2 hours ago
u12e8u1261u12f5u1291 u132du121du1265u120d u12a0u1325u120bu1242 u12a0u134bu129eu127d #tplf #debretsiongebremichael #esayasafewerk ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
የቡድኑ ጭምብል አጥላቂ አፋኞች #tplf #debretsiongebremichael #esayasafewerk
9 hours ago
🚨 በህወሓት አመራሮች ላይ የተጣለው የአሜሪካ ቪዛ እገዳ ማብራሪያ! በጠበቃ ሙሉዓለም ጌታቸው ማብራሪያ ተሰጥቶበታል። #usvisa #tplf #ethiopiannews #ussanctions #asylum
15 hours ago
አሜሪካ በሕወሓት አመራሮች እና ቤተሰቦቻቸው ላይ የቪዛ እገዳ ጣለች #tplf #ussanctions #visaban #tigraycrisis #ethiopianpolitics #usforeignpolicy
15 hours ago
The US has imposed visa bans on TPLF extremist leaders and their immediate families, accusing them of obstructing the peace process in northern Ethiopia.
#ethiopia #tigray #tplf #usvisaban #marcorubio #peaceinethiopia #hornofafrica ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
The US has imposed visa bans on TPLF extremist leaders and their immediate families, accusing them of obstructing the peace process in northern Ethiopia.
#ethiopia #tigray #tplf #usvisaban #marcorubio #peaceinethiopia #hornofafrica
20 hours ago
ሰበር መረጃ‼️አሜሪካ በህወሓት ላይ እገዳ‼️
አሜሪካ በህወሓት (TPLF) አባላት እና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ እገዳ ጣለች።
የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ በሰሜን ኢትዮጵያ እንዲሁም በመላ ቀጠና ያለውን ሰላምና ደህንነት አደጋ ላይ ጥለዋል ባሏቸው የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አባላት እና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ የቪዛ ገደብ መጣሉን አስታውቀዋል።
ውሳኔው የተላለፈው በስደተኞችና ዜግነት አዋጅ አንቀጽ 212(a)(3)(C) በተሰጣቸው ስልጣን መሰረት መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ እገዳው በትግራይ ክልል ያለውን ቀውስ ለመፍታት የሚደረገውን ጥረት በሚያስተጓጉሉ " አክራሪ አቋም " ባላቸው አባላትና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ ያነጣጠረ መሆኑን ገልጸዋል።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፣ በህወሓት አመራሮችና በኢትዮጵያ መንግሥት መካከል እየተባባሰ የመጣው ውጥረት የሰሜን ኢትዮጵያን ሰላም ዳግም ስጋት ላይ መጣሉን ጠቅሷል።
