1 month ago
በጣና ዳርቻ ላይ የሚገነባው የቱሪዝም መዳረሻ
#bahirdar #tourismethiopia #midrocinvestmentgroup #laketana #newproject #ethiopiarising #ባሕርዳር #ኢትዮጵያ
1 month ago
የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት አካል የሆነው ግዙፉ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት በባህር ዳር ከተማ ተመረቀ
#ethiopia | በውቧ ባህር ዳር ከተማ በከፍተኛ ወጪ የተገነባው ግዙፉ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ዛሬ ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በታላቅ ስነ ስርዓት ተመርቋል።
በደቡባዊ የጣና ሀይቅ ዳርቻ ላይ ያረፈው ይህ ሪዞርት በጎርጎራ በኩል የተጀመረውን የቱሪዝም ልማት ብርሃን ወደ ሌላኛው የሀይቁ ዳርቻ ያሸጋገረ ግዙፍ ኢንቨስትመንት ነው።
ፕሮጀክቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በገበታ ለሀገር እቅድ አማካኝነት ሁለት የጣና ሀይቅ ዳርቻዎችን በቱሪዝም ለማስተሳሰር የነደፉትን ታላቅ ራዕይ ዳር ያደረሰ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የታሪካዊቷን የጎርጎራ ከተማ ገፅታ ከመቀየር ባለፈ በዐፄ ፋሲለደስ መናገሻ ጎንደር የሚገኙ የቤተ መንግስት ቅርሶችን በከፍተኛ ጥራት በማደስ ለዘላቂ ቱሪዝም ዝግጁ እንዲሆኑ አድርገዋል።
ከዚህም በተጨማሪ ለጎንደር ከተማ የመጠጥ ውሃ እና ለግብርና ልማት የሚውለው የመገጭ ግድብ ግንባታ ለውሃ ቱሪዝም አዲስ እድል ይዞ እየመጣ ይገኛል።
ይህንን መንግስታዊ ራዕይ በግል ኢንቨስትመንት በማገዝ የቤአኢካ እና የእህት ኩባንያዎቹ መስራች አቶ ካሳሁን ምስጋናው የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርትን በ 4.5 ቢሊዮን ብር ወጪ በሁለት አመት ከስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ገንብተው አጠናቀዋል።
ግለሰቡ በጎርጎራ ኢኮ ቱሪዝም ግንባታ እና በጎንደር ቅርሶች ጥገና ላይ የነበራቸውን ውጤታማ ተሳትፎ አሁን ደግሞ በቱሪዝም ኢንዱስትሪው ውስጥ በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ በኩል በስፋት ለመቀጠል ተዘጋጅተዋል።
አቶ ካሳሁን ለእነዚህ ስራዎች ስኬት የፌዴራል እና የክልል መንግስታት እንዲሁም የከተማ አስተዳደሮች ላደረጉላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ወደፊትም የፈለገ ግዮን እና የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርቶች በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ ስር በመሆን ልባችን ኢትዮጵያ ደረጃችን አለም አቀፍ በሚል መሪ ቃል ጥራት ያለው አገልግሎት ለጎብኚዎች እንደሚያቀርቡ ተገልጿል።
#bahirdar #tanalake #tourismethiopia #beaikainvestment #rodahospitality #development #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በውቧ ባህር ዳር ከተማ በከፍተኛ ወጪ የተገነባው ግዙፉ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ዛሬ ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በታላቅ ስነ ስርዓት ተመርቋል።
በደቡባዊ የጣና ሀይቅ ዳርቻ ላይ ያረፈው ይህ ሪዞርት በጎርጎራ በኩል የተጀመረውን የቱሪዝም ልማት ብርሃን ወደ ሌላኛው የሀይቁ ዳርቻ ያሸጋገረ ግዙፍ ኢንቨስትመንት ነው።
ፕሮጀክቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በገበታ ለሀገር እቅድ አማካኝነት ሁለት የጣና ሀይቅ ዳርቻዎችን በቱሪዝም ለማስተሳሰር የነደፉትን ታላቅ ራዕይ ዳር ያደረሰ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የታሪካዊቷን የጎርጎራ ከተማ ገፅታ ከመቀየር ባለፈ በዐፄ ፋሲለደስ መናገሻ ጎንደር የሚገኙ የቤተ መንግስት ቅርሶችን በከፍተኛ ጥራት በማደስ ለዘላቂ ቱሪዝም ዝግጁ እንዲሆኑ አድርገዋል።
ከዚህም በተጨማሪ ለጎንደር ከተማ የመጠጥ ውሃ እና ለግብርና ልማት የሚውለው የመገጭ ግድብ ግንባታ ለውሃ ቱሪዝም አዲስ እድል ይዞ እየመጣ ይገኛል።
ይህንን መንግስታዊ ራዕይ በግል ኢንቨስትመንት በማገዝ የቤአኢካ እና የእህት ኩባንያዎቹ መስራች አቶ ካሳሁን ምስጋናው የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርትን በ 4.5 ቢሊዮን ብር ወጪ በሁለት አመት ከስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ገንብተው አጠናቀዋል።
ግለሰቡ በጎርጎራ ኢኮ ቱሪዝም ግንባታ እና በጎንደር ቅርሶች ጥገና ላይ የነበራቸውን ውጤታማ ተሳትፎ አሁን ደግሞ በቱሪዝም ኢንዱስትሪው ውስጥ በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ በኩል በስፋት ለመቀጠል ተዘጋጅተዋል።
አቶ ካሳሁን ለእነዚህ ስራዎች ስኬት የፌዴራል እና የክልል መንግስታት እንዲሁም የከተማ አስተዳደሮች ላደረጉላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ወደፊትም የፈለገ ግዮን እና የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርቶች በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ ስር በመሆን ልባችን ኢትዮጵያ ደረጃችን አለም አቀፍ በሚል መሪ ቃል ጥራት ያለው አገልግሎት ለጎብኚዎች እንደሚያቀርቡ ተገልጿል።
#bahirdar #tanalake #tourismethiopia #beaikainvestment #rodahospitality #development #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 month ago
እንዲህ በትብብር ስንሠራ ወደ ብልጽግና የሚያሻግሩ ተግባራትን ማሳካት እንችላለን - ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ
******************
እንደ ፈለገ ጊዮን ኢኮ ሪዞርት ያሉ ግዙፍ የቱሪዝም ፕሮጀክቶች ለክልሉ ተጨማሪ ጸጋ ከመሆናቸውም በላይ የኢትዮጵያን የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ስለመሆናቸው የአማራ ክልል ርዕስ መስተዳድር አረጋ ከበደ ተናገሩ።
በባህር ዳር ከተማ የተገነባው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት በይፋ ተመርቋል።
ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፥ ሪዞርቱ ጥራት፣ ውበትና ምቾትን ከመላበሱ ባሻገር፣ ለታሪካዊው የጣና ሐይቅ ደህንነት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመገንባቱ ለሌሎች መሰል ፕሮጀክቶች እንደ አርአያ የሚጠቀስ መሆኑን አብራርተዋል።
ሪዞርቱ ከመንግሥትና ከግል ባለሀብቱ ጥንካሬ የተገኘ የጋራ ውጤት መሆኑን በመጥቀስ፣ "ሀሳብና ተግባር ሲገናኙ የማይታለፉ የሚመስሉ ፈታኝ ጊዜያትን በትብብር መሻገር እንደሚቻል የታየበት ነው ብለዋል።
ሪዞርቱ ለጎብኚዎች ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ከዘርፉ ማግኘት የሚገባንን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማግኘት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርም ገልጸዋል።
