4 hours ago
ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ2027 የሚካሄደውን የዓለም አቀፍ የፀረ-ዶፒንግ ትምህርት ጉባኤን እንድታስተናግድ በይፋ ተመረጠች
#ethiopia | ሀገራችን ኢትዮጵያ ለስፖርቱ ዘርፍ ዕድገት ለሰጠችው ልዩ ትኩረት ትልቅ ማሳያ የሚሆንና ከፍተኛ ፋይዳ ያለው ዓለም አቀፍ የባህልና የስፖርት ኩነትን የማዘጋጀት ዕድል አግኝታለች።
በዓለም አቀፉ የፀረ-ዶፒንግ ኤጀንሲ አስተናጋጅነት በየወቅቱ የሚካሄደው የዓለም አቀፍ የፀረ-ዶፒንግ ትምህርትና ሥልጠና ጉባኤ በፈረንጆቹ 2027 በኢትዮጵያ እንዲሰናዳ ተወስኗል።
ይህ ትልቅ መድረክ በፀረ-አበረታች ቅመሞች እንቅስቃሴ ላይ ሰፊ ተፅዕኖ ያለው ሲሆን ቀደም ሲል እ.ኤ.አ በ2018 በቻይና ቤጂንግ፣ በ2022 በአውስትራሊያ ሲድኒ እንዲሁም በ2024 በፈረንሳይ ፓሪስ መካሄዱ ይታወሳል።
ይህ የዓለም አቀፍ የፀረ-ዶፒንግ ትምህርት ጉባኤ በአፍሪካ አህጉር ሲካሄድ የአሁኑ የመጀመሪያው ነው። በመሆኑም መድረኩ ለሀገራችን መልካም ገጽታ ግንባታና ለስፖርት ቱሪዝም ዕድገት ከሚያበረክተው ዘርፈ ብዙ ጥቅም ባለፈ በአህጉር ደረጃ ንጹህ ስፖርትን ለማስፋፋትና የፀረ-አበረታች ቅመሞች ቁጥጥርን ይበልጥ ለማጠናከር ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
ከምንም በላይ ደግሞ ኢትዮጵያ የአበረታች ቅመሞች ወይም የዶፒንግ መከላከል ሥራዎችን በመደበኛው የትምህርት ሥርዓት ውስጥ በማካተት፣ ጠንካራ የሕግ ማዕቀፎችን በማውጣት፣ እንዲሁም አስተማማኝ የምርመራና የቁጥጥር ሥርዓቶችን በመዘርጋት ረገድ ያስመዘገበቻቸውን በርካታ ስኬቶች ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በተግባር ለማሳየትና ለማስተዋወቅ ትልቅ ዕድል ይፈጥራል።
#wada #globaleducationconference #cleansport #antidoping #sportstourism #africasports #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ሀገራችን ኢትዮጵያ ለስፖርቱ ዘርፍ ዕድገት ለሰጠችው ልዩ ትኩረት ትልቅ ማሳያ የሚሆንና ከፍተኛ ፋይዳ ያለው ዓለም አቀፍ የባህልና የስፖርት ኩነትን የማዘጋጀት ዕድል አግኝታለች።
በዓለም አቀፉ የፀረ-ዶፒንግ ኤጀንሲ አስተናጋጅነት በየወቅቱ የሚካሄደው የዓለም አቀፍ የፀረ-ዶፒንግ ትምህርትና ሥልጠና ጉባኤ በፈረንጆቹ 2027 በኢትዮጵያ እንዲሰናዳ ተወስኗል።
ይህ ትልቅ መድረክ በፀረ-አበረታች ቅመሞች እንቅስቃሴ ላይ ሰፊ ተፅዕኖ ያለው ሲሆን ቀደም ሲል እ.ኤ.አ በ2018 በቻይና ቤጂንግ፣ በ2022 በአውስትራሊያ ሲድኒ እንዲሁም በ2024 በፈረንሳይ ፓሪስ መካሄዱ ይታወሳል።
ይህ የዓለም አቀፍ የፀረ-ዶፒንግ ትምህርት ጉባኤ በአፍሪካ አህጉር ሲካሄድ የአሁኑ የመጀመሪያው ነው። በመሆኑም መድረኩ ለሀገራችን መልካም ገጽታ ግንባታና ለስፖርት ቱሪዝም ዕድገት ከሚያበረክተው ዘርፈ ብዙ ጥቅም ባለፈ በአህጉር ደረጃ ንጹህ ስፖርትን ለማስፋፋትና የፀረ-አበረታች ቅመሞች ቁጥጥርን ይበልጥ ለማጠናከር ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
ከምንም በላይ ደግሞ ኢትዮጵያ የአበረታች ቅመሞች ወይም የዶፒንግ መከላከል ሥራዎችን በመደበኛው የትምህርት ሥርዓት ውስጥ በማካተት፣ ጠንካራ የሕግ ማዕቀፎችን በማውጣት፣ እንዲሁም አስተማማኝ የምርመራና የቁጥጥር ሥርዓቶችን በመዘርጋት ረገድ ያስመዘገበቻቸውን በርካታ ስኬቶች ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በተግባር ለማሳየትና ለማስተዋወቅ ትልቅ ዕድል ይፈጥራል።
