3 days ago
የኢትዮጵያ ታላቅ ወዳጅ:
የፕሮፌሰር ኮሎኔል ኤንሪኮ ፒዬሮ ቦሲ መታሰቢያ
* ጣሊያናዊ ምሁር፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ናቸው
* ባለቤታቸው ወይዘሮ ሳራ የማነ እና ከልጃቸው ካሌብ ጆርጂ ሌጋሲያቸውን ( Legacy ) ለማስቀጠል እየታተሩ ናቸው
#ethiopia | በአፍሪካና በኢትዮጵያ ለበርካታ ዓመታት በሕክምና ሙያቸው፣ በደራሲነታቸውና በሰብአዊ ድጋፍ ሥራዎቻቸው ደካማና ረዳት የሌላቸውን ወገኖች ሲረዱ የቆዩት ታዋቂው ጣሊያናዊ ምሁር ፕሮፌሰር ኮሎኔል ኤንሪኮ ፒዬሮ ቦሲ (ዶክተር) በተወለዱ በ81 ዓመታቸው ሰኔ 10 ቀን 2024 ዓ.ም. ተለይተውናል።
ፕሮፌሰሩ ለአርባ አምስት ዓመታት በዘለቀው ሙያዊ ሕይወታቸው በአርባ ሁለት የአፍሪካ ሀገራት እየተዘዋወሩ በበጎ ፈቃደኝነት የሕክምና አገልግሎት የሰጡ ሲሆን፣ በኦርቶፔዲክስ (የአጥንት) እና በዴርማቶሎጂ (የቆዳ) ሕክምና ስፔሻሊስት ነበሩ።
በሱዳን የሚገኘውን ትልቅ ሆስፒታል ጣሊያኖች በሚገነቡበት ወቅት ከፍተኛ የገንዘብ ፈንድ በማምጣት ረገድ የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
በሀገራችን ኢትዮጵያም ለሀያ ዓመታት ያህል ያገለገሉ ሲሆን፣ የአዳማ አጠቃላይ ሆስፒታልን በማቋቋም የመጀመሪያው ዳይሬክተር በመሆን ሰርተዋል።
በተጨማሪም በዳኑ ሆስፒታል፣ በአቤት ሆስፒታል ድንገተኛ አደጋ ክፍል በአጥንት ስፔሻሊስትነት የሰሩ ሲሆን፣ በየዓመቱ ከጣሊያን ወደ ወሊሶ ሆስፒታል እየመጡ ሰፊ የኦፕራሲዮን ሕክምና አገልግሎት በነፃ ይሰጡ ነበር።
ፕሮፌሰር ኤንሪኮ የሰውን ልጅ በዘር፣ በቋንቋ፣ በቆዳ ቀለምና በሃይማኖት የማይለዩ ፍፁም የሰብአዊነት ተምሳሌት ነበሩ። በአውሮፓ የኮሶቮ ጦርነት ወቅት የአንድ ዓመት ደሞዛቸውን በመተው በጦርነቱ መሃል በነፃ የሕክምና አገልግሎት የሰጡ ሲሆን፣ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅትም በመጀመሪያዎቹ አምስት ጣሊያናውያን የሕክምና ባለሙያዎች ቡድን ውስጥ በመሆን በሄሊኮፕተር ወደ ስፍራው ያቀኑ ታላቅ ባለውለታ ናቸው።
በጣሊያን ሚላኖ "ናጋ" የተሰኘ የሕክምና ማዕከል በማቋቋምም አፍሪካውያንና የሌሎች ሀገራት ስደተኞችን፣ በተለይም የሕጋዊ ሰነድና የገንዘብ አቅም የሌላቸውን ወገኖች በነፃ ሲያክሙ ቆይተዋል።
ብዙዎች ስለ ሀገር ሲያነሱ "የአባት ሀገር" ወይም "የእናት ሀገር" ቢሉም፣ ፕሮፌሰሩ ግን ለኢትዮጵያ የነበራቸው ፍቅር ጥልቅ በመሆኑ ሁልጊዜም "የልጄ የካሌብ ሀገር" በማለት በኩራት ይገልጿት ነበር።
ስለ ኢትዮጵያ ታሪክ፣ ባህልና ወታደራዊ ታሪክ በርካታ ምርምሮችን ያደረጉት ፕሮፌሰሩ፣ በአጠቃላይ ከ46 በላይ መጻሕፍትን በኢንግሊዘኛና በጣሊያንኛ ቋንቋዎች አሳትመዋል።
ከእነዚህም መካከል "The History of Imperial Ethiopian Army" የተሰኘውና ለኢትዮጵያ ወታደራዊ ምርምር ማዕከል ያበረከቱት መጽሐፍ፣ "ደስታስ ይርስ ኤንድ ላይፍ 1892-1937" እና "Aethiopia la moneta Africana" የሚሉት ተጠቃሽ ናቸው። የቡና አመጣጥ ከኢትዮጵያ መሆኑን ለአለም ካስተዋወቁበት ስራቸው ባሻገር የዘመነ መሳፍንትን ፍፃሜ የሚያሳይ ታሪካዊ መጽሐፍ ይጠቀሳሉ።
እኝህ ታላቅ ምሁር ስኮላር፣ ዶክተር፣ የሚሊተሪ ኦፊሰር እና ደራሲ ብቻ ሳይሆኑ፣ በሚላኖ ካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ "ትንሹ ልዑል" የተሰኘውን የሕጻናት መጽሐፍ በ55 ዓለም አቀፍ ቋንቋዎች በመተርጎም ያሳተሙ ተርጓሚና ድንቅ የቅብ ሥራዎችን ያበረከቱ ሰዓሊም ነበሩ።
ምንም እንኳን ሞት በድንገት ከሚወዷቸው ባለቤታቸው ወይዘሮ ሳራ የማነ እና ከልጃቸው ካሌብ ጆርጂ ቢለያቸውም፣ ያኖሩት ታላቅ አሻራ ግን ከመቃብር በላይ ሁሌም ሕያው ሆኖ ይኖራል።
ባለቤታቸውና ልጃቸው የፕሮፌሰሩን ውርስና ሌጋሲ ለማስቀጠል፣ እሳቸው ሳይታተሙ የተዉትንና ስለ ኢትዮጵያ ጉዳይ በአምስት መቶ አምስት መቶ ገጾች የተቀነበቡ ሁለት አዳዲስ መጻሕፍትን ለሕትመት ለማብቃት እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ።
ፕሮፌሰሩ ኢትዮጵያን የመወደዳቸው ምዕራፍ የተገለጠው፤ የተጀመረው በባለቤታቸውና በልጃቸው እንደሆነ ይናገሩ ነበር። በዚህ መሠረት ቤተሰቦቻቸው በኢትዮጵያ ምድር በስማቸው ሙዚየም ለመክፈት አልያም በእርሳቸው የተሰሩ ሥራዎችን እንዲሁም ልዩ ልዩ ቁሳቁሶችን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየም ለማበርከት ሰፊ እንቅስቃሴ ላይ ናቸው።
የፕሮፌሰር ኮሎኔል ኤንሪኮ ፒዬሮ ቦሲን ሕይወትና ሥራዎች ፤ ለአገርና ለሕዝብ ያበረከቱትን አስተዋጸኦ በክብር የሚዘክር ሥራ ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ይጠበቃል።
#ethiopiaheritage #italianscholar #enricopierobossi #ethiopianhistory #humanitarian #enricobossi #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Ethiopia’s Great Friend:
In Memory of Professor Colonel Enrico Piero Bossi
Italian scholar and human rights advocate
His wife, Mrs. Sara Yemane, and their son, Caleb Giorgi, are working to preserve and continue his legacy.