በተለይም በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ በትግራይ የፀጥታ ኃይሎች (TSF) እና በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት (ENDF) መካከል የተከሰተው ቀጥተኛ ግጭት የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ የተገኘውን አንጻራዊ መረጋጋት የሚፈታተን መሆኑ አመልክቷል።
አሜሪካ በሰላምና በክብር መኖር የሚፈልገውን የትግራይን ጨምሮ መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብ መደገፏን እንደምትቀጥል የገለጸው መግለጫው፤ በክልሉ ሰላምና መረጋጋትን በሚያናጉ አካላት ላይ ተጠያቂነትን ለማስፈን ያሉትን አማራጮች ሁሉ ጥቅም ላይ እንደምታውል አስታውቃለች።
የቪዛ ማዕቀብ የተጣለባቸው የህወሓት (TPLF) አመራሮች እና ቤተሰቦቻቸው ስም በይፋ አልተገለጸም።
Seledadotio
Seledadotio
አሜሪካ በህወሓት (TPLF) አባላት እና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ እገዳ ጣለች።
የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ በሰሜን ኢትዮጵያ እንዲሁም በመላ ቀጠና ያለውን ሰላምና ደህንነት አደጋ ላይ ጥለዋል ባሏቸው የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አባላት እና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ የቪዛ ገደብ መጣሉን አስታውቀዋል።
ውሳኔው የተላለፈው በስደተኞችና ዜግነት አዋጅ አንቀጽ 212(a)(3)(C) በተሰጣቸው ስልጣን መሰረት መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ እገዳው በትግራይ ክልል ያለውን ቀውስ ለመፍታት የሚደረገውን ጥረት በሚያስተጓጉሉ " አክራሪ አቋም " ባላቸው አባላትና የቅርብ ቤተሰቦቻቸው ላይ ያነጣጠረ መሆኑን ገልጸዋል።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፣ በህወሓት አመራሮችና በኢትዮጵያ መንግሥት መካከል እየተባባሰ የመጣው ውጥረት የሰሜን ኢትዮጵያን ሰላም ዳግም ስጋት ላይ መጣሉን ጠቅሷል።
በተለይም በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ በትግራይ የፀጥታ ኃይሎች (TSF) እና በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት (ENDF) መካከል የተከሰተው ቀጥተኛ ግጭት የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ የተገኘውን አንጻራዊ መረጋጋት የሚፈታተን መሆኑ አመልክቷል።
አሜሪካ በሰላምና በክብር መኖር የሚፈልገውን የትግራይን ጨምሮ መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብ መደገፏን እንደምትቀጥል የገለጸው መግለጫው፤ በክልሉ ሰላምና መረጋጋትን በሚያናጉ አካላት ላይ ተጠያቂነትን ለማስፈን ያሉትን አማራጮች ሁሉ ጥቅም ላይ እንደምታውል አስታውቃለች።
የቪዛ ማዕቀብ የተጣለባቸው የህወሓት (TPLF) አመራሮች እና ቤተሰቦቻቸው ስም በይፋ አልተገለጸም።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
2 days ago
u12e8u12a8u1230u1228u12cd u1261u12f5u1295 u1328u12abu129d u12e8u1326u122du1290u1275 u12a0u12cbu1305 | Ethio Melhik | TPLF | War Proclamation |","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[],"color_ranges":[]},"id":"UzpfSTEwMDA2NDMyNTY2NjA0NDpWSzoxMDMwNjY3MTkzMjQ2Mzk2
