2 days ago
የጤናው ዘርፍ የአረንጓዴ አሻራ ተሳትፎ
📌 ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል
#ethiopia | በሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች እንዲሁም ሰራተኞች ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ከገፈርሳ ጉጄ ክፍለ ከተማ ጋር በመተባበር በዛሬ እለት በገፈርሳ ሰው ሰራሽ ሀይቅ ዳርቻ ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል።
በሸገር ከተማ በገፈርሳ ጉጄ አካባቢ በተካሄደው በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች እና የየደረጃው የአካባቢው አመራሮች እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላትና የማህበረሰብ ክፍሎች ከማለዳው 1 ሰዓት ጀምሮ በመገኘት ችግኝ ተክለዋል።
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ አረንጓዴ አሻራ እና የጤና ዘርፍ የማይለያዩ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። ችግኝ ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን ለህብረተሰብ ጤና፣ ለንጹህ አየር እና ለምግብ ዋስትና ማሻሻያ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፣ በተለይም ለአዲስ አበባ እና ለአካባቢው ህዝብ የንጹህ ውሃ ምንጭ የሆነውን የገፈርሳ አካባቢን መንከባከብ የሁላችንም ህብረ-ብሄራዊ ሀገራዊ ኃላፊነት እንደሆነ አስገንዝበዋል።
በዕለቱ በቦታው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ አካባቢዋን ለመጠበቅ የምታደርገው ጥረት በንግግር ሳይሆን በተግባር የሚገለጽ መሆኑን አብራርተዋል።
በዕለቱ ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን ከ30 ሺህ በላይ ችግኞችን የተከለ ሲሆን፣ በክረምቱ የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ-ግብር ደግሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ እስከ 250 ሺህ ችግኞችን ለመትከል እና ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ነጻ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ሚኒስትሯ ገልጸዋል።
በመጨረሻም ክብርት ሚኒስትሯ፣ የጤና ባለሙያዎች እና መላው የሀገራችን ህዝብ ቀኑ ሳያልቅ እና ጀምበር ሳትጠልቅ የድርሻቸውን ችግኝ በመትከል የዚህ ታሪካዊ ኩነት አካል እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
ከችግኝ ተከላው መርሐግብር ባሻገር የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በሸገር ከተማ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።
በጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ministryofhealth #treeplanting
#climateaction #publichealth
#environmentalhealth #gefersa #cleanenvironment #greenethiopia
#communitysupport
📌 ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል
#ethiopia | በሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች እንዲሁም ሰራተኞች ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ከገፈርሳ ጉጄ ክፍለ ከተማ ጋር በመተባበር በዛሬ እለት በገፈርሳ ሰው ሰራሽ ሀይቅ ዳርቻ ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል።
በሸገር ከተማ በገፈርሳ ጉጄ አካባቢ በተካሄደው በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች እና የየደረጃው የአካባቢው አመራሮች እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላትና የማህበረሰብ ክፍሎች ከማለዳው 1 ሰዓት ጀምሮ በመገኘት ችግኝ ተክለዋል።
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ አረንጓዴ አሻራ እና የጤና ዘርፍ የማይለያዩ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። ችግኝ ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን ለህብረተሰብ ጤና፣ ለንጹህ አየር እና ለምግብ ዋስትና ማሻሻያ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፣ በተለይም ለአዲስ አበባ እና ለአካባቢው ህዝብ የንጹህ ውሃ ምንጭ የሆነውን የገፈርሳ አካባቢን መንከባከብ የሁላችንም ህብረ-ብሄራዊ ሀገራዊ ኃላፊነት እንደሆነ አስገንዝበዋል።
በዕለቱ በቦታው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ አካባቢዋን ለመጠበቅ የምታደርገው ጥረት በንግግር ሳይሆን በተግባር የሚገለጽ መሆኑን አብራርተዋል።
በዕለቱ ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን ከ30 ሺህ በላይ ችግኞችን የተከለ ሲሆን፣ በክረምቱ የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ-ግብር ደግሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ እስከ 250 ሺህ ችግኞችን ለመትከል እና ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ነጻ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ሚኒስትሯ ገልጸዋል።
በመጨረሻም ክብርት ሚኒስትሯ፣ የጤና ባለሙያዎች እና መላው የሀገራችን ህዝብ ቀኑ ሳያልቅ እና ጀምበር ሳትጠልቅ የድርሻቸውን ችግኝ በመትከል የዚህ ታሪካዊ ኩነት አካል እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
ከችግኝ ተከላው መርሐግብር ባሻገር የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በሸገር ከተማ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።
በጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ministryofhealth #treeplanting
#climateaction #publichealth
#environmentalhealth #gefersa #cleanenvironment #greenethiopia
#communitysupport
8 days ago
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ የዶ/ር በርናንድ እና ሲ/ር እማዋይሽ ጅምር ሆስፒታል ለሕዝብ አገልግሎት እንዲውል ስምምነት አደረገ
#ethiopia | በጎንደር ከተማ የተጀመረው የዶክተር በርናንድ አንደርሰን እና የሲስተር እማዋይሽ ገሪማ መታሰቢያ ጅምር ሆስፒታል ለኢትዮጵያ ህዝብ የጤና አገልግሎትና የምርምር ማዕከል ሆኖ እንዲቀጥል ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከኑዛዜ ወራሾች እና ተጠቃሚዎች ጋር የጋራ መግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።
ስምምነት በ2008 ዓ.ም ተጀምሮ የነበረውን ሀገራዊ አላማ ከውልና ማስረጃ እንዲሁም ከእንደራሴው አቶ ዳዊት ደርበው ጋር በመተባበር ዳር ለማድረስ ያስቻለ ምዕራፍ መሆኑ ነው።
በተደረገው ስምምነት መሠረት ሆስፒታሉ የማይሸጥ፣ የማይለወጥ፣ ቅርጽና ይዘቱ ሳይለወጥ እንዲሁም ስመ ንብረቱ ወደ ሌላ ሶስተኛ ወገን ሳይተላለፍ የለጋሾቹ የዘላለም መታሰቢያ ሆኖ እንዲኖር ዋስትና ይሰጣል።
የተከናወነው ስምምነት መሠረት ዩኒቨርሲቲው ህንጻውን አጠናቆ ለህዝብ የህክምና አገልግሎት፣ ለትምህርት እና ለምርምር ማዋል የሚችለውን ጠንካራ መሰረት የጣለ ሲሆን፣ በኑዛዜው የተገለጹት ተጠቃሚዎች መብቶችም ሙሉ በሙሉ እንዲከበሩ ተደርጓል።
በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሥራት አፀደወይን ለጋሾቹ ለህዝብ ጥቅም የለገሱት ይህ በጎ አድራጎት ለወደፊቱ ትውልድ ትልቅ አርአያ የሚሆንና የሀገሪቱን የጤና ዘርፍ እንዲሁም የህክምና ቱሪዝም የሚያሳድግ መሆኑን ገልጸዋል።
የወራሾችን በመወከል ንግግር ያደረጉት አቶ ዳዊት ደርበው እንደገለጹት፣ በዕለቱ የተገኙበት ዋና ምክንያት በሲስተር ማዋይሽ ገሪማ ኑዛዜ መሠረት የተጀመረውን ሆስፒታል አጠናቀው ወደ ተግባር ለማዋል እንደሆነ አስረድተዋል።
