቆጂ ከተማ ነዋሪዎች እንዲሁም ከአዲስ አበባ የተጓዙ ከ70 በላይ የስፖርቱ አፍቃሪያን ተሳታፊ ሆነዋል።
ይህ ትልቅ ስፖርታዊ መርሃ ግብር የአትሌቲክስ ስፖርትን ለማሳደግ ከሚኖረው ሚና ባሻገር፣ የቦቆጂን ከተማ የቱሪዝም መስህቦችና አቅሞች ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ጎብኝዎች በሰፊው ለማስተዋወቅ ታላቅ ዕድል የፈጠረ ነው።
የመጀመሪያው ምዕራፉ በደብረ ብርሃን ከተማ ተጀምሮ አሁን በቦቆጂ ይፋዊ ጉዞውን የቀጠለው ይህ መርሃ ግብር፣ በኢትዮጵያ የስፖርት ቱሪዝም ልማት ላይ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ክስተት ሆኗል።
በዚህ ደማቅ የማስጀመሪያ ዝግጅት ላይ የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እንደገና አበበ፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ መኪዩ መሀመድ፣ የአርሲ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኢብራሒም ከድር እና የቦቆጂ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ ብርሃኔ ነገሰ ተገኝተዋል።
በተጨማሪም ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የቱሪዝም ዘርፍ ተወካዮች፣ ታዋቂ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችና የብዙኃን መገናኛ ባለሙያዎች በከተማዋ በመገኘት መርሃ ግብሩን ታድመዋል።
#bekoji #ethiopianclassic #greatethiopianrun #sportstourism #tourismethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ800 በላይ አዳዲስ የቱሪስት መስህቦች ተለይተዋል - የቱሪዝም ሚኒስትር
#ethiopia | በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሦስት ሩብ ዓመታት ኢትዮጵያ በቱሪዝም መስክ የላቀ ገጽታ የገነባችበት እና በርካታ ዓለም አቀፍ መድረኮችን በውጤታማነት ያስተናገደችበት ወቅት መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ ገለጹ።
ሚኒስትሯ ይህንን ያመለከቱት ተቋማቸው በበጀት ዓመቱ ያከናወናቸውን ዋና ዋና ተግባራት ለመገምገም እና በቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ለመወያየት ዛሬ ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከሠራተኞች ጋር ባደረጉት ጠቅላላ ስብሰባ ላይ ነው።
በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት በዓመቱ አዲሱ የቱሪዝም ፖሊሲ መጽደቁ ለዘርፉ ዕድገት ትልቅ መሠረት ጥሏል።
ከግሉ ዘርፍ እና ከክልል መስተዳድሮች ጋር ጠንካራ የሥራ ግንኙነት እንደነበር የገለጹት ሚኒስትሯ፣ አገሪቱን የስብሰባ፣ የጉዞ እና የዝግጅቶች ወይም የማክ ቱሪዝም መዳረሻ አድርጎ ለማስተዋወቅ ሰፊ ጥረት መደረጉንና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ800 በላይ አዳዲስ የቱሪስት መስህቦች መለየታቸውን አብራርተዋል።
በቀጣዩ አንድ ወር ውስጥ የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በውጤታማነት ማጠናቀቅ እንደሚገባ የጠቆሙት ሰላማዊት ካሳ፣ የፈጠራ አቀራረብ ያላቸውን የፕሮሞሽን ሥራዎች ማጠናከር፣ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ማሳደግ እና የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ሪፎርም የዝግጅት ምዕራፍን ማጠናቀቅ በትኩረት እንደሚሠራበት አስገንዝበዋል።
የቱሪዝም መዳረሻዎችና መሠረተ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ስለሺ ግርማ በበኩላቸው፣ ከተለመዱት የቱሪዝም ዓይነቶች በተጨማሪ አዳዲስ አማራጮችን ለይቶ በፖሊሲ ደረጃ ትኩረት እንዲያገኙ ማድረግ መቻሉ የዓመቱ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል።
የማርኬቲንግ እና ፕሮሞሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እንደገና አበበ በበጀት ዓመቱ የተመዘገቡ መልካም ተሞክሮዎችን በማስቀጠልና የታዩ ክፍተቶችን በማረም የዘርፉን ተወዳዳሪነት ይበልጥ ማሳደግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
#tourismethiopia #ethiopiatourism #micetourism #ethiopianheritage #tourismpolicy #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሦስት ሩብ ዓመታት ኢትዮጵያ በቱሪዝም መስክ የላቀ ገጽታ የገነባችበት እና በርካታ ዓለም አቀፍ መድረኮችን በውጤታማነት ያስተናገደችበት ወቅት መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ ገለጹ።
ሚኒስትሯ ይህንን ያመለከቱት ተቋማቸው በበጀት ዓመቱ ያከናወናቸውን ዋና ዋና ተግባራት ለመገምገም እና በቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ለመወያየት ዛሬ ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከሠራተኞች ጋር ባደረጉት ጠቅላላ ስብሰባ ላይ ነው።
በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት በዓመቱ አዲሱ የቱሪዝም ፖሊሲ መጽደቁ ለዘርፉ ዕድገት ትልቅ መሠረት ጥሏል።
ከግሉ ዘርፍ እና ከክልል መስተዳድሮች ጋር ጠንካራ የሥራ ግንኙነት እንደነበር የገለጹት ሚኒስትሯ፣ አገሪቱን የስብሰባ፣ የጉዞ እና የዝግጅቶች ወይም የማክ ቱሪዝም መዳረሻ አድርጎ ለማስተዋወቅ ሰፊ ጥረት መደረጉንና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ800 በላይ አዳዲስ የቱሪስት መስህቦች መለየታቸውን አብራርተዋል።
በቀጣዩ አንድ ወር ውስጥ የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በውጤታማነት ማጠናቀቅ እንደሚገባ የጠቆሙት ሰላማዊት ካሳ፣ የፈጠራ አቀራረብ ያላቸውን የፕሮሞሽን ሥራዎች ማጠናከር፣ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ማሳደግ እና የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ሪፎርም የዝግጅት ምዕራፍን ማጠናቀቅ በትኩረት እንደሚሠራበት አስገንዝበዋል።
የቱሪዝም መዳረሻዎችና መሠረተ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ስለሺ ግርማ በበኩላቸው፣ ከተለመዱት የቱሪዝም ዓይነቶች በተጨማሪ አዳዲስ አማራጮችን ለይቶ በፖሊሲ ደረጃ ትኩረት እንዲያገኙ ማድረግ መቻሉ የዓመቱ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል።
የማርኬቲንግ እና ፕሮሞሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እንደገና አበበ በበጀት ዓመቱ የተመዘገቡ መልካም ተሞክሮዎችን በማስቀጠልና የታዩ ክፍተቶችን በማረም የዘርፉን ተወዳዳሪነት ይበልጥ ማሳደግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
#tourismethiopia #ethiopiatourism #micetourism #ethiopianheritage #tourismpolicy #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Sponsored by
Surafel
2 months ago
የቡኖ ማላ ዓለም አቀፍ ኤክስፖ በዲላ ከተማ በደመቀ ሁኔታ መካሄድ ጀመረ
#ethiopia | በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የቡኖ ማላ ዓለም አቀፍ ኤክስፖ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጌዴኦ ዞን ዲላ ከተማ በሚገኘው የኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ በይፋ ተከፍቷል።
ይህ ታላቅ መድረክ የጌዴኦን የቡናና የሥጋ ምርት ሀብት በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማስተዋወቅ፣ የዲላን የኢንቨስትመንት ሳቢነት ለማሳደግ እንዲሁም በየአካባቢው የሚገኙ የቱሪስት መዳረሻዎችን ለዓለም ማህበረሰብ በሰፊው ለማስተዋወቅ ያለመ ነው።
