10 hours ago
ኢትዮጵያ ለዓለም ያስተማረችው አዲስ ታሪክ
****************
ትላንት በመላው ኢትዮጵያ በተካሄደው ታሪካዊ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ በ12 ሰዓታት ውስጥ ለመትከል ካቀደችው 800 ሚሊዮን ችግኝ 805 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል አዲስ የዓለም አቀፍ ሥነ ምህዳር ጥበቃ ታሪክ አስመዝግባለች።
ከማለዳው ጀምሮ በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ የመትከያ ስፍራዎች ወጣቶች፣ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አባላት እና ታዋቂ ግለሰቦች በተገኙበት የተካሄደው ይህ ታላቅ ሕዝባዊ ንቅናቄ ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ተፈጥሮአዊ ህልውና እና ለቀጣዩ ትውልድ አረንጓዴ ምድር ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጡበት ሆኗል።
ኢትዮጵያ ካቀደችው በላይ 805 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ባስመዘገበችው በዚህ ታላቅ ስኬት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጠንካራ መልእክቶችን አስተላልፋለች።
የአየር ንብረት መዛባትን ለመከላከል የሚደረገው ጥረት በመግለጫዎች እና በኮንፈረንሶች ብቻ ሳይሆን በተግባር መሬት ላይ በሚወርዱ ግዙፍ ሕዝባዊ ሥራዎች መመራት እንዳለበት በተግባር የተደገፈ መሪነቷን አሳይታለች።
በሌላ በኩል ሀገራችን የራሷን የደን ሽፋን ከማሳደግ እና የደረቁ የውኃ አካላትን ከመመለስ ባለፈ ለጎረቤት ሀገራት ችግኞችን በማካፈል በቀጣናው አረንጓዴ ኢኮኖሚን ለመገንባት የምታደርገውን ጥረት አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጣለች።
ኢትዮጵያ በራሷ አቅም እና በሕዝቧ ንቅናቄ ትልቅ ሀገራዊ ሀላፊነቷን መወጣቷን በመግለጽ የበለፀጉ ሀገራት እና የዓለም አቀፍ አካባቢ ጥበቃ ተቋማት ለአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የገቡትን የፋይናንስ እና የቴክኖሎጂ ድጋፍ ቃል በተግባር እንዲወጡ በድፍረት እንድትሞግት ትልቅ የዲፕሎማሲ ሞራል እና አቅም ፈጥሮላታል።
ይህ ታሪካዊ ስኬት ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተጣለባትን እምነት የሚያጸና ሲሆን፣ ሀገራችን በታላላቅ የዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤዎች ላይ በዘርፉ ያላትን የላቀ የሞራል ልዕልና እና ተደማጭነት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዳግም ያስመሰከረ ነው።
የተመዘገበው 805 ሚሊዮን ችግኝ ተከላ ስኬት የዛሬን የተፈጥሮ ቁስል እያከመ፣ የነገዋን ኢትዮጵያ እና የዓለምን ሥነ ምህዳር ለመጠበቅ በተግባር የተጻፈ ታሪካዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ምዕራፍ ነው።
በሃና ምንዳሁን
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #greenlegacy #planthope #climateresilience #ethiopiarising
****************
ትላንት በመላው ኢትዮጵያ በተካሄደው ታሪካዊ የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ በ12 ሰዓታት ውስጥ ለመትከል ካቀደችው 800 ሚሊዮን ችግኝ 805 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል አዲስ የዓለም አቀፍ ሥነ ምህዳር ጥበቃ ታሪክ አስመዝግባለች።
ከማለዳው ጀምሮ በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ የመትከያ ስፍራዎች ወጣቶች፣ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አባላት እና ታዋቂ ግለሰቦች በተገኙበት የተካሄደው ይህ ታላቅ ሕዝባዊ ንቅናቄ ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ተፈጥሮአዊ ህልውና እና ለቀጣዩ ትውልድ አረንጓዴ ምድር ያላቸውን ቁርጠኝነት በተግባር ያረጋገጡበት ሆኗል።
ኢትዮጵያ ካቀደችው በላይ 805 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ባስመዘገበችው በዚህ ታላቅ ስኬት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጠንካራ መልእክቶችን አስተላልፋለች።
የአየር ንብረት መዛባትን ለመከላከል የሚደረገው ጥረት በመግለጫዎች እና በኮንፈረንሶች ብቻ ሳይሆን በተግባር መሬት ላይ በሚወርዱ ግዙፍ ሕዝባዊ ሥራዎች መመራት እንዳለበት በተግባር የተደገፈ መሪነቷን አሳይታለች።
በሌላ በኩል ሀገራችን የራሷን የደን ሽፋን ከማሳደግ እና የደረቁ የውኃ አካላትን ከመመለስ ባለፈ ለጎረቤት ሀገራት ችግኞችን በማካፈል በቀጣናው አረንጓዴ ኢኮኖሚን ለመገንባት የምታደርገውን ጥረት አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጣለች።
ኢትዮጵያ በራሷ አቅም እና በሕዝቧ ንቅናቄ ትልቅ ሀገራዊ ሀላፊነቷን መወጣቷን በመግለጽ የበለፀጉ ሀገራት እና የዓለም አቀፍ አካባቢ ጥበቃ ተቋማት ለአየር ንብረት ለውጥ መከላከል የገቡትን የፋይናንስ እና የቴክኖሎጂ ድጋፍ ቃል በተግባር እንዲወጡ በድፍረት እንድትሞግት ትልቅ የዲፕሎማሲ ሞራል እና አቅም ፈጥሮላታል።
ይህ ታሪካዊ ስኬት ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተጣለባትን እምነት የሚያጸና ሲሆን፣ ሀገራችን በታላላቅ የዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጉባኤዎች ላይ በዘርፉ ያላትን የላቀ የሞራል ልዕልና እና ተደማጭነት ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዳግም ያስመሰከረ ነው።
የተመዘገበው 805 ሚሊዮን ችግኝ ተከላ ስኬት የዛሬን የተፈጥሮ ቁስል እያከመ፣ የነገዋን ኢትዮጵያ እና የዓለምን ሥነ ምህዳር ለመጠበቅ በተግባር የተጻፈ ታሪካዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ምዕራፍ ነው።
በሃና ምንዳሁን
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #greenlegacy #planthope #climateresilience #ethiopiarising
5 days ago
የኢትዮጵያ የክተት ጥሪ!
