10 days ago
ሰበር - የቴዲ አፍሮ ም/ ሥራ አስኪያጅና ቃል አቀባይ፣ ፍርድ ቤት በዋስ እንድትፈታ ትዕዛዝ ቢሰጥም፣ ፖሊስ ግን የአምስት ልጆች እናት የሆነችውን ወ/ሮ ማህሌትን አልለቅም በማለቱ ፍትህ ተጓድሏል። አባት የሌላቸው 5 ህጻናት እናታቸውን በናፍቆት እየጠበቁ ነው፤ እናትም በእስር ቤት በዋይታ ተሞልታለች። ዛሬ 6 ኪሎ በሚገኘው ጠቅላይ ፍርድ ቤት እንዲህ ሆነ!
#ethiopiannews #justice #teddyafro #ethiopiamusic
16 days ago
በአይራብ ዶኔሽን እና በጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን የተዘጋጀው ይፋዊ የዲጂታል ገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ-ግብር ሊካሄድ ነው
📌ተቋማቱ የጋራ ስምምነት ተፈራረሙ
#ethiopia | በአይራብ ዶኔሽን እና በጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን በጋራ የተዘጋጀው ይፋዊ የገቢ ማሰባሰቢያ የመክፈቻ ፕሮግራም በቅርቡ እንደሚካሄድ የተገለጸ ሲሆን፣ ሁለቱ ተቋማትም አብረው ለመሥራት የሚያስችላቸውን የጋራ ስምምነት በይፋ ተፈራርመዋል።
ይህ ልዩ መርሃ-ግብር ደህንነቱ በተጠበቀ፣ ግልጽነት ባለው እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በተደገፉ ዲጂታል የለጋሽነት መፍትሄዎች አማካኝነት፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰብአዊ እና ማህበረሰባዊ እገዛዎችን በዘላቂነት ለመደገፍ ያለመ ስትራቴጂካዊ የገቢ ማሰባሰብ አጋርነት መጀመሩን አብስረዋል።
በዕለቱም አይራብ ዶኔሽን የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ለጋሾች በቴሌብር ሱፐር አፕ እና በአይራብ ዶኔሽን ድረ-ገጽ አማካኝነት በቀላሉና በአስተማማኝ ሁኔታ መዋጮ ማድረግ የሚችሉበትን ምቹ ዲጂታል አሰራር በጉልህ የሚያሳይ ይሆናል።
የአይራብ ቴክ ሶሉሽን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር (AYRAB TECH SOLUTION PLC) መስራች አቶ ቢኒያም ፈቃዱ እና የጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር መሌቻ ሎጄ ህዝቡ እና የሚመለከተው አካል ሁሉ በዚህ ሰብአዊ ስራ ላይ ከጎናቸው እንዲሆንና አጋርነቱን እንዲያጠናክር ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
ጃታኒ አሊ ፋውንዴሽን በአርቆ አሳቢው ሻለቃ ጃታኒ አሊ ማስታወሻነት የተመሰረተ ሲሆን፣ ማህበረሰቡ ራሱን እንዲችል፣ ጠንካራ የሆነ ማህበረሰብ እንዲገነባ እና ዘላቂ ልማት እንዲፈጠር በትምህርት፣ በውሃ፣ በጤና እና በማህበረሰብ አቅም ግንባታ ላይ በትጋት እየሰራ ነው።
ዛሬ የፋውንዴሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚና በተለያዩ ሀገር የሃላፊነት ቦታዎች የሚያገለግሉ ብዙ ግለሰቦች ሻለቃ ጃታኒ አሊ በተቋቋመው ትምህርት ቤት የተማሩ ሲሆን፣ ይህም የፋውንዴሽኑ ትውልድ የሚቀይር ራዕይ ህያው ማስረጃ ነው።
የእርስዎ ድጋፍ አንድ ልጅ እንዲማር፣ አንድ ቤተሰብ ተስፋ እንዲያገኝ እና አንድ ማህበረሰብ በራሱ እግር እንዲቆም ያግዛል።
ዛሬ ይቀላቀሉ ፣ ይደግፉ ፣ዘላቂ ለውጥ ይፍጠሩ። ሲሉ ጥሪያቸውንም አስተላልፈዋል።
እንዲሁም: በቴሌብር ሱፐር አፕ ላይ በሚገኘው አይራብ(AYRAB) አፕ ላይ እና በአይራብ ዶኔሽን ( https://donate.ayrabtech.c... ) ሊንክ በመግባት በቀላሉ በሃገር ውስጥም ይሁን ከሃገር ውጪ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮዽያ ወዳጆች በቀላሉ የፈለጉትን እና የቻሉትን ያህል መለገስ የሚችሉ መሆኑን አሳውቀዋል።
ይህንን ትልቅ ሰብአዊ እቅድ በይፋ ለመጀመር በሚሰናዳው በዚሁ ደማቅ መርሃ-ግብር ላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ በጎ አድራጊዎች፣ የቢዝነስ መሪዎች፣ የሶሻል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ ታዋቂ የኢትዮጵያ ስብዕናዎች እና ከተለያዩ ዘርፎች የተወጣጡ ደጋፊዎች እንደሚገኙ ታውቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia #ayrabdonation #jatanialifoundation #digitalfundraising #techforgood #humanitarianaid #telebirr #addisababa #socialimpact #ethiopiannews
📌ተቋማቱ የጋራ ስምምነት ተፈራረሙ
#ethiopia | በአይራብ ዶኔሽን እና በጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን በጋራ የተዘጋጀው ይፋዊ የገቢ ማሰባሰቢያ የመክፈቻ ፕሮግራም በቅርቡ እንደሚካሄድ የተገለጸ ሲሆን፣ ሁለቱ ተቋማትም አብረው ለመሥራት የሚያስችላቸውን የጋራ ስምምነት በይፋ ተፈራርመዋል።
ይህ ልዩ መርሃ-ግብር ደህንነቱ በተጠበቀ፣ ግልጽነት ባለው እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በተደገፉ ዲጂታል የለጋሽነት መፍትሄዎች አማካኝነት፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰብአዊ እና ማህበረሰባዊ እገዛዎችን በዘላቂነት ለመደገፍ ያለመ ስትራቴጂካዊ የገቢ ማሰባሰብ አጋርነት መጀመሩን አብስረዋል።
በዕለቱም አይራብ ዶኔሽን የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ለጋሾች በቴሌብር ሱፐር አፕ እና በአይራብ ዶኔሽን ድረ-ገጽ አማካኝነት በቀላሉና በአስተማማኝ ሁኔታ መዋጮ ማድረግ የሚችሉበትን ምቹ ዲጂታል አሰራር በጉልህ የሚያሳይ ይሆናል።
የአይራብ ቴክ ሶሉሽን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር (AYRAB TECH SOLUTION PLC) መስራች አቶ ቢኒያም ፈቃዱ እና የጃተኒ አሊ ፋውንዴሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር መሌቻ ሎጄ ህዝቡ እና የሚመለከተው አካል ሁሉ በዚህ ሰብአዊ ስራ ላይ ከጎናቸው እንዲሆንና አጋርነቱን እንዲያጠናክር ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