ትናንት በተከናወነው የዝግጅቱ መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ የፌደራል እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የጌዴኦ ዞንና የዲላ ከተማ አመራሮች እንዲሁም በርካታ የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ኤክስፖው ዛሬም በተለያዩ ባለድርሻ አካላትና ጎብኚዎች መጎብኘቱን የሚቀጥል ሲሆን፣ ልዩ ልዩ የኪነ-ጥበብ እና የመዝናኛ ዝግጅቶችን በማካተት እስከ አመሻሹ ድረስ ክፍት ሆኖ እንደሚቆይ ታውቋል።
#bunomalaexpo #dilla #gedeo #southethiopia #coffeeexpo #tourismethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የቡኖ ማላ ዓለም አቀፍ ኤክስፖ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጌዴኦ ዞን ዲላ ከተማ በሚገኘው የኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ በይፋ ተከፍቷል።
ይህ ታላቅ መድረክ የጌዴኦን የቡናና የሥጋ ምርት ሀብት በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማስተዋወቅ፣ የዲላን የኢንቨስትመንት ሳቢነት ለማሳደግ እንዲሁም በየአካባቢው የሚገኙ የቱሪስት መዳረሻዎችን ለዓለም ማህበረሰብ በሰፊው ለማስተዋወቅ ያለመ ነው።
ትናንት በተከናወነው የዝግጅቱ መክፈቻ ሥነ-ሥርዓት ላይ የፌደራል እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የጌዴኦ ዞንና የዲላ ከተማ አመራሮች እንዲሁም በርካታ የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ኤክስፖው ዛሬም በተለያዩ ባለድርሻ አካላትና ጎብኚዎች መጎብኘቱን የሚቀጥል ሲሆን፣ ልዩ ልዩ የኪነ-ጥበብ እና የመዝናኛ ዝግጅቶችን በማካተት እስከ አመሻሹ ድረስ ክፍት ሆኖ እንደሚቆይ ታውቋል።
#bunomalaexpo #dilla #gedeo #southethiopia #coffeeexpo #tourismethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 months ago
በጣና ዳርቻ ላይ የሚገነባው የቱሪዝም መዳረሻ
#bahirdar #tourismethiopia #midrocinvestmentgroup #laketana #newproject #ethiopiarising #ባሕርዳር #ኢትዮጵያ
3 months ago
የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት አካል የሆነው ግዙፉ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት በባህር ዳር ከተማ ተመረቀ
#ethiopia | በውቧ ባህር ዳር ከተማ በከፍተኛ ወጪ የተገነባው ግዙፉ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ዛሬ ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በታላቅ ስነ ስርዓት ተመርቋል።
በደቡባዊ የጣና ሀይቅ ዳርቻ ላይ ያረፈው ይህ ሪዞርት በጎርጎራ በኩል የተጀመረውን የቱሪዝም ልማት ብርሃን ወደ ሌላኛው የሀይቁ ዳርቻ ያሸጋገረ ግዙፍ ኢንቨስትመንት ነው።
ፕሮጀክቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በገበታ ለሀገር እቅድ አማካኝነት ሁለት የጣና ሀይቅ ዳርቻዎችን በቱሪዝም ለማስተሳሰር የነደፉትን ታላቅ ራዕይ ዳር ያደረሰ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የታሪካዊቷን የጎርጎራ ከተማ ገፅታ ከመቀየር ባለፈ በዐፄ ፋሲለደስ መናገሻ ጎንደር የሚገኙ የቤተ መንግስት ቅርሶችን በከፍተኛ ጥራት በማደስ ለዘላቂ ቱሪዝም ዝግጁ እንዲሆኑ አድርገዋል።
ከዚህም በተጨማሪ ለጎንደር ከተማ የመጠጥ ውሃ እና ለግብርና ልማት የሚውለው የመገጭ ግድብ ግንባታ ለውሃ ቱሪዝም አዲስ እድል ይዞ እየመጣ ይገኛል።
ይህንን መንግስታዊ ራዕይ በግል ኢንቨስትመንት በማገዝ የቤአኢካ እና የእህት ኩባንያዎቹ መስራች አቶ ካሳሁን ምስጋናው የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርትን በ 4.5 ቢሊዮን ብር ወጪ በሁለት አመት ከስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ገንብተው አጠናቀዋል።
ግለሰቡ በጎርጎራ ኢኮ ቱሪዝም ግንባታ እና በጎንደር ቅርሶች ጥገና ላይ የነበራቸውን ውጤታማ ተሳትፎ አሁን ደግሞ በቱሪዝም ኢንዱስትሪው ውስጥ በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ በኩል በስፋት ለመቀጠል ተዘጋጅተዋል።
አቶ ካሳሁን ለእነዚህ ስራዎች ስኬት የፌዴራል እና የክልል መንግስታት እንዲሁም የከተማ አስተዳደሮች ላደረጉላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ወደፊትም የፈለገ ግዮን እና የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርቶች በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ ስር በመሆን ልባችን ኢትዮጵያ ደረጃችን አለም አቀፍ በሚል መሪ ቃል ጥራት ያለው አገልግሎት ለጎብኚዎች እንደሚያቀርቡ ተገልጿል።
#bahirdar #tanalake #tourismethiopia #beaikainvestment #rodahospitality #development #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በውቧ ባህር ዳር ከተማ በከፍተኛ ወጪ የተገነባው ግዙፉ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ዛሬ ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በታላቅ ስነ ስርዓት ተመርቋል።
በደቡባዊ የጣና ሀይቅ ዳርቻ ላይ ያረፈው ይህ ሪዞርት በጎርጎራ በኩል የተጀመረውን የቱሪዝም ልማት ብርሃን ወደ ሌላኛው የሀይቁ ዳርቻ ያሸጋገረ ግዙፍ ኢንቨስትመንት ነው።
ፕሮጀክቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በገበታ ለሀገር እቅድ አማካኝነት ሁለት የጣና ሀይቅ ዳርቻዎችን በቱሪዝም ለማስተሳሰር የነደፉትን ታላቅ ራዕይ ዳር ያደረሰ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የታሪካዊቷን የጎርጎራ ከተማ ገፅታ ከመቀየር ባለፈ በዐፄ ፋሲለደስ መናገሻ ጎንደር የሚገኙ የቤተ መንግስት ቅርሶችን በከፍተኛ ጥራት በማደስ ለዘላቂ ቱሪዝም ዝግጁ እንዲሆኑ አድርገዋል።
ከዚህም በተጨማሪ ለጎንደር ከተማ የመጠጥ ውሃ እና ለግብርና ልማት የሚውለው የመገጭ ግድብ ግንባታ ለውሃ ቱሪዝም አዲስ እድል ይዞ እየመጣ ይገኛል።
ይህንን መንግስታዊ ራዕይ በግል ኢንቨስትመንት በማገዝ የቤአኢካ እና የእህት ኩባንያዎቹ መስራች አቶ ካሳሁን ምስጋናው የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርትን በ 4.5 ቢሊዮን ብር ወጪ በሁለት አመት ከስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ገንብተው አጠናቀዋል።
ግለሰቡ በጎርጎራ ኢኮ ቱሪዝም ግንባታ እና በጎንደር ቅርሶች ጥገና ላይ የነበራቸውን ውጤታማ ተሳትፎ አሁን ደግሞ በቱሪዝም ኢንዱስትሪው ውስጥ በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ በኩል በስፋት ለመቀጠል ተዘጋጅተዋል።
አቶ ካሳሁን ለእነዚህ ስራዎች ስኬት የፌዴራል እና የክልል መንግስታት እንዲሁም የከተማ አስተዳደሮች ላደረጉላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ወደፊትም የፈለገ ግዮን እና የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርቶች በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ ስር በመሆን ልባችን ኢትዮጵያ ደረጃችን አለም አቀፍ በሚል መሪ ቃል ጥራት ያለው አገልግሎት ለጎብኚዎች እንደሚያቀርቡ ተገልጿል።
#bahirdar #tanalake #tourismethiopia #beaikainvestment #rodahospitality #development #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 months ago
አዲሱ የአራዳ ፓርክ የታሪክ ማስታወሻ የውበት ምንጭና የዘመናዊነት መገለጫ