#ethiopia | The renowned Italian scholar, Professor Colonel Enrico Piero Bossi (M.D.), who dedicated many years of his life in Africa and Ethiopia through his medical profession, authorship, and humanitarian activities, helping vulnerable and disadvantaged communities, passed away at the age of 81 on June 17, 2024.
During his distinguished 45-year professional career, Professor Bossi volunteered medical services across 42 African countries. He was a specialist in Orthopedics (bone and musculoskeletal medicine) and Dermatology (skin medicine).
He made a significant contribution to securing major funding for the construction of a large hospital in Sudan built by Italian organizations.
In Ethiopia, where he served for nearly twenty years, he played a key role in establishing Adama General Hospital and served as its first director.
Additionally, he worked as an orthopedic specialist at Danu Hospital and in the Emergency Department of Abet Hospital. Every year, he traveled from Italy to Woliso Hospital, where he provided extensive surgical services free of charge.
Professor Enrico was a true symbol of humanity, treating all people equally regardless of race, language, skin color, or religion. During the Kosovo War in Europe, he gave up an entire year’s salary to provide free medical services in the war zone. Likewise, during the Ethio-Eritrean War, he was among the first five Italian medical professionals who flew by helicopter to the conflict area to provide humanitarian assistance.
In Milan, Italy, he founded the medical center known as “NAGA,” where he provided free healthcare services to African immigrants and migrants from other countries, particularly those lacking legal documentation or financial means.
While many people refer to their homeland as their “fatherland” or “motherland,” Professor Bossi’s love for Ethiopia was so profound that he proudly referred to it as “the country of my son, Caleb.”
A dedicated researcher of Ethiopian history, culture, and military history, Professor Bossi authored and published more than 46 books in English and Italian.
Among his notable works are:
The History of Imperial Ethiopian Army
Destas Yirs and Life 1892–1937
Aethiopia la Moneta Africana
His work helped introduce Ethiopia’s role as the birthplace of coffee to the wider world. He also authored historical works documenting the end of the Era of the Princes (Zemene Mesafint).
Professor Bossi was not only a scholar, physician, military officer, and author, but also a translator and artist. At the Catholic University of Milan, he translated and published The Little Prince in 55 international languages and contributed remarkable artistic and illustrative works.
Although death unexpectedly separated him from his beloved wife, Mrs. Sara Yemane, and his son, Caleb Giorgi, the remarkable legacy he left behind will remain alive far beyond his grave.
To preserve Professor Bossi’s legacy, his wife and son are working to complete and publish two previously unpublished manuscripts. These extensive works, each consisting of approximately 500 pages, focus on Ethiopian subjects and were left unfinished by the professor.
The professor used to say that the chapter of his love for Ethiopia was revealed—and indeed began—with his wife and his child. Based on this, his family is actively working either to open a museum in Ethiopia bearing his name or to donate his works, along with various personal artifacts and items, to the Ethiopian National Museum.
It is hoped that the Ethiopian Heritage Authority will undertake initiatives to honor and commemorate Professor Colonel Enrico Piero Bossi’s life, work, and invaluable contributions to the nation and its people.
May his memory and contributions continue to inspire future generations.
#ethiopiaheritage #italianscholar #enricopierobossi #ethiopianhistory #humanitarian #enricobossi
የፕሮፌሰር ኮሎኔል ኤንሪኮ ፒዬሮ ቦሲ መታሰቢያ
* ጣሊያናዊ ምሁር፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ናቸው
* ባለቤታቸው ወይዘሮ ሳራ የማነ እና ከልጃቸው ካሌብ ጆርጂ ሌጋሲያቸውን ( Legacy ) ለማስቀጠል እየታተሩ ናቸው
#ethiopia | በአፍሪካና በኢትዮጵያ ለበርካታ ዓመታት በሕክምና ሙያቸው፣ በደራሲነታቸውና በሰብአዊ ድጋፍ ሥራዎቻቸው ደካማና ረዳት የሌላቸውን ወገኖች ሲረዱ የቆዩት ታዋቂው ጣሊያናዊ ምሁር ፕሮፌሰር ኮሎኔል ኤንሪኮ ፒዬሮ ቦሲ (ዶክተር) በተወለዱ በ81 ዓመታቸው ሰኔ 10 ቀን 2024 ዓ.ም. ተለይተውናል።
ፕሮፌሰሩ ለአርባ አምስት ዓመታት በዘለቀው ሙያዊ ሕይወታቸው በአርባ ሁለት የአፍሪካ ሀገራት እየተዘዋወሩ በበጎ ፈቃደኝነት የሕክምና አገልግሎት የሰጡ ሲሆን፣ በኦርቶፔዲክስ (የአጥንት) እና በዴርማቶሎጂ (የቆዳ) ሕክምና ስፔሻሊስት ነበሩ።
በሱዳን የሚገኘውን ትልቅ ሆስፒታል ጣሊያኖች በሚገነቡበት ወቅት ከፍተኛ የገንዘብ ፈንድ በማምጣት ረገድ የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
በሀገራችን ኢትዮጵያም ለሀያ ዓመታት ያህል ያገለገሉ ሲሆን፣ የአዳማ አጠቃላይ ሆስፒታልን በማቋቋም የመጀመሪያው ዳይሬክተር በመሆን ሰርተዋል።
በተጨማሪም በዳኑ ሆስፒታል፣ በአቤት ሆስፒታል ድንገተኛ አደጋ ክፍል በአጥንት ስፔሻሊስትነት የሰሩ ሲሆን፣ በየዓመቱ ከጣሊያን ወደ ወሊሶ ሆስፒታል እየመጡ ሰፊ የኦፕራሲዮን ሕክምና አገልግሎት በነፃ ይሰጡ ነበር።
ፕሮፌሰር ኤንሪኮ የሰውን ልጅ በዘር፣ በቋንቋ፣ በቆዳ ቀለምና በሃይማኖት የማይለዩ ፍፁም የሰብአዊነት ተምሳሌት ነበሩ። በአውሮፓ የኮሶቮ ጦርነት ወቅት የአንድ ዓመት ደሞዛቸውን በመተው በጦርነቱ መሃል በነፃ የሕክምና አገልግሎት የሰጡ ሲሆን፣ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅትም በመጀመሪያዎቹ አምስት ጣሊያናውያን የሕክምና ባለሙያዎች ቡድን ውስጥ በመሆን በሄሊኮፕተር ወደ ስፍራው ያቀኑ ታላቅ ባለውለታ ናቸው።
በጣሊያን ሚላኖ "ናጋ" የተሰኘ የሕክምና ማዕከል በማቋቋምም አፍሪካውያንና የሌሎች ሀገራት ስደተኞችን፣ በተለይም የሕጋዊ ሰነድና የገንዘብ አቅም የሌላቸውን ወገኖች በነፃ ሲያክሙ ቆይተዋል።
ብዙዎች ስለ ሀገር ሲያነሱ "የአባት ሀገር" ወይም "የእናት ሀገር" ቢሉም፣ ፕሮፌሰሩ ግን ለኢትዮጵያ የነበራቸው ፍቅር ጥልቅ በመሆኑ ሁልጊዜም "የልጄ የካሌብ ሀገር" በማለት በኩራት ይገልጿት ነበር።
ስለ ኢትዮጵያ ታሪክ፣ ባህልና ወታደራዊ ታሪክ በርካታ ምርምሮችን ያደረጉት ፕሮፌሰሩ፣ በአጠቃላይ ከ46 በላይ መጻሕፍትን በኢንግሊዘኛና በጣሊያንኛ ቋንቋዎች አሳትመዋል።
ከእነዚህም መካከል "The History of Imperial Ethiopian Army" የተሰኘውና ለኢትዮጵያ ወታደራዊ ምርምር ማዕከል ያበረከቱት መጽሐፍ፣ "ደስታስ ይርስ ኤንድ ላይፍ 1892-1937" እና "Aethiopia la moneta Africana" የሚሉት ተጠቃሽ ናቸው። የቡና አመጣጥ ከኢትዮጵያ መሆኑን ለአለም ካስተዋወቁበት ስራቸው ባሻገር የዘመነ መሳፍንትን ፍፃሜ የሚያሳይ ታሪካዊ መጽሐፍ ይጠቀሳሉ።