*************
የዘመን ማህደርን ገልጠን ወደ ኋላ ስንመለከት፣ ልክ ከ130 ዓመታት በፊት በ1888 ዓ.ም የኢትዮጵያ ተራሮች በታላቅ የክተት አዋጅ እና በነጋሪት ድምጽ ተንቀጥቅጠው ነበር። ወራሪው የፋሺስት ጦር ሉዓላዊ ድንበራችንን ጥሶ ክብራችንን ሊገፍና ነፃነታችንን ሊቀማ በዘመተ ጊዜ፣ የወቅቱ ንጉሥ አፄ ምኒልክ ያንን ታሪካዊ የክተት ጥሪ አሰሙ።
"ጉልበት ያለህ በጉልበትህ፣ ጉልበት የሌለህ በጸሎትህ እርዳኝ፤ ሀገር የሚያጠፋ ጠላት መጥቷልና ተነስ! ይህን ሳታደርግ ቀርተህ ሀገርህ ስትደፈር ዝም ብትል ግን ማርያምን እጣላሃለሁ!" የሚለው የንጉሡ ጥሪ ኢትዮጵያን ከዳር እስከ ዳር አነቃነቃት።
ያኔ ጥሪው የኅልውና ነበር፤ ሀገር የማዳን፣ ድንበር የተጋፋውን የፋሽስት ወራሪ ኃይል በጀግንነት የመመከት ጥሪ ነበር። በዚህ ብሔራዊ ጥሪ የተንቀሳቀሰው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ እንደ ማዕበል ተምሞ በዓድዋ ተራሮች ላይ በደሙ የነፃነት ታሪክ ጻፈ። ኢትዮጵያም በልጆቿ አንድነት ዳነች።
ዛሬ ደግሞ ዘመን ተቀይሯል። የትናንቱ ጠላት በጀግኖች አባቶቻችን ተሸንፎ ታሪክ ሆኗል። ነገር ግን ዛሬም በድጋሚ ኢትዮጵያ እየተጣራች ነው።
የዛሬዋ ኢትዮጵያ ጥሪ ግን፣ እንደ ትናንቱ የጦርነት የጠላት ወረራ ክተት አይደለም። የዛሬው ጥሪ ምድሪቱን የማከም፣ እናት ሀገርን አረንጓዴ ካባ የማልበስ እና ልምላሜዋን የመመለስ የብልጽግና ጥሪ ነው። ይህ ጥሪ አባቶቻችን በደም እና በአጥንታቸው ያስከበሯትን ውድ ሀገር፣ እኛ በአረንጓዴ ዐሻራችን አድሰን፣ በላባችን አልብሰን ልዕልናዋን በተግባር የምናረጋግጥበት ታሪካዊ አዋጅ ነው።
ኢትዮጵያን በአረንጓዴ ዐሻራ ወደ ከፍታ ማማ የማሸጋገር እና የጀመረችውን የተስፋ ጉዞ የማስቀጠል ተከታታይ እና ያልተቋረጠ የክተት ጥሪ ነው።
እነሆ የዘንድሮው የኢትዮጵያ የክተት ጥሪ ደግሞ ታሪክን በአዲስ መልክ ሊያድስ፣ ተደጋጋሚ ድሎችን ሊያስመዘግብ እና የዓለምን ክብረ ወሰን በድጋሚ ሊሰብር ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም የጋራ ሀገራዊ ቀጠሮ ይዟል።
በዚህ ታሪካዊ ዕለት፣ አዲሱ የመደመር ትውልድ 800 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር ለመትከል ሀገራዊ የክተት አዋጅ ታውጆለታል።
ከማለዳው የንጋት ጮራ ጀምሮ ጀንበር እስክትጠልቅ ድረስ፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እጆች፣ የነገዋን ሀገር በምናብ እያዩ በአንድ ልብ ይሰባሰባሉ። በእነዚህ ጥቂት የብርሃን ሰዓታት ውስጥ 800 ሚሊዮን የተስፋ ዘሮችን በኢትዮጵያ ማህፀን ውስጥ ያኖራሉ።
ይህ የሐምሌ 27ቱ ክተት ከዛፍ ተከላ የዘለለ እጅግ ጥልቅ የሆነ ሀገራዊ ትርጉም አለው። ይህ ድንቅ የአንድ ጀንበር ተአምር፣ የተረሱና የተራቆቱ ተራሮቻችን ዳግም ህይወት የሚዘሩበት፣ የነገው ትውልድ ንጹህ አየር የሚተነፍስበት እና የኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ በጽኑ መሰረት ላይ የሚገነባበት ህያው ታሪክ ነው።
ትናንት አባቶቻችን በነጋሪት ድምጽ ጥሪዋን ሰምተው ሀገር እንዳዳኑ ሁሉ፣ ዛሬም እኛ ልጆቿ ይህንን የአረንጓዴ ዐሻራ ጥሪ ሰምተን በጋራ ስንሰለፍ ኢትዮጵያ በልጆቿ እጅ ትንቆጠቆጣለች፣ ውበቷ ይደምቃል፣ ሉዓላዊነቷም በምጣኔ ሀብት ይረጋገጣል።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ፍቅር ተጣርታለች፤ ምድሪቱን ለማልበስ፣ 800 ሚሊዮን ዐሻራዎችን በአንድ ቀን ለማሳረፍ፣ ክተት ለሐምሌ 27!
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #greenlegacy #800milliontrees #ethiopiarising #environmentalprotection #ebcdotstream
*************
የዘመን ማህደርን ገልጠን ወደ ኋላ ስንመለከት፣ ልክ ከ130 ዓመታት በፊት በ1888 ዓ.ም የኢትዮጵያ ተራሮች በታላቅ የክተት አዋጅ እና በነጋሪት ድምጽ ተንቀጥቅጠው ነበር። ወራሪው የፋሺስት ጦር ሉዓላዊ ድንበራችንን ጥሶ ክብራችንን ሊገፍና ነፃነታችንን ሊቀማ በዘመተ ጊዜ፣ የወቅቱ ንጉሥ አፄ ምኒልክ ያንን ታሪካዊ የክተት ጥሪ አሰሙ።
"ጉልበት ያለህ በጉልበትህ፣ ጉልበት የሌለህ በጸሎትህ እርዳኝ፤ ሀገር የሚያጠፋ ጠላት መጥቷልና ተነስ! ይህን ሳታደርግ ቀርተህ ሀገርህ ስትደፈር ዝም ብትል ግን ማርያምን እጣላሃለሁ!" የሚለው የንጉሡ ጥሪ ኢትዮጵያን ከዳር እስከ ዳር አነቃነቃት።
ያኔ ጥሪው የኅልውና ነበር፤ ሀገር የማዳን፣ ድንበር የተጋፋውን የፋሽስት ወራሪ ኃይል በጀግንነት የመመከት ጥሪ ነበር። በዚህ ብሔራዊ ጥሪ የተንቀሳቀሰው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ እንደ ማዕበል ተምሞ በዓድዋ ተራሮች ላይ በደሙ የነፃነት ታሪክ ጻፈ። ኢትዮጵያም በልጆቿ አንድነት ዳነች።
ዛሬ ደግሞ ዘመን ተቀይሯል። የትናንቱ ጠላት በጀግኖች አባቶቻችን ተሸንፎ ታሪክ ሆኗል። ነገር ግን ዛሬም በድጋሚ ኢትዮጵያ እየተጣራች ነው።
የዛሬዋ ኢትዮጵያ ጥሪ ግን፣ እንደ ትናንቱ የጦርነት የጠላት ወረራ ክተት አይደለም። የዛሬው ጥሪ ምድሪቱን የማከም፣ እናት ሀገርን አረንጓዴ ካባ የማልበስ እና ልምላሜዋን የመመለስ የብልጽግና ጥሪ ነው። ይህ ጥሪ አባቶቻችን በደም እና በአጥንታቸው ያስከበሯትን ውድ ሀገር፣ እኛ በአረንጓዴ ዐሻራችን አድሰን፣ በላባችን አልብሰን ልዕልናዋን በተግባር የምናረጋግጥበት ታሪካዊ አዋጅ ነው።
ኢትዮጵያን በአረንጓዴ ዐሻራ ወደ ከፍታ ማማ የማሸጋገር እና የጀመረችውን የተስፋ ጉዞ የማስቀጠል ተከታታይ እና ያልተቋረጠ የክተት ጥሪ ነው።
እነሆ የዘንድሮው የኢትዮጵያ የክተት ጥሪ ደግሞ ታሪክን በአዲስ መልክ ሊያድስ፣ ተደጋጋሚ ድሎችን ሊያስመዘግብ እና የዓለምን ክብረ ወሰን በድጋሚ ሊሰብር ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም የጋራ ሀገራዊ ቀጠሮ ይዟል።
በዚህ ታሪካዊ ዕለት፣ አዲሱ የመደመር ትውልድ 800 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር ለመትከል ሀገራዊ የክተት አዋጅ ታውጆለታል።
ከማለዳው የንጋት ጮራ ጀምሮ ጀንበር እስክትጠልቅ ድረስ፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እጆች፣ የነገዋን ሀገር በምናብ እያዩ በአንድ ልብ ይሰባሰባሉ። በእነዚህ ጥቂት የብርሃን ሰዓታት ውስጥ 800 ሚሊዮን የተስፋ ዘሮችን በኢትዮጵያ ማህፀን ውስጥ ያኖራሉ።
ይህ የሐምሌ 27ቱ ክተት ከዛፍ ተከላ የዘለለ እጅግ ጥልቅ የሆነ ሀገራዊ ትርጉም አለው። ይህ ድንቅ የአንድ ጀንበር ተአምር፣ የተረሱና የተራቆቱ ተራሮቻችን ዳግም ህይወት የሚዘሩበት፣ የነገው ትውልድ ንጹህ አየር የሚተነፍስበት እና የኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ በጽኑ መሰረት ላይ የሚገነባበት ህያው ታሪክ ነው።
ትናንት አባቶቻችን በነጋሪት ድምጽ ጥሪዋን ሰምተው ሀገር እንዳዳኑ ሁሉ፣ ዛሬም እኛ ልጆቿ ይህንን የአረንጓዴ ዐሻራ ጥሪ ሰምተን በጋራ ስንሰለፍ ኢትዮጵያ በልጆቿ እጅ ትንቆጠቆጣለች፣ ውበቷ ይደምቃል፣ ሉዓላዊነቷም በምጣኔ ሀብት ይረጋገጣል።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ፍቅር ተጣርታለች፤ ምድሪቱን ለማልበስ፣ 800 ሚሊዮን ዐሻራዎችን በአንድ ቀን ለማሳረፍ፣ ክተት ለሐምሌ 27!
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #greenlegacy #800milliontrees #ethiopiarising #environmentalprotection #ebcdotstream
5 days ago
የኢትዮጵያ ክተት ጥሪ ለአረንጓዴ ዐሻራ!