ጃታኒ አሊ ፋውንዴሽን በአርቆ አሳቢው ሻለቃ ጃታኒ አሊ ማስታወሻነት የተመሰረተ ሲሆን፣ ማህበረሰቡ ራሱን እንዲችል፣ ጠንካራ የሆነ ማህበረሰብ እንዲገነባ እና ዘላቂ ልማት እንዲፈጠር በትምህርት፣ በውሃ፣ በጤና እና በማህበረሰብ አቅም ግንባታ ላይ በትጋት እየሰራ ነው።
ዛሬ የፋውንዴሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚና በተለያዩ ሀገር የሃላፊነት ቦታዎች የሚያገለግሉ ብዙ ግለሰቦች ሻለቃ ጃታኒ አሊ በተቋቋመው ትምህርት ቤት የተማሩ ሲሆን፣ ይህም የፋውንዴሽኑ ትውልድ የሚቀይር ራዕይ ህያው ማስረጃ ነው።
የእርስዎ ድጋፍ አንድ ልጅ እንዲማር፣ አንድ ቤተሰብ ተስፋ እንዲያገኝ እና አንድ ማህበረሰብ በራሱ እግር እንዲቆም ያግዛል።
ዛሬ ይቀላቀሉ ፣ ይደግፉ ፣ዘላቂ ለውጥ ይፍጠሩ። ሲሉ ጥሪያቸውንም አስተላልፈዋል።
እንዲሁም: በቴሌብር ሱፐር አፕ ላይ በሚገኘው አይራብ(AYRAB) አፕ ላይ እና በአይራብ ዶኔሽን ( https://donate.ayrabtech.c... ) ሊንክ በመግባት በቀላሉ በሃገር ውስጥም ይሁን ከሃገር ውጪ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮዽያ ወዳጆች በቀላሉ የፈለጉትን እና የቻሉትን ያህል መለገስ የሚችሉ መሆኑን አሳውቀዋል።
ይህንን ትልቅ ሰብአዊ እቅድ በይፋ ለመጀመር በሚሰናዳው በዚሁ ደማቅ መርሃ-ግብር ላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ በጎ አድራጊዎች፣ የቢዝነስ መሪዎች፣ የሶሻል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች፣ ታዋቂ የኢትዮጵያ ስብዕናዎች እና ከተለያዩ ዘርፎች የተወጣጡ ደጋፊዎች እንደሚገኙ ታውቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia #ayrabdonation #jatanialifoundation #digitalfundraising #techforgood #humanitarianaid #telebirr #addisababa #socialimpact #ethiopiannews
17 days ago
የኢትዮጵያ የቀይ ባህር ባለቤትነት ጥያቄ ከሀገራዊ ህልውና ጋር የተቆራኘ ነው :- የቀድሞው የአሰብ ከንቲባ አቶ ዳንኤል ሊበን
*******
የኢትዮጵያ የቀይ ባህር ባለቤትነት ጥያቄ በስሜት የሚነዳ ሳይሆን የታሪክ መሠረት ያለውና ከሀገራዊ ህልውና ጋር የተቆራኘ መሆኑን የቀድሞው የአሰብ ከተማ ከንቲባ አቶ ዳንኤል ሊበን ገለጹ።
አሰብ ከተማ የኢትዮጵያ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ደም ስር ከመሆኗም ባለፈ፣ የኢትዮጵያ የሉዓላዊነት ምልክት እንደሆነች ይነገራል።
ዛሬ ላይ በይፋ የቀረበው የኢትዮጵያ የቀይ ባህር ባለቤትነት ጥያቄ፣ ከወቅታዊ ስሜት ይልቅ ተጨባጭ የታሪክ መረጃዎችንና የህልውና አጀንዳን መሠረት ያደረገ ነው።
የቀድሞው የአሰብ ከተማ ከንቲባ አቶ ዳንኤል ሊበን ከኢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ የአሰብ የባህር በር ጥያቄ ታሪካዊ እውነታን የተመረኮዘ መሆኑን አብራርተዋል።
እንደ አቶ ዳንኤል ገለጻ፣ አሰብ በወቅቱ በኢትዮጵያ ውስጥ ከነበሩ ግንባር ቀደም ከተሞች አንዷ ከመሆኗም በላይ የሀገሪቱ ዋንኛ የገቢና ወጪ ንግድ ማዕከል በመሆን ለኢኮኖሚ እድገቱ እንደ ጀርባ አጥንት ታገለግል ነበር።
አቶ ዳንኤል የአሰብ ጥያቄ ዛሬ የተፈጠረ ሳይሆን ጥልቅ የታሪክ መሠረት ያለው መሆኑን ሲያስረዱም፤ አሰብ "የአሰብ ራስ-ገዝ አስተዳደር" (Assab Regional Autonomous) ተብላ ትጠራ እንደነበር አስታውሰዋል። ይህ መዋቅር አሰብን ከኤርትራ ራስ-ገዝ አስተዳደር ነጥሎ በቀጥታ ለማዕከላዊ መንግስት ተጠሪ የሚያደርግ ነበር።
የዚህ ራስ-ገዝ አስተዳደር ስፋትም ከምጽዋ አቅራቢያ ጀምሮ እስከ ጅቡቲ ጠረፍ ድረስ ያለውን ሰፊ የባህር ዳርቻ የሚያጠቃልል ነበር ይላሉ።
በ1983 ዓ.ም የመንግስት ለውጥ ሲመጣ የነበረውን ሁኔታ ያስታወሱት አቶ ዳንኤል፤ የከተማዋ ማህበራዊ ሕይወት፣ የትምህርት ሥርዓት እና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ከኢትዮጵያ መሃል ሀገር ጋር ፍጹም የተቆራኘ እንደነበር ገልጸዋል።
በወቅቱ አስመራ የነበሩ ነዋሪዎችም ቢሆኑ "አሰብ ለኢትዮጵያ አገልግሎት ካልሰጠች ለእኛም ፋይዳዋ አነስተኛ ነው" የሚል እምነት እንደነበራቸው ጠቅሰዋል።
በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤት እንድትሆን የሚቀርበው ጥያቄ ወቅታዊና ተገቢ መሆኑ አጠያያቂ አይደለም ብለዋል።
ከተማዋ የኢትዮጵያ የነዳጅ ማጣሪያ እና የትራንስፖርት ደም-ስር ሆና ለዓመታት ማገልገሏ፣ ዛሬ ለሚነሳው ጥያቄ ትልቅ የሞራልና የታሪክ አስረጂ ነው። ይህም የባህር በር ጥያቄው ህጋዊነት፣ ተገቢነት እና ወቅታዊነት የማይናወጥ መሠረት እንዳለው ያረጋግጣል።
በላሉ ኢታላ
#ethiopia #assab #redsea #addisababa #ethiopiannews #history
*******
የኢትዮጵያ የቀይ ባህር ባለቤትነት ጥያቄ በስሜት የሚነዳ ሳይሆን የታሪክ መሠረት ያለውና ከሀገራዊ ህልውና ጋር የተቆራኘ መሆኑን የቀድሞው የአሰብ ከተማ ከንቲባ አቶ ዳንኤል ሊበን ገለጹ።
አሰብ ከተማ የኢትዮጵያ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ደም ስር ከመሆኗም ባለፈ፣ የኢትዮጵያ የሉዓላዊነት ምልክት እንደሆነች ይነገራል።
ዛሬ ላይ በይፋ የቀረበው የኢትዮጵያ የቀይ ባህር ባለቤትነት ጥያቄ፣ ከወቅታዊ ስሜት ይልቅ ተጨባጭ የታሪክ መረጃዎችንና የህልውና አጀንዳን መሠረት ያደረገ ነው።
የቀድሞው የአሰብ ከተማ ከንቲባ አቶ ዳንኤል ሊበን ከኢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ የአሰብ የባህር በር ጥያቄ ታሪካዊ እውነታን የተመረኮዘ መሆኑን አብራርተዋል።
እንደ አቶ ዳንኤል ገለጻ፣ አሰብ በወቅቱ በኢትዮጵያ ውስጥ ከነበሩ ግንባር ቀደም ከተሞች አንዷ ከመሆኗም በላይ የሀገሪቱ ዋንኛ የገቢና ወጪ ንግድ ማዕከል በመሆን ለኢኮኖሚ እድገቱ እንደ ጀርባ አጥንት ታገለግል ነበር።
አቶ ዳንኤል የአሰብ ጥያቄ ዛሬ የተፈጠረ ሳይሆን ጥልቅ የታሪክ መሠረት ያለው መሆኑን ሲያስረዱም፤ አሰብ "የአሰብ ራስ-ገዝ አስተዳደር" (Assab Regional Autonomous) ተብላ ትጠራ እንደነበር አስታውሰዋል። ይህ መዋቅር አሰብን ከኤርትራ ራስ-ገዝ አስተዳደር ነጥሎ በቀጥታ ለማዕከላዊ መንግስት ተጠሪ የሚያደርግ ነበር።