እኝህ ታላቅ ምሁር ስኮላር፣ ዶክተር፣ የሚሊተሪ ኦፊሰር እና ደራሲ ብቻ ሳይሆኑ፣ በሚላኖ ካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ "ትንሹ ልዑል" የተሰኘውን የሕጻናት መጽሐፍ በ55 ዓለም አቀፍ ቋንቋዎች በመተርጎም ያሳተሙ ተርጓሚና ድንቅ የቅብ ሥራዎችን ያበረከቱ ሰዓሊም ነበሩ።
ምንም እንኳን ሞት በድንገት ከሚወዷቸው ባለቤታቸው ወይዘሮ ሳራ የማነ እና ከልጃቸው ካሌብ ጆርጂ ቢለያቸውም፣ ያኖሩት ታላቅ አሻራ ግን ከመቃብር በላይ ሁሌም ሕያው ሆኖ ይኖራል።
ባለቤታቸውና ልጃቸው የፕሮፌሰሩን ውርስና ሌጋሲ ለማስቀጠል፣ እሳቸው ሳይታተሙ የተዉትንና ስለ ኢትዮጵያ ጉዳይ በአምስት መቶ አምስት መቶ ገጾች የተቀነበቡ ሁለት አዳዲስ መጻሕፍትን ለሕትመት ለማብቃት እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ።
ፕሮፌሰሩ ኢትዮጵያን የመወደዳቸው ምዕራፍ የተገለጠው፤ የተጀመረው በባለቤታቸውና በልጃቸው እንደሆነ ይናገሩ ነበር። በዚህ መሠረት ቤተሰቦቻቸው በኢትዮጵያ ምድር በስማቸው ሙዚየም ለመክፈት አልያም በእርሳቸው የተሰሩ ሥራዎችን እንዲሁም ልዩ ልዩ ቁሳቁሶችን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየም ለማበርከት ሰፊ እንቅስቃሴ ላይ ናቸው።
የፕሮፌሰር ኮሎኔል ኤንሪኮ ፒዬሮ ቦሲን ሕይወትና ሥራዎች ፤ ለአገርና ለሕዝብ ያበረከቱትን አስተዋጸኦ በክብር የሚዘክር ሥራ ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ይጠበቃል።
#ethiopiaheritage #italianscholar #enricopierobossi #ethiopianhistory #humanitarian #enricobossi #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Ethiopia’s Great Friend:
In Memory of Professor Colonel Enrico Piero Bossi
Italian scholar and human rights advocate
His wife, Mrs. Sara Yemane, and their son, Caleb Giorgi, are working to preserve and continue his legacy.
#ethiopia | The renowned Italian scholar, Professor Colonel Enrico Piero Bossi (M.D.), who dedicated many years of his life in Africa and Ethiopia through his medical profession, authorship, and humanitarian activities, helping vulnerable and disadvantaged communities, passed away at the age of 81 on June 17, 2024.
During his distinguished 45-year professional career, Professor Bossi volunteered medical services across 42 African countries. He was a specialist in Orthopedics (bone and musculoskeletal medicine) and Dermatology (skin medicine).
He made a significant contribution to securing major funding for the construction of a large hospital in Sudan built by Italian organizations.
In Ethiopia, where he served for nearly twenty years, he played a key role in establishing Adama General Hospital and served as its first director.
Additionally, he worked as an orthopedic specialist at Danu Hospital and in the Emergency Department of Abet Hospital. Every year, he traveled from Italy to Woliso Hospital, where he provided extensive surgical services free of charge.
Professor Enrico was a true symbol of humanity, treating all people equally regardless of race, language, skin color, or religion. During the Kosovo War in Europe, he gave up an entire year’s salary to provide free medical services in the war zone. Likewise, during the Ethio-Eritrean War, he was among the first five Italian medical professionals who flew by helicopter to the conflict area to provide humanitarian assistance.
In Milan, Italy, he founded the medical center known as “NAGA,” where he provided free healthcare services to African immigrants and migrants from other countries, particularly those lacking legal documentation or financial means.
While many people refer to their homeland as their “fatherland” or “motherland,” Professor Bossi’s love for Ethiopia was so profound that he proudly referred to it as “the country of my son, Caleb.”
A dedicated researcher of Ethiopian history, culture, and military history, Professor Bossi authored and published more than 46 books in English and Italian.
Among his notable works are:
The History of Imperial Ethiopian Army
Destas Yirs and Life 1892–1937
Aethiopia la Moneta Africana
His work helped introduce Ethiopia’s role as the birthplace of coffee to the wider world. He also authored historical works documenting the end of the Era of the Princes (Zemene Mesafint).
Professor Bossi was not only a scholar, physician, military officer, and author, but also a translator and artist. At the Catholic University of Milan, he translated and published The Little Prince in 55 international languages and contributed remarkable artistic and illustrative works.
Although death unexpectedly separated him from his beloved wife, Mrs. Sara Yemane, and his son, Caleb Giorgi, the remarkable legacy he left behind will remain alive far beyond his grave.
To preserve Professor Bossi’s legacy, his wife and son are working to complete and publish two previously unpublished manuscripts. These extensive works, each consisting of approximately 500 pages, focus on Ethiopian subjects and were left unfinished by the professor.
The professor used to say that the chapter of his love for Ethiopia was revealed—and indeed began—with his wife and his child. Based on this, his family is actively working either to open a museum in Ethiopia bearing his name or to donate his works, along with various personal artifacts and items, to the Ethiopian National Museum.
It is hoped that the Ethiopian Heritage Authority will undertake initiatives to honor and commemorate Professor Colonel Enrico Piero Bossi’s life, work, and invaluable contributions to the nation and its people.
May his memory and contributions continue to inspire future generations.
#ethiopiaheritage #italianscholar #enricopierobossi #ethiopianhistory #humanitarian #enricobossi
6 days ago
ኢትዮጵያን ከባሕር ያራቃት ማነው? እውነቱ ሲጋለጥ
https://youtu.be/TOizhJxRp... #ethiopia #redsea #tesfayebeljige #ethiopianhistory #redsea #redseacoast
6 days ago
ኢትዮጵያ የዓባይ ምንጭ.. የቀይ ባሕር ቁልፍ
https://youtu.be/TOizhJxRp... #ethiopia #redsea #tesfayebeljige #ethiopianhistory #redsea #redseacoast
6 days ago
u12a2u1275u12eeu1335u12eb u1260u1240u12ed u1263u1215u122d u12f3u122du127b
https://youtu.be/TOizhJxRp... #ethiopia #redsea #tesfayebeljige #ethiopianhistory #redsea #redseacoast ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"ExternalUrl","__isEntity":"ExternalUrl","url":"https://l.facebook.com/l.p...
ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ዳርቻ
https://youtu.be/TOizhJxRp... #ethiopia #redsea #tesfayebeljige #ethiopianhistory #redsea #redseacoast
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ከመቃብር በላይ የሚውል መልካም ስም
በአሰላ የመጋቤ በረከት ግርማ ደምሴ መታሰቢያ ሙዚየም ተመረቀ!
#ethiopia | ባለፉት ጥቂት ሰዓታት በአርሲ ዞን አሰላ ከተማ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ አንድ ታሪካዊ ክስተት ተከናውኗል።
በሀገርና በቤተክርስቲያን ዘንድ እጅግ የሚከበሩትና "መጋቤ በረከት" የሚል ማዕረግ የተሰጣቸው የታላቁ አባት የመጋቤ በረከት ግርማ ደምሴ የመታሰቢያ ህንፃ ሙዚየም በታላቅ ድምቀት ተመርቋል።
የልጆች ስጦታ፦
እኚህ ታላቅ አባት ካረፉ አንድ ዓመት ሲሞላቸው ልጆቻቸው ከአባታቸው የተረከቡትን በጎነት ለታሪክ እንዲተርፍ ከ62 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበትን ባለ ሁለት ወለል ሙዚየም ገንብተው ለምረቃ አብቅተዋል።
"ጊዳድ" መጽሐፍ፦
የአባታቸውን የህይወት ጉዞ፣ የንግድ ስኬትና የቤተሰብ አመራር ጥበብ የሚዳስሰው "ጊዳድ" የተሰኘው መጽሐፍ በጸሐፊ ሌሊሳ ኢድሪስ ተዘጋጅቶ በአማርኛና በአፋን ኦሮሞ ለንባብ በቅቷል።
ታሪካዊ ምስክርነት፦
ሙዚየሙ የአባቱን መልካም ስራዎች የሚገልጹ ፎቶግራፎች፣ ቁሳቁሶችና መረጃዎችን የያዘ ሲሆን፤ አዳራሽና ቢሮዎችንም ያካተተ ዘመናዊ ህንፃ ነው።
መጋቤ በረከት ግርማ ደምሴ (1949 - 2017 ዓ.ም)
በአርሲ ዞን ተወልደው በንግዱ ዓለም ስኬታማ የነበሩ ሲሆን፤ አምስት ልጆችን በስነ-ምግባር አሳድገው ለሀገር ያበቁ ታላቅ አባት ናቸው።
በቤተክርስቲያን ግንባታ፣ በማህበራዊ ልማትና በሽምግልና ስራቸው "የቱሩፋት አበጋዝ" ተብለው ይወደሳሉ።
እውነትን በመናገርና ችግረኞችን በመርዳት የሚታወቁት እኚህ አባት፣ በ68 ዓመታቸው ሚያዚያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ማረፋቸው ይታወሳል።
ሀብት ለራስ ብቻ ሳይሆን እንዲህ ለታሪክና ለወገን ሲተርፍ ትልቅ ትርጉም ይኖረዋል። የመጋቤ በረከት ግርማ ልጆች ለአባታቸው ያደረጉት ይህ ተግባር፣ ማንኛውም ሰው በህይወት ዘመኑ የሚዘራው በጎነት እንዲህ በክብር እንደሚታጨድ ማሳያ ነው። አሰላ ዛሬ የአንድ ብርቱ አባት ታሪክ ህያው ሆኖ ሲታደስ ውላለች!
መልካም ስራ ከመቃብር በላይ ይውላል!
#getu #megabebereketgirma #asella #legacy #gidatbook #ethiopianhistory #ethiopianorthodox #arsi #inspiration #መጋቤበረከትግርማ #አሰላ #ታሪክ #ጊዳድ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
በአሰላ የመጋቤ በረከት ግርማ ደምሴ መታሰቢያ ሙዚየም ተመረቀ!
#ethiopia | ባለፉት ጥቂት ሰዓታት በአርሲ ዞን አሰላ ከተማ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ አንድ ታሪካዊ ክስተት ተከናውኗል።
በሀገርና በቤተክርስቲያን ዘንድ እጅግ የሚከበሩትና "መጋቤ በረከት" የሚል ማዕረግ የተሰጣቸው የታላቁ አባት የመጋቤ በረከት ግርማ ደምሴ የመታሰቢያ ህንፃ ሙዚየም በታላቅ ድምቀት ተመርቋል።
የልጆች ስጦታ፦
እኚህ ታላቅ አባት ካረፉ አንድ ዓመት ሲሞላቸው ልጆቻቸው ከአባታቸው የተረከቡትን በጎነት ለታሪክ እንዲተርፍ ከ62 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበትን ባለ ሁለት ወለል ሙዚየም ገንብተው ለምረቃ አብቅተዋል።
"ጊዳድ" መጽሐፍ፦
የአባታቸውን የህይወት ጉዞ፣ የንግድ ስኬትና የቤተሰብ አመራር ጥበብ የሚዳስሰው "ጊዳድ" የተሰኘው መጽሐፍ በጸሐፊ ሌሊሳ ኢድሪስ ተዘጋጅቶ በአማርኛና በአፋን ኦሮሞ ለንባብ በቅቷል።
ታሪካዊ ምስክርነት፦
ሙዚየሙ የአባቱን መልካም ስራዎች የሚገልጹ ፎቶግራፎች፣ ቁሳቁሶችና መረጃዎችን የያዘ ሲሆን፤ አዳራሽና ቢሮዎችንም ያካተተ ዘመናዊ ህንፃ ነው።
መጋቤ በረከት ግርማ ደምሴ (1949 - 2017 ዓ.ም)
በአርሲ ዞን ተወልደው በንግዱ ዓለም ስኬታማ የነበሩ ሲሆን፤ አምስት ልጆችን በስነ-ምግባር አሳድገው ለሀገር ያበቁ ታላቅ አባት ናቸው።
በቤተክርስቲያን ግንባታ፣ በማህበራዊ ልማትና በሽምግልና ስራቸው "የቱሩፋት አበጋዝ" ተብለው ይወደሳሉ።
እውነትን በመናገርና ችግረኞችን በመርዳት የሚታወቁት እኚህ አባት፣ በ68 ዓመታቸው ሚያዚያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ማረፋቸው ይታወሳል።
ሀብት ለራስ ብቻ ሳይሆን እንዲህ ለታሪክና ለወገን ሲተርፍ ትልቅ ትርጉም ይኖረዋል። የመጋቤ በረከት ግርማ ልጆች ለአባታቸው ያደረጉት ይህ ተግባር፣ ማንኛውም ሰው በህይወት ዘመኑ የሚዘራው በጎነት እንዲህ በክብር እንደሚታጨድ ማሳያ ነው። አሰላ ዛሬ የአንድ ብርቱ አባት ታሪክ ህያው ሆኖ ሲታደስ ውላለች!
መልካም ስራ ከመቃብር በላይ ይውላል!