እርሳቸውም በኑዛዜው እንደራሴ በመሆን የተሰጣቸውን ሙሉ ስልጣን በመጠቀም ሥራውን ለማስፈጸም እንደተገኙ ገልጸው፣ ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ ሲስተር ማዋይሽ በህይወት በነበረችበት ጊዜ ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ጋር አድርጋው የነበረውን ውል እንደገና በማነቃቃት የጀመሩትን ሂደት ለማጠናቀቅ መሆኑን አብራርተዋል።
ስምምነቱ ከተጠናቀቀ በኋላም ተሳታፊዎች የዶክተር በርናንድ አንደርሰን እና የሲስተር እማዋይሽ ገሪማ መታሰቢያ ሙዚየምን እንዲሁም የሆስፒታሉን ጅምር ግንባታ በጋራ ጎብኝተዋል።
#gondaruniversity #drbernardandsisteremawesh #gondar #ethiopia #healthcare #medicalresearch #legacy #publichealth
#ethiopia | በጎንደር ከተማ የተጀመረው የዶክተር በርናንድ አንደርሰን እና የሲስተር እማዋይሽ ገሪማ መታሰቢያ ጅምር ሆስፒታል ለኢትዮጵያ ህዝብ የጤና አገልግሎትና የምርምር ማዕከል ሆኖ እንዲቀጥል ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከኑዛዜ ወራሾች እና ተጠቃሚዎች ጋር የጋራ መግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።
ስምምነት በ2008 ዓ.ም ተጀምሮ የነበረውን ሀገራዊ አላማ ከውልና ማስረጃ እንዲሁም ከእንደራሴው አቶ ዳዊት ደርበው ጋር በመተባበር ዳር ለማድረስ ያስቻለ ምዕራፍ መሆኑ ነው።
በተደረገው ስምምነት መሠረት ሆስፒታሉ የማይሸጥ፣ የማይለወጥ፣ ቅርጽና ይዘቱ ሳይለወጥ እንዲሁም ስመ ንብረቱ ወደ ሌላ ሶስተኛ ወገን ሳይተላለፍ የለጋሾቹ የዘላለም መታሰቢያ ሆኖ እንዲኖር ዋስትና ይሰጣል።
የተከናወነው ስምምነት መሠረት ዩኒቨርሲቲው ህንጻውን አጠናቆ ለህዝብ የህክምና አገልግሎት፣ ለትምህርት እና ለምርምር ማዋል የሚችለውን ጠንካራ መሰረት የጣለ ሲሆን፣ በኑዛዜው የተገለጹት ተጠቃሚዎች መብቶችም ሙሉ በሙሉ እንዲከበሩ ተደርጓል።
በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሥራት አፀደወይን ለጋሾቹ ለህዝብ ጥቅም የለገሱት ይህ በጎ አድራጎት ለወደፊቱ ትውልድ ትልቅ አርአያ የሚሆንና የሀገሪቱን የጤና ዘርፍ እንዲሁም የህክምና ቱሪዝም የሚያሳድግ መሆኑን ገልጸዋል።
የወራሾችን በመወከል ንግግር ያደረጉት አቶ ዳዊት ደርበው እንደገለጹት፣ በዕለቱ የተገኙበት ዋና ምክንያት በሲስተር ማዋይሽ ገሪማ ኑዛዜ መሠረት የተጀመረውን ሆስፒታል አጠናቀው ወደ ተግባር ለማዋል እንደሆነ አስረድተዋል።
እርሳቸውም በኑዛዜው እንደራሴ በመሆን የተሰጣቸውን ሙሉ ስልጣን በመጠቀም ሥራውን ለማስፈጸም እንደተገኙ ገልጸው፣ ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ ሲስተር ማዋይሽ በህይወት በነበረችበት ጊዜ ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ጋር አድርጋው የነበረውን ውል እንደገና በማነቃቃት የጀመሩትን ሂደት ለማጠናቀቅ መሆኑን አብራርተዋል።
ስምምነቱ ከተጠናቀቀ በኋላም ተሳታፊዎች የዶክተር በርናንድ አንደርሰን እና የሲስተር እማዋይሽ ገሪማ መታሰቢያ ሙዚየምን እንዲሁም የሆስፒታሉን ጅምር ግንባታ በጋራ ጎብኝተዋል።
#gondaruniversity #drbernardandsisteremawesh #gondar #ethiopia #healthcare #medicalresearch #legacy #publichealth
2 months ago
የፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች መቋቋም ስጋት የሕክምናው ዘርፍ ፈተና
#ethiopia | በተለያዩ የመድኃኒት መሸጫ ፋርማሲዎች፣ በሙያ ማህበራት፣ በጤና ተቋማትና በማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ሰሞኑን ስለ ፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች መቋቋም ወይም Antimicrobial Resistance (AMR) ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ መልዕክቶች ሲስተላለፉ ቆይተዋል።
ይህ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ ትኩረት ሊሰጠው የቻለው በየዓመቱ የሚታሰበውን ዓለም አቀፍ የባለሙያዎችና የህዝብ ንቅናቄ መድረክን ተከትሎ ነው።
የመድኃኒት መቋቋም የሚባለው ክስተት ባክቴሪያዎች፣ ፈንገሶች፣ ቫይረሶችና መሰል ጥቃቅን ተህዋሲያን እነሱን ለማጥፋት የሚታዘዙ መድኃኒቶችን የመላመድና የመቋቋም አቅም ሲያዳብሩ የሚፈጠር የጤና እክል ነው።
ይህ ሁኔታ ቀደም ሲል በቀላሉ መፈወስ የሚችሉ የጤና ችግሮችን ውስብስብ ከማድረጉም በላይ ለተጨማሪ የሕክምና ወጪና ለከፋ የህይወት መጥፋት አደጋ የሚያጋልጥ መሆኑ ይነገራል።
ችግሩ በዓለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፋ ቢገኝም አሁንም ድረስ ከብዙሃኑ ህብረተሰብ ተገቢውን ትኩረት አላገኘም።
በተለይም አንቲባዮቲክስ ወይም የፀረ-ባክቴሪያ መድኃኒቶችን ያለ ሐኪም ትዕዛዝ በራስ ፍቃድ መውሰድ፣ የተጀመረን የሕክምና ጊዜ አጠናቆ አለመጨረስና መድኃኒቶችን ያለአግባብ መጠቀም ለችግሩ መባባስ ዋነኛ መንስኤዎች ሆነዋል።
የዘርፉ ባለሙያዎች ይህንን የጤና ስጋት ዝምተኛው ወይም ቀዝቃዛው ሱናሚ ሲሉ ይጠሩታል።
እንደ ድንገተኛ ወረርሽኝ በአንድ ጊዜ ህዝብን ባያጠቃም በሂደት ግን በዝግታ እየተስፋፋ የዘመናዊ ሕክምና ስኬቶችንና መሠረቶችን ትልቅ አደጋ ላይ እየጣለ ይገኛል።
ስለሆነም መድኃኒቶችን በከፍተኛ ኃላፊነት መጠቀም፣ የሕክምና ባለሙያዎችን ምክር በአግባቡ መተግበርና ህብረተሰቡን ማስተማር የሁሉንም አካላት ርብርብ ይጠይቃል።
ዛሬ የምናሳየው ጥንቃቄና የምንወስደው እርምጃ ወደፊት ውጤታማና ፈዋሽ መድኃኒቶች እንዲኖሩን ለማድረግ ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
ሃና ልካስ
#amr #antimicrobialresistance #healthnews #publichealth #medicine #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በተለያዩ የመድኃኒት መሸጫ ፋርማሲዎች፣ በሙያ ማህበራት፣ በጤና ተቋማትና በማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ሰሞኑን ስለ ፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች መቋቋም ወይም Antimicrobial Resistance (AMR) ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ መልዕክቶች ሲስተላለፉ ቆይተዋል።
ይህ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ ትኩረት ሊሰጠው የቻለው በየዓመቱ የሚታሰበውን ዓለም አቀፍ የባለሙያዎችና የህዝብ ንቅናቄ መድረክን ተከትሎ ነው።
የመድኃኒት መቋቋም የሚባለው ክስተት ባክቴሪያዎች፣ ፈንገሶች፣ ቫይረሶችና መሰል ጥቃቅን ተህዋሲያን እነሱን ለማጥፋት የሚታዘዙ መድኃኒቶችን የመላመድና የመቋቋም አቅም ሲያዳብሩ የሚፈጠር የጤና እክል ነው።
ይህ ሁኔታ ቀደም ሲል በቀላሉ መፈወስ የሚችሉ የጤና ችግሮችን ውስብስብ ከማድረጉም በላይ ለተጨማሪ የሕክምና ወጪና ለከፋ የህይወት መጥፋት አደጋ የሚያጋልጥ መሆኑ ይነገራል።
ችግሩ በዓለም አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፋ ቢገኝም አሁንም ድረስ ከብዙሃኑ ህብረተሰብ ተገቢውን ትኩረት አላገኘም።
በተለይም አንቲባዮቲክስ ወይም የፀረ-ባክቴሪያ መድኃኒቶችን ያለ ሐኪም ትዕዛዝ በራስ ፍቃድ መውሰድ፣ የተጀመረን የሕክምና ጊዜ አጠናቆ አለመጨረስና መድኃኒቶችን ያለአግባብ መጠቀም ለችግሩ መባባስ ዋነኛ መንስኤዎች ሆነዋል።
የዘርፉ ባለሙያዎች ይህንን የጤና ስጋት ዝምተኛው ወይም ቀዝቃዛው ሱናሚ ሲሉ ይጠሩታል።
እንደ ድንገተኛ ወረርሽኝ በአንድ ጊዜ ህዝብን ባያጠቃም በሂደት ግን በዝግታ እየተስፋፋ የዘመናዊ ሕክምና ስኬቶችንና መሠረቶችን ትልቅ አደጋ ላይ እየጣለ ይገኛል።
ስለሆነም መድኃኒቶችን በከፍተኛ ኃላፊነት መጠቀም፣ የሕክምና ባለሙያዎችን ምክር በአግባቡ መተግበርና ህብረተሰቡን ማስተማር የሁሉንም አካላት ርብርብ ይጠይቃል።
ዛሬ የምናሳየው ጥንቃቄና የምንወስደው እርምጃ ወደፊት ውጤታማና ፈዋሽ መድኃኒቶች እንዲኖሩን ለማድረግ ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
ሃና ልካስ
#amr #antimicrobialresistance #healthnews #publichealth #medicine #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
4 months ago
እነዚህን 69 ደረጃቸውን ያልጠበቁ የምግብ ምርቶች እንዳትጠቀሙ!
