3 months ago
አሜሪካ ለመግባት በሚያስገድድደው የ15 ሺሕ ዶላር የገንዘብ ማስያዣ ደንብ ኢትዮጵያ ተካተተች
#ethiopia | የዩናይትድ ስቴትስ የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ መስተዳድር፣ ወደ አሜሪካ መግባት በሚፈልጉ የተወሰኑ ሀገራት ዜጎች ላይ አዲስ የገንዘብ ማስያዣ መመሪያ ማውጣቱን የጀርመን ድምፅ ዘግቧል። ይህ መመሪያ ከመጪው መጋቢት 24 ጀምሮ ተግባራዊ መሆን እንደሚጀምር ተገልጿል።
የደንቡ ዋና ዋና ነጥቦች፦
* የገንዘብ መጠኑ፦ መመሪያው የሚመለከታቸው ሀገራት ዜጎች የአሜሪካ ቪዛ ለማግኘት ከሌሎች መስፈርቶች በተጨማሪ 15,000 ዶላር ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
* የቪዛ ዓይነቶች፦ ማስያዣው ግዴታ የሚሆነው ለሥራ (B1) እና ለጉብኝት (B2) ቪዛ አመልካቾች ላይ ነው።
* የተካተቱ ሀገራት፦ መጀመሪያ ላይ የ38 ሀገራት ዜጎችን ብቻ ይለይ የነበረው ዝርዝር፣ አሁን ኢትዮጵያን ጨምሮ የሌሎች 12 ሀገራት ዜጎች ተካተውበታል። በአጠቃላይ በዝርዝሩ ውስጥ የተካተቱት የ50 ሀገራት ዜጎች ሲሆኑ፣ አብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት ናቸው።
* የገንዘብ አመላለስ፦ ተጓዦች ቆይታቸውን አጠናቅቀው ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ ያስያዙት ገንዘብ እንደሚመለስላቸው ተጠቁሟል።
ይህ አዲስ አሰራር በተለይ በጎብኝዎችና በንግድ ተጓዦች ላይ የሚኖረው ተፅዕኖ ከፍተኛ እንደሚሆን እየተነገረ ይገኛል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #usa #visapolicy #ethiopia #travelnews #usvisa #breakingnews #africa #donaldtrump
#ethiopia | የዩናይትድ ስቴትስ የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ መስተዳድር፣ ወደ አሜሪካ መግባት በሚፈልጉ የተወሰኑ ሀገራት ዜጎች ላይ አዲስ የገንዘብ ማስያዣ መመሪያ ማውጣቱን የጀርመን ድምፅ ዘግቧል። ይህ መመሪያ ከመጪው መጋቢት 24 ጀምሮ ተግባራዊ መሆን እንደሚጀምር ተገልጿል።
የደንቡ ዋና ዋና ነጥቦች፦
* የገንዘብ መጠኑ፦ መመሪያው የሚመለከታቸው ሀገራት ዜጎች የአሜሪካ ቪዛ ለማግኘት ከሌሎች መስፈርቶች በተጨማሪ 15,000 ዶላር ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
* የቪዛ ዓይነቶች፦ ማስያዣው ግዴታ የሚሆነው ለሥራ (B1) እና ለጉብኝት (B2) ቪዛ አመልካቾች ላይ ነው።
* የተካተቱ ሀገራት፦ መጀመሪያ ላይ የ38 ሀገራት ዜጎችን ብቻ ይለይ የነበረው ዝርዝር፣ አሁን ኢትዮጵያን ጨምሮ የሌሎች 12 ሀገራት ዜጎች ተካተውበታል። በአጠቃላይ በዝርዝሩ ውስጥ የተካተቱት የ50 ሀገራት ዜጎች ሲሆኑ፣ አብዛኞቹ የአፍሪካ ሀገራት ናቸው።
* የገንዘብ አመላለስ፦ ተጓዦች ቆይታቸውን አጠናቅቀው ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ ያስያዙት ገንዘብ እንደሚመለስላቸው ተጠቁሟል።
ይህ አዲስ አሰራር በተለይ በጎብኝዎችና በንግድ ተጓዦች ላይ የሚኖረው ተፅዕኖ ከፍተኛ እንደሚሆን እየተነገረ ይገኛል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #usa #visapolicy #ethiopia #travelnews #usvisa #breakingnews #africa #donaldtrump
5 months ago
🇺🇸 አሜሪካ የቋሚ ነዋሪነት ቪዛ ሂደትን ኢትዮጵያን ጨምሮ በ75 ሀገራት ላይ ልታቆም ነው
#ethiopia | የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት የዲቪ (Diversity Visa) እና ሌሎች የቋሚ ነዋሪነት ቪዛዎችን (Immigrant Visa) የመስጠት ሂደት በ75 ሀገራት ላይ ለጊዜው እንዲቋረጥ መወሰኑ ተሰማ። ፎክስ ኒውስ የስቴት ዲፓርትመንትን የውስጥ ማስታወሻ ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው፣ ውሳኔው ከፊታችን ጥር 21 ቀን 2026 ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል።