#getu #megabebereketgirma #asella #legacy #gidatbook #ethiopianhistory #ethiopianorthodox #arsi #inspiration #መጋቤበረከትግርማ #አሰላ #ታሪክ #ጊዳድ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
2 months ago
ተፈሪ መኮንን
የመቶ ዓመቱ የጥቁር ህዝቦች የዕውቀት ፋና
#ethiopia | "ኢትዮጵያን በዕውቀት መገንባት!" በሚል መሪ ቃል ሚያዝያ 19 ቀን 1917 ዓ.ም. በልዑል ተፈሪ መኮንን (በኋላ አፄ ኃይለ ሥላሴ) የተመረቀው ታሪካዊው ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ዛሬ መቶኛ ዓመቱን (Centenary) ያከብራል።
ይህ ተቋም ለኢትዮጵያ ዘመናዊነት መሠረት የጣለ፣ "የአፍሪካው ሃርቫርድ" ተብሎ የሚጠራ የዕውቀት ማማ ነው።
በታሪክ ቅጥር ግቢው ውስጥ ያለፉ ታላላቅ ኢትዮጵያውያን፦
ተፈሪ መኮንን ለሀገርና ለዓለም የተረፉ ብሩህ አእምሮዎችን አፍርቷል። ጥቂቶቹን ለመጥቀስ፦
ጸሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተ-ወልድ፦
ታዋቂው ዲፕሎማትና የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር።
ሎሬት አፈወርቅ ተክሌ፦
በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁት ታላቁ ሰዓሊ።
ክቡር ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁ፦
የ"ፍቅር እስከ መቃብር" ደራሲና ዲፕሎማት።
ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ፦
አንጋፋው የቀዶ ጥገና ሐኪም የሀገር ባለውለታ።
🔍 ተፈሪ መኮንን ለምን ይለያል?
የዘመናዊነት መነሻ፦
የመጀመሪያው አዳሪ ትምህርት ቤትና ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ዲፕሎማሲ መሠረት የሆኑ ምሁራን መፍለቂያ ነው።
የዩኒቨርሲቲው እናት፦
በ1943 ዓ.ም. አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሲመሰረት፣ የመጀመሪያዎቹ ተማሪዎችና መምህራን የተገኙት ከዚሁ ተቋም ነበር።
ዛሬም በታሪክ ስሙ
ዛሬ "ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ" በሚል ስያሜው የነገዎቹን የቴክኒክና የኢንዱስትሪ ባለሙያዎች እያፈራ ይገኛል።
ይህ ተቋም ትምህርት ቤት ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ፅናትና የብልህነት መታወቂያ ነው። ጣሊያን ንብረቱን ቢዘርፈውም፣ ኢትዮጵያውያን ግን በዕውቀት ተመልሰው ገነቡት። ዛሬ ላይ ተቋሙ ታሪካዊ ስሙን መልሶ መቶ ዓመቱን ሲያከብር ለሁላችንም ኩራት ነው።
ተፈሪ መኮንን - የመቶ ዓመት የብርሃን ጉዞ!
#getu #teferimekonnen #centenary #ethiopianhistory #moderneducation #addisababa #teferimekonnenpolytechnic #historybuilders #ተፈሪመኮንን #መቶዓመት #ታሪክ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
የመቶ ዓመቱ የጥቁር ህዝቦች የዕውቀት ፋና
#ethiopia | "ኢትዮጵያን በዕውቀት መገንባት!" በሚል መሪ ቃል ሚያዝያ 19 ቀን 1917 ዓ.ም. በልዑል ተፈሪ መኮንን (በኋላ አፄ ኃይለ ሥላሴ) የተመረቀው ታሪካዊው ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ዛሬ መቶኛ ዓመቱን (Centenary) ያከብራል።
ይህ ተቋም ለኢትዮጵያ ዘመናዊነት መሠረት የጣለ፣ "የአፍሪካው ሃርቫርድ" ተብሎ የሚጠራ የዕውቀት ማማ ነው።
በታሪክ ቅጥር ግቢው ውስጥ ያለፉ ታላላቅ ኢትዮጵያውያን፦
ተፈሪ መኮንን ለሀገርና ለዓለም የተረፉ ብሩህ አእምሮዎችን አፍርቷል። ጥቂቶቹን ለመጥቀስ፦
ጸሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተ-ወልድ፦
ታዋቂው ዲፕሎማትና የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር።
ሎሬት አፈወርቅ ተክሌ፦
በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁት ታላቁ ሰዓሊ።
ክቡር ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁ፦
የ"ፍቅር እስከ መቃብር" ደራሲና ዲፕሎማት።
ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ፦
አንጋፋው የቀዶ ጥገና ሐኪም የሀገር ባለውለታ።
🔍 ተፈሪ መኮንን ለምን ይለያል?
የዘመናዊነት መነሻ፦
የመጀመሪያው አዳሪ ትምህርት ቤትና ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ዲፕሎማሲ መሠረት የሆኑ ምሁራን መፍለቂያ ነው።
የዩኒቨርሲቲው እናት፦
በ1943 ዓ.ም. አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሲመሰረት፣ የመጀመሪያዎቹ ተማሪዎችና መምህራን የተገኙት ከዚሁ ተቋም ነበር።
ዛሬም በታሪክ ስሙ
ዛሬ "ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ" በሚል ስያሜው የነገዎቹን የቴክኒክና የኢንዱስትሪ ባለሙያዎች እያፈራ ይገኛል።
ይህ ተቋም ትምህርት ቤት ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ፅናትና የብልህነት መታወቂያ ነው። ጣሊያን ንብረቱን ቢዘርፈውም፣ ኢትዮጵያውያን ግን በዕውቀት ተመልሰው ገነቡት። ዛሬ ላይ ተቋሙ ታሪካዊ ስሙን መልሶ መቶ ዓመቱን ሲያከብር ለሁላችንም ኩራት ነው።
ተፈሪ መኮንን - የመቶ ዓመት የብርሃን ጉዞ!
#getu #teferimekonnen #centenary #ethiopianhistory #moderneducation #addisababa #teferimekonnenpolytechnic #historybuilders #ተፈሪመኮንን #መቶዓመት #ታሪክ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
3 months ago
🎭 "እንዝታ" ትውፊታዊ ቴአትር — በባህር ዳር!