#ethiopia | የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ባደረገው የገበያ ቁጥጥርና ፍተሻ፣ ጥራትና ደህንነታቸው ያልተረጋገጡ እንዲሁም አስገዳጅ መስፈርቶችን ያላሟሉ 69 የምግብ ምርቶችን ለይቶ ይፋ አድርጓል።
በ570 የንግድ ተቋማት ላይ በተደረገ ፍተሻ 32 የገበታ ጨው፣ 19 የምግብ ዘይት፣ 6 የለውዝ ቅቤ፣ 6 የማር ዓይነቶች እንዲሁም ከረሜላና የሕፃናት ምግቦች ደረጃቸውን ያልጠበቁ ሆነው ተገኝተዋል።
ማንኛውንም ምርት ሲገዙ የገላጭ ጽሑፍ፣ የአምራች መረጃ፣ የመለያ ቁጥር (Batch Number) እና የጥራት ምልክት መኖሩን ማረጋገጥ ይገባል።
ባለስልጣኑ እንዳትጠቀሟቸው የከለከላቸው ዋና ዋና ምርቶች፦
የገበታ ጨው ዓይነቶች (ከፊሉ)፦
ሰይፋ፣ ቲና፣ እሙሹ፣ ቃሊ፣ አዮዲን፣ እኑ፣ አራዳ፣ ንጉስ፣ ሀሮት፣ ኩል፣ አሜን፣ ሰቦኑማ፣ እቱ፣ መክሊት፣ ዳግም፣ መርሰን፣ ኒሀል፣ ሊቅ፣ ስካይ፣ ናፊ፣ አቤ፣ ሳሮማ፣ ፀሐይ፣ ማሩ፣ እንቁ፣ ሰኒ፣ ሚያዋ፣ ስኬት፣ ሔራል፣ ቤዝ፣ ገዳ።
የምግብ ዘይት ዓይነቶች፦
ምስራቅ ፀሐይ፣ ቃል፣ አፍራን፣ ኒያ፣ ሪሃ፣ ኤአይ ሻኪር፣ ኤ1-ኑር፣ ጥራ፣ ረዲ፣ አያን፣ ሳፊያ፣ እሰይ፣ አማን፣ ላምሮት ኬኬ፣ እድገት፣ ራኒያ፣ ሸገር፣ ሀይላለ፣ ፍፁም የተጣራ።
ማርና የለውዝ ቅቤ፦
ሀራ፣ ሶራ፣ ብሉ፣ ስዊት ክሬም፣ ሉሲ፣ ስንቅ (ለውዝ ቅቤ)፤ ቤዛ ማር፣ ውብሸት የማር ጠጅ፣ ጂጂ ማር፣ አምባሰል ነጭ ማር፣ የኢሉባቦር ማር።
ከረሜላ፦
ቡርቃ ሎሊፖፕ፣ አዩ ፓፕ፣ አፍሪ፣ ዴሉክሴ።
#getu #efda #foodsafetyethiopia #publichealth #addisababa #ethiopia #consumerprotection #healthyeating #alert #ጥራትቁጥጥር #ጤና #ምግብናመድኃኒት #አዲስአበባ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ባደረገው የገበያ ቁጥጥርና ፍተሻ፣ ጥራትና ደህንነታቸው ያልተረጋገጡ እንዲሁም አስገዳጅ መስፈርቶችን ያላሟሉ 69 የምግብ ምርቶችን ለይቶ ይፋ አድርጓል።
በ570 የንግድ ተቋማት ላይ በተደረገ ፍተሻ 32 የገበታ ጨው፣ 19 የምግብ ዘይት፣ 6 የለውዝ ቅቤ፣ 6 የማር ዓይነቶች እንዲሁም ከረሜላና የሕፃናት ምግቦች ደረጃቸውን ያልጠበቁ ሆነው ተገኝተዋል።
ማንኛውንም ምርት ሲገዙ የገላጭ ጽሑፍ፣ የአምራች መረጃ፣ የመለያ ቁጥር (Batch Number) እና የጥራት ምልክት መኖሩን ማረጋገጥ ይገባል።
ባለስልጣኑ እንዳትጠቀሟቸው የከለከላቸው ዋና ዋና ምርቶች፦
የገበታ ጨው ዓይነቶች (ከፊሉ)፦
ሰይፋ፣ ቲና፣ እሙሹ፣ ቃሊ፣ አዮዲን፣ እኑ፣ አራዳ፣ ንጉስ፣ ሀሮት፣ ኩል፣ አሜን፣ ሰቦኑማ፣ እቱ፣ መክሊት፣ ዳግም፣ መርሰን፣ ኒሀል፣ ሊቅ፣ ስካይ፣ ናፊ፣ አቤ፣ ሳሮማ፣ ፀሐይ፣ ማሩ፣ እንቁ፣ ሰኒ፣ ሚያዋ፣ ስኬት፣ ሔራል፣ ቤዝ፣ ገዳ።
የምግብ ዘይት ዓይነቶች፦
ምስራቅ ፀሐይ፣ ቃል፣ አፍራን፣ ኒያ፣ ሪሃ፣ ኤአይ ሻኪር፣ ኤ1-ኑር፣ ጥራ፣ ረዲ፣ አያን፣ ሳፊያ፣ እሰይ፣ አማን፣ ላምሮት ኬኬ፣ እድገት፣ ራኒያ፣ ሸገር፣ ሀይላለ፣ ፍፁም የተጣራ።
ማርና የለውዝ ቅቤ፦
ሀራ፣ ሶራ፣ ብሉ፣ ስዊት ክሬም፣ ሉሲ፣ ስንቅ (ለውዝ ቅቤ)፤ ቤዛ ማር፣ ውብሸት የማር ጠጅ፣ ጂጂ ማር፣ አምባሰል ነጭ ማር፣ የኢሉባቦር ማር።
ከረሜላ፦
ቡርቃ ሎሊፖፕ፣ አዩ ፓፕ፣ አፍሪ፣ ዴሉክሴ።
#getu #efda #foodsafetyethiopia #publichealth #addisababa #ethiopia #consumerprotection #healthyeating #alert #ጥራትቁጥጥር #ጤና #ምግብናመድኃኒት #አዲስአበባ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
4 months ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአዲስ መልክ የተደራጀውን የአርማውር ሐንሰን የምርምር ማዕከል መረቁ
#ethiopia | ለበርካታ ዓመታት በአለርት የሕክምና ማዕከል ውስጥ በተወሰነ አቅም የምርምር ሥራዎችን ሲያከናውን የቆየው የአርማውር ሐንሰን የምርምር ተቋም በመንግሥት ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት በአዲስ መልክ ሪፎርም ተደርጓል።
ይህ ተቋም በአዋጅ በድጋሚ እንዲደራጅ ከተደረገ በኋላ አስፈላጊው የግንባታ ሥራ ተጠናቆለትና ዘመናዊ ግብዓቶች ተሟልተውለት በዛሬው ዕለት በኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በይፋ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።
ተቋሙ ወደዚህ አዲስ ምዕራፍ የተሸጋገረው በሀገሪቱ የጤና ምርምር ዘርፍ ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላትና የሳይንስ ምርምርን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ታቅዶ መሆኑ ተገልጿል።
ይህ ዘመናዊ የምርምር ማዕከል በውስጡ 40 የሚደርሱ ላቦራቶሪዎችን የያዘ ሲሆን በተለይም የላቁ የጂኖሚክስ እና የባዮኢንፎርማቲክስ የምርምር ቦታዎችን በማካተቱ በዘርፉ ትልቅ አቅም ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
ከዚህ በተጨማሪም ማዕከሉ በሀገር ውስጥ የሚመረቱ መድኃኒቶችን ጥራት፣ ደህንነትና ብቃት በተገቢው ሁኔታ የሚያረጋግጥ የባዮኢኩዊቫለንስ ማዕከልን በውስጡ አካቶ የያዘ በመሆኑ ለሀገር በቀል የመድኃኒት ኢንዱስትሪ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል።
ይህ ግዙፍ የምርምር ተቋም መገንባቱ ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ ራሷን ችላ የሕዝቧን ደህንነት ለመጠበቅ ለምታደርገው ጥረት እንደ ትልቅ ስኬት የሚቆጠር ነው።
#ethiopia #ahri #medicalresearch #healthinnovation #abiyahmed #scienceandtechnology #genomics #bioinformatics #publichealth
#ethiopia | ለበርካታ ዓመታት በአለርት የሕክምና ማዕከል ውስጥ በተወሰነ አቅም የምርምር ሥራዎችን ሲያከናውን የቆየው የአርማውር ሐንሰን የምርምር ተቋም በመንግሥት ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት በአዲስ መልክ ሪፎርም ተደርጓል።
ይህ ተቋም በአዋጅ በድጋሚ እንዲደራጅ ከተደረገ በኋላ አስፈላጊው የግንባታ ሥራ ተጠናቆለትና ዘመናዊ ግብዓቶች ተሟልተውለት በዛሬው ዕለት በኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በይፋ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።
ተቋሙ ወደዚህ አዲስ ምዕራፍ የተሸጋገረው በሀገሪቱ የጤና ምርምር ዘርፍ ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላትና የሳይንስ ምርምርን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ታቅዶ መሆኑ ተገልጿል።
ይህ ዘመናዊ የምርምር ማዕከል በውስጡ 40 የሚደርሱ ላቦራቶሪዎችን የያዘ ሲሆን በተለይም የላቁ የጂኖሚክስ እና የባዮኢንፎርማቲክስ የምርምር ቦታዎችን በማካተቱ በዘርፉ ትልቅ አቅም ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
ከዚህ በተጨማሪም ማዕከሉ በሀገር ውስጥ የሚመረቱ መድኃኒቶችን ጥራት፣ ደህንነትና ብቃት በተገቢው ሁኔታ የሚያረጋግጥ የባዮኢኩዊቫለንስ ማዕከልን በውስጡ አካቶ የያዘ በመሆኑ ለሀገር በቀል የመድኃኒት ኢንዱስትሪ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል።
ይህ ግዙፍ የምርምር ተቋም መገንባቱ ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ ራሷን ችላ የሕዝቧን ደህንነት ለመጠበቅ ለምታደርገው ጥረት እንደ ትልቅ ስኬት የሚቆጠር ነው።
#ethiopia #ahri #medicalresearch #healthinnovation #abiyahmed #scienceandtechnology #genomics #bioinformatics #publichealth
4 months ago
#ፊንላንድ፦ የዓለማችን ደስተኛዋ ሀገር ለ8 ተከታታይ ዓመት! 🌍🌿
#ethiopia | ጨለማና ረጅም ክረምት ቢኖርባቸውም፣ በደስታ ግን የዓለምን ብርሃን መሆን ችለዋል!
ፊንላንድ የ2025 የዓለም የደስታ ሪፖርት (World Happiness Report) ለ8ኛ ተከታታይ ዓመት በመሪነት አጠናቃለች። ይህ ውጤት በአጋጣሚ የተገኘ ሳይሆን "በእቅድ የተገነባ" እንደሆነ ባለሙያዎች ይናገራሉ።
የፊንላንድ የደስታ ሚስጥሮች ምንድን ናቸው?
የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰሮችና ተመራማሪዎች ለዚህ ስኬት አራት ዋና ዋና ምክንያቶችን ያስቀምጣሉ፦
1. ጥልቅ ማህበራዊ ትስስር፦ሰዎች እርስ በእርሳቸው ያላቸው ግንኙነት በጣም ጠንካራ ነው።
2. በተቋማት ላይ ያለው እምነት፦ ዜጎች በመንግስት እና በማህበራዊ ተቋማት ላይ ያላቸው እምነት ከፍተኛ ነው።
3. ከተፈጥሮ ጋር መተሳሰር፦ ፊንላንዳውያን ከተፈጥሮ ጋር ያላቸው ጥልቅ ቁርኝት ለአእምሮ ሰላማቸው ትልቅ አስተዋፅኦ አለው።
4. የእኩልነት ስሜት፦የጤና እና የደህንነት አገልግሎቶች ለሁሉም እኩል መዳረሳቸው።
"ደስታ ይገነባል እንጂ አይገዛም!