የከሰረው ቡድን ጨካኝ የጦርነት አዋጅ | Ethio Melhik | TPLF | War Proclamation |
3 days ago
u12e8u12a8u1230u1228u12cd u1261u12f5u1295 u1328u12abu129d u12e8u1326u122du1290u1275 u12a0u12cbu1305 | Ethio Melhik | TPLF | War Proclamation | #ethiomelhik #nationalsecurity #abiyahmed #berhanujula #tplfcrisis #ethiopianarmy ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
የከሰረው ቡድን ጨካኝ የጦርነት አዋጅ | Ethio Melhik | TPLF | War Proclamation | #ethiomelhik #nationalsecurity #abiyahmed #berhanujula #tplfcrisis #ethiopianarmy
1 month ago
በኮስቲ ከተማ በሚገኝ የነዳጅ ማከማቻ ላይ የድሮን ጥቃት ተሰነዘረ
በሱዳን ዋይት ናይል ግዛት በምትገኘው ኮስቲ ከተማ፣ ራባክን በሚያዋስነው አቅጣጫ በሚገኝ የነዳጅ ማከማቻ ዴፖ ላይ የፈጣን ድጋፍ ሰጪ ኃይሎች የድሮን ጥቃት መፈጸማቸው ተዘገበ።
በኬናና ኢንዱስትሪ ኮምፕሌክስ ውስጥ የሚገኙ የነዳጅ ታንከሮች እና የኤታኖል ማምረቻ ክፍሎች ላይ ያነጣጠረ ሲሆን፣ በቦታው ላይ ከፍተኛ የእሳት አደጋ መከሰቱ ተገልጿል።
የሱዳን መገናኛ ብዙኃን እና ወታደራዊ ምንጮች ድሮኖቹ የተነሱት #ከኢትዮጵያ ግዛት (በተለይም ከባሕር ዳር አየር ማረፊያ) እንደሆነ በድጋሚ ክስ አቅርበዋል።የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ግንቦት 2026 በሰጠው መግለጫ፤ "ክሱ መሰረተ ቢስ ነው" በማለት ውድቅ አድርጎታል። ይልቁንም የሱዳን ጦር ለህወሓት (TPLF) ታጣቂዎች ድጋፍ እየሰጠ ነው ሲል መልሶ ከሷል።
ይህንን ክስተት ተከትሎ ሱዳን በኢትዮጵያ የሚገኘውን አምባሳደሯን ለምክክር ወደ ካርቱም መጥራቷ ተሰምቷል። ይህም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ወደ ከፋ ደረጃ እየተሸጋገረ መሆኑን ያሳያል።
seledadotio
seledadotio
በሱዳን ዋይት ናይል ግዛት በምትገኘው ኮስቲ ከተማ፣ ራባክን በሚያዋስነው አቅጣጫ በሚገኝ የነዳጅ ማከማቻ ዴፖ ላይ የፈጣን ድጋፍ ሰጪ ኃይሎች የድሮን ጥቃት መፈጸማቸው ተዘገበ።
በኬናና ኢንዱስትሪ ኮምፕሌክስ ውስጥ የሚገኙ የነዳጅ ታንከሮች እና የኤታኖል ማምረቻ ክፍሎች ላይ ያነጣጠረ ሲሆን፣ በቦታው ላይ ከፍተኛ የእሳት አደጋ መከሰቱ ተገልጿል።
የሱዳን መገናኛ ብዙኃን እና ወታደራዊ ምንጮች ድሮኖቹ የተነሱት #ከኢትዮጵያ ግዛት (በተለይም ከባሕር ዳር አየር ማረፊያ) እንደሆነ በድጋሚ ክስ አቅርበዋል።የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ግንቦት 2026 በሰጠው መግለጫ፤ "ክሱ መሰረተ ቢስ ነው" በማለት ውድቅ አድርጎታል። ይልቁንም የሱዳን ጦር ለህወሓት (TPLF) ታጣቂዎች ድጋፍ እየሰጠ ነው ሲል መልሶ ከሷል።
ይህንን ክስተት ተከትሎ ሱዳን በኢትዮጵያ የሚገኘውን አምባሳደሯን ለምክክር ወደ ካርቱም መጥራቷ ተሰምቷል። ይህም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ወደ ከፋ ደረጃ እየተሸጋገረ መሆኑን ያሳያል።