እንደ ርዕሰ መስተዳድሩ ገለጻ፥ የጣና ሐይቅ የኢትዮጵያ ጥንታዊ ሥልጣኔ መገለጫ እንደመሆኑ፣ አሁን ላይ ተግባራዊ እየሆነ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ፖሊሲ ደግሞ ዛሬን ከነገ በማገናኘት የቱሪዝም ሀብቶቻችንን ለትውልድ በሚተርፍ መልኩ ለማልማት ዕድል ፈጥሯል።
እንዲህ በትብብር ሲሥሠራ ወደ ብልጽግና የሚያሻግሩ ተግባራትን ማሳካት እንደሚቻል በመጠቆም፣ ዛሬም ሆነ ነገ ትብብራችንን በማጠናከር ለትውልድ የሚተርፍ አሻራ ማኖር ይገባል ብለዋል።
ከልማትና ከትብብር ውጪ ያለው አማራጭ የጥፋት መንገድ መሆኑን በማስገንዘብ፣ ሁሉም አካላት ለክልሉና ለሀገር ዕድገት በጋራ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል።
በአሸናፊ እንዳለ
#ethiopia #bahirdar #felegegion #resort #ebc
******************
እንደ ፈለገ ጊዮን ኢኮ ሪዞርት ያሉ ግዙፍ የቱሪዝም ፕሮጀክቶች ለክልሉ ተጨማሪ ጸጋ ከመሆናቸውም በላይ የኢትዮጵያን የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ስለመሆናቸው የአማራ ክልል ርዕስ መስተዳድር አረጋ ከበደ ተናገሩ።
በባህር ዳር ከተማ የተገነባው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት በይፋ ተመርቋል።
ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፥ ሪዞርቱ ጥራት፣ ውበትና ምቾትን ከመላበሱ ባሻገር፣ ለታሪካዊው የጣና ሐይቅ ደህንነት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመገንባቱ ለሌሎች መሰል ፕሮጀክቶች እንደ አርአያ የሚጠቀስ መሆኑን አብራርተዋል።
ሪዞርቱ ከመንግሥትና ከግል ባለሀብቱ ጥንካሬ የተገኘ የጋራ ውጤት መሆኑን በመጥቀስ፣ "ሀሳብና ተግባር ሲገናኙ የማይታለፉ የሚመስሉ ፈታኝ ጊዜያትን በትብብር መሻገር እንደሚቻል የታየበት ነው ብለዋል።
ሪዞርቱ ለጎብኚዎች ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ከዘርፉ ማግኘት የሚገባንን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማግኘት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርም ገልጸዋል።
እንደ ርዕሰ መስተዳድሩ ገለጻ፥ የጣና ሐይቅ የኢትዮጵያ ጥንታዊ ሥልጣኔ መገለጫ እንደመሆኑ፣ አሁን ላይ ተግባራዊ እየሆነ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ፖሊሲ ደግሞ ዛሬን ከነገ በማገናኘት የቱሪዝም ሀብቶቻችንን ለትውልድ በሚተርፍ መልኩ ለማልማት ዕድል ፈጥሯል።
እንዲህ በትብብር ሲሥሠራ ወደ ብልጽግና የሚያሻግሩ ተግባራትን ማሳካት እንደሚቻል በመጠቆም፣ ዛሬም ሆነ ነገ ትብብራችንን በማጠናከር ለትውልድ የሚተርፍ አሻራ ማኖር ይገባል ብለዋል።
ከልማትና ከትብብር ውጪ ያለው አማራጭ የጥፋት መንገድ መሆኑን በማስገንዘብ፣ ሁሉም አካላት ለክልሉና ለሀገር ዕድገት በጋራ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል።
በአሸናፊ እንዳለ
#ethiopia #bahirdar #felegegion #resort #ebc
2 months ago
ባሕር ዳር፦ ወጣት ብሩክ የሠራው አዲሱ መኪና
#የጥበበኛ እጆች ባለቤት የሆነውና በባሕር ዳር ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ በአውቶ ኤሌክትሪክ ዘርፍ የተመረቀው ወጣት ብሩክ ወንዲፍራው፣ የማይቻል የሚመስለውን በተግባር አሳይቷል።
ከዚህ ቀደም የተለያዩ የኢንዱስትሪ ማሽኖችን የሠራው ብሩክ፣ አሁን ደግሞ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ጥሬ ዕቃዎች የተሠራች ባለ አራት እግር መኪና ይፋ አድርጓል።
የተሽከርካሪዋ ልዩ መገለጫዎች
ሞተር
ባለ 300 ሲሲ (CC) ሞተር የተገጠመላት።
አቅም