ፊንላንድ "የደስታ መሰረተ-ልማት" (Infrastructure of Happiness) የምንለውን ስርዓት መገንባት ችላለች። ይህም ግለሰቦችና ማህበረሰቡ እንዲበለጽጉ የሚያደርግ ባህልና ጠንካራ ተቋማትን ያካትታል።
*ለዓለም ማስጠንቀቂያ የሆነው መረጃ፦
በተቃራኒው እንደ አሜሪካ ያሉ ሀገራት በደስታ ደረጃቸው ዝቅ ብለዋል። ላለፉት 20 ዓመታት ብቻውን የሚመገብ (Dining alone) ሰው ቁጥር በ53% መጨመሩ፣ ማህበራዊ መገለል ለደስታ ማጣት ትልቁ ምክንያት መሆኑን ያሳያል።
ትምህርቱ፦
እውነተኛ ደስታ የሚመጣው ከሀብት ብቻ ሳይሆን እርስ በእርስ ከመተማመን፣ ከተፈጥሮ ጋር ከመታረቅ እና ጠንካራ ማህበራዊ ግንኙነት ከመፍጠር ነው። ይህ ፊንላንድ ለዓለም እያስተማረች ያለችው ታላቅ የቤት ስራ ነው።
ባምላኩ ነኝ, ከጅማ ህክምና ማዕከል
ምንጭ፦
የ2025 የዓለም የደስታ ሪፖርት (ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ፣ ጋለፕ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት)
#happiestcountry #finlandlife #worldhappinessreport #publichealth #wellbeing #socialconnection #ethiopia #jimma
#ethiopia | ጨለማና ረጅም ክረምት ቢኖርባቸውም፣ በደስታ ግን የዓለምን ብርሃን መሆን ችለዋል!
ፊንላንድ የ2025 የዓለም የደስታ ሪፖርት (World Happiness Report) ለ8ኛ ተከታታይ ዓመት በመሪነት አጠናቃለች። ይህ ውጤት በአጋጣሚ የተገኘ ሳይሆን "በእቅድ የተገነባ" እንደሆነ ባለሙያዎች ይናገራሉ።
የፊንላንድ የደስታ ሚስጥሮች ምንድን ናቸው?
የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰሮችና ተመራማሪዎች ለዚህ ስኬት አራት ዋና ዋና ምክንያቶችን ያስቀምጣሉ፦
1. ጥልቅ ማህበራዊ ትስስር፦ሰዎች እርስ በእርሳቸው ያላቸው ግንኙነት በጣም ጠንካራ ነው።
2. በተቋማት ላይ ያለው እምነት፦ ዜጎች በመንግስት እና በማህበራዊ ተቋማት ላይ ያላቸው እምነት ከፍተኛ ነው።
3. ከተፈጥሮ ጋር መተሳሰር፦ ፊንላንዳውያን ከተፈጥሮ ጋር ያላቸው ጥልቅ ቁርኝት ለአእምሮ ሰላማቸው ትልቅ አስተዋፅኦ አለው።
4. የእኩልነት ስሜት፦የጤና እና የደህንነት አገልግሎቶች ለሁሉም እኩል መዳረሳቸው።
"ደስታ ይገነባል እንጂ አይገዛም!
ፊንላንድ "የደስታ መሰረተ-ልማት" (Infrastructure of Happiness) የምንለውን ስርዓት መገንባት ችላለች። ይህም ግለሰቦችና ማህበረሰቡ እንዲበለጽጉ የሚያደርግ ባህልና ጠንካራ ተቋማትን ያካትታል።
*ለዓለም ማስጠንቀቂያ የሆነው መረጃ፦
በተቃራኒው እንደ አሜሪካ ያሉ ሀገራት በደስታ ደረጃቸው ዝቅ ብለዋል። ላለፉት 20 ዓመታት ብቻውን የሚመገብ (Dining alone) ሰው ቁጥር በ53% መጨመሩ፣ ማህበራዊ መገለል ለደስታ ማጣት ትልቁ ምክንያት መሆኑን ያሳያል።
ትምህርቱ፦
እውነተኛ ደስታ የሚመጣው ከሀብት ብቻ ሳይሆን እርስ በእርስ ከመተማመን፣ ከተፈጥሮ ጋር ከመታረቅ እና ጠንካራ ማህበራዊ ግንኙነት ከመፍጠር ነው። ይህ ፊንላንድ ለዓለም እያስተማረች ያለችው ታላቅ የቤት ስራ ነው።
ባምላኩ ነኝ, ከጅማ ህክምና ማዕከል
ምንጭ፦
የ2025 የዓለም የደስታ ሪፖርት (ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ፣ ጋለፕ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት)
#happiestcountry #finlandlife #worldhappinessreport #publichealth #wellbeing #socialconnection #ethiopia #jimma
4 months ago
ማያ በጎ አድራጎት ድርጅት በህፃናት የአፈጣጠር ችግር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ
#ethiopia | የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ከማያ የበጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር በአፈጣጠር ችግር ምክንያት በሚከሰቱ የጀርባ አጥንት ክፍተት (Spina Bifida) እና የአንጎል ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት (Hydrocephalus) ዙሪያ ያተኮረ ልዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ አካሂዷል።
በመድረኩ ላይ እንደተገለጸው በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ44 ሺህ በላይ ህፃናት በእነዚህ የጤና ችግሮች ምክንያት የሚወለዱ ሲሆን፣ ለችግሩ ዋነኛው መንስኤ እናቶች በእርግዝና ወቅት የሚገጥማቸው የፎሊክ አሲድ ወይም የቫይታሚን ቢ9 እጥረት መሆኑ በሰፊው ተብራርቷል።
እነዚህ የአፈጣጠር ችግሮች በህፃናቱ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ሲሆን፣ በተለይም ለዕድሜ ልክ የሚዘልቅ የመንቀሳቀስ መገደብ እና ራስን ችሎ የመፀዳዳት ችግር እንደሚገጥማቸው ተመላክቷል።
ይህንን ችግር በዘላቂነት ለመከላከል በመንግስት የተጀመረው ምግቦችን በፎሊክ አሲድ የማበልጸግ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የተገለጸ ሲሆን፣ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩም ይህንን ሀገራዊ ጥረት በግለሰብ፣ በማህበረሰብ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ ለማገዝ ያለመ እንደሆነ ተጠቁሟል።
በመድረኩ ላይ የአካቶ ትምህርት እና የዜጎች ተጠቃሚነት ጉዳይም በስፋት የተነሳ ሲሆን፣ በእነዚህ የጤና ችግሮች የተጠቁ ህፃናት የማህበረሰቡ አካል መሆናቸው ታምኖበት ትምህርትን ጨምሮ ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶችን የማግኘት መብታቸው ሊከበር እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል።
መርሃ ግብሩ በእነዚህ ህፃናት ሰብአዊ መብት እና ማህበራዊ ተሳትፎ ዙሪያ ሰፊ ውይይት ያደረገ ሲሆን፣ ህብረተሰቡ ለችግሩ ተጋላጭ የሆኑ ወገኖችን ከመገለል እንዲታደግና አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ አሳስቧል።
በዚህ መርሃ ግብር ላይ የፌዴራል ጤና ሚኒስቴር ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ፣ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እና የማያ በጎ አድራጎት ድርጅት መስራቾች አስተባባሪዎች ተገኝተዋል።
ከእነዚህም በተጨማሪ የጥበብ ባለሙያዎች፣ የሚዲያ አካላት፣ እንዲሁም የችግሩ ተጋላጭ የሆኑ ህፃናትና ወላጆቻቸው በመሳተፍ ስለ በሽታው መከላከያ መንገዶች እና ስላለው ተግዳሮት በቂ ግንዛቤ እንዲጨበጥ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#healthawareness #ethiopia #spinabifida #hydrocephalus #mayacharitableorganization #publichealth #folicacid #inclusion #addisababa
#ethiopia | የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ከማያ የበጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር በአፈጣጠር ችግር ምክንያት በሚከሰቱ የጀርባ አጥንት ክፍተት (Spina Bifida) እና የአንጎል ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት (Hydrocephalus) ዙሪያ ያተኮረ ልዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ አካሂዷል።
በመድረኩ ላይ እንደተገለጸው በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ44 ሺህ በላይ ህፃናት በእነዚህ የጤና ችግሮች ምክንያት የሚወለዱ ሲሆን፣ ለችግሩ ዋነኛው መንስኤ እናቶች በእርግዝና ወቅት የሚገጥማቸው የፎሊክ አሲድ ወይም የቫይታሚን ቢ9 እጥረት መሆኑ በሰፊው ተብራርቷል።
እነዚህ የአፈጣጠር ችግሮች በህፃናቱ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ሲሆን፣ በተለይም ለዕድሜ ልክ የሚዘልቅ የመንቀሳቀስ መገደብ እና ራስን ችሎ የመፀዳዳት ችግር እንደሚገጥማቸው ተመላክቷል።
ይህንን ችግር በዘላቂነት ለመከላከል በመንግስት የተጀመረው ምግቦችን በፎሊክ አሲድ የማበልጸግ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የተገለጸ ሲሆን፣ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩም ይህንን ሀገራዊ ጥረት በግለሰብ፣ በማህበረሰብ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ ለማገዝ ያለመ እንደሆነ ተጠቁሟል።
በመድረኩ ላይ የአካቶ ትምህርት እና የዜጎች ተጠቃሚነት ጉዳይም በስፋት የተነሳ ሲሆን፣ በእነዚህ የጤና ችግሮች የተጠቁ ህፃናት የማህበረሰቡ አካል መሆናቸው ታምኖበት ትምህርትን ጨምሮ ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶችን የማግኘት መብታቸው ሊከበር እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል።
መርሃ ግብሩ በእነዚህ ህፃናት ሰብአዊ መብት እና ማህበራዊ ተሳትፎ ዙሪያ ሰፊ ውይይት ያደረገ ሲሆን፣ ህብረተሰቡ ለችግሩ ተጋላጭ የሆኑ ወገኖችን ከመገለል እንዲታደግና አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ አሳስቧል።
በዚህ መርሃ ግብር ላይ የፌዴራል ጤና ሚኒስቴር ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ፣ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እና የማያ በጎ አድራጎት ድርጅት መስራቾች አስተባባሪዎች ተገኝተዋል።
ከእነዚህም በተጨማሪ የጥበብ ባለሙያዎች፣ የሚዲያ አካላት፣ እንዲሁም የችግሩ ተጋላጭ የሆኑ ህፃናትና ወላጆቻቸው በመሳተፍ ስለ በሽታው መከላከያ መንገዶች እና ስላለው ተግዳሮት በቂ ግንዛቤ እንዲጨበጥ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#healthawareness #ethiopia #spinabifida #hydrocephalus #mayacharitableorganization #publichealth #folicacid #inclusion #addisababa
4 months ago
የላቀ የክብር ሽልማት ለፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ!
