1 month ago
ውበቷን ገልጦ ስሟን እና ታሪኳን ያስተሳሰረ የአርባምንጭ ከተማ ኮሪደር ልማት
************************************
በኢትዮጵያ ለቱሪስት መስብነት የታደለችውና የተትረፈረፈ የተፈጥሮ ፀጋ ባለቤት የሆነችው አርባምንጭ ከተማ፣ በሀይቆች፣ በተራሮች፣ በዛፎች እና ደሴቶች ተከባ አረንጓዴ የተላበሰች የተቀናጀ ልማትን ዘርግታለች።
ስሟን እና ታሪኳን አስተሳስሮ በተሠራው በኮሪደር ልማትም ይበልጥ ሳቢና ማራኪ የቱሪስት መዳረሻ ሆናለች።
በከተማዋ በ12 ምድብ ተከፋፍሎ የተሠራው የኮሪደር ልማት ሥራ የሕዝብ መዝናኛ፣ የስፖርት ማዘውተሪያ፣ የገበያ ማዕከላት፣ የህፃናት መጫዋቻ ቦታ፣ የመኪና ማቆሚያዎች እንዲሁም ታሪኳንና ስሟን የሚወክሉ 40/42 እና 63/8 የሚባሉ የደረጃ ፕሮጀክቶችንም አካትቷል።
40/42 የሚለው ስያሜ የተሰጠውም ቱሪስቶችን ወደ አርባዎቹ ምንጮች እና አርባምንጭ ደን የሚወስደው ደረጃ የአርባምንጭ አርባ ምንጮች መገለጫ ሲሆን፣ 42 ደግሞ አርባ ሁለቱን የጋሞ “ደሬዎች” ማለትም ጎሳዎችን የሚወክሉ ናችው።
63/8 ተብሎ የተሰየመው ሌላኛው ፕሮጀክት ደግሞ በ1955 ዓ.ም የተቆረቆረች አርባምንጭ ዛሬ 63 ዓመት መሆኑንና እና 8 ደግሞ ለረጅም ጊዜ የነበረውን የልማት ጥማት ከለውጡ ማግሥት ጀምሮ በርካታ ልማት የተሠራበት በመሆኑ 8 የልማት ዓመታትን ለመግለጽ ታስቦ ነው።
የከተማ ኮሪደር ልማት በተለይ የመንገድ መሠረት ልማት በየአቅጣጫው አንዱ ከአንዱ ጋር የተሳሰረ ሲሆን፣ የአንዱ ሎት (ምድብ) መነሻ ለሌላይኛው ደግሞ መድረሻ ይሆናል።
በዚህም አርባምንጭ ዙሪያዋን የከበቡ ሀይቆች፣ ተራሮች እና አረንጓዴን ለማየት አመቺ ሆኖ እየተሠራ ይገኛል።
ከ50 በላይ የሕዝብ መዝናኛዎች ያለው የአርባምንጭ ኮሪደር ልማት በርካታ የስፖርት ማዘውተሪያ፣ የአካል ጉዳተኞችና እግረኞች ምቹ መንገድ፣ የፐብሊክ ፕላዛዎች እና አንፊ ቴአትር ጨምሮ የተለያዩ የሕዝብ መገልገያዎች ያካተተ ነው።
ከተማዋን በሙሉ በማካለል እየተሠራ የሚገኘው ከ20 ኪሎ ሜትር በላይ የሚረዝመው የኮሪደር ልማት ሥራ አርባምንጭን ይበልጥ የዘመነች እና የቱሪዝም ከተማ አድርጓታል።
በትዕግስቱ ቡቼ
#ethiopia #ebc #corriderdevelopment #urbandevelopment #arbaminch
************************************
በኢትዮጵያ ለቱሪስት መስብነት የታደለችውና የተትረፈረፈ የተፈጥሮ ፀጋ ባለቤት የሆነችው አርባምንጭ ከተማ፣ በሀይቆች፣ በተራሮች፣ በዛፎች እና ደሴቶች ተከባ አረንጓዴ የተላበሰች የተቀናጀ ልማትን ዘርግታለች።
ስሟን እና ታሪኳን አስተሳስሮ በተሠራው በኮሪደር ልማትም ይበልጥ ሳቢና ማራኪ የቱሪስት መዳረሻ ሆናለች።
በከተማዋ በ12 ምድብ ተከፋፍሎ የተሠራው የኮሪደር ልማት ሥራ የሕዝብ መዝናኛ፣ የስፖርት ማዘውተሪያ፣ የገበያ ማዕከላት፣ የህፃናት መጫዋቻ ቦታ፣ የመኪና ማቆሚያዎች እንዲሁም ታሪኳንና ስሟን የሚወክሉ 40/42 እና 63/8 የሚባሉ የደረጃ ፕሮጀክቶችንም አካትቷል።
40/42 የሚለው ስያሜ የተሰጠውም ቱሪስቶችን ወደ አርባዎቹ ምንጮች እና አርባምንጭ ደን የሚወስደው ደረጃ የአርባምንጭ አርባ ምንጮች መገለጫ ሲሆን፣ 42 ደግሞ አርባ ሁለቱን የጋሞ “ደሬዎች” ማለትም ጎሳዎችን የሚወክሉ ናችው።
63/8 ተብሎ የተሰየመው ሌላኛው ፕሮጀክት ደግሞ በ1955 ዓ.ም የተቆረቆረች አርባምንጭ ዛሬ 63 ዓመት መሆኑንና እና 8 ደግሞ ለረጅም ጊዜ የነበረውን የልማት ጥማት ከለውጡ ማግሥት ጀምሮ በርካታ ልማት የተሠራበት በመሆኑ 8 የልማት ዓመታትን ለመግለጽ ታስቦ ነው።
የከተማ ኮሪደር ልማት በተለይ የመንገድ መሠረት ልማት በየአቅጣጫው አንዱ ከአንዱ ጋር የተሳሰረ ሲሆን፣ የአንዱ ሎት (ምድብ) መነሻ ለሌላይኛው ደግሞ መድረሻ ይሆናል።
በዚህም አርባምንጭ ዙሪያዋን የከበቡ ሀይቆች፣ ተራሮች እና አረንጓዴን ለማየት አመቺ ሆኖ እየተሠራ ይገኛል።
ከ50 በላይ የሕዝብ መዝናኛዎች ያለው የአርባምንጭ ኮሪደር ልማት በርካታ የስፖርት ማዘውተሪያ፣ የአካል ጉዳተኞችና እግረኞች ምቹ መንገድ፣ የፐብሊክ ፕላዛዎች እና አንፊ ቴአትር ጨምሮ የተለያዩ የሕዝብ መገልገያዎች ያካተተ ነው።
ከተማዋን በሙሉ በማካለል እየተሠራ የሚገኘው ከ20 ኪሎ ሜትር በላይ የሚረዝመው የኮሪደር ልማት ሥራ አርባምንጭን ይበልጥ የዘመነች እና የቱሪዝም ከተማ አድርጓታል።
በትዕግስቱ ቡቼ
#ethiopia #ebc #corriderdevelopment #urbandevelopment #arbaminch
1 month ago
በኮሪደር ልማት የመደመር መንግሥትን እሳቤዎችና የሥራ ጥራት ማሳየት ተችሏል - የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ
****************
የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የዘርፉን አፈጻጸምና ቀጣይ አቅጣጫዎች የሚገመግምበት የሴክተር ጉባኤ በአርባምንጭ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
በአርባምንጭ ከተማ ከንቲባ መስፍን መንዛ (ዶ/ር) የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት በተከፈተው የሴክተር ጉባኤ ግምገማ፥ የፌደራል፣ የክልልና የከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና ባለድርሻ አካላት ታድመዋል።
