10 days ago
"የዜሮ እዳ ባለቤቶች"
#ethiopia | በዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) በኩል የሚሰጡ የብድር አቅርቦት እና የፋይናንስ ድጋፍ ለብዙ አፍሪካ ሀገራት ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት ነው።
2026 ከተቋሙ አነስተኛ የብድር እዳ ያለባቸው የአፍሪካ ሀገራት ዝርዝር ይፋ ሆኗል።
እንደ አለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ወቅታዊ መረጃ አነስተኛ የብድር እዳ ካለባቸው ሀገራት መካከል በመጀመሪያው ተሰልፈው የሚገኙት በድርጅቱ አሰራርና አጠራር መሠረት የዜሮ እዳ ባለቤት የሆኑት ሀገራት ናቸው።
በዚህም ቦትስዋና፣ ሊቢያ፣ ኤርትራ፣ አልጄሪያ፣ ናይጄሪያ እና ሞሪሸስ ከIMF ጋር አሁናዊ የብድር እዳ የሌለባቸው ሀገራት በመሆን የዝርዝሩን አናት ይዘዋል።
በሌላ በኩል ከተቋሙ ጋር ንቁ የብድር ፕሮግራም እያካሄዱ ነገር ግን በዝቅተኛ የብድር መጠን ዝርዝር ውስጥ የተካተቱት 10 የአፍሪካ ሀገራትም አሉ።
ሌሶቶ፣ ኤስዋቲኒ፣ ጂቡቲ፣ ኮምሮስ፣
ሳኦ ቶሜ ፕሬንስፔ፣ኢኳቶሪያል ጊኒ፣ጊኒ ቢሳዎ፣ኬፕ ቨርዴ፣ ሲሸልስ እና ቡሩንዲ ከድርጅቱ አነስተኛ የብድር መጠን ያለባቸው የአፍሪካ ሀገራት ናቸው ተብሏል።
አነስተኛ የብድር እዳ ካለባቸው ሀገራት መሀከል አብዛኞቹ ደሴትና አነስተኛ የህዝብ ቁጥር ያላቸው ሀገራት ናቸው።
የIMF እዳ አነስተኛ መሆኑ ሀገራቱ የራሳቸውን የኢኮኖሚ ፖሊሲ በነጻነት ለመቅረጽና ከውጭ ጫና ለመጠበቅ ትልቅ እድል እንደሚፈጥርላቸው ነው የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች የሚናገሩት።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #imf #debt #economi
#ethiopia | በዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) በኩል የሚሰጡ የብድር አቅርቦት እና የፋይናንስ ድጋፍ ለብዙ አፍሪካ ሀገራት ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት ነው።
2026 ከተቋሙ አነስተኛ የብድር እዳ ያለባቸው የአፍሪካ ሀገራት ዝርዝር ይፋ ሆኗል።
እንደ አለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ወቅታዊ መረጃ አነስተኛ የብድር እዳ ካለባቸው ሀገራት መካከል በመጀመሪያው ተሰልፈው የሚገኙት በድርጅቱ አሰራርና አጠራር መሠረት የዜሮ እዳ ባለቤት የሆኑት ሀገራት ናቸው።
በዚህም ቦትስዋና፣ ሊቢያ፣ ኤርትራ፣ አልጄሪያ፣ ናይጄሪያ እና ሞሪሸስ ከIMF ጋር አሁናዊ የብድር እዳ የሌለባቸው ሀገራት በመሆን የዝርዝሩን አናት ይዘዋል።
በሌላ በኩል ከተቋሙ ጋር ንቁ የብድር ፕሮግራም እያካሄዱ ነገር ግን በዝቅተኛ የብድር መጠን ዝርዝር ውስጥ የተካተቱት 10 የአፍሪካ ሀገራትም አሉ።
ሌሶቶ፣ ኤስዋቲኒ፣ ጂቡቲ፣ ኮምሮስ፣
ሳኦ ቶሜ ፕሬንስፔ፣ኢኳቶሪያል ጊኒ፣ጊኒ ቢሳዎ፣ኬፕ ቨርዴ፣ ሲሸልስ እና ቡሩንዲ ከድርጅቱ አነስተኛ የብድር መጠን ያለባቸው የአፍሪካ ሀገራት ናቸው ተብሏል።
አነስተኛ የብድር እዳ ካለባቸው ሀገራት መሀከል አብዛኞቹ ደሴትና አነስተኛ የህዝብ ቁጥር ያላቸው ሀገራት ናቸው።
የIMF እዳ አነስተኛ መሆኑ ሀገራቱ የራሳቸውን የኢኮኖሚ ፖሊሲ በነጻነት ለመቅረጽና ከውጭ ጫና ለመጠበቅ ትልቅ እድል እንደሚፈጥርላቸው ነው የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች የሚናገሩት።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #imf #debt #economi
15 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የታወቁት የኢኮኖሚ ተንታኝ አቶ ክቡር ገና "Who Should Own Ethiopia’s Gold? The IMF’s Dangerous Advice" (የኢትዮጵያ ወርቅ የማን መሆን አለበት? የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት አደገኛ ምክር) በሚል ባወጡት አዲስ የሞጋች ሀሳብ ጽሑፍ፣ የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከወርቅ ገበያ አሠራር በሂደት እንዲወጣ የሰጠውን ምክር በጥብቅ ተቃወሙ። ተንታኙ የብሔራዊ ባንክ ከወርቅ ገበያ መውጣት አገራዊ የኢኮኖሚ ልዑላኔንና የውጭ ምንዛሬ ማከማቸት አቅምን አደጋ ላይ የሚጥል አደገኛ አካሄድ እንደሆነ ገልጸዋል።
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በቅርቡ ባወጣው የብድር ክለሳ ሪፖርቱ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የወርቅ ገበያ አሠራሩን ማሻሻልና በሂደት ከወርቅ ገበያ ገዢነት በሙሉ በመውጣት ቦታውን ለግል ንግድ ባንኮች መልቀቅ እንዳለበት አሳስቧል። አይ ኤም ኤፍ ይህን ያለው ማዕከላዊ ባንኮች መደበኛ የሸቀጥ ነጋዴ መሆን የለባቸውም በሚል የኢኮኖሚ ንድፈ-ሐሳብ መሠረት ቢሆንም፣ አቶ ክቡር ገና እንደሚሞግቱት ግን ይህ ምክር የበለጸጉና የዳበረ የፋይናንስ ሥርዓት ያላቸውን እንደ ስዊዘርላንድና ካናዳ ያሉ አገራትን ታሳቢ ያደረገ እንጂ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ውስጥ ለምትገኘው ኢትዮጵያ ፈጽሞ የማይሰራና አደገኛ ነው። ወርቅ ለኢትዮጵያ ተራ የንግድ ሸቀጥ ሳይሆን የአገሪቱን የውጭ ምንዛሬ የመጠባበቂያ ክምችት የሚያጠናክር፣ አስፈላጊ የነዳጅና የመድኃኒት ግዢዎችን የሚሸፍን እና የአገሪቱን የፋይናንስ ሕልውና የሚያስጠብቅ ስልታዊ አገራዊ ሀብት ነው።
አይ ኤም ኤፍ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክን በግል ንግድ ባንኮች ለመተካት የሚያቀርበው መሬት የማይነካ መላምት የግል ባንኮችን እና የብሔራዊ ባንክን መሠረታዊ ዓላማ ያላገናዘበ መሆኑንም ተንታኙ ያብራራሉ። የግል ንግድ ባንኮች የሚሰሩት ለባለአክሲዮኖቻቸው ትርፍ ለማብዛት ሲሆን፣ ቅድሚያ የሚሰጡትም ለወለድና ለአገልግሎት ክፍያ እንጂ ለአገራዊ የኢኮኖሚ ልማት አይደለም። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የተቋቋመው የአገሪቱን ገንዘብ ዋጋ ለማስጠበቅ፣ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ለማሳደግ እና የአገሪቱን የረጅም ጊዜ የልማት ፍላጎቶች ለማረጋገጥ በመሆኑ፣ የአገሪቱን ዋና የውጭ ምንዛሬ ምንጭ ለግል ባንኮች አሳልፎ መስጠት አገራዊ የኢኮኖሚ ጥቅምንም አሳልፎ መስጠት ነው።
በተጨማሪም አይ ኤም ኤፍ ብሔራዊ ባንክ ከዓለም አቀፍ የወርቅ ዋጋ በላይ ጨምሮ ከአገር ውስጥ አምራቾች ወርቅ መግዛቱን እንደ ገበያ ማዛባት ቢነቅፈውም፣ አቶ ክቡር ገና ግን ይህ አሠራር ተግባራዊና አስፈላጊ መሆኑን ይሞግታሉ። ብሔራዊ ባንክ እየተወዳደረ ያለው ድበር ተሻጋሪ ከሆኑ የኮንትሮባንድ መረቦች ጋር በመሆኑ፣ ተጨማሪ ዋጋ ከፍሎ ወርቁን ወደ መደበኛው የሕግ አሠራር ማስገባት ካልቻለ አገሪቱ ወርቁንም፣ የውጭ ምንዛሬውንም ሆነ የታክስ ገቢዋን ሙሉ በሙሉ ታጣለች።
አቶ ክቡር ገና በጽሑፋቸው ማጠቃለያ ላይ እንዳሰመሩበት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የወርቅ ግዢ አሠራሩን ግልጽ ማድረግና ማዘመን አለበት እንጂ ከገበያው መውጣት የለበትም። ኢትዮጵያ አሁንም የውጭ ምንዛሬ እጥረት ያለባት፣ የኢንዱስትሪ ሽግግሯ ያልተጠናቀቀ እና የኢኮኖሚ ልዑላኔዋ በግንባታ ላይ ያለች አገር በመሆኗ፣ በዚህ ሁኔታ ውስጥ አገሪቱ ያላትን ብቸኛ ስልታዊ የወርቅ ሀብት ቁጥጥር አሳልፋ እንድትሰጥ የቀረበው የምክር ሀሳብ ልማታዊ ሳይሆን ወደኋላ ማፈግፈግ እንደሆነ በመግለጽ ደምድመዋል።
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በቅርቡ ባወጣው የብድር ክለሳ ሪፖርቱ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የወርቅ ገበያ አሠራሩን ማሻሻልና በሂደት ከወርቅ ገበያ ገዢነት በሙሉ በመውጣት ቦታውን ለግል ንግድ ባንኮች መልቀቅ እንዳለበት አሳስቧል። አይ ኤም ኤፍ ይህን ያለው ማዕከላዊ ባንኮች መደበኛ የሸቀጥ ነጋዴ መሆን የለባቸውም በሚል የኢኮኖሚ ንድፈ-ሐሳብ መሠረት ቢሆንም፣ አቶ ክቡር ገና እንደሚሞግቱት ግን ይህ ምክር የበለጸጉና የዳበረ የፋይናንስ ሥርዓት ያላቸውን እንደ ስዊዘርላንድና ካናዳ ያሉ አገራትን ታሳቢ ያደረገ እንጂ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ውስጥ ለምትገኘው ኢትዮጵያ ፈጽሞ የማይሰራና አደገኛ ነው። ወርቅ ለኢትዮጵያ ተራ የንግድ ሸቀጥ ሳይሆን የአገሪቱን የውጭ ምንዛሬ የመጠባበቂያ ክምችት የሚያጠናክር፣ አስፈላጊ የነዳጅና የመድኃኒት ግዢዎችን የሚሸፍን እና የአገሪቱን የፋይናንስ ሕልውና የሚያስጠብቅ ስልታዊ አገራዊ ሀብት ነው።
አይ ኤም ኤፍ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክን በግል ንግድ ባንኮች ለመተካት የሚያቀርበው መሬት የማይነካ መላምት የግል ባንኮችን እና የብሔራዊ ባንክን መሠረታዊ ዓላማ ያላገናዘበ መሆኑንም ተንታኙ ያብራራሉ። የግል ንግድ ባንኮች የሚሰሩት ለባለአክሲዮኖቻቸው ትርፍ ለማብዛት ሲሆን፣ ቅድሚያ የሚሰጡትም ለወለድና ለአገልግሎት ክፍያ እንጂ ለአገራዊ የኢኮኖሚ ልማት አይደለም። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የተቋቋመው የአገሪቱን ገንዘብ ዋጋ ለማስጠበቅ፣ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ለማሳደግ እና የአገሪቱን የረጅም ጊዜ የልማት ፍላጎቶች ለማረጋገጥ በመሆኑ፣ የአገሪቱን ዋና የውጭ ምንዛሬ ምንጭ ለግል ባንኮች አሳልፎ መስጠት አገራዊ የኢኮኖሚ ጥቅምንም አሳልፎ መስጠት ነው።
በተጨማሪም አይ ኤም ኤፍ ብሔራዊ ባንክ ከዓለም አቀፍ የወርቅ ዋጋ በላይ ጨምሮ ከአገር ውስጥ አምራቾች ወርቅ መግዛቱን እንደ ገበያ ማዛባት ቢነቅፈውም፣ አቶ ክቡር ገና ግን ይህ አሠራር ተግባራዊና አስፈላጊ መሆኑን ይሞግታሉ። ብሔራዊ ባንክ እየተወዳደረ ያለው ድበር ተሻጋሪ ከሆኑ የኮንትሮባንድ መረቦች ጋር በመሆኑ፣ ተጨማሪ ዋጋ ከፍሎ ወርቁን ወደ መደበኛው የሕግ አሠራር ማስገባት ካልቻለ አገሪቱ ወርቁንም፣ የውጭ ምንዛሬውንም ሆነ የታክስ ገቢዋን ሙሉ በሙሉ ታጣለች።
አቶ ክቡር ገና በጽሑፋቸው ማጠቃለያ ላይ እንዳሰመሩበት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የወርቅ ግዢ አሠራሩን ግልጽ ማድረግና ማዘመን አለበት እንጂ ከገበያው መውጣት የለበትም። ኢትዮጵያ አሁንም የውጭ ምንዛሬ እጥረት ያለባት፣ የኢንዱስትሪ ሽግግሯ ያልተጠናቀቀ እና የኢኮኖሚ ልዑላኔዋ በግንባታ ላይ ያለች አገር በመሆኗ፣ በዚህ ሁኔታ ውስጥ አገሪቱ ያላትን ብቸኛ ስልታዊ የወርቅ ሀብት ቁጥጥር አሳልፋ እንድትሰጥ የቀረበው የምክር ሀሳብ ልማታዊ ሳይሆን ወደኋላ ማፈግፈግ እንደሆነ በመግለጽ ደምድመዋል።
20 days ago
''አዳዲስ ቀረጦች ሊጣሉ ነው‼️
በነዳጅ፣ በሪል እስቴት፣ በአልኮልና በትምባሆ እንዲሁም በኢንቨስትመንት ታክስ ነፃ መብቶች ላይ አዳዲስ ቀረጦች ሊጣሉ መሆኑ ተሰምቷል።
IMF እንደገለጸው የኢትዮጵያ መንግሥት 5 ቢሊዮን ዶላር አዲስ የውጭ ብድር ለማግኘት ሲል እነዚህን ሰፊ የታክስ ማሻሻያዎች ተግባራዊ ለማድረግ ወስኗል። ይህ የሆነው የብድሩ ቅድመ ሁኔታ የሀገሪቱን የውስጥ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ ስለሚጠይቅ እንደሆነም ተብራርቷል።
በዚህም መሠረት የነዳጅ ድጎማው ሙሉ በሙሉ ተነስቶ ዋጋው በገበያ እንዲወሰን የሚደረግ ሲሆን፣ በሪል እስቴት፣ በመኪና ባለቤትነት እና በተለያዩ ምርቶች ላይ አዳዲስ ቀረጦች የሚጣሉ ይሆናል ተብሏል።
• ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በአንድ ወቅት የዓለም አቀፉን የገንዘብ ድርጅት (IMF) ብድር ቀላልነት ሲገልጹ «ከአይ.ኤም.ኤፍ መበደር ከእናት መቀነት እንደ መፍታት ነው...» ማለታቸው ይታወሳል። ይሁን እንጂ ዛሬ ላይ የዚያ "ቀላል" ብድር ዋጋና ቅድመ-ሁኔታዎች በዜጎች ኪስ ላይ እየፈጠሩት ያለው ጫና ቀላል አለመሆኑን ብዙዎች እየተናገሩ ይገኛሉ።
በየጊዜው የሚጨመሩ ታክሶች፣ አዳዲስ ቀረጦች እና የዋጋ ንረቱ «ለመሆኑ ለብድር ተብሎ በሕዝብ ላይ ታክስ መጫን ተለመደ እንዴ?» የሚል ጥያቄ አስነስቷል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀገሪቱ እየተተገበሩ ያሉ የፖሊሲ ለውጦች (የኤክሳይዝ ታክስ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ማሻሻያዎች እና የተለያዩ የአገልግሎት ክፍያ ጭማሪዎች) ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ያለውን ማህበረሰብ ክፉኛ እየፈተኑት ይገኛሉ።
ከውጭ ምንዛሬ ተመን መለቀቅ ጋር ተዳምሮ የሸቀጦች ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል።
Seledadotio
Seledadotio
በነዳጅ፣ በሪል እስቴት፣ በአልኮልና በትምባሆ እንዲሁም በኢንቨስትመንት ታክስ ነፃ መብቶች ላይ አዳዲስ ቀረጦች ሊጣሉ መሆኑ ተሰምቷል።
IMF እንደገለጸው የኢትዮጵያ መንግሥት 5 ቢሊዮን ዶላር አዲስ የውጭ ብድር ለማግኘት ሲል እነዚህን ሰፊ የታክስ ማሻሻያዎች ተግባራዊ ለማድረግ ወስኗል። ይህ የሆነው የብድሩ ቅድመ ሁኔታ የሀገሪቱን የውስጥ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ ስለሚጠይቅ እንደሆነም ተብራርቷል።
በዚህም መሠረት የነዳጅ ድጎማው ሙሉ በሙሉ ተነስቶ ዋጋው በገበያ እንዲወሰን የሚደረግ ሲሆን፣ በሪል እስቴት፣ በመኪና ባለቤትነት እና በተለያዩ ምርቶች ላይ አዳዲስ ቀረጦች የሚጣሉ ይሆናል ተብሏል።
• ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በአንድ ወቅት የዓለም አቀፉን የገንዘብ ድርጅት (IMF) ብድር ቀላልነት ሲገልጹ «ከአይ.ኤም.ኤፍ መበደር ከእናት መቀነት እንደ መፍታት ነው...» ማለታቸው ይታወሳል። ይሁን እንጂ ዛሬ ላይ የዚያ "ቀላል" ብድር ዋጋና ቅድመ-ሁኔታዎች በዜጎች ኪስ ላይ እየፈጠሩት ያለው ጫና ቀላል አለመሆኑን ብዙዎች እየተናገሩ ይገኛሉ።
በየጊዜው የሚጨመሩ ታክሶች፣ አዳዲስ ቀረጦች እና የዋጋ ንረቱ «ለመሆኑ ለብድር ተብሎ በሕዝብ ላይ ታክስ መጫን ተለመደ እንዴ?» የሚል ጥያቄ አስነስቷል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀገሪቱ እየተተገበሩ ያሉ የፖሊሲ ለውጦች (የኤክሳይዝ ታክስ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ማሻሻያዎች እና የተለያዩ የአገልግሎት ክፍያ ጭማሪዎች) ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ያለውን ማህበረሰብ ክፉኛ እየፈተኑት ይገኛሉ።
ከውጭ ምንዛሬ ተመን መለቀቅ ጋር ተዳምሮ የሸቀጦች ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል።
Seledadotio
Seledadotio
21 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ዛሬ በዋና ዋና የአሜሪካ እና የዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ (ዩኤኢ) ከተሞች በሚገኙ መደበኛ ያልሆኑ የምንዛሬ ገበያዎች፣ የአንድ አሜሪካን ዶላር የመግዣ ዋጋ 181.60 የኢትዮጵያ ብር መድረሱ ታውቋል። ይህ ከፍተኛ የምንዛሬ ፍላጎት እና የጥቁር ገበያ ንረት፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ከሚከተለው የጉምሩክ እና የታክስ ፖሊሲ ጋር ቀጥተኛ ትስስር እንዳለው ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) በቅርቡ ባወጣው ሂሳዊ ሪፖርት አጋልጧል።
አይ.ኤም.ኤፍ (IMF) ይፋ ባደረገው 5ኛው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ ማሻሻያ የግምገማ ሪፖርት ላይ እንዳስገነዘበው፣ በመንግሥት በኩል የተጣሉት "የተጋነኑ" እና "የዘፈቀደ" የጉምሩክ ቀረጥ ተመኖች ሀገሪቱን ለከፍተኛ የኮንትሮባንድ ንግድ እያጋለጧት ይገኛሉ። ሪፖርቱ በግልጽ እንዳስቀመጠው፣ እነዚህ ምክንያታዊ ያልሆኑ የታክስ ጫናዎች ነጋዴዎች የውጭ ምንዛሬን በህገ-ወጥ መንገድ (በጥቁር ገበያ) እንዲፈልጉ ዋነኛ ገፊ ምክንያት ሆነዋል።
ለዚህ የኢኮኖሚ መዛባት እና የጥቁር ገበያ መስፋፋት በዋነኝነት አስተዋጽኦ ያደረጉት የመንግሥት የታክስ እርምጃዎች የሚከተሉት ናቸው:-
▪️ እስከ 35 በመቶ የሚደርሰው ከፍተኛ የጉምሩክ ቀረጥ
▪️የ 10 በመቶ ተጨማሪ ቀረጥ ወይም ሱር ታክስ
▪️ ከ 5 በመቶ እስከ 500 በመቶ የሚደርሰው እጅግ የተጋነነ የኤክሳይዝ ታክስ ምጣኔ
እነዚህ የተደራረቡ የታክስ ጫናዎች ሕጋዊውን የንግድ ሥርዓት በማዳከም፣ ነጋዴው ማትረፍ ወደሚችልበት የኮንትሮባንድ አማራጭ እንዲያዘነብል ማስገደዳቸውን ተቋሙ በሪፖርቱ አብራርቷል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ መንግሥት ይህንን አሳሳቢ ችግር ለመቅረፍ በማሰብ አዳዲስ የታክስ ፖሊሲ ማሻሻያዎችን ማጽደቁን ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) በሪፖርቱ አወድሷል። በተጨማሪም በቀጣዮቹ ጊዜያት መንግሥት አዲስ የታክስ ፖሊሲ ተግባራዊ ለማድረግ ማቀዱን ሪፖርቱ ጠቁሟል። በዚህም መሠረት፣ መንግሥት በነዳጅ ተሽከርካሪዎች ላይ አዲስ ታክስ የሚጥል ሲሆን፣ የዚህ እርምጃ ዋና ዓላማዎች የመንግሥትን የገቢ አሰባሰብ አቅም ከፍ ማድረግ እንዲሁም ከነዳጅ ነጻ የሆኑ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን አጠቃቀም በሀገር ውስጥ በስፋት ማበረታታት መሆኑ ተገልጿል።
እነዚህ አዳዲስ የፖሊሲ ማሻሻያዎች የጥቁር ገበያውን የምንዛሬ ጫና እና የኮንትሮባንድ ንግድን ምን ያህል ሊገቱት ይችላሉ የሚለው በቀጣይ የመንግሥት የተግባር አፈጻጸም ላይ የሚመዘን ይሆናል።
አይ.ኤም.ኤፍ (IMF) ይፋ ባደረገው 5ኛው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ ማሻሻያ የግምገማ ሪፖርት ላይ እንዳስገነዘበው፣ በመንግሥት በኩል የተጣሉት "የተጋነኑ" እና "የዘፈቀደ" የጉምሩክ ቀረጥ ተመኖች ሀገሪቱን ለከፍተኛ የኮንትሮባንድ ንግድ እያጋለጧት ይገኛሉ። ሪፖርቱ በግልጽ እንዳስቀመጠው፣ እነዚህ ምክንያታዊ ያልሆኑ የታክስ ጫናዎች ነጋዴዎች የውጭ ምንዛሬን በህገ-ወጥ መንገድ (በጥቁር ገበያ) እንዲፈልጉ ዋነኛ ገፊ ምክንያት ሆነዋል።
ለዚህ የኢኮኖሚ መዛባት እና የጥቁር ገበያ መስፋፋት በዋነኝነት አስተዋጽኦ ያደረጉት የመንግሥት የታክስ እርምጃዎች የሚከተሉት ናቸው:-
▪️ እስከ 35 በመቶ የሚደርሰው ከፍተኛ የጉምሩክ ቀረጥ
▪️የ 10 በመቶ ተጨማሪ ቀረጥ ወይም ሱር ታክስ
▪️ ከ 5 በመቶ እስከ 500 በመቶ የሚደርሰው እጅግ የተጋነነ የኤክሳይዝ ታክስ ምጣኔ
እነዚህ የተደራረቡ የታክስ ጫናዎች ሕጋዊውን የንግድ ሥርዓት በማዳከም፣ ነጋዴው ማትረፍ ወደሚችልበት የኮንትሮባንድ አማራጭ እንዲያዘነብል ማስገደዳቸውን ተቋሙ በሪፖርቱ አብራርቷል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ መንግሥት ይህንን አሳሳቢ ችግር ለመቅረፍ በማሰብ አዳዲስ የታክስ ፖሊሲ ማሻሻያዎችን ማጽደቁን ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) በሪፖርቱ አወድሷል። በተጨማሪም በቀጣዮቹ ጊዜያት መንግሥት አዲስ የታክስ ፖሊሲ ተግባራዊ ለማድረግ ማቀዱን ሪፖርቱ ጠቁሟል። በዚህም መሠረት፣ መንግሥት በነዳጅ ተሽከርካሪዎች ላይ አዲስ ታክስ የሚጥል ሲሆን፣ የዚህ እርምጃ ዋና ዓላማዎች የመንግሥትን የገቢ አሰባሰብ አቅም ከፍ ማድረግ እንዲሁም ከነዳጅ ነጻ የሆኑ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን አጠቃቀም በሀገር ውስጥ በስፋት ማበረታታት መሆኑ ተገልጿል።
እነዚህ አዳዲስ የፖሊሲ ማሻሻያዎች የጥቁር ገበያውን የምንዛሬ ጫና እና የኮንትሮባንድ ንግድን ምን ያህል ሊገቱት ይችላሉ የሚለው በቀጣይ የመንግሥት የተግባር አፈጻጸም ላይ የሚመዘን ይሆናል።