#ethiopia | በኢትዮጵያ የጤና ምርምር ዘርፍ ጉልህ አሻራ ያሳረፉት ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ፣ በቲቢ (TB) ምርምርና አመራር ዘርፍ ላሳዩት አርአያነት ያለው ተግባር የትራክ (TRAC) ልዩ የክብር ሽልማት ተበረከተላቸው።
የአመራር ብቃት፦ የቲቢ ምርምር አማካሪ ጉባኤን (TRAC) በማጠናከርና የምርምር ባህልን በመገንባት ረገድ ላሳዩት ቀዳሚነት።
በመረጃ ላይ የተመሰረቱ የፖሊሲ ሃሳቦችን በማመንጨት የሀገሪቱን የጤና ስትራቴጂ በማገዝ።
ኢትዮጵያ ቲቢን ለመከላከልና ለማጥፋት በምታደርገው ጥረት ውስጥ የምርምር አቅጣጫዎችን በመቅረጽ ረገድ ላበረከቱት ጉልህ ሚና።
በምርምር ግኝቶችና በሕዝብ ጤና ፖሊሲዎች መካከል ጠንካራ ድልድይ በመገንባት የጤናውን ዘርፍ ወደ አዲስ ምዕራፍ በማሸጋገራቸው።
ፕሮፌሰር አፈወርቅ በአሁኑ ወቅት የአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት (AHRI) ዋና ዳይሬክተር እና የቲቢ ምርምር አማካሪ ጉባኤ (TRAC) ሰብሳቢ ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ።
#professorafeworkkassu #ahri #trac #healthresearch #ethiopia #tbresearch #publichealth #awardexcellence #medicalscience #getutemesgenmedia #ኢትዮጵያ #ጤና #ምርምር
#ethiopia | በኢትዮጵያ የጤና ምርምር ዘርፍ ጉልህ አሻራ ያሳረፉት ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ፣ በቲቢ (TB) ምርምርና አመራር ዘርፍ ላሳዩት አርአያነት ያለው ተግባር የትራክ (TRAC) ልዩ የክብር ሽልማት ተበረከተላቸው።
የአመራር ብቃት፦ የቲቢ ምርምር አማካሪ ጉባኤን (TRAC) በማጠናከርና የምርምር ባህልን በመገንባት ረገድ ላሳዩት ቀዳሚነት።
በመረጃ ላይ የተመሰረቱ የፖሊሲ ሃሳቦችን በማመንጨት የሀገሪቱን የጤና ስትራቴጂ በማገዝ።
ኢትዮጵያ ቲቢን ለመከላከልና ለማጥፋት በምታደርገው ጥረት ውስጥ የምርምር አቅጣጫዎችን በመቅረጽ ረገድ ላበረከቱት ጉልህ ሚና።
በምርምር ግኝቶችና በሕዝብ ጤና ፖሊሲዎች መካከል ጠንካራ ድልድይ በመገንባት የጤናውን ዘርፍ ወደ አዲስ ምዕራፍ በማሸጋገራቸው።
ፕሮፌሰር አፈወርቅ በአሁኑ ወቅት የአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት (AHRI) ዋና ዳይሬክተር እና የቲቢ ምርምር አማካሪ ጉባኤ (TRAC) ሰብሳቢ ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ።
#professorafeworkkassu #ahri #trac #healthresearch #ethiopia #tbresearch #publichealth #awardexcellence #medicalscience #getutemesgenmedia #ኢትዮጵያ #ጤና #ምርምር
4 months ago
አዎ! ቲቢን ለማጥፋት እንችላለን! ...
#ethiopia | የጤና ሚኒስቴር 20ኛውን ዓመታዊ የቲቢ ምርምር ጉባኤ እና የዓለም አቀፍ የቲቢ ቀንን ምክንያት በማድረግ ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ያዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ተካሂዷል።
ይህ የንቅናቄ መድረክ የተዘጋጀው የሚዲያ አካላት በበሽታው መከላከል እና መቆጣጠር ስራ ላይ ያላቸውን ከፍተኛ ሚና ውጤታማ በሆነ መንገድ እንዲወጡ ለማስቻል ሲሆን በስልጠናው ላይ ከተለያዩ ተቋማት የተወከሉ የጤና ባለሙያዎች እና ጋዜጠኞች ተሳትፈዋል።
በውይይቱ ላይ የተገኙት የአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ፤ በሽታውን ከመከላከል ባለፈ ሙሉ ለሙሉ ለማጥፋት በሚደረገው ጥረት ውስጥ የመገናኛ ብዙሃን ህብረተሰቡን በማንቃት በኩል የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
በጤና ሚኒስቴር የበሽታ መከላከል እና መቆጣጠር መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ሕይወት ሰለሞን በበኩላቸው፤ የሚዲያ ባለሙያዎች ስለ በሽታው ትክክለኛ መረጃ ለህዝብ በማድረስ ረገድ ያላቸውን ፋይዳ አብራርተዋል።
በጤና ሚኒስቴር የቲቢ፣ ስጋ ደዌ እና ሌሎች የሳንባ በሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር ዴስክ ኃላፊ አቶ ታየ ለታ ደግሞ፤ የቲቢ በሽታ ዛሬም በሰው ዘር ላይ ከፍተኛ ሕመምና ሞት እያስከተለ መሆኑን በመጠቆም፣ ቁጥጥሩን ለማጠናከር ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
የዓለም ቲቢ ቀን በየዓመቱ መጋቢት 15 ቀን (March 24) የሚከበር ሲሆን፣ ዕለቱ የተመረጠውም የዛሬ 140 ዓመት ታዋቂው ጀርመናዊ ተመራማሪ ዶ/ር ሮበርት ኮች የቲቢ በሽታ መንስኤ የሆነውን “ማይኮባክቴሪያም ቲዩበርክሎስስ” ማግኘቱን ለዓለም ያበሰረበትን ቀን ለማስታወስ ነው።
ዘንድሮም ቀኑ “አዎ! ቲቢን ለማጥፋት እንችላለን! በመንግስት መሪነት፤ በሕዝባችን ኃይል!!” በሚል መሪ ቃል በተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ይከበራል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #health #worldtbday #tbprevention #mediaawareness #publichealth #getutemesgen
#ethiopia | የጤና ሚኒስቴር 20ኛውን ዓመታዊ የቲቢ ምርምር ጉባኤ እና የዓለም አቀፍ የቲቢ ቀንን ምክንያት በማድረግ ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ያዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ተካሂዷል።
ይህ የንቅናቄ መድረክ የተዘጋጀው የሚዲያ አካላት በበሽታው መከላከል እና መቆጣጠር ስራ ላይ ያላቸውን ከፍተኛ ሚና ውጤታማ በሆነ መንገድ እንዲወጡ ለማስቻል ሲሆን በስልጠናው ላይ ከተለያዩ ተቋማት የተወከሉ የጤና ባለሙያዎች እና ጋዜጠኞች ተሳትፈዋል።
በውይይቱ ላይ የተገኙት የአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ፤ በሽታውን ከመከላከል ባለፈ ሙሉ ለሙሉ ለማጥፋት በሚደረገው ጥረት ውስጥ የመገናኛ ብዙሃን ህብረተሰቡን በማንቃት በኩል የድርሻቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።
በጤና ሚኒስቴር የበሽታ መከላከል እና መቆጣጠር መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ሕይወት ሰለሞን በበኩላቸው፤ የሚዲያ ባለሙያዎች ስለ በሽታው ትክክለኛ መረጃ ለህዝብ በማድረስ ረገድ ያላቸውን ፋይዳ አብራርተዋል።
በጤና ሚኒስቴር የቲቢ፣ ስጋ ደዌ እና ሌሎች የሳንባ በሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር ዴስክ ኃላፊ አቶ ታየ ለታ ደግሞ፤ የቲቢ በሽታ ዛሬም በሰው ዘር ላይ ከፍተኛ ሕመምና ሞት እያስከተለ መሆኑን በመጠቆም፣ ቁጥጥሩን ለማጠናከር ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
የዓለም ቲቢ ቀን በየዓመቱ መጋቢት 15 ቀን (March 24) የሚከበር ሲሆን፣ ዕለቱ የተመረጠውም የዛሬ 140 ዓመት ታዋቂው ጀርመናዊ ተመራማሪ ዶ/ር ሮበርት ኮች የቲቢ በሽታ መንስኤ የሆነውን “ማይኮባክቴሪያም ቲዩበርክሎስስ” ማግኘቱን ለዓለም ያበሰረበትን ቀን ለማስታወስ ነው።
ዘንድሮም ቀኑ “አዎ! ቲቢን ለማጥፋት እንችላለን! በመንግስት መሪነት፤ በሕዝባችን ኃይል!!” በሚል መሪ ቃል በተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ይከበራል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #health #worldtbday #tbprevention #mediaawareness #publichealth #getutemesgen
5 months ago
ዓለም ለከፋ የኒውክሌር ስጋት ዝግጁ እንድትሆን የዓለም ጤና ድርጅት ጥሪ አቀረበ!