#ethiopia | በታሪካዊ ትውፊት የተዋቀረውና በብዙዎች ዘንድ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው "እንዝታ" የተሰኘው ትውፊታዊ ቴአትር፣ ነገ መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በታላቅ ድምቀት ለእይታ ይቀርባል።
የጥበብ አፍቃሪዎች ሁሉ በዚህ ልዩ መድረክ ላይ እንዲገኙ ተጋብዘዋል።
የዝግጅቱ ቦታ እና ሰዓት
ቦታ፦ ባህር ዳር ከተማ፣ በሙሉዓለም ባሕል ማዕከል
ቀን፦ ነገ መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም
ደራሲያን፦
ደሳለኝ ድረስ (መረዋ) እና ንብረት ያለው
አዘጋጅ፦ አባይነህ በለጠ
ረዳት አዘጋጅ፦ ህሩይ አበበ
ፕሮዳክሽን ማናጀር፦ ይስማው ዮሐንስ
መብራት፦ ደጉ ሙልጌታ
ስፖት ላይት፦ መንግስቱ መኮንን
መድረክ ግንባታ፦ ሙልጌታ አለኸኝ
ድምጽ ግብዓት፦ በለጠ ወንዴ
አልባሳት እና ቁሳቁስ፦ የዝና አዱኛ
🎭 ተዋንያን
በርካታ ተሰጥኦ ያላቸው ተዋንያን በመድረኩ ላይ ይከሰታሉ፦
ግዮን አለምሰገድ፣ አሳሱሁ መንግሥቱ፣ ይታየው አንዴ፣ ያለምስራ ገድፍ፣ ጊዜኔው አዲስ፣ መማር አለባቸው፣ ስዩም መኮነን፣ አመልማል ተክሉ፣ ብርሃኑ ውብአየሁ፣ ተዋቸው ወረታው፣ አመለወርቅ ወንዲራድ፣ ማስተዋል አድማሱ፣ ይኽነው ባለህ እና ሌሎችም።
ፕሮዳክሽን
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ዝክረ ታሪክ ጽሕፈት ቤት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#enzita #traditionaltheatre #ethiopiantheatre #bahirdar #mulualemculturalcenter #amharaculture #ethiopianarts #ethiopianhistory #culturalheritage #bahirdarevents
#ethiopia | በታሪካዊ ትውፊት የተዋቀረውና በብዙዎች ዘንድ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው "እንዝታ" የተሰኘው ትውፊታዊ ቴአትር፣ ነገ መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በታላቅ ድምቀት ለእይታ ይቀርባል።
የጥበብ አፍቃሪዎች ሁሉ በዚህ ልዩ መድረክ ላይ እንዲገኙ ተጋብዘዋል።
የዝግጅቱ ቦታ እና ሰዓት
ቦታ፦ ባህር ዳር ከተማ፣ በሙሉዓለም ባሕል ማዕከል
ቀን፦ ነገ መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም
ደራሲያን፦
ደሳለኝ ድረስ (መረዋ) እና ንብረት ያለው
አዘጋጅ፦ አባይነህ በለጠ
ረዳት አዘጋጅ፦ ህሩይ አበበ
ፕሮዳክሽን ማናጀር፦ ይስማው ዮሐንስ
መብራት፦ ደጉ ሙልጌታ
ስፖት ላይት፦ መንግስቱ መኮንን
መድረክ ግንባታ፦ ሙልጌታ አለኸኝ
ድምጽ ግብዓት፦ በለጠ ወንዴ
አልባሳት እና ቁሳቁስ፦ የዝና አዱኛ
🎭 ተዋንያን
በርካታ ተሰጥኦ ያላቸው ተዋንያን በመድረኩ ላይ ይከሰታሉ፦
ግዮን አለምሰገድ፣ አሳሱሁ መንግሥቱ፣ ይታየው አንዴ፣ ያለምስራ ገድፍ፣ ጊዜኔው አዲስ፣ መማር አለባቸው፣ ስዩም መኮነን፣ አመልማል ተክሉ፣ ብርሃኑ ውብአየሁ፣ ተዋቸው ወረታው፣ አመለወርቅ ወንዲራድ፣ ማስተዋል አድማሱ፣ ይኽነው ባለህ እና ሌሎችም።
ፕሮዳክሽን
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ዝክረ ታሪክ ጽሕፈት ቤት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#enzita #traditionaltheatre #ethiopiantheatre #bahirdar #mulualemculturalcenter #amharaculture #ethiopianarts #ethiopianhistory #culturalheritage #bahirdarevents
3 months ago
ድላችን ሐውልት
የካራማራ ድል መታሰቢያ ሐውልት
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ፊት ለፊት የሚገኘውና "ድላችን" ተብሎ የሚጠራው ሐውልት በ1970 ዓ.ም በምስራቅ ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት የዚያድ ባሬን ወራሪ ጦር ድል ለማድረግ መስዋዕት ለሆኑት የኢትዮጵያና የኩባ ወታደሮች መታሰቢያ እንዲሆን ታስቦ የተገነባ ሲሆን፣ የድሉን አራተኛ ዓመት በማክበር በ1974 ዓ.ም ተመርቋል።
የሐውልቱ ስነ-ጥበባዊ ንድፍ በወቅቱ በነበሩ የኢትዮጵያና የሰሜን ኮሪያ (Mansudae Art Studio) ባለሙያዎች ትብብር የተሰራ ነው።
የግንባታው ዘይቤ "ሶሻሊስት ሪአሊዝም" የተከተለ በመሆኑ፣ የሐውልቱ ግዝፈትና የወታደሮቹ አቋቋም የጥንካሬና የድል አድራጊነት ስሜትን በጉልህ ያንጸባርቃል።
በሐውልቱ አናት ላይ የሚታዩት ሶስት ወታደሮች የመደበኛ ጦርን፣ የአየር ኃይልን እና የክብር ዘበኛን ወይም የሚሊሻን ተወካዮች ሲሆኑ፣ የለበሱት ወታደራዊ ልብስና የያዟቸው የኤኬ-47 (AK-47) ጠመንጃዎች በወቅቱ የነበረውን ትክክለኛ ወታደራዊ ትጥቅ የሚወክሉ ናቸው።
በሐውልቱ የታችኛው ክፍል በሚገኘው ሰፊ ግድግዳ ላይ የኢትዮጵያና የኩባ ወታደሮች ጎን ለጎን ሆነው ሲዋጉ የሚያሳይ ምስል ተቀርጾ ይገኛል። በተጨማሪም በጦርነቱ ህይወታቸውን ያጡ የ160 ኩባውያን ወታደሮች ፎቶግራፍ በሐውልቱ ግራና ቀኝ ባሉት ግንቦች ላይ በሴራሚክ ተሰርቶ ተለጥፎ ይታያል።
ይህ ሐውልቱ የኢትዮጵያን የግዛት አንድነት ለማስከበር የተከፈለውን መስዋዕትነት ብቻ ሳይሆን፣ በወቅቱ የነበረውን ጥልቅ የኢትዮ-ኩባ ወታደራዊና ፖለቲካዊ ቁርኝት እንዲሁም የሶቪየት ህብረትን የርዕዮተ ዓለም ተጽዕኖ በግልጽ የሚያሳይ ነው።
ምንም እንኳን በ1983 ዓ.ም የደርግ መንግስት መውደቅን ተከትሎ ሐውልቱ የፖለቲካ ምልክት ተደርጎ በመወሰዱ የኩባ ወታደሮች ፎቶግራፎች ተነስተውና ጥገና ተነፍጎት ለዓመታት ቢቆይም፣ ቆይቶ ግን በሁለቱ አገራት ስምምነት መሰረት ዳግም ታድሷል።
በአሁኑ ወቅት ሐውልቱ ከፖለቲካዊ ወገንተኝነት ባለፈ የሀገር ሉዓላዊነት የተከበረበትን ታሪክ የሚዘክር ብሄራዊ ቅርስ ተደርጎ ይወሰዳል።
በየዓመቱ የካቲት 26 ቀን የሚከበረው የካራማራ ድል ቀንም በዚህ ስፍራ በታላቅ ስነ-ስርዓት ይታሰባል።