23 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለወርቅ አቅራቢዎች ከዓለም አቀፍ የገበያ ዋጋ በላይ ይከፍል የነበረውን ከ5 እስከ 15 በመቶ የሚደርስ የማበረታቻ ክፍያ እ.ኤ.አ እስከ መጪው ሴፕቴምበር 2026 መጨረሻ ድረስ እንደሚያቆም የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) በዚህ ሳምንት ባወጣው ሰነድ አስታውቋል። ተቋሙ እንዳስገነዘበው፣ ብሔራዊ ባንኩ ዳግም ካፒታል የመገንባት እቅዱ ጎን ለጎን በወርቅ ገበያ ውስጥ የሚያደርገውን ቀጥተኛ ተሳትፎ የሚያስቀር የረጅም ጊዜ ስትራቴጂ እስከ ዲሴምበር 2026 መጨረሻ ድረስ ተግባራዊ ይደረጋል። እስከዚያው ድረስ ግን ማዕከላዊ ባንኩ የወርቅ ጥራትን የማረጋገጥ አቅሙን እና የውስጥ አሰራር ሂደቱን ለማሻሻል እየሰራ ይገኛል።
የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ሰነድ፣ የህገ-ወጥ የወርቅ ንግድ ለትይዩ (ጥቁር) የውጭ ምንዛሬ ገበያ መስፋፋት የራሱን አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን አብራርቷል። በተለይም የወርቅ ወጪ ንግድ ዋነኛ የውጭ ምንዛሬ ምንጭ በሆነበት ሁኔታ፣ ብሔራዊ ባንኩ የሚከፍለው የማበረታቻ ክፍያ ትይዩውን የውጭ ምንዛሬ ተመን ለመወሰን አስተዋፅዖ እያደረገ መሆኑ ህጋዊውን እና ትይዩውን ተመን ለማቀራረብ በሚደረገው ጥረት ላይ ማነቆ ሆኗል። ለዚህ የውጭ ምንዛሬ የገበያ ልዩነት መስፋፋት ሌሎች ምክንያቶች ተብለው ከተዘረዘሩት ውስጥ በባንኮች በኩል ያለው ከፍተኛ የግብይት ወጪ፣ ብሔራዊ ባንኩ የሚያስከፍለው የውጭ ምንዛሬ ኮሚሽን (በዚህ ሳምንት ወደ 1.5 በመቶ ዝቅ ብሏል)፣ እና የባንኮች የውጭ ምንዛሬ አመዳደብ አሰራር ላይ የሚስተዋሉ የጋራ ስምምነቶች ተጠቃሽ ናቸው። በተጨማሪም ከውጭ በሚገቡ እቃዎች ላይ የተጣለው ከፍተኛ የጉምሩክ ቀረጥ እና ታክስ ህገ-ወጥ የኮንትሮባንድ ንግድን በማበረታታት፣ ነጋዴዎች የውጭ ምንዛሬን ከጥቁር ገበያ እንዲፈልጉ እያስገደዳቸው መሆኑ በሰነዱ ተብራርቷል።
በሌላ በኩል በ2026/27 የበጀት ዓመት የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ አፈጻጸም ጠንካራ ሆኖ እንደሚቀጥል የአይኤምኤፍ ባለሙያዎች ተንብየዋል። ከኖቬምበር 2025 ጀምሮ የቡና ዋጋ በዓለም አቀፍ ገበያ የ35 በመቶ ቅናሽ ቢያሳይም፣ ኢትዮጵያ ከዘርፉ የምታገኘው ገቢ ወደ ሶስት ቢሊዮን ዶላር ይጠጋል ተብሎ ይጠበቃል። የወጪ ንግዱ መሻሻል እና የዓለም አቀፍ የወርቅ ዋጋ መጨመር የሸቀጦች የንግድ ሚዛን ጉድለትን በዓመቱ መጨረሻ ወደ 12.6 ቢሊዮን ዶላር በትንሹ ጠበብ እንዲል ያደርገዋል ተብሏል።
ይሁን እንጂ በአሜሪካ እና ኢራን ግጭት ሳቢያ እየጨመረ የመጣው የነዳጅ ዋጋ፣ እንዲሁም የቡና እና የወርቅ ዋጋ በዓለም አቀፍ ገበያ ሊያሳይ የሚችለው የዋጋ ማሽቆልቆል በሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ላይ ጫና ሊፈጥር እንደሚችል ተቋሙ አስጠንቅቋል። በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ ክምችት የ2.1 ወራት የገቢ ንግድን ብቻ የሚሸፍን ሲሆን፣ በ2028 በሚጠናቀቀው የአይኤምኤፍ ፕሮግራም ይህንን ክምችት ወደ 3.5 ወራት ለማሳደግ የታቀደው ግብ ፈታኝ ሊሆን እንደሚችል ተጠቁሟል።
የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ሰነድ፣ የህገ-ወጥ የወርቅ ንግድ ለትይዩ (ጥቁር) የውጭ ምንዛሬ ገበያ መስፋፋት የራሱን አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን አብራርቷል። በተለይም የወርቅ ወጪ ንግድ ዋነኛ የውጭ ምንዛሬ ምንጭ በሆነበት ሁኔታ፣ ብሔራዊ ባንኩ የሚከፍለው የማበረታቻ ክፍያ ትይዩውን የውጭ ምንዛሬ ተመን ለመወሰን አስተዋፅዖ እያደረገ መሆኑ ህጋዊውን እና ትይዩውን ተመን ለማቀራረብ በሚደረገው ጥረት ላይ ማነቆ ሆኗል። ለዚህ የውጭ ምንዛሬ የገበያ ልዩነት መስፋፋት ሌሎች ምክንያቶች ተብለው ከተዘረዘሩት ውስጥ በባንኮች በኩል ያለው ከፍተኛ የግብይት ወጪ፣ ብሔራዊ ባንኩ የሚያስከፍለው የውጭ ምንዛሬ ኮሚሽን (በዚህ ሳምንት ወደ 1.5 በመቶ ዝቅ ብሏል)፣ እና የባንኮች የውጭ ምንዛሬ አመዳደብ አሰራር ላይ የሚስተዋሉ የጋራ ስምምነቶች ተጠቃሽ ናቸው። በተጨማሪም ከውጭ በሚገቡ እቃዎች ላይ የተጣለው ከፍተኛ የጉምሩክ ቀረጥ እና ታክስ ህገ-ወጥ የኮንትሮባንድ ንግድን በማበረታታት፣ ነጋዴዎች የውጭ ምንዛሬን ከጥቁር ገበያ እንዲፈልጉ እያስገደዳቸው መሆኑ በሰነዱ ተብራርቷል።
በሌላ በኩል በ2026/27 የበጀት ዓመት የኢትዮጵያ የወጪ ንግድ አፈጻጸም ጠንካራ ሆኖ እንደሚቀጥል የአይኤምኤፍ ባለሙያዎች ተንብየዋል። ከኖቬምበር 2025 ጀምሮ የቡና ዋጋ በዓለም አቀፍ ገበያ የ35 በመቶ ቅናሽ ቢያሳይም፣ ኢትዮጵያ ከዘርፉ የምታገኘው ገቢ ወደ ሶስት ቢሊዮን ዶላር ይጠጋል ተብሎ ይጠበቃል። የወጪ ንግዱ መሻሻል እና የዓለም አቀፍ የወርቅ ዋጋ መጨመር የሸቀጦች የንግድ ሚዛን ጉድለትን በዓመቱ መጨረሻ ወደ 12.6 ቢሊዮን ዶላር በትንሹ ጠበብ እንዲል ያደርገዋል ተብሏል።
ይሁን እንጂ በአሜሪካ እና ኢራን ግጭት ሳቢያ እየጨመረ የመጣው የነዳጅ ዋጋ፣ እንዲሁም የቡና እና የወርቅ ዋጋ በዓለም አቀፍ ገበያ ሊያሳይ የሚችለው የዋጋ ማሽቆልቆል በሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ላይ ጫና ሊፈጥር እንደሚችል ተቋሙ አስጠንቅቋል። በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ ክምችት የ2.1 ወራት የገቢ ንግድን ብቻ የሚሸፍን ሲሆን፣ በ2028 በሚጠናቀቀው የአይኤምኤፍ ፕሮግራም ይህንን ክምችት ወደ 3.5 ወራት ለማሳደግ የታቀደው ግብ ፈታኝ ሊሆን እንደሚችል ተጠቁሟል።
Sponsored by
Surafel
24 days ago
የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሪ ክምችት ከሪፎርሙ በፊት ከነበረው በ20 እጥፍ አድጓል
**********************
የውጭ ምንዛሪ መጠባበቂያ ክምችት በ2018 በጀት ዓመት ከፍተኛ ጭማሪ በማሳየት መጠኑ ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በፊት ከነበረው በ20 እጥፍ ማደጉን የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ አስታውቋል።
ኮሚቴው ከ7ኛ ስብሰባው በኋላ በሰጠው መግለጫ እንዳብራራው፥ በሐምሌ ወር 2016 ተግባራዊ ከተደረገው ሁሉን አቀፍ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ማግስት ሀገራችን በአጠቃላይ የውጭ ኢኮኖሚ ሚዛን ትርፍ ማስመዝገብ ችላለች።
ይህም ከሪፎርሙ በፊት ከነበረው ጉድለት አንፃር ሲታይ ዘርፉ ከፍተኛ መሻሻል ላይ መሆኑን ያመላክታል።
አጠቃላይ የማሻሻያ እርምጃዎቹ የውጭ ገበያ ተወዳዳሪነትን እና የውጭ ምንዛሪ ገቢን በማሳደግ የውጭ ኢኮኖሚ ዘርፉን ዘላቂነት እያረጋገጡ መሆኑ ተገልጿል።
በበጀት ዓመቱ የተመዘገበው የሸቀጦች ወጪ ንግድ ገቢ በሶስት እጥፍ ማደግ፣ እንዲሁም በግለሰቦች እና በመንግሥት የሃዋላ ፍሰት ላይ የታየው አበረታች መሻሻል የሸቀጦች ገቢ ንግድ መጨመርን በከፊል እንዲያካክስ ረድቶታል።
በዚህም የተነሳ በ2016 በጀት ዓመት 6.2 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ደርሶ የነበረው የሂሳብ ሚዛን ጉድለት በ2018 በጀት ዓመት ወደ 1.8 ቢሊዮን ዶላር በከፍተኛ ሁኔታ ሊቀንስ መቻሉ በመግለጫው ተጠቁሟል።
በተጨማሪም በበጀት ዓመቱ የተመዘገበው የካፒታል ሂሳብ ትርፍ ለአጠቃላይ የክፍያ ሚዛኑ መሻሻል የጎላ አስተዋፅዖ ማበርከቱ ተገልጿል።
ኮሚቴው የዓለም አቀፉን የገንዘብ ድርጅት (IMF) የሐምሌ 2018 ትንበያ ዋቢ በማድረግ እንደገመገመው፣ በመካከለኛው ምሥራቅ የተከሰተው ግጭት ቀደም ሲል ሲጠበቅ የነበረው የተረጋጋ የዓለም ኢኮኖሚ አቅጣጫ እንዲዛባ አድርጓል።
በመሆኑም ዓለም አቀፍ ዕድገት በ2026 ወደ 3.0 በመቶ እንደሚቀንስ እና በ2027 ደግሞ መጠነኛ መሻሻል በማሳየት 3.4 በመቶ እንደሚሆን ተተንብዮአል።
በተመሳሳይ፣ አጠቃላይ የዓለም የዋጋ ግሽበት በ2026 ወደ 4.7 በመቶ ጭማሪ ካሳየ በኋላ በ2027 ወደ 3.9 በመቶ ይቀንሳል ተብሎ የሚጠበቅ ቢሆንም፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የአለመረጋጋት ስጋቶች አሁንም ድረስ መቀጠላቸውን ኮሚቴው አስገንዝቧል።
#ethiopia #ebc #nationalbankofethiopia #foreignexchange #economicreform #macroeconomics #exportgrowth #imf #globaleconomy
**********************
የውጭ ምንዛሪ መጠባበቂያ ክምችት በ2018 በጀት ዓመት ከፍተኛ ጭማሪ በማሳየት መጠኑ ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በፊት ከነበረው በ20 እጥፍ ማደጉን የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ አስታውቋል።
ኮሚቴው ከ7ኛ ስብሰባው በኋላ በሰጠው መግለጫ እንዳብራራው፥ በሐምሌ ወር 2016 ተግባራዊ ከተደረገው ሁሉን አቀፍ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ማግስት ሀገራችን በአጠቃላይ የውጭ ኢኮኖሚ ሚዛን ትርፍ ማስመዝገብ ችላለች።
ይህም ከሪፎርሙ በፊት ከነበረው ጉድለት አንፃር ሲታይ ዘርፉ ከፍተኛ መሻሻል ላይ መሆኑን ያመላክታል።
አጠቃላይ የማሻሻያ እርምጃዎቹ የውጭ ገበያ ተወዳዳሪነትን እና የውጭ ምንዛሪ ገቢን በማሳደግ የውጭ ኢኮኖሚ ዘርፉን ዘላቂነት እያረጋገጡ መሆኑ ተገልጿል።
በበጀት ዓመቱ የተመዘገበው የሸቀጦች ወጪ ንግድ ገቢ በሶስት እጥፍ ማደግ፣ እንዲሁም በግለሰቦች እና በመንግሥት የሃዋላ ፍሰት ላይ የታየው አበረታች መሻሻል የሸቀጦች ገቢ ንግድ መጨመርን በከፊል እንዲያካክስ ረድቶታል።
በዚህም የተነሳ በ2016 በጀት ዓመት 6.2 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ደርሶ የነበረው የሂሳብ ሚዛን ጉድለት በ2018 በጀት ዓመት ወደ 1.8 ቢሊዮን ዶላር በከፍተኛ ሁኔታ ሊቀንስ መቻሉ በመግለጫው ተጠቁሟል።
በተጨማሪም በበጀት ዓመቱ የተመዘገበው የካፒታል ሂሳብ ትርፍ ለአጠቃላይ የክፍያ ሚዛኑ መሻሻል የጎላ አስተዋፅዖ ማበርከቱ ተገልጿል።
ኮሚቴው የዓለም አቀፉን የገንዘብ ድርጅት (IMF) የሐምሌ 2018 ትንበያ ዋቢ በማድረግ እንደገመገመው፣ በመካከለኛው ምሥራቅ የተከሰተው ግጭት ቀደም ሲል ሲጠበቅ የነበረው የተረጋጋ የዓለም ኢኮኖሚ አቅጣጫ እንዲዛባ አድርጓል።
በመሆኑም ዓለም አቀፍ ዕድገት በ2026 ወደ 3.0 በመቶ እንደሚቀንስ እና በ2027 ደግሞ መጠነኛ መሻሻል በማሳየት 3.4 በመቶ እንደሚሆን ተተንብዮአል።
በተመሳሳይ፣ አጠቃላይ የዓለም የዋጋ ግሽበት በ2026 ወደ 4.7 በመቶ ጭማሪ ካሳየ በኋላ በ2027 ወደ 3.9 በመቶ ይቀንሳል ተብሎ የሚጠበቅ ቢሆንም፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የአለመረጋጋት ስጋቶች አሁንም ድረስ መቀጠላቸውን ኮሚቴው አስገንዝቧል።
#ethiopia #ebc #nationalbankofethiopia #foreignexchange #economicreform #macroeconomics #exportgrowth #imf #globaleconomy
1 month ago
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በአምስተኛው የኢኮኖሚ ሪፎርም ግምገማ ማጠናቀቂያ ለኢትዮጵያ የ464 ሚሊዮን ዶላር ተጨማሪ የብድር ክፍያ ፈቀደ
ይህም አጠቃላይ የገንዘብ ድጋፉን 2.647 ቢሊዮን ዶላር አድርሶታል።
ድርጅቱ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም የተመዘገቡትን የወጪ ንግድ እና የታክስ ገቢ እድገቶች ያደነቀ ቢሆንም፣ በመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ምክንያት የነዳጅ ዋጋ መናር ያሳደረውን ጫና ለመቋቋም 200 ሚሊዮን ዶላር ቀድሞ እንዲለቀቅ ማድረጉን ገልጿል።
በተጨማሪም IMF ሁለተኛ ዙር የዋጋ ንረት ከተከሰተ ብሔራዊ ባንክ ፖሊሲውን ይበልጥ ሊያጠብቅ እንደሚገባ አሳስቧል።
ባንኩ በወርቅ ግብይት ላይ ያለውን ቀጥተኛ ተሳትፎ እንዲያቆም፣ ድጎማዎች ሲነሱ ተጋላጭ ወገኖች እንዲጠበቁ፣ እና አዳዲስ ገለልተኛ የቦርድ አባላትን በመሾም የባንኩን ገለልተኝነት እንዲያጠናክር መክሯል።
Seledadotio
Seledadotio
ይህም አጠቃላይ የገንዘብ ድጋፉን 2.647 ቢሊዮን ዶላር አድርሶታል።
ድርጅቱ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም የተመዘገቡትን የወጪ ንግድ እና የታክስ ገቢ እድገቶች ያደነቀ ቢሆንም፣ በመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ምክንያት የነዳጅ ዋጋ መናር ያሳደረውን ጫና ለመቋቋም 200 ሚሊዮን ዶላር ቀድሞ እንዲለቀቅ ማድረጉን ገልጿል።
በተጨማሪም IMF ሁለተኛ ዙር የዋጋ ንረት ከተከሰተ ብሔራዊ ባንክ ፖሊሲውን ይበልጥ ሊያጠብቅ እንደሚገባ አሳስቧል።
ባንኩ በወርቅ ግብይት ላይ ያለውን ቀጥተኛ ተሳትፎ እንዲያቆም፣ ድጎማዎች ሲነሱ ተጋላጭ ወገኖች እንዲጠበቁ፣ እና አዳዲስ ገለልተኛ የቦርድ አባላትን በመሾም የባንኩን ገለልተኝነት እንዲያጠናክር መክሯል።
Seledadotio
Seledadotio
1 month ago
አዋሽ ባንክ ከታክስ በፊት 40.7 ቢሊዮን ብር ያልተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ።
#fastmereja I አዋሽ ባንክ እ.ኤ.አ. ጁን 30 ቀን 2026 በተጠናቀቀው የሒሳብ ዓመት በታሪኩ ከፍተኛ የተባለውን እመርታ በማስመዝገብ፣ ጠቅላላ የተቀማጭ ገንዘብ መጠኑን ብር 467.8 ቢሊዮን ማድረሱን የባንኩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀሐይ ሽፈራው በዛሬው ዕለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቁ።
ይህ አፈጻጸም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የብር 135 ቢሊዮን (41 በመቶ) ጭማሪ ያሳየ ሲሆን፣ በባንኩም ሆነ በሀገሪቱ የግል ባንኮች ታሪክ በአንድ ዓመት ውስጥ የተመዘገበ እጅግ ከፍተኛው የተቀማጭ ገንዘብ ዕድገት መሆኑ ተነግሯል።
የውጭ ምንዛሬ ግኝትን በተመለከተ፣ መንግሥት ካደረገው የውጭ ምንዛሬ ማሻሻያ ፖሊሲና ባንኩ ከተከተላቸው አሠራሮች በመነሳት ከፍተኛ ዕድገት የታየ ሲሆን፣ የ635 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ጭማሪ በማሳየት በሰኔ 2026 መጨረሻ ላይ ጠቅላላ የውጭ ምንዛሬ ግኝቱ 2.65 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ደርሷል። በተመሳሳይ የባንኩ ጠቅላላ ሀብት ብር 622 ቢሊዮን የደረሰ ሲሆን፣ የተከፈለ ካፒታሉ ደግሞ በ38 በመቶ (የብር 10.6 ቢሊዮን) ዕድገት በማሳየት 38.5 ቢሊዮን ብር ደርሷል።
ይህ የካፒታል መጠን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለግል ባንኮች ካስቀመጠው ዝቅተኛው ባለ 5 ቢሊዮን ብር መመዘኛ ጋር ሲነጻጸር ከሰባት እጥፍ በላይ ከፍ ያለ በመሆኑ ባንኩ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ስጋቶችን የመቋቋም አቅሙ በከፍተኛ ደረጃ ማደጉን ያሳያል ተብሏል።
በበጀት ዓመቱ አዋሽ ባንክ ከብር 85.37 ቢሊዮን በላይ ጠቅላላ ገቢ የሰበሰበ ሲሆን፣ ጠቅላላ ወጪው ብር 44.62 ቢሊዮን ሆኖ ተመዝግቧል። በዚህም መሠረት ከቀረጥና ከቅናሽ በፊት ያለው ጠቅላላ ትርፍ (Gross Profit before Provision and Tax) ብር 40.7 ቢሊዮን የደረሰ ሲሆን፣ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የብር 11.8 ቢሊዮን ብልጫ አለው።
ባንኩ በአሁኑ ወቅት ከ17 ሚሊዮን በላይ ደንበኞችን ማፍራት የቻለ ሲሆን፣ ይህንን ስኬት ያገኘው በሀገሪቱ ባሉት 1,010 መደበኛ ቅርንጫፎች፣ ከ10 በላይ የዲጂታል ቅርንጫፎች (e-branches)፣ ከ1,270 በላይ ኤቲኤሞች፣ ከ18,000 በላይ የባንክ ወኪሎች እንዲሁም እንደ Awash Birr Pro እና Online Banking ባሉ የኦንላይን ቴክኖሎጂዎቹ አማካኝነት ነው።
አዋሽ ባንክ ባሳየው ተከታታይና እመርታ የተሞላበት የሥራ አፈጻጸም ምክንያት በGlobal Finance ለ5 ተከታታይ ዓመታት "የኢትዮጵያ ምርጥ ባንክ" ተብሎ የተመረጠ ሲሆን፣ የሽልማት ሥነ-ሥርዓቱም በሚቀጥለው ዓመት በሚካሄደው የዓለም ባንክና ዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ስብሰባ ወቅት እንደሚፈጸም ታውቋል።
ባንኩ ከንግድ ሥራው ጎን ለጎን ማኅበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በተለያዩ ማኅበራዊና አካባቢያዊ ችግሮች ለተጠቁ የሕብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ የሚውል የብር 500 ሚሊዮን ወጪ ማድረጉም በመግለጫው ተጠቅሷል።
#ቢዝነስ
#fastmereja I አዋሽ ባንክ እ.ኤ.አ. ጁን 30 ቀን 2026 በተጠናቀቀው የሒሳብ ዓመት በታሪኩ ከፍተኛ የተባለውን እመርታ በማስመዝገብ፣ ጠቅላላ የተቀማጭ ገንዘብ መጠኑን ብር 467.8 ቢሊዮን ማድረሱን የባንኩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀሐይ ሽፈራው በዛሬው ዕለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቁ።
ይህ አፈጻጸም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የብር 135 ቢሊዮን (41 በመቶ) ጭማሪ ያሳየ ሲሆን፣ በባንኩም ሆነ በሀገሪቱ የግል ባንኮች ታሪክ በአንድ ዓመት ውስጥ የተመዘገበ እጅግ ከፍተኛው የተቀማጭ ገንዘብ ዕድገት መሆኑ ተነግሯል።
የውጭ ምንዛሬ ግኝትን በተመለከተ፣ መንግሥት ካደረገው የውጭ ምንዛሬ ማሻሻያ ፖሊሲና ባንኩ ከተከተላቸው አሠራሮች በመነሳት ከፍተኛ ዕድገት የታየ ሲሆን፣ የ635 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ጭማሪ በማሳየት በሰኔ 2026 መጨረሻ ላይ ጠቅላላ የውጭ ምንዛሬ ግኝቱ 2.65 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ደርሷል። በተመሳሳይ የባንኩ ጠቅላላ ሀብት ብር 622 ቢሊዮን የደረሰ ሲሆን፣ የተከፈለ ካፒታሉ ደግሞ በ38 በመቶ (የብር 10.6 ቢሊዮን) ዕድገት በማሳየት 38.5 ቢሊዮን ብር ደርሷል።
ይህ የካፒታል መጠን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለግል ባንኮች ካስቀመጠው ዝቅተኛው ባለ 5 ቢሊዮን ብር መመዘኛ ጋር ሲነጻጸር ከሰባት እጥፍ በላይ ከፍ ያለ በመሆኑ ባንኩ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ስጋቶችን የመቋቋም አቅሙ በከፍተኛ ደረጃ ማደጉን ያሳያል ተብሏል።
በበጀት ዓመቱ አዋሽ ባንክ ከብር 85.37 ቢሊዮን በላይ ጠቅላላ ገቢ የሰበሰበ ሲሆን፣ ጠቅላላ ወጪው ብር 44.62 ቢሊዮን ሆኖ ተመዝግቧል። በዚህም መሠረት ከቀረጥና ከቅናሽ በፊት ያለው ጠቅላላ ትርፍ (Gross Profit before Provision and Tax) ብር 40.7 ቢሊዮን የደረሰ ሲሆን፣ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የብር 11.8 ቢሊዮን ብልጫ አለው።
ባንኩ በአሁኑ ወቅት ከ17 ሚሊዮን በላይ ደንበኞችን ማፍራት የቻለ ሲሆን፣ ይህንን ስኬት ያገኘው በሀገሪቱ ባሉት 1,010 መደበኛ ቅርንጫፎች፣ ከ10 በላይ የዲጂታል ቅርንጫፎች (e-branches)፣ ከ1,270 በላይ ኤቲኤሞች፣ ከ18,000 በላይ የባንክ ወኪሎች እንዲሁም እንደ Awash Birr Pro እና Online Banking ባሉ የኦንላይን ቴክኖሎጂዎቹ አማካኝነት ነው።
አዋሽ ባንክ ባሳየው ተከታታይና እመርታ የተሞላበት የሥራ አፈጻጸም ምክንያት በGlobal Finance ለ5 ተከታታይ ዓመታት "የኢትዮጵያ ምርጥ ባንክ" ተብሎ የተመረጠ ሲሆን፣ የሽልማት ሥነ-ሥርዓቱም በሚቀጥለው ዓመት በሚካሄደው የዓለም ባንክና ዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ስብሰባ ወቅት እንደሚፈጸም ታውቋል።
ባንኩ ከንግድ ሥራው ጎን ለጎን ማኅበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በተለያዩ ማኅበራዊና አካባቢያዊ ችግሮች ለተጠቁ የሕብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ የሚውል የብር 500 ሚሊዮን ወጪ ማድረጉም በመግለጫው ተጠቅሷል።
#ቢዝነስ