#ethiopia | በዓለማችን ላይ እየታየ ያለው የጂኦፖለቲካዊ ውጥረት አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ተከትሎ፣ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ሊከሰቱ ለሚችሉ የኒውክሌር ወይም የራዲዮአክቲቭ ድንገተኛ አደጋዎች ከፍተኛ የዝግጅት ሥራ መጀመሩን አስታውቋል።
የድርጅቱ የቀጠና ዳይሬክተር ዶክተር ሃናን ባልኪ እንደገለጹት፣ ተቋሙ በአሁኑ ወቅት የጤና ባለሙያዎችን በማሰልጠን፣ የሕክምና ምላሽ ዕቅዶችን በማሻሻል እና የድንገተኛ ጊዜ ግብዓቶችን በማደራጀት ላይ በትኩረት እየሰራ ይገኛል።
⚠️ ዋና ዋና ነጥቦች፦
* የዝግጅቱ ስፋት፦ ዝግጅቱ በኒውክሌር ተቋማት ላይ ከሚደርሱ ድንገተኛ አደጋዎች ጀምሮ እስከ ከፋ የጦርነት ሁኔታዎች ድረስ ያሉትን እጅግ አስከፊ ስጋቶች ታሳቢ ያደረገ ነው።
* ምክንያቱ፦ በሀገራት መካከል ያለው አለመረጋጋት እና ወቅታዊው የዓለም ሁኔታ ለማንኛውም ያልተጠበቀ ክስተት አስቀድሞ መዘጋጀትን የግድ ማድረጉ ተገልጿል።
* የድርጅቱ አቋም፦ ምንም እንኳ እንዲህ ያሉ አደጋዎች በፍጹም እንዳይከሰቱ ምኞታቸው ቢሆንም፣ የሰው ልጆችን ደህንነት ለመጠበቅ ቅድመ መከላከል ቀዳሚ ግብ መሆኑን አሳስበዋል።
ይህ የዓለም ጤና ድርጅት እርምጃ፣ ዓለም አቀፍ ውጥረቶች በሰው ልጆች ጤና ላይ ሊያመጡ የሚችሉትን ከፍተኛ ስጋት በግልጽ የሚያሳይ ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #መናኸሪያFm #worldhealthorganization #nuclearsafety #globalnews #publichealth #breakingnews #stayinformed #emergencypreparedness
#ethiopia | በዓለማችን ላይ እየታየ ያለው የጂኦፖለቲካዊ ውጥረት አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ተከትሎ፣ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ሊከሰቱ ለሚችሉ የኒውክሌር ወይም የራዲዮአክቲቭ ድንገተኛ አደጋዎች ከፍተኛ የዝግጅት ሥራ መጀመሩን አስታውቋል።
የድርጅቱ የቀጠና ዳይሬክተር ዶክተር ሃናን ባልኪ እንደገለጹት፣ ተቋሙ በአሁኑ ወቅት የጤና ባለሙያዎችን በማሰልጠን፣ የሕክምና ምላሽ ዕቅዶችን በማሻሻል እና የድንገተኛ ጊዜ ግብዓቶችን በማደራጀት ላይ በትኩረት እየሰራ ይገኛል።
⚠️ ዋና ዋና ነጥቦች፦
* የዝግጅቱ ስፋት፦ ዝግጅቱ በኒውክሌር ተቋማት ላይ ከሚደርሱ ድንገተኛ አደጋዎች ጀምሮ እስከ ከፋ የጦርነት ሁኔታዎች ድረስ ያሉትን እጅግ አስከፊ ስጋቶች ታሳቢ ያደረገ ነው።
* ምክንያቱ፦ በሀገራት መካከል ያለው አለመረጋጋት እና ወቅታዊው የዓለም ሁኔታ ለማንኛውም ያልተጠበቀ ክስተት አስቀድሞ መዘጋጀትን የግድ ማድረጉ ተገልጿል።
* የድርጅቱ አቋም፦ ምንም እንኳ እንዲህ ያሉ አደጋዎች በፍጹም እንዳይከሰቱ ምኞታቸው ቢሆንም፣ የሰው ልጆችን ደህንነት ለመጠበቅ ቅድመ መከላከል ቀዳሚ ግብ መሆኑን አሳስበዋል።
ይህ የዓለም ጤና ድርጅት እርምጃ፣ ዓለም አቀፍ ውጥረቶች በሰው ልጆች ጤና ላይ ሊያመጡ የሚችሉትን ከፍተኛ ስጋት በግልጽ የሚያሳይ ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #መናኸሪያFm #worldhealthorganization #nuclearsafety #globalnews #publichealth #breakingnews #stayinformed #emergencypreparedness
5 months ago
በስፓይና ቢፊዳ እና ሀይድሮሴፋለስ ግንዛቤ የፈጠረ የተማሪዎች ውድድር ተካሄደ
#ethiopia | ሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች ከኒው አይሲቲ እና ኢቨንት ኦርጋናይዘር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የተማሪዎች የኪነ-ጥበብ እና የክህሎት ውድድር በወዳጅነት አደባባይ ተካሄደ።
መርሃ ግብሩ በተለይም በስፓይና ቢፊዳ (የነርቭ ዘንግ ክፍተት) እና በሀይድሮሴፋለስ (በጭንቅላት ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት) ዙሪያ ማህበረሰባዊ ግንዛቤን ለማሳደግ ያለመ መሆኑን አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
በዕለቱ በተካሄደው ውድድር ላይ ተማሪዎች በግጥም፣ ሙዚቃ፣ ስዕል እና ሞዴሊንግ እና በጥያቄና መልስ እንዲሁም አነቃቂ ንግግሮች ውድድር ተካሂዷል።
በተለይም በስፓይና ቢፊዳ (የነርቭ ዘንግ ክፍተት) እና በሀይድሮሴፋለስ (በጭንቅላት ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት) አስቀድሞ ለመከላከል የሚረዱ የጥንቃቄ መንገዶች እና የአመጋገብ ስርዓት ላይ ያተኮሩ መልዕክቶች ተላልፈዋል።
የሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ቤዛ በሻህ እንደገለጹት፤ እነዚህ የአፈጣጠር ችግሮች የጤና ተግዳሮት ብቻ ሳይሆኑ ሰፊ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ስነ-ልቦናዊ ጫና የሚያሳድሩ ጉዳዮች መሆናቸውን ገልጸው ችግሩን ከ70-75 በመቶ ፎሊክ አሲድ በመውሰድ መከላከል እንደሚቻል ተናግረዋል።
በዝግጅቱ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ምሁራን፣ የታሪክ ተመራማሪዎች፣ የጥበብ ባለሙያዎች፣ መምህራን እና ተማሪዎች ተገኝተዋል።
ይህ የተማሪዎች ላይ ትኩረት አድርጎ የተጀመረው የግንዛቤ ማስጨበጫ ውድድር በየሶስት ወሩ በተከታታይ እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
#spinabifida #hydrocephalus #awareness #hopesbh #publichealth #childhealth #ethiopia #prevention #educationalevent #friendshipsquare
#ethiopia | ሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች ከኒው አይሲቲ እና ኢቨንት ኦርጋናይዘር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የተማሪዎች የኪነ-ጥበብ እና የክህሎት ውድድር በወዳጅነት አደባባይ ተካሄደ።
መርሃ ግብሩ በተለይም በስፓይና ቢፊዳ (የነርቭ ዘንግ ክፍተት) እና በሀይድሮሴፋለስ (በጭንቅላት ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት) ዙሪያ ማህበረሰባዊ ግንዛቤን ለማሳደግ ያለመ መሆኑን አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
በዕለቱ በተካሄደው ውድድር ላይ ተማሪዎች በግጥም፣ ሙዚቃ፣ ስዕል እና ሞዴሊንግ እና በጥያቄና መልስ እንዲሁም አነቃቂ ንግግሮች ውድድር ተካሂዷል።
በተለይም በስፓይና ቢፊዳ (የነርቭ ዘንግ ክፍተት) እና በሀይድሮሴፋለስ (በጭንቅላት ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት) አስቀድሞ ለመከላከል የሚረዱ የጥንቃቄ መንገዶች እና የአመጋገብ ስርዓት ላይ ያተኮሩ መልዕክቶች ተላልፈዋል።
የሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ቤዛ በሻህ እንደገለጹት፤ እነዚህ የአፈጣጠር ችግሮች የጤና ተግዳሮት ብቻ ሳይሆኑ ሰፊ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ስነ-ልቦናዊ ጫና የሚያሳድሩ ጉዳዮች መሆናቸውን ገልጸው ችግሩን ከ70-75 በመቶ ፎሊክ አሲድ በመውሰድ መከላከል እንደሚቻል ተናግረዋል።
በዝግጅቱ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ምሁራን፣ የታሪክ ተመራማሪዎች፣ የጥበብ ባለሙያዎች፣ መምህራን እና ተማሪዎች ተገኝተዋል።
ይህ የተማሪዎች ላይ ትኩረት አድርጎ የተጀመረው የግንዛቤ ማስጨበጫ ውድድር በየሶስት ወሩ በተከታታይ እንደሚካሄድ አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
#spinabifida #hydrocephalus #awareness #hopesbh #publichealth #childhealth #ethiopia #prevention #educationalevent #friendshipsquare
Sponsored by
Surafel
5 months ago
የኢትዮጵያ የጤና ደህንነት ወደ ዲጂታል ምዕራፍ ተሸጋገረ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) የሀገሪቱን የጤና ስጋቶች በአንድ ማዕከል ለመቆጣጠር የሚያስችለውን ዘመናዊ የዲጂታል አሰራር ሥርዓት ዛሬ በይፋ አስመርቋል። ይህ አዲስ "የቁጥጥር ማዕከል" ኢትዮጵያ ለወረርሽኞችና ለድንገተኛ የጤና አደጋዎች ያላትን ምላሽ ፈጣንና መረጃን መሰረት ያደረገ ያደርገዋል።
🚀 ዋና ዋና ነጥቦች፦
ከወረዳ እስከ ማዕከል፦ አዲሱ አሰራር በእያንዳንዱ ወረዳ የሚታዩ የጤና ስጋቶችን በቅርበት ለመለየትና መረጃዎችን በፍጥነት ለመለዋወጥ ያስችላል።