*************
የዘመን ማህደርን ገልጠን ወደ ኋላ ስንመለከት፣ ልክ ከ130 ዓመታት በፊት በ1888 ዓ.ም የኢትዮጵያ ተራሮች በታላቅ የክተት አዋጅ እና በነጋሪት ድምጽ ተንቀጥቅጠው ነበር። ወራሪው የፋሺስት ጦር ሉዓላዊ ድንበራችንን ጥሶ ክብራችንን ሊገፍና ነፃነታችንን ሊቀማ በዘመተ ጊዜ፣ የወቅቱ ንጉሥ አፄ ምኒልክ ያንን ታሪካዊ የክተት ጥሪ አሰሙ።
"ጉልበት ያለህ በጉልበትህ፣ ጉልበት የሌለህ በጸሎትህ እርዳኝ፤ ሀገር የሚያጠፋ ጠላት መጥቷልና ተነስ! ይህን ሳታደርግ ቀርተህ ሀገርህ ስትደፈር ዝም ብትል ግን ማርያምን እጣላሃለሁ!" የሚለው የንጉሡ ጥሪ ኢትዮጵያን ከዳር እስከ ዳር አነቃነቃት።
ያኔ ጥሪው የኅልውና ነበር፤ ሀገር የማዳን፣ ድንበር የተጋፋውን የፋሽስት ወራሪ ኃይል በጀግንነት የመመከት ጥሪ ነበር። በዚህ ብሔራዊ ጥሪ የተንቀሳቀሰው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ እንደ ማዕበል ተምሞ በዓድዋ ተራሮች ላይ በደሙ የነፃነት ታሪክ ጻፈ። ኢትዮጵያም በልጆቿ አንድነት ዳነች።
ዛሬ ደግሞ ዘመን ተቀይሯል። የትናንቱ ጠላት በጀግኖች አባቶቻችን ተሸንፎ ታሪክ ሆኗል። ነገር ግን ዛሬም በድጋሚ ኢትዮጵያ እየተጣራች ነው።
የዛሬዋ ኢትዮጵያ ጥሪ ግን፣ እንደ ትናንቱ የጦርነት የጠላት ወረራ ክተት አይደለም። የዛሬው ጥሪ ምድሪቱን የማከም፣ እናት ሀገርን አረንጓዴ ካባ የማልበስ እና ልምላሜዋን የመመለስ የብልጽግና ጥሪ ነው። ይህ ጥሪ አባቶቻችን በደም እና በአጥንታቸው ያስከበሯትን ውድ ሀገር፣ እኛ በአረንጓዴ ዐሻራችን አድሰን፣ በላባችን አልብሰን ልዕልናዋን በተግባር የምናረጋግጥበት ታሪካዊ አዋጅ ነው።
ኢትዮጵያን በአረንጓዴ ዐሻራ ወደ ከፍታ ማማ የማሸጋገር እና የጀመረችውን የተስፋ ጉዞ የማስቀጠል ተከታታይ እና ያልተቋረጠ የክተት ጥሪ ነው።
እነሆ የዘንድሮው የኢትዮጵያ የክተት ጥሪ ደግሞ ታሪክን በአዲስ መልክ ሊያድስ፣ ተደጋጋሚ ድሎችን ሊያስመዘግብ እና የዓለምን ክብረ ወሰን በድጋሚ ሊሰብር ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም የጋራ ሀገራዊ ቀጠሮ ይዟል።
በዚህ ታሪካዊ ዕለት፣ አዲሱ የመደመር ትውልድ 800 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር ለመትከል ሀገራዊ የክተት አዋጅ ታውጆለታል።
ከማለዳው የንጋት ጮራ ጀምሮ ጀንበር እስክትጠልቅ ድረስ፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እጆች፣ የነገዋን ሀገር በምናብ እያዩ በአንድ ልብ ይሰባሰባሉ። በእነዚህ ጥቂት የብርሃን ሰዓታት ውስጥ 800 ሚሊዮን የተስፋ ዘሮችን በኢትዮጵያ ማህፀን ውስጥ ያኖራሉ።
ይህ የሐምሌ 27ቱ ክተት ከዛፍ ተከላ የዘለለ እጅግ ጥልቅ የሆነ ሀገራዊ ትርጉም አለው። ይህ ድንቅ የአንድ ጀንበር ተአምር፣ የተረሱና የተራቆቱ ተራሮቻችን ዳግም ህይወት የሚዘሩበት፣ የነገው ትውልድ ንጹህ አየር የሚተነፍስበት እና የኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ በጽኑ መሰረት ላይ የሚገነባበት ህያው ታሪክ ነው።
ትናንት አባቶቻችን በነጋሪት ድምጽ ጥሪዋን ሰምተው ሀገር እንዳዳኑ ሁሉ፣ ዛሬም እኛ ልጆቿ ይህንን የአረንጓዴ ዐሻራ ጥሪ ሰምተን በጋራ ስንሰለፍ ኢትዮጵያ በልጆቿ እጅ ትንቆጠቆጣለች፣ ውበቷ ይደምቃል፣ ሉዓላዊነቷም በምጣኔ ሀብት ይረጋገጣል።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ፍቅር ተጣርታለች፤ ምድሪቱን ለማልበስ፣ 800 ሚሊዮን ዐሻራዎችን በአንድ ቀን ለማሳረፍ፣ ክተት ለሐምሌ 27!
#ethiopia #ebc #greenlegacy #800milliontrees #ethiopiarising #environmentalprotection #ebcdotstream
*************
የዘመን ማህደርን ገልጠን ወደ ኋላ ስንመለከት፣ ልክ ከ130 ዓመታት በፊት በ1888 ዓ.ም የኢትዮጵያ ተራሮች በታላቅ የክተት አዋጅ እና በነጋሪት ድምጽ ተንቀጥቅጠው ነበር። ወራሪው የፋሺስት ጦር ሉዓላዊ ድንበራችንን ጥሶ ክብራችንን ሊገፍና ነፃነታችንን ሊቀማ በዘመተ ጊዜ፣ የወቅቱ ንጉሥ አፄ ምኒልክ ያንን ታሪካዊ የክተት ጥሪ አሰሙ።
"ጉልበት ያለህ በጉልበትህ፣ ጉልበት የሌለህ በጸሎትህ እርዳኝ፤ ሀገር የሚያጠፋ ጠላት መጥቷልና ተነስ! ይህን ሳታደርግ ቀርተህ ሀገርህ ስትደፈር ዝም ብትል ግን ማርያምን እጣላሃለሁ!" የሚለው የንጉሡ ጥሪ ኢትዮጵያን ከዳር እስከ ዳር አነቃነቃት።
ያኔ ጥሪው የኅልውና ነበር፤ ሀገር የማዳን፣ ድንበር የተጋፋውን የፋሽስት ወራሪ ኃይል በጀግንነት የመመከት ጥሪ ነበር። በዚህ ብሔራዊ ጥሪ የተንቀሳቀሰው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ እንደ ማዕበል ተምሞ በዓድዋ ተራሮች ላይ በደሙ የነፃነት ታሪክ ጻፈ። ኢትዮጵያም በልጆቿ አንድነት ዳነች።
ዛሬ ደግሞ ዘመን ተቀይሯል። የትናንቱ ጠላት በጀግኖች አባቶቻችን ተሸንፎ ታሪክ ሆኗል። ነገር ግን ዛሬም በድጋሚ ኢትዮጵያ እየተጣራች ነው።
የዛሬዋ ኢትዮጵያ ጥሪ ግን፣ እንደ ትናንቱ የጦርነት የጠላት ወረራ ክተት አይደለም። የዛሬው ጥሪ ምድሪቱን የማከም፣ እናት ሀገርን አረንጓዴ ካባ የማልበስ እና ልምላሜዋን የመመለስ የብልጽግና ጥሪ ነው። ይህ ጥሪ አባቶቻችን በደም እና በአጥንታቸው ያስከበሯትን ውድ ሀገር፣ እኛ በአረንጓዴ ዐሻራችን አድሰን፣ በላባችን አልብሰን ልዕልናዋን በተግባር የምናረጋግጥበት ታሪካዊ አዋጅ ነው።
ኢትዮጵያን በአረንጓዴ ዐሻራ ወደ ከፍታ ማማ የማሸጋገር እና የጀመረችውን የተስፋ ጉዞ የማስቀጠል ተከታታይ እና ያልተቋረጠ የክተት ጥሪ ነው።
እነሆ የዘንድሮው የኢትዮጵያ የክተት ጥሪ ደግሞ ታሪክን በአዲስ መልክ ሊያድስ፣ ተደጋጋሚ ድሎችን ሊያስመዘግብ እና የዓለምን ክብረ ወሰን በድጋሚ ሊሰብር ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም የጋራ ሀገራዊ ቀጠሮ ይዟል።
በዚህ ታሪካዊ ዕለት፣ አዲሱ የመደመር ትውልድ 800 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር ለመትከል ሀገራዊ የክተት አዋጅ ታውጆለታል።
ከማለዳው የንጋት ጮራ ጀምሮ ጀንበር እስክትጠልቅ ድረስ፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እጆች፣ የነገዋን ሀገር በምናብ እያዩ በአንድ ልብ ይሰባሰባሉ። በእነዚህ ጥቂት የብርሃን ሰዓታት ውስጥ 800 ሚሊዮን የተስፋ ዘሮችን በኢትዮጵያ ማህፀን ውስጥ ያኖራሉ።
ይህ የሐምሌ 27ቱ ክተት ከዛፍ ተከላ የዘለለ እጅግ ጥልቅ የሆነ ሀገራዊ ትርጉም አለው። ይህ ድንቅ የአንድ ጀንበር ተአምር፣ የተረሱና የተራቆቱ ተራሮቻችን ዳግም ህይወት የሚዘሩበት፣ የነገው ትውልድ ንጹህ አየር የሚተነፍስበት እና የኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ በጽኑ መሰረት ላይ የሚገነባበት ህያው ታሪክ ነው።
ትናንት አባቶቻችን በነጋሪት ድምጽ ጥሪዋን ሰምተው ሀገር እንዳዳኑ ሁሉ፣ ዛሬም እኛ ልጆቿ ይህንን የአረንጓዴ ዐሻራ ጥሪ ሰምተን በጋራ ስንሰለፍ ኢትዮጵያ በልጆቿ እጅ ትንቆጠቆጣለች፣ ውበቷ ይደምቃል፣ ሉዓላዊነቷም በምጣኔ ሀብት ይረጋገጣል።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ፍቅር ተጣርታለች፤ ምድሪቱን ለማልበስ፣ 800 ሚሊዮን ዐሻራዎችን በአንድ ቀን ለማሳረፍ፣ ክተት ለሐምሌ 27!