#ethiopia #cuba #karamaramonument #addisababa #history #victorymonument #ethiopianhistory #militaryheritage #coldwarhistory
የካራማራ ድል መታሰቢያ ሐውልት
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ፊት ለፊት የሚገኘውና "ድላችን" ተብሎ የሚጠራው ሐውልት በ1970 ዓ.ም በምስራቅ ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት የዚያድ ባሬን ወራሪ ጦር ድል ለማድረግ መስዋዕት ለሆኑት የኢትዮጵያና የኩባ ወታደሮች መታሰቢያ እንዲሆን ታስቦ የተገነባ ሲሆን፣ የድሉን አራተኛ ዓመት በማክበር በ1974 ዓ.ም ተመርቋል።
የሐውልቱ ስነ-ጥበባዊ ንድፍ በወቅቱ በነበሩ የኢትዮጵያና የሰሜን ኮሪያ (Mansudae Art Studio) ባለሙያዎች ትብብር የተሰራ ነው።
የግንባታው ዘይቤ "ሶሻሊስት ሪአሊዝም" የተከተለ በመሆኑ፣ የሐውልቱ ግዝፈትና የወታደሮቹ አቋቋም የጥንካሬና የድል አድራጊነት ስሜትን በጉልህ ያንጸባርቃል።
በሐውልቱ አናት ላይ የሚታዩት ሶስት ወታደሮች የመደበኛ ጦርን፣ የአየር ኃይልን እና የክብር ዘበኛን ወይም የሚሊሻን ተወካዮች ሲሆኑ፣ የለበሱት ወታደራዊ ልብስና የያዟቸው የኤኬ-47 (AK-47) ጠመንጃዎች በወቅቱ የነበረውን ትክክለኛ ወታደራዊ ትጥቅ የሚወክሉ ናቸው።
በሐውልቱ የታችኛው ክፍል በሚገኘው ሰፊ ግድግዳ ላይ የኢትዮጵያና የኩባ ወታደሮች ጎን ለጎን ሆነው ሲዋጉ የሚያሳይ ምስል ተቀርጾ ይገኛል። በተጨማሪም በጦርነቱ ህይወታቸውን ያጡ የ160 ኩባውያን ወታደሮች ፎቶግራፍ በሐውልቱ ግራና ቀኝ ባሉት ግንቦች ላይ በሴራሚክ ተሰርቶ ተለጥፎ ይታያል።
ይህ ሐውልቱ የኢትዮጵያን የግዛት አንድነት ለማስከበር የተከፈለውን መስዋዕትነት ብቻ ሳይሆን፣ በወቅቱ የነበረውን ጥልቅ የኢትዮ-ኩባ ወታደራዊና ፖለቲካዊ ቁርኝት እንዲሁም የሶቪየት ህብረትን የርዕዮተ ዓለም ተጽዕኖ በግልጽ የሚያሳይ ነው።
ምንም እንኳን በ1983 ዓ.ም የደርግ መንግስት መውደቅን ተከትሎ ሐውልቱ የፖለቲካ ምልክት ተደርጎ በመወሰዱ የኩባ ወታደሮች ፎቶግራፎች ተነስተውና ጥገና ተነፍጎት ለዓመታት ቢቆይም፣ ቆይቶ ግን በሁለቱ አገራት ስምምነት መሰረት ዳግም ታድሷል።
በአሁኑ ወቅት ሐውልቱ ከፖለቲካዊ ወገንተኝነት ባለፈ የሀገር ሉዓላዊነት የተከበረበትን ታሪክ የሚዘክር ብሄራዊ ቅርስ ተደርጎ ይወሰዳል።
በየዓመቱ የካቲት 26 ቀን የሚከበረው የካራማራ ድል ቀንም በዚህ ስፍራ በታላቅ ስነ-ስርዓት ይታሰባል።
#ethiopia #cuba #karamaramonument #addisababa #history #victorymonument #ethiopianhistory #militaryheritage #coldwarhistory
5 months ago
📚 ታሪክን የሚያረቅና ትውልድን የሚያነጽ አዲስ መጽሐፍ ሊመረቅ ነው! 🇪🇹
#ethiopia | "በአምባሳደር ተስፋዬ ሀቢሶ የተፃፈው የከምባታ እና የሀዲያ ህዝቦች ታሪክ መጽሐፍ"
በኢትዮጵያ ፖለቲካ እና ዲፕሎማሲ ረጅም ልምድ ባላቸው በአምባሳደር ተስፋዬ ሀቢሶ የተዘጋጀውና የከምባታ እና ሀዲያ ህዝቦችን ታሪክ፣ አስተዳደር እና ባህላዊ ትስስር በጥልቀት የሚዳስሰው አዲስ መጽሐፍ በታላቅ ድምቀት ይመረቃል።
የመጽሐፉ ልዩ ባህሪያት፡
✅ ታሪክን ወደኋላ ሄዶ በጥልቀት ይመረምራል፤ የተዛቡ ትርክቶችን ለማረቅ ፍቱን መድሃኒት ነው።
✅ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ምሁራን ጋር በመመካከር የተዘጋጀ የጥናት ውጤት ነው።
✅ የህዝቦችን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ታሪካዊ ትስስር በማጉላት ለሀገር ግንባታ መንገድ ይጠቁማል።
የምርቃት መርሐ ግብር:
📅 ቀን: የፊታችን እሁድ የካቲት 1 ቀን 2018 ዓ.ም
clock ሰዓት: ከቀኑ 8:00 ሰዓት ጀምሮ
📍 ቦታ: ቦሌ አደይ አበባ ስታዲየም አካባቢ በሚገኘው ብሉ ስካይ ሆቴል
በዕለቱ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ታዋቂ ፖለቲከኞች፣ ምሁራን እና የሀገር ሽማግሌዎች በሚታደሙበት በዚህ መድረክ ላይ እርስዎም ተጋብዘዋል!
ታሪክን ከምንጩ እንጠጣ!
#ambassadortesfayehabiso #newbook #history #kembata #hadiya #ethiopianhistory #booklaunch #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
#ethiopia | "በአምባሳደር ተስፋዬ ሀቢሶ የተፃፈው የከምባታ እና የሀዲያ ህዝቦች ታሪክ መጽሐፍ"
በኢትዮጵያ ፖለቲካ እና ዲፕሎማሲ ረጅም ልምድ ባላቸው በአምባሳደር ተስፋዬ ሀቢሶ የተዘጋጀውና የከምባታ እና ሀዲያ ህዝቦችን ታሪክ፣ አስተዳደር እና ባህላዊ ትስስር በጥልቀት የሚዳስሰው አዲስ መጽሐፍ በታላቅ ድምቀት ይመረቃል።
የመጽሐፉ ልዩ ባህሪያት፡
✅ ታሪክን ወደኋላ ሄዶ በጥልቀት ይመረምራል፤ የተዛቡ ትርክቶችን ለማረቅ ፍቱን መድሃኒት ነው።
✅ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ምሁራን ጋር በመመካከር የተዘጋጀ የጥናት ውጤት ነው።
✅ የህዝቦችን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ታሪካዊ ትስስር በማጉላት ለሀገር ግንባታ መንገድ ይጠቁማል።
የምርቃት መርሐ ግብር:
📅 ቀን: የፊታችን እሁድ የካቲት 1 ቀን 2018 ዓ.ም
clock ሰዓት: ከቀኑ 8:00 ሰዓት ጀምሮ
📍 ቦታ: ቦሌ አደይ አበባ ስታዲየም አካባቢ በሚገኘው ብሉ ስካይ ሆቴል
በዕለቱ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ታዋቂ ፖለቲከኞች፣ ምሁራን እና የሀገር ሽማግሌዎች በሚታደሙበት በዚህ መድረክ ላይ እርስዎም ተጋብዘዋል!
ታሪክን ከምንጩ እንጠጣ!
#ambassadortesfayehabiso #newbook #history #kembata #hadiya #ethiopianhistory #booklaunch #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
5 months ago
📚 የዶ/ር ያየህይራድ ቅጣው የህይወት ታሪክ መጽሐፍ ሊመረቅ ነው!