#ethiopia | የአራዳ ፓርክ ቀደም ሲል የነበረውን የቆሻሻ የብክለትና የድህነት ገጽታ ሙሉ በሙሉ በመቀየር በአዲስ መልክ የተገነባ ታላቅ ፕሮጀክት ነው::
ይህ ስራ የቆዩ አሉታዊ የታሪክ አሻራዎችን በማጥፋት የኢትዮጵያን አዲስ ማንነትና ውበት ለትውልድ በሚተርክ መልኩ ተከናውኗል::
ከፒያሳ አካባቢ የለቀቁ ነዋሪዎች ለሰብአዊ ክብር ከማይመጥኑ ቤቶች ወጥተው መሰረተ ልማት ወደተሟላላቸው ዘመናዊ መኖሪያዎች እንዲገቡ ተደርጓል::
ነዋሪዎቹ ማህበራዊ ትስስራቸውን ሳይበጥሱ እድርና እቁባቸውን ጠብቀው እንዲኖሩ መደረጉም የልማቱ ልዩ ገጽታ ነው:: ፒያሳ ዳግም የተገነባችው እውነተኛ ስልጣኔን በሚያንጸባርቅ መልኩ ሲሆን በአካባቢው የነበሩ ወንዞችም ከቆሻሻ ጸድተው ለስራ እድል ፈጠራና ለቱሪስት መዳረሻነት እንዲውሉ ተደርገዋል::
በ40 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው የአራዳ ፓርክ የሚከተሉትን ዋና ዋና አገልግሎቶች ይዟል
የመንገድና የትራንስፖርት መሰረተ ልማት
5 ኪሎ ሜትር የአስፓልት መንገድ 6 ኪሎ ሜትር የእግረኛ መንገድ 5 ኪሎ ሜትር የብስክሌት መስመር እና 5 ኪሎ ሜትር የመሮጫ ትራክ ተገንብቶለታል::
የንግድና የፋይናንስ ዘርፍ
ከፒያሳ ለተነሱ ነጋዴዎች ቅድሚያ የሚሰጥባቸው 131 ዘመናዊ ሱቆች 7 ካፌና ሬስቶራንቶች አንድ ትልቅ ሱፐርማርኬት እና የባንክ ቅርንጫፍ ተካተዋል::
የመዝናኛና የስፖርት አገልግሎቶች
ዘመናዊ የአካል ብቃት ማእከል 7 አዳራሾች 8 ፕላዛዎች 3 አንፊ ቴአትሮች እና ማራኪ የሆነ ተንቀሳቃሽ ፏፏቴ ይገኛሉ:: በተጨማሪም 100 ሜትር ርዝመት ያለው የሀገሪቱ ረጅሙ የሰንደቅ ዓላማ መስቀያ በዚሁ ፓርክ ተተክሏል::
የህጻናትና ቤተሰብ ስፍራዎች
አራት ዘመናዊ የህጻናት መጫወቻዎች እና ህጻናት ስለ ሀገራቸው ግንዛቤ የሚያገኙበት ትንሿ ከተማ የተሰኘ ልዩ ስፍራ ተዘጋጅቷል::
የአረንጓዴ ልማትና የንጽህና አገልግሎት
15 ሄክታር መሬት በሳርና በተክሎች የተሸፈነ ሲሆን 22 የህዝብ መጸዳጃ ቤቶች እና 131 መኪናዎችን የሚይዝ ሰፊ ማቆሚያ ተገንብቷል::
ይህ ፕሮጀክት የመሬት አጠቃቀምን በብቃት ያረጋገጠ ሲሆን ከመሬት በታች ለሱቆችና ለአዳራሾች ከላይ ደግሞ ለፕላዛ አገልግሎት እንዲውል ተደርጓል::
እንዲሁም በአካባቢው የነበሩ ከ700 በላይ ታሪካዊ ቤቶችና ህንጻዎች ይዘታቸውን ሳይለቁ እንዲታደሱ ተደርጓል::
በአጠቃላይ ፓርኩ ከንግድ እስከ ስፖርት እንዲሁም ከቤተሰብ መዝናኛ እስከ ስነ ጥበብ መድረኮችን የያዘ የከተማዋ አዲስ የቱሪስት መስህብ ነው::
#aradapark #piassa #addisababacity #urbandevelopment #greenlegacy #tourismethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የአራዳ ፓርክ ቀደም ሲል የነበረውን የቆሻሻ የብክለትና የድህነት ገጽታ ሙሉ በሙሉ በመቀየር በአዲስ መልክ የተገነባ ታላቅ ፕሮጀክት ነው::
ይህ ስራ የቆዩ አሉታዊ የታሪክ አሻራዎችን በማጥፋት የኢትዮጵያን አዲስ ማንነትና ውበት ለትውልድ በሚተርክ መልኩ ተከናውኗል::
ከፒያሳ አካባቢ የለቀቁ ነዋሪዎች ለሰብአዊ ክብር ከማይመጥኑ ቤቶች ወጥተው መሰረተ ልማት ወደተሟላላቸው ዘመናዊ መኖሪያዎች እንዲገቡ ተደርጓል::
ነዋሪዎቹ ማህበራዊ ትስስራቸውን ሳይበጥሱ እድርና እቁባቸውን ጠብቀው እንዲኖሩ መደረጉም የልማቱ ልዩ ገጽታ ነው:: ፒያሳ ዳግም የተገነባችው እውነተኛ ስልጣኔን በሚያንጸባርቅ መልኩ ሲሆን በአካባቢው የነበሩ ወንዞችም ከቆሻሻ ጸድተው ለስራ እድል ፈጠራና ለቱሪስት መዳረሻነት እንዲውሉ ተደርገዋል::
በ40 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው የአራዳ ፓርክ የሚከተሉትን ዋና ዋና አገልግሎቶች ይዟል
የመንገድና የትራንስፖርት መሰረተ ልማት
5 ኪሎ ሜትር የአስፓልት መንገድ 6 ኪሎ ሜትር የእግረኛ መንገድ 5 ኪሎ ሜትር የብስክሌት መስመር እና 5 ኪሎ ሜትር የመሮጫ ትራክ ተገንብቶለታል::
የንግድና የፋይናንስ ዘርፍ
ከፒያሳ ለተነሱ ነጋዴዎች ቅድሚያ የሚሰጥባቸው 131 ዘመናዊ ሱቆች 7 ካፌና ሬስቶራንቶች አንድ ትልቅ ሱፐርማርኬት እና የባንክ ቅርንጫፍ ተካተዋል::
የመዝናኛና የስፖርት አገልግሎቶች
ዘመናዊ የአካል ብቃት ማእከል 7 አዳራሾች 8 ፕላዛዎች 3 አንፊ ቴአትሮች እና ማራኪ የሆነ ተንቀሳቃሽ ፏፏቴ ይገኛሉ:: በተጨማሪም 100 ሜትር ርዝመት ያለው የሀገሪቱ ረጅሙ የሰንደቅ ዓላማ መስቀያ በዚሁ ፓርክ ተተክሏል::
የህጻናትና ቤተሰብ ስፍራዎች
አራት ዘመናዊ የህጻናት መጫወቻዎች እና ህጻናት ስለ ሀገራቸው ግንዛቤ የሚያገኙበት ትንሿ ከተማ የተሰኘ ልዩ ስፍራ ተዘጋጅቷል::
የአረንጓዴ ልማትና የንጽህና አገልግሎት
15 ሄክታር መሬት በሳርና በተክሎች የተሸፈነ ሲሆን 22 የህዝብ መጸዳጃ ቤቶች እና 131 መኪናዎችን የሚይዝ ሰፊ ማቆሚያ ተገንብቷል::
ይህ ፕሮጀክት የመሬት አጠቃቀምን በብቃት ያረጋገጠ ሲሆን ከመሬት በታች ለሱቆችና ለአዳራሾች ከላይ ደግሞ ለፕላዛ አገልግሎት እንዲውል ተደርጓል::
እንዲሁም በአካባቢው የነበሩ ከ700 በላይ ታሪካዊ ቤቶችና ህንጻዎች ይዘታቸውን ሳይለቁ እንዲታደሱ ተደርጓል::
በአጠቃላይ ፓርኩ ከንግድ እስከ ስፖርት እንዲሁም ከቤተሰብ መዝናኛ እስከ ስነ ጥበብ መድረኮችን የያዘ የከተማዋ አዲስ የቱሪስት መስህብ ነው::
#aradapark #piassa #addisababacity #urbandevelopment #greenlegacy #tourismethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
4 months ago
ዝሆን ገድሎ 5,000 ብር ቅጣት አበቃለት
#ethiopia | ኢትዮጵያ ጠንካራ የዱር እንስሳት ጥበቃ ህግ ልታፀድቅ ነው
"የአንድ ዝሆን የህይወት ዘመን የቱሪዝም ገቢ 1.6 ሚሊዮን ዶላር ሆኖ ሳለ፣ የገዳዩ ቅጣት 5,000 ብር ብቻ መሆኑ ሊያበቃ ነው!"
የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ላለፉት 18 ዓመታት በስራ ላይ የቆየውንና ለህገ-ወጦች "ምቹ" የነበረውን ህግ በአዲስና እጅግ ጠንካራ በሆነ ህግ ለመተካት ዝግጅቱን አጠናቋል።
አዲሱ ህግ እስከ እድሜ ልክ እስራትና የ234 ሺህ ዶላር ቅጣት የሚጥለውን የኬንያን ጥብቅ ተሞክሮ መሰረት ያደረገ ነው።
በአሁኑ ህግ ሁለት ዝሆኖችን ገድሎ የተገኘ ግለሰብ የሚቀጣው በ5,000 ብር ብቻ ሲሆን፣ ይህም ከሀገር ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ አንጻር "አስተማሪ" እንዳልሆነ ባለስልጣኑ ገልጿል።
ከቅጣት ባለፈ "የተፈጥሮ ሀብትን ያወደመ አካል የጠፋውን ሀብት እንዲተካ" የሚያስገድድ አሰራር በረቂቁ ተካቷል።
ህገ-ወጥ ንግዱን "አክሳሪ" በማድረግ ብርቅዬ እንስሳትን ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍና የቱሪዝም ገቢን ማሳደግ።
ተፈጥሮን መጠበቅ ለነገው ትውልድ የሚተርፍ ቅርስ መገንባት ነው!
#getu #wildlifeprotection #ethiopianews #saveelephants #tourismethiopia #newlaw #biodiversity #natureconservation #የዱርእንስሳት #ኢትዮጵያ #ሰበርዜና #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | ኢትዮጵያ ጠንካራ የዱር እንስሳት ጥበቃ ህግ ልታፀድቅ ነው
"የአንድ ዝሆን የህይወት ዘመን የቱሪዝም ገቢ 1.6 ሚሊዮን ዶላር ሆኖ ሳለ፣ የገዳዩ ቅጣት 5,000 ብር ብቻ መሆኑ ሊያበቃ ነው!"
የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ላለፉት 18 ዓመታት በስራ ላይ የቆየውንና ለህገ-ወጦች "ምቹ" የነበረውን ህግ በአዲስና እጅግ ጠንካራ በሆነ ህግ ለመተካት ዝግጅቱን አጠናቋል።
አዲሱ ህግ እስከ እድሜ ልክ እስራትና የ234 ሺህ ዶላር ቅጣት የሚጥለውን የኬንያን ጥብቅ ተሞክሮ መሰረት ያደረገ ነው።
በአሁኑ ህግ ሁለት ዝሆኖችን ገድሎ የተገኘ ግለሰብ የሚቀጣው በ5,000 ብር ብቻ ሲሆን፣ ይህም ከሀገር ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ አንጻር "አስተማሪ" እንዳልሆነ ባለስልጣኑ ገልጿል።
ከቅጣት ባለፈ "የተፈጥሮ ሀብትን ያወደመ አካል የጠፋውን ሀብት እንዲተካ" የሚያስገድድ አሰራር በረቂቁ ተካቷል።
ህገ-ወጥ ንግዱን "አክሳሪ" በማድረግ ብርቅዬ እንስሳትን ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍና የቱሪዝም ገቢን ማሳደግ።
ተፈጥሮን መጠበቅ ለነገው ትውልድ የሚተርፍ ቅርስ መገንባት ነው!