#ethiopia #ebc #greenlegacy #800milliontrees #ethiopiarising #environmentalprotection #ebcdotstream
6 days ago
አረንጓዴ ዐሻራ፡ በኢትዮጵያውያን ዘንድ አዲስ የኅብረት እና የጋራ ዓላማ ባህልን የፈጠረ መርሐ-ግብር
**********************************
ኢትዮጵያ በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የጀመረችው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ዛሬ ላይ የኢትዮጵያን ገጽታ ከመስዋብ አልፎ የምግብ ዋስትና እና የዲፕሎማሲ አቅም የለወጠ ታላቅ ሀገራዊ እና አህጉራዊ ንቅናቄ ሆኖ ታይቷል።
ባለፉት ሰባት ዓመታት የተመዘገቡት ስኬቶች ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ላይ ያሳየችውን ተግባራዊ ምላሽ እና ያስመዘገበችውን ዘላቂ ፍሬ በጥልቀት የሚያስረዱ ናቸው።
ከሥነ ምህዳር እና ተፈጥሮ ጥበቃ አንጻር ባለፉት ሰባት ዓመታት ውስጥ ከ48 ቢሊዮኖች በላይ ችግኞችን በመትከል ምድርን ለማከም ተችሏል። ይህም የኢትዮጵያ የደን ሽፋን ከነበረበት ዝቅተኛ ደረጃ በማስወጣት በአጭር ጊዜ ውስጥ የደን ሽፋኗ እንዲያገግም አስችላል።
በየዓመቱ የሚካሄደው ይህ ዘመቻ የአፈር መሸርሸርን ከመቀነስ፣ የከርሰ ምድር ውኃን ከማጎልበት እና የተጎዱ የሥነ ምህዳር ክፍሎችን መልሶ ከመገንባት አንጻር እጅግ የጎላ ሚና ተጫውቷል።
ቀደም ሲል በድርቅ እና በአፈር መሸርሸር የተጠቁ አካባቢዎች ዛሬ ላይ አረንጓዴ ለብሰው በማገገም ይገኛሉ።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ከተራ የተፈጥሮ ጥበቃ ባለፈ ወደ ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ምንጭነት ተሸጋግሯል። በተለይም ባለፉት ዓመታት ትኩረት የተሰጣቸው የተቀናጁ የፍራፍሬ (አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ፣ ብርቱካን) እና የቡና ችግኞች ተከላ ዐበይት ውጤቶችን እያስገኙ ይገኛሉ።
ይህም ገቢያቸው አነስተኛ ለሆኑ አባወራዎች አዲስ የገቢ ምንጭ ከመፍጠሩም በላይ በሀገር ውስጥ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ለውጭ ገበያ የሚላኩ ምርቶችን በማሳደግ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ለማጠናከር ትልቅ መሠረት ጥሏል።
መርሐ-ግብሩ በመላው ኢትዮጵያውያን ዘንድ አዲስ የኅብረት እና የጋራ ዓላማ ባህልን ፈጥሯል።
እድሜ፣ ጾታ፣ የፖለቲካም ሆነ የሃይማኖት ልዩነት ሳይበግረው በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ ሚሊዮኖች ዜጎች በአንድ ጀምበር ወጥተው ችግኝ የመትከል ልምድን ማዳበራቸው ሀገራዊ አንድነትን እና የመረዳዳት መንፈስን አጠናክሮታል።
ይህም ኢትዮጵያውያን በትብብር ከተነሱ የማይሻገሩት ፈተና እንደሌለ በተግባር ያሳዩበት ታላቅ ማኅበራዊ ሀብት ሆኗል።
የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ የሀገር ወሰንን ተሻግሮ ለአጎራባች ሀገራት ችግኞችን በማካፈል የቀጣናዊ ትስስር እና የ አረንጓዴ ዲፕሎማሲ ማሳያ መሆን ችሏል።
የአየር ንብረት ለውጥን ለመመከት ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና የፖለቲካ መሪዎች በሚታገሉበት በዚህ ወቅት ኢትዮጵያ በተግባር ያሳየችው ይህ ንቅናቄ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ሙገሳ እና ዕውቅና እንድታገኝ አድርጓታል።
ባለፉት 7 ዓመታት የተካሄደው የአረንጓዴ ዐሻራ ጉዞ ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ፣ በምግብ እራስን መቻል፣ በሕዝባዊ አንድነት እና በዓለም አቀፍ ተፅዕኖ ፈጣሪነት ያስመዘገበችው ድል ነው።
ኢትዮጵያውያን ይህን የተተከለውን ተስፋ ጠብቀው በማሳደግ እና ወደ ተሻለ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም በመቀየር ለቀጣዩ ትውልድ አረንጓዴ፣ የተረጋጋች እና የበለፀገች ሀገርን ለማስረከብ ተሰናድተዋል።
በሃና ምንዳሁን
#ebc #ethiopia #ebcdotstream #greenlegacy #greenethiopia #climateaction #ethiopiarising
**********************************
ኢትዮጵያ በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የጀመረችው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ዛሬ ላይ የኢትዮጵያን ገጽታ ከመስዋብ አልፎ የምግብ ዋስትና እና የዲፕሎማሲ አቅም የለወጠ ታላቅ ሀገራዊ እና አህጉራዊ ንቅናቄ ሆኖ ታይቷል።
ባለፉት ሰባት ዓመታት የተመዘገቡት ስኬቶች ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ላይ ያሳየችውን ተግባራዊ ምላሽ እና ያስመዘገበችውን ዘላቂ ፍሬ በጥልቀት የሚያስረዱ ናቸው።
ከሥነ ምህዳር እና ተፈጥሮ ጥበቃ አንጻር ባለፉት ሰባት ዓመታት ውስጥ ከ48 ቢሊዮኖች በላይ ችግኞችን በመትከል ምድርን ለማከም ተችሏል። ይህም የኢትዮጵያ የደን ሽፋን ከነበረበት ዝቅተኛ ደረጃ በማስወጣት በአጭር ጊዜ ውስጥ የደን ሽፋኗ እንዲያገግም አስችላል።
በየዓመቱ የሚካሄደው ይህ ዘመቻ የአፈር መሸርሸርን ከመቀነስ፣ የከርሰ ምድር ውኃን ከማጎልበት እና የተጎዱ የሥነ ምህዳር ክፍሎችን መልሶ ከመገንባት አንጻር እጅግ የጎላ ሚና ተጫውቷል።
ቀደም ሲል በድርቅ እና በአፈር መሸርሸር የተጠቁ አካባቢዎች ዛሬ ላይ አረንጓዴ ለብሰው በማገገም ይገኛሉ።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ከተራ የተፈጥሮ ጥበቃ ባለፈ ወደ ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ምንጭነት ተሸጋግሯል። በተለይም ባለፉት ዓመታት ትኩረት የተሰጣቸው የተቀናጁ የፍራፍሬ (አቮካዶ፣ ማንጎ፣ ፓፓያ፣ ብርቱካን) እና የቡና ችግኞች ተከላ ዐበይት ውጤቶችን እያስገኙ ይገኛሉ።
