2 months ago
ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ2027 የሚካሄደውን የዓለም አቀፍ የፀረ-ዶፒንግ ትምህርት ጉባኤን እንድታስተናግድ በይፋ ተመረጠች
#ethiopia | ሀገራችን ኢትዮጵያ ለስፖርቱ ዘርፍ ዕድገት ለሰጠችው ልዩ ትኩረት ትልቅ ማሳያ የሚሆንና ከፍተኛ ፋይዳ ያለው ዓለም አቀፍ የባህልና የስፖርት ኩነትን የማዘጋጀት ዕድል አግኝታለች።
በዓለም አቀፉ የፀረ-ዶፒንግ ኤጀንሲ አስተናጋጅነት በየወቅቱ የሚካሄደው የዓለም አቀፍ የፀረ-ዶፒንግ ትምህርትና ሥልጠና ጉባኤ በፈረንጆቹ 2027 በኢትዮጵያ እንዲሰናዳ ተወስኗል።
ይህ ትልቅ መድረክ በፀረ-አበረታች ቅመሞች እንቅስቃሴ ላይ ሰፊ ተፅዕኖ ያለው ሲሆን ቀደም ሲል እ.ኤ.አ በ2018 በቻይና ቤጂንግ፣ በ2022 በአውስትራሊያ ሲድኒ እንዲሁም በ2024 በፈረንሳይ ፓሪስ መካሄዱ ይታወሳል።
ይህ የዓለም አቀፍ የፀረ-ዶፒንግ ትምህርት ጉባኤ በአፍሪካ አህጉር ሲካሄድ የአሁኑ የመጀመሪያው ነው። በመሆኑም መድረኩ ለሀገራችን መልካም ገጽታ ግንባታና ለስፖርት ቱሪዝም ዕድገት ከሚያበረክተው ዘርፈ ብዙ ጥቅም ባለፈ በአህጉር ደረጃ ንጹህ ስፖርትን ለማስፋፋትና የፀረ-አበረታች ቅመሞች ቁጥጥርን ይበልጥ ለማጠናከር ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
ከምንም በላይ ደግሞ ኢትዮጵያ የአበረታች ቅመሞች ወይም የዶፒንግ መከላከል ሥራዎችን በመደበኛው የትምህርት ሥርዓት ውስጥ በማካተት፣ ጠንካራ የሕግ ማዕቀፎችን በማውጣት፣ እንዲሁም አስተማማኝ የምርመራና የቁጥጥር ሥርዓቶችን በመዘርጋት ረገድ ያስመዘገበቻቸውን በርካታ ስኬቶች ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በተግባር ለማሳየትና ለማስተዋወቅ ትልቅ ዕድል ይፈጥራል።
#wada #globaleducationconference #cleansport #antidoping #sportstourism #africasports #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ሀገራችን ኢትዮጵያ ለስፖርቱ ዘርፍ ዕድገት ለሰጠችው ልዩ ትኩረት ትልቅ ማሳያ የሚሆንና ከፍተኛ ፋይዳ ያለው ዓለም አቀፍ የባህልና የስፖርት ኩነትን የማዘጋጀት ዕድል አግኝታለች።
በዓለም አቀፉ የፀረ-ዶፒንግ ኤጀንሲ አስተናጋጅነት በየወቅቱ የሚካሄደው የዓለም አቀፍ የፀረ-ዶፒንግ ትምህርትና ሥልጠና ጉባኤ በፈረንጆቹ 2027 በኢትዮጵያ እንዲሰናዳ ተወስኗል።
ይህ ትልቅ መድረክ በፀረ-አበረታች ቅመሞች እንቅስቃሴ ላይ ሰፊ ተፅዕኖ ያለው ሲሆን ቀደም ሲል እ.ኤ.አ በ2018 በቻይና ቤጂንግ፣ በ2022 በአውስትራሊያ ሲድኒ እንዲሁም በ2024 በፈረንሳይ ፓሪስ መካሄዱ ይታወሳል።
ይህ የዓለም አቀፍ የፀረ-ዶፒንግ ትምህርት ጉባኤ በአፍሪካ አህጉር ሲካሄድ የአሁኑ የመጀመሪያው ነው። በመሆኑም መድረኩ ለሀገራችን መልካም ገጽታ ግንባታና ለስፖርት ቱሪዝም ዕድገት ከሚያበረክተው ዘርፈ ብዙ ጥቅም ባለፈ በአህጉር ደረጃ ንጹህ ስፖርትን ለማስፋፋትና የፀረ-አበረታች ቅመሞች ቁጥጥርን ይበልጥ ለማጠናከር ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
ከምንም በላይ ደግሞ ኢትዮጵያ የአበረታች ቅመሞች ወይም የዶፒንግ መከላከል ሥራዎችን በመደበኛው የትምህርት ሥርዓት ውስጥ በማካተት፣ ጠንካራ የሕግ ማዕቀፎችን በማውጣት፣ እንዲሁም አስተማማኝ የምርመራና የቁጥጥር ሥርዓቶችን በመዘርጋት ረገድ ያስመዘገበቻቸውን በርካታ ስኬቶች ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በተግባር ለማሳየትና ለማስተዋወቅ ትልቅ ዕድል ይፈጥራል።
#wada #globaleducationconference #cleansport #antidoping #sportstourism #africasports #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
5 months ago
አትሌት ድርቤ ወልተጂ የሁለት ዓመት እገዳ ተጣለባት!