seledadotio
seledadotio
1 month ago
ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል የትግራይ ክልል ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ!
ዛሬ በተካሄደው 6ኛው ዘመን 6ኛው መደበኛ የትግራይ ምክር ቤት ጉባኤ ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል በአብዛኛው ድምፅ የክልሉ ፕሬዝዳንት ሆነው በይፋ ተመርጠዋል።
በዚሁ ስብሰባ ላይ ወይዘሮ ኪሮስ ሐጎስ አፈ-ጉባኤ፣ ወይዘሮ ምህረት በርሄ ደግሞ ምክትል አፈ-ጉባኤ ሆነው ተሰይመዋል።
ምክር ቤቱ ስራውን በይፋ የጀመረው የፕሪቶሪያው ስምምነት በፌደራል መንግስቱ በኩል ተጥሷል በሚል ሲሆን፣ አዲሱ ፕሬዝዳንትም እስከ ቀጣዩ ስብሰባ ድረስ በአስፈፃሚው አካል ላይ አስፈላጊውን ማስተካከያና ሹመት እንዲያደርጉ ሙሉ ስልጣን ተሰጥቷቸዋል።
ይህ እርምጃ በትግራይ ፖለቲካዊ መድረክ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ሲሆን፣ ከፌደራል መንግስቱ ጋር ያለውን ግንኙነት ወዴት ሊያመራው እንደሚችል የብዙዎች መነጋገሪያ ሆኗል።
Via TPLF
ዛሬ በተካሄደው 6ኛው ዘመን 6ኛው መደበኛ የትግራይ ምክር ቤት ጉባኤ ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል በአብዛኛው ድምፅ የክልሉ ፕሬዝዳንት ሆነው በይፋ ተመርጠዋል።
በዚሁ ስብሰባ ላይ ወይዘሮ ኪሮስ ሐጎስ አፈ-ጉባኤ፣ ወይዘሮ ምህረት በርሄ ደግሞ ምክትል አፈ-ጉባኤ ሆነው ተሰይመዋል።
ምክር ቤቱ ስራውን በይፋ የጀመረው የፕሪቶሪያው ስምምነት በፌደራል መንግስቱ በኩል ተጥሷል በሚል ሲሆን፣ አዲሱ ፕሬዝዳንትም እስከ ቀጣዩ ስብሰባ ድረስ በአስፈፃሚው አካል ላይ አስፈላጊውን ማስተካከያና ሹመት እንዲያደርጉ ሙሉ ስልጣን ተሰጥቷቸዋል።
ይህ እርምጃ በትግራይ ፖለቲካዊ መድረክ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ሲሆን፣ ከፌደራል መንግስቱ ጋር ያለውን ግንኙነት ወዴት ሊያመራው እንደሚችል የብዙዎች መነጋገሪያ ሆኗል።
Via TPLF
Sponsored by
Surafel
4 months ago
የህወሓት ወታደራዊ ክንፍ ከፍተኛ መኮንኖች አዲስ አበባ ገቡ
በህወሓት (TPLF) ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች እና በድርጅቱ የፖለቲካ መዋቅር መካከል ያለው ልዩነት ከመቼውም ጊዜ በላይ እየሰፋ መምጣቱን የሚያሳዩ መረጃዎች እየወጡ ነው።
ይህ እንቅስቃሴ በህወሓት የውስጥ አንድነት ላይ ከፍተኛ ጥያቄ ያስነሳ ሲሆን፤ ድርጅቱ ለዓመታት ሲመካበት የነበረው የወታደራዊ መዋቅር ቁጥጥር እየላላ መምጣቱን ያመላክታል።
ወደ መዲናዋ አዲስ አበባ ከገቡት ከፍተኛ መኮንኖች መካከል ብሪጋዴር ጀነራል ጉዕሽ ገብረ አንዱ ናቸው።
ጀነራሉ ቀደም ሲል በህወሓት ቁጥጥር ስር ውለው በእስር ላይ የነበሩ ሲሆን፣ በቅርቡ በዋስ ተለቀው ጉዟቸውን ወደ አዲስ አበባ ማድረጋቸው የሁኔታውን ውስብስብነት ያሳያል።
ከእሳቸው ጋርም ኮሎኔል ከበደ ፍቃዱ እና ኮሎኔል ንጉስ ወልደገብርኤል (ወለጋ) የተባሉ መኮንኖች አብረው መግባታቸው ተረጋግጧል።
እነዚህ መኮንኖች ድርጅቱን "ለግል ወይም ለቡድን ጥቅም ሰራዊቱን እንደ ንብረት ይጠቀማል" በሚል እንደሚከሱ ተሰምቷል።
seledadotio
seledadotio
