ኢትዮጵያዊው የቴክኖሎጂ ስራ ፈጣሪ በሰፊቃድ ጌታቸው በአፍሪካ ምርጥ 100 የንግድ ጀግኖች ዝርዝር ውስጥ ተካተቱ
#fastmereja | የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኩባንያ የሆነው "ኢግል ላይን ሲስተም ቴክኖሎጂ" መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ በሰፊቃድ ጌታቸው፣ በ2026ቱ "አፍሪካ ቢዝነስ ሄሮውስ" (ABH) ውድድር ከመላው አፍሪካ ከተውጣጡ ከ24 ሺህ በላይ ተወዳዳሪዎች መካከል በማለፍ፣ በምርጥ 100 የንግድ ጀግኖች ዝርዝር ውስጥ መካተታቸው ተገለጸ።
በሰፊቃድ ጌታቸው የሚመራው "ኢግል ላይን ሲስተም ቴክኖሎጂ" በተለይም በፋይናንስ፣ በግብርና፣ በዲጂታል ክፍያ እና በቱሪዝም ዘርፎች ከሁለት ደርዘን በላይ የቴክኖሎጂ መፍትሄዎችን በማዘጋጀት ይታወቃል። በዘርፉ ካበረከቷቸው ፈጠራዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ከአንድ ሚሊየን ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የግብርና ግብዓት ግዥን ያቀለለው የ"ጌትፊ ኢንተርፕራይዝ" (GetFee Enterprise) የክፍያ ስብስብ መድረክ እና የዳሽን ባንክ የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ ዋነኞቹ ናቸው።
በተጨማሪም እንደ "ካሽ ጎ" (CashGo)፣ "ኢትዮ-ዳይሬክት ኮኔክት" (Ethio-Direct Connect) እና የ"ዱቤ አለ" (DubeAle) የክፍያ መድረክ የመሳሰሉ ፈጠራዎች በኢትዮጵያ የዲጂታል ፋይናንስ ስነ-ምህዳር ውስጥ ያላቸውን ተፅእኖ አሳይተዋል። ከእነዚህም ባሻገር ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ ማሰባሰቢያ የሆነውን "ItsMyDam.com" መድረክ በማልማትም ይታወቃሉ።
የአፍሪካ ቢዝነስ ሄሮውስ (ABH) ተነሳሽነት በ2018 ዓ.ም. በአሊባባ መስራች ጃክ ማ የተጀመረ ሲሆን፣ ዓላማውም በየአመቱ በአህጉሪቱ አስር ምርጥ ስራ ፈጣሪዎችን በመለየት የገንዘብ ድጋፍ፣ ስልጠና እና የአማካሪነት አገልግሎት መስጠት ነው። ለዘንድሮው የውድድር ዘመን በአጠቃላይ 1.5 ሚሊዮን ዶላር የሽልማት በጀት ተይዞለታል።
የሰፊቃድ ጌታቸው በምርጥ 100 ዝርዝር ውስጥ መካተት፣ ኢትዮጵያውያን ስራ ፈጣሪዎች በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያላቸውን አቅም በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማሳየትና አህጉራዊ ተወዳዳሪነትን ለመቀዳጀት እንደ ትልቅ ምዕራፍ ተወስዷል። ቀደም ሲል ከነበሩት ዓመታት አንጻር፣ በውድድሩ የኢትዮጵያውያን ተሳትፎ እየጨመረ መምጣቱን መረጃዎች ይጠቁማሉ።
#fastmereja | የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኩባንያ የሆነው "ኢግል ላይን ሲስተም ቴክኖሎጂ" መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ በሰፊቃድ ጌታቸው፣ በ2026ቱ "አፍሪካ ቢዝነስ ሄሮውስ" (ABH) ውድድር ከመላው አፍሪካ ከተውጣጡ ከ24 ሺህ በላይ ተወዳዳሪዎች መካከል በማለፍ፣ በምርጥ 100 የንግድ ጀግኖች ዝርዝር ውስጥ መካተታቸው ተገለጸ።
በሰፊቃድ ጌታቸው የሚመራው "ኢግል ላይን ሲስተም ቴክኖሎጂ" በተለይም በፋይናንስ፣ በግብርና፣ በዲጂታል ክፍያ እና በቱሪዝም ዘርፎች ከሁለት ደርዘን በላይ የቴክኖሎጂ መፍትሄዎችን በማዘጋጀት ይታወቃል። በዘርፉ ካበረከቷቸው ፈጠራዎች መካከል በኦሮሚያ ክልል ከአንድ ሚሊየን ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የግብርና ግብዓት ግዥን ያቀለለው የ"ጌትፊ ኢንተርፕራይዝ" (GetFee Enterprise) የክፍያ ስብስብ መድረክ እና የዳሽን ባንክ የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ ዋነኞቹ ናቸው።
በተጨማሪም እንደ "ካሽ ጎ" (CashGo)፣ "ኢትዮ-ዳይሬክት ኮኔክት" (Ethio-Direct Connect) እና የ"ዱቤ አለ" (DubeAle) የክፍያ መድረክ የመሳሰሉ ፈጠራዎች በኢትዮጵያ የዲጂታል ፋይናንስ ስነ-ምህዳር ውስጥ ያላቸውን ተፅእኖ አሳይተዋል። ከእነዚህም ባሻገር ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድጋፍ ማሰባሰቢያ የሆነውን "ItsMyDam.com" መድረክ በማልማትም ይታወቃሉ።
የአፍሪካ ቢዝነስ ሄሮውስ (ABH) ተነሳሽነት በ2018 ዓ.ም. በአሊባባ መስራች ጃክ ማ የተጀመረ ሲሆን፣ ዓላማውም በየአመቱ በአህጉሪቱ አስር ምርጥ ስራ ፈጣሪዎችን በመለየት የገንዘብ ድጋፍ፣ ስልጠና እና የአማካሪነት አገልግሎት መስጠት ነው። ለዘንድሮው የውድድር ዘመን በአጠቃላይ 1.5 ሚሊዮን ዶላር የሽልማት በጀት ተይዞለታል።
የሰፊቃድ ጌታቸው በምርጥ 100 ዝርዝር ውስጥ መካተት፣ ኢትዮጵያውያን ስራ ፈጣሪዎች በቴክኖሎጂ ዘርፍ ያላቸውን አቅም በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማሳየትና አህጉራዊ ተወዳዳሪነትን ለመቀዳጀት እንደ ትልቅ ምዕራፍ ተወስዷል። ቀደም ሲል ከነበሩት ዓመታት አንጻር፣ በውድድሩ የኢትዮጵያውያን ተሳትፎ እየጨመረ መምጣቱን መረጃዎች ይጠቁማሉ።
11 hours ago