🇪🇹 ኢትዮጵያ በዝርዝሩ ውስጥ ትገኛለች
የቪዛ ሂደቱ ይቋረጥባቸዋል ከተባሉ ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ አንዷ ስትሆን፣ በተጨማሪም ኤርትራ፣ ግብፅ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሶማሊያ፣ ሩሲያ፣ ብራዚል፣ ፓኪስታን እና ታይላንድ ይገኙበታል።
🔍 የውሳኔው ምክንያት፦ "የመንግስት ድጋፍ ጥገኝነትን መቀነስ"
የስቴት ዲፓርትመንት ቃል አቀባይ ቶሚ ፒጎት እንደገለጹት፣ ይህ እርምጃ የተወሰደው ወደ አሜሪካ የሚገቡ ስደተኞች በመንግስት ድጋፍ (Welfare) ላይ ጥገኛ የሚሆኑበትን ሁኔታ ለመገምገም ነው።
* ጥብቅ መመዘኛ፦ የቪዛ መኮንኖች የአመልካቾችን የጤና ሁኔታ፣ የቋንቋ ክህሎት እና የፋይናንስ አቅም በጥብቅ እንዲመረምሩ ቀደም ብሎ ታዝዘዋል።
* የኢትዮጵያውያን ተሳትፎ፦ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቅርቡ በሰጡት መግለጫ፣ በአሜሪካ ከሚኖሩ የኢትዮጵያ ተወላጆች መካከል 47.6% ያህሉ በቤተሰባቸው ውስጥ ቢያንስ አንድ የመንግስት ድጋፍ ተጠቃሚ እንዳለ መጥቀሳቸው ለውሳኔው እንደ አንድ ምክንያት ተነስተዋል።
⏳ የቪዛ ጠያቂዎች እጣ ፈንታ ምን ይሆናል?
ይህ እገዳ ስቴት ዲፓርትመንት አዲስ መመሪያ እና የግምገማ ውጤት እስኪያወጣ ድረስ ለተወሰነ ጊዜ (ላልተወሰነ ጊዜ ሊሆን ይችላል) የቪዛ ሂደቱ ቆሞ እንደሚቆይ ተገልጿል። ይህም ማለት በእነዚህ ሀገራት ውስጥ የሚገኙ እና የቪዛ ቃለ-መጠይቅ የሚጠባበቁ አመልካቾች ሂደታቸው ይስተጓጎላል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#አሜሪካ #ቪዛ #ኢትዮጵያ #ዲቪ #ስደት #ትራምፕ #ስቴትዲፓርትመንት #usvisa #ethiopia #dv2026 #immigrationnews
#ethiopia | የአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት የዲቪ (Diversity Visa) እና ሌሎች የቋሚ ነዋሪነት ቪዛዎችን (Immigrant Visa) የመስጠት ሂደት በ75 ሀገራት ላይ ለጊዜው እንዲቋረጥ መወሰኑ ተሰማ። ፎክስ ኒውስ የስቴት ዲፓርትመንትን የውስጥ ማስታወሻ ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው፣ ውሳኔው ከፊታችን ጥር 21 ቀን 2026 ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል።
🇪🇹 ኢትዮጵያ በዝርዝሩ ውስጥ ትገኛለች
የቪዛ ሂደቱ ይቋረጥባቸዋል ከተባሉ ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ አንዷ ስትሆን፣ በተጨማሪም ኤርትራ፣ ግብፅ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሶማሊያ፣ ሩሲያ፣ ብራዚል፣ ፓኪስታን እና ታይላንድ ይገኙበታል።
🔍 የውሳኔው ምክንያት፦ "የመንግስት ድጋፍ ጥገኝነትን መቀነስ"
የስቴት ዲፓርትመንት ቃል አቀባይ ቶሚ ፒጎት እንደገለጹት፣ ይህ እርምጃ የተወሰደው ወደ አሜሪካ የሚገቡ ስደተኞች በመንግስት ድጋፍ (Welfare) ላይ ጥገኛ የሚሆኑበትን ሁኔታ ለመገምገም ነው።
* ጥብቅ መመዘኛ፦ የቪዛ መኮንኖች የአመልካቾችን የጤና ሁኔታ፣ የቋንቋ ክህሎት እና የፋይናንስ አቅም በጥብቅ እንዲመረምሩ ቀደም ብሎ ታዝዘዋል።
* የኢትዮጵያውያን ተሳትፎ፦ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቅርቡ በሰጡት መግለጫ፣ በአሜሪካ ከሚኖሩ የኢትዮጵያ ተወላጆች መካከል 47.6% ያህሉ በቤተሰባቸው ውስጥ ቢያንስ አንድ የመንግስት ድጋፍ ተጠቃሚ እንዳለ መጥቀሳቸው ለውሳኔው እንደ አንድ ምክንያት ተነስተዋል።
⏳ የቪዛ ጠያቂዎች እጣ ፈንታ ምን ይሆናል?