በህወሓት (TPLF) ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች እና በድርጅቱ የፖለቲካ መዋቅር መካከል ያለው ልዩነት ከመቼውም ጊዜ በላይ እየሰፋ መምጣቱን የሚያሳዩ መረጃዎች እየወጡ ነው።
ይህ እንቅስቃሴ በህወሓት የውስጥ አንድነት ላይ ከፍተኛ ጥያቄ ያስነሳ ሲሆን፤ ድርጅቱ ለዓመታት ሲመካበት የነበረው የወታደራዊ መዋቅር ቁጥጥር እየላላ መምጣቱን ያመላክታል።
ወደ መዲናዋ አዲስ አበባ ከገቡት ከፍተኛ መኮንኖች መካከል ብሪጋዴር ጀነራል ጉዕሽ ገብረ አንዱ ናቸው።
ጀነራሉ ቀደም ሲል በህወሓት ቁጥጥር ስር ውለው በእስር ላይ የነበሩ ሲሆን፣ በቅርቡ በዋስ ተለቀው ጉዟቸውን ወደ አዲስ አበባ ማድረጋቸው የሁኔታውን ውስብስብነት ያሳያል።
ከእሳቸው ጋርም ኮሎኔል ከበደ ፍቃዱ እና ኮሎኔል ንጉስ ወልደገብርኤል (ወለጋ) የተባሉ መኮንኖች አብረው መግባታቸው ተረጋግጧል።
እነዚህ መኮንኖች ድርጅቱን "ለግል ወይም ለቡድን ጥቅም ሰራዊቱን እንደ ንብረት ይጠቀማል" በሚል እንደሚከሱ ተሰምቷል።
seledadotio
seledadotio
6 months ago
አብይ ቀጥቅጦ ነው ያሸነፈን''‼️ የትግራይን ጀኖሳይድ የፈፀመው ፋኖ እና ሻቢያ ነው'' የጠቅላይ ሚንስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ አቶ ጌታቸው ረዳ‼️
👉ፋኖ ከፌደራል መንግስት ጋር ግጭት የገባው ፕሪቶሪያ ተፈረመ ብሎ ነው፣ሌላ ጥያቄ የለውም።
👉''ተፈናቃዮች እንዳይመለሱ አግቶ የያዘው ህወሓት ነው፣ህወሓት ተፈናቃዮችን አግቶ እያስራበ ነው''
👉"ፋኖ ጋሸና ደረሰ ብሎ መንግሥት የሚፈርስ የሚመስለው ብዙ ሰው አለ"
ልጅ ሁኘ እልኸኛ ነበርኩ ሰውም ልምታህ ካለኝ ጭቅጭቅ ውስጥ ገብቼ ስስ ብልት ካገኘው ምናምን እልና ግን አንድ አንድ ጊዜ ደግሞ ማሰብ አለብህ መጀመሪያ ዙር ትሞክርና ከቀጠቀጠህ ትመክራለህ ከዚያ የሆነ ሰአት ላይ ገላጋይ ቢመጣ ጥሩ ነው።
ነገር ግን እየወደክ እየተነሳህ አሁንም ካልጣልኩት የምትል ከሆነ ስህተት ነው፣ አዕምሮ የለህም ማለት ነው በማለት tplfን ወርፈዋል። ባለፈው ጦርነት የTplf አመራሮች አድስ አበባ እንገባለን በሚል illusion (ቅዠት) ነው ጦርነት የገባነው።
አሁንም የህወሃት አመራሮች አድስ አበባ እንገባለን በሚል ጦርነት ለማስነሳት እየቆሰቁሱ ነው ግን አይቻልም አድስ አበባ በባቡር መምጣት ይችላሉ እንጅ በጦርነት ግን አይሆንም በማለት የጠቅላይ ሚንስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ አቶ ጌታቸው ረዳ በNBC ETHIOPIA ጣቢያ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል።
ጨምረውም አቶ ጌታቸው ረዳ የሰሜኑ ጦርነት ከመጀመሩ በፊት ''ጠቅላይ ሚስትሩ ግጭት ውስጥ ከገባን ሻቢያ ይጠቀምብናል ላስቆመው አልችል፣ ልዩነታችንን አቻችለን ብንሰራ ነው የሚያዋጣን ብለውን ነበር በሰአቱ ግን ማንም የተቀበላቸው አመራር አልነበረም በማለት የምስክርነት ቃል የሚመስል ከወትሮው የተለየ መልዕክት ተናግረዋል።
ሌላው ደግሞ የትግራይን ጀኖሳይድ የፈፀመው ፋኖ እና ሻዕቢያ ነው'' ትግራይ ውስጥ እኮ ያልገባ የለም እድል ገጠመኝ ያለ ማንኛውም የግል ሽፍታ የነበረ ሳይቀር ነው ትግራይ ላይ የተረባረበው በማለት መንግስትን ከትግራዩ ጀኖሳይድ ተጠያቂነት ገለል ለማድረግ በሚመስል አኳኳን ሀሳባቸውን በውይይቱ ተንፍሰዋል።
seledadotio
seledadotio
👉ፋኖ ከፌደራል መንግስት ጋር ግጭት የገባው ፕሪቶሪያ ተፈረመ ብሎ ነው፣ሌላ ጥያቄ የለውም።