#wada #globaleducationconference #cleansport #antidoping #sportstourism #africasports #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
ጋናዊው ወጣት ተጨዋች ዶምኒክ ፍሪምፖንግ በታጣቂዎች ጥቃት ተገደለ
#ethiopia | በጋና እግር ኳስ ሊግ ታሪክ እጅግ አሰቃቂ የተባለ ጥቃት በቤሬኩም ቼልሲ ክለብ ላይ ደርሷል። የክለቡ ተስፈኛ ተጨዋች የሆነው የ20 ዓመቱ ዶምኒክ ፍሪምፖንግ በታጠቁ ዘራፊዎች በተከፈተ ጥቃት ህይወቱ ማለፉ ተረጋግጧል።
ክለቡ ቤሬኩም ቼልሲ የሊግ ጨዋታውን አከናውኖ በባስ በመመለስ ላይ እያለ፣ ማንነታቸው ያልታወቁ የታጠቁ ዘራፊዎች ተሽከርካሪውን አስቁመው ጥቃት ከፍተዋል።
ወጣቱ ተጨዋች ዶምኒክ ፍሪምፖንግ በጭንቅላቱ ላይ በደረሰበት የጥይት ጉዳት ህይወቱ ወዲያውኑ አልፏል።
በጥቃቱ ሳቢያ በርካታ የቡድኑ ተጨዋቾችና የቴክኒክ አባላት ላይ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት የደረሰ ሲሆን፣ አንዳንድ የቡድኑ አባላት ደግሞ ያሉበት ደብዛ መጥፋቱ ተነግሯል።
የጋና እግር ኳስ ፌዴሬሽን (GFA) ባወጣው መግለጫ በድርጊቱ እጅግ ማዘኑን ገልጾ፣ ለተጨዋቹ ቤተሰቦችና ለክለቡ ደጋፊዎች መጽናናትን ተመኝቷል። ድርጊቱን የፈጸሙ አካላትን በቁጥጥር ስር ለማዋልም ምርመራ እየተካሄደ መሆኑ ተገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ #getutemesgen #getu #tikvahsport #ghana #berekumchelsea #dominicfrimpong #gfa #footballnews #africasports #ghanapremierleague #ጋና #እግርኳስ #አሳዛኝዜና
#ethiopia | በጋና እግር ኳስ ሊግ ታሪክ እጅግ አሰቃቂ የተባለ ጥቃት በቤሬኩም ቼልሲ ክለብ ላይ ደርሷል። የክለቡ ተስፈኛ ተጨዋች የሆነው የ20 ዓመቱ ዶምኒክ ፍሪምፖንግ በታጠቁ ዘራፊዎች በተከፈተ ጥቃት ህይወቱ ማለፉ ተረጋግጧል።
ክለቡ ቤሬኩም ቼልሲ የሊግ ጨዋታውን አከናውኖ በባስ በመመለስ ላይ እያለ፣ ማንነታቸው ያልታወቁ የታጠቁ ዘራፊዎች ተሽከርካሪውን አስቁመው ጥቃት ከፍተዋል።
ወጣቱ ተጨዋች ዶምኒክ ፍሪምፖንግ በጭንቅላቱ ላይ በደረሰበት የጥይት ጉዳት ህይወቱ ወዲያውኑ አልፏል።
በጥቃቱ ሳቢያ በርካታ የቡድኑ ተጨዋቾችና የቴክኒክ አባላት ላይ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት የደረሰ ሲሆን፣ አንዳንድ የቡድኑ አባላት ደግሞ ያሉበት ደብዛ መጥፋቱ ተነግሯል።
የጋና እግር ኳስ ፌዴሬሽን (GFA) ባወጣው መግለጫ በድርጊቱ እጅግ ማዘኑን ገልጾ፣ ለተጨዋቹ ቤተሰቦችና ለክለቡ ደጋፊዎች መጽናናትን ተመኝቷል። ድርጊቱን የፈጸሙ አካላትን በቁጥጥር ስር ለማዋልም ምርመራ እየተካሄደ መሆኑ ተገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ #getutemesgen #getu #tikvahsport #ghana #berekumchelsea #dominicfrimpong #gfa #footballnews #africasports #ghanapremierleague #ጋና #እግርኳስ #አሳዛኝዜና
Comments