#getu #wildlifeprotection #ethiopianews #saveelephants #tourismethiopia #newlaw #biodiversity #natureconservation #የዱርእንስሳት #ኢትዮጵያ #ሰበርዜና #ጌጡተመስገን #getutemesgen
5 months ago
(G-power Face of Ethiopia) ፕሮጀክት በይፋ ተጀመረ!
#ethiopia | ኢትዮጵያ ያላትን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ጸጋዎች ለዓለም የምታሳይበት አዲስና ዘመናዊ "ዲጂታል መስኮት" ተከፍቷል።
የቱሪዝም ሚኒስቴር ከቲክቶክ (TikTok) Creative አዋርድ አዘጋጆች ጋር በመተባበር፣ የሀገሪቱን መልካም ገጽታ ለመገንባትና የቱሪስት መዳረሻዎችን በስፋት ለማስተዋወቅ ያለመ "G-power Face of Ethiopia" የተሰኘ ፕሮጀክት በዛሬው ዕለት ይፋ አድርጓል።
የፕሮጀክቱ ፋይዳ?
የዘንድሮው ፕሮጀክት ትኩረቱን በቴክኖሎጂና በዲጂታል አማራጮች ላይ ማድረጉ ልዩ ያደርገዋል።
በቱሪዝም ሚኒስቴር የፕሮሞሽን ስራ አስፈፃሚ አቶ ተሾመ ተክሉ እንደገለጹት፣ ይህ አሰራር በዘርፉ ላይ አዲስ መነቃቃትን ከመፍጠሩም በላይ የሀገሪቱን ውበት በቀላሉ ለዓለም ተደራሽ ለማድረግ ትልቅ አቅም ይኖረዋል።
ከቁንጅና ውድድር ባለፈ፦ የቱሪዝም አምባሳደሮች!🔎
የፕሮጀክቱ ስራ አስኪያጅ መቅድም ደረጀ እንዳብራሩት፣ "Face of Ethiopia" ከተለመዱት የውበት ውድድሮች ለየት ያለ አካሄድ አለው።
ተወዳዳሪዎች ስለሚወክሏቸው ክልሎች ባህል፣ ታሪክና የቱሪዝም እምቅ ሀብት ጥልቅ ስልጠና የሚሰጣቸው ሲሆን፣ ይህም ወጣቶቹ በመድረክ ላይ ከመታየት ባለፈ የሀገራቸው እውነተኛ "የቱሪዝም አምባሳደሮች" እንዲሆኑ ያስችላቸዋል።
እንዴት መመዝገብ ይቻላል?
የቲክቶክ ፈጣሪዎች ያላቸውን ሰፊ ተደራሽነት በመጠቀም ፕሮጀክቱን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ የታቀደ ሲሆን፣ በውድድሩ ላይ መሳተፍ ለሚፈልጉ ወጣቶች ምዝገባ መጀመሩ ተበስሯል።
* የምዝገባ ድረ-ገጽ፦
www.faceofethiopia.et
ኢትዮጵያን በዲጂታሉ ዓለም በአዲስ መልክ ለማስተዋወቅ የሚደረገው ይህ ጉዞ፣ ለቱሪዝም ዘርፉ ትልቅ እመርታ እንደሚሆን ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #faceofethiopia #landoforigins #visitethiopia #tourismethiopia #gpower #digitalpromotion #ethiopia #tiktokethiopia
#ethiopia | ኢትዮጵያ ያላትን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ጸጋዎች ለዓለም የምታሳይበት አዲስና ዘመናዊ "ዲጂታል መስኮት" ተከፍቷል።
የቱሪዝም ሚኒስቴር ከቲክቶክ (TikTok) Creative አዋርድ አዘጋጆች ጋር በመተባበር፣ የሀገሪቱን መልካም ገጽታ ለመገንባትና የቱሪስት መዳረሻዎችን በስፋት ለማስተዋወቅ ያለመ "G-power Face of Ethiopia" የተሰኘ ፕሮጀክት በዛሬው ዕለት ይፋ አድርጓል።
የፕሮጀክቱ ፋይዳ?
የዘንድሮው ፕሮጀክት ትኩረቱን በቴክኖሎጂና በዲጂታል አማራጮች ላይ ማድረጉ ልዩ ያደርገዋል።
በቱሪዝም ሚኒስቴር የፕሮሞሽን ስራ አስፈፃሚ አቶ ተሾመ ተክሉ እንደገለጹት፣ ይህ አሰራር በዘርፉ ላይ አዲስ መነቃቃትን ከመፍጠሩም በላይ የሀገሪቱን ውበት በቀላሉ ለዓለም ተደራሽ ለማድረግ ትልቅ አቅም ይኖረዋል።
ከቁንጅና ውድድር ባለፈ፦ የቱሪዝም አምባሳደሮች!🔎
የፕሮጀክቱ ስራ አስኪያጅ መቅድም ደረጀ እንዳብራሩት፣ "Face of Ethiopia" ከተለመዱት የውበት ውድድሮች ለየት ያለ አካሄድ አለው።
ተወዳዳሪዎች ስለሚወክሏቸው ክልሎች ባህል፣ ታሪክና የቱሪዝም እምቅ ሀብት ጥልቅ ስልጠና የሚሰጣቸው ሲሆን፣ ይህም ወጣቶቹ በመድረክ ላይ ከመታየት ባለፈ የሀገራቸው እውነተኛ "የቱሪዝም አምባሳደሮች" እንዲሆኑ ያስችላቸዋል።
እንዴት መመዝገብ ይቻላል?
የቲክቶክ ፈጣሪዎች ያላቸውን ሰፊ ተደራሽነት በመጠቀም ፕሮጀክቱን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ የታቀደ ሲሆን፣ በውድድሩ ላይ መሳተፍ ለሚፈልጉ ወጣቶች ምዝገባ መጀመሩ ተበስሯል።
* የምዝገባ ድረ-ገጽ፦
www.faceofethiopia.et
ኢትዮጵያን በዲጂታሉ ዓለም በአዲስ መልክ ለማስተዋወቅ የሚደረገው ይህ ጉዞ፣ ለቱሪዝም ዘርፉ ትልቅ እመርታ እንደሚሆን ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #faceofethiopia #landoforigins #visitethiopia #tourismethiopia #gpower #digitalpromotion #ethiopia #tiktokethiopia
5 months ago
የተጓዥ ኪነ-ጥበብ ጉዞ ወደ ንጉሥ ካዎ ጦና ምድር! 🎭✨
#ethiopia | የተጓዥ ኪነ-ጥበብ መርሐ-ግብር ሁለተኛ ዙር ጉዞውን በተፈጥሮ ሀብት በታደለችውና ታሪካዊቷ ወላይታ ሶዶ በደማቅ ሁኔታ ጀምሯል። ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ ወመዘክር እና ባይራ ትሬዲንግ በጋራ ባዘጋጁት በዚህ መርሐ-ግብር ደራሲያን፣ ገጣሚያንና ጋዜጠኞች የንባብና የባህል ግንዛቤን ለህዝቡ ለማድረስ ተገኝተዋል።
📍 የወላይታ ሶዶ የማይታለፉ የቱሪስት መስህቦች፦
1. ተፈጥሯዊ ድንቆች፦
ዳሞታ ተራራ (Mount Damota)፦ ለከተማዋ ግርማ ሞገስ የሰጠ፣ ለተራራ መውጣት (Hiking) እና ለፓራግላይዲንግ ምቹ የሆነ ድንቅ ስፍራ።
2. ባህላዊና ታሪካዊ እሴቶች፦
የወላይታ ባህል ማዕከል፦ የሕዝቡን ታሪክና ቁሳቁስ በጎጆ መልክ በተገነባ ሙዚየም የሚዘክር።
ጣፋጭ ምግቦች፦ የወላይታ "ሙቾ" (ቆጮና ቅቤ) እና ማራኪው የቡና አፈላል ሥርዓት።
ጊፋታ (Giffata)፦ የወላይታ ዘመን መለወጫ በዓልና ድንቅ ባህላዊ ጭፈራዎች።
✨ የነገው መርሐ-ግብር፦
በነገው ዕለት በሶዶ ከተማ ታዋቂ ደራሲያንና ገጣሚያን የኪነ-ጥበብ ስራዎቻቸውን ለህዝቡ የሚያቀርቡ ሲሆን፣ ታሪክንና ቱሪዝምን ለማበልጸግ ትልቅ ግንዛቤ ይፈጠራል ተብሎ ይጠበቃል።
#ኢትዮጵያ #ወላይታሶዶ #ቱሪዝም #የተጓዥኪነጥበብ #ዳሞታተራራ #አጆራፏፏቴ #ባህል #ethiopia #visitwolaita #tourismethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
#ethiopia | የተጓዥ ኪነ-ጥበብ መርሐ-ግብር ሁለተኛ ዙር ጉዞውን በተፈጥሮ ሀብት በታደለችውና ታሪካዊቷ ወላይታ ሶዶ በደማቅ ሁኔታ ጀምሯል። ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ ወመዘክር እና ባይራ ትሬዲንግ በጋራ ባዘጋጁት በዚህ መርሐ-ግብር ደራሲያን፣ ገጣሚያንና ጋዜጠኞች የንባብና የባህል ግንዛቤን ለህዝቡ ለማድረስ ተገኝተዋል።