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ትናንት የኢትዮጵያ መንግስት ክስ ሊመሰርቱበት ከተዘጋጁት የ1 ቢሊዮን ዶላር የዩሮ ቦንድ አበዳሪዎች ጋር በመርህ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሱን መዘገባችን ይታወሳል። ይህንን ዜና ተከትሎ፣ የፋይናንስ ባለሙያዎች የስምምነቱን ጥልቅ ይዘት፣ መንግስት የገባባቸውን አዳዲስ ግዴታዎች እና በቀጣይ የሀገሪቱ የዕዳ መክፈል አቅም ላይ የሚያሳድረውን ተጽዕኖ በስፋት እየተነተኑት ይገኛሉ።
ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉት የፋይናንስ ባለሙያው ዶ/ር አብዱልመናን መሐመድ፣ ስምምነቱ ሁለቱንም ወገኖች ከተለያየ አቅጣጫ ተጠቃሚ ያደረገ መሆኑን ያስረዳሉ። መንግስት ከተጋረጠበት የህግ ክስ ስጋት እና ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ መገለል ለመዳን ይህንን ስምምነት ከመቀበል ውጪ "ሌላ ምንም ዓይነት የተሻለ አማራጭ አልነበረውም" ሲሉ ይሞግታሉ።
በአንጻሩ አበዳሪዎቹ (የቦንድ ባለቤቶቹ) የ12 በመቶ የዕዳ ቅናሽ (Haircut) ቢደረግባቸውም፣ አጠቃላይ ሊገጥማቸው ይችል የነበረውን ከፍተኛ ኪሳራ መቀነስ በመቻላቸው እና አዳዲስ መብቶችን በማግኘታቸው ለእነሱ "በጣም ጥሩ ስምምነት" መሆኑን ባለሙያው አስምረውበታል።
ባለሙያው በትንታኔያቸው ትልቅ ትኩረት የሰጡት አበዳሪዎቹ ስምምነቱን እንዲቀበሉ ያስቻላቸውን አዲሱን "የማኒ ዋራንት" አንቀጽ ነው። በዚህ ስምምነት መሰረት ኢትዮጵያ ወደፊት አዲስ ቦንድ ለዓለም አቀፍ ገበያ ብታቀርብ፣ እነዚህ ነባር አበዳሪዎች በከፍተኛ ወለድ ቅድሚያ የመግዛት መብት አግኝተዋል። ይህ የወደፊት ወለድ የአሜሪካ መንግስት ከሚከፍለው ወለድ ላይ 4.6% ተደምሮበት በአጠቃላይ እስከ 9 በመቶ ሊደርስ እንደሚችል ዶ/ር አብዱልመናን አብራርተዋል።
መንግስት የወለድ መጠኑ ከፍተኛ በመሆኑ የተነሳ አዲሱን ቦንድ ላለማውጣት (እንዳያወጣ) ቢወስን እንኳ፣ ለአበዳሪዎቹ እስከ 90 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ የካሳ ክፍያ (Buyout option) ለመክፈል መስማማቱ ከበድ ያለ የገንዘብ ግዴታ መሆኑን ባለሙያው አስረድተዋል። መጠኑ "በጣም ከፍተኛ" ቢሆንም፣ መንግስት ይህንኑ የካሳ ክፍያ አማራጭ ሊከተል እንደሚችል ግምታቸውን አስቀምጠዋል።
ምንም እንኳን ስምምነቱ ለመንግስት ከባድ የገንዘብ ጫናዎችን ያካተተ ቢሆንም፣ በሌሎች የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ውጥኖች ላይ ግን አዎንታዊ ሚና እንዳለው ባለሙያው ያምናሉ።
የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) የስምምነቱን ይዘት የኢትዮጵያን የዕዳ ጫና የመሸከም አቅም ያገናዘበ ነው ብሎ ማረጋገጡ ትልቅ እርምጃ ነው። ከዚህም ባለፈ እንደ ቻይና እና ፈረንሳይ ካሉ የሁለትዮሽ አበዳሪ ሀገራት ጋር ለሚደረገው ሰፊ የዕዳ ሽግሽግ እና ማራዘም ድርድር በተፋጠነ ሁኔታ እልባት ለመስጠት ይህ የዩሮ ቦንድ ስምምነት ትልቅ የበር ከፋችነት ሚና እንደሚኖረው የፋይናንስ ባለሙያው ዶ/ር አብዱልመናን በትንታኔያቸው አመላክተዋል።
ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉት የፋይናንስ ባለሙያው ዶ/ር አብዱልመናን መሐመድ፣ ስምምነቱ ሁለቱንም ወገኖች ከተለያየ አቅጣጫ ተጠቃሚ ያደረገ መሆኑን ያስረዳሉ። መንግስት ከተጋረጠበት የህግ ክስ ስጋት እና ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ መገለል ለመዳን ይህንን ስምምነት ከመቀበል ውጪ "ሌላ ምንም ዓይነት የተሻለ አማራጭ አልነበረውም" ሲሉ ይሞግታሉ።
በአንጻሩ አበዳሪዎቹ (የቦንድ ባለቤቶቹ) የ12 በመቶ የዕዳ ቅናሽ (Haircut) ቢደረግባቸውም፣ አጠቃላይ ሊገጥማቸው ይችል የነበረውን ከፍተኛ ኪሳራ መቀነስ በመቻላቸው እና አዳዲስ መብቶችን በማግኘታቸው ለእነሱ "በጣም ጥሩ ስምምነት" መሆኑን ባለሙያው አስምረውበታል።
ባለሙያው በትንታኔያቸው ትልቅ ትኩረት የሰጡት አበዳሪዎቹ ስምምነቱን እንዲቀበሉ ያስቻላቸውን አዲሱን "የማኒ ዋራንት" አንቀጽ ነው። በዚህ ስምምነት መሰረት ኢትዮጵያ ወደፊት አዲስ ቦንድ ለዓለም አቀፍ ገበያ ብታቀርብ፣ እነዚህ ነባር አበዳሪዎች በከፍተኛ ወለድ ቅድሚያ የመግዛት መብት አግኝተዋል። ይህ የወደፊት ወለድ የአሜሪካ መንግስት ከሚከፍለው ወለድ ላይ 4.6% ተደምሮበት በአጠቃላይ እስከ 9 በመቶ ሊደርስ እንደሚችል ዶ/ር አብዱልመናን አብራርተዋል።
መንግስት የወለድ መጠኑ ከፍተኛ በመሆኑ የተነሳ አዲሱን ቦንድ ላለማውጣት (እንዳያወጣ) ቢወስን እንኳ፣ ለአበዳሪዎቹ እስከ 90 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ የካሳ ክፍያ (Buyout option) ለመክፈል መስማማቱ ከበድ ያለ የገንዘብ ግዴታ መሆኑን ባለሙያው አስረድተዋል። መጠኑ "በጣም ከፍተኛ" ቢሆንም፣ መንግስት ይህንኑ የካሳ ክፍያ አማራጭ ሊከተል እንደሚችል ግምታቸውን አስቀምጠዋል።
ምንም እንኳን ስምምነቱ ለመንግስት ከባድ የገንዘብ ጫናዎችን ያካተተ ቢሆንም፣ በሌሎች የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ውጥኖች ላይ ግን አዎንታዊ ሚና እንዳለው ባለሙያው ያምናሉ።
የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) የስምምነቱን ይዘት የኢትዮጵያን የዕዳ ጫና የመሸከም አቅም ያገናዘበ ነው ብሎ ማረጋገጡ ትልቅ እርምጃ ነው። ከዚህም ባለፈ እንደ ቻይና እና ፈረንሳይ ካሉ የሁለትዮሽ አበዳሪ ሀገራት ጋር ለሚደረገው ሰፊ የዕዳ ሽግሽግ እና ማራዘም ድርድር በተፋጠነ ሁኔታ እልባት ለመስጠት ይህ የዩሮ ቦንድ ስምምነት ትልቅ የበር ከፋችነት ሚና እንደሚኖረው የፋይናንስ ባለሙያው ዶ/ር አብዱልመናን በትንታኔያቸው አመላክተዋል።
1 month ago
ኢትዮጵያ ያለባትን የ1 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ዕዳ ለመክፈል ከአበዳሪዎቿ ጋር ስምምነት ላይ ደረሰች!
ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ የግል አበዳሪዎች ተበድራው የነበረውን 1 ቢሊዮን ዶላር (ዩሮቦንድ) በወቅቱ መክፈል አቅቷት የነበረ ቢሆንም አሁን ግን ዕዳውን የምታቀልበት የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሷን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ።
ኢትዮጵያ ከነበረባት 1 ቢሊዮን ዶላር ላይ የ12% ቅናሽ የተደረገላት ሲሆን በዚህ መሰረት የምትከፍለው ዕዳ ወደ 880 ሚሊዮን ዶላር ዝቅ ብሏል።
ይህንን 880 ሚሊዮን ዶላር እስከ 2029 ድረስ በ6.15% ወለድ በየደረጃው እንድትከፍል ጊዜ የተሰጣት ሲሆን ባለፉት ሁለት ዓመታት ሳትከፍል ያሳለፈችውን 99.4 ሚሊዮን ዶላር የወለድ ዕዳ ትከፍላለች።
ስምምነቱ ወደፊት ኢትዮጵያ ብድር ባስፈለጋት ጊዜ እስከ 1 ቢሊዮን ዶላር ድረስ በድጋሚ የመበደር መብት ወይም ዕድልን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል።
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) እና ዋናዎቹ አበዳሪ ሀገራት (ቻይና እና ፈረንሳይ) ስምምነቱን የደገፉ ሲሆን ይህም የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ገፅታ የሚያሻሽልና ተጨማሪ የውጭ ብድርና 1እርዳታ በቀላሉ እንድታገኝ በር የሚከፍት በመሆኑ .በገበያው ላይ ትልቅ ተስፋን ጥሏል።
በየአብሥራ ተፈራ
Seledadotio
Seledadotio
ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ የግል አበዳሪዎች ተበድራው የነበረውን 1 ቢሊዮን ዶላር (ዩሮቦንድ) በወቅቱ መክፈል አቅቷት የነበረ ቢሆንም አሁን ግን ዕዳውን የምታቀልበት የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሷን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ።
ኢትዮጵያ ከነበረባት 1 ቢሊዮን ዶላር ላይ የ12% ቅናሽ የተደረገላት ሲሆን በዚህ መሰረት የምትከፍለው ዕዳ ወደ 880 ሚሊዮን ዶላር ዝቅ ብሏል።
ይህንን 880 ሚሊዮን ዶላር እስከ 2029 ድረስ በ6.15% ወለድ በየደረጃው እንድትከፍል ጊዜ የተሰጣት ሲሆን ባለፉት ሁለት ዓመታት ሳትከፍል ያሳለፈችውን 99.4 ሚሊዮን ዶላር የወለድ ዕዳ ትከፍላለች።
ስምምነቱ ወደፊት ኢትዮጵያ ብድር ባስፈለጋት ጊዜ እስከ 1 ቢሊዮን ዶላር ድረስ በድጋሚ የመበደር መብት ወይም ዕድልን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል።
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) እና ዋናዎቹ አበዳሪ ሀገራት (ቻይና እና ፈረንሳይ) ስምምነቱን የደገፉ ሲሆን ይህም የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ገፅታ የሚያሻሽልና ተጨማሪ የውጭ ብድርና 1እርዳታ በቀላሉ እንድታገኝ በር የሚከፍት በመሆኑ .በገበያው ላይ ትልቅ ተስፋን ጥሏል።
በየአብሥራ ተፈራ
Seledadotio
Seledadotio
1 month ago
የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ለኢትዮጵያና ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት አስቸኳይ የገንዘብ ድጋፍ ሊያደርግ ነው።
የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በቅርቡ በነበረው የኢራን ጦርነት ምክንያት የተፈጠረውን የኤኮኖሚ ቀውስ ለመታደግ ኢትዮጵያን ጨምሮ ለተወሰኑ የአፍሪቃ ሃገራት የሚሰጠውን የገንዘብ ድጋፍ ሊያሳድግ ነው። ድርጅቱ ድጋፉን ከማሳደግ በተጨማሪ ገንዘቡን በፍጥነት ለማቅረብ ማቀዱም ተሰምቷል።
የድርጅቱ ቃል አቀባይ ጁሊ ኮዛክ እንዳሉት በመርኃ ግብሩ ኢትዮጵያ ፣ጋምቢያ እና ቡርኪና ፋሶ ተጠቃሚ ሲሆኑ በተጨማሪ ማላዊ አዲስ የፋይናንስ ድጋፍ እንድታገኝ ከተቋሙ ጋር የተፋጠነ ውይይት እያደረገች መሆኑ ተገልጿል።
ከዚህ በተጨማሪ ሳኦ ቶሜ እና ፕሪንሲፔም የ25 ሚሊዮን ዶላር የትብብር መርሃግብር አካል የሆነውን 6.1 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት ከስምምነት መድረሳቸውን የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።
የአይ ኤም ኤፍ (IMF) የአፍሪካ ዳይሬክተር ዘይን ዘይዳን በዋሽንግተን በሰጡት መግለጫ፥ በመካከለኛው ምስራቅ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት የአፍሪካ ቀጠና "ከባድ ፈተና" ውስጥ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ምንም እንኳን አሁን የተኩስ አቁም ስምምነት ቢደረስም በጦርነቱ ምክንያት የተስተጓጎለው የባህረ ሰላጤው ሀገራት የኃይል እና የነዳጅ ምርት ወደ ቀድሞ ቦታው ለመመለስ ከ6 እስከ 7 ወራት ሊፈጅ እንደሚችል ጠቁመዋል።
የነዳጅ ምርት አቅርቦቱ መቋረጥ በአፍሪካ ሀገራት ላይ ከፍተኛ የነዳጅ እና የማዳበሪያ ዋጋ ንረትን ያስከተለ መሆኑን የጠቀሰው ዘገባው አይ ኤም ኤፍ ይህንን ችግር ለመቅረፍ የአደጋ ጊዜ ፕሮግራሞቹን እያሰፋ መሆኑን ገልጿል።
እንደ ድርጅቱ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሰሃራ በታች ያሉ የአፍሪካ ሀገራት ያደረጓቸው የኤኮኖሚ ማሻሻያዎች አሁን ለተከሰተው የኃይል አቅርቦት መናወጥ የተሻለ የመቋቋም አቅም እንዲኖራቸው ረድቷቸዋል ። ይሁን እንጂ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ ተጨማሪ የአፍሪካ ሀገራት የገንዘብ ድጋፍ ሊጠይቁ እንደሚችሉ ግን አልሸሸገም።
DW Amharic
የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በቅርቡ በነበረው የኢራን ጦርነት ምክንያት የተፈጠረውን የኤኮኖሚ ቀውስ ለመታደግ ኢትዮጵያን ጨምሮ ለተወሰኑ የአፍሪቃ ሃገራት የሚሰጠውን የገንዘብ ድጋፍ ሊያሳድግ ነው። ድርጅቱ ድጋፉን ከማሳደግ በተጨማሪ ገንዘቡን በፍጥነት ለማቅረብ ማቀዱም ተሰምቷል።
የድርጅቱ ቃል አቀባይ ጁሊ ኮዛክ እንዳሉት በመርኃ ግብሩ ኢትዮጵያ ፣ጋምቢያ እና ቡርኪና ፋሶ ተጠቃሚ ሲሆኑ በተጨማሪ ማላዊ አዲስ የፋይናንስ ድጋፍ እንድታገኝ ከተቋሙ ጋር የተፋጠነ ውይይት እያደረገች መሆኑ ተገልጿል።
ከዚህ በተጨማሪ ሳኦ ቶሜ እና ፕሪንሲፔም የ25 ሚሊዮን ዶላር የትብብር መርሃግብር አካል የሆነውን 6.1 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት ከስምምነት መድረሳቸውን የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።
የአይ ኤም ኤፍ (IMF) የአፍሪካ ዳይሬክተር ዘይን ዘይዳን በዋሽንግተን በሰጡት መግለጫ፥ በመካከለኛው ምስራቅ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት የአፍሪካ ቀጠና "ከባድ ፈተና" ውስጥ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ምንም እንኳን አሁን የተኩስ አቁም ስምምነት ቢደረስም በጦርነቱ ምክንያት የተስተጓጎለው የባህረ ሰላጤው ሀገራት የኃይል እና የነዳጅ ምርት ወደ ቀድሞ ቦታው ለመመለስ ከ6 እስከ 7 ወራት ሊፈጅ እንደሚችል ጠቁመዋል።
የነዳጅ ምርት አቅርቦቱ መቋረጥ በአፍሪካ ሀገራት ላይ ከፍተኛ የነዳጅ እና የማዳበሪያ ዋጋ ንረትን ያስከተለ መሆኑን የጠቀሰው ዘገባው አይ ኤም ኤፍ ይህንን ችግር ለመቅረፍ የአደጋ ጊዜ ፕሮግራሞቹን እያሰፋ መሆኑን ገልጿል።
እንደ ድርጅቱ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሰሃራ በታች ያሉ የአፍሪካ ሀገራት ያደረጓቸው የኤኮኖሚ ማሻሻያዎች አሁን ለተከሰተው የኃይል አቅርቦት መናወጥ የተሻለ የመቋቋም አቅም እንዲኖራቸው ረድቷቸዋል ። ይሁን እንጂ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ ተጨማሪ የአፍሪካ ሀገራት የገንዘብ ድጋፍ ሊጠይቁ እንደሚችሉ ግን አልሸሸገም።
DW Amharic
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ መንግስት ለ2026/27 በጀት ዓመት ካቀረበው 2.34 ትሪሊዮን ብር ሪከርድ በጀት ውስጥ፣ 542.1 ቢሊዮን ብር (ወይም 3.4 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር) ለዕዳ ክፍያ ማዋሉ ተገለጸ። ይህ ግዙፍ ምደባ መንግስት ላቀደው ጠቅላላ በጀት የዕዳ መክፈያ ግዴታዎች ምን ያህል ከፍተኛውን የወጪ ድርሻ እየወሰዱ እንደሆነ በግልጽ የሚያሳይ ነው። የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሺዴ በጀቱን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀረቡ ሲሆን የበጀት ማዕቀፉ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) ጋር የሚደረገውን የኢኮኖሚ ማሻሻያ፣ የውጭ ምንዛሬ ገበያውን ከፊል ነጻ ማድረግን፣ የ10.1 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት ግብን እና እያደገ የመጣውን የወጪ ፍላጎት ታሳቢ ያደረገ መሆኑ ተገልጿል።
በአሁኑ ወቅት የዕዳ ክፍያ በመንግስት በጀት ውስጥ እጅግ ከፍተኛውን ድርሻ ይዟል። ይህ የዕዳ ክፍያ ከመደበኛ ወጪው 43.8 በመቶውን የሚሸፍን ነው። ይሁን እንጂ ትክክለኛው የዕዳ መክፈያ ፍላጎት 581.1 ቢሊዮን ብር መሆኑን ባለስልጣናቱ የገለጹ ሲሆን፣ ይህም የ39 ቢሊዮን ብር የፋይናንስ ክፍተት ፈጥሯል። ለዕዳ ክፍያ የተመደበው የዘንድሮው በጀት፣ ባለፈው በጀት ዓመት (2025/26) ተመድቦ ከነበረው 463.4 ቢሊዮን ብር ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ጭማሪ አሳይቷል። የዚህ ጭማሪ ዋና ምክንያቶች ኢትዮጵያ ያለባት ከባድ የብድር ጫና እንዲሁም የብር የመግዛት አቅም መዳከም (በብር የሚከፈለውን የውጭ ዕዳ መጠን ስለሚያሳድገው) ናቸው። ኢትዮጵያ በ2023 መገባደጃ ላይ የአንድ ቢሊዮን ዶላር ዩሮቦንድ ዕዳዋን መክፈል ተስኗት የነበረ ሲሆን፣ የዕዳ ማክበጃ ድርድር በማድረግ ላይ ትገኛለች።
በገቢ እና ወጪ ዝርዝር ዕቅዱ መሰረት፣ መንግስት 1.82 ትሪሊዮን ብር ገቢ እና እርዳታ ለመሰብሰብ ያቀደ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 1.5 ትሪሊዮን ብሩ (ወይም 82 በመቶው) ከታክስ የሚሰበሰብ ነው። የታክስ አሰባሰቡን በዝርዝር ስንመለከት፣ ከደመወዝ ገቢ ግብር 97.3 ቢሊዮን ብር፣ ከሀገር ውስጥ ቀጥታ ታክስ 427.5 ቢሊዮን ብር፣ ከንግድ ትርፍ ግብር 263 ቢሊዮን ብር፣ ከተዘዋዋሪ ታክስ 278 ቢሊዮን ብር፣ እንዲሁም ከተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) 339 ቢሊዮን ብር ይሰበሰባል ተብሎ ይጠበቃል።
በሌላ በኩል 1.2 ትሪሊዮን ብር ለመደበኛ ወጪ እንዲሁም 568 ቢሊዮን ብር ለካፒታል ወጪ ተመድቧል። ከዚህም በተጨማሪ ለማዳበሪያ፣ ለነዳጅ እና ለኢትዮጵያ ነዳጅ ድርጅት አቅም ማሳደጊያ የሚውል 236.4 ቢሊዮን ብር የድጎማ በጀት ተይዟል። ለፌዴራል እና ለክልል አስተዳደሮች 520.6 ቢሊዮን ብር የበጀት ድጋፍ ሲመደብ፣ 14 ቢሊዮን ብር ደግሞ ለዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈጸሚያ እንዲውል ተወስኗል።
መንግስት ወጪውን ቢያሳድግም የ308.6 ቢሊዮን ብር (የጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት 1.4 በመቶ) የተጣራ የበጀት ጉድለት ያጋጥመዋል ተብሎ ተገምቷል። ይህንን ክፍተት ለመሸፈን መንግስት በአብዛኛው ከሀገር ውስጥ በሚያገኘው 302.9 ቢሊዮን ብር ብድር ላይ የሚመረኮዝ ሲሆን፣ ከውጭ ምንጮች ይጠበቃል የተባለው 5.7 ቢሊዮን ብር ብቻ ነው። ይህ ሁኔታ የውጭ ፋይናንስ ውስን በመሆኑ መንግስት ክፍተቱን ለመድፈን በሀገር ውስጥ ብድር ላይ በእጅጉ ጥገኛ መሆኑን ያሳያል።
በጀቱ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጸድቆ ለፓርላማ የተመራ ሲሆን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት መንግስት የዕድገት ፍላጎቱን፣ እያሻቀበ ከመጣው የዕዳ ክፍያ፣ የድጎማ ጫና እና ውስን ከሆነው የውጭ ፋይናንስ ጋር እንዴት አጣጥሞ እንደሚሄድ በበጀቱ ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በአሁኑ ወቅት የዕዳ ክፍያ በመንግስት በጀት ውስጥ እጅግ ከፍተኛውን ድርሻ ይዟል። ይህ የዕዳ ክፍያ ከመደበኛ ወጪው 43.8 በመቶውን የሚሸፍን ነው። ይሁን እንጂ ትክክለኛው የዕዳ መክፈያ ፍላጎት 581.1 ቢሊዮን ብር መሆኑን ባለስልጣናቱ የገለጹ ሲሆን፣ ይህም የ39 ቢሊዮን ብር የፋይናንስ ክፍተት ፈጥሯል። ለዕዳ ክፍያ የተመደበው የዘንድሮው በጀት፣ ባለፈው በጀት ዓመት (2025/26) ተመድቦ ከነበረው 463.4 ቢሊዮን ብር ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ጭማሪ አሳይቷል። የዚህ ጭማሪ ዋና ምክንያቶች ኢትዮጵያ ያለባት ከባድ የብድር ጫና እንዲሁም የብር የመግዛት አቅም መዳከም (በብር የሚከፈለውን የውጭ ዕዳ መጠን ስለሚያሳድገው) ናቸው። ኢትዮጵያ በ2023 መገባደጃ ላይ የአንድ ቢሊዮን ዶላር ዩሮቦንድ ዕዳዋን መክፈል ተስኗት የነበረ ሲሆን፣ የዕዳ ማክበጃ ድርድር በማድረግ ላይ ትገኛለች።
በገቢ እና ወጪ ዝርዝር ዕቅዱ መሰረት፣ መንግስት 1.82 ትሪሊዮን ብር ገቢ እና እርዳታ ለመሰብሰብ ያቀደ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 1.5 ትሪሊዮን ብሩ (ወይም 82 በመቶው) ከታክስ የሚሰበሰብ ነው። የታክስ አሰባሰቡን በዝርዝር ስንመለከት፣ ከደመወዝ ገቢ ግብር 97.3 ቢሊዮን ብር፣ ከሀገር ውስጥ ቀጥታ ታክስ 427.5 ቢሊዮን ብር፣ ከንግድ ትርፍ ግብር 263 ቢሊዮን ብር፣ ከተዘዋዋሪ ታክስ 278 ቢሊዮን ብር፣ እንዲሁም ከተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) 339 ቢሊዮን ብር ይሰበሰባል ተብሎ ይጠበቃል።
በሌላ በኩል 1.2 ትሪሊዮን ብር ለመደበኛ ወጪ እንዲሁም 568 ቢሊዮን ብር ለካፒታል ወጪ ተመድቧል። ከዚህም በተጨማሪ ለማዳበሪያ፣ ለነዳጅ እና ለኢትዮጵያ ነዳጅ ድርጅት አቅም ማሳደጊያ የሚውል 236.4 ቢሊዮን ብር የድጎማ በጀት ተይዟል። ለፌዴራል እና ለክልል አስተዳደሮች 520.6 ቢሊዮን ብር የበጀት ድጋፍ ሲመደብ፣ 14 ቢሊዮን ብር ደግሞ ለዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈጸሚያ እንዲውል ተወስኗል።