በመድረኩ የተገኙት የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትሯ ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ፥ የኮሪደር ልማት ከተሞችን በመቅረጽና መልክ በመስጠት ረገድ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ አንስተው፤ በዚህም የመደመር መንግሥትን እሳቤዎችና የሥራ ጥራት ማሳየት መቻሉን ገልጸዋል።
በሀገራችን እየተከናወነ ያለው የመንገድና የኮሪደር ልማት፣ በበለጠ ትስስር የበለጸገች ፍትሐዊት ሀገር የመመስረት ራዕይን የሚያሳካ ስለመሆኑ በመድረኩ ተነስቷል።
በከተሞች የታየውን አስደማሚ ስኬት በገጠር ኮሪደር ልማት በማስቀጠል ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ በትኩረት እንደሚሠራም በጉባኤው ተመላክቷል።
የመደመር መንግሥት ፕሮጀክቶችን ከመጀመር ባለፈ የተጀመሩትን በጥራት በማጠናቀቅ ረገድ በትኩረት እየሠራ ስለመሆኑም ተነስቷል።
በጥቅሉ ዛሬ በየቦታው እየተመዘገቡ ያሉ ስኬቶች ሁሉ የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥትን ታታሪነትና ትጋት ፍንትው አድርገው የሚያሳዩ ናቸው ተብሏል።
የተጀመረው የብልጽግና ጉዞ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የሕዝብ፣ የመንግሥትና የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ወሳኝ ነው የተባለ ሲሆን፣ በቀጣይም የመሠረተ ልማት ውጥኖችን በትብብር በመፈጸም ጠንካራ ሀገር ለመገንባት መረባረብ እንደሚገባ መልዕክት ተላልፏል።
#ethiopia #urbandevelopment #urbancorridor #ebc
****************
የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የዘርፉን አፈጻጸምና ቀጣይ አቅጣጫዎች የሚገመግምበት የሴክተር ጉባኤ በአርባምንጭ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።
በአርባምንጭ ከተማ ከንቲባ መስፍን መንዛ (ዶ/ር) የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት በተከፈተው የሴክተር ጉባኤ ግምገማ፥ የፌደራል፣ የክልልና የከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና ባለድርሻ አካላት ታድመዋል።
በመድረኩ የተገኙት የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትሯ ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ፥ የኮሪደር ልማት ከተሞችን በመቅረጽና መልክ በመስጠት ረገድ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ አንስተው፤ በዚህም የመደመር መንግሥትን እሳቤዎችና የሥራ ጥራት ማሳየት መቻሉን ገልጸዋል።
በሀገራችን እየተከናወነ ያለው የመንገድና የኮሪደር ልማት፣ በበለጠ ትስስር የበለጸገች ፍትሐዊት ሀገር የመመስረት ራዕይን የሚያሳካ ስለመሆኑ በመድረኩ ተነስቷል።
በከተሞች የታየውን አስደማሚ ስኬት በገጠር ኮሪደር ልማት በማስቀጠል ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ በትኩረት እንደሚሠራም በጉባኤው ተመላክቷል።
የመደመር መንግሥት ፕሮጀክቶችን ከመጀመር ባለፈ የተጀመሩትን በጥራት በማጠናቀቅ ረገድ በትኩረት እየሠራ ስለመሆኑም ተነስቷል።
በጥቅሉ ዛሬ በየቦታው እየተመዘገቡ ያሉ ስኬቶች ሁሉ የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥትን ታታሪነትና ትጋት ፍንትው አድርገው የሚያሳዩ ናቸው ተብሏል።
የተጀመረው የብልጽግና ጉዞ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የሕዝብ፣ የመንግሥትና የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ወሳኝ ነው የተባለ ሲሆን፣ በቀጣይም የመሠረተ ልማት ውጥኖችን በትብብር በመፈጸም ጠንካራ ሀገር ለመገንባት መረባረብ እንደሚገባ መልዕክት ተላልፏል።
#ethiopia #urbandevelopment #urbancorridor #ebc
3 months ago
የአዲስ አበባ የተቀናጁ የልማት ፕሮጀክቶች የከተማዋን ዓለምአቀፍ ዝና እና ተወዳዳሪነት በከፍተኛ ደረጃ እያሳደጉት ነው
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ በመከናወን ላይ የሚገኙት የተቀናጁ የልማት ስራዎች የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ የነዋሪዎችን የኑሮ ጥራት እያሻሻሉ መሆኑን የዘርፉ ምሁራን ገለጹ።
ኤን ቢ ሲ ኢትዮጵያ (NBC Ethiopia) “አዲሲቱ አዲስ” በሚል መሪ ቃል ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ እንደተጠቆመው፤ ከተማዋ ካለፉት ጥቂት ዓመታት ወዲህ እያሳየችው ያለው እድገት እጅግ ተስፋ ሰጪ ነው።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኪነ-ህንጻ መምህር የሆኑት ዳዊት በንቲ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ ከተማዋ በተመሰረተችባቸው የቀድሞ ዘመናት በታቀደ ፕላን ያልተመራች በመሆኑ ዘመናዊነትን ለማምጣት ፈታኝ ሆኖ ቆይቷል። ይሁን እንጂ ከ2010 ዓ.ም ወዲህ ተግባራዊ እየተደረጉ ያሉ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ይህንን ታሪክ እየቀየሩት ይገኛሉ።