ይህም ገቢያቸው አነስተኛ ለሆኑ አባወራዎች አዲስ የገቢ ምንጭ ከመፍጠሩም በላይ በሀገር ውስጥ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ለውጭ ገበያ የሚላኩ ምርቶችን በማሳደግ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን ለማጠናከር ትልቅ መሠረት ጥሏል።
መርሐ-ግብሩ በመላው ኢትዮጵያውያን ዘንድ አዲስ የኅብረት እና የጋራ ዓላማ ባህልን ፈጥሯል።
እድሜ፣ ጾታ፣ የፖለቲካም ሆነ የሃይማኖት ልዩነት ሳይበግረው በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ ሚሊዮኖች ዜጎች በአንድ ጀምበር ወጥተው ችግኝ የመትከል ልምድን ማዳበራቸው ሀገራዊ አንድነትን እና የመረዳዳት መንፈስን አጠናክሮታል።
ይህም ኢትዮጵያውያን በትብብር ከተነሱ የማይሻገሩት ፈተና እንደሌለ በተግባር ያሳዩበት ታላቅ ማኅበራዊ ሀብት ሆኗል።
የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ የሀገር ወሰንን ተሻግሮ ለአጎራባች ሀገራት ችግኞችን በማካፈል የቀጣናዊ ትስስር እና የ አረንጓዴ ዲፕሎማሲ ማሳያ መሆን ችሏል።
የአየር ንብረት ለውጥን ለመመከት ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና የፖለቲካ መሪዎች በሚታገሉበት በዚህ ወቅት ኢትዮጵያ በተግባር ያሳየችው ይህ ንቅናቄ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ሙገሳ እና ዕውቅና እንድታገኝ አድርጓታል።
ባለፉት 7 ዓመታት የተካሄደው የአረንጓዴ ዐሻራ ጉዞ ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ፣ በምግብ እራስን መቻል፣ በሕዝባዊ አንድነት እና በዓለም አቀፍ ተፅዕኖ ፈጣሪነት ያስመዘገበችው ድል ነው።
ኢትዮጵያውያን ይህን የተተከለውን ተስፋ ጠብቀው በማሳደግ እና ወደ ተሻለ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም በመቀየር ለቀጣዩ ትውልድ አረንጓዴ፣ የተረጋጋች እና የበለፀገች ሀገርን ለማስረከብ ተሰናድተዋል።
በሃና ምንዳሁን
#ebc #ethiopia #ebcdotstream #greenlegacy #greenethiopia #climateaction #ethiopiarising
Sponsored by
Surafel
8 days ago
በሐሳብ ልዕልና ሀገራዊ መግባባትን እንገነባለን
****************
በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ጉዞ ውስጥ ዘላቂ ሰላም የሚረጋገጠው እና ሀገራዊ መግባባት የሚፈጠረው በኃይል አማራጭ ሳይሆን በሥልጡን የሐሳብ ማዕድ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት እንደገለጹት፣ በአሁኑ ወቅት ሀገራችን በጽኑ የምትሻው እና የሚያስፈልጋት ጠብመንጃ ያነገቡ የጥፋት ኃይሎችን ሳይሆን፣ በሐሳብ ብስለት፣ በእውነት፣ በዕውቀት እና በጽናት ታጥቀው የተሰናዱ የሰላም ታጋዮችን ነው።
ስለሆነም ከዚሁ መሠረታዊ ሐሳብ በመነሣት የታሪክ አጋጣሚዎች እና የዓለማችን ተሞክሮዎች እንደሚያስረዱት በብረት ኃይል የሚመጣ ስኬት ጊዜያዊ እና ሀገርን ወደ ከፋ ውድመት የሚያስገባ እንጂ ዘላቂ መፍትሔ አይሆንም።
የጠብመንጃ መንገድ የጥላቻ እና የጥፋት አዙሪትን ከማንገሥ ባለፈ የማኅበረሰብ እሴቶችን የሚያፈርስ ሲሆን በሐሳብ ብስለት እና በዕውቀት የታጠቁ የሰላም ታጋዮች ግን የተለያዩ አመለካከቶችን አቃፊ በሆነ መንገድ በማስተናገድ የሕዝቦችን የጋራ የወደፊት ዕድል በጽኑ መሠረት ላይ ይገነባሉ።
በእውነት እና በዕውቀት ላይ የተመሠረተ ምክክር ለዘመናት የዘለቁ ሀገራዊ አለመግባባቶችን እና ስብራቶችን የመጠገን ከፍተኛ አቅም አለው።
እውነተኛ የሰላም ታጋይነት ሀገራዊ እውነታዎችን በግልጽነት ለመቀበል፣ ታሪካዊ ጠባሳዎችን በጥበብ ለማከም እና የልዩነቶችን ምንጭ በጥልቅ ዕውቀት መርምሮ ዘላቂ መፍትሔ ለማስቀመጥ ያስችላል።
ይህም ሀገራዊ ምክክሩ ከይስሙላ የፖለቲካ ድርድር አልፎ የሕዝቦችን እውነተኛ አንድነት የሚያመጣ የታሪክ ምዕራፍ እንዲሆን ያደርገዋል።
የውይይት እና የእርቅ መንገድ ከግጭት በተቃራኒ የረጅም ጊዜ ትዕግሥትን፣ የሐሳብ ልዕልናን እና የመደማመጥ ባህልን ይጠይቃል።
በመሆኑም የማኅበረሰብ መሪዎች፣ ምሁራን፣ ወጣቶች እና መላው ሕዝብ በጠብመንጃ ቦታ የሐሳብ የበላይነት እንዲነግሥ በማድረግ ረገድ ታሪካዊ ኃላፊነታቸውን መወጣት ይጠበቅባቸዋል።
አሁን እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሐሳብ ብስለት እና በዕውቀት የተዘጋጁ የሰላም ታጋዮች ሀገራቸውን የሚታደጉበት ታላቅ መድረክ ነው።
በሃና ምንዳሁን
#ebc #ethiopia #nationaldialogue #peace #reason #ethiopiarising
****************
በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ጉዞ ውስጥ ዘላቂ ሰላም የሚረጋገጠው እና ሀገራዊ መግባባት የሚፈጠረው በኃይል አማራጭ ሳይሆን በሥልጡን የሐሳብ ማዕድ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ወቅት እንደገለጹት፣ በአሁኑ ወቅት ሀገራችን በጽኑ የምትሻው እና የሚያስፈልጋት ጠብመንጃ ያነገቡ የጥፋት ኃይሎችን ሳይሆን፣ በሐሳብ ብስለት፣ በእውነት፣ በዕውቀት እና በጽናት ታጥቀው የተሰናዱ የሰላም ታጋዮችን ነው።
ስለሆነም ከዚሁ መሠረታዊ ሐሳብ በመነሣት የታሪክ አጋጣሚዎች እና የዓለማችን ተሞክሮዎች እንደሚያስረዱት በብረት ኃይል የሚመጣ ስኬት ጊዜያዊ እና ሀገርን ወደ ከፋ ውድመት የሚያስገባ እንጂ ዘላቂ መፍትሔ አይሆንም።
የጠብመንጃ መንገድ የጥላቻ እና የጥፋት አዙሪትን ከማንገሥ ባለፈ የማኅበረሰብ እሴቶችን የሚያፈርስ ሲሆን በሐሳብ ብስለት እና በዕውቀት የታጠቁ የሰላም ታጋዮች ግን የተለያዩ አመለካከቶችን አቃፊ በሆነ መንገድ በማስተናገድ የሕዝቦችን የጋራ የወደፊት ዕድል በጽኑ መሠረት ላይ ይገነባሉ።
በእውነት እና በዕውቀት ላይ የተመሠረተ ምክክር ለዘመናት የዘለቁ ሀገራዊ አለመግባባቶችን እና ስብራቶችን የመጠገን ከፍተኛ አቅም አለው።
እውነተኛ የሰላም ታጋይነት ሀገራዊ እውነታዎችን በግልጽነት ለመቀበል፣ ታሪካዊ ጠባሳዎችን በጥበብ ለማከም እና የልዩነቶችን ምንጭ በጥልቅ ዕውቀት መርምሮ ዘላቂ መፍትሔ ለማስቀመጥ ያስችላል።
ይህም ሀገራዊ ምክክሩ ከይስሙላ የፖለቲካ ድርድር አልፎ የሕዝቦችን እውነተኛ አንድነት የሚያመጣ የታሪክ ምዕራፍ እንዲሆን ያደርገዋል።