👉''ተፈናቃዮች እንዳይመለሱ አግቶ የያዘው ህወሓት ነው፣ህወሓት ተፈናቃዮችን አግቶ እያስራበ ነው''
👉"ፋኖ ጋሸና ደረሰ ብሎ መንግሥት የሚፈርስ የሚመስለው ብዙ ሰው አለ"
ልጅ ሁኘ እልኸኛ ነበርኩ ሰውም ልምታህ ካለኝ ጭቅጭቅ ውስጥ ገብቼ ስስ ብልት ካገኘው ምናምን እልና ግን አንድ አንድ ጊዜ ደግሞ ማሰብ አለብህ መጀመሪያ ዙር ትሞክርና ከቀጠቀጠህ ትመክራለህ ከዚያ የሆነ ሰአት ላይ ገላጋይ ቢመጣ ጥሩ ነው።
ነገር ግን እየወደክ እየተነሳህ አሁንም ካልጣልኩት የምትል ከሆነ ስህተት ነው፣ አዕምሮ የለህም ማለት ነው በማለት tplfን ወርፈዋል። ባለፈው ጦርነት የTplf አመራሮች አድስ አበባ እንገባለን በሚል illusion (ቅዠት) ነው ጦርነት የገባነው።
አሁንም የህወሃት አመራሮች አድስ አበባ እንገባለን በሚል ጦርነት ለማስነሳት እየቆሰቁሱ ነው ግን አይቻልም አድስ አበባ በባቡር መምጣት ይችላሉ እንጅ በጦርነት ግን አይሆንም በማለት የጠቅላይ ሚንስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ አቶ ጌታቸው ረዳ በNBC ETHIOPIA ጣቢያ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል።
ጨምረውም አቶ ጌታቸው ረዳ የሰሜኑ ጦርነት ከመጀመሩ በፊት ''ጠቅላይ ሚስትሩ ግጭት ውስጥ ከገባን ሻቢያ ይጠቀምብናል ላስቆመው አልችል፣ ልዩነታችንን አቻችለን ብንሰራ ነው የሚያዋጣን ብለውን ነበር በሰአቱ ግን ማንም የተቀበላቸው አመራር አልነበረም በማለት የምስክርነት ቃል የሚመስል ከወትሮው የተለየ መልዕክት ተናግረዋል።
ሌላው ደግሞ የትግራይን ጀኖሳይድ የፈፀመው ፋኖ እና ሻዕቢያ ነው'' ትግራይ ውስጥ እኮ ያልገባ የለም እድል ገጠመኝ ያለ ማንኛውም የግል ሽፍታ የነበረ ሳይቀር ነው ትግራይ ላይ የተረባረበው በማለት መንግስትን ከትግራዩ ጀኖሳይድ ተጠያቂነት ገለል ለማድረግ በሚመስል አኳኳን ሀሳባቸውን በውይይቱ ተንፍሰዋል።
seledadotio
seledadotio
7 months ago
"ሊፈርስ ከጫፍ ደርሷል"ምንጮች
የፌደራል መንግስቱ እና የትግራይ ክልል አመራሮች ከሁለት አመት ደም አፋሳሽ ጦርነት በኋላ የደረሱበት የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት፣ በተለያዩ አዳዲስ ውዝግቦች ምክንያት "ሊፈርስ ከጫፍ ደርሷል" ሲሉ የተለያዩ ሪፖርቶች አመልክተዋል።
ውጥረቱ በዋናነት የተከሰተው፣ በDDR (ትጥቅ መፍታት፣ ከሠራዊት ማሰናበት እና መልሶ ማቋቋም) ስምምነት መሠረት ለክልሉ ታጣቂዎች ከፌደራል መንግስቱ ይላክ የነበረው ድጎማ እና በጀት መቋረጡን ተከትሎ መሆኑን ዘገባዎቹ አመልክተዋል።
ይህ የDDR በጀት መቋረጥ በክልሉ ውስጥ አዲስ የፋይናንስ ቀውስ የፈጠረ ሲሆን፣ አብዛኞቹ የትግራይ ክልል የመንግስት ሰራተኞች የሁለት ወር ደመወዝ እንዳልተከፈላቸው ከጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ተናግረዋል።
ለዚህም ምክንያት፣ አንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የክልሉ ባለስልጣን እንደተናገሩት፣ የDDR በጀቱ በመቋረጡ የክልሉ አስተዳደር "ለሕዝቡ አገልግሎት (ለሲቪል ሰራተኞች) የተመደበውን መደበኛ በጀት፣ ለታጣቂዎቹ ኃይሎች ደመወዝ ክፍያ እያዋለው ነው" ብለዋል።
ምንም እንኳን ከፌደራል መንግስት የሚላከው መደበኛ በጀት ባይቋረጥም፣ በክልሉ አመራሮች በኩል በጀት የማዛወር ስራ እየተሰራ መሆኑ፣ የህዝብ አገልጋዮች ደመወዝ እንዲያጡ ማድረጉን ምንጮቹ ተናግረዋል። ከቀናት በፊትም የተለያዩ የመንግስት ሰራተኞች "ደሞዛችን ይከፈለን" የሚል ተቃውሞ በተለያዩ የትግራይ ከተሞች ማሰማታቸው ይታወሳል።