ይህ እገዳ ስቴት ዲፓርትመንት አዲስ መመሪያ እና የግምገማ ውጤት እስኪያወጣ ድረስ ለተወሰነ ጊዜ (ላልተወሰነ ጊዜ ሊሆን ይችላል) የቪዛ ሂደቱ ቆሞ እንደሚቆይ ተገልጿል። ይህም ማለት በእነዚህ ሀገራት ውስጥ የሚገኙ እና የቪዛ ቃለ-መጠይቅ የሚጠባበቁ አመልካቾች ሂደታቸው ይስተጓጎላል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#አሜሪካ #ቪዛ #ኢትዮጵያ #ዲቪ #ስደት #ትራምፕ #ስቴትዲፓርትመንት #usvisa #ethiopia #dv2026 #immigrationnews
10 months ago
የአሜሪካ ቪዛ ማስያዣ ክፍያ ጉዳይ
በአበበ ፈለቀ
#ethiopia | ወደ አሜሪካ የB-1 እና የB-2 የቢዝነስ እና የጉብኝት ቪዛ ለሚጠይቁ ሰወች እንደ ሁኔታው የ5፣ የ10 እና የ15 ሺህ ዶላር ማስያዣ የሚጠይቅ ድንጋጌ መውጣቱ ይታወቃል።
ይሄ ከነሃሴ 14፣ 2017 ዓ/ም ጀምሮ ለአንድ አመት የሚቆየው የሙከራ መርሃ ግብር “ሁሉም ሃገራት ላይ ተፈጻሚ ነው” የሚለው እሳቤ የተሳሳተ ነው። ይሄን ቅድመ ሁኔታ እንዲያሟሉ የሚጠየቁ ሃገራት፣ በአሜሪካ የሃገር ውስጥ ደህንነት መስርያ ቤት ሪፖርት መሰረት፣ ከዚህ ቀደም ወደ አሜሪካ መጥተው ያልተመለሱ ወይም የዘገዩ በርካታ ዜጎች ያሉባቸው ሃገራት እንደሆኑ ነው የተገለጸው።
በዚህም መሰረት በአሁኑ ሰአት ቅድመ ሁኔታው ተግባራዊ እንዲሆንባቸው የተመረጡት የመጀመርያወቹ ሃገራት ማላዊ እና ዛምቢያ ናቸው። እስከ አሁን ባለው መረጃ ከሁለቱ ሃገራት ሌላ ይህ ቅድመ ሁኔታ በየትኛውም ሃገር ላይ ተፈጻሚ አይደለም።
ያም ሆኖ በዚሁ የአንድ አመት የሙከራ መርሃ ግብር ጊዜ ውስጥ ሌሎች ሃገራት በዚሁ ዝርዝር ውስጥ ሊጨመሩ ይችላሉ። ሃገራቱ መጨመራቸው በተገለጸ በ15 ቀናት ውስጥ ቅድመ ሁኔታው ተፈጻሚ ይሆንባቸዋል ማለት ነው።
#usvisa #visausa #visa #b1b2visa #usa #ethiopia #followersreels
በአበበ ፈለቀ
#ethiopia | ወደ አሜሪካ የB-1 እና የB-2 የቢዝነስ እና የጉብኝት ቪዛ ለሚጠይቁ ሰወች እንደ ሁኔታው የ5፣ የ10 እና የ15 ሺህ ዶላር ማስያዣ የሚጠይቅ ድንጋጌ መውጣቱ ይታወቃል።
ይሄ ከነሃሴ 14፣ 2017 ዓ/ም ጀምሮ ለአንድ አመት የሚቆየው የሙከራ መርሃ ግብር “ሁሉም ሃገራት ላይ ተፈጻሚ ነው” የሚለው እሳቤ የተሳሳተ ነው። ይሄን ቅድመ ሁኔታ እንዲያሟሉ የሚጠየቁ ሃገራት፣ በአሜሪካ የሃገር ውስጥ ደህንነት መስርያ ቤት ሪፖርት መሰረት፣ ከዚህ ቀደም ወደ አሜሪካ መጥተው ያልተመለሱ ወይም የዘገዩ በርካታ ዜጎች ያሉባቸው ሃገራት እንደሆኑ ነው የተገለጸው።
በዚህም መሰረት በአሁኑ ሰአት ቅድመ ሁኔታው ተግባራዊ እንዲሆንባቸው የተመረጡት የመጀመርያወቹ ሃገራት ማላዊ እና ዛምቢያ ናቸው። እስከ አሁን ባለው መረጃ ከሁለቱ ሃገራት ሌላ ይህ ቅድመ ሁኔታ በየትኛውም ሃገር ላይ ተፈጻሚ አይደለም።