በተለይም ዘመናዊ ፓርኮች፣ ሰፊ አረንጓዴ ስፍራዎች፣ የወንዝ ዳርቻ ልማቶች እንዲሁም ለእግረኛ እና ለብስክሌት ተጓዦች ምቹ የሆኑ መንገዶች መገንባታቸው የነዋሪዎችን የአኗኗር ዘይቤ ወደ ተሻለ ደረጃ አሸጋግረውታል።
የከተማ እና ቀጣናዊ ፕላኒንግ ተመራማሪው ኢንጂነር እሸትአየሁ ክንፉ በበኩላቸው፤ በአሁኑ ወቅት እየተተገበረ ያለው የከተማ ማደስ ስራ ፍትሃዊነትን ያከለለ እና አዲስ አበባን ከሌሎች የዓለም ታላላቅ ከተሞች ጋር እኩል ተወዳዳሪ ለማድረግ ያለመ መሆኑን አስረድተዋል።
እነዚህ የተቀናጁ ስራዎች ከተማዋ ለኑሮ ምቹ እና ለቴክኖሎጂ ዝግጁ እንድትሆን ትልቅ ሚና እየተጫወቱ እንደሚገኙም ተመላክቷል።
የኤንቢሲ ምክትል ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዘካርያስ ብርሀኑ በመድረኩ መክፈቻ ላይ እንደተናገሩት፤ አዲስ አበባ አሁን ላይ ተጨባጭና ግዙፍ ለውጥ እያስመዘገበች ያለች ከተማ በመሆኗ ይህንን ለውጥ ከዓለምአቀፍ ተሞክሮዎች ጋር በማነጻጸር የጥናት ውይይት ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል ብለዋል።
#addisababa #urbandevelopment #ethiopiaprogress #moderncity #greendevelopment #cityplanning #newaddis #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ በመከናወን ላይ የሚገኙት የተቀናጁ የልማት ስራዎች የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ የነዋሪዎችን የኑሮ ጥራት እያሻሻሉ መሆኑን የዘርፉ ምሁራን ገለጹ።
ኤን ቢ ሲ ኢትዮጵያ (NBC Ethiopia) “አዲሲቱ አዲስ” በሚል መሪ ቃል ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ እንደተጠቆመው፤ ከተማዋ ካለፉት ጥቂት ዓመታት ወዲህ እያሳየችው ያለው እድገት እጅግ ተስፋ ሰጪ ነው።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኪነ-ህንጻ መምህር የሆኑት ዳዊት በንቲ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ ከተማዋ በተመሰረተችባቸው የቀድሞ ዘመናት በታቀደ ፕላን ያልተመራች በመሆኑ ዘመናዊነትን ለማምጣት ፈታኝ ሆኖ ቆይቷል። ይሁን እንጂ ከ2010 ዓ.ም ወዲህ ተግባራዊ እየተደረጉ ያሉ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ይህንን ታሪክ እየቀየሩት ይገኛሉ።
በተለይም ዘመናዊ ፓርኮች፣ ሰፊ አረንጓዴ ስፍራዎች፣ የወንዝ ዳርቻ ልማቶች እንዲሁም ለእግረኛ እና ለብስክሌት ተጓዦች ምቹ የሆኑ መንገዶች መገንባታቸው የነዋሪዎችን የአኗኗር ዘይቤ ወደ ተሻለ ደረጃ አሸጋግረውታል።
የከተማ እና ቀጣናዊ ፕላኒንግ ተመራማሪው ኢንጂነር እሸትአየሁ ክንፉ በበኩላቸው፤ በአሁኑ ወቅት እየተተገበረ ያለው የከተማ ማደስ ስራ ፍትሃዊነትን ያከለለ እና አዲስ አበባን ከሌሎች የዓለም ታላላቅ ከተሞች ጋር እኩል ተወዳዳሪ ለማድረግ ያለመ መሆኑን አስረድተዋል።
እነዚህ የተቀናጁ ስራዎች ከተማዋ ለኑሮ ምቹ እና ለቴክኖሎጂ ዝግጁ እንድትሆን ትልቅ ሚና እየተጫወቱ እንደሚገኙም ተመላክቷል።
የኤንቢሲ ምክትል ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዘካርያስ ብርሀኑ በመድረኩ መክፈቻ ላይ እንደተናገሩት፤ አዲስ አበባ አሁን ላይ ተጨባጭና ግዙፍ ለውጥ እያስመዘገበች ያለች ከተማ በመሆኗ ይህንን ለውጥ ከዓለምአቀፍ ተሞክሮዎች ጋር በማነጻጸር የጥናት ውይይት ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል ብለዋል።
#addisababa #urbandevelopment #ethiopiaprogress #moderncity #greendevelopment #cityplanning #newaddis #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 months ago
አዲሱ የአራዳ ፓርክ የታሪክ ማስታወሻ የውበት ምንጭና የዘመናዊነት መገለጫ
#ethiopia | የአራዳ ፓርክ ቀደም ሲል የነበረውን የቆሻሻ የብክለትና የድህነት ገጽታ ሙሉ በሙሉ በመቀየር በአዲስ መልክ የተገነባ ታላቅ ፕሮጀክት ነው::
ይህ ስራ የቆዩ አሉታዊ የታሪክ አሻራዎችን በማጥፋት የኢትዮጵያን አዲስ ማንነትና ውበት ለትውልድ በሚተርክ መልኩ ተከናውኗል::
ከፒያሳ አካባቢ የለቀቁ ነዋሪዎች ለሰብአዊ ክብር ከማይመጥኑ ቤቶች ወጥተው መሰረተ ልማት ወደተሟላላቸው ዘመናዊ መኖሪያዎች እንዲገቡ ተደርጓል::
ነዋሪዎቹ ማህበራዊ ትስስራቸውን ሳይበጥሱ እድርና እቁባቸውን ጠብቀው እንዲኖሩ መደረጉም የልማቱ ልዩ ገጽታ ነው:: ፒያሳ ዳግም የተገነባችው እውነተኛ ስልጣኔን በሚያንጸባርቅ መልኩ ሲሆን በአካባቢው የነበሩ ወንዞችም ከቆሻሻ ጸድተው ለስራ እድል ፈጠራና ለቱሪስት መዳረሻነት እንዲውሉ ተደርገዋል::