የውይይት እና የእርቅ መንገድ ከግጭት በተቃራኒ የረጅም ጊዜ ትዕግሥትን፣ የሐሳብ ልዕልናን እና የመደማመጥ ባህልን ይጠይቃል።
በመሆኑም የማኅበረሰብ መሪዎች፣ ምሁራን፣ ወጣቶች እና መላው ሕዝብ በጠብመንጃ ቦታ የሐሳብ የበላይነት እንዲነግሥ በማድረግ ረገድ ታሪካዊ ኃላፊነታቸውን መወጣት ይጠበቅባቸዋል።
አሁን እየተካሄደ ያለው ሀገራዊ ምክክር በሐሳብ ብስለት እና በዕውቀት የተዘጋጁ የሰላም ታጋዮች ሀገራቸውን የሚታደጉበት ታላቅ መድረክ ነው።
በሃና ምንዳሁን
#ebc #ethiopia #nationaldialogue #peace #reason #ethiopiarising
12 days ago
ከፖለቲካ መረጋጋት ወደ ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚያሸጋግረው አዲስ ተስፋ
**********************
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ስኬት ከሀገራዊ የፖለቲካ መረጋጋት ባሻገር ለሀገራችን ሁለንተናዊ ብልፅግና ጠንካራ መሰረት የሚጥል ወሳኝ ምሶሶ ነው።
ዘላቂ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ዕድገት ሊመጣ የሚችለው አስተማማኝ ሰላም እና የተረጋጋ የፖለቲካ ምህዳር ሲኖር ብቻ እንደመሆኑ መጠን፣ ይህ ሀገራዊ የምክክር መድረክ ለኢኮኖሚው መነቃቃት ዋና ቁልፍ ሆኖ ያገለግላል።
በተለይም ረጅም ጊዜ የዘለቁ ግጭቶች እና የትርክት ልዩነቶች በሀገራዊ ምክክሩ አማካኝነት በሰላማዊ መንገድ እልባት ሲያገኙ ትልቅ ሀገራዊ ፋይዳ ይኖረዋል። አጨቃጫቂ ጉዳዮች የጋራ መፍትሔ አግኝተው እንደ ማኅበረሰብ መተማመን እና መረጋጋት ይሰፍናል።
በዚህም ሀገራችን ለግጭት እና ለፀጥታ ማስከበር የምታወጣውን ከፍተኛ የሰው እና የገንዘብ ሀብት ወደ አገልግሎት መስጫ ተቋማት፣ መሠረተ-ልማት ግንባታ፣ እንዲሁም ወደ ትምህርት እና ጤና ዘርፍ እንድታዞር ያስችላታል።
ይህ ሰላማዊ ከባቢ ደግሞ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ኢንቨስትመንትን በከፍተኛ ሁኔታ በመሳብ ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድልን ይፈጥራል፤ ሀገራዊ ምርታማነትንም ያሳድጋል።
በአሁኑ ወቅት የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን መሪነት እየተደረገ ያለው የምክክር ጉባኤ ይህንን ራዕይ ዕውን ለማድረግ የተጀመሩ ተስፋ ሰጪ እርምጃዎች ናቸው።
በምክክሩ ወቅት የሚነሱ የኢኮኖሚ እና የማኅበራዊ ፍላጎቶች ታይተው የጋራ መግባባት ላይ ሲደረስ፣ ማኅበራዊ ፍትህ እና ፍትሐዊ የሀብት ክፍፍል እንዲሰፍን ያደርጋል።
ይህ ተግባር ድህነትን ከመቀነስ ባለፈ፣ ጠንካራ የማኅበረሰብ ትስስርን በማጎልበት እኩልነት የሰፈነበትን ማኅበራዊ ብልፅግና ዕውን ያደርጋል።
ከዚህም በተጨማሪ ሀገራዊ ምክክሩ ጠንካራ እና ገለልተኛ ተቋማትን ለመገንባት መንገድ በመክፈት ለመልካም አስተዳደር መስፈን ትልቅ አስተዋፅኦ አለው።
ግልፅነት፣ ተጠያቂነት እና የሕግ የበላይነት የሰፈነበት ሥርዓት ሲገነባ ሙስና እና የሀብት ብክነት ይቀንሳሉ።
በአጠቃላይ ሀገራዊ ምክክሩ ሰላምን፣ ማኅበራዊ ፍትህን እና ጠንካራ ተቋማዊ አሠራርን በማረጋገጥ፣ ኢትዮጵያን ወደ ተሟላ እና ዘላቂ ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚያሸጋግር ታሪካዊ ዕድል ነው።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #ebc #nationaldialogue #sustainablepeace #economicgrowth #ethiopiarising
**********************
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ስኬት ከሀገራዊ የፖለቲካ መረጋጋት ባሻገር ለሀገራችን ሁለንተናዊ ብልፅግና ጠንካራ መሰረት የሚጥል ወሳኝ ምሶሶ ነው።
ዘላቂ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ዕድገት ሊመጣ የሚችለው አስተማማኝ ሰላም እና የተረጋጋ የፖለቲካ ምህዳር ሲኖር ብቻ እንደመሆኑ መጠን፣ ይህ ሀገራዊ የምክክር መድረክ ለኢኮኖሚው መነቃቃት ዋና ቁልፍ ሆኖ ያገለግላል።
በተለይም ረጅም ጊዜ የዘለቁ ግጭቶች እና የትርክት ልዩነቶች በሀገራዊ ምክክሩ አማካኝነት በሰላማዊ መንገድ እልባት ሲያገኙ ትልቅ ሀገራዊ ፋይዳ ይኖረዋል። አጨቃጫቂ ጉዳዮች የጋራ መፍትሔ አግኝተው እንደ ማኅበረሰብ መተማመን እና መረጋጋት ይሰፍናል።
በዚህም ሀገራችን ለግጭት እና ለፀጥታ ማስከበር የምታወጣውን ከፍተኛ የሰው እና የገንዘብ ሀብት ወደ አገልግሎት መስጫ ተቋማት፣ መሠረተ-ልማት ግንባታ፣ እንዲሁም ወደ ትምህርት እና ጤና ዘርፍ እንድታዞር ያስችላታል።
ይህ ሰላማዊ ከባቢ ደግሞ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ኢንቨስትመንትን በከፍተኛ ሁኔታ በመሳብ ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድልን ይፈጥራል፤ ሀገራዊ ምርታማነትንም ያሳድጋል።
በአሁኑ ወቅት የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን መሪነት እየተደረገ ያለው የምክክር ጉባኤ ይህንን ራዕይ ዕውን ለማድረግ የተጀመሩ ተስፋ ሰጪ እርምጃዎች ናቸው።
በምክክሩ ወቅት የሚነሱ የኢኮኖሚ እና የማኅበራዊ ፍላጎቶች ታይተው የጋራ መግባባት ላይ ሲደረስ፣ ማኅበራዊ ፍትህ እና ፍትሐዊ የሀብት ክፍፍል እንዲሰፍን ያደርጋል።
ይህ ተግባር ድህነትን ከመቀነስ ባለፈ፣ ጠንካራ የማኅበረሰብ ትስስርን በማጎልበት እኩልነት የሰፈነበትን ማኅበራዊ ብልፅግና ዕውን ያደርጋል።
ከዚህም በተጨማሪ ሀገራዊ ምክክሩ ጠንካራ እና ገለልተኛ ተቋማትን ለመገንባት መንገድ በመክፈት ለመልካም አስተዳደር መስፈን ትልቅ አስተዋፅኦ አለው።
ግልፅነት፣ ተጠያቂነት እና የሕግ የበላይነት የሰፈነበት ሥርዓት ሲገነባ ሙስና እና የሀብት ብክነት ይቀንሳሉ።
በአጠቃላይ ሀገራዊ ምክክሩ ሰላምን፣ ማኅበራዊ ፍትህን እና ጠንካራ ተቋማዊ አሠራርን በማረጋገጥ፣ ኢትዮጵያን ወደ ተሟላ እና ዘላቂ ሁለንተናዊ ብልፅግና የሚያሸጋግር ታሪካዊ ዕድል ነው።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #ebc #nationaldialogue #sustainablepeace #economicgrowth #ethiopiarising
29 days ago
የ5ቱ ዓመታት ገፆች፤ ታሪክ ተሰርቷል!