የዚህ ራስ-ገዝ አስተዳደር ስፋትም ከምጽዋ አቅራቢያ ጀምሮ እስከ ጅቡቲ ጠረፍ ድረስ ያለውን ሰፊ የባህር ዳርቻ የሚያጠቃልል ነበር ይላሉ።
በ1983 ዓ.ም የመንግስት ለውጥ ሲመጣ የነበረውን ሁኔታ ያስታወሱት አቶ ዳንኤል፤ የከተማዋ ማህበራዊ ሕይወት፣ የትምህርት ሥርዓት እና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ከኢትዮጵያ መሃል ሀገር ጋር ፍጹም የተቆራኘ እንደነበር ገልጸዋል።
በወቅቱ አስመራ የነበሩ ነዋሪዎችም ቢሆኑ "አሰብ ለኢትዮጵያ አገልግሎት ካልሰጠች ለእኛም ፋይዳዋ አነስተኛ ነው" የሚል እምነት እንደነበራቸው ጠቅሰዋል።
በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤት እንድትሆን የሚቀርበው ጥያቄ ወቅታዊና ተገቢ መሆኑ አጠያያቂ አይደለም ብለዋል።
ከተማዋ የኢትዮጵያ የነዳጅ ማጣሪያ እና የትራንስፖርት ደም-ስር ሆና ለዓመታት ማገልገሏ፣ ዛሬ ለሚነሳው ጥያቄ ትልቅ የሞራልና የታሪክ አስረጂ ነው። ይህም የባህር በር ጥያቄው ህጋዊነት፣ ተገቢነት እና ወቅታዊነት የማይናወጥ መሠረት እንዳለው ያረጋግጣል።
በላሉ ኢታላ
#ethiopia #assab #redsea #addisababa #ethiopiannews #history
17 days ago
🚨 3 ዓመት ሙሉ ያለ ደመወዝ? የኤምባሲው ሰራተኞች በአዲስ አበባ አድማ ሊመቱ ነው! #ethiopia #addisababa #workersrights #ethiopiannews #newsupdate
Sponsored by
Surafel
24 days ago
u1230u1260u122d - u1260u12a2u1275u12eeu1335u12eb u12f5u1295u1260u122d u12a0u1245u122bu1262u12eb u12e8u1231u12f3u1295 u1326u122du1290u1275 u12a0u12f2u1235 u1218u120du12ad u12a5u12e8u12ebu12d8 u1290u12cd! #sudan #ethiopia #sudancrisis #ethiopiannews #geopolitics ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ሰበር - በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ የሱዳን ጦርነት አዲስ መልክ እየያዘ ነው! #sudan #ethiopia #sudancrisis #ethiopiannews #geopolitics
26 days ago
ሰማያዊ ኢኮኖሚ፡ ኢትዮጵያ ወደ ባሕር እየተመለሰች ነው #ebcdotstream #blueeconomy #gerd #የሕዳሴ_ግድብ #ethiopiannews #redsea
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
27 days ago
🚨 ያልተጠበቀ ጉድ! የደብረ ማርቆስ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዜና አቅጣጫውን ቀየረ! የኮሌጁ ፌስቡክ ገፅ በታጣቂዎች እጅ ገብቷል! #ethiopia #debremarkos #ethiopiannews #amhararegion #trendingethiopia
27 days ago
የቴዲ አፍሮ ስዎች በፈተና ላይ! ፖሊስ ተጨማሪ ጊዜ ሊጠይቅባቸው ነው! #teddyafro #ethiopia #ethiopiannews #facebookreels #ethiopianmusic
የቴዲ አፍሮ ስዎች በፈተና ላይ! ፖሊስ ተጨማሪ ጊዜ ሊጠይቅባቸው ነው! #teddyafro #ethiopia #ethiopiannews #facebookreels #ethiopianmusic
Sponsored by
Surafel
27 days ago
የቴዲ አፍሮ ስዎች በፈተና ላይ! ፖሊስ ተጨማሪ ጊዜ ሊጠይቅባቸው ነው! #teddyafro #ethiopia #ethiopiannews #facebookreels #ethiopianmusic
የቴዲ አፍሮ ስዎች በፈተና ላይ! ፖሊስ ተጨማሪ ጊዜ ሊጠይቅባቸው ነው! #teddyafro #ethiopia #ethiopiannews #facebookreels #ethiopianmusic
29 days ago
ሰበር - የቴዲ አፍሮ የሙዚቃ አልበም ግራፊክ ዲዛይነር በፌዴራል ፖሊስ ተወሰደ #teddyafro #etorika #ethiopiannews #zehabesha #ethiopia
1 month ago
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአፍሪካ ቁንጮ መሆኑን የሚያስመሰክር የ2026 የአፔክስ የክብር ሽልማት ተቀዳጀ
#ethiopia | የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአህጉሪቱ ያለውን ቀዳሚነት የሚያረጋግጥ የአፔክስ የመንገደኞች ምርጫ የ2026 የአፍሪካ ምርጥ አየር መንገድ ሽልማትን በድጋሚ ወስዷል፡፡
ይህ ሽልማት ተቋሙ ለተሳፋሪዎቹ የሚሰጠውን ምቹ፣ ቀልጣፋ እና አስተማማኝ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ዓለም አቀፍ እውቅና የሰጠ ሲሆን በአቪዬሽን ኢንዱስትሪው ውስጥ ያለውን ተወዳዳሪነት ይበልጥ እንደሚያጎላው ተመልክቷል፡፡
የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ሽልማቱን በተረከቡበት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት ይህ ስኬት የተመዘገበው በመላው የአየር መንገዱ ሰራተኞችና አመራሮች ከፍተኛ ጥረት መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ሽልማቱ በቀጥታ በመንገደኞች ድምፅና ምርጫ የተሰጠ መሆኑ ልዩ ትርጉም እንደሚሰጠው የጠቀሱት ዋና ስራ አስፈጻሚው በቀጣይም የደንበኞችን አመኔታ ለማርካትና የአገልግሎት ጥራትን ይበልጥ ለማዘመን ከፍተኛ መነሳሳትን እንደሚፈጥር አስረድተዋል፡፡
#ethiopianairlines #aviation #africabestairline #apexawards #flyethiopian #ethiopiannews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአህጉሪቱ ያለውን ቀዳሚነት የሚያረጋግጥ የአፔክስ የመንገደኞች ምርጫ የ2026 የአፍሪካ ምርጥ አየር መንገድ ሽልማትን በድጋሚ ወስዷል፡፡
ይህ ሽልማት ተቋሙ ለተሳፋሪዎቹ የሚሰጠውን ምቹ፣ ቀልጣፋ እና አስተማማኝ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ዓለም አቀፍ እውቅና የሰጠ ሲሆን በአቪዬሽን ኢንዱስትሪው ውስጥ ያለውን ተወዳዳሪነት ይበልጥ እንደሚያጎላው ተመልክቷል፡፡
የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ሽልማቱን በተረከቡበት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት ይህ ስኬት የተመዘገበው በመላው የአየር መንገዱ ሰራተኞችና አመራሮች ከፍተኛ ጥረት መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ሽልማቱ በቀጥታ በመንገደኞች ድምፅና ምርጫ የተሰጠ መሆኑ ልዩ ትርጉም እንደሚሰጠው የጠቀሱት ዋና ስራ አስፈጻሚው በቀጣይም የደንበኞችን አመኔታ ለማርካትና የአገልግሎት ጥራትን ይበልጥ ለማዘመን ከፍተኛ መነሳሳትን እንደሚፈጥር አስረድተዋል፡፡
#ethiopianairlines #aviation #africabestairline #apexawards #flyethiopian #ethiopiannews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 month ago
1 month ago
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ኢትዮጵያውያን ከአሜሪካ እንዳይባረሩ ፍርድ ቤት ወሰነ
#ethiopia | የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጊዜያዊ መኖሪያ ፈቃድ እንዲታገድ ያሳለፈው ውሳኔ በፍርድ ቤት መታገዱ ተሰምቷል፡፡
የትራምፕ አስተዳደር ከ5 ሺሕ በላይ ኢትዮጵያውያንን ለማበራር የሚያስችለውን የጊዜያዊ ከላላ ፈቃድ (Temporary Protected Status-TPS) መሻሩ ይታወሳል፡፡ ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት አምርቶ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ላይ የተደቀነውን የመባረር ስጋት የሚቀለብስ እግድ በአሜሪካ የፌደራል ፍርድ ቤት ተጥሏል፡፡
ለ5000 ኢትዮጵያውያን የተሰጠዉው ጊዜያዊ የከለላ ፈቃድ የተሰረዘበትን ውሳኔ፣ የሀገሪቱ ፌደራል ፍርድ ቤት ቦስተን ዲስትሪክት ዳኛ ውድቅ አድርገውታል፡፡ የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ከአሜሪካ ለቀው እንዲወጡ የተሰጣቸው የሦስት ወር ጊዜ ገደብ እየተገባደደ በመሆኑ አጣብቂኝ ውስጥ ለገቡት ኢትዮጵያውያን ስደተኞች አፎይታ የሚሰጥ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
ውሳኔው የተቀበለበሰበት ክስ የቀረበው በሦስት ኢትዮጵያውያን እና አፍሪካን ኮሚውኒቲስ ቱጌዘር (African Communities Together) በተባለ ተሟጋች ቡድን ነው ተብሏል።
የቦስተኑ ፍርድ ቤት ዳኛ ብሬይን መርፊይ ትናንት በሰጡት ውሳኔ የትራምፕ አስተዳደር ትዕዛዝ አስቀድሞ የታሰበና የተወሰነ እንጂ፣ “በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ አጥንቶና አገናዝቦ የተወሰነ አይደለም” ብለዋል።
በአሜሪካ በተፈጥሮ አደጋዎች፣ በጦርነትና በሌሎች ልዩ አደጋዎች ምክንያት ከየሀገራቸዉ የሸሹ ሰዎች በጊዜያዊነት የመኖርና የመስራት ፈቃድ ይሰጣቸዋል። በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያን ጨምሮ የጊዜያዊ ከለላ ፈቃድ ፈቃድ የተሰጣቸዉ የ13 ሀገራት ዜጎች በአሜሪካ እንደሚኖሩ መረጃዎች ያመላክታሉ ሲል አንድ አፍታ ዘግቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ethiopia #ethiopiannews #ኢትዮጵያ #ethiopianinus #diaspora #ustps #andaftamedia #አንድአፍታ
#ethiopia | የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጊዜያዊ መኖሪያ ፈቃድ እንዲታገድ ያሳለፈው ውሳኔ በፍርድ ቤት መታገዱ ተሰምቷል፡፡
የትራምፕ አስተዳደር ከ5 ሺሕ በላይ ኢትዮጵያውያንን ለማበራር የሚያስችለውን የጊዜያዊ ከላላ ፈቃድ (Temporary Protected Status-TPS) መሻሩ ይታወሳል፡፡ ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት አምርቶ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ላይ የተደቀነውን የመባረር ስጋት የሚቀለብስ እግድ በአሜሪካ የፌደራል ፍርድ ቤት ተጥሏል፡፡
ለ5000 ኢትዮጵያውያን የተሰጠዉው ጊዜያዊ የከለላ ፈቃድ የተሰረዘበትን ውሳኔ፣ የሀገሪቱ ፌደራል ፍርድ ቤት ቦስተን ዲስትሪክት ዳኛ ውድቅ አድርገውታል፡፡ የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ከአሜሪካ ለቀው እንዲወጡ የተሰጣቸው የሦስት ወር ጊዜ ገደብ እየተገባደደ በመሆኑ አጣብቂኝ ውስጥ ለገቡት ኢትዮጵያውያን ስደተኞች አፎይታ የሚሰጥ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡
ውሳኔው የተቀበለበሰበት ክስ የቀረበው በሦስት ኢትዮጵያውያን እና አፍሪካን ኮሚውኒቲስ ቱጌዘር (African Communities Together) በተባለ ተሟጋች ቡድን ነው ተብሏል።
የቦስተኑ ፍርድ ቤት ዳኛ ብሬይን መርፊይ ትናንት በሰጡት ውሳኔ የትራምፕ አስተዳደር ትዕዛዝ አስቀድሞ የታሰበና የተወሰነ እንጂ፣ “በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ አጥንቶና አገናዝቦ የተወሰነ አይደለም” ብለዋል።
በአሜሪካ በተፈጥሮ አደጋዎች፣ በጦርነትና በሌሎች ልዩ አደጋዎች ምክንያት ከየሀገራቸዉ የሸሹ ሰዎች በጊዜያዊነት የመኖርና የመስራት ፈቃድ ይሰጣቸዋል። በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያን ጨምሮ የጊዜያዊ ከለላ ፈቃድ ፈቃድ የተሰጣቸዉ የ13 ሀገራት ዜጎች በአሜሪካ እንደሚኖሩ መረጃዎች ያመላክታሉ ሲል አንድ አፍታ ዘግቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ethiopia #ethiopiannews #ኢትዮጵያ #ethiopianinus #diaspora #ustps #andaftamedia #አንድአፍታ
2 months ago
''የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት ሞሮኮ በመሆኗ ደስ ብሎኛል'' አሽራፍ ሀኪሚ
#ethiopia | ሴኔጋል በሜዳ ላይ አሸንፋ የነበረ ቢሆንም፣ የካፍ (CAF) ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ በወሰነው ያልተጠበቀ ውሳኔ፣ ውጤቱን በመሻር ዋንጫውን በፎርፌ ለሞሮኮ መስጠቱ አይዘነጋም።