"ከእናት እቅፍ እስከ ልጅ ልጅ ምርኲዝ ትዝታዎቼ"
#ethiopia | የቀድሞ የትምህርት ሚኒስትር፣ የጄነራል ዊንጌት ብርቱ ተማሪ፣ በፈረንሳይ የህክምና ትምህርታቸውን የተከታተሉ እና የ"ዕድገት በሕብረት" ዘመቻ ላይ አሻራቸውን ያኖሩት የ85 ዓመቱ አዛውርት ዶ/ር ያየህይራድ ቅጣው፤ የህይወት ታሪካቸው በደራሲ እና ጋዜጠኛ ዕዝራ እጅጉ አሰናኝነት ለመጽሐፍ በቅቷል።
የምረቃው ልዩ ድምቀቶች፡-
✨ የክብር መልዕክት: የቀድሞዋ ፕሬዚዳንት ክብርት ወይዘሮ ሣህለወርቅ ዘውዴ ለባለታሪኩ ክብር የቪዲዮ መልዕክት ያስተላልፋሉ።
✨ ዶክመንተሪ: በሳቤህ ዞን እና በተወዳጅ ሚድያ የተዘጋጀ የ3 ሰዓት የድምፅ ዶክመንተሪ ይመረቃል።
✨ እንግዶች: ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ እና ሌሎች ታላላቅ ሰዎች ይገኛሉ፤ መጽሐፉን አቶ ደመላሽ አማረ ይዳስሱታል።
ይህንን በናይእግዚ ኅሩይ አርታኢነት እና በተወዳጅ ሚድያ (ዕዝራ እጅጉ) አዘጋጅነት የተሰናዳውን የ350 ገጽ ታሪካዊ መጽሐፍ ለመታደም እርሶም ተጋብዘዋል።
📅 ቀን: ቅዳሜ ጥር 9 ቀን 2018 ዓ.ም
⌚ ሰዓት: ከቀኑ 8:30 ጀምሮ
📍 ቦታ: ራስ መኮንን አዳራሽ (አ.አ.ዩ)
ኑ! የታላላቆችን ታሪክ እንስማ፤ እንማር!
#dryayehyirad #booklaunch #ethiopianhistory #biography #tewodajmedia #addisababa
"ከእናት እቅፍ እስከ ልጅ ልጅ ምርኲዝ ትዝታዎቼ"
#ethiopia | የቀድሞ የትምህርት ሚኒስትር፣ የጄነራል ዊንጌት ብርቱ ተማሪ፣ በፈረንሳይ የህክምና ትምህርታቸውን የተከታተሉ እና የ"ዕድገት በሕብረት" ዘመቻ ላይ አሻራቸውን ያኖሩት የ85 ዓመቱ አዛውርት ዶ/ር ያየህይራድ ቅጣው፤ የህይወት ታሪካቸው በደራሲ እና ጋዜጠኛ ዕዝራ እጅጉ አሰናኝነት ለመጽሐፍ በቅቷል።
የምረቃው ልዩ ድምቀቶች፡-
✨ የክብር መልዕክት: የቀድሞዋ ፕሬዚዳንት ክብርት ወይዘሮ ሣህለወርቅ ዘውዴ ለባለታሪኩ ክብር የቪዲዮ መልዕክት ያስተላልፋሉ።
✨ ዶክመንተሪ: በሳቤህ ዞን እና በተወዳጅ ሚድያ የተዘጋጀ የ3 ሰዓት የድምፅ ዶክመንተሪ ይመረቃል።
✨ እንግዶች: ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ እና ሌሎች ታላላቅ ሰዎች ይገኛሉ፤ መጽሐፉን አቶ ደመላሽ አማረ ይዳስሱታል።
ይህንን በናይእግዚ ኅሩይ አርታኢነት እና በተወዳጅ ሚድያ (ዕዝራ እጅጉ) አዘጋጅነት የተሰናዳውን የ350 ገጽ ታሪካዊ መጽሐፍ ለመታደም እርሶም ተጋብዘዋል።
📅 ቀን: ቅዳሜ ጥር 9 ቀን 2018 ዓ.ም
⌚ ሰዓት: ከቀኑ 8:30 ጀምሮ
📍 ቦታ: ራስ መኮንን አዳራሽ (አ.አ.ዩ)
ኑ! የታላላቆችን ታሪክ እንስማ፤ እንማር!
#dryayehyirad #booklaunch #ethiopianhistory #biography #tewodajmedia #addisababa
5 months ago
ኢየሩሳሌምን በደብረ ሮሃ! 🇪🇹⛪️
#ethiopia | ንጉሥ ላሊበላ "ኢየሩሳሌምን" በኢትዮጵያ ምድር ለመሥራት 23 ዓመታት እንደፈጀባቸው ያውቃሉ?
የዛግዌ ሥርወ መንግሥት ንጉሥ የሆኑት ቅዱስ ላሊበላ፤ 11ዱን ድንቅ የውቅር አብያተ ክርስቲያናት ሲያሳንጹ በጥልቅ መንፈሳዊ ምሳሌነት ነው።
ሦስቱ ምድቦችና ምሳሌነታቸው፡-
1️⃣ ምድራዊ ኢየሩሳሌም (1ኛው ምድብ)፦ ምዕመናን ወደ ቅድስት ሀገር መሄድ ሳይችሉ ሲቀሩ ሥርዓታቸውን በሀገር ውስጥ እንዲፈጽሙ የተሠራ።
(እንደ ቤተ መድኃኔዓለምና ቤተ ማርያም ያሉት)።
2️⃣ ሰማያዊ ኢየሩሳሌም (2ኛው ምድብ)፦ የመላእክት ከተማን እና መንግሥተ ሰማያትን የሚወክሉ።
(እንደ ቤተ አማኑኤል እና ቤተ ገብርኤል ያሉት)።
3️⃣ የኖኅ መርከብ (3ኛው ምድብ)፦ በመስቀል ቅርጽ የታነጸውና የንጉሡ የመጨረሻ ሥራ የሆነው ቤተ ጊዮርጊስ።
ግንባታው፡ ከላይ ከጣሪያው ተጀምሮ ወደ ታች የተጠረበ (Top-down) እና የውኃ መፋሰሻ ያለው ረቂቅ የኢንጂነሪንግ ጥበብ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#lalibela #ethiopianhistory #zagwedynasty #architecture #ethiopia
#ethiopia | ንጉሥ ላሊበላ "ኢየሩሳሌምን" በኢትዮጵያ ምድር ለመሥራት 23 ዓመታት እንደፈጀባቸው ያውቃሉ?
የዛግዌ ሥርወ መንግሥት ንጉሥ የሆኑት ቅዱስ ላሊበላ፤ 11ዱን ድንቅ የውቅር አብያተ ክርስቲያናት ሲያሳንጹ በጥልቅ መንፈሳዊ ምሳሌነት ነው።
ሦስቱ ምድቦችና ምሳሌነታቸው፡-
1️⃣ ምድራዊ ኢየሩሳሌም (1ኛው ምድብ)፦ ምዕመናን ወደ ቅድስት ሀገር መሄድ ሳይችሉ ሲቀሩ ሥርዓታቸውን በሀገር ውስጥ እንዲፈጽሙ የተሠራ።
(እንደ ቤተ መድኃኔዓለምና ቤተ ማርያም ያሉት)።
2️⃣ ሰማያዊ ኢየሩሳሌም (2ኛው ምድብ)፦ የመላእክት ከተማን እና መንግሥተ ሰማያትን የሚወክሉ።
(እንደ ቤተ አማኑኤል እና ቤተ ገብርኤል ያሉት)።
3️⃣ የኖኅ መርከብ (3ኛው ምድብ)፦ በመስቀል ቅርጽ የታነጸውና የንጉሡ የመጨረሻ ሥራ የሆነው ቤተ ጊዮርጊስ።
ግንባታው፡ ከላይ ከጣሪያው ተጀምሮ ወደ ታች የተጠረበ (Top-down) እና የውኃ መፋሰሻ ያለው ረቂቅ የኢንጂነሪንግ ጥበብ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#lalibela #ethiopianhistory #zagwedynasty #architecture #ethiopia
Sponsored by
Surafel
Comments