መንግስት ወጪውን ቢያሳድግም የ308.6 ቢሊዮን ብር (የጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት 1.4 በመቶ) የተጣራ የበጀት ጉድለት ያጋጥመዋል ተብሎ ተገምቷል። ይህንን ክፍተት ለመሸፈን መንግስት በአብዛኛው ከሀገር ውስጥ በሚያገኘው 302.9 ቢሊዮን ብር ብድር ላይ የሚመረኮዝ ሲሆን፣ ከውጭ ምንጮች ይጠበቃል የተባለው 5.7 ቢሊዮን ብር ብቻ ነው። ይህ ሁኔታ የውጭ ፋይናንስ ውስን በመሆኑ መንግስት ክፍተቱን ለመድፈን በሀገር ውስጥ ብድር ላይ በእጅጉ ጥገኛ መሆኑን ያሳያል።
በጀቱ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጸድቆ ለፓርላማ የተመራ ሲሆን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት መንግስት የዕድገት ፍላጎቱን፣ እያሻቀበ ከመጣው የዕዳ ክፍያ፣ የድጎማ ጫና እና ውስን ከሆነው የውጭ ፋይናንስ ጋር እንዴት አጣጥሞ እንደሚሄድ በበጀቱ ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
2 months ago
IMF ለኢትዮጵያ የ468 ሚሊዮን ዶላር ተጨማሪ የገንዘብ ድጋፍ የሚያስገኝ የስምምነት ደረጃ ላይ መድረሱን አስታወቀ
የኔታ ሚዲያ
የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የባለሙያዎች ቡድን እና የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት በ3.4 ቢሊዮን ዶላር የተራዘመ የብድር ማዕቀፍ (ECF) አምስተኛው ክለሳ ላይ ከስምምነት መድረሳቸውን ድርጅቱ አስታወቀ።
ይህ በባለሙያዎች ደረጃ የተደረሰው ስምምነት በIMF ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሲጸድቅ ኢትዮጵያ ወደ 468 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚጠጋ ተጨማሪ ገንዘብ ማግኘት የምትችል ይሆናል።
በአልቫሮ ፒሪስ የተመራው የIMF የባለሙያዎች ቡድን ከአምስተኛው ክለሳ ጋር በተያያዘ ከግንቦት 1 እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በአካል ከዚያ በኋላ ደግሞ በበይነ መረብ (ቨርቿል) ውይይት ሲያደርግ ቆይቷል።
የልዑካን ቡድኑ መሪ አልቫሮ ፒሪስ ባወጡት መግለጫ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት አገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳቸውን በተሳካ ሁኔታ መተግበራቸውን መቀጠላቸውን ገልጸዋል።
እ.ኤ.አ እስከ 2026 መጀመሪያ ድረስ የምርት አመላካቾች፣ ወጪ ንግድ፣ የውጭ ምንዛሬ ክምችት እና የመንግሥት ገቢ መሻሻል ማሳየታቸውንና የዋጋ ንረትም መቀነሱን ጠቁመዋል።
ሆኖም በመካከለኛው ምስራቅ የተቀሰቀሰው ጦርነት በንግድ እንቅስቃሴ ላይ መስተጓጎል መፍጠሩን፣ ጊዜያዊ የነዳጅ እጥረት ማስከተሉን እና የገቢ ነዳጅና ማዳበሪያ ዋጋን በከፍተኛ ሁኔታ ማናሩን መግለጫው አመልክቷል።
ይህ ትልቅ ውጫዊ ተጽዕኖ ቢሆንም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አሁንም ጠንካራ መሆኑንና በምርት ዕድገትና በሸማቾች ዋጋ ንረት ላይ ያሳደረው ተጽዕኖ እስካሁን መጠነኛ መሆኑ ተገልጿል።
የIMF መግለጫ በመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ምክንያት ዓለም አቀፋዊ አለመረጋጋትና የሸቀጦች ዋጋ መዋዠቅ በመጨመሩ፣ በኢኮኖሚው ላይ ሊደቀኑ የሚችሉ ስጋቶች መጨመራቸውን ያስጠነቅቃል። በመሆኑም ለነዚህ አዳዲስ ተግዳሮቶች ብልህ ምላሽ መስጠትና የሀብት አጠቃቀምን በጥንቃቄ መምራት እንደሚያስፈልግ አሳስቧል።
ማክሮ-ኢኮኖሚያዊ መረጋጋትን በዘላቂነት ለማስቀጠል የሚከተሉት መሠረታዊ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ድርጅቱ መክሯል፦
• የገንዘብ ፖሊሲ ማጥበቅ፦ የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲን ማስቀጠል።
• የውጭ ምንዛሬ ገበያ ማሻሻያ፦ የውጭ ምንዛሬ ገበያው ይበልጥ ግልጽና ውጤታማ በሆነ መንገድ እንዲሠራ ማድረግ።
• የአገር ውስጥ ገቢና ወጪ አስተዳደር፦ የአገር ውስጥ ገቢ ማሰባሰብን ማሳደግና የወጪ አስተዳደርን በጥንቃቄ በመምራት የፋይናንስ ዘላቂነትን ማረጋገጥ።
• መዋቅራዊ ማሻሻያዎች፦ የንግድ አካባቢን ማሻሻል፣ የፋይናንስ ዘርፉን ጥንካሬ ማጠናከርና የግል ዘርፉ መር ለሆነ ዕድገት በር መክፈት።
የውጭ ዕዳ ሽግሽግ
የኢትዮጵያን የዕዳ ዘላቂነት ለመመለስ የሚያስችል አጠቃላይ የውጭ ዕዳ ሽግሽግ (treatment) ለማግኘት መልካም ግስጋሴ እየታየ መሆኑን IMF ገልጿል። ከባለሥልጣናት አበዳሪዎች ጋር የሚደረገው የዕዳ መልሶ ማዋቀር ውይይት እንደተጠበቀው እየገፋ ሲሆን ከቦንድ ባለቤቶች ጋር የሚደረገው ድርድርም መቀጠሉ ተጠቅሷል።
የIMF ልዑካን ቡድን በአዲስ አበባ በነበረው ቆይታ ከገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ፣ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ እና ከሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ እንዲሁም ከግል ዘርፉና ከልማት አጋሮች ተወካዮች ጋር ፍሬያማ ውይይት ማድረጉን በመግለጽ ለተደረገለት ትብብር ምስጋና አቅርቧል።
ይህ አምስተኛው ክለሳ በIMF ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሲጸድቅ ኢትዮጵያ በዚሁ ማዕቀፍ እስካሁን ያገኘችው አጠቃላይ የገንዘብ ድጋፍ ወደ 2.65 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ከፍ ይላል።
የኔታ ሚዲያ
የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የባለሙያዎች ቡድን እና የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት በ3.4 ቢሊዮን ዶላር የተራዘመ የብድር ማዕቀፍ (ECF) አምስተኛው ክለሳ ላይ ከስምምነት መድረሳቸውን ድርጅቱ አስታወቀ።
ይህ በባለሙያዎች ደረጃ የተደረሰው ስምምነት በIMF ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሲጸድቅ ኢትዮጵያ ወደ 468 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚጠጋ ተጨማሪ ገንዘብ ማግኘት የምትችል ይሆናል።
በአልቫሮ ፒሪስ የተመራው የIMF የባለሙያዎች ቡድን ከአምስተኛው ክለሳ ጋር በተያያዘ ከግንቦት 1 እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በአካል ከዚያ በኋላ ደግሞ በበይነ መረብ (ቨርቿል) ውይይት ሲያደርግ ቆይቷል።
የልዑካን ቡድኑ መሪ አልቫሮ ፒሪስ ባወጡት መግለጫ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት አገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳቸውን በተሳካ ሁኔታ መተግበራቸውን መቀጠላቸውን ገልጸዋል።
እ.ኤ.አ እስከ 2026 መጀመሪያ ድረስ የምርት አመላካቾች፣ ወጪ ንግድ፣ የውጭ ምንዛሬ ክምችት እና የመንግሥት ገቢ መሻሻል ማሳየታቸውንና የዋጋ ንረትም መቀነሱን ጠቁመዋል።
ሆኖም በመካከለኛው ምስራቅ የተቀሰቀሰው ጦርነት በንግድ እንቅስቃሴ ላይ መስተጓጎል መፍጠሩን፣ ጊዜያዊ የነዳጅ እጥረት ማስከተሉን እና የገቢ ነዳጅና ማዳበሪያ ዋጋን በከፍተኛ ሁኔታ ማናሩን መግለጫው አመልክቷል።
ይህ ትልቅ ውጫዊ ተጽዕኖ ቢሆንም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አሁንም ጠንካራ መሆኑንና በምርት ዕድገትና በሸማቾች ዋጋ ንረት ላይ ያሳደረው ተጽዕኖ እስካሁን መጠነኛ መሆኑ ተገልጿል።
የIMF መግለጫ በመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ምክንያት ዓለም አቀፋዊ አለመረጋጋትና የሸቀጦች ዋጋ መዋዠቅ በመጨመሩ፣ በኢኮኖሚው ላይ ሊደቀኑ የሚችሉ ስጋቶች መጨመራቸውን ያስጠነቅቃል። በመሆኑም ለነዚህ አዳዲስ ተግዳሮቶች ብልህ ምላሽ መስጠትና የሀብት አጠቃቀምን በጥንቃቄ መምራት እንደሚያስፈልግ አሳስቧል።
ማክሮ-ኢኮኖሚያዊ መረጋጋትን በዘላቂነት ለማስቀጠል የሚከተሉት መሠረታዊ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ድርጅቱ መክሯል፦
• የገንዘብ ፖሊሲ ማጥበቅ፦ የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲን ማስቀጠል።
• የውጭ ምንዛሬ ገበያ ማሻሻያ፦ የውጭ ምንዛሬ ገበያው ይበልጥ ግልጽና ውጤታማ በሆነ መንገድ እንዲሠራ ማድረግ።
• የአገር ውስጥ ገቢና ወጪ አስተዳደር፦ የአገር ውስጥ ገቢ ማሰባሰብን ማሳደግና የወጪ አስተዳደርን በጥንቃቄ በመምራት የፋይናንስ ዘላቂነትን ማረጋገጥ።
• መዋቅራዊ ማሻሻያዎች፦ የንግድ አካባቢን ማሻሻል፣ የፋይናንስ ዘርፉን ጥንካሬ ማጠናከርና የግል ዘርፉ መር ለሆነ ዕድገት በር መክፈት።
የውጭ ዕዳ ሽግሽግ
የኢትዮጵያን የዕዳ ዘላቂነት ለመመለስ የሚያስችል አጠቃላይ የውጭ ዕዳ ሽግሽግ (treatment) ለማግኘት መልካም ግስጋሴ እየታየ መሆኑን IMF ገልጿል። ከባለሥልጣናት አበዳሪዎች ጋር የሚደረገው የዕዳ መልሶ ማዋቀር ውይይት እንደተጠበቀው እየገፋ ሲሆን ከቦንድ ባለቤቶች ጋር የሚደረገው ድርድርም መቀጠሉ ተጠቅሷል።
የIMF ልዑካን ቡድን በአዲስ አበባ በነበረው ቆይታ ከገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ፣ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ እና ከሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ እንዲሁም ከግል ዘርፉና ከልማት አጋሮች ተወካዮች ጋር ፍሬያማ ውይይት ማድረጉን በመግለጽ ለተደረገለት ትብብር ምስጋና አቅርቧል።
ይህ አምስተኛው ክለሳ በIMF ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሲጸድቅ ኢትዮጵያ በዚሁ ማዕቀፍ እስካሁን ያገኘችው አጠቃላይ የገንዘብ ድጋፍ ወደ 2.65 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ከፍ ይላል።
2 months ago
የአይኤምኤፍ (IMF) የብር ምንዛሬ ሙሉ በሙሉ በገበያ እንዲወሰንና ድጎማዎች እንዲነሱ ጠየቀ
#fastmereja I የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ልዑክ በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም ላይ ያደረገውን አምስተኛ ግምገማ በአዲስ አበባ አጠናቋል። ድርጅቱ የኢትዮጵያ መንግስት የብርን የውጭ ምንዛሬ ተመን ሙሉ በሙሉ ለገበያ ፍላጎትና አቅርቦት እንዲተው፣ የመንግስት ቀጥተኛ ድጎማዎችን በሂደት እንዲያስወግድ እና የሀገር ውስጥ ታክስ ስብሰባን በከፍተኛ ሁኔታ እንዲያሳድግ ጠይቋል።
ይህ የአይኤምኤፍ ጥያቄ ተግባራዊ መሆን መጀመሩን ተከትሎ፣ ውሳኔው በተራው ህዝብ እና በንግዱ ማህበረሰብ ላይ ፈጣንና ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ይገኛል። የብር የመግዛት አቅም መውረድ፣ የዋጋ ንረት መናር እና የኑሮ ውድነት መባባስ ዋነኛ ማሳያዎች ናቸው።
በተጨማሪም መንግስት የታክስ ገቢውን ለማሳደግ የጀመረው ጥብቅ ቁጥጥር፣ መደበኛውን የታክስ ህግ የማስከበር ሂደት ወደ አስገዳጅ የቀየረው ይመስላል ሲሉ የዘርፉ ባለሙያዎች ስጋታቸውን ገልጸዋል።
ምንም እንኳን ማሻሻያው የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ መረጋጋትን ያመጣል ተብሎ በዓለም አቀፍ ተቋማት ቢታመንም፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ግን ማህበረሰቡን እና የግሉን ዘርፍ ክፉኛ እየፈተነ ይገኛል። መንግስት በበኩሉ የድሆችን ጫና ለመቀነስ የማህበራዊ ደህንነት መረቦችን እንደሚዘረጋ ቀደም ሲል መግለጹ ይታወሳል።
ዘገባው የአዲስ ፎርቹን ነው።
#fastmereja I የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ልዑክ በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም ላይ ያደረገውን አምስተኛ ግምገማ በአዲስ አበባ አጠናቋል። ድርጅቱ የኢትዮጵያ መንግስት የብርን የውጭ ምንዛሬ ተመን ሙሉ በሙሉ ለገበያ ፍላጎትና አቅርቦት እንዲተው፣ የመንግስት ቀጥተኛ ድጎማዎችን በሂደት እንዲያስወግድ እና የሀገር ውስጥ ታክስ ስብሰባን በከፍተኛ ሁኔታ እንዲያሳድግ ጠይቋል።
ይህ የአይኤምኤፍ ጥያቄ ተግባራዊ መሆን መጀመሩን ተከትሎ፣ ውሳኔው በተራው ህዝብ እና በንግዱ ማህበረሰብ ላይ ፈጣንና ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ይገኛል። የብር የመግዛት አቅም መውረድ፣ የዋጋ ንረት መናር እና የኑሮ ውድነት መባባስ ዋነኛ ማሳያዎች ናቸው።
በተጨማሪም መንግስት የታክስ ገቢውን ለማሳደግ የጀመረው ጥብቅ ቁጥጥር፣ መደበኛውን የታክስ ህግ የማስከበር ሂደት ወደ አስገዳጅ የቀየረው ይመስላል ሲሉ የዘርፉ ባለሙያዎች ስጋታቸውን ገልጸዋል።
ምንም እንኳን ማሻሻያው የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ መረጋጋትን ያመጣል ተብሎ በዓለም አቀፍ ተቋማት ቢታመንም፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ግን ማህበረሰቡን እና የግሉን ዘርፍ ክፉኛ እየፈተነ ይገኛል። መንግስት በበኩሉ የድሆችን ጫና ለመቀነስ የማህበራዊ ደህንነት መረቦችን እንደሚዘረጋ ቀደም ሲል መግለጹ ይታወሳል።
ዘገባው የአዲስ ፎርቹን ነው።
3 months ago
"ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) ዋና ዳይሬክተር ክርስታሊና ጆርጂየቫ ጋር ውይይት አድርገናል"ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) ዋና ዳይሬክተር ክርስታሊና ጆርጂየቫ ጋር ተገናኝተን በኢኮኖሚያዊ እድገት፣ በአጋርነት እና ቅድሚያ በሚሰጣቸው የጋራ ጉዳዮች ላይ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ገጻቸው ባጋሩት መልዕክት አስታውቀዋል።
ለነበረን ጠቃሚ የሃሳብ ልውውጥና ቀጣይነት ላለው አጋርነት ምስጋናዬ የላቀ ነው ብለዋል።
ሁለተኛ አመቱን እየያዘ ያለው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሸያ አፈጻጸም IMF እንዴት እንደሚያየው በዝርዝር እንደሚገመገም ይጠበቃል።
seledadotio
seledadotio
ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) ዋና ዳይሬክተር ክርስታሊና ጆርጂየቫ ጋር ተገናኝተን በኢኮኖሚያዊ እድገት፣ በአጋርነት እና ቅድሚያ በሚሰጣቸው የጋራ ጉዳዮች ላይ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ገጻቸው ባጋሩት መልዕክት አስታውቀዋል።
ለነበረን ጠቃሚ የሃሳብ ልውውጥና ቀጣይነት ላለው አጋርነት ምስጋናዬ የላቀ ነው ብለዋል።
ሁለተኛ አመቱን እየያዘ ያለው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሸያ አፈጻጸም IMF እንዴት እንደሚያየው በዝርዝር እንደሚገመገም ይጠበቃል።
seledadotio
seledadotio
Sponsored by
Surafel
3 months ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከIMF ዋና ዳይሬክተር ክርስታሊና ጆርጂየቫ ጋር ተወያዩ
***********
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) ዋና ዳይሬክተር ክርስታሊና ጆርጂየቫ ጋር በኢኮኖሚያዊ ዕድገት፣ በአጋርነት እና ቅድሚያ በሚሰጣቸው የጋራ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ማድረጋቸውን ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጽ ባሰፈሩት መልዕክት፣ ”ለነበረን ጠቃሚ የሐሳብ ልውውጥ እና ቀጣይነት ላለው አጋርነት ምስጋናዬ የላቀ ነው” ብለዋል።
#ebc #ethiopia #pmabiyahmed #imf
***********
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) ዋና ዳይሬክተር ክርስታሊና ጆርጂየቫ ጋር በኢኮኖሚያዊ ዕድገት፣ በአጋርነት እና ቅድሚያ በሚሰጣቸው የጋራ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ማድረጋቸውን ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጽ ባሰፈሩት መልዕክት፣ ”ለነበረን ጠቃሚ የሐሳብ ልውውጥ እና ቀጣይነት ላለው አጋርነት ምስጋናዬ የላቀ ነው” ብለዋል።
#ebc #ethiopia #pmabiyahmed #imf
3 months ago
የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት የሚቀጥል ከሆነ የከፋ የኢኮኖሚ ቀውስ ሊከተል ይችላል፦ IMF
*********************
የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ፣ የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት የሚቀጥል ከሆነ፣ የከፋ የኢኮኖሚ ቀውስ ሊከተል እንደሚችል አስጠነቀቁ።
ጦርነቱ የሚቀጥል ከሆነ የነዳጅ ዋጋ ንረቱ ተባብሶ የአንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ እስከ 125 ዶላር ሊደርስ እንደሚችል ስጋታቸውን ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ሁኔታ እያገረሸ ያለው የዋጋ ግሽበትም በዚሁ ከቀጠለ በዓለም ዙሪያ የኑሮ ውድነቱን ይበልጥ ያባብሰዋል ነው ያሉት።
IMF ግጭቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ይቆማል በሚል ቀደም ሲል አስቀምጦት የነበረው የ3.1% አማካይ ዕድገት እና የ4.4% አማካይ ግሽበት ትንበያም አሁን ባለው ሁኔታ ሊሳካ እንደማይችልና ሁኔታው ከዚህ የከፋ እንደሚሆን ጠቁመዋል።
ጦርነቱ በቶሎ ካልቆመ የዓለም ኢኮኖሚ ዕድገት ይበልጥ እየቀነሰና የዋጋ ግሽበት ደግሞ ይበልጥ እየጨመረ መሄዱ የማይቀር ነው ብለዋል።
በሀና ምንዳሁን
#middleeastwar #oilprice #economy #imf #ebc
*********************
የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ፣ የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት የሚቀጥል ከሆነ፣ የከፋ የኢኮኖሚ ቀውስ ሊከተል እንደሚችል አስጠነቀቁ።
ጦርነቱ የሚቀጥል ከሆነ የነዳጅ ዋጋ ንረቱ ተባብሶ የአንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ እስከ 125 ዶላር ሊደርስ እንደሚችል ስጋታቸውን ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ሁኔታ እያገረሸ ያለው የዋጋ ግሽበትም በዚሁ ከቀጠለ በዓለም ዙሪያ የኑሮ ውድነቱን ይበልጥ ያባብሰዋል ነው ያሉት።
IMF ግጭቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ይቆማል በሚል ቀደም ሲል አስቀምጦት የነበረው የ3.1% አማካይ ዕድገት እና የ4.4% አማካይ ግሽበት ትንበያም አሁን ባለው ሁኔታ ሊሳካ እንደማይችልና ሁኔታው ከዚህ የከፋ እንደሚሆን ጠቁመዋል።
ጦርነቱ በቶሎ ካልቆመ የዓለም ኢኮኖሚ ዕድገት ይበልጥ እየቀነሰና የዋጋ ግሽበት ደግሞ ይበልጥ እየጨመረ መሄዱ የማይቀር ነው ብለዋል።
በሀና ምንዳሁን
#middleeastwar #oilprice #economy #imf #ebc
3 months ago
ኢትዮጵያ የአፍሪካ የኢኮኖሚ ግስጋሴ መሪ
✅የ2026 የኢኮኖሚ እድገት ትንበያ (IMF): 9.2%
✅ከአፍሪካ ሀገራት መካከል ቀዳሚዋና ፈጣን እድገት አስመዝጋቢ
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #development
✅የ2026 የኢኮኖሚ እድገት ትንበያ (IMF): 9.2%
✅ከአፍሪካ ሀገራት መካከል ቀዳሚዋና ፈጣን እድገት አስመዝጋቢ
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #development
4 months ago
ጅቡቲ የደረሱት ነዳጅ ጫኝ መርከቦች
#ethiopia ||ወደ ጅቡቲ ወደብ የደረሱ ሶስት ግዙፍ መርከቦች በኢትዮጵያ አጋጥሞ ለነበረው የነዳጅ እጥረት መጠነኛ እፎይታ እንደሚያመጡ ተገለጸ።