📍 የወላይታ ሶዶ የማይታለፉ የቱሪስት መስህቦች፦
1. ተፈጥሯዊ ድንቆች፦
ዳሞታ ተራራ (Mount Damota)፦ ለከተማዋ ግርማ ሞገስ የሰጠ፣ ለተራራ መውጣት (Hiking) እና ለፓራግላይዲንግ ምቹ የሆነ ድንቅ ስፍራ።
2. ባህላዊና ታሪካዊ እሴቶች፦
የወላይታ ባህል ማዕከል፦ የሕዝቡን ታሪክና ቁሳቁስ በጎጆ መልክ በተገነባ ሙዚየም የሚዘክር።
ጣፋጭ ምግቦች፦ የወላይታ "ሙቾ" (ቆጮና ቅቤ) እና ማራኪው የቡና አፈላል ሥርዓት።
ጊፋታ (Giffata)፦ የወላይታ ዘመን መለወጫ በዓልና ድንቅ ባህላዊ ጭፈራዎች።
✨ የነገው መርሐ-ግብር፦
በነገው ዕለት በሶዶ ከተማ ታዋቂ ደራሲያንና ገጣሚያን የኪነ-ጥበብ ስራዎቻቸውን ለህዝቡ የሚያቀርቡ ሲሆን፣ ታሪክንና ቱሪዝምን ለማበልጸግ ትልቅ ግንዛቤ ይፈጠራል ተብሎ ይጠበቃል።
#ኢትዮጵያ #ወላይታሶዶ #ቱሪዝም #የተጓዥኪነጥበብ #ዳሞታተራራ #አጆራፏፏቴ #ባህል #ethiopia #visitwolaita #tourismethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
Sponsored by
Surafel
5 months ago
የበላይነህ ክንዴ ግሩፕ "ሂልተን ባህር ዳር" ግንባታ ተጠናክሮ ቀጥሏል
#ethiopia | ታዋቂው የንግድ ተቋም በላይነህ ክንዴ ግሩፕ (BKG) በአማራ ክልል ርዕሰ መዲና ባህር ዳር ከተማ እያስገነባ የሚገኘው የ"ሂልተን ባህር ዳር" ሆቴል ግንባታ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ። ግሩፑ ሆቴሉን በአጭር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት የሚያስችሉ የሥራ ሂደቶች ውጤት እያሳዩ መሆኑን ገልጿል።
የግሩፑ ተከታታይ ስኬቶች
በላይነህ ክንዴ ግሩፕ በኢንቨስትመንት ዘርፍ ያለውን ተነሳሽነት በተግባር እያሳየ የሚገኝ ሲሆን፣ በቅርቡ የሚከተሉትን መጠነ ሰፊ ፕሮጀክቶች መያዙ ይታወቃል፡
* ሎጎ ሀይቅ ሪዞርት፡ በቅርቡ ግንባታው በጥራትና በፍጥነት ተጠናቆ ለምረቃ የበቃው ይህ ሪዞርት፣ የግሩፑን የአፈጻጸም ብቃት ማሳያ ሆኗል።
* አዳማ ራስ ሆቴል፡ በባህር ዳሩ ፕሮጀክት ጎን ለጎን፣ በአዳማ ከተማ የሚገኘውን የአዳማ ራስ ሆቴል የማጠናቀቂያ ሥራዎችን በከፍተኛ ትኩረት እያከናወነ ይገኛል።
ይህ በባህር ዳር እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ሆቴል፣ ከተማዋ ያላትን የቱሪስት መስህብነት ይበልጥ ከማሳደጉም በላይ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiopia #bahirdar #hiltonbahirdar #aradafm #belaynehkindegroup #investment #tourismethiopia #development
#ethiopia | ታዋቂው የንግድ ተቋም በላይነህ ክንዴ ግሩፕ (BKG) በአማራ ክልል ርዕሰ መዲና ባህር ዳር ከተማ እያስገነባ የሚገኘው የ"ሂልተን ባህር ዳር" ሆቴል ግንባታ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ። ግሩፑ ሆቴሉን በአጭር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት የሚያስችሉ የሥራ ሂደቶች ውጤት እያሳዩ መሆኑን ገልጿል።
የግሩፑ ተከታታይ ስኬቶች
በላይነህ ክንዴ ግሩፕ በኢንቨስትመንት ዘርፍ ያለውን ተነሳሽነት በተግባር እያሳየ የሚገኝ ሲሆን፣ በቅርቡ የሚከተሉትን መጠነ ሰፊ ፕሮጀክቶች መያዙ ይታወቃል፡
* ሎጎ ሀይቅ ሪዞርት፡ በቅርቡ ግንባታው በጥራትና በፍጥነት ተጠናቆ ለምረቃ የበቃው ይህ ሪዞርት፣ የግሩፑን የአፈጻጸም ብቃት ማሳያ ሆኗል።
* አዳማ ራስ ሆቴል፡ በባህር ዳሩ ፕሮጀክት ጎን ለጎን፣ በአዳማ ከተማ የሚገኘውን የአዳማ ራስ ሆቴል የማጠናቀቂያ ሥራዎችን በከፍተኛ ትኩረት እያከናወነ ይገኛል።
ይህ በባህር ዳር እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ሆቴል፣ ከተማዋ ያላትን የቱሪስት መስህብነት ይበልጥ ከማሳደጉም በላይ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiopia #bahirdar #hiltonbahirdar #aradafm #belaynehkindegroup #investment #tourismethiopia #development
6 months ago
🌊 የወሎ አዲሱ የቱሪዝም ፈርጥ - ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት! 🇪🇹
#ethiopia | በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ 'የገበታ ለትውልድ' ውጥን የተገነባው ዘመናዊው ሪዞርት
በ13.3 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው እና የወሎን ተፈጥሮ ከዘመናዊ የቱሪዝም አገልግሎት ጋር ያሰናኘው ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት፤ ኢትዮጵያ በቱሪዝም ዘርፍ ያላትን እምቅ አቅም የሚያሳይ አዲስ መዳረሻ ሆኗል።
ሪዞርቱ ምን ይዟል?
✅ ዓለም አቀፍ ደረጃ:
ዘመናዊ ምግብ ቤቶች እና መኝታ ክፍሎች።
✅ መዝናኛ:
የመዋኛ ገንዳዎች እና ለዓይን የሚማርኩ አረንጓዴ ስፍራዎች።
✅ መሰረተ ልማት:
የውስጥ ለውስጥ አስፋልት መንገዶች እና የሄሊኮፕተር ማረፊያ (Helipad)።
✅ ተፈጥሮ:
በተለያዩ የፍራፍሬ ዞኖች እና በደን የተከበበ መሆኑ ልዩ ትውስታን ይፈጥራል።
ይህ ፕሮጀክት የወሎን ህዝብ ባህላዊ እና ተፈጥሯዊ እሴቶች ለዓለም በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ ሚና ይጫወታል።
#logolakeresort #wollo #tourismethiopia #dineforgenerations #gebetaletewled #pmabiy #ethiopia #nature #resort #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
#ethiopia | በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ 'የገበታ ለትውልድ' ውጥን የተገነባው ዘመናዊው ሪዞርት
በ13.3 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው እና የወሎን ተፈጥሮ ከዘመናዊ የቱሪዝም አገልግሎት ጋር ያሰናኘው ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት፤ ኢትዮጵያ በቱሪዝም ዘርፍ ያላትን እምቅ አቅም የሚያሳይ አዲስ መዳረሻ ሆኗል።
ሪዞርቱ ምን ይዟል?