በአንድ ጊዜ 4 ሰዎችን የመጫን አቅም ያላትና ከባጃጅ የተሻለ ፍጥነት የምትጓዝ።
ክብደት
ከ400 ኪሎ ግራም በላይ ክብደት አላት።
ወጪ
ለመሥራት ከ350 ሺህ ብር በላይ ወጪ ተደርጎባታል።
የብሩክ ትልቅ ራዕይ
የብሩክ ህልም መኪና ሠርቶ ማሳየት ብቻ አይደለም። በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ከውጭ የሚገቡ ተሽከርካሪዎችን በሀገር ውስጥ በጥራት ማምረት እና ለብዙ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር ነው። ድጋፍ ካገኘ ደግሞ በቀጣይ በኤሌክትሪክ የሚሠሩ ዘመናዊ ተሽከርካሪዎችን የማምረት ትልቅ ዕቅድ አለው።
የነገዋ ኢትዮጵያ ከመግዛት ወጥታ ወደ ማምረት የምትገባው በእንዲህ ያሉ ጀግኖች እጅ ነው።
#ቴዎድሮስ ደሴ ( አሚኮ)
#getu #innovationethiopia #bahirdar #techhero #madeinethiopia #engineeringexcellence #youthempowerment #ethiopiadecides #automotiveinnovation #ባሕርዳር #ፈጠራ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#የጥበበኛ እጆች ባለቤት የሆነውና በባሕር ዳር ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ በአውቶ ኤሌክትሪክ ዘርፍ የተመረቀው ወጣት ብሩክ ወንዲፍራው፣ የማይቻል የሚመስለውን በተግባር አሳይቷል።
ከዚህ ቀደም የተለያዩ የኢንዱስትሪ ማሽኖችን የሠራው ብሩክ፣ አሁን ደግሞ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ጥሬ ዕቃዎች የተሠራች ባለ አራት እግር መኪና ይፋ አድርጓል።
የተሽከርካሪዋ ልዩ መገለጫዎች
ሞተር
ባለ 300 ሲሲ (CC) ሞተር የተገጠመላት።
አቅም
በአንድ ጊዜ 4 ሰዎችን የመጫን አቅም ያላትና ከባጃጅ የተሻለ ፍጥነት የምትጓዝ።
ክብደት
ከ400 ኪሎ ግራም በላይ ክብደት አላት።
ወጪ
ለመሥራት ከ350 ሺህ ብር በላይ ወጪ ተደርጎባታል።
የብሩክ ትልቅ ራዕይ
የብሩክ ህልም መኪና ሠርቶ ማሳየት ብቻ አይደለም። በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ከውጭ የሚገቡ ተሽከርካሪዎችን በሀገር ውስጥ በጥራት ማምረት እና ለብዙ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር ነው። ድጋፍ ካገኘ ደግሞ በቀጣይ በኤሌክትሪክ የሚሠሩ ዘመናዊ ተሽከርካሪዎችን የማምረት ትልቅ ዕቅድ አለው።
የነገዋ ኢትዮጵያ ከመግዛት ወጥታ ወደ ማምረት የምትገባው በእንዲህ ያሉ ጀግኖች እጅ ነው።
#ቴዎድሮስ ደሴ ( አሚኮ)
#getu #innovationethiopia #bahirdar #techhero #madeinethiopia #engineeringexcellence #youthempowerment #ethiopiadecides #automotiveinnovation #ባሕርዳር #ፈጠራ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ባሕርዳር ለአንጋፋው የጥበብ ሰው ግዮን ዓለምሰገድ የክብር እውቅና ሰጠች
#ethiopia | በኢትዮጵያ የቲያትርና የፊልም ጥበብ ውስጥ ጉልህ አሻራ ያሳረፈውና በትውልድ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ መፍጠር የቻለው አንጋፋው ተዋናይ ግዮን ዓለምሰገድ በባሕርዳር ከተማ ደማቅ የክብርና የእውቅና ተሰጥቷል።
በውቧ የጣና ዳርቻ ከተማ በተከናወነው በዚህ የክብር መርሀግብር ላይ በርካታ የኪነጥበብ ባለሙያዎች ወዳጅ ቤተሰብ በተገኙበት ለከያኒው የሚገባውን አክብሮት ተሰጥቷል።
አንጋፋው ባለቅኔና ደራሲ ጌትነት እንየው ለግዮን ዓለምሰገድ የክብር ካባ በማልበስ ለጥበብ የከፈለውን የሕይወት ዘመን መስዋዕትነት ዘክሯል።