አሁን ደግሞ የሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን አምበል አሽራፍ ሀኪሚ ዝምታውን ሰብሯል። ሀኪሚ ይህን የካፍ ውሳኔ እና የዋንጫ ድል በታላቅ ደስታ እንደሚቀበለው በይፋ ገልጿል።
“የአፍሪካ ዋንጫውን በዚህ መንገድ (በፎርፌ) ማሸነፍ ቢኖርብንም፣ በታላቅ ደስታ እንቀበለዋለን፤” ሲል አምበሉ ሀኪሚ ተናግሯል። አክሎም “በድሉ እጅግ በጣም ደስተኞች ነን፤ ይህንን ጊዜም ለረጅም ጊዜ ስጠብቀው ነበር” በማለት አስተያየቱን ሰጥቷል።
እርግጥ ነው፣ ነገሮች ገና እልባት አላገኙም! የካፍ የመጨረሻ ውሳኔ አሁን በዓለም አቀፉ የስፖርት ገላጋይ ፍርድ ቤት (TAS) ውሳኔ እንዲሰጥበት ተላልፏል። የሴኔጋል ይግባኝ ውጤቱን ሊቀለብሰው ይችላል ወይስ ሞሮኮ ዋንጫዋን በይፋ ታስቀራለች? በቀጣይ አዳዲስ መረጃዎች ሲወጡ የምናቀርብላችሁ ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #afcon #hakimi #morocco #senegal #caf #tas #footballnews #abelbirhanu #ethiopiannews #sportupdates
#ethiopia | ሴኔጋል በሜዳ ላይ አሸንፋ የነበረ ቢሆንም፣ የካፍ (CAF) ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ በወሰነው ያልተጠበቀ ውሳኔ፣ ውጤቱን በመሻር ዋንጫውን በፎርፌ ለሞሮኮ መስጠቱ አይዘነጋም።
አሁን ደግሞ የሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን አምበል አሽራፍ ሀኪሚ ዝምታውን ሰብሯል። ሀኪሚ ይህን የካፍ ውሳኔ እና የዋንጫ ድል በታላቅ ደስታ እንደሚቀበለው በይፋ ገልጿል።
“የአፍሪካ ዋንጫውን በዚህ መንገድ (በፎርፌ) ማሸነፍ ቢኖርብንም፣ በታላቅ ደስታ እንቀበለዋለን፤” ሲል አምበሉ ሀኪሚ ተናግሯል። አክሎም “በድሉ እጅግ በጣም ደስተኞች ነን፤ ይህንን ጊዜም ለረጅም ጊዜ ስጠብቀው ነበር” በማለት አስተያየቱን ሰጥቷል።
እርግጥ ነው፣ ነገሮች ገና እልባት አላገኙም! የካፍ የመጨረሻ ውሳኔ አሁን በዓለም አቀፉ የስፖርት ገላጋይ ፍርድ ቤት (TAS) ውሳኔ እንዲሰጥበት ተላልፏል። የሴኔጋል ይግባኝ ውጤቱን ሊቀለብሰው ይችላል ወይስ ሞሮኮ ዋንጫዋን በይፋ ታስቀራለች? በቀጣይ አዳዲስ መረጃዎች ሲወጡ የምናቀርብላችሁ ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #afcon #hakimi #morocco #senegal #caf #tas #footballnews #abelbirhanu #ethiopiannews #sportupdates
2 months ago
ገንዘብ አልሰጠኸኝም በሚል አባቱን የገደለው ግለሰብ በ18 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ
#ethiopia | በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ካፋ ዞን፣ የገንዘብ ጥያቄ በማንሳት የ60 ዓመት ወላጅ አባቱን ደብድቦ የገደለው ግለሰብ በ18 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ተወሰነ።
ወንጀሉ የተፈጸመው በዞኑ ገዋታ ወረዳ፣ ዶማ ቀበሌ ውስጥ ህዳር 3 ቀን 2018 ዓ.ም. ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ላይ መሆኑን ፖሊስ አረጋግጧል። ተከሳሽ ሀብታሙ ዳጤ "ቡና ለቅሜ እና የእንጨት ማገዶ ሸጬ ያገኘሁትን ገንዘብ አልሰጠኸኝም" በሚል ሰበብ ከወላጅ አባቱ ጋር ግጭት ውስጥ ይገባል።
ይህንኑ ተከትሎም በመኖሪያ ቤታቸው ደጅ ላይ በባህር ዛፍ ዱላ የ60 ዓመት አባቱን ጭንቅላት ላይ በጭካኔ በመደብደብ ከባድ ጉዳት ያደርስባቸዋል። አባትየው ህይወታቸውን ለማትረፍ ወደ ህክምና ተቋም ቢወሰዱም፣ በደረሰባቸው ከባድ ጉዳት ምክንያት ህይወታቸው ሊያልፍ ችሏል።
ይህን አሳዛኝ ድርጊት ተከትሎም፣ የካፋ ዞን ዐቃቤ ህግ በፖሊስ የምርመራ መዝገብ ላይ ተመስርቶ ግለሰቡ ላይ የሰው ግድያ ወንጀል ክስ በመመስረት ለካፋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቅርቦታል።
ጉዳዩን ሲከታተል የቆየው የካፋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም፣ የቀረበለትን የዐቃቤ ህግ ማስረጃ እና የግራ ቀኙን ክርክር መርምሮ ተከሳሹን ጥፋተኛ ብሎታል።
በመሆኑም መጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ.ም. በዋለው የወንጀል ችሎት፣ ጥፋተኛው ሀብታሙ ዳጤ በ18 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ የቅጣት ውሳኔ ማሳለፉን ዐቃቤ ህግ ዮናስ ተረፈ ለክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን አብራርተዋል።
(የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ፖሊስ ኮሚሽን ነው)
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ካፋ #ወንጀልና_ቅጣት #የደቡብ_ምዕራብ_ኢትዮጵያ_ፖሊስ #ኢትዮጵያ_ዜና #kafazone #ethiopiannews
#ethiopia | በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ካፋ ዞን፣ የገንዘብ ጥያቄ በማንሳት የ60 ዓመት ወላጅ አባቱን ደብድቦ የገደለው ግለሰብ በ18 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ተወሰነ።
ወንጀሉ የተፈጸመው በዞኑ ገዋታ ወረዳ፣ ዶማ ቀበሌ ውስጥ ህዳር 3 ቀን 2018 ዓ.ም. ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ላይ መሆኑን ፖሊስ አረጋግጧል። ተከሳሽ ሀብታሙ ዳጤ "ቡና ለቅሜ እና የእንጨት ማገዶ ሸጬ ያገኘሁትን ገንዘብ አልሰጠኸኝም" በሚል ሰበብ ከወላጅ አባቱ ጋር ግጭት ውስጥ ይገባል።
ይህንኑ ተከትሎም በመኖሪያ ቤታቸው ደጅ ላይ በባህር ዛፍ ዱላ የ60 ዓመት አባቱን ጭንቅላት ላይ በጭካኔ በመደብደብ ከባድ ጉዳት ያደርስባቸዋል። አባትየው ህይወታቸውን ለማትረፍ ወደ ህክምና ተቋም ቢወሰዱም፣ በደረሰባቸው ከባድ ጉዳት ምክንያት ህይወታቸው ሊያልፍ ችሏል።
ይህን አሳዛኝ ድርጊት ተከትሎም፣ የካፋ ዞን ዐቃቤ ህግ በፖሊስ የምርመራ መዝገብ ላይ ተመስርቶ ግለሰቡ ላይ የሰው ግድያ ወንጀል ክስ በመመስረት ለካፋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቅርቦታል።