ያም ሆኖ በዚሁ የአንድ አመት የሙከራ መርሃ ግብር ጊዜ ውስጥ ሌሎች ሃገራት በዚሁ ዝርዝር ውስጥ ሊጨመሩ ይችላሉ። ሃገራቱ መጨመራቸው በተገለጸ በ15 ቀናት ውስጥ ቅድመ ሁኔታው ተፈጻሚ ይሆንባቸዋል ማለት ነው።
#usvisa #visausa #visa #b1b2visa #usa #ethiopia #followersreels
10 months ago
የአሜሪካ የቱሪስት እና የቢዝነስ ቪዛ ፈላጊዎች እስከ 15 ሺ ዶላር ማስያዣ ሊጠየቁ ነው ተባለ
#ethiopia | የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ወደ አገሪቱ ለመግባት የB-1 የቢዝነስ እና የB-2 የቱሪስት ቪዛ ለሚጠይቁ አመልካቾች እስከ 15 ሺህ ዶላር የሚደርስ ገንዘብ በማስያዣነት ሊጠየቁ እንደሚችሉ አስታውቋል።
ይህ በሁለት ሳምንት ውስጥ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል የተባለው የሙከራ ፕሮግራም ከቪዛ ጊዜያቸው በላይ የሚቆዩ ጎብኚዎችን ለመከላከል ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ቢሮ ያወጣው ይህ ማስታወቂያ በርካታ ሰዎች ወደ አገሪቱ ለመግባት የሚያደርጉትን ሂደት አስቸጋሪ ያደርግባቸዋል ተብሏል።
እንደ የፌደራል መንግሥቱ የምዝገባ ማስታወቂያ ከሆነ ይህ አሠራር በቀጣዮቹ 12 ወራት ውስጥ በሙከራነት በተወሰኑ አገራት ላይ ተግባራዊ ይሆናል።
የሙከራ መርሃ ግብሩ አሜሪካ ውስጥ ከቪዛ ጊዜያቸው በላይ ለረጅም ጊዜ የሚቆዩ ዜጎች ባሏቸው አገራት እና የአገር ውስጥ ሰነዶች ላይ የላላ ቁጥጥር በሚያደርጉ አገራት ላይ ተግባራዊ መደረግ ይጀምራል ተብሏል። የእነዚህ አገራት ዜጎች ለቪዛ ሲያመለክቱ 5,000፣ 10,000 ወይም 15,000 ዶላር በማስያዣነት እንዲያቀርቡ ሊጠየቁ እንደሚችሉ ተገልጿል።
ይህ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ አሠራር ይፋ የሆነው የትራምፕ አስተዳደር ወደ አሜሪካ ለመግባት የሚጠየቁ የቪዛ አመልካቾች መስፈርቶችን እያጠናከረ በመጣበት ወቅት ነው። ፕሬዝደንት ትራምፕ ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ ሰነድ አልባ ስደተኞችን ከአገር ማስወጣት እንዲሁም የድንበር ቁጥጥሩን ለማጠናከር በጀት ከፍ የማድረግ እና ወደ አገሪቱ በሕገወጥ መንገድ የገቡ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር የማዋል እርምጃዎችን ሲወስዱ ቆይተዋል። በሰኔ ወር ከ19 አገራት ወደ አሜሪካ ለመግባት የሚያመለክቱ ግለሰቦች ላይ ከብሔራዊ ደኅንነት ጋር በተያያዙ ምክንያቶች የጉዞ እገዳ ጥለዋል።