ከመጋቢት 19 እስከ 23 ባሉት ቀናት የደረሱት እነዚህ መርከቦች በአጠቃላይ 143 ሺህ ሜትሪክ ቶን የጄት ነዳጅ እና ናፍጣ ይዘው መምጣታቸው ታውቋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ኢኮኖሚ ላይ ስላንዣበበው ስጋት አስጠንቅቋል።
በባህረ ሰላጤው አካባቢ እየታየ ያለው ጂኦፖለቲካዊ ውጥረት ዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮችን በማስተጓጎል እና የጭነት ትራንስፖርት ዋጋን በማስወደድ በቀጣናው ሀገራት ላይ ከፍተኛ የዋጋ ንረት ሊያስከትል እንደሚችል የድርጅቱ ትንታኔ አመልክቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #capitalnews #ethiopia #djibouti #fuelshortage #imf #eastafrica #globaleconomy #geopolitics #newsupdate #ነዳጅ #ኢትዮጵያ #ጅቡቲ #ኢኮኖሚ
#ethiopia ||ወደ ጅቡቲ ወደብ የደረሱ ሶስት ግዙፍ መርከቦች በኢትዮጵያ አጋጥሞ ለነበረው የነዳጅ እጥረት መጠነኛ እፎይታ እንደሚያመጡ ተገለጸ።
ከመጋቢት 19 እስከ 23 ባሉት ቀናት የደረሱት እነዚህ መርከቦች በአጠቃላይ 143 ሺህ ሜትሪክ ቶን የጄት ነዳጅ እና ናፍጣ ይዘው መምጣታቸው ታውቋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ኢኮኖሚ ላይ ስላንዣበበው ስጋት አስጠንቅቋል።
በባህረ ሰላጤው አካባቢ እየታየ ያለው ጂኦፖለቲካዊ ውጥረት ዓለም አቀፍ የንግድ መስመሮችን በማስተጓጎል እና የጭነት ትራንስፖርት ዋጋን በማስወደድ በቀጣናው ሀገራት ላይ ከፍተኛ የዋጋ ንረት ሊያስከትል እንደሚችል የድርጅቱ ትንታኔ አመልክቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #capitalnews #ethiopia #djibouti #fuelshortage #imf #eastafrica #globaleconomy #geopolitics #newsupdate #ነዳጅ #ኢትዮጵያ #ጅቡቲ #ኢኮኖሚ
Sponsored by
Surafel
4 months ago
በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ግጭት በዓለም ኢኮኖሚ ላይ የሚያሳድረውን ጫና ለመቀነስ የጋራ ግብረ-ኃይል ተቋቋመ
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ያለው ጦርነት በዓለም አቀፍ የኢነርጂ አቅርቦት እና በኢኮኖሚው መረጋጋት ላይ የደቀነውን ከፍተኛ ስጋት ለመቋቋም፣ ሦስቱ ግዙፍ ተቋማት ማለትም የዓለም ባንክ፣ ዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) እና ዓለም አቀፍ የኢነርጂ ኤጀንሲ (IEA) በጋራ ለመስራት መስማማታቸውን አስታወቁ።
ተቋማቱ ባወጡት የጋራ መግለጫ፣ ግጭቱ ያስከተለው የነዳጅ፣ የጋዝ እና የማዳበሪያ ዋጋ መናር በተለይም በታዳጊና ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው ሀገራት ላይ የኑሮ ውድነት እና የልማት ጫና እያሳደረ መሆኑን ገልጸዋል። ይህንን የገበያ መዋዠቅ በዘላቂነት ለመቆጣጠር እንዲቻልም አዲስ አስተባባሪ ቡድን ማዋቀራቸውን ይፋ አድርገዋል።
የተቋማቱ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች፦
በጦርነቱ ምክንያት በኃይል አቅርቦት ላይ የሚታየውን መቆራረጥ እና የዋጋ መዋዠቅ በቅርበት መከታተል።
በዋጋ ንረት ሳቢያ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ቀውስ ለገጠማቸው ሀገራት የገንዘብ ድጋፍ ማቅረብ።
ሀገራት የኃይል አቅርቦት ዋስትናቸውን እንዲያረጋግጡና የኢኮኖሚ ጫናውን እንዲቋቋሙ የሚያስችሉ የፖሊሲ አማራጮችን መንደፍ።
ይህ ጥምረት በተለይ የማዳበሪያ ዋጋ መናር በዓለም አቀፍ የምግብ ዋስትና ላይ ሊያስከትል የሚችለውን አደጋ ለመቀነስ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #worldbank #imf #iea #middleeastconflict #globaleconomy #energysecurity #ethiopia #economicnews
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ያለው ጦርነት በዓለም አቀፍ የኢነርጂ አቅርቦት እና በኢኮኖሚው መረጋጋት ላይ የደቀነውን ከፍተኛ ስጋት ለመቋቋም፣ ሦስቱ ግዙፍ ተቋማት ማለትም የዓለም ባንክ፣ ዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) እና ዓለም አቀፍ የኢነርጂ ኤጀንሲ (IEA) በጋራ ለመስራት መስማማታቸውን አስታወቁ።
ተቋማቱ ባወጡት የጋራ መግለጫ፣ ግጭቱ ያስከተለው የነዳጅ፣ የጋዝ እና የማዳበሪያ ዋጋ መናር በተለይም በታዳጊና ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው ሀገራት ላይ የኑሮ ውድነት እና የልማት ጫና እያሳደረ መሆኑን ገልጸዋል። ይህንን የገበያ መዋዠቅ በዘላቂነት ለመቆጣጠር እንዲቻልም አዲስ አስተባባሪ ቡድን ማዋቀራቸውን ይፋ አድርገዋል።
የተቋማቱ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች፦
በጦርነቱ ምክንያት በኃይል አቅርቦት ላይ የሚታየውን መቆራረጥ እና የዋጋ መዋዠቅ በቅርበት መከታተል።
በዋጋ ንረት ሳቢያ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ቀውስ ለገጠማቸው ሀገራት የገንዘብ ድጋፍ ማቅረብ።
ሀገራት የኃይል አቅርቦት ዋስትናቸውን እንዲያረጋግጡና የኢኮኖሚ ጫናውን እንዲቋቋሙ የሚያስችሉ የፖሊሲ አማራጮችን መንደፍ።
ይህ ጥምረት በተለይ የማዳበሪያ ዋጋ መናር በዓለም አቀፍ የምግብ ዋስትና ላይ ሊያስከትል የሚችለውን አደጋ ለመቀነስ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #worldbank #imf #iea #middleeastconflict #globaleconomy #energysecurity #ethiopia #economicnews
5 months ago
ፖላንድ አሁን በዓለም ላይ ካሉ 20 ግዙፍ ኢኮኖሚዎች ተርታ ተሰልፋለች፦ ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ?
በ1989 የኮሚኒዝም ውድቀትን ተከትሎ የፖላንድ ኢኮኖሚ አስገራሚ ለውጥ አሳይቷል። በአንድ ወቅት ደካማና ያልተረጋጋ የነበረው ኢኮኖሚዋ፣ ዛሬ በአውሮፓ ውስጥ ስኬታማ ከሚባሉት አንዱ ሆኗል።
ከአንድ ትውልድ በፊት በፖላንድ ስኳር እና ዱቄት የሚገዙት በኩፖን ነበር፤ ዜጎቿም ከምዕራብ ጀርመናውያን ጋር ሲነጻጸር የአስረኛ እጅ ያህል ብቻ ነበር የሚያገኙት። ዛሬ ግን የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ስዊዘርላንድን በመቅደም፣ ከቢሊዮን ዶላር በላይ ዓመታዊ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) በማስመዝገብ በዓለም 20ኛው ግዙፍ ኢኮኖሚ ለመሆን በቅቷል።
ይህ ከ1989-90 የኮሚኒዝም ፍርስራሽ ተነስተው ወደ አውሮፓ የእድገት ሻምፒዮንነት የተደረገ ታሪካዊ ዝላይ ነው - ይህም ለተራው ህዝብ ብልጽግናን እንዴት ማምጣት እንደሚቻል ትምህርት የሚሰጥ መሆኑን ኢኮኖሚስቶች ይናገራሉ።
የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደርም ይህ ዕውቅና ሊሰጠው ይገባል በሚል ፖላንድ በቀጣይ ዓመት በሚካሄደው የቡድን 20 ጉባኤ ላይ እንድትጋበዝ ፍላጎት አለው።
ይህ ለውጥ እንደ ጆአና ኮዋልስካ ባሉ ሰዎች ሕይወት ውስጥ ይንጸባረቃል። በበርሊን እና በዋርሶ መካከል በምትገኘው ፖዝናን ከተማ ውስጥ መሃንዲስ የሆነችው ጆአና፣ በአሜሪካ ለአምስት ዓመታት ከቆየች በኋላ ወደ ሀገሯ ተመልሳለች።
"ወደ ፖላንድ ከተመለስኩ በኋላ የሚናፍቀኝ ነገር እንዳለ ብዙ ጊዜ እጠየቃለሁ፣ እውነቱን ለመናገር ግን ተቃራኒው ነው የሚሰማኝ" ትላለች። "በብዙ ዘርፎች ከአሜሪካ ቀድመን እንገኛለን።"
ኮዋልስካ በፖዝናን የሱፐር ኮምፒውቲንግ እና ኔትወርክ ማእከል ውስጥ ትሰራለች። ማእከሉ በፖላንድ የመጀመሪያውን አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ፋብሪካ እያለማ ሲሆን፣ በአውሮፓ ህብረት ከሚደገፉ አስር የኳንተም ኮምፒውተሮች አንዱ ጋርም እያገናኘው ይገኛል።
በፖዝናን ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ ከተመረቀች በኋላ በአሜሪካ ማይክሮሶፍት ውስጥ የሰራች ቢሆንም፣ "የተልዕኮ ስሜት" ይጎድላት እንደነበር ትናገራለች። "በተለይ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ረገድ ቴክኖሎጂው በፖላንድ በሚገርም ፍጥነት እያደገ ነው፤ ለዚህም ነው መመለሱ በጣም የሳበኝ" ትላለች።
ከድህነት መውጣት
ለቡድን 20 ጉባኤ የቀረበው ግብዣ ትልቅ ትርጉም ያለው ቢሆንም፣ እስካሁን በንግድ ቡድኑ ውስጥ እንግዳ ሀገር ሙሉ አባል የሆነችበት አጋጣሚ የለም። ሆኖም ግን አሃዞቹ የራሳቸውን ታሪክ ይናገራሉ፦ በ35 ዓመታት ውስጥ የፖላንድ የነፍስ ወከፍ ገቢ በ2025 ወደ 55,340 ዶላር አድጓል፣ ይህም የአውሮፓ ህብረት አማካይ 85% ነው።
በ1990 ከነበረበት 6,730 ዶላር ሲነጻጸር ግዙፍ ዝላይ ሲሆን፣ አሁን በዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) መረጃ መሠረት ከጃፓን (52,039 ዶላር) ጋር እኩል ደረጃ ላይ ትገኛለች።
ፖላንድ እ.ኤ.አ. በ2004 የአውሮፓ ህብረትን ከተቀላቀለች በኋላ፣ ኢኮኖሚዋ በአማካይ በዓመት 3.8% አድጓል፤ ይህም ከአውሮፓ አማካይ 1.8% በእጥፍ ይበልጣል።
እንደ ማርሲን ፒዮንትኮቭስኪ ገለጻ፣ ለዚህ ስኬት ቁልፉ አንድ ምክንያት ብቻ አይደለም። ዋነኞቹ ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው፦
ጠንካራ ተቋማት፦ ገለልተኛ የዳኝነት አካል፣ ፍትሃዊ ውድድርን የሚያረጋግጥ የፀረ-ሞኖፖሊ ተቋም እና የባንክ ቀውስን የሚከላከሉ ጠንካራ ደንቦች።
ሙስናን መከላከል፦ ለተቋማቱ ጥንካሬ ምስጋና ይግባውና እንደሌሎች የቀድሞ ኮሚኒስት ሀገራት ኢኮኖሚው በሙስና እና በባለሀብቶች አልተመዘበረም።
የአውሮፓ ህብረት ድጋፍ፦ ከህብረቱ የተገኘው በቢሊዮን የሚቆጠር ዩሮ እርዳታ እና የጋራ ገበያ ተጠቃሚነት።
ፖለቲካዊ ስምምነት፦ የርዕዮተ ዓለም ልዩነት ሳይገድባቸው፣ ሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች ወደ አውሮፓ ህብረት የመግባት የረጅም ጊዜ ግብ ላይ ተስማምተው መቆየታቸው።
"ፖላንዳውያን ወዴት እንደሚሄዱ ያውቁ ነበር" ይላሉ ፒዮንትኮቭስኪ። ምዕራባውያን ለ500 ዓመታት ያዳበሩትን የተቋማት አሰራር እና ህጎችን ፖላንድ በአጭር ጊዜ ወስዳ ተግባራዊ አድርጋለች።
የሶላሪስ ኩባንያ ስኬት
በ1996 በፖዝናን የተመሰረተው የሶላሪስ ኩባንያ፣ ዛሬ 15% የገበያ ድርሻ በመያዝ በአውሮፓ ግንባር ቀደም የኤሌክትሪክ አውቶቡስ አምራች ነው።
ይህ ኩባንያ የፖላንድን የስራ ፈጣሪነት እና የፈጠራ ብቃት ማሳያ ነው። እ.ኤ.አ. በ2011 ገና በአውሮፓ የኤሌክትሪክ ቴክኖሎጂ ባልተለመደበት ወቅት ምርቱን በመጀመሩ የቴክኖሎጂ መሪ መሆን ችሏል።
ፈታኝ ሁኔታዎች
የኢኮኖሚ እድገቱ ቢቀጥልም፣ ፖላንድ አሁንም እንደ ዝቅተኛ የልደት መጠን፣ የህዝብ ቁጥር እርጅና እና ከገጠርና ከተማ ያለውን የልማት ልዩነት የመሳሰሉ ፈተናዎች ከፊቷ አሉ። ሆኖም እንደ ካዚሚዬርዝ ፋላክ ያሉ ወጣቶች ሀገሪቱ ያላትን ተስፋ በማየት እዚያው ለመቆየት መርጠዋል። "ፖላንድ ተስፋ ያላት ሀገር ናት" ይላል።
ምንጭ፦AP / DH
በ1989 የኮሚኒዝም ውድቀትን ተከትሎ የፖላንድ ኢኮኖሚ አስገራሚ ለውጥ አሳይቷል። በአንድ ወቅት ደካማና ያልተረጋጋ የነበረው ኢኮኖሚዋ፣ ዛሬ በአውሮፓ ውስጥ ስኬታማ ከሚባሉት አንዱ ሆኗል።
ከአንድ ትውልድ በፊት በፖላንድ ስኳር እና ዱቄት የሚገዙት በኩፖን ነበር፤ ዜጎቿም ከምዕራብ ጀርመናውያን ጋር ሲነጻጸር የአስረኛ እጅ ያህል ብቻ ነበር የሚያገኙት። ዛሬ ግን የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ስዊዘርላንድን በመቅደም፣ ከቢሊዮን ዶላር በላይ ዓመታዊ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) በማስመዝገብ በዓለም 20ኛው ግዙፍ ኢኮኖሚ ለመሆን በቅቷል።
ይህ ከ1989-90 የኮሚኒዝም ፍርስራሽ ተነስተው ወደ አውሮፓ የእድገት ሻምፒዮንነት የተደረገ ታሪካዊ ዝላይ ነው - ይህም ለተራው ህዝብ ብልጽግናን እንዴት ማምጣት እንደሚቻል ትምህርት የሚሰጥ መሆኑን ኢኮኖሚስቶች ይናገራሉ።
የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደርም ይህ ዕውቅና ሊሰጠው ይገባል በሚል ፖላንድ በቀጣይ ዓመት በሚካሄደው የቡድን 20 ጉባኤ ላይ እንድትጋበዝ ፍላጎት አለው።
ይህ ለውጥ እንደ ጆአና ኮዋልስካ ባሉ ሰዎች ሕይወት ውስጥ ይንጸባረቃል። በበርሊን እና በዋርሶ መካከል በምትገኘው ፖዝናን ከተማ ውስጥ መሃንዲስ የሆነችው ጆአና፣ በአሜሪካ ለአምስት ዓመታት ከቆየች በኋላ ወደ ሀገሯ ተመልሳለች።
"ወደ ፖላንድ ከተመለስኩ በኋላ የሚናፍቀኝ ነገር እንዳለ ብዙ ጊዜ እጠየቃለሁ፣ እውነቱን ለመናገር ግን ተቃራኒው ነው የሚሰማኝ" ትላለች። "በብዙ ዘርፎች ከአሜሪካ ቀድመን እንገኛለን።"
ኮዋልስካ በፖዝናን የሱፐር ኮምፒውቲንግ እና ኔትወርክ ማእከል ውስጥ ትሰራለች። ማእከሉ በፖላንድ የመጀመሪያውን አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ፋብሪካ እያለማ ሲሆን፣ በአውሮፓ ህብረት ከሚደገፉ አስር የኳንተም ኮምፒውተሮች አንዱ ጋርም እያገናኘው ይገኛል።
በፖዝናን ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ ከተመረቀች በኋላ በአሜሪካ ማይክሮሶፍት ውስጥ የሰራች ቢሆንም፣ "የተልዕኮ ስሜት" ይጎድላት እንደነበር ትናገራለች። "በተለይ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ረገድ ቴክኖሎጂው በፖላንድ በሚገርም ፍጥነት እያደገ ነው፤ ለዚህም ነው መመለሱ በጣም የሳበኝ" ትላለች።
ከድህነት መውጣት
ለቡድን 20 ጉባኤ የቀረበው ግብዣ ትልቅ ትርጉም ያለው ቢሆንም፣ እስካሁን በንግድ ቡድኑ ውስጥ እንግዳ ሀገር ሙሉ አባል የሆነችበት አጋጣሚ የለም። ሆኖም ግን አሃዞቹ የራሳቸውን ታሪክ ይናገራሉ፦ በ35 ዓመታት ውስጥ የፖላንድ የነፍስ ወከፍ ገቢ በ2025 ወደ 55,340 ዶላር አድጓል፣ ይህም የአውሮፓ ህብረት አማካይ 85% ነው።
በ1990 ከነበረበት 6,730 ዶላር ሲነጻጸር ግዙፍ ዝላይ ሲሆን፣ አሁን በዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) መረጃ መሠረት ከጃፓን (52,039 ዶላር) ጋር እኩል ደረጃ ላይ ትገኛለች።
ፖላንድ እ.ኤ.አ. በ2004 የአውሮፓ ህብረትን ከተቀላቀለች በኋላ፣ ኢኮኖሚዋ በአማካይ በዓመት 3.8% አድጓል፤ ይህም ከአውሮፓ አማካይ 1.8% በእጥፍ ይበልጣል።
እንደ ማርሲን ፒዮንትኮቭስኪ ገለጻ፣ ለዚህ ስኬት ቁልፉ አንድ ምክንያት ብቻ አይደለም። ዋነኞቹ ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው፦
ጠንካራ ተቋማት፦ ገለልተኛ የዳኝነት አካል፣ ፍትሃዊ ውድድርን የሚያረጋግጥ የፀረ-ሞኖፖሊ ተቋም እና የባንክ ቀውስን የሚከላከሉ ጠንካራ ደንቦች።
ሙስናን መከላከል፦ ለተቋማቱ ጥንካሬ ምስጋና ይግባውና እንደሌሎች የቀድሞ ኮሚኒስት ሀገራት ኢኮኖሚው በሙስና እና በባለሀብቶች አልተመዘበረም።
የአውሮፓ ህብረት ድጋፍ፦ ከህብረቱ የተገኘው በቢሊዮን የሚቆጠር ዩሮ እርዳታ እና የጋራ ገበያ ተጠቃሚነት።
ፖለቲካዊ ስምምነት፦ የርዕዮተ ዓለም ልዩነት ሳይገድባቸው፣ ሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች ወደ አውሮፓ ህብረት የመግባት የረጅም ጊዜ ግብ ላይ ተስማምተው መቆየታቸው።
"ፖላንዳውያን ወዴት እንደሚሄዱ ያውቁ ነበር" ይላሉ ፒዮንትኮቭስኪ። ምዕራባውያን ለ500 ዓመታት ያዳበሩትን የተቋማት አሰራር እና ህጎችን ፖላንድ በአጭር ጊዜ ወስዳ ተግባራዊ አድርጋለች።
የሶላሪስ ኩባንያ ስኬት
በ1996 በፖዝናን የተመሰረተው የሶላሪስ ኩባንያ፣ ዛሬ 15% የገበያ ድርሻ በመያዝ በአውሮፓ ግንባር ቀደም የኤሌክትሪክ አውቶቡስ አምራች ነው።
ይህ ኩባንያ የፖላንድን የስራ ፈጣሪነት እና የፈጠራ ብቃት ማሳያ ነው። እ.ኤ.አ. በ2011 ገና በአውሮፓ የኤሌክትሪክ ቴክኖሎጂ ባልተለመደበት ወቅት ምርቱን በመጀመሩ የቴክኖሎጂ መሪ መሆን ችሏል።
ፈታኝ ሁኔታዎች
የኢኮኖሚ እድገቱ ቢቀጥልም፣ ፖላንድ አሁንም እንደ ዝቅተኛ የልደት መጠን፣ የህዝብ ቁጥር እርጅና እና ከገጠርና ከተማ ያለውን የልማት ልዩነት የመሳሰሉ ፈተናዎች ከፊቷ አሉ። ሆኖም እንደ ካዚሚዬርዝ ፋላክ ያሉ ወጣቶች ሀገሪቱ ያላትን ተስፋ በማየት እዚያው ለመቆየት መርጠዋል። "ፖላንድ ተስፋ ያላት ሀገር ናት" ይላል።
ምንጭ፦AP / DH
6 months ago
ኢትዮጵያ በ G20 ማዕቀፍ የመጀመሪያውን የብድር ሽግሽግ ስምምነት ከፈረንሳይ ጋር ተፈራረመች
ኢትዮጵያ እና ፈረንሳይ የሀገሪቱን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃ የሚደግፍ እና ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን የሚያጠናክር ስምምነት ትናንት በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ እና የፈረንሳይ የአውሮፓና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ኤሌኖሬ ካሮይት በጋራ ፈርመውታል።
የብድር እፎይታ፦ ኢትዮጵያ በ G20 የብድር ማዕቀፍ (Common Framework) መሠረት ከመንግሥታዊ አበዳሪዎች ኮሚቴ (OCC) አባል አገር ጋር የመጀመሪያውን የሁለትዮሽ የብድር ሽግሽግ ስምምነት ተፈራርማለች።
81.5 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ፦ ፈረንሳይ ለሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ (HGER 2.0) ማስፈጸሚያ የሚውል 80 ሚሊዮን ዩሮ የበጀት ድጋፍ እና 1.5 ሚሊዮን ዩሮ የቴክኒክ ድጋፍ አበርክታለች።
ስትራቴጂካዊ ፕሮጀክቶች፦ ፈረንሳይ በቢሾፍቱ በሚገነባው አዲሱ ግዙፍ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ላይ በቴክኖሎጂና በፋይናንስ ለመሳተፍ ፍላጎቷን አረጋግጣለች።
የኢነርጂ ዘርፍ፦ የሁለቱ አገራት አጠቃላይ ኢንቨስትመንት 600 ሚሊዮን ዩሮ የደረሰ ሲሆን፣ ግማሹ የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማትን ለማዘመን የሚውል ነው።
ተግዳሮቶች
ምንም እንኳን ይህ ስምምነት ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ትልቅ ተስፋ ቢሆንም፣ የሚከተሉት ነጥቦች ግን ትኩረት የሚሹ ናቸው፦
የእዳ ሽግግር እንጂ ስረዛ አይደለም፦ የብድር ሽግሽግ (Restructuring) ማለት የክፍያ ጊዜን ማራዘም እንጂ እዳው ተሰረዘ ማለት አይደለም። የኢኮኖሚ ማሻሻያው በተቀመጠለት ፍጥነትና ጥራት ካልተጓዘ፣ ወደፊት የሚመጣው የክፍያ ጫና ይበልጥ ሊከብድ ይችላል።
የማሻሻያው ማህበራዊ ዋጋ፦ እነዚህ ድጋፎች የሚመጡት በ IMF የሚመራውን የገበያ መር የኢኮኖሚ ማሻሻያ ተከትሎ ነው። ይህ ደግሞ በአጭር ጊዜ ውስጥ የኑሮ ውድነትን ሊያስከትል ስለሚችል፣ ድጋፉ ዝቅተኛውን ማህበረሰብ ለመታደግ መዋሉን ማረጋገጥ ወሳኝ ነው።
የአፈጻጸም ብቃት፦ ለግዙፍ ፕሮጀክቶች (እንደ አውሮፕላን ማረፊያ) የተመደበው ገንዘብ በተባለለት ጥራትና ጊዜ መከናወኑ መከታተል ትልቅ የቤት ስራ ይሆናል።
ኢትዮጵያ እና ፈረንሳይ የሀገሪቱን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እርምጃ የሚደግፍ እና ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን የሚያጠናክር ስምምነት ትናንት በአዲስ አበባ ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ እና የፈረንሳይ የአውሮፓና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ኤሌኖሬ ካሮይት በጋራ ፈርመውታል።
የብድር እፎይታ፦ ኢትዮጵያ በ G20 የብድር ማዕቀፍ (Common Framework) መሠረት ከመንግሥታዊ አበዳሪዎች ኮሚቴ (OCC) አባል አገር ጋር የመጀመሪያውን የሁለትዮሽ የብድር ሽግሽግ ስምምነት ተፈራርማለች።
81.5 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ፦ ፈረንሳይ ለሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ (HGER 2.0) ማስፈጸሚያ የሚውል 80 ሚሊዮን ዩሮ የበጀት ድጋፍ እና 1.5 ሚሊዮን ዩሮ የቴክኒክ ድጋፍ አበርክታለች።