ጉዳዩን ሲከታተል የቆየው የካፋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም፣ የቀረበለትን የዐቃቤ ህግ ማስረጃ እና የግራ ቀኙን ክርክር መርምሮ ተከሳሹን ጥፋተኛ ብሎታል።
በመሆኑም መጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ.ም. በዋለው የወንጀል ችሎት፣ ጥፋተኛው ሀብታሙ ዳጤ በ18 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ የቅጣት ውሳኔ ማሳለፉን ዐቃቤ ህግ ዮናስ ተረፈ ለክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን አብራርተዋል።
(የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ፖሊስ ኮሚሽን ነው)
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ካፋ #ወንጀልና_ቅጣት #የደቡብ_ምዕራብ_ኢትዮጵያ_ፖሊስ #ኢትዮጵያ_ዜና #kafazone #ethiopiannews
2 months ago
350 ሺህ ዶላር :
ኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ በዋሽንግተን ዲሲ አሰባሰበ
የኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ ትላንት መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም. በዋሽንግተን ዲሲ ማርዮት ሆቴል ባከናወነው የማጠቃለያ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር 350 ሺህ ዶላር በማግኘት በታላቅ ስኬት መጠናቀቁን የድርጅቱ መሥራችና የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ብርሃን ተድላ አስታውቀዋል።
እስካሁን 110 ሺህ ዶላር በቀጥታ በባንክ ገቢ የተደረገ ሲሆን፣ ቀሪው ቃል የተገባና በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚሰበሰብ ነው።
በተገኘው ገንዘብ በሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ በወረፋ ላይ ለሚገኙ 120 ሕፃናት የልብ ቀዶ ጥገና ሕክምና ለመስጠት ዕቅድ ተይዟል።
ከጣሊያን ከመጡ ሦስት ድርጅቶች ጋር በመተባበር 50 ተጨማሪ ሕፃናትን ለማከም ዝግጅት እየተጠናቀቀ ነው። ይህም በቅርብ ወራት ውስጥ ሕክምና የሚያገኙ ሕፃናትን ቁጥር 170 ያደርሰዋል።
በቀጣይ አንድ ዓመት ውስጥ በአራት የሀገሪቱ አካባቢዎች በሚገኙ የመንግሥት ሆስፒታሎች የልብ ቀዶ ጥገና ማዕከላትን ለማቋቋም ታቅዶ እየተሠራ ይገኛል።
ለዝግጅቱ ስኬት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረጉት የበጎ ፈቃድ አምባሳደር ወጣት አዶናይ ብርሃነ፣ ወይዘሮ ሐና ክብሩና ባለቤታቸው ሳሚ የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
በዝግጅቱ ላይ የዋሽንግተን ዲሲ እጩ ከንቲባ ሚስተር ኬኒየን ማክደፊ፣ ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል እና ሊቀ ማዕምራን ፕሮፌሰር ዘበነ ለማን ጨምሮ በርካታ እንግዶች ተገኝተዋል።
አቶ ብርሃን ተድላ ኢትዮጵያውያን የልብ ቀዶ ጥገና ባለሙያዎች አዲስ የሚቋቋመውን የባለሙያዎች ቡድን እንዲቀላቀሉና ወገኖቻቸውን እንዲረዱ ጥሪ አቅርበዋል።
#getu #ethiopiannews #hearttoheart #childrenshealth #fundraising #washingtondc #ethiopiandiaspora #heartsurgery #charity #የልብሕሙማን #ሰብአዊነት #ዋሽንግተንዲሲ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
ኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ በዋሽንግተን ዲሲ አሰባሰበ
የኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ ትላንት መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም. በዋሽንግተን ዲሲ ማርዮት ሆቴል ባከናወነው የማጠቃለያ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር 350 ሺህ ዶላር በማግኘት በታላቅ ስኬት መጠናቀቁን የድርጅቱ መሥራችና የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ብርሃን ተድላ አስታውቀዋል።
እስካሁን 110 ሺህ ዶላር በቀጥታ በባንክ ገቢ የተደረገ ሲሆን፣ ቀሪው ቃል የተገባና በአጭር ጊዜ ውስጥ የሚሰበሰብ ነው።
በተገኘው ገንዘብ በሁለት ወራት ጊዜ ውስጥ በወረፋ ላይ ለሚገኙ 120 ሕፃናት የልብ ቀዶ ጥገና ሕክምና ለመስጠት ዕቅድ ተይዟል።
ከጣሊያን ከመጡ ሦስት ድርጅቶች ጋር በመተባበር 50 ተጨማሪ ሕፃናትን ለማከም ዝግጅት እየተጠናቀቀ ነው። ይህም በቅርብ ወራት ውስጥ ሕክምና የሚያገኙ ሕፃናትን ቁጥር 170 ያደርሰዋል።
በቀጣይ አንድ ዓመት ውስጥ በአራት የሀገሪቱ አካባቢዎች በሚገኙ የመንግሥት ሆስፒታሎች የልብ ቀዶ ጥገና ማዕከላትን ለማቋቋም ታቅዶ እየተሠራ ይገኛል።
ለዝግጅቱ ስኬት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረጉት የበጎ ፈቃድ አምባሳደር ወጣት አዶናይ ብርሃነ፣ ወይዘሮ ሐና ክብሩና ባለቤታቸው ሳሚ የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
በዝግጅቱ ላይ የዋሽንግተን ዲሲ እጩ ከንቲባ ሚስተር ኬኒየን ማክደፊ፣ ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል እና ሊቀ ማዕምራን ፕሮፌሰር ዘበነ ለማን ጨምሮ በርካታ እንግዶች ተገኝተዋል።
አቶ ብርሃን ተድላ ኢትዮጵያውያን የልብ ቀዶ ጥገና ባለሙያዎች አዲስ የሚቋቋመውን የባለሙያዎች ቡድን እንዲቀላቀሉና ወገኖቻቸውን እንዲረዱ ጥሪ አቅርበዋል።
#getu #ethiopiannews #hearttoheart #childrenshealth #fundraising #washingtondc #ethiopiandiaspora #heartsurgery #charity #የልብሕሙማን #ሰብአዊነት #ዋሽንግተንዲሲ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
3 months ago
⚡️ 613 የጸጥታ አካላትና ኃላፊዎችን ጨምሮ በነዳጅ አሻጥር የተሳተፉ ግለሰቦች ታሰሩ!