✅ ዓለም አቀፍ ደረጃ:
ዘመናዊ ምግብ ቤቶች እና መኝታ ክፍሎች።
✅ መዝናኛ:
የመዋኛ ገንዳዎች እና ለዓይን የሚማርኩ አረንጓዴ ስፍራዎች።
✅ መሰረተ ልማት:
የውስጥ ለውስጥ አስፋልት መንገዶች እና የሄሊኮፕተር ማረፊያ (Helipad)።
✅ ተፈጥሮ:
በተለያዩ የፍራፍሬ ዞኖች እና በደን የተከበበ መሆኑ ልዩ ትውስታን ይፈጥራል።
ይህ ፕሮጀክት የወሎን ህዝብ ባህላዊ እና ተፈጥሯዊ እሴቶች ለዓለም በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ ሚና ይጫወታል።
#logolakeresort #wollo #tourismethiopia #dineforgenerations #gebetaletewled #pmabiy #ethiopia #nature #resort #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
7 months ago
🍴 ሼፍ ማርከስ ልምዱን አካፈለ
#ethiopia | በሳይንስ ሙዚየም በተካሄደ ልዩ መድረክ፣ አዲስ አበባ የቱሪዝም መዳረሻነቷ እየጎላ በመምጣቱ የኢትዮጵያ የምግብ አሰራር ባህል ዘመኑን በዋጀ መልኩ ሊያድግ እንደሚገባ ጥሪ ቀረበ።
📈 የቱሪስቶች ፍሰትና የገበያ ዕድል
የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን ኮሚሽነር ሁንዴ ከበደ እንደገለጹት፣ ባለፉት ስድስት ወራት ብቻ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ቱሪስቶች መዲናዋን ጎብኝተዋል። ይህ ቁጥር የቱሪዝም ስነ-ምህዳሩን ለማሳደግ ትልቅ ዕድል የሚፈጥር ሲሆን፣ በተለይም ለምግብ ዝግጅት ባለሙያዎች እና ለሆቴሎች ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀ ልምድ እንዲያገኙ በር ከፋች መሆኑን ጠቁመዋል።
👨🍳 "ምግብ የታሪክ መግለጫ መሣሪያ ነው" — ማርከስ ሳሙኤልሰን
በዓለም አቀፍ ደረጃ ስመ-ጥር የሆኑት እና የስምንት ጊዜ የ"ጀምስ ቢርድ አዋርድ" አሸናፊው ባለሙያ ማርከስ ሳሙኤልሰን በመድረኩ ላይ ተገኝተው ንግግር አድርገዋል።
ማርከስ "ምግብ አንድ ሀገር ታሪኳን ለዓለም የምታስተዋውቅበት ታላቅ መሣሪያ ነው" ካሉ በኋላ፣ ኢትዮጵያ እጅግ አስደናቂ የምግብ ባህል እና ልዩ የፈጠራ አቅም እንዳላት መስክረዋል።
🏗️ ምግብ እንደ ብሔራዊ መሠረተ ልማት
የዘሌማን ኮሚኒኬሽን እና አካዳሚ ዳይሬክተር ዘላለም ወልደማርያም በበኩላቸው፣ የምግብ አሰራር ጥበብ ምግብን ከማቅረብ ባለፈ ብሔራዊ መሠረተ ልማትን የመገንባት ያህል ዋጋ እንዳለው ገልጸዋል። ይህ ዓይነቱ የልምድ ልውውጥ አዲስ አበባና ኢትዮጵያ ዓለምን በልህቀትና በራስ መተማመን ለመቀበል የሚያስችላቸውን አቅም እንደሚፈጥርም አክለዋል።
ቁልፍ ነጥቦች፦
* የቱሪስት ቁጥር፦ ግማሽ ሚሊዮን (በ6 ወራት)
* ልዩ እንግዳ፦ ማርከስ ሳሙኤልሰን (ታዋቂው የምግብ ባለሙያ)
* ዋና ጭብጥ፦ የምግብ አሰራር ባህልን ለቱሪዝም እድገት መጠቀም
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#አዲስአበባ #ቱሪዝም #የኢትዮጵያምግብ #ማርከስሳሙኤልሰን #ሳይንስሙዚየም #ኢትዮጵያ #addisababa #tourismethiopia #marcussamuelsson #gastronomy
#ethiopia | በሳይንስ ሙዚየም በተካሄደ ልዩ መድረክ፣ አዲስ አበባ የቱሪዝም መዳረሻነቷ እየጎላ በመምጣቱ የኢትዮጵያ የምግብ አሰራር ባህል ዘመኑን በዋጀ መልኩ ሊያድግ እንደሚገባ ጥሪ ቀረበ።
📈 የቱሪስቶች ፍሰትና የገበያ ዕድል
የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን ኮሚሽነር ሁንዴ ከበደ እንደገለጹት፣ ባለፉት ስድስት ወራት ብቻ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ቱሪስቶች መዲናዋን ጎብኝተዋል። ይህ ቁጥር የቱሪዝም ስነ-ምህዳሩን ለማሳደግ ትልቅ ዕድል የሚፈጥር ሲሆን፣ በተለይም ለምግብ ዝግጅት ባለሙያዎች እና ለሆቴሎች ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀ ልምድ እንዲያገኙ በር ከፋች መሆኑን ጠቁመዋል።
👨🍳 "ምግብ የታሪክ መግለጫ መሣሪያ ነው" — ማርከስ ሳሙኤልሰን
በዓለም አቀፍ ደረጃ ስመ-ጥር የሆኑት እና የስምንት ጊዜ የ"ጀምስ ቢርድ አዋርድ" አሸናፊው ባለሙያ ማርከስ ሳሙኤልሰን በመድረኩ ላይ ተገኝተው ንግግር አድርገዋል።
ማርከስ "ምግብ አንድ ሀገር ታሪኳን ለዓለም የምታስተዋውቅበት ታላቅ መሣሪያ ነው" ካሉ በኋላ፣ ኢትዮጵያ እጅግ አስደናቂ የምግብ ባህል እና ልዩ የፈጠራ አቅም እንዳላት መስክረዋል።
🏗️ ምግብ እንደ ብሔራዊ መሠረተ ልማት
የዘሌማን ኮሚኒኬሽን እና አካዳሚ ዳይሬክተር ዘላለም ወልደማርያም በበኩላቸው፣ የምግብ አሰራር ጥበብ ምግብን ከማቅረብ ባለፈ ብሔራዊ መሠረተ ልማትን የመገንባት ያህል ዋጋ እንዳለው ገልጸዋል። ይህ ዓይነቱ የልምድ ልውውጥ አዲስ አበባና ኢትዮጵያ ዓለምን በልህቀትና በራስ መተማመን ለመቀበል የሚያስችላቸውን አቅም እንደሚፈጥርም አክለዋል።
ቁልፍ ነጥቦች፦
* የቱሪስት ቁጥር፦ ግማሽ ሚሊዮን (በ6 ወራት)
* ልዩ እንግዳ፦ ማርከስ ሳሙኤልሰን (ታዋቂው የምግብ ባለሙያ)
* ዋና ጭብጥ፦ የምግብ አሰራር ባህልን ለቱሪዝም እድገት መጠቀም
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#አዲስአበባ #ቱሪዝም #የኢትዮጵያምግብ #ማርከስሳሙኤልሰን #ሳይንስሙዚየም #ኢትዮጵያ #addisababa #tourismethiopia #marcussamuelsson #gastronomy
7 months ago
🍽️ ክትፎን ጨምሮ አራት የጉራጌ ዕሴቶች ወደ ዩኔስኮ (UNESCO) ሊያመሩ ነው
#ethiopia | የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ፣ ታዋቂውን የጉራጌ ክትፎን ጨምሮ አራት የጉራጌ ባህላዊ እሴቶችን በዓለም የማይዳሰሱ ቅርሶች ዝርዝር ውስጥ ለማስመዝገብ ጥናት መጀመሩን አስታወቀ።
🥩 ክትፎ፦ ከምግብነት በላይ የሆነ የማንነት መገለጫ
የጉራጌ ክትፎ በዩኔስኮ ቅድሚያ ከተሰጣቸው እሴቶች መካከል ቀዳሚው ነው። ክትፎ ለጉራጌ ማህበረሰብ ምግብ ብቻ ሳይሆን የእንግዳ መቀበያ፣ የማህበራዊ ትስስር እና የጥበብ መገለጫ ነው። በአሁኑ ወቅት የክትፎ አዘገጃጀት፣ ከቆጮ፣ ከሚጥሚጣ እና ከንጥር ቅቤ ጋር ያለው ቁርኝት በጥልቀት እየተጠና ይገኛል።
📜 ሊመዘገቡ የታጩት አራት የኩራት ምንጮች፦
* የክትፎ አዘገጃጀት ጥበብ፦ ልዩ የሆነው የማክተፍ፣ የቅመማ ቅመም አጠቃቀምና የማቅረብ ስነስርዓት።
* ባህላዊ የክብ ቤት አሰራር፦ ያለ ሚስማር የሚገነባውና ለዘመናት የሚቆየው፣ የምህንድስና ጥበብ የታየበት የቤት አሰራር።
* የጎርደና የዳኝነት ስርአት፦ ለማህበራዊ ሰላምና ፍትህ የሚጠቀሙበት ጥንታዊና ውጤታማ የዳኝነት ስርዓት።
* የጀፎረ (መንደር) አወቃቀር፦ ለጋራ መስተጋብር በሚመች መልኩ የሚሰሩ ሰፋፊ መንገዶችና ማራኪ የመንደር አቀማመጥ።
📍 የጥናቱ ሂደት ምን ደረጃ ላይ ይገኛል?