በ40 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው የአራዳ ፓርክ የሚከተሉትን ዋና ዋና አገልግሎቶች ይዟል
የመንገድና የትራንስፖርት መሰረተ ልማት
5 ኪሎ ሜትር የአስፓልት መንገድ 6 ኪሎ ሜትር የእግረኛ መንገድ 5 ኪሎ ሜትር የብስክሌት መስመር እና 5 ኪሎ ሜትር የመሮጫ ትራክ ተገንብቶለታል::
የንግድና የፋይናንስ ዘርፍ
ከፒያሳ ለተነሱ ነጋዴዎች ቅድሚያ የሚሰጥባቸው 131 ዘመናዊ ሱቆች 7 ካፌና ሬስቶራንቶች አንድ ትልቅ ሱፐርማርኬት እና የባንክ ቅርንጫፍ ተካተዋል::
የመዝናኛና የስፖርት አገልግሎቶች
ዘመናዊ የአካል ብቃት ማእከል 7 አዳራሾች 8 ፕላዛዎች 3 አንፊ ቴአትሮች እና ማራኪ የሆነ ተንቀሳቃሽ ፏፏቴ ይገኛሉ:: በተጨማሪም 100 ሜትር ርዝመት ያለው የሀገሪቱ ረጅሙ የሰንደቅ ዓላማ መስቀያ በዚሁ ፓርክ ተተክሏል::
የህጻናትና ቤተሰብ ስፍራዎች
አራት ዘመናዊ የህጻናት መጫወቻዎች እና ህጻናት ስለ ሀገራቸው ግንዛቤ የሚያገኙበት ትንሿ ከተማ የተሰኘ ልዩ ስፍራ ተዘጋጅቷል::
የአረንጓዴ ልማትና የንጽህና አገልግሎት
15 ሄክታር መሬት በሳርና በተክሎች የተሸፈነ ሲሆን 22 የህዝብ መጸዳጃ ቤቶች እና 131 መኪናዎችን የሚይዝ ሰፊ ማቆሚያ ተገንብቷል::
ይህ ፕሮጀክት የመሬት አጠቃቀምን በብቃት ያረጋገጠ ሲሆን ከመሬት በታች ለሱቆችና ለአዳራሾች ከላይ ደግሞ ለፕላዛ አገልግሎት እንዲውል ተደርጓል::
እንዲሁም በአካባቢው የነበሩ ከ700 በላይ ታሪካዊ ቤቶችና ህንጻዎች ይዘታቸውን ሳይለቁ እንዲታደሱ ተደርጓል::
በአጠቃላይ ፓርኩ ከንግድ እስከ ስፖርት እንዲሁም ከቤተሰብ መዝናኛ እስከ ስነ ጥበብ መድረኮችን የያዘ የከተማዋ አዲስ የቱሪስት መስህብ ነው::
#aradapark #piassa #addisababacity #urbandevelopment #greenlegacy #tourismethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የአራዳ ፓርክ ቀደም ሲል የነበረውን የቆሻሻ የብክለትና የድህነት ገጽታ ሙሉ በሙሉ በመቀየር በአዲስ መልክ የተገነባ ታላቅ ፕሮጀክት ነው::
ይህ ስራ የቆዩ አሉታዊ የታሪክ አሻራዎችን በማጥፋት የኢትዮጵያን አዲስ ማንነትና ውበት ለትውልድ በሚተርክ መልኩ ተከናውኗል::
ከፒያሳ አካባቢ የለቀቁ ነዋሪዎች ለሰብአዊ ክብር ከማይመጥኑ ቤቶች ወጥተው መሰረተ ልማት ወደተሟላላቸው ዘመናዊ መኖሪያዎች እንዲገቡ ተደርጓል::
ነዋሪዎቹ ማህበራዊ ትስስራቸውን ሳይበጥሱ እድርና እቁባቸውን ጠብቀው እንዲኖሩ መደረጉም የልማቱ ልዩ ገጽታ ነው:: ፒያሳ ዳግም የተገነባችው እውነተኛ ስልጣኔን በሚያንጸባርቅ መልኩ ሲሆን በአካባቢው የነበሩ ወንዞችም ከቆሻሻ ጸድተው ለስራ እድል ፈጠራና ለቱሪስት መዳረሻነት እንዲውሉ ተደርገዋል::
በ40 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው የአራዳ ፓርክ የሚከተሉትን ዋና ዋና አገልግሎቶች ይዟል
የመንገድና የትራንስፖርት መሰረተ ልማት
5 ኪሎ ሜትር የአስፓልት መንገድ 6 ኪሎ ሜትር የእግረኛ መንገድ 5 ኪሎ ሜትር የብስክሌት መስመር እና 5 ኪሎ ሜትር የመሮጫ ትራክ ተገንብቶለታል::
የንግድና የፋይናንስ ዘርፍ
ከፒያሳ ለተነሱ ነጋዴዎች ቅድሚያ የሚሰጥባቸው 131 ዘመናዊ ሱቆች 7 ካፌና ሬስቶራንቶች አንድ ትልቅ ሱፐርማርኬት እና የባንክ ቅርንጫፍ ተካተዋል::
የመዝናኛና የስፖርት አገልግሎቶች
ዘመናዊ የአካል ብቃት ማእከል 7 አዳራሾች 8 ፕላዛዎች 3 አንፊ ቴአትሮች እና ማራኪ የሆነ ተንቀሳቃሽ ፏፏቴ ይገኛሉ:: በተጨማሪም 100 ሜትር ርዝመት ያለው የሀገሪቱ ረጅሙ የሰንደቅ ዓላማ መስቀያ በዚሁ ፓርክ ተተክሏል::
የህጻናትና ቤተሰብ ስፍራዎች
አራት ዘመናዊ የህጻናት መጫወቻዎች እና ህጻናት ስለ ሀገራቸው ግንዛቤ የሚያገኙበት ትንሿ ከተማ የተሰኘ ልዩ ስፍራ ተዘጋጅቷል::
የአረንጓዴ ልማትና የንጽህና አገልግሎት
15 ሄክታር መሬት በሳርና በተክሎች የተሸፈነ ሲሆን 22 የህዝብ መጸዳጃ ቤቶች እና 131 መኪናዎችን የሚይዝ ሰፊ ማቆሚያ ተገንብቷል::
ይህ ፕሮጀክት የመሬት አጠቃቀምን በብቃት ያረጋገጠ ሲሆን ከመሬት በታች ለሱቆችና ለአዳራሾች ከላይ ደግሞ ለፕላዛ አገልግሎት እንዲውል ተደርጓል::
እንዲሁም በአካባቢው የነበሩ ከ700 በላይ ታሪካዊ ቤቶችና ህንጻዎች ይዘታቸውን ሳይለቁ እንዲታደሱ ተደርጓል::
በአጠቃላይ ፓርኩ ከንግድ እስከ ስፖርት እንዲሁም ከቤተሰብ መዝናኛ እስከ ስነ ጥበብ መድረኮችን የያዘ የከተማዋ አዲስ የቱሪስት መስህብ ነው::
#aradapark #piassa #addisababacity #urbandevelopment #greenlegacy #tourismethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 months ago
ለአርቲስቶች የተለየ የፈጠራ ድባብ ያስፈልጋቸዋል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