#ethiopia | የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ እንዳስታወቁት፤ በነዳጅ ሕገ-ወጥ ንግድ እና አሻጥር ላይ ተሳትፈው የተገኙ 613 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
በእስር እርምጃው ከተያዙት ግለሰቦች መካከል የንግድ ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎች፣ የቡድን መሪዎች፣ የሬጉላቶሪ ባለሙያዎች፣ የነዳጅ ማደያ ባለቤቶችና ሠራተኞች፣ እንዲሁም በየደረጃው የሚገኙ የጸጥታ አካላት ይገኙበታል።
በስድስት ክልሎች እና በሁለት የከተማ አስተዳደሮች በተደረገው ጥብቅ ፍተሻ፤ 250,221 ሊትር ቤንዚን እና 198,432 ሊትር ናፍጣ በሕገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር እና ጥቅም ላይ ሲውል ተይዞ መወረሱንም ሚኒስትሩ አብራርተዋል።
በተጨማሪም ከተወረሰው ነዳጅ ውስጥ በሽያጭ እንዲውል ከተደረገው 48,663,432.21 ብር ለመንግስት ገቢ መደረጉ ተገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiopia #ethiopiannews #dailynews #fuel #ministryoftrade #addisababa #ኢትዮጵያ #ዜና #ነዳጅ #አቤልብርሃኑ
#ethiopia | የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ እንዳስታወቁት፤ በነዳጅ ሕገ-ወጥ ንግድ እና አሻጥር ላይ ተሳትፈው የተገኙ 613 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
በእስር እርምጃው ከተያዙት ግለሰቦች መካከል የንግድ ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎች፣ የቡድን መሪዎች፣ የሬጉላቶሪ ባለሙያዎች፣ የነዳጅ ማደያ ባለቤቶችና ሠራተኞች፣ እንዲሁም በየደረጃው የሚገኙ የጸጥታ አካላት ይገኙበታል።
በስድስት ክልሎች እና በሁለት የከተማ አስተዳደሮች በተደረገው ጥብቅ ፍተሻ፤ 250,221 ሊትር ቤንዚን እና 198,432 ሊትር ናፍጣ በሕገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር እና ጥቅም ላይ ሲውል ተይዞ መወረሱንም ሚኒስትሩ አብራርተዋል።
በተጨማሪም ከተወረሰው ነዳጅ ውስጥ በሽያጭ እንዲውል ከተደረገው 48,663,432.21 ብር ለመንግስት ገቢ መደረጉ ተገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiopia #ethiopiannews #dailynews #fuel #ministryoftrade #addisababa #ኢትዮጵያ #ዜና #ነዳጅ #አቤልብርሃኑ
3 months ago
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊ በደረሰባቸው ጥቃት ህይወታቸው አለፈ
#ethiopia | የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ወ/ሮ አዱኛ አዛዥ፣ የተሰጣቸውን የመንግስት የስራ ተልዕኮ አጠናቅቀው በመመለስ ላይ እያሉ በደረሰባቸው ድንገተኛ ጥቃት ህይወታቸው ማለፉ ተገለጸ።
ኃላፊዋ ጥቃቱ ከደረሰባቸው በኋላ በህክምና ማዕከል እርዳታ ሲደረግላቸው የቆየ ቢሆንም፣ ህይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም። ወ/ሮ አዱኛ በቀድሞው የጋሞ ጎፋ ዞን፣ በደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል፣ እንዲሁም አዲሱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከተመሰረተ ወዲህ በተለያዩ የኃላፊነት እርከኖች ላይ ሀገርንና ህዝብን በቅንነት ያገለገሉ ብርቱ አመራር እንደነበሩ ተገልጿል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በባለስልጣኗ ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን በመግለጽ፤ ድርጊቱን ያልተገቡ ፍላጎቶችን በጉልበትና በጦር መሳሪያ ለማስፈጸም የሚንቀሳቀሱ ጥቂት ኋላቀር ቡድኖች የፈጸሙት የጥፋት ተግባር ሲል ኮንኖታል።
በመሆኑም የክልሉ መንግስት እንዲህ አይነት እኩይ ተግባራትን አምርሮ እንደሚታገል አሳውቆ፣ በጥቃቱ ተሳታፊ የሆኑና የተባበሩ አካላትን ለይቶ ለህግ ለማቅረብና የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል። ፍትህ እስኪሰፍንም ድረስ ህብረተሰቡ የተለመደውን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪውን አስተላልፏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ዜና #ደቡብ_ኢትዮጵያ #ኢትዮጵያ #ወቅታዊ_መረጃ #southethiopia #ethiopiannews
#ethiopia | የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ወ/ሮ አዱኛ አዛዥ፣ የተሰጣቸውን የመንግስት የስራ ተልዕኮ አጠናቅቀው በመመለስ ላይ እያሉ በደረሰባቸው ድንገተኛ ጥቃት ህይወታቸው ማለፉ ተገለጸ።
ኃላፊዋ ጥቃቱ ከደረሰባቸው በኋላ በህክምና ማዕከል እርዳታ ሲደረግላቸው የቆየ ቢሆንም፣ ህይወታቸውን ማትረፍ አልተቻለም። ወ/ሮ አዱኛ በቀድሞው የጋሞ ጎፋ ዞን፣ በደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል፣ እንዲሁም አዲሱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከተመሰረተ ወዲህ በተለያዩ የኃላፊነት እርከኖች ላይ ሀገርንና ህዝብን በቅንነት ያገለገሉ ብርቱ አመራር እንደነበሩ ተገልጿል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት በባለስልጣኗ ህልፈት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን በመግለጽ፤ ድርጊቱን ያልተገቡ ፍላጎቶችን በጉልበትና በጦር መሳሪያ ለማስፈጸም የሚንቀሳቀሱ ጥቂት ኋላቀር ቡድኖች የፈጸሙት የጥፋት ተግባር ሲል ኮንኖታል።
በመሆኑም የክልሉ መንግስት እንዲህ አይነት እኩይ ተግባራትን አምርሮ እንደሚታገል አሳውቆ፣ በጥቃቱ ተሳታፊ የሆኑና የተባበሩ አካላትን ለይቶ ለህግ ለማቅረብና የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል። ፍትህ እስኪሰፍንም ድረስ ህብረተሰቡ የተለመደውን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪውን አስተላልፏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ዜና #ደቡብ_ኢትዮጵያ #ኢትዮጵያ #ወቅታዊ_መረጃ #southethiopia #ethiopiannews
3 months ago
🛑 ሰበር ዜና፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ መካከለኛው ምስራቅ የሚደረጉ በረራዎችን መሰረዙን አስታወቀ
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ አሁን ላይ እየታየ ያለው የጸጥታ ሁኔታ አስተማማኝ ባለመሆኑ፣ "የአፍሪካ ኩራት" የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቀጠናው የሚያደርጋቸውን አንዳንድ በረራዎች ለጊዜው ማቋረጡን ገልጿል።
የትኞቹ ከተሞች ላይ በረራ ተቋረጠ?
እስካሁን ባለው መረጃ መሰረት ወደሚከተሉት ከተሞች የሚደረጉ በረራዎች ተሰርዘዋል፦
* አማን (ዮርዳኖስ)
* ቴል አቪቭ (እስራኤል)
* ዳማም (ሳዑዲ ዓረቢያ)
* ቤይሩት (ሊባኖስ)
አየር መንገዱ የአካባቢውን ሁኔታ በንቃት እየተከታተለ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ ውሳኔው የተላለፈው የተጓዦችን እና የሰራተኞችን ደህንነት በዋነኝነት ከግምት ውስጥ በማስገባት እንደሆነ አስታውቋል።
ለተጓዦች የተሰጠ ምክር፦
መንገድ ከመጀመርዎ በፊት መረጃ መያዝ ብልህነት ነው! ወደ እነዚህ አካባቢዎች ለመጓዝ እቅድ ያላችሁ ተጓዦች ወደ አውሮፕላን ማረፊያ ከመሄዳችሁ በፊት፦
* በአየር መንገዱ የዲጂታል አማራጮች (ድረ-ገጽ እና መተግበሪያ) የበረራዎን ሁኔታ ያረጋግጡ።
* በበረራ ትኬት የቆረጡበትን የጉዞ ወኪል (Travel Agency) ያነጋግሩ።
* ወይም በኢሜይል አድራሻ reservation @ethiopianairlines .com በመጠቀም መረጃ ይጠይቁ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለተፈጠረው መስተጓጎል ይቅርታ እየጠየቀ፣ ሁኔታዎች ሲስተካከሉ ተጨማሪ መረጃዎችን እንደሚሰጥም አመልክቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiopianairlines #travelalert #middleeastsecurity #flightupdate #flyethiopian #safetyfirst #ethiopiannews
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ አሁን ላይ እየታየ ያለው የጸጥታ ሁኔታ አስተማማኝ ባለመሆኑ፣ "የአፍሪካ ኩራት" የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቀጠናው የሚያደርጋቸውን አንዳንድ በረራዎች ለጊዜው ማቋረጡን ገልጿል።
የትኞቹ ከተሞች ላይ በረራ ተቋረጠ?