800 ሚሊዮን ብር ድጋፍ፦ ዲጂታላይዜሽኑን እስከ ታችኛው መዋቅር ለማውረድ፣ ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የICT መሣሪያዎች ለክልል ጤና ቢሮዎች ተከፋፍለዋል።
የልህቀት ማዕከል፦ ይህ እርምጃ ተቋሙን በምስራቅ አፍሪካ የጤና ዘርፍ ግንባር ቀደም የልህቀት ማዕከል ለማድረግ የተያዘውን ግብ ያሳካል።
እንደ ኮቪድ-19 ያሉ ወረርሽኞች በገጠሙን ጊዜ ትልቁ ፈተና የነበረው የተበታተነና የዘገየ የመረጃ ልውውጥ ነበር። አሁን ግን ቴክኖሎጂን በመጠቀም ወረርሽኞችን ገና በጅምራቸው መለየትና የቅድመ ማስጠንቀቂያ እርምጃዎችን መውሰድ ይቻላል።
#publichealth #digitalhealth #ethiopia #healthtech #ephi #diseasesurveillance #innovation #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
#ethiopia | የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት (EPHI) የሀገሪቱን የጤና ስጋቶች በአንድ ማዕከል ለመቆጣጠር የሚያስችለውን ዘመናዊ የዲጂታል አሰራር ሥርዓት ዛሬ በይፋ አስመርቋል። ይህ አዲስ "የቁጥጥር ማዕከል" ኢትዮጵያ ለወረርሽኞችና ለድንገተኛ የጤና አደጋዎች ያላትን ምላሽ ፈጣንና መረጃን መሰረት ያደረገ ያደርገዋል።
🚀 ዋና ዋና ነጥቦች፦
ከወረዳ እስከ ማዕከል፦ አዲሱ አሰራር በእያንዳንዱ ወረዳ የሚታዩ የጤና ስጋቶችን በቅርበት ለመለየትና መረጃዎችን በፍጥነት ለመለዋወጥ ያስችላል።
800 ሚሊዮን ብር ድጋፍ፦ ዲጂታላይዜሽኑን እስከ ታችኛው መዋቅር ለማውረድ፣ ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የICT መሣሪያዎች ለክልል ጤና ቢሮዎች ተከፋፍለዋል።
የልህቀት ማዕከል፦ ይህ እርምጃ ተቋሙን በምስራቅ አፍሪካ የጤና ዘርፍ ግንባር ቀደም የልህቀት ማዕከል ለማድረግ የተያዘውን ግብ ያሳካል።
እንደ ኮቪድ-19 ያሉ ወረርሽኞች በገጠሙን ጊዜ ትልቁ ፈተና የነበረው የተበታተነና የዘገየ የመረጃ ልውውጥ ነበር። አሁን ግን ቴክኖሎጂን በመጠቀም ወረርሽኞችን ገና በጅምራቸው መለየትና የቅድመ ማስጠንቀቂያ እርምጃዎችን መውሰድ ይቻላል።
#publichealth #digitalhealth #ethiopia #healthtech #ephi #diseasesurveillance #innovation #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
6 months ago
ዶ/ር መቅደስ ዳባ ለሀገር ባበረከቱት አስተዋጽኦ ተሸለሙ! 🇪🇹
#ethiopia | "የማርበርግ ቫይረስን ከኢትዮጵያ ለማጥፋት ላደረጉት አመራር እውቅና ተሰጠ"
የጤና ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር መቅደስ ዳባ፤ ሀገር አቀፍ የጤና ግብረ ኃይልን በመምራት ድንገተኛ የጤና አደጋ ክስተቶችን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ላሳዩት ከፍተኛ ቁርጠኝነት የእውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
በተለይም የማርበርግ ቫይረስ በሽታ (Marburg Virus) ከኢትዮጵያ እንዲወገድ ባደረጉት ከፍተኛ አስተዋጽኦ፤ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ በተከበሩ አቶ ታገሰ ጫፎ እጅ ሽልማቱን ተቀብለዋል።
ይህ ሽልማት የጤናው ዘርፍ ለህብረተሰቡ ደህንነት እየከፈለ ላለው ዋጋ ትልቅ ማረጋገጫ ነው።
ክብርት ሚኒስትር ላደረጉት አስተዋጽኦ እናመሰግናለን! 👏🏥
#drmekdesdaba #ministryofhealth #award #publichealth #ethiopia #marburgfree #moh
#ethiopia | "የማርበርግ ቫይረስን ከኢትዮጵያ ለማጥፋት ላደረጉት አመራር እውቅና ተሰጠ"
የጤና ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር መቅደስ ዳባ፤ ሀገር አቀፍ የጤና ግብረ ኃይልን በመምራት ድንገተኛ የጤና አደጋ ክስተቶችን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ላሳዩት ከፍተኛ ቁርጠኝነት የእውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
በተለይም የማርበርግ ቫይረስ በሽታ (Marburg Virus) ከኢትዮጵያ እንዲወገድ ባደረጉት ከፍተኛ አስተዋጽኦ፤ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ በተከበሩ አቶ ታገሰ ጫፎ እጅ ሽልማቱን ተቀብለዋል።
ይህ ሽልማት የጤናው ዘርፍ ለህብረተሰቡ ደህንነት እየከፈለ ላለው ዋጋ ትልቅ ማረጋገጫ ነው።
ክብርት ሚኒስትር ላደረጉት አስተዋጽኦ እናመሰግናለን! 👏🏥
#drmekdesdaba #ministryofhealth #award #publichealth #ethiopia #marburgfree #moh
7 months ago
🛑 በኢሊባቡር ዞን በህገ-ወጥ መንገድ የታረደው ስጋ ተወገደ
#ethiopia | በኢሊባቡር ዞን ሀሉ ወረዳ ውስጥ ያለ ቅድመ ጤና ምርመራ እና ከንግድ ፈቃድ ውጭ በድብቅ እርድ ሲፈፅሙ የተገኙ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለጠ።
🔍 ዋና ዋና ነጥቦች፦
* ጥቆማው፡ ድርጊቱ የተደረሰበት ከአካባቢው ማህበረሰብ በተገኘ ጥቆማ መሰረት ሲሆን፣ እርዱ የተከናወነው ለጤና ምቹ ባልሆነ ቦታ እና በድብቅ ነበር።
* እርምጃው፡ በህገ-ወጥ መንገድ የታረደው በሬ ስጋ ለጤና አደገኛ መሆኑ በእይታ በመረጋገጡ፣ ለምግብነት ሳይውል እንዲወገድ ተደርጓል።
* ተጠርጣሪዎቹ፡ ግለሰቦቹ ስጋውን በተሽከርካሪ ጭነው ለተጠቃሚዎች ለማቅረብ ሲሞክሩ እጅ ከፍንጅ የተያዙ ሲሆን፣ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው ይገኛል።
* ህጋዊ ተጠያቂነት፡ በኦሮሚያ ክልል የስጋ ምርቶችን ለመቆጣጠር የወጣውን መመሪያ ቁጥር 8/2014 በመጥቀስ ተጠርጣሪዎቹ ላይ ክስ እንደሚመሰረትባቸው የወረዳው ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
ህብረተሰቡ መሰል ህገ-ወጥ ድርጊቶችን ሲመለከት ለሚመለከተው አካል ጥቆማ በመስጠት ጤናውን እንዲጠብቅ መልዕክት ተላልፏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia #iluababor #publichealth #legalaction #illegalslaughtering #dagujournal #oromia #news
#ethiopia | በኢሊባቡር ዞን ሀሉ ወረዳ ውስጥ ያለ ቅድመ ጤና ምርመራ እና ከንግድ ፈቃድ ውጭ በድብቅ እርድ ሲፈፅሙ የተገኙ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለጠ።
🔍 ዋና ዋና ነጥቦች፦
* ጥቆማው፡ ድርጊቱ የተደረሰበት ከአካባቢው ማህበረሰብ በተገኘ ጥቆማ መሰረት ሲሆን፣ እርዱ የተከናወነው ለጤና ምቹ ባልሆነ ቦታ እና በድብቅ ነበር።
* እርምጃው፡ በህገ-ወጥ መንገድ የታረደው በሬ ስጋ ለጤና አደገኛ መሆኑ በእይታ በመረጋገጡ፣ ለምግብነት ሳይውል እንዲወገድ ተደርጓል።
* ተጠርጣሪዎቹ፡ ግለሰቦቹ ስጋውን በተሽከርካሪ ጭነው ለተጠቃሚዎች ለማቅረብ ሲሞክሩ እጅ ከፍንጅ የተያዙ ሲሆን፣ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው ይገኛል።
* ህጋዊ ተጠያቂነት፡ በኦሮሚያ ክልል የስጋ ምርቶችን ለመቆጣጠር የወጣውን መመሪያ ቁጥር 8/2014 በመጥቀስ ተጠርጣሪዎቹ ላይ ክስ እንደሚመሰረትባቸው የወረዳው ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
ህብረተሰቡ መሰል ህገ-ወጥ ድርጊቶችን ሲመለከት ለሚመለከተው አካል ጥቆማ በመስጠት ጤናውን እንዲጠብቅ መልዕክት ተላልፏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia #iluababor #publichealth #legalaction #illegalslaughtering #dagujournal #oromia #news
7 months ago
📢 በኢትዮጵያ የማርበርግ ወረርሽኝን የመቆጣጠር ስራ ውጤት እያሳየ ነው
#ethiopia | የጤና ሚኒስቴር በሀገራችን ተከስቶ የነበረውን የማርበርግ ቫይረስ ወረርሽኝን አስመልክቶ ወቅታዊ መረጃ ሰጥቷል። ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ፣ ወረርሽኙን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለመቆጣጠር በተደረገው የተቀናጀ ርብርብ አመርቂ ውጤት መመዝገቡን ገልጿል።
📊 የወረርሽኙ ሁኔታ በቁጥር (ከህዳር 5 እስከ ታህሳስ 27)
ባለፉት ሁለት ወራት ውስጥ የበሽታውን ስርጭት ለመለየት ሰፊ የላብራቶሪ ምርመራዎች ተካሄደዋል፦
* አጠቃላይ የተመረመሩ ሰዎች፦ 3,800
* ቫይረሱ የተገኘባቸው፦ 14 ሰዎች
* የሞቱ፦ 9 ሰዎች
* ያገገሙ፦ 5 ሰዎች
🛡️ ጥንቃቄው አሁንም ይቀጥላል!