*******************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "የማህበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ" በሚል በተዘጋጀው መድረክ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ አርቲስቶች ካላቸው ልዩ ተሰጥኦና የፈጠራ ብቃት አኳያ የሚመጥን ድባብ መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሳተላይት ከተማ ፕሮጀክት ውስጥ ስለሚገነባው የኪነ-ጥበብ ማዕከል ባደረጉት ገለጻ፣ በግንባታ ላይ ያለው "ግራንድ ሰርክል ሆል" ግማሽ አካሉ ለአርት ጋለሪ እንዲውል ተደርጎ ታስቦ እየተገነባ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ይህ ተግባር ለዛሬው ብቻ ሳይሆን ለነገውም ትውልድ ጭምር ታስቦ የተከናወነ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስረድተዋል።
አርቲስቶች ካላቸው ልዩ የመፍጠር ተሰጥኦ ባሻገር ማንኛውም ሰው ከሚያስብበት መንገድ ወጣ ያለ አመለካከትና የአኗኗር ዘይቤ ያላቸው በመሆናቸው፣ ለሥራቸውና ለፈጠራቸው ምቹ የሆነና ከልማድ የወጣ አካባቢ እንደሚፈልጉ አብራርተዋል።
ይህን መሰል ለአርቲስቶች ምቹ የሆነ የሥራ ድባብ መፍጠር ለኢትዮጵያ ቀላል ባይሆንም፣ መንግሥት ግን የአርቲስቶችን ልዩ ባህርይና ፍላጎት ከግምት ውስጥ ያስገቡ ማዕከላትን በመገንባት ለዘርፉ ያለውን ክብርና ትኩረት በተግባር እያሳየ መሆኑን ተናግረዋል።
#ebc #ethiopia #pmabiyahmed #artgallery #creativeeconomy #urbandevelopment
*******************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "የማህበራዊ ልማት እመርታ ለሀገር ግንባታ" በሚል በተዘጋጀው መድረክ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ አርቲስቶች ካላቸው ልዩ ተሰጥኦና የፈጠራ ብቃት አኳያ የሚመጥን ድባብ መፍጠር አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሳተላይት ከተማ ፕሮጀክት ውስጥ ስለሚገነባው የኪነ-ጥበብ ማዕከል ባደረጉት ገለጻ፣ በግንባታ ላይ ያለው "ግራንድ ሰርክል ሆል" ግማሽ አካሉ ለአርት ጋለሪ እንዲውል ተደርጎ ታስቦ እየተገነባ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ይህ ተግባር ለዛሬው ብቻ ሳይሆን ለነገውም ትውልድ ጭምር ታስቦ የተከናወነ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስረድተዋል።
አርቲስቶች ካላቸው ልዩ የመፍጠር ተሰጥኦ ባሻገር ማንኛውም ሰው ከሚያስብበት መንገድ ወጣ ያለ አመለካከትና የአኗኗር ዘይቤ ያላቸው በመሆናቸው፣ ለሥራቸውና ለፈጠራቸው ምቹ የሆነና ከልማድ የወጣ አካባቢ እንደሚፈልጉ አብራርተዋል።
ይህን መሰል ለአርቲስቶች ምቹ የሆነ የሥራ ድባብ መፍጠር ለኢትዮጵያ ቀላል ባይሆንም፣ መንግሥት ግን የአርቲስቶችን ልዩ ባህርይና ፍላጎት ከግምት ውስጥ ያስገቡ ማዕከላትን በመገንባት ለዘርፉ ያለውን ክብርና ትኩረት በተግባር እያሳየ መሆኑን ተናግረዋል።
#ebc #ethiopia #pmabiyahmed #artgallery #creativeeconomy #urbandevelopment
4 months ago
ሩጫ ለልማት
ከኢትዮ ሪል እስቴት ጋር ለተሻለ ነገ እንሩጥ! 🏃♂️✨
ኢትዮጵያ የፈጣን ዕድገት ጉዞ ላይ ናት!
በዚህ ጉዞ ውስጥ የሪል እስቴት ልማት የመኖሪያ ቤቶችን በመገንባት፣ የከተማ መዋቅርን በማሻሻልና የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር ትልቅ አሻራ እያሳረፈ ይገኛል።
የ“ኢትዮ ሪል እስቴት ልማት ሩጫ” ፋይዳ፦
የአንድነት ምልክት፦
ወጣቶች፣ ቤተሰቦች፣ ባለሙያዎችና የቢዝነስ ማህበረሰቡ በአንድነት ለተሻለ ነገ የሚሮጡበት መድረክ ነው።
የልማት አጋርነት፦
ከአርኪ ኤቨንትስ እና ከእፎይ ለቤቴ ትሬዲንግ ጋር በመተባበር የተዘጋጀው ይህ ሩጫ፣ ልማት የሁላችንም የጋራ ጉዞ መሆኑን ያበስራል።
ኢኮኖሚያዊ ዕድገት፦
የዘርፉን እንቅስቃሴ በማነቃቃት ለሀገር ግንባታ የሚኖረውን አስተዋፅኦ ማጉላት።
ከኢትዮ ሪል እስቴት ጋር እንሮጥ — ለተሻለ ነገ፣ ለተገነባ ሕይወት!
#ethiorealestaterun #runfordevelopment #ethiopiaprogress #arkievents #effoylebete #urbandevelopment #healthyliving #addisababa #realestateethiopia #ልማት #ሩጫ #ሪልእስቴት #ኢትዮጵያ #ለተሻለነገ
ከኢትዮ ሪል እስቴት ጋር ለተሻለ ነገ እንሩጥ! 🏃♂️✨
ኢትዮጵያ የፈጣን ዕድገት ጉዞ ላይ ናት!
በዚህ ጉዞ ውስጥ የሪል እስቴት ልማት የመኖሪያ ቤቶችን በመገንባት፣ የከተማ መዋቅርን በማሻሻልና የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር ትልቅ አሻራ እያሳረፈ ይገኛል።
የ“ኢትዮ ሪል እስቴት ልማት ሩጫ” ፋይዳ፦
የአንድነት ምልክት፦
ወጣቶች፣ ቤተሰቦች፣ ባለሙያዎችና የቢዝነስ ማህበረሰቡ በአንድነት ለተሻለ ነገ የሚሮጡበት መድረክ ነው።
የልማት አጋርነት፦
ከአርኪ ኤቨንትስ እና ከእፎይ ለቤቴ ትሬዲንግ ጋር በመተባበር የተዘጋጀው ይህ ሩጫ፣ ልማት የሁላችንም የጋራ ጉዞ መሆኑን ያበስራል።
ኢኮኖሚያዊ ዕድገት፦
የዘርፉን እንቅስቃሴ በማነቃቃት ለሀገር ግንባታ የሚኖረውን አስተዋፅኦ ማጉላት።
ከኢትዮ ሪል እስቴት ጋር እንሮጥ — ለተሻለ ነገ፣ ለተገነባ ሕይወት!