ስትራቴጂካዊ ፕሮጀክቶች፦ ፈረንሳይ በቢሾፍቱ በሚገነባው አዲሱ ግዙፍ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ላይ በቴክኖሎጂና በፋይናንስ ለመሳተፍ ፍላጎቷን አረጋግጣለች።
የኢነርጂ ዘርፍ፦ የሁለቱ አገራት አጠቃላይ ኢንቨስትመንት 600 ሚሊዮን ዩሮ የደረሰ ሲሆን፣ ግማሹ የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማትን ለማዘመን የሚውል ነው።
ተግዳሮቶች
ምንም እንኳን ይህ ስምምነት ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ትልቅ ተስፋ ቢሆንም፣ የሚከተሉት ነጥቦች ግን ትኩረት የሚሹ ናቸው፦
የእዳ ሽግግር እንጂ ስረዛ አይደለም፦ የብድር ሽግሽግ (Restructuring) ማለት የክፍያ ጊዜን ማራዘም እንጂ እዳው ተሰረዘ ማለት አይደለም። የኢኮኖሚ ማሻሻያው በተቀመጠለት ፍጥነትና ጥራት ካልተጓዘ፣ ወደፊት የሚመጣው የክፍያ ጫና ይበልጥ ሊከብድ ይችላል።
የማሻሻያው ማህበራዊ ዋጋ፦ እነዚህ ድጋፎች የሚመጡት በ IMF የሚመራውን የገበያ መር የኢኮኖሚ ማሻሻያ ተከትሎ ነው። ይህ ደግሞ በአጭር ጊዜ ውስጥ የኑሮ ውድነትን ሊያስከትል ስለሚችል፣ ድጋፉ ዝቅተኛውን ማህበረሰብ ለመታደግ መዋሉን ማረጋገጥ ወሳኝ ነው።
የአፈጻጸም ብቃት፦ ለግዙፍ ፕሮጀክቶች (እንደ አውሮፕላን ማረፊያ) የተመደበው ገንዘብ በተባለለት ጥራትና ጊዜ መከናወኑ መከታተል ትልቅ የቤት ስራ ይሆናል።
6 months ago
የዶላር ዳግም ልደት ወይስ የኢኮኖሚ ቁማር? የኢትዮጵያ “ቢግ ባንግ” ሪፎርም እና የነፃ ገበያ መገፋፋት
1. የካቲት 4 ቀን 2018 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ይፋ ያደረገው የውጭ ምንዛሪ መመሪያ፣ ዝም ብሎ የቴክኒክ ሰነድ አይደለም፤ ይልቁንም ላለፉት 50 ዓመታት የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ደም ስር አንቆ የያዘውን “የቁጥጥር ሰንሰለት” የሚበጣጥስ መጥረቢያ ነው። ይህ 19 ነጥቦችን የያዘው አዋጅ፣ ኢትዮጵያ በታሪኳ አድርጋው የማታውቀውን የኢኮኖሚ “ቢግ ባንግ” (Big Bang) ሽግግር መጀመሯን ያበስራል። በኢኮኖሚ ፈላስፎች መነጽር ሲታይ፣ ይህ እርምጃ አዳም ስሚዝ “የማይታየው እጅ” (Invisible Hand) ብሎ የጠራውን ገበያ መር ስርዓት በኢትዮጵያ ምድር ለመትከል የተደረገ ደፋር ሙከራ ነው።
2. የዚህ ሪፎርም ዋነኛው መነሻ ከአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ጋር የተደረሰው የ 3.4 ቢሊዮን ዶላር የብድር ስምምነት ቢሆንም፣ ውስጣዊ ፍላጎቱ ግን የኢትዮጵያን የውጭ ምንዛሪ ረሃብ በዘላቂነት መፍታት ነው። ቀደም ሲል በኦፊሴላዊው የምንዛሪ ዋጋ እና በጥቁር ገበያው መካከል የነበረው ልዩነት (Premium) ከ 100% በላይ ማደጉ፣ ምርት ወደ ውጭ የሚላክበትን ሳይሆን ዶላር የሚሸሸግበትን ኢኮኖሚ ፈጥሮ ነበር። አዲሱ መመሪያ ይህንን “የጥላ ኢኮኖሚ” አፍርሶ፣ ዶላርን ከጓዳ ወደ ባንክ አደባባይ ለማውጣት የታለመ ነው።
3. የአገልግሎት ላኪዎች 100% ገቢያቸውን እንዲይዙ መፈቀዱ (አንቀጽ 1)፣ ከቲዮሪ አንጻር “የባለቤትነት መብት” (Property Rights) ማረጋገጫ ነው። ጆን ሎክ እንደሚለው፣ አንድ ሰው በጥረቱ ያገኘውን ሀብት የመጠቀም ሙሉ መብት ሊኖረው ይገባል። መንግስት ቀደም ሲል ከላኪዎች ላይ ይነጥቅ የነበረውን 50% እና ከዚያ በላይ ድርሻ መተዉ፣ ላኪዎች ይበልጥ እንዲያመርቱ ትልቅ ማበረታቻ (Incentive) ይፈጥራል። ይህ ደግሞ በረዥም ጊዜ የሀገሪቱን የወጪ ንግድ ገቢ በቢሊዮን ዶላሮች እንደሚያሳድገው ይጠበቃል።
4. ግለሰቦች ለቤተሰቦቻቸው እስከ 3,000 ዶላር እንዲልኩ መፈቀዱ (አንቀጽ 8)፣ የመንግስትን የቁጥጥር ስፋት (State Scope) በእጅጉ ይቀንሳል። ይህ እርምጃ ሚልተን ፍሪድማን “Capitalism and Freedom” በሚለው መጽሐፉ የጠቀሰውን የግል ኢኮኖሚ ነፃነት የሚያንፀባርቅ ነው። ዜጎች በገዛ ገንዘባቸው የልጆቻቸውን ትምህርትና ህክምና እንዲከፍሉ መፈቀዱ፣ በህዝብና በመንግስት መካከል ለዘመናት ተሸርሽሮ የነበረውን ማህበራዊ ውል (Social Contract) መልሶ የማደስ አቅም አለው።
5. ዳታዎች እንደሚያሳዩት፣ ኢትዮጵያ በየአመቱ ከዳያስፖራ የምታገኘው ሬሚታንስ (Remittance) ከ 5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ቢሆንም፣ ከግማሽ በላይ የሚሆነው በህገ-ወጥ መንገድ ይዘዋወር ነበር። አዲሱ መመሪያ ዶላርን ያለ ሰነድ መመንዘር መፍቀዱ (አንቀጽ 7)፣ ይህን በጥቁር ገበያ የሚመላለሰውን ቢሊዮን ዶላር ወደ ህጋዊው ስርዓት የሚመልስ “መግነጢሳዊ ኃይል” ነው። ይህ የገንዘብ ፍሰት ወደ ባንኮች ሲገባ፣ ባንኮች ለኢንዱስትሪው የሚሰጡት የብድር አቅም (Liquidity) በእጥፍ ሊያድግ ይችላል።
6. የውጭ ኢንቨስተሮች ትርፋቸውን ያለ ገደብ እንዲያወጡ መፈቀዱ (አንቀጽ 16) ግን የሁለት ስለት ቢላዋ ነው። ለዴቪድ ሪካርዶ የንግድ ቲዮሪ ተከታዮች፣ ይህ እርምጃ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን (FDI) የሚስብ ማር ነው። ሆኖም፣ እንደ ጆሴፍ ስቲግሊዝ ያሉ ሊቃውንት “የካፒታል ሽሽት” (Capital Flight) ስጋትን ያነሳሉ። በሀገር ውስጥ የፖለቲካ አለመረጋጋት ቢከሰት፣ ኢንቨስተሮች ያላቸውን ዶላር ይዘው በአንድ ጀምበር ቢወጡ፣ የኢትዮጵያ የውጭ መጠባበቂያ ክምችት (Foreign Reserve) ድንገት ሊሟጠጥ ይችላል።
7. የባንኮች ራስ-ገዝነት (Autonomy) መጨመር ሌላው የዚህ ሪፎርም ምሰሶ ነው። ባንኮች የፎርዋርድ ግብይት (Forward Transaction) እንዲያካሂዱ መፈቀዱ (አንቀጽ 9)፣ ነጋዴዎች ለወደፊት ግዢዎቻቸው የምንዛሪ ዋጋን ቀድመው እንዲቆልፉ (Hedging) ይረዳቸዋል። ይህ በንግድ ዓለም ውስጥ ያለውን እርግጠኛ አለመሆን (Uncertainty) በመቀነስ፣ የዋጋ ግሽበትን ለማረጋጋት የሚረዳ ዘመናዊ የፋይናንስ መሳሪያ ነው።
8. ይሁን እንጂ፣ ባንኮች ከካፒታላቸው 10% ዋስትና እንዲሰጡ መፈቀዱ (አንቀጽ 14) ልብ አንጠልጣይ አደጋ አለው። የኢትዮጵያ ባንኮች በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ቀውስ የመመታት ልምድ የላቸውም። ባንኮች የገቡት ዋስትና ተቀባይነት አጥቶ ወይም ብድሩ ሳይከፈል ቢቀር፣ የሀገር ውስጥ ባንኮች መክሰር (Bank Failure) ደረጃ ሊደርሱ ይችላሉ። ይህ ደግሞ በዜጎች ቁጠባ ላይ ትልቅ አደጋ ስለሚደቅን፣ የብሔራዊ ባንክ የቁጥጥር ዓይን (Supervision) እጅግ ንቁ መሆን አለበት።
9. የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች ጥሬ ገንዘብ የመያዝ አቅማቸው ወደ 25% ማደጉ (አንቀጽ 18)፣ የገበያውን የዶላር ዝውውር (Circulation) ያቀልጠዋል። ይህ እርምጃ የጥቁር ገበያ ደላሎችን ከስራ የሚያስወጣ ቢሆንም፣ አዲሶቹ የፍቃድ ባለቤቶች ራሳቸው ወደ “ህጋዊ ደላላነት” እንዳይቀየሩ ጥብቅ ኦዲት ይፈልጋል። የገንዘብ ማጠብ (Money Laundering) ወንጀሎችን ለመከላከል የዲጂታል ክትትል ስርዓት የግድ ይላል።
10. የቬትናምን ተሞክሮ ብንመለከት፣ ሀገሪቱ በ 1980 ዎቹ መጨረሻ መሰል እርምጃ ስትወስድ፣ በአምራች ዘርፉ ላይ ትልቅ ስራ ሰርታ ነበር። ኢትዮጵያ ግን አሁንም 80% የምትጠቀመውን ሸቀጥ ከውጭ ታስገባለች። ዶላር በነፃነት መዘዋወሩ ብቻውን ለውጥ አያመጣም፤ የምርት አብዮት ካልታከለበት፣ ነፃ ገበያው የውጭ ሀገራት ምርቶች መጣያ (Dumping ground) የመሆን አደጋ አለው።
11. የዋጋ ግሽበት (Inflation) የዚህ ሪፎርም ትልቁ ጠላት ነው። የምንዛሪ ዋጋው ለገበያ ሲተው፣ የብር ዋጋ መውደቁ አይቀሬ ነው። ይህ ደግሞ የመድኃኒት፣ የነዳጅ እና የፋብሪካ ጥሬ እቃዎች ዋጋን ሊያስንረው ይችላል። ኬይንስ እንደሚለው፣ በመካከለኛ ጊዜ ኢኮኖሚው ቢረጋጋም፣ “በመጨረሻ ሁላችንም እንሞታለን”። ስለዚህ ዝቅተኛው ማህበረሰብ በዚህ የሽግግር ወቅት በኑሮ ውድነት እንዳይቀጠቀጥ መንግስት የማህበራዊ ድጋፍ መረቦችን ማጠናከር አለበት።
12. 100 ዶላር የነበረው የሂሳብ መክፈቻ መቅረት (አንቀጽ 5)፣ ለድሃው ዜጋ የተሰጠ የኢኮኖሚ “ዲሞክራሲ” ነው። ይህም የባንክ አገልግሎት ተደራሽነትን (Financial Inclusion) በመጨመር፣ ህዝቡ በዶላር እንዲቆጥብና የሀገር ውስጥ ካፒታል እንዲያድግ ያደርጋል። ይህ የባህሪ ለውጥ (Behavioral Change) በረዥም ጊዜ የሀገሪቱን የቁጠባ ባህል ይቀይረዋል።
13. ድርጅቶች ከሀገር ውጭ መዋእለ ነዋያቸውን እንዲያፈሱ መፈቀዱ (አንቀጽ 6) ግን እጅግ አነጋጋሪ ነው። ኢትዮጵያ ራሷ የካፒታል እጥረት ባለባት ሁኔታ፣ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ዶላር ይዘው ወደ ውጭ እንዲወጡ መፈቀዱ በምን ስሌት እንደመጣ ግልጽ አይደለም። ይህ ነጥብ ባለሀብቶች ሀብታቸውን ወደ አስተማማኝ ሀገራት እንዲያሸሹ (Flight to Safety) በር ሊከፍት ይችላል።
1. የካቲት 4 ቀን 2018 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ይፋ ያደረገው የውጭ ምንዛሪ መመሪያ፣ ዝም ብሎ የቴክኒክ ሰነድ አይደለም፤ ይልቁንም ላለፉት 50 ዓመታት የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ደም ስር አንቆ የያዘውን “የቁጥጥር ሰንሰለት” የሚበጣጥስ መጥረቢያ ነው። ይህ 19 ነጥቦችን የያዘው አዋጅ፣ ኢትዮጵያ በታሪኳ አድርጋው የማታውቀውን የኢኮኖሚ “ቢግ ባንግ” (Big Bang) ሽግግር መጀመሯን ያበስራል። በኢኮኖሚ ፈላስፎች መነጽር ሲታይ፣ ይህ እርምጃ አዳም ስሚዝ “የማይታየው እጅ” (Invisible Hand) ብሎ የጠራውን ገበያ መር ስርዓት በኢትዮጵያ ምድር ለመትከል የተደረገ ደፋር ሙከራ ነው።
2. የዚህ ሪፎርም ዋነኛው መነሻ ከአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ጋር የተደረሰው የ 3.4 ቢሊዮን ዶላር የብድር ስምምነት ቢሆንም፣ ውስጣዊ ፍላጎቱ ግን የኢትዮጵያን የውጭ ምንዛሪ ረሃብ በዘላቂነት መፍታት ነው። ቀደም ሲል በኦፊሴላዊው የምንዛሪ ዋጋ እና በጥቁር ገበያው መካከል የነበረው ልዩነት (Premium) ከ 100% በላይ ማደጉ፣ ምርት ወደ ውጭ የሚላክበትን ሳይሆን ዶላር የሚሸሸግበትን ኢኮኖሚ ፈጥሮ ነበር። አዲሱ መመሪያ ይህንን “የጥላ ኢኮኖሚ” አፍርሶ፣ ዶላርን ከጓዳ ወደ ባንክ አደባባይ ለማውጣት የታለመ ነው።
3. የአገልግሎት ላኪዎች 100% ገቢያቸውን እንዲይዙ መፈቀዱ (አንቀጽ 1)፣ ከቲዮሪ አንጻር “የባለቤትነት መብት” (Property Rights) ማረጋገጫ ነው። ጆን ሎክ እንደሚለው፣ አንድ ሰው በጥረቱ ያገኘውን ሀብት የመጠቀም ሙሉ መብት ሊኖረው ይገባል። መንግስት ቀደም ሲል ከላኪዎች ላይ ይነጥቅ የነበረውን 50% እና ከዚያ በላይ ድርሻ መተዉ፣ ላኪዎች ይበልጥ እንዲያመርቱ ትልቅ ማበረታቻ (Incentive) ይፈጥራል። ይህ ደግሞ በረዥም ጊዜ የሀገሪቱን የወጪ ንግድ ገቢ በቢሊዮን ዶላሮች እንደሚያሳድገው ይጠበቃል።
4. ግለሰቦች ለቤተሰቦቻቸው እስከ 3,000 ዶላር እንዲልኩ መፈቀዱ (አንቀጽ 8)፣ የመንግስትን የቁጥጥር ስፋት (State Scope) በእጅጉ ይቀንሳል። ይህ እርምጃ ሚልተን ፍሪድማን “Capitalism and Freedom” በሚለው መጽሐፉ የጠቀሰውን የግል ኢኮኖሚ ነፃነት የሚያንፀባርቅ ነው። ዜጎች በገዛ ገንዘባቸው የልጆቻቸውን ትምህርትና ህክምና እንዲከፍሉ መፈቀዱ፣ በህዝብና በመንግስት መካከል ለዘመናት ተሸርሽሮ የነበረውን ማህበራዊ ውል (Social Contract) መልሶ የማደስ አቅም አለው።
5. ዳታዎች እንደሚያሳዩት፣ ኢትዮጵያ በየአመቱ ከዳያስፖራ የምታገኘው ሬሚታንስ (Remittance) ከ 5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ቢሆንም፣ ከግማሽ በላይ የሚሆነው በህገ-ወጥ መንገድ ይዘዋወር ነበር። አዲሱ መመሪያ ዶላርን ያለ ሰነድ መመንዘር መፍቀዱ (አንቀጽ 7)፣ ይህን በጥቁር ገበያ የሚመላለሰውን ቢሊዮን ዶላር ወደ ህጋዊው ስርዓት የሚመልስ “መግነጢሳዊ ኃይል” ነው። ይህ የገንዘብ ፍሰት ወደ ባንኮች ሲገባ፣ ባንኮች ለኢንዱስትሪው የሚሰጡት የብድር አቅም (Liquidity) በእጥፍ ሊያድግ ይችላል።
6. የውጭ ኢንቨስተሮች ትርፋቸውን ያለ ገደብ እንዲያወጡ መፈቀዱ (አንቀጽ 16) ግን የሁለት ስለት ቢላዋ ነው። ለዴቪድ ሪካርዶ የንግድ ቲዮሪ ተከታዮች፣ ይህ እርምጃ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን (FDI) የሚስብ ማር ነው። ሆኖም፣ እንደ ጆሴፍ ስቲግሊዝ ያሉ ሊቃውንት “የካፒታል ሽሽት” (Capital Flight) ስጋትን ያነሳሉ። በሀገር ውስጥ የፖለቲካ አለመረጋጋት ቢከሰት፣ ኢንቨስተሮች ያላቸውን ዶላር ይዘው በአንድ ጀምበር ቢወጡ፣ የኢትዮጵያ የውጭ መጠባበቂያ ክምችት (Foreign Reserve) ድንገት ሊሟጠጥ ይችላል።
7. የባንኮች ራስ-ገዝነት (Autonomy) መጨመር ሌላው የዚህ ሪፎርም ምሰሶ ነው። ባንኮች የፎርዋርድ ግብይት (Forward Transaction) እንዲያካሂዱ መፈቀዱ (አንቀጽ 9)፣ ነጋዴዎች ለወደፊት ግዢዎቻቸው የምንዛሪ ዋጋን ቀድመው እንዲቆልፉ (Hedging) ይረዳቸዋል። ይህ በንግድ ዓለም ውስጥ ያለውን እርግጠኛ አለመሆን (Uncertainty) በመቀነስ፣ የዋጋ ግሽበትን ለማረጋጋት የሚረዳ ዘመናዊ የፋይናንስ መሳሪያ ነው።
8. ይሁን እንጂ፣ ባንኮች ከካፒታላቸው 10% ዋስትና እንዲሰጡ መፈቀዱ (አንቀጽ 14) ልብ አንጠልጣይ አደጋ አለው። የኢትዮጵያ ባንኮች በዓለም አቀፍ የፋይናንስ ቀውስ የመመታት ልምድ የላቸውም። ባንኮች የገቡት ዋስትና ተቀባይነት አጥቶ ወይም ብድሩ ሳይከፈል ቢቀር፣ የሀገር ውስጥ ባንኮች መክሰር (Bank Failure) ደረጃ ሊደርሱ ይችላሉ። ይህ ደግሞ በዜጎች ቁጠባ ላይ ትልቅ አደጋ ስለሚደቅን፣ የብሔራዊ ባንክ የቁጥጥር ዓይን (Supervision) እጅግ ንቁ መሆን አለበት።
9. የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች ጥሬ ገንዘብ የመያዝ አቅማቸው ወደ 25% ማደጉ (አንቀጽ 18)፣ የገበያውን የዶላር ዝውውር (Circulation) ያቀልጠዋል። ይህ እርምጃ የጥቁር ገበያ ደላሎችን ከስራ የሚያስወጣ ቢሆንም፣ አዲሶቹ የፍቃድ ባለቤቶች ራሳቸው ወደ “ህጋዊ ደላላነት” እንዳይቀየሩ ጥብቅ ኦዲት ይፈልጋል። የገንዘብ ማጠብ (Money Laundering) ወንጀሎችን ለመከላከል የዲጂታል ክትትል ስርዓት የግድ ይላል።
10. የቬትናምን ተሞክሮ ብንመለከት፣ ሀገሪቱ በ 1980 ዎቹ መጨረሻ መሰል እርምጃ ስትወስድ፣ በአምራች ዘርፉ ላይ ትልቅ ስራ ሰርታ ነበር። ኢትዮጵያ ግን አሁንም 80% የምትጠቀመውን ሸቀጥ ከውጭ ታስገባለች። ዶላር በነፃነት መዘዋወሩ ብቻውን ለውጥ አያመጣም፤ የምርት አብዮት ካልታከለበት፣ ነፃ ገበያው የውጭ ሀገራት ምርቶች መጣያ (Dumping ground) የመሆን አደጋ አለው።
11. የዋጋ ግሽበት (Inflation) የዚህ ሪፎርም ትልቁ ጠላት ነው። የምንዛሪ ዋጋው ለገበያ ሲተው፣ የብር ዋጋ መውደቁ አይቀሬ ነው። ይህ ደግሞ የመድኃኒት፣ የነዳጅ እና የፋብሪካ ጥሬ እቃዎች ዋጋን ሊያስንረው ይችላል። ኬይንስ እንደሚለው፣ በመካከለኛ ጊዜ ኢኮኖሚው ቢረጋጋም፣ “በመጨረሻ ሁላችንም እንሞታለን”። ስለዚህ ዝቅተኛው ማህበረሰብ በዚህ የሽግግር ወቅት በኑሮ ውድነት እንዳይቀጠቀጥ መንግስት የማህበራዊ ድጋፍ መረቦችን ማጠናከር አለበት።
12. 100 ዶላር የነበረው የሂሳብ መክፈቻ መቅረት (አንቀጽ 5)፣ ለድሃው ዜጋ የተሰጠ የኢኮኖሚ “ዲሞክራሲ” ነው። ይህም የባንክ አገልግሎት ተደራሽነትን (Financial Inclusion) በመጨመር፣ ህዝቡ በዶላር እንዲቆጥብና የሀገር ውስጥ ካፒታል እንዲያድግ ያደርጋል። ይህ የባህሪ ለውጥ (Behavioral Change) በረዥም ጊዜ የሀገሪቱን የቁጠባ ባህል ይቀይረዋል።
13. ድርጅቶች ከሀገር ውጭ መዋእለ ነዋያቸውን እንዲያፈሱ መፈቀዱ (አንቀጽ 6) ግን እጅግ አነጋጋሪ ነው። ኢትዮጵያ ራሷ የካፒታል እጥረት ባለባት ሁኔታ፣ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ዶላር ይዘው ወደ ውጭ እንዲወጡ መፈቀዱ በምን ስሌት እንደመጣ ግልጽ አይደለም። ይህ ነጥብ ባለሀብቶች ሀብታቸውን ወደ አስተማማኝ ሀገራት እንዲያሸሹ (Flight to Safety) በር ሊከፍት ይችላል።
6 months ago
መንግሥት ተጨማሪ ታክሶችን ሊጥል ነው ተባለ።
የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ አስተዳደር ወደ ስልጣን ከመጣ በኋላ ከደረጋቸው ለውጦች አንዱና በተፅዕኖው የበርካታ ዜጎችን ሕይወት የሚነካው የኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሀ ግብር ነው።
የአለም የገንዘብ ድርጅትን ቅድመ ሁኔታዎች የተከተለውንና መንግስት “ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ” ሲል የጠራው ፕሮግራም በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ2019 ተጀምሮ የነበረ ቢሆንም በትግራዩ ጦርነት ሳቢያ ተጓትቶ የሁለተኛውና “የተሟላ” ነው የተባለው መርሀ ግብር በ2024 (ሐምሌ 2016) ተጀምሯል።
ይህን ማሻሻያ በተመለከተ የአይኤምኤፍ (IMF) ከሰሞኑ በሂደቱ ላይ ጥልቅ ግምገማ አድርጓል።
ከኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት ጋር በዝግ ባደረገው ውይይት የተነሱ ፍሬ ሐሳቦች፤ የተወሰዱ እርምጃዎችና ወደፊት የተያዙ ዕቅዶች ተዘርዝረዋል።
ዋዜማ ራድዮ ተመለከትኩት ባለው የIMF ሪፖርት መሰረት መንግሥት አዳዲስ ታክሶችን ለመጣል ተዘጋጅቷል።
የገንዘብ ሚንስትሩ አህመድ ሺዴ ለIMF ዋና ዳይሬክተር ባለፈው ወር የጻፉት ደብዳቤም በዚህ የIMF ሰነድ ውስጥ ተካቷል፡፡
ደብዳቤው እንደሚለው መንግሥት ብዙ ዓይነት ታክሶችን ለመጣል እያሰበ ነው፡፡
ከእነዚህም አንዱ የተሽከርካሪ ባለቤትነት ግብር ሪፎርም ነው፤ ክልሎችና ፌደራል መንግስት ይሄን ግብር በሚሰበስቡበት ሁኔታ ላይ በቅርቡ በፓርላማ ምክክር እንደሚደረግም ሰነዱ ይገልጻል፡፡
የመንግሥት ገቢ ማሰባሰብን በተመለከተ IMF ባዘዘው መሠረት፤ መንግሥት በነዳጅ፣ ኤሌክትሪክ፣ ቴሌ፣ ማዳበሪያና ሌሎች የሚያደርገውን ድጐማ በማንሳት የመንግሥት ገቢን ሲያሳብጥ የሕዝቡን ኑሮ እያጎሳቆለ ይገኛል፡፡
seledadotio
seledadotio
የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ አስተዳደር ወደ ስልጣን ከመጣ በኋላ ከደረጋቸው ለውጦች አንዱና በተፅዕኖው የበርካታ ዜጎችን ሕይወት የሚነካው የኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሀ ግብር ነው።
የአለም የገንዘብ ድርጅትን ቅድመ ሁኔታዎች የተከተለውንና መንግስት “ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ” ሲል የጠራው ፕሮግራም በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ2019 ተጀምሮ የነበረ ቢሆንም በትግራዩ ጦርነት ሳቢያ ተጓትቶ የሁለተኛውና “የተሟላ” ነው የተባለው መርሀ ግብር በ2024 (ሐምሌ 2016) ተጀምሯል።
ይህን ማሻሻያ በተመለከተ የአይኤምኤፍ (IMF) ከሰሞኑ በሂደቱ ላይ ጥልቅ ግምገማ አድርጓል።
ከኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት ጋር በዝግ ባደረገው ውይይት የተነሱ ፍሬ ሐሳቦች፤ የተወሰዱ እርምጃዎችና ወደፊት የተያዙ ዕቅዶች ተዘርዝረዋል።
ዋዜማ ራድዮ ተመለከትኩት ባለው የIMF ሪፖርት መሰረት መንግሥት አዳዲስ ታክሶችን ለመጣል ተዘጋጅቷል።
የገንዘብ ሚንስትሩ አህመድ ሺዴ ለIMF ዋና ዳይሬክተር ባለፈው ወር የጻፉት ደብዳቤም በዚህ የIMF ሰነድ ውስጥ ተካቷል፡፡
ደብዳቤው እንደሚለው መንግሥት ብዙ ዓይነት ታክሶችን ለመጣል እያሰበ ነው፡፡
ከእነዚህም አንዱ የተሽከርካሪ ባለቤትነት ግብር ሪፎርም ነው፤ ክልሎችና ፌደራል መንግስት ይሄን ግብር በሚሰበስቡበት ሁኔታ ላይ በቅርቡ በፓርላማ ምክክር እንደሚደረግም ሰነዱ ይገልጻል፡፡
የመንግሥት ገቢ ማሰባሰብን በተመለከተ IMF ባዘዘው መሠረት፤ መንግሥት በነዳጅ፣ ኤሌክትሪክ፣ ቴሌ፣ ማዳበሪያና ሌሎች የሚያደርገውን ድጐማ በማንሳት የመንግሥት ገቢን ሲያሳብጥ የሕዝቡን ኑሮ እያጎሳቆለ ይገኛል፡፡
seledadotio
seledadotio
6 months ago
⚖️ የኢትዮጵያ የዩሮቦንድ እዳ ክርክር ወደ ለንደን ፍርድ ቤት ሊያመራ ነው፡ ለአገሪቱ ኢኮኖሚ ምን አንድምታ አለው?
