6 days ago
የኩርሙክ ወርቅ ማዕድን ሥራውን በነሐሴ ወር ሊጀምር መሆኑ ተገለጸ
👉የቻይናው ግዙፍ ወርቅ አምራች 9 በመቶ ድርሻ ለመውሰድ ተስማምቷል
የካናዳው ማዕድን አምራች ኩባንያ የሆነው አላይድ ጎልድ ኮርፖሬሽን በኢትዮጵያ የሚገኘውን ግዙፉን የኩርሙክ ወርቅ ማዕድን ማውጫ ፕሮጀክት ግንባታ አጠናቆ በመጪው የነሐሴ ወር ውስጥ ሥራ ሊጀምር መሆኑን አስታወቀ። ማዕድን ማውጫው ሥራውን ሲጀምር የመጀመሪያውን ወርቅ ምርት በቅርብ ሳምንታት ውስጥ ለገበያ ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ ወሳኝ መረጃ ይፋ የሆነው ከአላይድ ጎልድ እና ከቻይናው ዚጂን ጎልድ ኢንተርናሽናል ጋር የነበረው የ4 ቢሊዮን ዶላር የመገዛት ስምምነት መሰረዙን ተከትሎ ነው።
እንደሚታወሰው የቻይናው ኩባንያ አላይድ ጎልድን በአክሲዮን ለመግዛት አቅዶ አንዳንድ ቅድመ ሁኔታዎች በመዘግየታቸው የስምምነቱ የመጨረሻ የጊዜ ገደብ ሊከበር እንዳልቻለ አላይድ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጠቅሷል።
ሆኖም ሁለቱ ኩባንያዎች ሙሉ ግዢውን በመሰረዝ ፋንታ በግንኙነታቸው ለመቀጠል እና አዲስ አጋርነት ለመፍጠር በመስማማታቸው ዚጂን ጎልድ በግምት 295 ሚሊዮን ዶላር ስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንት በአላይድ ጎልድ ላይ አድርጓል።
በዚህ አዲስ የኢንቨስትመንት ስምምነት መሠረት ዚጂን ጎልድ 12.8 ሚሊዮን መደበኛ አክሲዮኖችን የሚገዛ ሲሆን፣ ይህም የኩባንያውን 9.2 በመቶ ድርሻ እንዲይዝ ያስችለዋል።
አላይድ ጎልድ እንዳስታወቀው ከዚህ አጋርነት ከሚገኘው የገንዘብ መጠን ውስጥ ከፍተኛው ድርሻ ለኩባንያው ዕድገት ስትራቴጂ፣ ለአሰራር ማሻሻያ እና በተለይም በኢትዮጵያ የሚገኘውን የኩርሙክ ወርቅ ማዕድን ፕሮጀክት ግንባታ ወደ ምርት ለማሸጋገር ይውላል። ከዚህ በተጨማሪ በ ማሊ የሚገኘውን የሳዲዮላ ማዕድን ማስፋፊያ፣ በኮትዲዕፍዋር ያሉ የምርት ማሳደግ ሥራዎችን እና በሌሎችም አካባቢዎች የሚደረጉ የፍለጋ ሥራዎችን ፋይናንስ ለማድረግ ያገለግላል ብሏል።
የኩርሙክ ወርቅ ማዕድን ማውጫ ሥራውን መጀመር ለኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ ትልቅ ፋይዳ ያለው ሲሆን፣ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ከማሳደግ ባለፈ ለአካባቢው ማህበረሰብ በርካታ የስራ እድሎችን ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
#ቅዳሜገበያ #etbusinessview #ethiopia #alliedgoldcorp #mali #cotedivoire #canada #china #zijingold Ministry of Finance - Ethiopia Ministry of Mines - Ethiopia Abiy Ahmed Ali
👉የቻይናው ግዙፍ ወርቅ አምራች 9 በመቶ ድርሻ ለመውሰድ ተስማምቷል
የካናዳው ማዕድን አምራች ኩባንያ የሆነው አላይድ ጎልድ ኮርፖሬሽን በኢትዮጵያ የሚገኘውን ግዙፉን የኩርሙክ ወርቅ ማዕድን ማውጫ ፕሮጀክት ግንባታ አጠናቆ በመጪው የነሐሴ ወር ውስጥ ሥራ ሊጀምር መሆኑን አስታወቀ። ማዕድን ማውጫው ሥራውን ሲጀምር የመጀመሪያውን ወርቅ ምርት በቅርብ ሳምንታት ውስጥ ለገበያ ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ ወሳኝ መረጃ ይፋ የሆነው ከአላይድ ጎልድ እና ከቻይናው ዚጂን ጎልድ ኢንተርናሽናል ጋር የነበረው የ4 ቢሊዮን ዶላር የመገዛት ስምምነት መሰረዙን ተከትሎ ነው።