በትራምፕ የስደተኞች ፖሊሲ ምክንያት የተወሰኑ ጎብኚዎች ወደ አሜሪካ የሚያደርጉትን ጉብኝት እየሰረዙ መሆኑ ይሰማል። ከነሐሴ 20 ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል የተባለው ይህ አዲሱ የቪዛ ማስያዣ ገንዘብ ፕሮግራም ለአንድ ዓመት ያህል ይቆያል ተብሎ ተገምቷል። #dj #usvisa
#ethiopia | የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ወደ አገሪቱ ለመግባት የB-1 የቢዝነስ እና የB-2 የቱሪስት ቪዛ ለሚጠይቁ አመልካቾች እስከ 15 ሺህ ዶላር የሚደርስ ገንዘብ በማስያዣነት ሊጠየቁ እንደሚችሉ አስታውቋል።
ይህ በሁለት ሳምንት ውስጥ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል የተባለው የሙከራ ፕሮግራም ከቪዛ ጊዜያቸው በላይ የሚቆዩ ጎብኚዎችን ለመከላከል ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ቢሮ ያወጣው ይህ ማስታወቂያ በርካታ ሰዎች ወደ አገሪቱ ለመግባት የሚያደርጉትን ሂደት አስቸጋሪ ያደርግባቸዋል ተብሏል።
እንደ የፌደራል መንግሥቱ የምዝገባ ማስታወቂያ ከሆነ ይህ አሠራር በቀጣዮቹ 12 ወራት ውስጥ በሙከራነት በተወሰኑ አገራት ላይ ተግባራዊ ይሆናል።
የሙከራ መርሃ ግብሩ አሜሪካ ውስጥ ከቪዛ ጊዜያቸው በላይ ለረጅም ጊዜ የሚቆዩ ዜጎች ባሏቸው አገራት እና የአገር ውስጥ ሰነዶች ላይ የላላ ቁጥጥር በሚያደርጉ አገራት ላይ ተግባራዊ መደረግ ይጀምራል ተብሏል። የእነዚህ አገራት ዜጎች ለቪዛ ሲያመለክቱ 5,000፣ 10,000 ወይም 15,000 ዶላር በማስያዣነት እንዲያቀርቡ ሊጠየቁ እንደሚችሉ ተገልጿል።
ይህ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ አሠራር ይፋ የሆነው የትራምፕ አስተዳደር ወደ አሜሪካ ለመግባት የሚጠየቁ የቪዛ አመልካቾች መስፈርቶችን እያጠናከረ በመጣበት ወቅት ነው። ፕሬዝደንት ትራምፕ ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ ሰነድ አልባ ስደተኞችን ከአገር ማስወጣት እንዲሁም የድንበር ቁጥጥሩን ለማጠናከር በጀት ከፍ የማድረግ እና ወደ አገሪቱ በሕገወጥ መንገድ የገቡ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር የማዋል እርምጃዎችን ሲወስዱ ቆይተዋል። በሰኔ ወር ከ19 አገራት ወደ አሜሪካ ለመግባት የሚያመለክቱ ግለሰቦች ላይ ከብሔራዊ ደኅንነት ጋር በተያያዙ ምክንያቶች የጉዞ እገዳ ጥለዋል።
በትራምፕ የስደተኞች ፖሊሲ ምክንያት የተወሰኑ ጎብኚዎች ወደ አሜሪካ የሚያደርጉትን ጉብኝት እየሰረዙ መሆኑ ይሰማል። ከነሐሴ 20 ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል የተባለው ይህ አዲሱ የቪዛ ማስያዣ ገንዘብ ፕሮግራም ለአንድ ዓመት ያህል ይቆያል ተብሎ ተገምቷል። #dj #usvisa
Sponsored by
Surafel
Comments