#ethiopia | ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ድርቤ ወልተጂ፣ የዶፒንግ ምርመራ ለማድረግ ፍቃደኛ ባለመሆኗ ምክንያት በስፖርት ገላጋይ ፍርድ ቤት (CAS) የሁለት ዓመት እገዳ ተጥሎባታል።
የቅጣቱ ዝርዝር ነጥቦች፦
የቅጣቱ ምክንያት፦ የኢትዮጵያ ፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለሥልጣን ምርመራ እንዲደረግላት ቢጠይቃትም ፍቃደኛ ባለመሆኗ (Refusal to submit to sample collection)።
የእገዳው ጊዜ፦ ቅጣቱ እስከ 2027 ዓ.ም የሚቆይ ይሆናል።
የውጤት መሰረዝ፦ ከየካቲት 2025 ጀምሮ ያስመዘገበቻቸው ውጤቶች በሙሉ ውድቅ ተደርገዋል።
የሜዳሊያ መነጠቅ፦ በ2025 የናንጂንግ የዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ያገኘችው የብር ሜዳሊያ ተሰርዟል። በዚህም መሰረት ጆርጂያ አዳኝ ቤል የብር፣ ጆርጂያ ግሪፊት ደግሞ የነሐስ ሜዳሊያ ባለቤት እንዲሆኑ ተወስኗል።
አትሌት ድርቤ ነፃ መሆኗን ለማረጋገጥ ጥረት ብታደርግም፣ ምርመራን መቃወም ወይም ፍቃደኛ አለመሆን በአትሌቲክስ ሕግ እንደ አዎንታዊ (Positive) ውጤት ስለሚቆጠር ቅጣቱ ሊጸናባት ችሏል። በዚህም ምክንያት በ2025 የቶኪዮ ዓለም ሻምፒዮና ላይ እንዳትሳተፍ መደረጓ ይታወሳል።
✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ (ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
#diribewelteji #athleticsethiopia #dopingban #cas #worldathletics #antidoping #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
#ethiopia | ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ድርቤ ወልተጂ፣ የዶፒንግ ምርመራ ለማድረግ ፍቃደኛ ባለመሆኗ ምክንያት በስፖርት ገላጋይ ፍርድ ቤት (CAS) የሁለት ዓመት እገዳ ተጥሎባታል።
የቅጣቱ ዝርዝር ነጥቦች፦
የቅጣቱ ምክንያት፦ የኢትዮጵያ ፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለሥልጣን ምርመራ እንዲደረግላት ቢጠይቃትም ፍቃደኛ ባለመሆኗ (Refusal to submit to sample collection)።
የእገዳው ጊዜ፦ ቅጣቱ እስከ 2027 ዓ.ም የሚቆይ ይሆናል።
የውጤት መሰረዝ፦ ከየካቲት 2025 ጀምሮ ያስመዘገበቻቸው ውጤቶች በሙሉ ውድቅ ተደርገዋል።
የሜዳሊያ መነጠቅ፦ በ2025 የናንጂንግ የዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ያገኘችው የብር ሜዳሊያ ተሰርዟል። በዚህም መሰረት ጆርጂያ አዳኝ ቤል የብር፣ ጆርጂያ ግሪፊት ደግሞ የነሐስ ሜዳሊያ ባለቤት እንዲሆኑ ተወስኗል።
አትሌት ድርቤ ነፃ መሆኗን ለማረጋገጥ ጥረት ብታደርግም፣ ምርመራን መቃወም ወይም ፍቃደኛ አለመሆን በአትሌቲክስ ሕግ እንደ አዎንታዊ (Positive) ውጤት ስለሚቆጠር ቅጣቱ ሊጸናባት ችሏል። በዚህም ምክንያት በ2025 የቶኪዮ ዓለም ሻምፒዮና ላይ እንዳትሳተፍ መደረጓ ይታወሳል።
✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ (ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
#diribewelteji #athleticsethiopia #dopingban #cas #worldathletics #antidoping #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
Comments