ከDDR በጀት መቋረጥ በተጨማሪ፣ ከዚህ ቀደም የትግራይ ኃይሎች የአፋር ክልልን ድንበር ጥሰው የገቡ ቢሆንም በኋላ ላይ ለቀው ቢወጡም፣ ድርጊቱ ራሱ በስምምነቱ ላይ የፈጠረው ስጋት ከፍተኛ እንደሆነ ተገልጿል።
በሌላ በኩል፣ የህዝቡን እንግልት አባብሷል የተባለ የነዳጅ እጥረት በክልሉ ተከስቷል። ምንም እንኳን ነዳጅ ወደ ክልሉ እየገባ መሆኑ ቢነገርም፣ "ነዳጁ የት እየደረሰ እንደሆነ አይታወቅም" ያሉት ነዋሪዎች፣ ህዝቡ በከፍተኛ የነዳጅ እጥረት እየተሰቃየ መሆኑን ገልጸዋል።
በክልሉ በተፈጠረው በዚህ አዲስ ውጥረት እና አስተዳደራዊ ችግር ዙሪያ፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩ አካል የሆኑት ጄኔራል ታደሰ ወረደ ዝምታን መምረጣቸው የተለያዩ ጥያቄዎችን አስነስቷል።
ጄኔራሉ በጉዳዩ ላይ አስተያየት ከመስጠት መቆጠባቸው፣ "ምናልባት በህወሓት (TPLF) ሃይሎች ተጽዕኖ ስር ወድቀው ይሆን?" የሚል ግምት እንዲፈጠር ማድረጉን ዘሐበሻ ዘግቧል።
seledadotio
seledadotio
የፌደራል መንግስቱ እና የትግራይ ክልል አመራሮች ከሁለት አመት ደም አፋሳሽ ጦርነት በኋላ የደረሱበት የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት፣ በተለያዩ አዳዲስ ውዝግቦች ምክንያት "ሊፈርስ ከጫፍ ደርሷል" ሲሉ የተለያዩ ሪፖርቶች አመልክተዋል።
ውጥረቱ በዋናነት የተከሰተው፣ በDDR (ትጥቅ መፍታት፣ ከሠራዊት ማሰናበት እና መልሶ ማቋቋም) ስምምነት መሠረት ለክልሉ ታጣቂዎች ከፌደራል መንግስቱ ይላክ የነበረው ድጎማ እና በጀት መቋረጡን ተከትሎ መሆኑን ዘገባዎቹ አመልክተዋል።
ይህ የDDR በጀት መቋረጥ በክልሉ ውስጥ አዲስ የፋይናንስ ቀውስ የፈጠረ ሲሆን፣ አብዛኞቹ የትግራይ ክልል የመንግስት ሰራተኞች የሁለት ወር ደመወዝ እንዳልተከፈላቸው ከጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ተናግረዋል።
ለዚህም ምክንያት፣ አንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የክልሉ ባለስልጣን እንደተናገሩት፣ የDDR በጀቱ በመቋረጡ የክልሉ አስተዳደር "ለሕዝቡ አገልግሎት (ለሲቪል ሰራተኞች) የተመደበውን መደበኛ በጀት፣ ለታጣቂዎቹ ኃይሎች ደመወዝ ክፍያ እያዋለው ነው" ብለዋል።
ምንም እንኳን ከፌደራል መንግስት የሚላከው መደበኛ በጀት ባይቋረጥም፣ በክልሉ አመራሮች በኩል በጀት የማዛወር ስራ እየተሰራ መሆኑ፣ የህዝብ አገልጋዮች ደመወዝ እንዲያጡ ማድረጉን ምንጮቹ ተናግረዋል። ከቀናት በፊትም የተለያዩ የመንግስት ሰራተኞች "ደሞዛችን ይከፈለን" የሚል ተቃውሞ በተለያዩ የትግራይ ከተሞች ማሰማታቸው ይታወሳል።
ከDDR በጀት መቋረጥ በተጨማሪ፣ ከዚህ ቀደም የትግራይ ኃይሎች የአፋር ክልልን ድንበር ጥሰው የገቡ ቢሆንም በኋላ ላይ ለቀው ቢወጡም፣ ድርጊቱ ራሱ በስምምነቱ ላይ የፈጠረው ስጋት ከፍተኛ እንደሆነ ተገልጿል።
በሌላ በኩል፣ የህዝቡን እንግልት አባብሷል የተባለ የነዳጅ እጥረት በክልሉ ተከስቷል። ምንም እንኳን ነዳጅ ወደ ክልሉ እየገባ መሆኑ ቢነገርም፣ "ነዳጁ የት እየደረሰ እንደሆነ አይታወቅም" ያሉት ነዋሪዎች፣ ህዝቡ በከፍተኛ የነዳጅ እጥረት እየተሰቃየ መሆኑን ገልጸዋል።
በክልሉ በተፈጠረው በዚህ አዲስ ውጥረት እና አስተዳደራዊ ችግር ዙሪያ፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩ አካል የሆኑት ጄኔራል ታደሰ ወረደ ዝምታን መምረጣቸው የተለያዩ ጥያቄዎችን አስነስቷል።