#ethiorealestaterun #runfordevelopment #ethiopiaprogress #arkievents #effoylebete #urbandevelopment #healthyliving #addisababa #realestateethiopia #ልማት #ሩጫ #ሪልእስቴት #ኢትዮጵያ #ለተሻለነገ
Sponsored by
Surafel
4 months ago
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የወርቅ ኢዮቤልዩ ተጠናቀቀ፤
የቤት አቅርቦትን በዘላቂነት ለመፍታት ቃል ተገባ
#ethiopia | ላለፉት ሦስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ምስረታ 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል ዛሬ በማጠቃለያ መድረክና ዕውቅና በመስጠት ተጠናቋል።
በኮርፖሬሽኑ የተገነቡ አዳዲስ ሕንጻዎች የተመረቁ ሲሆን፣ የተቋሙን የሪፎርም ስኬት የሚያሳይ ኤግዚቢሽን ለዕይታ ክፍት ሆኖ ቆይቷል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ረሻድ ከማል (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ በቀጣይ ዓመታት የቤት አቅርቦት ፍላጎትን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉ ሰፋፊ ዕቅዶች ተይዘዋል።
ዕውቅና፦ ለተቋሙ ግማሽ ክፍለ ዘመን ጉዞና ለተመዘገቡ ስኬቶች አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ልዩ ዕውቅና ተሰጥቷል።
ዶ/ር ረሻድ ተቋሙ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ያከናወነው የሪፎርም ሥራ ውጤታማ መሆኑን ጠቁመው፣ የቤት ፍላጎት የሰው ልጅ መሠረታዊ መብት በመሆኑ ባለድርሻ አካላት ከኮርፖሬሽኑ ጋር በቅንጅት እንዲሠሩ ጥሪ አቅርበዋል።
#getu #federalhousingcorporation #goldenjubilee #housingethiopia #drreshadkemal #realestateethiopia #urbandevelopment #addisababa #ethiopianews #የፌዴራልቤቶችኮርፖሬሽን #ወርቅኢዮቤልዩ #ቤትልማት #ሪልስቴት #አዲስአበባ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
የቤት አቅርቦትን በዘላቂነት ለመፍታት ቃል ተገባ
#ethiopia | ላለፉት ሦስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ምስረታ 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል ዛሬ በማጠቃለያ መድረክና ዕውቅና በመስጠት ተጠናቋል።
በኮርፖሬሽኑ የተገነቡ አዳዲስ ሕንጻዎች የተመረቁ ሲሆን፣ የተቋሙን የሪፎርም ስኬት የሚያሳይ ኤግዚቢሽን ለዕይታ ክፍት ሆኖ ቆይቷል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ረሻድ ከማል (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ በቀጣይ ዓመታት የቤት አቅርቦት ፍላጎትን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉ ሰፋፊ ዕቅዶች ተይዘዋል።
ዕውቅና፦ ለተቋሙ ግማሽ ክፍለ ዘመን ጉዞና ለተመዘገቡ ስኬቶች አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ልዩ ዕውቅና ተሰጥቷል።
ዶ/ር ረሻድ ተቋሙ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ያከናወነው የሪፎርም ሥራ ውጤታማ መሆኑን ጠቁመው፣ የቤት ፍላጎት የሰው ልጅ መሠረታዊ መብት በመሆኑ ባለድርሻ አካላት ከኮርፖሬሽኑ ጋር በቅንጅት እንዲሠሩ ጥሪ አቅርበዋል።
#getu #federalhousingcorporation #goldenjubilee #housingethiopia #drreshadkemal #realestateethiopia #urbandevelopment #addisababa #ethiopianews #የፌዴራልቤቶችኮርፖሬሽን #ወርቅኢዮቤልዩ #ቤትልማት #ሪልስቴት #አዲስአበባ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
5 months ago
በአዲስ አበባ የግንባታ ዘርፍ የሠራተኞችን ደኅንነት የሚያስከብር አዲስ መመሪያ ሊተገበር ነው
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ በሚካሄዱ የሕንፃ ግንባታዎች ላይ የሚከሰቱ አደጋዎችንና የሕይወት መጥፋትን ለመቀነስ፣ የግንባታ ባለቤቶች (አስገንቢዎች) የሠራተኞችን ደኅንነት የሚከታተል ባለሙያ እንዲቀጥሩ የሚያስገድድ አዲስ መመሪያ እየተዘጋጀ መሆኑ ተገለጸ።
የአዲስ አበባ ከተማ ግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን እንዳስታወቀው፣ ይህ መመሪያ ማንኛውም አስገንቢ ልክ እንደ አማካሪና ኮንትራክተር ሁሉ በዘርፉ የሠለጠነ የደኅንነት ባለሙያ እንዲመድብ ያስገድዳል። 17 ነጥቦችን የያዘው ይህ ሰነድ፣ የግንባታ አካባቢዎች በደኅንነት መረብ እንዲሸፈኑ እንዲሁም ሠራተኞች እንደ ራስ ቆብ (Helmet)፣ የደኅንነት ጫማ፣ ጓንትና አንጸባራቂ ልብሶችን በግዴታ እንዲጠቀሙ የሚያዝ ነው።
ባለሥልጣኑ ለዚሁ ተግባር እንዲውል በ2018 በጀት ዓመት 2,000 ባለሙያዎችን ለማሠልጠን አቅዶ፣ እስካሁን ከ800 በላይ የሚሆኑትን ማሠልጠኑ ተመላክቷል።
ይህ ጥብቅ መመሪያ አስፈላጊ የሆነው ባለፉት ሦስት ዓመታት ብቻ በግንባታ ቦታዎች ላይ በሚከሰቱ ጥንቃቄ የጎደላቸው አደጋዎች የ142 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ተከትሎ እንደሆነ የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል ያለው ስፑትኒክ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #addisababa #constructionsafety #ethiopianews #safetyfirst #urbandevelopment #buildingregulation #ethiopia