***************
የዘመናት ታሪክ ገፆች ሲገለጡ የአንድ ሀገር ዕጣ ፈንታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከስር መሰረቱ ተነቅንቆ አዲስ መልክ የሚይዝበት አጋጣሚ እጅግ ጥቂት ነው።
ላለፉት አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ የተዘረጉትን የልማትና የለውጥ ገፆች ስናነብ፣ የተካሄደው ጉዞ "ለውጥ" ወይም "ሪፎርም" በሚሉ ቃላት ብቻ የሚገለፅ አይደለም።
ይልቁንም ከሪፎርም ባሻገር ወደ አብዮት የተጠጋ፣ የኢትዮጵያን አጠቃላይ ገፅታ የለወጠና ሥር ነቀል መዋቅራዊ ሽግግርን ያረጋገጠ ታላቅ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው።
በዓለም የኢኮኖሚ ታሪክ ውስጥ፣ ጥቂት ሀገራት ብቻ ናቸው በፈጣን ጊዜ ውስጥ አስደናቂ የሚባል የዕድገት ዝላይ (Leapfrogging) ማሳየት የቻሉት።
ቻይና በሰላሳ ዓመታት ያመጣችው መዋቅራዊ ለውጥ፣ ደቡብ ኮሪያ በጄኔራል ፓርክ ቹንግ ሂ ቆራጥ መሪነት የተጓዘችው የኢንዱስትሪ ሽግግር፣ እንዲሁም ታይዋን ያስመዘገበችው የቴክኖሎጂ ስኬት ሁሌም በምሳሌነት ይነሳሉ።
ነገር ግን፣ ኢትዮጵያ በአምስት ዓመታት ውስጥ ብቻ እያስመዘገበች ያለው የለውጥ ፍጥነትና ስፋት እጅግ አስደናቂ ሆኖ እናገኘዋለን። በጠንካራና ቁርጠኛ አመራር እየተመራች፣ ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ ወደ ታላቅነት የምታደርገው ሽግግር ከግምት በላይ የሆነ ጉዞ ነው።
ይህ ተአምራዊ የሚባል ዝላይ በገሃድ ከሚታይባቸው መስኮች አንዱ ግብርና ነው። ለዘመናት በልመናና በስንዴ ዕርዳታ ጥገኝነት ስትታወቅ የነበረችው ሀገር፣ በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ የምግብ ሉዓላዊነቷን አረጋግጣ ወደ ስንዴ ላኪነት መሸጋገሯ እውነተኛ የኢኮኖሚ "ሉዓላዊነት" ማረጋገጫ ነው።
በተጠናከረ የኩታገጠም እና የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት፣ የስንዴ ምርት በ2017 በጀት ዓመት 280 ሚሊዮን ኩንታል መድረሱ የዚህ ፈጣን ስኬት ማሳያ ነው። ኢኮኖሚው ከአንድ ወጥ ጥገኝነት ወጥቶ ወደ ብዝሃ-ዘርፍ ልማት በማደግ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገቡ በጥቂት ሀገራት ብቻ የሚሳካ ታላቅ ድል ነው።
የለውጡ ጅረት በግብርና ብቻ አልተገታም። በአረንጓዴ ኢኮኖሚው ዘርፍ፣ እስከ ኮፕ ጉባኤ ድረስ ከ65 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል በእስካሁኑ ጉዞ የሀገራችንን የደን ሽፋን ከ17 በመቶ ወደ 23.6 በመቶ ከፍ በማድረግ ኢትዮጵያ የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ መከላከያ ተምሳሌት ሆናለች።
በውሃና ኃይል (ኤነርጂ) ሽግግር፣ ታላቁን የሕዳሴ ግድብን ጨምሮ በርካታ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ የኃይል ማመንጨት አቅምን ወደ 9,554 ሜጋ ዋት አሳድጋለች።
በተለይም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን (EV) በመጠቀም የነዳጅ ጥገኝነትን መቀነስና የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ሌላው የዘርፉ ስኬት ነው።
በከተማ ልማት ዘርፍም የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች ከተሞቻችንን የውበት፣ የንፅህናና የሥልጣኔ ማዕከል አድርገዋቸዋል።
በኢንዱስትሪና በዲጂታል ዘርፍ፣ "ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄንና የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን በመተግበር፣ እንዲሁም ከ58 ሚሊዮን በላይ የቴሌብር ተጠቃሚዎችን በማፍራትና የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ቁጥር በማስፋፋት ዘመኑን የዋጀ የቴክኖሎጂ አብዮት ተካሂዷል።
በማዕድን ዘርፍ የተከናወኑት የሪፎርም ስራዎችም እንዲሁ እጅግ አስደናቂ ናቸው። የኮንትሮባንድ ንግድን በመግታትና የወርቅ ምርትን ከ3.3 ቶን ወደ 38.8 ቶን በማሳደግ፣ ዘርፉ የውጭ ምንዛሬ ግኝታችንን ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሯል።
የቱሪዝም ዘርፉም በተመሳሳይ በገበታ ለሀገርና በሌሎች የቱሪዝም መዳረሻዎች ልማት፣ የውጭ ቱሪስት ፍሰትን ወደ 1.3 ሚሊዮን በማድረስ ሀገራችንን ወደ ተፈጥሯዊ የቱሪዝም መዳረሻነት ቀይሯታል።
በዲፕሎማሲውና በፖለቲካው መስክም የተመዘገበው ስኬት የሚያስደምም ነው። ኢትዮጵያ የነበሩባትን ውስብስብ ጫናዎች በብልሃት ተቋቁማ፣ የውጭ ፖሊሲዋን ሚዛናዊ በማድረግ ወደ ብሪክስ (BRICS) አባልነት መቀላቀሏ ዓለም አቀፍ ተደማጭነቷን አረጋግጧል።
በድምሩ ሲታይ እነዚህ ሁሉ ስኬቶች በአንድ ላይ ሲገመገሙ ኢትዮጵያ በእርግጥም ተአምራዊ በሚባል የለውጥ ጎዳና ላይ ትገኛለች። ይህን ሁሉ ውስብስብ ሀገራዊ፣ ቀጠናዊና ዓለም አቀፍ ጫና ተቋቁሞ ማሳካት የቻለው "መፍጠር፣ መፍጠንና መዝለል" በሚል መርህ የተቃኘው የፖለቲካ ኢኮኖሚ ሥርዓትና ቆራጥ አመራር በመኖሩ ነው።
ይህ እንደ አዲስ የጀመረው የለውጥና የዝላይ ጉዞ በአጭር ጊዜ ከግብ ሲደርስ፣ ኢትዮጵያ በብልፅግና ማማ ላይ ደምቃ በመውጣት የአፍሪካዊ ተምሳሌትነትን አልፋ የዓለም የብልፅግና ተምሳሌት እንደምትሆን አያጠራጥርም።
የ5ቱ ዓመታት ገፆች፣ የዚህችን ታላቅ ሀገር አይበገሬነትና ትንሣኤ በደማቁ የፃፉ ህያው የድል ድርሳናት ናቸው!