ጄኔራሉ በጉዳዩ ላይ አስተያየት ከመስጠት መቆጠባቸው፣ "ምናልባት በህወሓት (TPLF) ሃይሎች ተጽዕኖ ስር ወድቀው ይሆን?" የሚል ግምት እንዲፈጠር ማድረጉን ዘሐበሻ ዘግቧል።
seledadotio
seledadotio
8 months ago
በመላው ኢትዮጵያ፣ የዛሬው ዕለት ጥቅምት 24 በ ሕወሓት (TPLF) ኃይሎች በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ሰሜን ዕዝ ላይ የተፈጸመው ዘግናኝ ጥቃት መታሰቢያ ሆኖ እየዋለ ነው።
ክስተቱ የተፈጸመው አምስት ዓመታት የሞላው ሲሆን፣ ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም. ምሽት ላይ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ "መቼም የማይረሳው ጥቁር ጠባሳ" ተብሎ ይታወሳል።
የዛሬ አምስት ዓመት ምሽት ላይ፣ የትግራይ ክልልን ሲጠብቅ በነበረው የሰሜን ዕዝ ላይ፣ በክልሉ ታጣቂ ኃይሎች የተቀናጀ ጥቃት ተፈጽሟል። ይህ ድርጊት የመከላከያ ሠራዊቱ አባላት ተኝተው በነበሩበት ወይም ለጥቃት ባልተዘጋጁበት ሁኔታ የተፈጸመ በመሆኑ፣ የመንግስት ባለሥልጣናት እና የሠራዊቱ አባላት በገዛ ወገን የተፈጸመ ከፍተኛ የክህደት ወንጀል በማለት ይገልጹታል።
የጥቃቱ ዋና ዒላማዎች የነበሩት የሰሜን ዕዝ ዋና ዋና የጦር ካምፖች እና የጦር መሣሪያ ግምጃ ቤቶች ሲሆኑ፣ ዓላማውም የመከላከያ ሠራዊቱን ማዳከም እና የሀገሪቱን ሰንሰለት መበጠስ ነበር።
በወቅቱ በሺዎች የሚቆጠሩ የሠራዊት አባላት በመገደል፣ በመቁሰል ወይም በምርኮ መያዛቸው የተዘገበ ሲሆን፣ ጥቃቱ ለሁለት ዓመታት ለዘለቀው ሰሜናዊ የኢትዮጵያ ጦርነት መነሻና ዋነኛ ምክንያት ሆኗል።
በዛሬው ዕለት በመላ ሀገሪቱ "እንዳይደገም፤ መቼም አንረሳውም" በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ዝግጅቶች እየታሰበ ነው።
seledadotio
seledadotio
ክስተቱ የተፈጸመው አምስት ዓመታት የሞላው ሲሆን፣ ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም. ምሽት ላይ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ "መቼም የማይረሳው ጥቁር ጠባሳ" ተብሎ ይታወሳል።
የዛሬ አምስት ዓመት ምሽት ላይ፣ የትግራይ ክልልን ሲጠብቅ በነበረው የሰሜን ዕዝ ላይ፣ በክልሉ ታጣቂ ኃይሎች የተቀናጀ ጥቃት ተፈጽሟል። ይህ ድርጊት የመከላከያ ሠራዊቱ አባላት ተኝተው በነበሩበት ወይም ለጥቃት ባልተዘጋጁበት ሁኔታ የተፈጸመ በመሆኑ፣ የመንግስት ባለሥልጣናት እና የሠራዊቱ አባላት በገዛ ወገን የተፈጸመ ከፍተኛ የክህደት ወንጀል በማለት ይገልጹታል።
የጥቃቱ ዋና ዒላማዎች የነበሩት የሰሜን ዕዝ ዋና ዋና የጦር ካምፖች እና የጦር መሣሪያ ግምጃ ቤቶች ሲሆኑ፣ ዓላማውም የመከላከያ ሠራዊቱን ማዳከም እና የሀገሪቱን ሰንሰለት መበጠስ ነበር።
በወቅቱ በሺዎች የሚቆጠሩ የሠራዊት አባላት በመገደል፣ በመቁሰል ወይም በምርኮ መያዛቸው የተዘገበ ሲሆን፣ ጥቃቱ ለሁለት ዓመታት ለዘለቀው ሰሜናዊ የኢትዮጵያ ጦርነት መነሻና ዋነኛ ምክንያት ሆኗል።
በዛሬው ዕለት በመላ ሀገሪቱ "እንዳይደገም፤ መቼም አንረሳውም" በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ዝግጅቶች እየታሰበ ነው።
seledadotio
seledadotio
Comments