ኢትዮጵያ ያለባትን የ1 ቢሊዮን ዶላር የዩሮቦንድ እዳ ለማሻሻል ከግል አበዳሪዎች ጋር ስታደርግ የነበረው ድርድር ባለመሳካቱ፣ ጉዳዩ ወደ ለንደን ፍርድ ቤት ሊያመራ መሆኑ ተሰምቷል።
ይህ ክርክር አገሪቱ ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ጋር የጀመረችውን የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የብድር ሽግሽግ ሂደት ሊያጓትት ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል።
ዋናው የክርክር ነጥብ ምንድነው?
የኢትዮጵያ መንግሥት እና የግል አበዳሪዎች በጥር ወር መጀመሪያ ላይ የ15% ቅናሽ (Haircut) የሚያካትት ስምምነት ላይ ደርሰው የነበረ ቢሆንም፣ የፓሪስ ክለብን ጨምሮ የመንግሥት አበዳሪዎች ኮሚቴ (OCC) ስምምነቱን ውድቅ አድርጎታል።
ምክንያቱ፦ "የአበዳሪዎች እኩልነት" (Comparability of Treatment) የሚባለውን መርህ ይጥሳል። የመንግሥት አበዳሪዎች እንደሚሉት፣ የቀረበው ስምምነት ለግል አበዳሪዎች ከእነሱ በበለጠ የተሻለ ጥቅም ይሰጣል።
የቦንድ ባለቤቶች ምላሽ፦ የግል አበዳሪዎቹ በበኩላቸው "መንግሥት በቅን ልቦና አልተደራደረም" በሚል ጉዳዩን ወደ ለንደን ፍርድ ቤት እንደሚወስዱት አስታውቀዋል።
📊 የኢትዮጵያ እዳ በቁጥር (እስከ ሰኔ 2024 የነበረው መረጃ)
የኢትዮጵያ አጠቃላይ የውጭ እዳ 28.9 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን፣ ስብጥሩም የሚከተለው ነው፦
ባለብዙ ወገን አበዳሪዎች (World Bank, IMF ወዘተ)፦ 52%
የመንግሥት የሁለትዮሽ አበዳሪዎች (ቻይና፣ ፈረንሳይ ወዘተ)፦ 28%
የግል አበዳሪዎች (ዩሮቦንድን ጨምሮ)፦ 20%
የሌሎች አገራት ተሞክሮ፡ ዛምቢያ እና ስሪላንካ
ኢትዮጵያ አሁን የገጠማት ፈተና ከዚህ ቀደም ሌሎች አገራት ካለፉበት ሂደት ጋር ይመሳሰላል፦
የዛምቢያ ተሞክሮ ፦ ዛምቢያ እዳዋን ለማሽጋሸግ ለሦስት ዓመታት ያህል ስትታገል ቆይታለች። ልክ እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ፣ በግል አበዳሪዎች እና በመንግሥት አበዳሪዎች (በተለይ ቻይና) መካከል በነበረው "እኩልነት" ክርክር ምክንያት ሂደቱ ተጓትቶ ነበር። ዛምቢያ ስምምነት ላይ የደረሰችው የግል አበዳሪዎች የአገሪቱ ኢኮኖሚ ሲያድግ ተጨማሪ ክፍያ የሚያገኙበትን (Value Recovery Instrument) መካኒዝም ካካተቱ በኋላ ነው።
የስሪላንካ ተሞክሮ ፦ ስሪላንካ በG20 የጋራ ማዕቀፍ (Common Framework) ውስጥ ባለመሆኗ በራሷ ድርድር ስታደርግ ቆይታለች። ይሁን እንጂ የግል አበዳሪዎች በፍርድ ቤት ክስ መመስረታቸው አገሪቱ ከአይ ኤም ኤፍ (IMF) የምታገኘው የገንዘብ ድጋፍ እንዲዘገይ አድርጎባታል።
⚠️ ሊከሰቱ የሚችሉ አደጋዎች
የIMF ድጋፍ መጓተት፦ በፍርድ ቤት የሚደረግ ረጅም ክርክር አይ ኤም ኤፍ ለኢትዮጵያ የሚሰጠውን የገንዘብ ድጋፍ (EFF) ቀጣይ ምዕራፎች ሊያስተጓጉል ይችላል።
የገበያ መገለል፦ ክርክሩ እስካልተፈታ ድረስ ኢትዮጵያ ወደ ዓለም አቀፍ የገንዘብ ገበያ ተመልሳ ተጨማሪ ብድር ለማግኘት ትቸገራለች።
የበጀት ጫና፦ ለትምህርት፣ ለጤና እና ለልማት መዋል ያለበት የውጭ ምንዛሬ ለእዳ ክፍያ እንዲውል ጫና ሊፈጥር ይችላል።
ኢትዮጵያ ያለባትን የ1 ቢሊዮን ዶላር የዩሮቦንድ እዳ ለማሻሻል ከግል አበዳሪዎች ጋር ስታደርግ የነበረው ድርድር ባለመሳካቱ፣ ጉዳዩ ወደ ለንደን ፍርድ ቤት ሊያመራ መሆኑ ተሰምቷል።
ይህ ክርክር አገሪቱ ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ጋር የጀመረችውን የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የብድር ሽግሽግ ሂደት ሊያጓትት ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል።
ዋናው የክርክር ነጥብ ምንድነው?
የኢትዮጵያ መንግሥት እና የግል አበዳሪዎች በጥር ወር መጀመሪያ ላይ የ15% ቅናሽ (Haircut) የሚያካትት ስምምነት ላይ ደርሰው የነበረ ቢሆንም፣ የፓሪስ ክለብን ጨምሮ የመንግሥት አበዳሪዎች ኮሚቴ (OCC) ስምምነቱን ውድቅ አድርጎታል።
ምክንያቱ፦ "የአበዳሪዎች እኩልነት" (Comparability of Treatment) የሚባለውን መርህ ይጥሳል። የመንግሥት አበዳሪዎች እንደሚሉት፣ የቀረበው ስምምነት ለግል አበዳሪዎች ከእነሱ በበለጠ የተሻለ ጥቅም ይሰጣል።
የቦንድ ባለቤቶች ምላሽ፦ የግል አበዳሪዎቹ በበኩላቸው "መንግሥት በቅን ልቦና አልተደራደረም" በሚል ጉዳዩን ወደ ለንደን ፍርድ ቤት እንደሚወስዱት አስታውቀዋል።
📊 የኢትዮጵያ እዳ በቁጥር (እስከ ሰኔ 2024 የነበረው መረጃ)
የኢትዮጵያ አጠቃላይ የውጭ እዳ 28.9 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን፣ ስብጥሩም የሚከተለው ነው፦
ባለብዙ ወገን አበዳሪዎች (World Bank, IMF ወዘተ)፦ 52%
የመንግሥት የሁለትዮሽ አበዳሪዎች (ቻይና፣ ፈረንሳይ ወዘተ)፦ 28%
የግል አበዳሪዎች (ዩሮቦንድን ጨምሮ)፦ 20%
የሌሎች አገራት ተሞክሮ፡ ዛምቢያ እና ስሪላንካ
ኢትዮጵያ አሁን የገጠማት ፈተና ከዚህ ቀደም ሌሎች አገራት ካለፉበት ሂደት ጋር ይመሳሰላል፦
የዛምቢያ ተሞክሮ ፦ ዛምቢያ እዳዋን ለማሽጋሸግ ለሦስት ዓመታት ያህል ስትታገል ቆይታለች። ልክ እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ፣ በግል አበዳሪዎች እና በመንግሥት አበዳሪዎች (በተለይ ቻይና) መካከል በነበረው "እኩልነት" ክርክር ምክንያት ሂደቱ ተጓትቶ ነበር። ዛምቢያ ስምምነት ላይ የደረሰችው የግል አበዳሪዎች የአገሪቱ ኢኮኖሚ ሲያድግ ተጨማሪ ክፍያ የሚያገኙበትን (Value Recovery Instrument) መካኒዝም ካካተቱ በኋላ ነው።
የስሪላንካ ተሞክሮ ፦ ስሪላንካ በG20 የጋራ ማዕቀፍ (Common Framework) ውስጥ ባለመሆኗ በራሷ ድርድር ስታደርግ ቆይታለች። ይሁን እንጂ የግል አበዳሪዎች በፍርድ ቤት ክስ መመስረታቸው አገሪቱ ከአይ ኤም ኤፍ (IMF) የምታገኘው የገንዘብ ድጋፍ እንዲዘገይ አድርጎባታል።
⚠️ ሊከሰቱ የሚችሉ አደጋዎች
የIMF ድጋፍ መጓተት፦ በፍርድ ቤት የሚደረግ ረጅም ክርክር አይ ኤም ኤፍ ለኢትዮጵያ የሚሰጠውን የገንዘብ ድጋፍ (EFF) ቀጣይ ምዕራፎች ሊያስተጓጉል ይችላል።
የገበያ መገለል፦ ክርክሩ እስካልተፈታ ድረስ ኢትዮጵያ ወደ ዓለም አቀፍ የገንዘብ ገበያ ተመልሳ ተጨማሪ ብድር ለማግኘት ትቸገራለች።
የበጀት ጫና፦ ለትምህርት፣ ለጤና እና ለልማት መዋል ያለበት የውጭ ምንዛሬ ለእዳ ክፍያ እንዲውል ጫና ሊፈጥር ይችላል።
Sponsored by
Surafel
7 months ago
ታላቁ የህዳሴ ግድብ… በጥንቃቄ ሊያዝ የሚገባው ጉዳይ!
በክቡር ገና የተፃፈ
ዶናልድ ትራምፕ መጽሐፍ ቅዱስን ጨብጠው ለሁለተኛ ጊዜ ቃለ መሃላ ከፈጸሙ አንድ ዓመት ሞላቸው። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የድሮው በህግና በደንብ የሚመራው ዓለም አቀፋዊ ሥርዓት በዝምታ መድረኩን ለቆ የወጣ ይመስላል።
ጃንዋሪ 20 ቀን 2025 (ጥር 12 ቀን 2017 ዓ.ም.) የተከናወነው የፕሬዝዳንቱ በዓለ ሲመት ከበዓልነት ባለፈ አንድ ትልቅ አዋጅ ነበረ።
“አሜሪካ ትቅደም!” (America First) የሚለው የ47ኛው ፕሬዝዳንት መፈክር ትርጉሙ ግልፅ ነው። አሜሪካ አንድን ነገር ከፈለገች ትወስደዋለች፤ ደንቦቹ ካልተመቿት ደግሞ ትቀዳቸዋለች።
አሁን ደግሞ የዓባይ ወንዝ በነዚህ “አዳዲስ ህጎች” ኢላማ ውስጥ ገብቷል።
የትራምፕ ደብዳቤ እና የ“ሽምግልና” ትርጉም
ከጥቂት ቀናት በፊት ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለግብፁ ፕሬዝዳንት አብደል ፈታህ ኤል-ሲሲ የፃፉት ደብዳቤ በይፋ ወጥቷል። የደብዳቤው ቃና ወዳጃዊ ቢመስልም መልዕክቱ ግን የሚያሰጋ ነው። ትራምፕ የአፍሪካ አገራት መፍታት ያልቻሉትን የህዳሴ ግድብ ውዝግብ እኔ “እፈታዋለሁ” ብለዋል።
ነገር ግን ባለፉት 12 ወራት እንደተማርነው፣ በትራምፕ ዓለም ውስጥ “ሽምግልና” ማለት በእኩልነት ላይ የተመሠረተ ውይይት አይደለም። በዓለም አቀፍ ህግ ወይም በተባበሩት መንግስታት ስምምነቶች ላይ የተመሰረተ ሂደትም አይደለም።
ሽምግልናው “ድርድር” (Deal) ነው። ወይ የቀረበልህን ትቀበላለህ፣ ካልሆነ ግን ሌላ የምታጣው ነገር ይኖራል።
አንድ ታዋቂ ተንታኝ በቅርቡ እንደፃፈው፦
“በትራምፕ ዘመን ዓለም አቀፍ ህግ የሚባል ነገር የለም፤ የአሜሪካን ፍላጎት የሚገታ ምንም ዓይነት ገደብ እንደሌለ በግልፅ እየታየ ነው።”
ስለዚህ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት የዓባይን ጉዳይ እፈታለሁ ሲሉ፣ “መፍትሔው የማን ነው?” ብሎ መጠየቅ የግድ ይላል።
የግድቡ ባለቤት ማን ነው?
ታላቁ የህዳሴ ግድብ በአሜሪካ እርዳታ ወይም በአይ ኤም ኤፍ (IMF) ብድር የተገነባ አይደለም። በብራሰልስ ወይም በቤጂንግ የታቀደም አይደለም። ግድቡ በኢትዮጵያውያን እጅ፣ በኢትዮጵያውያን ላብ እና በኢትዮጵያውያን ጥሪት የተገነባ ነው። ከምርቱ ቀንሶ የሰጠው ገበሬ፤ ከወርሃዊ ደሞዟ ቀንሳ የላከችው ነርስ፤
ስለ ብርሃንና ስለ ውሃ የሚዘምሩ ህፃናት…
ይህ ግድብ የኤሌክትሪክ ማመንጫ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያውያን የራስን በራስ የማስተዳደር (Self-reliance) ታላቅ ሀውልት ነው። አሁን ግን የዓለማችን ኃያል ሀገር “ግድቡ እንዴት ጥቅም ላይ መዋል እንዳለበት እኔ እወስናለሁ” እያለን ነው።
የአቅም እንጂ የህግ ጉዳይ መሆን አቁሟል
ይህ ጉዳይ አሁን ስለ ውሃ ብቻ አይደለም። ጉዳዩ ስለ ሉዓላዊነት እና ስለ ቅድመ-ሁኔታ ነው። ኢትዮጵያ የራሷን የወደፊት ዕጣ ፈንታ በራሷ ትወስናለች ወይስ በሌላ ሰው የቼዝ ጠረጴዛ ላይ ትጫወታለች? የሚል ጥያቄ ነው።
ዓለም ተለውጧል። በአንድ ወቅት ዓለም አቀፍ ህግ አገራትን የሚያስተሳስር ሰንሰለት ነበረ። ያ ዘመን አብቅቷል። በቬንዙዌላ፣ በግሪንላንድ፣ በታይዋንና በዩክሬን ያየነው ይሄንኑ ነው። አሁን ደግሞ በዓባይ ላይ እያየነው ነው። ኃይል የህግን ቦታ ሲተካ ዲፕሎማሲ ተውኔት ይሆናል፤ ስምምነቶች ደግሞ የመድረክ ጌጥ ብቻ ይሆናሉ።
ኢትዮጵያ ምን ማድረግ አለባት?
በፈገግታ እጅ መስጠት? ወይስ ለታላቁ ግዛት (Empire) ጣልቃ ገብነት ምስጋና ማቅረብ? በፍጹም! ይልቁንም ድምፃችንን ከፍ አድርገን አንድነታችንን ማጠናከር አለብን። በጩኸት ሳይሆን በሚከተሉት ግልፅ ነጥቦች፦
ግድቡ የኢትዮጵያውያን ሀብት ነው፦ የውጭ ካፒታል ግድቡን በባለቤትነት የመምራት መብት የለውም።
ፍትሃዊ ተጠቃሚነት መብት ነው፦ የውሃ አጠቃቀም የማንም ችሮታ ሳይሆን ተፈጥሯዊ መብት ነው።
የአፍሪካ መፍትሔ ለአፍሪካ፦ ይህ አማራጭ ሳይሆን መሰረት መሆን ያለበት ጉዳይ ነው።
ይህ ግድብ ስጦታ ወይም ምፅዋት አይደለም፤ የኢትዮጵያ የክብር መግለጫ ነው። ስለዚህ ኢትዮጵያ በዋሽንግተን በዝግ በር ለሚበሰል ማንኛውም “መፍትሔ” መንበርከክ የለባትም።
መልዕክት ለአፍሪካውያን
ውድ አንባቢዎች፣ ይህ ጉዳይ የኢትዮጵያ ብቻ አይደለም። ዛሬ ስለ ውሃ ከሆነ፣ ነገ ስለ ማዕድናት፣ ስለ ንግድ ወይም ስለ መሬት ሊሆን ይችላል። አፍሪካውያን እጣ ፈንታቸውን በራሳቸው የመወሰን መብታቸውን ለማስከበር በፅኑ መቆም አለባቸው።
ዓባይ የሚፈሰው በአሜሪካ ፈቃድ አይደለም፤ የህዳሴው ግድብም የቆመው በአሜሪካ ይሁንታ አይደለም። ኢትዮጵያ የራሷን ሀብት በማልማቷ ለማንም አታጎበድድም።
በመጨረሻም፣ ጉዳዩ ስለ ግድቡ ብቻ አይደለም፤ ስለ ክብርና ስለ ሉዓላዊነት ነው። ኃያላን “ትክክለኛውን” ነገር በጉልበት ለመወሰን በሚሞክሩበት በዚህ ዓለም፣ እራሳችንን እንዲህ ብለን መጠየቅ አለብን፦
ፍትሃዊነትን የሚለካው ማነው?
“ኃላፊነት የተሞላበት” የሚለውን ቃል ትርጉም የሚሰጠው ማነው?
ዳኛው ራሱ ተጫዋች ሲሆንስ ምን ይከሰታል?