እንደሚታወሰው የቻይናው ኩባንያ አላይድ ጎልድን በአክሲዮን ለመግዛት አቅዶ አንዳንድ ቅድመ ሁኔታዎች በመዘግየታቸው የስምምነቱ የመጨረሻ የጊዜ ገደብ ሊከበር እንዳልቻለ አላይድ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጠቅሷል።
ሆኖም ሁለቱ ኩባንያዎች ሙሉ ግዢውን በመሰረዝ ፋንታ በግንኙነታቸው ለመቀጠል እና አዲስ አጋርነት ለመፍጠር በመስማማታቸው ዚጂን ጎልድ በግምት 295 ሚሊዮን ዶላር ስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንት በአላይድ ጎልድ ላይ አድርጓል።
በዚህ አዲስ የኢንቨስትመንት ስምምነት መሠረት ዚጂን ጎልድ 12.8 ሚሊዮን መደበኛ አክሲዮኖችን የሚገዛ ሲሆን፣ ይህም የኩባንያውን 9.2 በመቶ ድርሻ እንዲይዝ ያስችለዋል።
አላይድ ጎልድ እንዳስታወቀው ከዚህ አጋርነት ከሚገኘው የገንዘብ መጠን ውስጥ ከፍተኛው ድርሻ ለኩባንያው ዕድገት ስትራቴጂ፣ ለአሰራር ማሻሻያ እና በተለይም በኢትዮጵያ የሚገኘውን የኩርሙክ ወርቅ ማዕድን ፕሮጀክት ግንባታ ወደ ምርት ለማሸጋገር ይውላል። ከዚህ በተጨማሪ በ ማሊ የሚገኘውን የሳዲዮላ ማዕድን ማስፋፊያ፣ በኮትዲዕፍዋር ያሉ የምርት ማሳደግ ሥራዎችን እና በሌሎችም አካባቢዎች የሚደረጉ የፍለጋ ሥራዎችን ፋይናንስ ለማድረግ ያገለግላል ብሏል።
የኩርሙክ ወርቅ ማዕድን ማውጫ ሥራውን መጀመር ለኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ ትልቅ ፋይዳ ያለው ሲሆን፣ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ከማሳደግ ባለፈ ለአካባቢው ማህበረሰብ በርካታ የስራ እድሎችን ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
#ቅዳሜገበያ #etbusinessview #ethiopia #alliedgoldcorp #mali #cotedivoire #canada #china #zijingold Ministry of Finance - Ethiopia Ministry of Mines - Ethiopia Abiy Ahmed Ali
2 months ago
ኮትዲቯር በኢኳዶር ላይ ድል አስመዘገበች
#ethiopia | በዓለም ዋንጫ ምድብ አምስት የመጀመሪያ ጨዋታ የኮትዲቯር ብሔራዊ ቡድን በአማድ ዲያሎ የመጨረሻ ደቂቃ ግብ ኢኳዶርን 1 ለ 0 በሆነ ጠባብ ውጤት አሸንፏል።
በሁለተኛው አጋማሽ ተቀይሮ ወደ ሜዳ የገባው የማንችስተር ዩናይትዱ የፊት መስመር ተጫዋች ባስቆጠራት ወሳኝ ጎል ሀገሩ የሶስት ነጥብ ባለቤት መሆን ችላለች።
ይህ ድል ኮትዲቯር ከ2014 ዓመተ ምህረት በኋላ በዓለም ዋንጫ መድረክ ላይ ያስመዘገበችው የመጀመሪያው የድል ምዕራፍ ሆኖ ተመዝግቧል።
#worldcup #cotedivoire #ecuador #amaddiallo #footballnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በዓለም ዋንጫ ምድብ አምስት የመጀመሪያ ጨዋታ የኮትዲቯር ብሔራዊ ቡድን በአማድ ዲያሎ የመጨረሻ ደቂቃ ግብ ኢኳዶርን 1 ለ 0 በሆነ ጠባብ ውጤት አሸንፏል።
በሁለተኛው አጋማሽ ተቀይሮ ወደ ሜዳ የገባው የማንችስተር ዩናይትዱ የፊት መስመር ተጫዋች ባስቆጠራት ወሳኝ ጎል ሀገሩ የሶስት ነጥብ ባለቤት መሆን ችላለች።
ይህ ድል ኮትዲቯር ከ2014 ዓመተ ምህረት በኋላ በዓለም ዋንጫ መድረክ ላይ ያስመዘገበችው የመጀመሪያው የድል ምዕራፍ ሆኖ ተመዝግቧል።
#worldcup #cotedivoire #ecuador #amaddiallo #footballnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
በዓለም ዋንጫ የአፍሪካ አህጉር ተወካዮች የሆኑት ኮትዲቯር እና ቱኒዚያ ዛሬ ወደ ሜዳ ይገባሉ