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ በሚካሄዱ የሕንፃ ግንባታዎች ላይ የሚከሰቱ አደጋዎችንና የሕይወት መጥፋትን ለመቀነስ፣ የግንባታ ባለቤቶች (አስገንቢዎች) የሠራተኞችን ደኅንነት የሚከታተል ባለሙያ እንዲቀጥሩ የሚያስገድድ አዲስ መመሪያ እየተዘጋጀ መሆኑ ተገለጸ።
የአዲስ አበባ ከተማ ግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን እንዳስታወቀው፣ ይህ መመሪያ ማንኛውም አስገንቢ ልክ እንደ አማካሪና ኮንትራክተር ሁሉ በዘርፉ የሠለጠነ የደኅንነት ባለሙያ እንዲመድብ ያስገድዳል። 17 ነጥቦችን የያዘው ይህ ሰነድ፣ የግንባታ አካባቢዎች በደኅንነት መረብ እንዲሸፈኑ እንዲሁም ሠራተኞች እንደ ራስ ቆብ (Helmet)፣ የደኅንነት ጫማ፣ ጓንትና አንጸባራቂ ልብሶችን በግዴታ እንዲጠቀሙ የሚያዝ ነው።
ባለሥልጣኑ ለዚሁ ተግባር እንዲውል በ2018 በጀት ዓመት 2,000 ባለሙያዎችን ለማሠልጠን አቅዶ፣ እስካሁን ከ800 በላይ የሚሆኑትን ማሠልጠኑ ተመላክቷል።
ይህ ጥብቅ መመሪያ አስፈላጊ የሆነው ባለፉት ሦስት ዓመታት ብቻ በግንባታ ቦታዎች ላይ በሚከሰቱ ጥንቃቄ የጎደላቸው አደጋዎች የ142 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ተከትሎ እንደሆነ የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል ያለው ስፑትኒክ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #addisababa #constructionsafety #ethiopianews #safetyfirst #urbandevelopment #buildingregulation #ethiopia
5 months ago
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን 50ኛ ዓመት
ከውድቀት ወደ ስኬት የተሻገረበት "የወርቅ ኢዮቤልዩ"! ✨
#ethiopia | የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የተመሰረተበትን 50ኛ ዓመት በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ማክበር ጀምሯል።
የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ረሻድ ከማል በመክፈቻው መርሃ ግብር ላይ እንደገለጹት፤ ሀገራዊ ለውጡ ለተቋሙ "ዳግም ውልደት" ሆኖለታል።
የለውጡ ትሩፋቶች እንደ ዶ/ር ረሻድ ገለጻ፦
ተቋማዊ ሪፎርም፦ ተቋሙ ከነበረበት ውስብስብ ችግር ተላቆ አዲስ የስኬት ምዕራፍ ላይ መድረስ ችሏል።
የመንግስት ትኩረት፦
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሚመራው መንግሥት ለተቋሙ በሰጠው ልዩ ትኩረት ኮርፖሬሽኑ አገልግሎቱን እንዲያሳድግ አስችሎታል።
ቴክኖሎጂ መር መፍትሔዎች፦ በቀጣይ የመኖሪያ ቤት አቅርቦትን ለማሻሻል ዘመናዊና ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረጉ ስራዎች ላይ ትኩረት ተደርጓል።
⚽️ ጤናማና ምርታማ ሰራተኛ፦
የኢዮቤልዩ በዓሉ አካል የሆነው ስፖርታዊ ውድድርም ተጀምሯል። ይህ ውድድር በስምንት ቡድኖች መካከል የሚካሄድ ሲሆን፣ ዓላማውም የሰራተኛውን አንድነት በማጠናከር ለላቀ ውጤት ማዘጋጀት እንደሆነ ተገልጿል።
የኮርፖሬሽኑ አዲስ ገጽታ፦
ባለፉት ጥቂት ዓመታት የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በአዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች እየገነባቸው ያሉ ዘመናዊ የመኖሪያ መንደሮች (Apartments) የተቋሙን አዲስ ቁመናና የሪፎርሙን ውጤት በተግባር እያሳዩ እንደሚገኙ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ረሻድ ከማል አስታውቀዋል።
#federalhousingcorporation #fhc50 #housingethiopia #infrastructure #urbandevelopment #drreshadkemal #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
ከውድቀት ወደ ስኬት የተሻገረበት "የወርቅ ኢዮቤልዩ"! ✨
#ethiopia | የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የተመሰረተበትን 50ኛ ዓመት በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ማክበር ጀምሯል።
የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ረሻድ ከማል በመክፈቻው መርሃ ግብር ላይ እንደገለጹት፤ ሀገራዊ ለውጡ ለተቋሙ "ዳግም ውልደት" ሆኖለታል።
የለውጡ ትሩፋቶች እንደ ዶ/ር ረሻድ ገለጻ፦
ተቋማዊ ሪፎርም፦ ተቋሙ ከነበረበት ውስብስብ ችግር ተላቆ አዲስ የስኬት ምዕራፍ ላይ መድረስ ችሏል።
የመንግስት ትኩረት፦
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሚመራው መንግሥት ለተቋሙ በሰጠው ልዩ ትኩረት ኮርፖሬሽኑ አገልግሎቱን እንዲያሳድግ አስችሎታል።
ቴክኖሎጂ መር መፍትሔዎች፦ በቀጣይ የመኖሪያ ቤት አቅርቦትን ለማሻሻል ዘመናዊና ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረጉ ስራዎች ላይ ትኩረት ተደርጓል።
⚽️ ጤናማና ምርታማ ሰራተኛ፦
የኢዮቤልዩ በዓሉ አካል የሆነው ስፖርታዊ ውድድርም ተጀምሯል። ይህ ውድድር በስምንት ቡድኖች መካከል የሚካሄድ ሲሆን፣ ዓላማውም የሰራተኛውን አንድነት በማጠናከር ለላቀ ውጤት ማዘጋጀት እንደሆነ ተገልጿል።
የኮርፖሬሽኑ አዲስ ገጽታ፦