እስካሁን ባለው መረጃ መሰረት ወደሚከተሉት ከተሞች የሚደረጉ በረራዎች ተሰርዘዋል፦
* አማን (ዮርዳኖስ)
* ቴል አቪቭ (እስራኤል)
* ዳማም (ሳዑዲ ዓረቢያ)
* ቤይሩት (ሊባኖስ)
አየር መንገዱ የአካባቢውን ሁኔታ በንቃት እየተከታተለ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ ውሳኔው የተላለፈው የተጓዦችን እና የሰራተኞችን ደህንነት በዋነኝነት ከግምት ውስጥ በማስገባት እንደሆነ አስታውቋል።
ለተጓዦች የተሰጠ ምክር፦
መንገድ ከመጀመርዎ በፊት መረጃ መያዝ ብልህነት ነው! ወደ እነዚህ አካባቢዎች ለመጓዝ እቅድ ያላችሁ ተጓዦች ወደ አውሮፕላን ማረፊያ ከመሄዳችሁ በፊት፦
* በአየር መንገዱ የዲጂታል አማራጮች (ድረ-ገጽ እና መተግበሪያ) የበረራዎን ሁኔታ ያረጋግጡ።
* በበረራ ትኬት የቆረጡበትን የጉዞ ወኪል (Travel Agency) ያነጋግሩ።
* ወይም በኢሜይል አድራሻ reservation @ethiopianairlines .com በመጠቀም መረጃ ይጠይቁ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለተፈጠረው መስተጓጎል ይቅርታ እየጠየቀ፣ ሁኔታዎች ሲስተካከሉ ተጨማሪ መረጃዎችን እንደሚሰጥም አመልክቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiopianairlines #travelalert #middleeastsecurity #flightupdate #flyethiopian #safetyfirst #ethiopiannews
Sponsored by
Surafel
4 months ago
🚨 ሱዳን በኢትዮጵያውያን ተዋጊዎች ላይ የሞት ፍርድ ልታስተላልፍ ነው!
#ethiopia | በሱዳን እየተካሄደ ባለው የእርስ በእርስ ጦርነት "ለፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች (RSF)" ወግነው ተሰልፈዋል የተባሉ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ 122 የውጭ ሀገር ዜጎች ላይ ክስ መመስረቱ ተሰማ።
የክሱ ዝርዝር እና የተከሳሾቹ ማንነት፦
የሱዳን ወንጀል ምርመራ ቢሮ ዳይሬክተር እንቲሳር አብዱልሙታር እንደገለጹት፣ እነዚህ ተከሳሾች ከኢትዮጵያ፣ ኮሎምቢያ፣ ቻድ እና ደቡብ ሱዳን የመጡ "ቅጥረኛ ተዋጊዎች" ናቸው። ተከሳሾቹ በሱዳን ጦር ላይ በግንባር ቀደምትነት ሲዋጉ እንደነበር ተገልጿል።
ጥብቅ ማስጠንቀቂያ፦
ዳይሬክተሯ አጽንኦት ሰጥተው እንደተናገሩት፣ ተከሳሾቹ የተመሰረተባቸው ክስ "የግድያ ወንጀል" በመሆኑ፣ ጥፋተኝነታቸው ሲረጋገጥ የሚጠብቃቸው ቅጣት "በእርግጠኝነት የሞት ፍርድ" እንደሆነ አስታውቀዋል።
ሌሎች አስደንጋጭ መረጃዎች፦
* ጦርነቱ ከተጀመረ ወዲህ በሱዳን 188 ሺሕ 405 የሚጠጉ የተለያዩ የወንጀል ክሶች ተመስርተዋል።
* በግዳጅ ተሰልፈው ሲዋጉ የተገኙ 135 ህፃናት ተለይተው ለቤተሰቦቻቸው መመለሳቸው ተገልጿል።
ይህ ክስ በኢትዮጵያ እና በሱዳን መካከል ያለውን ግንኙነት ምን ያህል ሊያሻክረው እንደሚችል የብዙዎች ስጋት ሆኗል። በተለይም በሞት ፍርድ ዙሪያ የሚሰጡ ውሳኔዎች የዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ትኩረት ይስባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#thiqah #sudan #ethiopia #rsf #sudanwar #breakingnews #legalaction #africanews #ethiopiannews #sudantribune
#ethiopia | በሱዳን እየተካሄደ ባለው የእርስ በእርስ ጦርነት "ለፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች (RSF)" ወግነው ተሰልፈዋል የተባሉ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ 122 የውጭ ሀገር ዜጎች ላይ ክስ መመስረቱ ተሰማ።
የክሱ ዝርዝር እና የተከሳሾቹ ማንነት፦
የሱዳን ወንጀል ምርመራ ቢሮ ዳይሬክተር እንቲሳር አብዱልሙታር እንደገለጹት፣ እነዚህ ተከሳሾች ከኢትዮጵያ፣ ኮሎምቢያ፣ ቻድ እና ደቡብ ሱዳን የመጡ "ቅጥረኛ ተዋጊዎች" ናቸው። ተከሳሾቹ በሱዳን ጦር ላይ በግንባር ቀደምትነት ሲዋጉ እንደነበር ተገልጿል።
ጥብቅ ማስጠንቀቂያ፦
ዳይሬክተሯ አጽንኦት ሰጥተው እንደተናገሩት፣ ተከሳሾቹ የተመሰረተባቸው ክስ "የግድያ ወንጀል" በመሆኑ፣ ጥፋተኝነታቸው ሲረጋገጥ የሚጠብቃቸው ቅጣት "በእርግጠኝነት የሞት ፍርድ" እንደሆነ አስታውቀዋል።
ሌሎች አስደንጋጭ መረጃዎች፦
* ጦርነቱ ከተጀመረ ወዲህ በሱዳን 188 ሺሕ 405 የሚጠጉ የተለያዩ የወንጀል ክሶች ተመስርተዋል።
* በግዳጅ ተሰልፈው ሲዋጉ የተገኙ 135 ህፃናት ተለይተው ለቤተሰቦቻቸው መመለሳቸው ተገልጿል።
ይህ ክስ በኢትዮጵያ እና በሱዳን መካከል ያለውን ግንኙነት ምን ያህል ሊያሻክረው እንደሚችል የብዙዎች ስጋት ሆኗል። በተለይም በሞት ፍርድ ዙሪያ የሚሰጡ ውሳኔዎች የዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ትኩረት ይስባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#thiqah #sudan #ethiopia #rsf #sudanwar #breakingnews #legalaction #africanews #ethiopiannews #sudantribune