ለነዚህ ጥያቄዎች የምንሰጠው ምላሽ ለኢትዮጵያም ሆነ ለአፍሪካ የወደፊት ህልውና ወሳኝ ነው።
በክቡር ገና የተፃፈ
ዶናልድ ትራምፕ መጽሐፍ ቅዱስን ጨብጠው ለሁለተኛ ጊዜ ቃለ መሃላ ከፈጸሙ አንድ ዓመት ሞላቸው። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የድሮው በህግና በደንብ የሚመራው ዓለም አቀፋዊ ሥርዓት በዝምታ መድረኩን ለቆ የወጣ ይመስላል።
ጃንዋሪ 20 ቀን 2025 (ጥር 12 ቀን 2017 ዓ.ም.) የተከናወነው የፕሬዝዳንቱ በዓለ ሲመት ከበዓልነት ባለፈ አንድ ትልቅ አዋጅ ነበረ።
“አሜሪካ ትቅደም!” (America First) የሚለው የ47ኛው ፕሬዝዳንት መፈክር ትርጉሙ ግልፅ ነው። አሜሪካ አንድን ነገር ከፈለገች ትወስደዋለች፤ ደንቦቹ ካልተመቿት ደግሞ ትቀዳቸዋለች።
አሁን ደግሞ የዓባይ ወንዝ በነዚህ “አዳዲስ ህጎች” ኢላማ ውስጥ ገብቷል።
የትራምፕ ደብዳቤ እና የ“ሽምግልና” ትርጉም
ከጥቂት ቀናት በፊት ፕሬዝዳንት ትራምፕ ለግብፁ ፕሬዝዳንት አብደል ፈታህ ኤል-ሲሲ የፃፉት ደብዳቤ በይፋ ወጥቷል። የደብዳቤው ቃና ወዳጃዊ ቢመስልም መልዕክቱ ግን የሚያሰጋ ነው። ትራምፕ የአፍሪካ አገራት መፍታት ያልቻሉትን የህዳሴ ግድብ ውዝግብ እኔ “እፈታዋለሁ” ብለዋል።
ነገር ግን ባለፉት 12 ወራት እንደተማርነው፣ በትራምፕ ዓለም ውስጥ “ሽምግልና” ማለት በእኩልነት ላይ የተመሠረተ ውይይት አይደለም። በዓለም አቀፍ ህግ ወይም በተባበሩት መንግስታት ስምምነቶች ላይ የተመሰረተ ሂደትም አይደለም።
ሽምግልናው “ድርድር” (Deal) ነው። ወይ የቀረበልህን ትቀበላለህ፣ ካልሆነ ግን ሌላ የምታጣው ነገር ይኖራል።
አንድ ታዋቂ ተንታኝ በቅርቡ እንደፃፈው፦
“በትራምፕ ዘመን ዓለም አቀፍ ህግ የሚባል ነገር የለም፤ የአሜሪካን ፍላጎት የሚገታ ምንም ዓይነት ገደብ እንደሌለ በግልፅ እየታየ ነው።”
ስለዚህ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት የዓባይን ጉዳይ እፈታለሁ ሲሉ፣ “መፍትሔው የማን ነው?” ብሎ መጠየቅ የግድ ይላል።
የግድቡ ባለቤት ማን ነው?
ታላቁ የህዳሴ ግድብ በአሜሪካ እርዳታ ወይም በአይ ኤም ኤፍ (IMF) ብድር የተገነባ አይደለም። በብራሰልስ ወይም በቤጂንግ የታቀደም አይደለም። ግድቡ በኢትዮጵያውያን እጅ፣ በኢትዮጵያውያን ላብ እና በኢትዮጵያውያን ጥሪት የተገነባ ነው። ከምርቱ ቀንሶ የሰጠው ገበሬ፤ ከወርሃዊ ደሞዟ ቀንሳ የላከችው ነርስ፤
ስለ ብርሃንና ስለ ውሃ የሚዘምሩ ህፃናት…
ይህ ግድብ የኤሌክትሪክ ማመንጫ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያውያን የራስን በራስ የማስተዳደር (Self-reliance) ታላቅ ሀውልት ነው። አሁን ግን የዓለማችን ኃያል ሀገር “ግድቡ እንዴት ጥቅም ላይ መዋል እንዳለበት እኔ እወስናለሁ” እያለን ነው።
የአቅም እንጂ የህግ ጉዳይ መሆን አቁሟል
ይህ ጉዳይ አሁን ስለ ውሃ ብቻ አይደለም። ጉዳዩ ስለ ሉዓላዊነት እና ስለ ቅድመ-ሁኔታ ነው። ኢትዮጵያ የራሷን የወደፊት ዕጣ ፈንታ በራሷ ትወስናለች ወይስ በሌላ ሰው የቼዝ ጠረጴዛ ላይ ትጫወታለች? የሚል ጥያቄ ነው።
ዓለም ተለውጧል። በአንድ ወቅት ዓለም አቀፍ ህግ አገራትን የሚያስተሳስር ሰንሰለት ነበረ። ያ ዘመን አብቅቷል። በቬንዙዌላ፣ በግሪንላንድ፣ በታይዋንና በዩክሬን ያየነው ይሄንኑ ነው። አሁን ደግሞ በዓባይ ላይ እያየነው ነው። ኃይል የህግን ቦታ ሲተካ ዲፕሎማሲ ተውኔት ይሆናል፤ ስምምነቶች ደግሞ የመድረክ ጌጥ ብቻ ይሆናሉ።
ኢትዮጵያ ምን ማድረግ አለባት?
በፈገግታ እጅ መስጠት? ወይስ ለታላቁ ግዛት (Empire) ጣልቃ ገብነት ምስጋና ማቅረብ? በፍጹም! ይልቁንም ድምፃችንን ከፍ አድርገን አንድነታችንን ማጠናከር አለብን። በጩኸት ሳይሆን በሚከተሉት ግልፅ ነጥቦች፦
ግድቡ የኢትዮጵያውያን ሀብት ነው፦ የውጭ ካፒታል ግድቡን በባለቤትነት የመምራት መብት የለውም።
ፍትሃዊ ተጠቃሚነት መብት ነው፦ የውሃ አጠቃቀም የማንም ችሮታ ሳይሆን ተፈጥሯዊ መብት ነው።
የአፍሪካ መፍትሔ ለአፍሪካ፦ ይህ አማራጭ ሳይሆን መሰረት መሆን ያለበት ጉዳይ ነው።
ይህ ግድብ ስጦታ ወይም ምፅዋት አይደለም፤ የኢትዮጵያ የክብር መግለጫ ነው። ስለዚህ ኢትዮጵያ በዋሽንግተን በዝግ በር ለሚበሰል ማንኛውም “መፍትሔ” መንበርከክ የለባትም።
መልዕክት ለአፍሪካውያን
ውድ አንባቢዎች፣ ይህ ጉዳይ የኢትዮጵያ ብቻ አይደለም። ዛሬ ስለ ውሃ ከሆነ፣ ነገ ስለ ማዕድናት፣ ስለ ንግድ ወይም ስለ መሬት ሊሆን ይችላል። አፍሪካውያን እጣ ፈንታቸውን በራሳቸው የመወሰን መብታቸውን ለማስከበር በፅኑ መቆም አለባቸው።
ዓባይ የሚፈሰው በአሜሪካ ፈቃድ አይደለም፤ የህዳሴው ግድብም የቆመው በአሜሪካ ይሁንታ አይደለም። ኢትዮጵያ የራሷን ሀብት በማልማቷ ለማንም አታጎበድድም።
በመጨረሻም፣ ጉዳዩ ስለ ግድቡ ብቻ አይደለም፤ ስለ ክብርና ስለ ሉዓላዊነት ነው። ኃያላን “ትክክለኛውን” ነገር በጉልበት ለመወሰን በሚሞክሩበት በዚህ ዓለም፣ እራሳችንን እንዲህ ብለን መጠየቅ አለብን፦
ፍትሃዊነትን የሚለካው ማነው?
“ኃላፊነት የተሞላበት” የሚለውን ቃል ትርጉም የሚሰጠው ማነው?
ዳኛው ራሱ ተጫዋች ሲሆንስ ምን ይከሰታል?
ለነዚህ ጥያቄዎች የምንሰጠው ምላሽ ለኢትዮጵያም ሆነ ለአፍሪካ የወደፊት ህልውና ወሳኝ ነው።
7 months ago
ከ1 ቢሊዮን ወደ 850 ሚሊዮን ዶላር፦ የኢትዮጵያ የዩሮ ቦንድ እዳ እንዲቀንስ ስምምነት ተደረሰ
ኢትዮጵያ ከዩሮ ቦንድ አበዳሪዎች ጋር ስታደርገው የነበረው የብድር ሽግሽግ ድርድር ስኬታማ ውጤት ማስመዝገቡ የተገለጸ ሲሆን፣ በመሰረታዊ ነጥቦች ላይ በተደረሰው ስምምነት መሰረት የሀገሪቱ አጠቃላይ የዩሮ ቦንድ እዳ መጠን በ15 በመቶ ወይም በ150 ሚሊዮን ዶላር እንዲቀንስ ተደርጓል።
ዓለም አቀፍ ጠበቆችን ቀጥራ ከአበዳሪዎች ጋር ስትደራደር የቆየችው ኢትዮጵያ፣ የ1 ቢሊዮን ዶላር እዳ እንዲሸጋሸግላት ባቀረበችው ጥያቄ ላይ ስምምነት ላይ መደረሱን የድርድሩ ሰነድ የሚያሳይ ሲሆን ይህም ለሀገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ትልቅ እመርታ ተደርጎ ተወስዷል።
በስምምነቱ መሰረት ዋናው የብድር መጠን (Haircut) ተደርጎለት ወደ 850 ሚሊዮን ዶላር ዝቅ እንዲል የተወሰነ ሲሆን፣ ይህ እዳ እስከ 2020 የኢትዮጵያ በጀት ዓመት ተከፍሎ እንዲጠናቀቅ ታቅዷል።
በተጨማሪም ቀደም ሲል በሦስት ዙር መከፈል የነበረበትና ሳይከፈል በመቆየቱ ኢትዮጵያን ለ "ቴክኒካዊ ውድቀት" (Technical Default) ዳርጓት የነበረው የ99 ሚሊዮን ዶላር የወለድ እዳ፣ አሁን ላይ ሀገሪቱ በአንድ ጊዜ ለመክፈል መስማማቷ በሰነዱ ላይ ሰፍሯል።
የረጅም ጊዜ ክፍያውን በተመለከተ፣ በቀጣዮቹ 8 ዓመታት ውስጥ የተሻለ የወጪ ንግድ ገቢ ከተገኘ ከገቢው 2.5 በመቶ በመቀነስ በዓመት 180 ሚሊዮን ዶላር እንድትከፍል ተወስኗል።
ይህ አሃዝ አበዳሪዎች ቀደም ሲል ከጠየቁት የ4.75 በመቶ የክፍያ ምጣኔ በእጅጉ የቀነሰ ሲሆን፣ ይህም በIMF የኢኮኖሚ ግምገማዎች ላይ ተመስርቶ የቀረበ የክፍያ አማራጭ መሆኑ ታውቋል። ስምምነቱ በይፋ ሥራ ላይ እንዲውልም የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት
(IMF) የመጨረሻ ይሁንታ እየተጠበቀ ይገኛል።
ይህ የብድር ሽግሽግ ስምምነት ኢትዮጵያ ወደ ዓለም አቀፍ የገንዘብ ገበያ በድጋሚ ለመመለስ ለምታደርገው ጥረት ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል ተብሏል።
የእዳ ጫናው መቀነሱ እንደ Fitch እና S&P ያሉ ተቋማት ለሀገሪቱ የሚሰጡትን የክሬዲት ደረጃ ሊያሻሽለው እንደሚችል የሚጠበቅ ሲሆን፣ ይህም በሀገሪቱ ላይ የነበረውን የብድር አለመክፈል ስጋት በመቀነስ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት (FDI) እንዲጨምር ምቹ ሁኔታን ይፈጥራም የሚል ትንበያ ባለሙያዎች ይሰጣሉ።
ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ2014 የገባችበት የ1 ቢሊዮን ዶላር የዩሮ ቦንድ እዳ በታህሳስ 2023 መከፈል የነበረበት ቢሆንም፣ በወቅቱ በነበረው የውጭ ምንዛሬ እጥረት ምክንያት ሳይከፈል መቆየቱ ይታወሳል። ይህ አዲስ ስምምነት ሀገሪቱ ካለባት የብድር ጫና ወጥታ የጀመረችውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ (Macroeconomic Reform) በዘላቂነት ለማስቀጠል የሚረዳ ወሳኝ እርምጃ መሆኑን የድርድሩ ውጤት ያመለክታል።
ኢትዮጵያ ከዩሮ ቦንድ አበዳሪዎች ጋር ስታደርገው የነበረው የብድር ሽግሽግ ድርድር ስኬታማ ውጤት ማስመዝገቡ የተገለጸ ሲሆን፣ በመሰረታዊ ነጥቦች ላይ በተደረሰው ስምምነት መሰረት የሀገሪቱ አጠቃላይ የዩሮ ቦንድ እዳ መጠን በ15 በመቶ ወይም በ150 ሚሊዮን ዶላር እንዲቀንስ ተደርጓል።
ዓለም አቀፍ ጠበቆችን ቀጥራ ከአበዳሪዎች ጋር ስትደራደር የቆየችው ኢትዮጵያ፣ የ1 ቢሊዮን ዶላር እዳ እንዲሸጋሸግላት ባቀረበችው ጥያቄ ላይ ስምምነት ላይ መደረሱን የድርድሩ ሰነድ የሚያሳይ ሲሆን ይህም ለሀገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ትልቅ እመርታ ተደርጎ ተወስዷል።
በስምምነቱ መሰረት ዋናው የብድር መጠን (Haircut) ተደርጎለት ወደ 850 ሚሊዮን ዶላር ዝቅ እንዲል የተወሰነ ሲሆን፣ ይህ እዳ እስከ 2020 የኢትዮጵያ በጀት ዓመት ተከፍሎ እንዲጠናቀቅ ታቅዷል።
በተጨማሪም ቀደም ሲል በሦስት ዙር መከፈል የነበረበትና ሳይከፈል በመቆየቱ ኢትዮጵያን ለ "ቴክኒካዊ ውድቀት" (Technical Default) ዳርጓት የነበረው የ99 ሚሊዮን ዶላር የወለድ እዳ፣ አሁን ላይ ሀገሪቱ በአንድ ጊዜ ለመክፈል መስማማቷ በሰነዱ ላይ ሰፍሯል።
የረጅም ጊዜ ክፍያውን በተመለከተ፣ በቀጣዮቹ 8 ዓመታት ውስጥ የተሻለ የወጪ ንግድ ገቢ ከተገኘ ከገቢው 2.5 በመቶ በመቀነስ በዓመት 180 ሚሊዮን ዶላር እንድትከፍል ተወስኗል።
ይህ አሃዝ አበዳሪዎች ቀደም ሲል ከጠየቁት የ4.75 በመቶ የክፍያ ምጣኔ በእጅጉ የቀነሰ ሲሆን፣ ይህም በIMF የኢኮኖሚ ግምገማዎች ላይ ተመስርቶ የቀረበ የክፍያ አማራጭ መሆኑ ታውቋል። ስምምነቱ በይፋ ሥራ ላይ እንዲውልም የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት
(IMF) የመጨረሻ ይሁንታ እየተጠበቀ ይገኛል።
ይህ የብድር ሽግሽግ ስምምነት ኢትዮጵያ ወደ ዓለም አቀፍ የገንዘብ ገበያ በድጋሚ ለመመለስ ለምታደርገው ጥረት ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል ተብሏል።
የእዳ ጫናው መቀነሱ እንደ Fitch እና S&P ያሉ ተቋማት ለሀገሪቱ የሚሰጡትን የክሬዲት ደረጃ ሊያሻሽለው እንደሚችል የሚጠበቅ ሲሆን፣ ይህም በሀገሪቱ ላይ የነበረውን የብድር አለመክፈል ስጋት በመቀነስ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት (FDI) እንዲጨምር ምቹ ሁኔታን ይፈጥራም የሚል ትንበያ ባለሙያዎች ይሰጣሉ።
ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ2014 የገባችበት የ1 ቢሊዮን ዶላር የዩሮ ቦንድ እዳ በታህሳስ 2023 መከፈል የነበረበት ቢሆንም፣ በወቅቱ በነበረው የውጭ ምንዛሬ እጥረት ምክንያት ሳይከፈል መቆየቱ ይታወሳል። ይህ አዲስ ስምምነት ሀገሪቱ ካለባት የብድር ጫና ወጥታ የጀመረችውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ (Macroeconomic Reform) በዘላቂነት ለማስቀጠል የሚረዳ ወሳኝ እርምጃ መሆኑን የድርድሩ ውጤት ያመለክታል።
7 months ago
አንጋፋው ኢኮኖሚስት አበበ አዕምሮ ሥላሴ ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በጡረታ ሊገለሉ ነው
#ethiopia | በዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ውስጥ ለ32 ዓመታት በተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊነቶች ሲያገለግሉ የቆዩት ኢትዮጵያዊው የምጣኔ ሀብት ባለሙያ አቶ አበበ አዕምሮ ሥላሴ፣ ከሦስት ወራት በኋላ በጡረታ ከኃላፊነታቸው እንደሚገለሉ ተሰማ።
🎓 የሦስት አስርተ ዓመታት የላቀ አገልግሎት
አቶ አበበ ባለፉት 10 ዓመታት የድርጅቱ የአፍሪካ ዲፓርትመንት ዳይሬክተር በመሆን አህጉሪቱን በኢኮኖሚ ፖሊሲ ቀረፃና ትንተና ሲመሩ ቆይተዋል።
በቆይታቸውም፦
* በማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ፣ በፋይናንስና ገንዘብ ነክ ጉዳዮች እንዲሁም በዕዳ ሽግሽግ ላይ ሰፊ ስራዎችን አከናውነዋል።
* በተለይ ከ2008 ጀምሮ የአፍሪካ ክፍልን በመምራት በአህጉሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ አሻራ አሳርፈዋል።
🛡️ አፍሪካን በፈተና ወቅት የመሩት መሪ
የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂየቫ እንደገለጹት፣ አቶ አበበ በተለይ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ፣ በዓለም አቀፍ የዋጋ ግሽበት እና በአህጉሪቱ በነበሩ ግጭቶች ወቅት አፍሪካን ከድርጅቱ ጋር በማስተሳሰር ረገድ የማይተካ ሚና ተጫውተዋል። ከሰሃራ በታች ያሉ ሀገራት የዕዳ ጫናን እንዲቋቋሙ እና ተጨማሪ እርዳታ እንዲያገኙ በማድረግ ረገድም በታማኝነት ማገልገላቸውን ዳይሬክተሯ መስክረዋል።
💡 የታማኝነት እና የሙያ ብቃት ተምሳሌት
ኢኮኖሚስቱ አበበ አዕምሮ ሥላሴ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሚቀረጹ የኢኮኖሚ ፕሮግራሞች በሰጡት ከፍተኛ የሙያ ምክርና ድጋፍ በድርጅቱ አመራሮች ዘንድ ትልቅ አክብሮት አትርፈዋል። ጡረታ መውጣታቸውንም ተከትሎ ክሪስታሊና ጆርጂየቫ ለነበራቸው ቆይታና ለታማኝ አገልግሎታቸው ምስጋናቸውን አቅርበውላቸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#አበበአዕምሮሥላሴ #imf #አፍሪካ #ኢኮኖሚ #ኢትዮጵያ #ጡረታ #ማክሮኢኮኖሚ #abebeselassie #globalfinance
#ethiopia | በዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ውስጥ ለ32 ዓመታት በተለያዩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊነቶች ሲያገለግሉ የቆዩት ኢትዮጵያዊው የምጣኔ ሀብት ባለሙያ አቶ አበበ አዕምሮ ሥላሴ፣ ከሦስት ወራት በኋላ በጡረታ ከኃላፊነታቸው እንደሚገለሉ ተሰማ።
🎓 የሦስት አስርተ ዓመታት የላቀ አገልግሎት
አቶ አበበ ባለፉት 10 ዓመታት የድርጅቱ የአፍሪካ ዲፓርትመንት ዳይሬክተር በመሆን አህጉሪቱን በኢኮኖሚ ፖሊሲ ቀረፃና ትንተና ሲመሩ ቆይተዋል።
በቆይታቸውም፦
* በማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ፣ በፋይናንስና ገንዘብ ነክ ጉዳዮች እንዲሁም በዕዳ ሽግሽግ ላይ ሰፊ ስራዎችን አከናውነዋል።
* በተለይ ከ2008 ጀምሮ የአፍሪካ ክፍልን በመምራት በአህጉሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ አሻራ አሳርፈዋል።
🛡️ አፍሪካን በፈተና ወቅት የመሩት መሪ
የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂየቫ እንደገለጹት፣ አቶ አበበ በተለይ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ፣ በዓለም አቀፍ የዋጋ ግሽበት እና በአህጉሪቱ በነበሩ ግጭቶች ወቅት አፍሪካን ከድርጅቱ ጋር በማስተሳሰር ረገድ የማይተካ ሚና ተጫውተዋል። ከሰሃራ በታች ያሉ ሀገራት የዕዳ ጫናን እንዲቋቋሙ እና ተጨማሪ እርዳታ እንዲያገኙ በማድረግ ረገድም በታማኝነት ማገልገላቸውን ዳይሬክተሯ መስክረዋል።
💡 የታማኝነት እና የሙያ ብቃት ተምሳሌት
ኢኮኖሚስቱ አበበ አዕምሮ ሥላሴ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሚቀረጹ የኢኮኖሚ ፕሮግራሞች በሰጡት ከፍተኛ የሙያ ምክርና ድጋፍ በድርጅቱ አመራሮች ዘንድ ትልቅ አክብሮት አትርፈዋል። ጡረታ መውጣታቸውንም ተከትሎ ክሪስታሊና ጆርጂየቫ ለነበራቸው ቆይታና ለታማኝ አገልግሎታቸው ምስጋናቸውን አቅርበውላቸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#አበበአዕምሮሥላሴ #imf #አፍሪካ #ኢኮኖሚ #ኢትዮጵያ #ጡረታ #ማክሮኢኮኖሚ #abebeselassie #globalfinance
7 months ago
አቶ አበበ አእምሮ ስላሴ ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት በጡረታ ሊሰናበቱ ነው
በዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የአፍሪካ መምሪያ ዳይሬክተር የሆኑት ኢትዮጵያዊው አቶ አበበ አእምሮ ስላሴ፣ ከግንቦት ጀምሮ ኃላፊነታቸውን እንደሚለቁ ተገልጿል።
አቶ አበበ ድርጅቱን በፈረንጆቹ 1994 የተቀላቀሉ ሲሆን፣ ላለፉት 32 ዓመታት በተለያዩ ከፍተኛ የኃላፊነት ቦታዎች አገልግለዋል።
ከ2016 ጀምሮ የድርጅቱ ደግሞ የአፍሪካ መምሪያ ዳይሬክተር በመሆን ሰርተዋል።
በቆይታቸውም አፍሪካ በኮቪድ-19 እና በኢኮኖሚ ቀውስ ወቅት የነበሩባትን ፈተናዎች እንድትወጣ ረድተዋል።
በተለይም ለሰሃራ በታች አፍሪካ የሚሰጠውን ድጋፍ በማሳደግና በቦርዱ ውስጥ የአህጉሪቱ ድምፅ እንዲጎለብት በማድረግ ትልቅ ሚና ተጫውተዋል።
የIMF ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂየቫ፤ አቶ አበበ ላሳዩት ጥንካሬ፣ ስትራቴጂካዊ አመራርና ለድርጅቱ ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የአፍሪካ መምሪያ ዳይሬክተር የሆኑት ኢትዮጵያዊው አቶ አበበ አእምሮ ስላሴ፣ ከግንቦት ጀምሮ ኃላፊነታቸውን እንደሚለቁ ተገልጿል።
አቶ አበበ ድርጅቱን በፈረንጆቹ 1994 የተቀላቀሉ ሲሆን፣ ላለፉት 32 ዓመታት በተለያዩ ከፍተኛ የኃላፊነት ቦታዎች አገልግለዋል።
ከ2016 ጀምሮ የድርጅቱ ደግሞ የአፍሪካ መምሪያ ዳይሬክተር በመሆን ሰርተዋል።
በቆይታቸውም አፍሪካ በኮቪድ-19 እና በኢኮኖሚ ቀውስ ወቅት የነበሩባትን ፈተናዎች እንድትወጣ ረድተዋል።
በተለይም ለሰሃራ በታች አፍሪካ የሚሰጠውን ድጋፍ በማሳደግና በቦርዱ ውስጥ የአህጉሪቱ ድምፅ እንዲጎለብት በማድረግ ትልቅ ሚና ተጫውተዋል።
የIMF ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂየቫ፤ አቶ አበበ ላሳዩት ጥንካሬ፣ ስትራቴጂካዊ አመራርና ለድርጅቱ ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
Comments