ባለፉት ጥቂት ዓመታት የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በአዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች እየገነባቸው ያሉ ዘመናዊ የመኖሪያ መንደሮች (Apartments) የተቋሙን አዲስ ቁመናና የሪፎርሙን ውጤት በተግባር እያሳዩ እንደሚገኙ የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ረሻድ ከማል አስታውቀዋል።
#federalhousingcorporation #fhc50 #housingethiopia #infrastructure #urbandevelopment #drreshadkemal #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
6 months ago
🏙️"ሩቅ መሄድ አያስፈልግም!ኢትዮጵያን ተመልከቱ'' የኬንያ ብሔራዊ ምክር ቤት አባል ጁኔት መሐመድ
#ethiopia | የጎረቤት ምስክርነት ሁልጊዜም ለየት ያለ ትርጉም አለው፤ በተለይ ደግሞ ነገሮችን በቅርበት ለሚከታተሉ የፖለቲካ ሰዎች። ሰሞኑን የኬንያው የፓርላማ አባል ጁኔት መሐመድ ስለ አዲስ አበባ የሰጡት አስተያየት የከተማዋን ፈጣን ለውጥና የአፍሪካውያንን አመለካከት በአዲስ መነጽር የሚያሳይ ሆኗል።
ጁኔት አዲስ አበባን "የአፍሪካዋ አዲሷ ዱባይ" ሲሉ ነው የጠሯት። ይህ ስያሜ ለከተማዋ ዝም ብሎ የተሰጠ የውበት ሙገሳ ብቻ ሳይሆን፣ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የተከናወኑ ግዙፍ ሥራዎች ውጤት መሆኑን አመልክተዋል።
🌟 ለውጡን ጎልተው እንዲታዩ ያደረጉ ቁልፍ ነጥቦች
የምክር ቤት አባሉ ለአድናቆታቸው እንደ ምክንያት የጠቀሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች፦
* ዘመናዊ መሠረተ ልማትና ውበት፦ በከተማዋ የተገነቡት አዳዲስ ፓርኮች፣ መንገዶችና ዘመናዊ ሕንፃዎች አዲስ አበባን ለነዋሪዎች ምቹ፣ ለጎብኚዎች ደግሞ ማራኪ መዳረሻ አድርገዋታል።
* የማይነጥፍ ሰላምና ደኅንነት፦ "ማንም ሰው በሌሊት ያለ ሥጋት መንቀሳቀስ የሚችልባት ከተማ" በማለት የገለጿት ሲሆን፣ ይህም ለከተማዋ የኢኮኖሚና የቱሪዝም ዕድገት ትልቅ መሠረት መሆኑን ጠቁመዋል።
* የአፍሪካ ኩራትና ተምሳሌትነት፦ ኢትዮጵያ በታሪኳ ቅኝ ያልተገዛች የነፃነት ተምሳሌት እንደመሆኗ፣ አሁን ደግሞ በኢኮኖሚና በከተማ ልማት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ትልቅ ትምህርት እየሰጠች መሆኑን ገልጸዋል።
🌍 "ሩቅ መሄድ አያስፈልግም!"
ጁኔት መሐመድ አንድ ትልቅ መልእክት አስተላልፈዋል፦ "ልምድ ለመቅሰም ወደ ሩቅ ሀገራት ከመመልከት ይልቅ፣ አጠገባችን ያለችውን ኢትዮጵያን ማየት ይበቃል!" ይህ አስተያየት ኢትዮጵያ በራሷ አቅም አህጉራዊ ተፅዕኖዋን እያሳደገች መሆኑንና አዲስ አበባም የንግድ፣ የቱሪዝም እና የሰላም ማዕከል እየሆነች መምጣቷን የሚያረጋግጥ ነው። በጥቁር ሕዝቦች ታሪክ የነፃነት አርማ የነበረችው ሀገር፣ ዛሬ በልማትም የኩራት ምንጭነቷን እያስመሰከረች ትገኛለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ebc #ethiopia #addisababa #africarising #urbandevelopment #newdubai #africanexcellence #junetmohamed #greencity
#ethiopia | የጎረቤት ምስክርነት ሁልጊዜም ለየት ያለ ትርጉም አለው፤ በተለይ ደግሞ ነገሮችን በቅርበት ለሚከታተሉ የፖለቲካ ሰዎች። ሰሞኑን የኬንያው የፓርላማ አባል ጁኔት መሐመድ ስለ አዲስ አበባ የሰጡት አስተያየት የከተማዋን ፈጣን ለውጥና የአፍሪካውያንን አመለካከት በአዲስ መነጽር የሚያሳይ ሆኗል።
ጁኔት አዲስ አበባን "የአፍሪካዋ አዲሷ ዱባይ" ሲሉ ነው የጠሯት። ይህ ስያሜ ለከተማዋ ዝም ብሎ የተሰጠ የውበት ሙገሳ ብቻ ሳይሆን፣ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የተከናወኑ ግዙፍ ሥራዎች ውጤት መሆኑን አመልክተዋል።
🌟 ለውጡን ጎልተው እንዲታዩ ያደረጉ ቁልፍ ነጥቦች
የምክር ቤት አባሉ ለአድናቆታቸው እንደ ምክንያት የጠቀሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች፦
* ዘመናዊ መሠረተ ልማትና ውበት፦ በከተማዋ የተገነቡት አዳዲስ ፓርኮች፣ መንገዶችና ዘመናዊ ሕንፃዎች አዲስ አበባን ለነዋሪዎች ምቹ፣ ለጎብኚዎች ደግሞ ማራኪ መዳረሻ አድርገዋታል።
* የማይነጥፍ ሰላምና ደኅንነት፦ "ማንም ሰው በሌሊት ያለ ሥጋት መንቀሳቀስ የሚችልባት ከተማ" በማለት የገለጿት ሲሆን፣ ይህም ለከተማዋ የኢኮኖሚና የቱሪዝም ዕድገት ትልቅ መሠረት መሆኑን ጠቁመዋል።
* የአፍሪካ ኩራትና ተምሳሌትነት፦ ኢትዮጵያ በታሪኳ ቅኝ ያልተገዛች የነፃነት ተምሳሌት እንደመሆኗ፣ አሁን ደግሞ በኢኮኖሚና በከተማ ልማት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ትልቅ ትምህርት እየሰጠች መሆኑን ገልጸዋል።
🌍 "ሩቅ መሄድ አያስፈልግም!"
ጁኔት መሐመድ አንድ ትልቅ መልእክት አስተላልፈዋል፦ "ልምድ ለመቅሰም ወደ ሩቅ ሀገራት ከመመልከት ይልቅ፣ አጠገባችን ያለችውን ኢትዮጵያን ማየት ይበቃል!" ይህ አስተያየት ኢትዮጵያ በራሷ አቅም አህጉራዊ ተፅዕኖዋን እያሳደገች መሆኑንና አዲስ አበባም የንግድ፣ የቱሪዝም እና የሰላም ማዕከል እየሆነች መምጣቷን የሚያረጋግጥ ነው። በጥቁር ሕዝቦች ታሪክ የነፃነት አርማ የነበረችው ሀገር፣ ዛሬ በልማትም የኩራት ምንጭነቷን እያስመሰከረች ትገኛለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ebc #ethiopia #addisababa #africarising #urbandevelopment #newdubai #africanexcellence #junetmohamed #greencity
Comments