ሚኒስቴሩ በአሁኑ ወቅት ከተረጋገጠ ታማሚ ጋር ንክኪ ኖሮት ክትትል የሚደረግለት ሰው አለመኖሩን ቢያረጋግጥም፣ "ቸልተኝነት አያስፈልግም" ሲል አስጠንቅቋል። የበሽታውን ዳግም መከሰት ሙሉ በሙሉ ለመከላከል የሚከተሉት ጥንቃቄዎች ለቀጣዮቹ 21 ቀናት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስቧል፦
* የማኅበረሰብ አቀፍ መከላከያ መንገዶችን መተግበር።
* የጤና ስጋት ተግባቦቶችንና መመሪያዎችን መከተል።
🙏 ምስጋና እና እውቅና
በመጨረሻም ሚኒስቴሩ ወረርሽኙን ለመግታት በቆራጥነት ለተሳተፉ የጤና ባለሙያዎች፣ ለዘርፉ አመራሮች፣ ለአጋር ድርጅቶች እና መመሪያዎችን ተግባራዊ ላደረገው መላው የሕብረተሰብ ክፍል ላቅ ያለ ምስጋናውን አቅርቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#marburgvirus #ethiopiahealth #publichealth #staysafe #ministryofhealth #ethiopia #የጤናሚኒስቴር #ማርበርግ
#ethiopia | የጤና ሚኒስቴር በሀገራችን ተከስቶ የነበረውን የማርበርግ ቫይረስ ወረርሽኝን አስመልክቶ ወቅታዊ መረጃ ሰጥቷል። ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ፣ ወረርሽኙን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለመቆጣጠር በተደረገው የተቀናጀ ርብርብ አመርቂ ውጤት መመዝገቡን ገልጿል።
📊 የወረርሽኙ ሁኔታ በቁጥር (ከህዳር 5 እስከ ታህሳስ 27)
ባለፉት ሁለት ወራት ውስጥ የበሽታውን ስርጭት ለመለየት ሰፊ የላብራቶሪ ምርመራዎች ተካሄደዋል፦
* አጠቃላይ የተመረመሩ ሰዎች፦ 3,800
* ቫይረሱ የተገኘባቸው፦ 14 ሰዎች
* የሞቱ፦ 9 ሰዎች
* ያገገሙ፦ 5 ሰዎች
🛡️ ጥንቃቄው አሁንም ይቀጥላል!
ሚኒስቴሩ በአሁኑ ወቅት ከተረጋገጠ ታማሚ ጋር ንክኪ ኖሮት ክትትል የሚደረግለት ሰው አለመኖሩን ቢያረጋግጥም፣ "ቸልተኝነት አያስፈልግም" ሲል አስጠንቅቋል። የበሽታውን ዳግም መከሰት ሙሉ በሙሉ ለመከላከል የሚከተሉት ጥንቃቄዎች ለቀጣዮቹ 21 ቀናት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስቧል፦
* የማኅበረሰብ አቀፍ መከላከያ መንገዶችን መተግበር።
* የጤና ስጋት ተግባቦቶችንና መመሪያዎችን መከተል።
🙏 ምስጋና እና እውቅና
በመጨረሻም ሚኒስቴሩ ወረርሽኙን ለመግታት በቆራጥነት ለተሳተፉ የጤና ባለሙያዎች፣ ለዘርፉ አመራሮች፣ ለአጋር ድርጅቶች እና መመሪያዎችን ተግባራዊ ላደረገው መላው የሕብረተሰብ ክፍል ላቅ ያለ ምስጋናውን አቅርቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#marburgvirus #ethiopiahealth #publichealth #staysafe #ministryofhealth #ethiopia #የጤናሚኒስቴር #ማርበርግ
7 months ago
📢 የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ዕለታዊ መረጃ
ታህሳስ 20 ቀን 2018 ዓ.ም
#ethiopia | የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ የሕዝብ ጤና ኢንስቲትዩት በሀገራችን ያለውን የማርበርግ ቫይረስ በሽታ (Marburg Virus Disease) ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ የዕለቱን መረጃ ይፋ አድርገዋል።
🔍 የዕለቱ ዋና ዋና ነጥቦች፦
የክትትል ሁኔታ፦ የጤና ባለሙያዎች በሽታው ሊከሰትባቸው ይችላል ተብለው በተለዩ አካባቢዎች እና የድንበር መግቢያዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እና ክትትል እያደረጉ ይገኛሉ።
የላቦራቶሪ ምርመራ፦ ጥርጣሬ የታየባቸው ናሙናዎች በብሔራዊ የላቦራቶሪ ማዕከል ምርመራ እየተደረገባቸው ሲሆን፣ ውጤቱም በየጊዜው ለሕዝብ ይፋ ይደረጋል።
የቅድመ ዝግጅት ስራዎች፦ የሕክምና ማዕከላት አስፈላጊውን ግብዓት በማሟላት እና የሰው ኃይል በማሰልጠን ዝግጁነታቸውን አጠናክረዋል።
⚠️ ማስታወስ ያለብዎት ጥንቃቄዎች፦
የማርበርግ ቫይረስ በሽታ በከፍተኛ ትኩሳት፣ በራስ ምታት እና በጡንቻ ሕመም የሚጀምር ሲሆን፤ በሽታውን ለመከላከል የሚከተሉትን ነጥቦች ይተግብሩ፦
ንክኪን ማስወገድ፦ የታመመ ሰው ፈሳሽ (ደም፣ ምራቅ፣ ላብ) ጋር ከመነካካት ይቆጠቡ።
ንጽህናን መጠበቅ፦ እጅን በሳሙና እና በውኃ ደጋግሞ መታጠብ።
ሪፖርት ማድረግ፦ ከፍተኛ ትኩሳት እና መሰል ምልክቶች የታየበት ሰው ሲኖር በአቅራቢያዎ ለሚገኝ የጤና ተቋም ወይም በነፃ ስልክ መስመር 8335 በመደወል ያሳውቁ።
ውድ ተከታታዮቻችን፦ የጤና መረጃዎችን ከትክክለኛ ምንጮች ብቻ በመውሰድ ራስዎንና ቤተሰብዎን ከሐሰተኛ ወሬዎች ይጠብቁ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#marburgvirus #healthupdate #ethiopia #moh #ephi #publichealth #staysafe #prevention
ታህሳስ 20 ቀን 2018 ዓ.ም
#ethiopia | የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ የሕዝብ ጤና ኢንስቲትዩት በሀገራችን ያለውን የማርበርግ ቫይረስ በሽታ (Marburg Virus Disease) ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ የዕለቱን መረጃ ይፋ አድርገዋል።
🔍 የዕለቱ ዋና ዋና ነጥቦች፦
የክትትል ሁኔታ፦ የጤና ባለሙያዎች በሽታው ሊከሰትባቸው ይችላል ተብለው በተለዩ አካባቢዎች እና የድንበር መግቢያዎች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እና ክትትል እያደረጉ ይገኛሉ።
የላቦራቶሪ ምርመራ፦ ጥርጣሬ የታየባቸው ናሙናዎች በብሔራዊ የላቦራቶሪ ማዕከል ምርመራ እየተደረገባቸው ሲሆን፣ ውጤቱም በየጊዜው ለሕዝብ ይፋ ይደረጋል።
የቅድመ ዝግጅት ስራዎች፦ የሕክምና ማዕከላት አስፈላጊውን ግብዓት በማሟላት እና የሰው ኃይል በማሰልጠን ዝግጁነታቸውን አጠናክረዋል።
⚠️ ማስታወስ ያለብዎት ጥንቃቄዎች፦
የማርበርግ ቫይረስ በሽታ በከፍተኛ ትኩሳት፣ በራስ ምታት እና በጡንቻ ሕመም የሚጀምር ሲሆን፤ በሽታውን ለመከላከል የሚከተሉትን ነጥቦች ይተግብሩ፦
ንክኪን ማስወገድ፦ የታመመ ሰው ፈሳሽ (ደም፣ ምራቅ፣ ላብ) ጋር ከመነካካት ይቆጠቡ።
ንጽህናን መጠበቅ፦ እጅን በሳሙና እና በውኃ ደጋግሞ መታጠብ።
ሪፖርት ማድረግ፦ ከፍተኛ ትኩሳት እና መሰል ምልክቶች የታየበት ሰው ሲኖር በአቅራቢያዎ ለሚገኝ የጤና ተቋም ወይም በነፃ ስልክ መስመር 8335 በመደወል ያሳውቁ።
ውድ ተከታታዮቻችን፦ የጤና መረጃዎችን ከትክክለኛ ምንጮች ብቻ በመውሰድ ራስዎንና ቤተሰብዎን ከሐሰተኛ ወሬዎች ይጠብቁ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#marburgvirus #healthupdate #ethiopia #moh #ephi #publichealth #staysafe #prevention
Sponsored by
Surafel
Comments