የመምሪያው ኃላፊ ወይዘሮ መሰረት አመረጋ እንደገለጹት፣ ለኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን የቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቷል። ጥናቱ እንደተጠናቀቀ ሰነዱ በቀጥታ በፈረንሳይ ፓሪስ ለሚገኘው የዩኔስኮ ዋና መስሪያ ቤት ለውሳኔ ይላካል።
ከዚህ በተጨማሪ በዞኑ የሚገኙ ዕድሜ ጠገብ መስጂዶች፣ ጥንታዊ ኪታቦች፣ ገዳማትና ታሪካዊ ዋሻዎች ለቱሪስት መስህብነት እንዲውሉ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ጉራጌ #ክትፎ #ዩኔስኮ #ቅርስ #ኢትዮጵያ #ባህል #ቱሪዝም #የጉራጌባህል #gurage #kitfo #unesco #ethiopianheritage #tourismethiopia
#ethiopia | የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ፣ ታዋቂውን የጉራጌ ክትፎን ጨምሮ አራት የጉራጌ ባህላዊ እሴቶችን በዓለም የማይዳሰሱ ቅርሶች ዝርዝር ውስጥ ለማስመዝገብ ጥናት መጀመሩን አስታወቀ።
🥩 ክትፎ፦ ከምግብነት በላይ የሆነ የማንነት መገለጫ
የጉራጌ ክትፎ በዩኔስኮ ቅድሚያ ከተሰጣቸው እሴቶች መካከል ቀዳሚው ነው። ክትፎ ለጉራጌ ማህበረሰብ ምግብ ብቻ ሳይሆን የእንግዳ መቀበያ፣ የማህበራዊ ትስስር እና የጥበብ መገለጫ ነው። በአሁኑ ወቅት የክትፎ አዘገጃጀት፣ ከቆጮ፣ ከሚጥሚጣ እና ከንጥር ቅቤ ጋር ያለው ቁርኝት በጥልቀት እየተጠና ይገኛል።
📜 ሊመዘገቡ የታጩት አራት የኩራት ምንጮች፦
* የክትፎ አዘገጃጀት ጥበብ፦ ልዩ የሆነው የማክተፍ፣ የቅመማ ቅመም አጠቃቀምና የማቅረብ ስነስርዓት።
* ባህላዊ የክብ ቤት አሰራር፦ ያለ ሚስማር የሚገነባውና ለዘመናት የሚቆየው፣ የምህንድስና ጥበብ የታየበት የቤት አሰራር።
* የጎርደና የዳኝነት ስርአት፦ ለማህበራዊ ሰላምና ፍትህ የሚጠቀሙበት ጥንታዊና ውጤታማ የዳኝነት ስርዓት።
* የጀፎረ (መንደር) አወቃቀር፦ ለጋራ መስተጋብር በሚመች መልኩ የሚሰሩ ሰፋፊ መንገዶችና ማራኪ የመንደር አቀማመጥ።
📍 የጥናቱ ሂደት ምን ደረጃ ላይ ይገኛል?
የመምሪያው ኃላፊ ወይዘሮ መሰረት አመረጋ እንደገለጹት፣ ለኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን የቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቷል። ጥናቱ እንደተጠናቀቀ ሰነዱ በቀጥታ በፈረንሳይ ፓሪስ ለሚገኘው የዩኔስኮ ዋና መስሪያ ቤት ለውሳኔ ይላካል።
ከዚህ በተጨማሪ በዞኑ የሚገኙ ዕድሜ ጠገብ መስጂዶች፣ ጥንታዊ ኪታቦች፣ ገዳማትና ታሪካዊ ዋሻዎች ለቱሪስት መስህብነት እንዲውሉ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ጉራጌ #ክትፎ #ዩኔስኮ #ቅርስ #ኢትዮጵያ #ባህል #ቱሪዝም #የጉራጌባህል #gurage #kitfo #unesco #ethiopianheritage #tourismethiopia
7 months ago
ከ900 ሺህ በላይ ቱሪስቶች በልደት በዓል ላሊበላ ታደሙ
#ethiopia | የኢየሱስ ክርስቶስ እና የቅዱስ ላሊበላ የልደት በዓል (ገና) በዓለም ቅርስ በሆነችው የላሊበላ ከተማ በታላቅ ድምቀት ተከብሯል።
በዘንድሮው በዓል ላይ ከ900 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ እና ከ1 ሺህ 200 በላይ የውጭ ሀገራት ቱሪስቶች መታደማቸውን የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ መሳይ ወዳጄ አስታውቀዋል።
✅ ለበዓሉ የተደረጉ ዝግጅቶች
በዓሉ በሰላም እና በድምቀት እንዲጠናቀቅ ከአንድ ወር በፊት ስድስት የተለያዩ ኮሚቴዎች ተቋቁመው ሲሰሩ መቆየታቸውን ከንቲባው ገልጸዋል። ለቱሪስቶች ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፦
* የመሠረተ ልማት ዝግጅት፦ የኤሌክትሪክ፣ የውሃ እና የኮሙኒኬሽን አገልግሎቶች ያለ መቆራረጥ እንዲቀርቡ ተደርጓል።
* የእንግዳ ተቀባይነት ክትትል፦ ሆቴሎች ለተገቢው አገልግሎት ዝግጁ መሆናቸው፣ የአልጋ ንጽህና እና የምግብ ዝግጅት ጥራት በባለሙያዎች ክትትል ተደርጎበታል።
* የከተማ ውበት፦ የውቅር አብያተ ክርስቲያናቱ ግቢ እና አጠቃላይ ከተማዋ ሳቢና ማራኪ ሆና እንግዶችን እንድትቀበል ተደርጓል።
የላሊበላ ገና ለየት የሚያደርገው ምንድነው?
የላሊበላ ገና በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ በታሪካዊነቱ፣ በባህላዊ እሴቱ እና በሃይማኖታዊ ስነ-ስርዓቱ (በተለይም በቤዛ ኩሉ ዝማሬ) ይታወቃል። በዓሉን ለማክበር ወደ ስፍራው የሚሄዱ ቱሪስቶች፦
* ድንቅ የሆኑትን 11ዱን የውቅር አብያተ ክርስቲያናትን የመመልከት፣
* በዙሪያው ያሉ ታሪካዊ እና ተፈጥሯዊ ስፍራዎችን የመጎብኘት፣
* የጥንታዊቷን ኢትዮጵያ ስልጣኔ እና ጥበብ በአካል የመመስከር ዕድል ያገኛሉ።
ይህ የቱሪስት ቁጥር መጨመር ለከተማዋ የኢኮኖሚ መነቃቃት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው የተገለጸ ሲሆን፣ ላሊበላ አሁንም ቀዳሚዋ የኢትዮጵያ የቱሪስት መዳረሻ መሆኗን ዳግም አረጋግጣለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ላሊበላ #ገና #የልደትበዓል #ኢትዮጵያ #ቱሪዝም #ባህል #ታሪክ #lalibela #ethiopia #genna #christmasinethiopia #tourismethiopia
#ethiopia | የኢየሱስ ክርስቶስ እና የቅዱስ ላሊበላ የልደት በዓል (ገና) በዓለም ቅርስ በሆነችው የላሊበላ ከተማ በታላቅ ድምቀት ተከብሯል።
በዘንድሮው በዓል ላይ ከ900 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ እና ከ1 ሺህ 200 በላይ የውጭ ሀገራት ቱሪስቶች መታደማቸውን የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ መሳይ ወዳጄ አስታውቀዋል።
✅ ለበዓሉ የተደረጉ ዝግጅቶች
በዓሉ በሰላም እና በድምቀት እንዲጠናቀቅ ከአንድ ወር በፊት ስድስት የተለያዩ ኮሚቴዎች ተቋቁመው ሲሰሩ መቆየታቸውን ከንቲባው ገልጸዋል። ለቱሪስቶች ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፦
* የመሠረተ ልማት ዝግጅት፦ የኤሌክትሪክ፣ የውሃ እና የኮሙኒኬሽን አገልግሎቶች ያለ መቆራረጥ እንዲቀርቡ ተደርጓል።
* የእንግዳ ተቀባይነት ክትትል፦ ሆቴሎች ለተገቢው አገልግሎት ዝግጁ መሆናቸው፣ የአልጋ ንጽህና እና የምግብ ዝግጅት ጥራት በባለሙያዎች ክትትል ተደርጎበታል።
* የከተማ ውበት፦ የውቅር አብያተ ክርስቲያናቱ ግቢ እና አጠቃላይ ከተማዋ ሳቢና ማራኪ ሆና እንግዶችን እንድትቀበል ተደርጓል።
የላሊበላ ገና ለየት የሚያደርገው ምንድነው?
የላሊበላ ገና በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ በታሪካዊነቱ፣ በባህላዊ እሴቱ እና በሃይማኖታዊ ስነ-ስርዓቱ (በተለይም በቤዛ ኩሉ ዝማሬ) ይታወቃል። በዓሉን ለማክበር ወደ ስፍራው የሚሄዱ ቱሪስቶች፦
* ድንቅ የሆኑትን 11ዱን የውቅር አብያተ ክርስቲያናትን የመመልከት፣
* በዙሪያው ያሉ ታሪካዊ እና ተፈጥሯዊ ስፍራዎችን የመጎብኘት፣
* የጥንታዊቷን ኢትዮጵያ ስልጣኔ እና ጥበብ በአካል የመመስከር ዕድል ያገኛሉ።
ይህ የቱሪስት ቁጥር መጨመር ለከተማዋ የኢኮኖሚ መነቃቃት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው የተገለጸ ሲሆን፣ ላሊበላ አሁንም ቀዳሚዋ የኢትዮጵያ የቱሪስት መዳረሻ መሆኗን ዳግም አረጋግጣለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ላሊበላ #ገና #የልደትበዓል #ኢትዮጵያ #ቱሪዝም #ባህል #ታሪክ #lalibela #ethiopia #genna #christmasinethiopia #tourismethiopia
7 months ago
በሬዲዮ በምናብ ያስቃኘን ድምፅ፤ አሁን በምስል መጣ! 🇪🇹🎥
"ጋዜጠኛ አስቻለው ጌታቸው አዲስ የዩቲዩብ ቻናል ከፈተ"
#ethiopia | ለ10 ዓመታት በኢትዮጵያ ሬዲዮ "ኢትዮጵያን እንቃኛት" ፕሮግራም፤ የሀገራችንን ውብ የተፈጥሮ ፓርኮች እና አስቸጋሪ የመልክዓ ምድር አቀማመጦች በምናብ ስናይ እንደነበር ይታወሳል።
ያንን ውብ ድምፅ እና የጉዞ ታሪክ የተሸከመው ጋዜጠኛ አስቻለው ጌታቸው፤ አሁን ደግሞ በምስል ሊያስቃኘን "የጋዜጠኛው ቱሪስት" (The Journalist Tourist) በሚል አዲስ የዩቲዩብ ቻናል መጥቷል!