#ethiopia | በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ባለው የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ውድድር አፍሪካን ወክለው የሚሳተፉት ኮትዲቯር እና ቱኒዚያ ዛሬ ምሽት የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታቸውን ያከናውናሉ።
በዚህም መሠረት የዝሆኖቹ ሀገር ኮትዲቯር ከደቡብ አሜሪካዋ ጠንካራ ተጋጣሚ ኢኳዶር ጋር ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት ላይ ትገናኛለች።
በአውሮፓ ታዋቂ ሊጎች ውስጥ የሚጫወቱ በርካታ ባለክህሎት ተጫዋቾችን የያዘችው ኮትዲቯር ለኢኳዶር ከባድ ፈተና እንደምትሆን በስፋት ተገምቷል።
ሌላኛዋ የአፍሪካ ተወካይ ሰሜን አፍሪካዊቷ ቱኒዚያ በበኩሏ ከጠንካራዋ የአውሮፓ ሀገር ስዊድን ጋር ከሌሊቱ 11 ሰዓት ላይ ፍልሚያዋን ታደርጋለች።
ከእነዚህ ጨዋታዎች አስቀድሞ ምሽት ሁለት ሰዓት ላይ በዓለም እግር ኳስ ግዙፍ ስም ያላት ጀርመን ከካራካኦ ጋር የምታደርገው ጨዋታ በብዙዎች ዘንድ ይጠበቃል።
በተጨማሪም ኔዘርላንድ ከእስያዋ ተስፈኛ ሀገር ጃፓን ጋር የምታደርገው ጨዋታ የዛሬው ምሽት ሌላኛው አጓጊ መርሃ ግብር ነው።
ትናንት ምሽት በተከናወኑ ጨዋታዎች አውስትራሊያ ቱርኪዬን ሁለት ለባዶ ያሸነፈች ሲሆን ስኮትላንድ በበኩሏ ሃይቲን አንድ ለባዶ በሆነ ጠባብ ውጤት ማሸነፍ ችላለች።
በሌላ በኩል በአፍሪካ ኩራት የሆነችው ሞሮኮ ከዓለም እግር ኳስ ኃያሏ ብራዚል ጋር እንዲሁም ኳታር ከስዊዘርላንድ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ በተመሳሳይ አንድ ለአንድ በሆነ አቻ ውጤት አጠናቀዋል።
#worldcup2026 #africanfootball #cotedivoire #tunisia #fifaworldcup #footballnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ ባለው የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ውድድር አፍሪካን ወክለው የሚሳተፉት ኮትዲቯር እና ቱኒዚያ ዛሬ ምሽት የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታቸውን ያከናውናሉ።
በዚህም መሠረት የዝሆኖቹ ሀገር ኮትዲቯር ከደቡብ አሜሪካዋ ጠንካራ ተጋጣሚ ኢኳዶር ጋር ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት ላይ ትገናኛለች።
በአውሮፓ ታዋቂ ሊጎች ውስጥ የሚጫወቱ በርካታ ባለክህሎት ተጫዋቾችን የያዘችው ኮትዲቯር ለኢኳዶር ከባድ ፈተና እንደምትሆን በስፋት ተገምቷል።
ሌላኛዋ የአፍሪካ ተወካይ ሰሜን አፍሪካዊቷ ቱኒዚያ በበኩሏ ከጠንካራዋ የአውሮፓ ሀገር ስዊድን ጋር ከሌሊቱ 11 ሰዓት ላይ ፍልሚያዋን ታደርጋለች።
ከእነዚህ ጨዋታዎች አስቀድሞ ምሽት ሁለት ሰዓት ላይ በዓለም እግር ኳስ ግዙፍ ስም ያላት ጀርመን ከካራካኦ ጋር የምታደርገው ጨዋታ በብዙዎች ዘንድ ይጠበቃል።
በተጨማሪም ኔዘርላንድ ከእስያዋ ተስፈኛ ሀገር ጃፓን ጋር የምታደርገው ጨዋታ የዛሬው ምሽት ሌላኛው አጓጊ መርሃ ግብር ነው።
ትናንት ምሽት በተከናወኑ ጨዋታዎች አውስትራሊያ ቱርኪዬን ሁለት ለባዶ ያሸነፈች ሲሆን ስኮትላንድ በበኩሏ ሃይቲን አንድ ለባዶ በሆነ ጠባብ ውጤት ማሸነፍ ችላለች።
በሌላ በኩል በአፍሪካ ኩራት የሆነችው ሞሮኮ ከዓለም እግር ኳስ ኃያሏ ብራዚል ጋር እንዲሁም ኳታር ከስዊዘርላንድ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ በተመሳሳይ አንድ ለአንድ በሆነ አቻ ውጤት አጠናቀዋል።
#worldcup2026 #africanfootball #cotedivoire #tunisia #fifaworldcup #footballnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Comments