በአዶኒያስ ወ/አረጋይ
#ethiopiarising #historyinthemakinget #foodsovereigntyet #greenlegacyethiopia #ethiopiainbrics
***************
የዘመናት ታሪክ ገፆች ሲገለጡ የአንድ ሀገር ዕጣ ፈንታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከስር መሰረቱ ተነቅንቆ አዲስ መልክ የሚይዝበት አጋጣሚ እጅግ ጥቂት ነው።
ላለፉት አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ የተዘረጉትን የልማትና የለውጥ ገፆች ስናነብ፣ የተካሄደው ጉዞ "ለውጥ" ወይም "ሪፎርም" በሚሉ ቃላት ብቻ የሚገለፅ አይደለም።
ይልቁንም ከሪፎርም ባሻገር ወደ አብዮት የተጠጋ፣ የኢትዮጵያን አጠቃላይ ገፅታ የለወጠና ሥር ነቀል መዋቅራዊ ሽግግርን ያረጋገጠ ታላቅ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው።
በዓለም የኢኮኖሚ ታሪክ ውስጥ፣ ጥቂት ሀገራት ብቻ ናቸው በፈጣን ጊዜ ውስጥ አስደናቂ የሚባል የዕድገት ዝላይ (Leapfrogging) ማሳየት የቻሉት።
ቻይና በሰላሳ ዓመታት ያመጣችው መዋቅራዊ ለውጥ፣ ደቡብ ኮሪያ በጄኔራል ፓርክ ቹንግ ሂ ቆራጥ መሪነት የተጓዘችው የኢንዱስትሪ ሽግግር፣ እንዲሁም ታይዋን ያስመዘገበችው የቴክኖሎጂ ስኬት ሁሌም በምሳሌነት ይነሳሉ።
ነገር ግን፣ ኢትዮጵያ በአምስት ዓመታት ውስጥ ብቻ እያስመዘገበች ያለው የለውጥ ፍጥነትና ስፋት እጅግ አስደናቂ ሆኖ እናገኘዋለን። በጠንካራና ቁርጠኛ አመራር እየተመራች፣ ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ ወደ ታላቅነት የምታደርገው ሽግግር ከግምት በላይ የሆነ ጉዞ ነው።
ይህ ተአምራዊ የሚባል ዝላይ በገሃድ ከሚታይባቸው መስኮች አንዱ ግብርና ነው። ለዘመናት በልመናና በስንዴ ዕርዳታ ጥገኝነት ስትታወቅ የነበረችው ሀገር፣ በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ የምግብ ሉዓላዊነቷን አረጋግጣ ወደ ስንዴ ላኪነት መሸጋገሯ እውነተኛ የኢኮኖሚ "ሉዓላዊነት" ማረጋገጫ ነው።
በተጠናከረ የኩታገጠም እና የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት፣ የስንዴ ምርት በ2017 በጀት ዓመት 280 ሚሊዮን ኩንታል መድረሱ የዚህ ፈጣን ስኬት ማሳያ ነው። ኢኮኖሚው ከአንድ ወጥ ጥገኝነት ወጥቶ ወደ ብዝሃ-ዘርፍ ልማት በማደግ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገቡ በጥቂት ሀገራት ብቻ የሚሳካ ታላቅ ድል ነው።
የለውጡ ጅረት በግብርና ብቻ አልተገታም። በአረንጓዴ ኢኮኖሚው ዘርፍ፣ እስከ ኮፕ ጉባኤ ድረስ ከ65 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል በእስካሁኑ ጉዞ የሀገራችንን የደን ሽፋን ከ17 በመቶ ወደ 23.6 በመቶ ከፍ በማድረግ ኢትዮጵያ የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ መከላከያ ተምሳሌት ሆናለች።
በውሃና ኃይል (ኤነርጂ) ሽግግር፣ ታላቁን የሕዳሴ ግድብን ጨምሮ በርካታ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ የኃይል ማመንጨት አቅምን ወደ 9,554 ሜጋ ዋት አሳድጋለች።
በተለይም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን (EV) በመጠቀም የነዳጅ ጥገኝነትን መቀነስና የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ሌላው የዘርፉ ስኬት ነው።
በከተማ ልማት ዘርፍም የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች ከተሞቻችንን የውበት፣ የንፅህናና የሥልጣኔ ማዕከል አድርገዋቸዋል።
በኢንዱስትሪና በዲጂታል ዘርፍ፣ "ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄንና የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን በመተግበር፣ እንዲሁም ከ58 ሚሊዮን በላይ የቴሌብር ተጠቃሚዎችን በማፍራትና የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ቁጥር በማስፋፋት ዘመኑን የዋጀ የቴክኖሎጂ አብዮት ተካሂዷል።
በማዕድን ዘርፍ የተከናወኑት የሪፎርም ስራዎችም እንዲሁ እጅግ አስደናቂ ናቸው። የኮንትሮባንድ ንግድን በመግታትና የወርቅ ምርትን ከ3.3 ቶን ወደ 38.8 ቶን በማሳደግ፣ ዘርፉ የውጭ ምንዛሬ ግኝታችንን ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሯል።
የቱሪዝም ዘርፉም በተመሳሳይ በገበታ ለሀገርና በሌሎች የቱሪዝም መዳረሻዎች ልማት፣ የውጭ ቱሪስት ፍሰትን ወደ 1.3 ሚሊዮን በማድረስ ሀገራችንን ወደ ተፈጥሯዊ የቱሪዝም መዳረሻነት ቀይሯታል።
በዲፕሎማሲውና በፖለቲካው መስክም የተመዘገበው ስኬት የሚያስደምም ነው። ኢትዮጵያ የነበሩባትን ውስብስብ ጫናዎች በብልሃት ተቋቁማ፣ የውጭ ፖሊሲዋን ሚዛናዊ በማድረግ ወደ ብሪክስ (BRICS) አባልነት መቀላቀሏ ዓለም አቀፍ ተደማጭነቷን አረጋግጧል።
በድምሩ ሲታይ እነዚህ ሁሉ ስኬቶች በአንድ ላይ ሲገመገሙ ኢትዮጵያ በእርግጥም ተአምራዊ በሚባል የለውጥ ጎዳና ላይ ትገኛለች። ይህን ሁሉ ውስብስብ ሀገራዊ፣ ቀጠናዊና ዓለም አቀፍ ጫና ተቋቁሞ ማሳካት የቻለው "መፍጠር፣ መፍጠንና መዝለል" በሚል መርህ የተቃኘው የፖለቲካ ኢኮኖሚ ሥርዓትና ቆራጥ አመራር በመኖሩ ነው።
ይህ እንደ አዲስ የጀመረው የለውጥና የዝላይ ጉዞ በአጭር ጊዜ ከግብ ሲደርስ፣ ኢትዮጵያ በብልፅግና ማማ ላይ ደምቃ በመውጣት የአፍሪካዊ ተምሳሌትነትን አልፋ የዓለም የብልፅግና ተምሳሌት እንደምትሆን አያጠራጥርም።
የ5ቱ ዓመታት ገፆች፣ የዚህችን ታላቅ ሀገር አይበገሬነትና ትንሣኤ በደማቁ የፃፉ ህያው የድል ድርሳናት ናቸው!
በአዶኒያስ ወ/አረጋይ
#ethiopiarising #historyinthemakinget #foodsovereigntyet #greenlegacyethiopia #ethiopiainbrics
1 month ago
የኢትዮጵያ ዳግም ማንሰራራት ምስጢር #ebcdotstream #ethiopianeconomy #megaprojectsethiopia #ethiopiarising
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
2 months ago
Safeguarding the dreams of 130 million people requires a modern, tech-driven defense. Ethiopia has built an unshakeable digital and military shield.
#nationalsecurity #digitalshield #ethiopiarising #hornofafrica
2 months ago
የአፍርሶ የመጀመር የታሪክ ስብራት እንዴት ተገረሰሰ? ጀምሮ መጨረስ አዲሱ የኢትዮጵያ መለያ
#medemer #policycontinuity #ethiopiarising #gerd #infrastructuredevelopment
Sponsored by
Surafel
2 months ago
የጀመረችውን የምትጨርስ ታላቅ ሀገር
***
ትናንት በጥርጣሬ 'ይቻላል ወይ?' ተብለው የተጠየቁ የትልልቅ ሕልሞቻችን፣ ዛሬ የኢትዮጵያን የጽናት ቁመት ለዓለም የሚመሰክሩ ግዙፍ ማማዎች ሆነው በግርማ ሞገስ ቆመዋል። ይህ እንዴት ተቻለ? መልሱን በተከታዩ ማስፈንጠሪያ ያገኙታል ➡️ https://youtu.be/Pmr7GFRFo...
#medemer #policycontinuity #ethiopiarising #gerd
3 months ago
ዓለም ሁሉ ሊያያት የሚጓጓላት ከተማ
#addisababatransformation #danielcarl #addisababacorridor #ethiopiarising #africancities #smartcitiesafrica
3 months ago
በጣና ዳርቻ ላይ የሚገነባው የቱሪዝም መዳረሻ
#bahirdar #tourismethiopia #midrocinvestmentgroup #laketana #newproject #ethiopiarising #ባሕርዳር #ኢትዮጵያ
9 months ago
Excited to share that the new Forbes Africa magazine is spotlighting Ethiopia’s dynamic growth across multiple sectors!
I had the privilege of contributing an interview focusing on Ethiopia’s tourism sector exploring our rich heritage, sustainable initiatives, and the unique experiences that make our country a must-visit destination.
It’s inspiring to see our story being shared on a continental platform like Forbes Africa!
Download the issue here 👇
https://cms.forbesafrica.c...
Discover how Ethiopia is positioning itself as a global tourism hub and learn more about the exciting developments in other sectors driving Africa’s growth!
#visitethiopia 🇪🇹 #landoforigins #forbesafrica #ethiopiarising #tourism #innovation #culturemeetsopportunity #proudlyethiopian
I had the privilege of contributing an interview focusing on Ethiopia’s tourism sector exploring our rich heritage, sustainable initiatives, and the unique experiences that make our country a must-visit destination.
It’s inspiring to see our story being shared on a continental platform like Forbes Africa!
Download the issue here 👇
https://cms.forbesafrica.c...
Discover how Ethiopia is positioning itself as a global tourism hub and learn more about the exciting developments in other sectors driving Africa’s growth!
#visitethiopia 🇪🇹 #landoforigins #forbesafrica #ethiopiarising #tourism #innovation #culturemeetsopportunity #proudlyethiopian
Sponsored by
Surafel
Comments