ጋዜጠኛ አስቻለው ማን ነው?
✅ ተወልዶ ያደገው በተፈጥሮ መስህቡ ባሌ ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ ነው።
✅ በሰሜን ተራራዎች ከቧሂት እስከ ራስ ዳሸን፣ በጋምቤላ አስቸጋሪ ረግረጋማ ቦታዎች እና በሌሎችም ፈታኝ ስፍራዎች ተጉዞ ኢትዮጵያን አስተዋውቋል።
✅ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን (ETV) በዶክመንተሪ እና በኤዲተርነት ለ6 ዓመታት አገልግሏል።
✅ አሁን ደግሞ "ማውንቴንስ ሚዲያ"ን አቋቁሞ በቱሪዝም እና ተፈጥሮ ጥበቃ ላይ እየሰራ ይገኛል።
የኢትዮጵያን የቱሪዝም ሀብት በልዩ አቀራረብ ለማየት የዩቲዩብ ቻናሉን Subscribe በማድረግ ቤተሰብ እንሁን፣ እናበረታታው!
👇
🔗 ሊንኩን ይጫኑ: https://www.youtube.com/@%...
መልካም በዓል! 🎄
#aschalewgetachew #ethiopianenkangnat #tourismethiopia #travel #newchannel #ethiopia
"ጋዜጠኛ አስቻለው ጌታቸው አዲስ የዩቲዩብ ቻናል ከፈተ"
#ethiopia | ለ10 ዓመታት በኢትዮጵያ ሬዲዮ "ኢትዮጵያን እንቃኛት" ፕሮግራም፤ የሀገራችንን ውብ የተፈጥሮ ፓርኮች እና አስቸጋሪ የመልክዓ ምድር አቀማመጦች በምናብ ስናይ እንደነበር ይታወሳል።
ያንን ውብ ድምፅ እና የጉዞ ታሪክ የተሸከመው ጋዜጠኛ አስቻለው ጌታቸው፤ አሁን ደግሞ በምስል ሊያስቃኘን "የጋዜጠኛው ቱሪስት" (The Journalist Tourist) በሚል አዲስ የዩቲዩብ ቻናል መጥቷል!
ጋዜጠኛ አስቻለው ማን ነው?
✅ ተወልዶ ያደገው በተፈጥሮ መስህቡ ባሌ ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ ነው።
✅ በሰሜን ተራራዎች ከቧሂት እስከ ራስ ዳሸን፣ በጋምቤላ አስቸጋሪ ረግረጋማ ቦታዎች እና በሌሎችም ፈታኝ ስፍራዎች ተጉዞ ኢትዮጵያን አስተዋውቋል።
✅ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን (ETV) በዶክመንተሪ እና በኤዲተርነት ለ6 ዓመታት አገልግሏል።
✅ አሁን ደግሞ "ማውንቴንስ ሚዲያ"ን አቋቁሞ በቱሪዝም እና ተፈጥሮ ጥበቃ ላይ እየሰራ ይገኛል።
የኢትዮጵያን የቱሪዝም ሀብት በልዩ አቀራረብ ለማየት የዩቲዩብ ቻናሉን Subscribe በማድረግ ቤተሰብ እንሁን፣ እናበረታታው!
👇
🔗 ሊንኩን ይጫኑ: https://www.youtube.com/@%...
መልካም በዓል! 🎄
#aschalewgetachew #ethiopianenkangnat #tourismethiopia #travel #newchannel #ethiopia
Sponsored by
Surafel
7 months ago
🚆 የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ፃፈ
* በቀን 14 ባቡሮች በመስመር ላይ
#ethiopia | የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር አገልግሎት መጀመሩን ተከትሎ ታይቶ የማይታወቅ አዲስ የሥራ ክንውን ማስመዝገቡን አስታወቀ። ተቋሙ በአንድ ቀን ብቻ 14 ባቡሮችን (7 የባቡር ጥንዶችን) በተሳካ ሁኔታ በማንቀሳቀስ የሎጂስቲክስ አቅሙን ለዓለም አሳይቷል።
📦 የጭነት ትራንስፖርት ስኬት
ከተሰማሩት 14 ባቡሮች መካከል 11ዱ የጭነት ባቡሮች ሲሆኑ፣ ከእነዚህም ውስጥ፦
4ቱ የኢትዮጵያን ምርት ወደ ውጭ የላኩ (Export)፣
7ቱ ደግሞ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ (Import) የንግድ ቁሳቁሶችን የጫኑ ናቸው።
ይህም ተቋሙ የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ በታመነ እና ቀልጣፋ መንገድ የመሸከም ብቃቱን በተግባር ያረጋገጠበት ሆኗል።
Passenger & Tourism | የመንገደኞችና የቱሪዝም አገልግሎት
በእለቱ ከጭነት ባሻገር በመንገደኞች ዘርፍም የላቀ አፈፃፀም ተመዝግቧል። በቀን ውስጥ 3 የመንገደኞች ባቡሮች አገልግሎት የሰጡ ሲሆን፦
አንድ የሀገር ውስጥ የባቡር ጉዞ፣
አንድ ዓለም አቀፍ (አዲስ አበባ - ጅቡቲ) ጉዞ፣
አንድ ልዩ የቱሪዝም ፓኬጅ አገልግሎት ተከናውኗል።
🚀 የወደፊት ዕቅድ
የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር (EDR) በዚህ ስኬት ሳይወሰን፣ በቅርብ ጊዜ ውስጥ በቀን የሚንቀሳቀሱ የባቡር ስብስቦችን ወደ 16 (8 የባቡር ጥንዶች) ከፍ ለማድረግ አቅዶ እየሰራ ይገኛል። ይህም የሀገሪቱን የዲጂታልና የኢኮኖሚ ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል።
#ethiopia #djibouti #edr #railwaysuccess #logistics #tourismethiopia #economicgrowth #ethiodjiboutirailway
* በቀን 14 ባቡሮች በመስመር ላይ
#ethiopia | የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር አገልግሎት መጀመሩን ተከትሎ ታይቶ የማይታወቅ አዲስ የሥራ ክንውን ማስመዝገቡን አስታወቀ። ተቋሙ በአንድ ቀን ብቻ 14 ባቡሮችን (7 የባቡር ጥንዶችን) በተሳካ ሁኔታ በማንቀሳቀስ የሎጂስቲክስ አቅሙን ለዓለም አሳይቷል።
📦 የጭነት ትራንስፖርት ስኬት
ከተሰማሩት 14 ባቡሮች መካከል 11ዱ የጭነት ባቡሮች ሲሆኑ፣ ከእነዚህም ውስጥ፦
4ቱ የኢትዮጵያን ምርት ወደ ውጭ የላኩ (Export)፣
7ቱ ደግሞ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ (Import) የንግድ ቁሳቁሶችን የጫኑ ናቸው።
ይህም ተቋሙ የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ በታመነ እና ቀልጣፋ መንገድ የመሸከም ብቃቱን በተግባር ያረጋገጠበት ሆኗል።
Passenger & Tourism | የመንገደኞችና የቱሪዝም አገልግሎት
በእለቱ ከጭነት ባሻገር በመንገደኞች ዘርፍም የላቀ አፈፃፀም ተመዝግቧል። በቀን ውስጥ 3 የመንገደኞች ባቡሮች አገልግሎት የሰጡ ሲሆን፦
አንድ የሀገር ውስጥ የባቡር ጉዞ፣
አንድ ዓለም አቀፍ (አዲስ አበባ - ጅቡቲ) ጉዞ፣
አንድ ልዩ የቱሪዝም ፓኬጅ አገልግሎት ተከናውኗል።
🚀 የወደፊት ዕቅድ
የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር (EDR) በዚህ ስኬት ሳይወሰን፣ በቅርብ ጊዜ ውስጥ በቀን የሚንቀሳቀሱ የባቡር ስብስቦችን ወደ 16 (8 የባቡር ጥንዶች) ከፍ ለማድረግ አቅዶ እየሰራ ይገኛል። ይህም የሀገሪቱን የዲጂታልና የኢኮኖሚ ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል።
#ethiopia #djibouti #edr #railwaysuccess #logistics #tourismethiopia #economicgrowth #ethiodjiboutirailway
Comments