ግዮን ዓለምሰገድ በመድረክ ላይ ያለውን ገጸ-ባህሪ በሕይወት የመሳል፣ የድምፅ አጠቃቀምና የሰውነት እንቅስቃሴን በተመጣጣኝ ሁኔታ የማዋሃድ ልዩ ክህሎቱ የሚታወቅ ሲሆን ከትወና ባለፈም ለወጣት ባለሙያዎች መንገድ አሳይና አስተማሪ በመሆን የዘርፉን ዕድገት ሲደግፍ የቆየ የጥበብ አውራ ነው።
ይህ በባሕርዳር ከተማ የተዘጋጀው የምስጋና መርሃ-ግብር እንዲሳካ ስንታየሁ ገብሩ፣ አበባው ደረበ ፣ ቻሌ ማረው ፣ ደሳለኝ ድረስ እና ሌሎች የጥበብ ጓደኞቹ ከባሕርዳር ጥበብ አፍቃሪዎች ጋር በመሆን ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል።
የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ "እንኳን ደስ አለህ" በማለት የማይተካና የማይደፈር የሙያ አበርክቶት እንዳለው ምስክርነታቸውን የሰጡ ሲሆን ይህ አይነቱ በሕይወት እያሉ የመከበር ባህል ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
ጌጡ ተመስገን (Getu Temesgen)
#gionalemseged #bahirdar #ethiopiantheatre #artrecognition #getnetenyew #ethiopianart #tana #lifetimeachievement #cinemaethiopia #culturalheritage
#ethiopia | በኢትዮጵያ የቲያትርና የፊልም ጥበብ ውስጥ ጉልህ አሻራ ያሳረፈውና በትውልድ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ መፍጠር የቻለው አንጋፋው ተዋናይ ግዮን ዓለምሰገድ በባሕርዳር ከተማ ደማቅ የክብርና የእውቅና ተሰጥቷል።
በውቧ የጣና ዳርቻ ከተማ በተከናወነው በዚህ የክብር መርሀግብር ላይ በርካታ የኪነጥበብ ባለሙያዎች ወዳጅ ቤተሰብ በተገኙበት ለከያኒው የሚገባውን አክብሮት ተሰጥቷል።
አንጋፋው ባለቅኔና ደራሲ ጌትነት እንየው ለግዮን ዓለምሰገድ የክብር ካባ በማልበስ ለጥበብ የከፈለውን የሕይወት ዘመን መስዋዕትነት ዘክሯል።
ግዮን ዓለምሰገድ በመድረክ ላይ ያለውን ገጸ-ባህሪ በሕይወት የመሳል፣ የድምፅ አጠቃቀምና የሰውነት እንቅስቃሴን በተመጣጣኝ ሁኔታ የማዋሃድ ልዩ ክህሎቱ የሚታወቅ ሲሆን ከትወና ባለፈም ለወጣት ባለሙያዎች መንገድ አሳይና አስተማሪ በመሆን የዘርፉን ዕድገት ሲደግፍ የቆየ የጥበብ አውራ ነው።
ይህ በባሕርዳር ከተማ የተዘጋጀው የምስጋና መርሃ-ግብር እንዲሳካ ስንታየሁ ገብሩ፣ አበባው ደረበ ፣ ቻሌ ማረው ፣ ደሳለኝ ድረስ እና ሌሎች የጥበብ ጓደኞቹ ከባሕርዳር ጥበብ አፍቃሪዎች ጋር በመሆን ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል።
የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ "እንኳን ደስ አለህ" በማለት የማይተካና የማይደፈር የሙያ አበርክቶት እንዳለው ምስክርነታቸውን የሰጡ ሲሆን ይህ አይነቱ በሕይወት እያሉ የመከበር ባህል ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
ጌጡ ተመስገን (Getu Temesgen)
#gionalemseged #bahirdar #ethiopiantheatre #artrecognition #getnetenyew #ethiopianart #tana #lifetimeachievement #cinemaethiopia #culturalheritage
3 months ago
ያከበሩት ያከብራል
በአርቲስት ግዮን ዓለምሰገድ የክብር ምሽት ነገ በባህር ዳር እንገናኝ
#ethiopia | የጥበብ ባለውለታዎችን ማክበርና እውቅና መስጠት የሰለጠነ ማህበረሰብ መገለጫ ነው። ነገ ቅዳሜ መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ "የግዮን መንገድ" የተሰኘ ልዩ የምስጋናና የእውቅና መርሃ-ግብር በደማቅ ሁኔታ ይካሄዳል።
የዕለቱ ተመስጋኝ፦
አርቲስት ግዮን ዓለምሰገድ
የዕለቱ የክብር እንግዳ፦
አንጋፋውና በቅርቡ ትልቅ ክብር የተሰጠው አርቲስት ጌትነት እንየው
ነገ ቅዳሜ፣ ከቀኑ 8:00 ሰዓት ጀምሮ
ባህር ዳር፣ ዩኒሰን ሆቴል
የጥበብ አፍቃሪዎችና የጥበብ ባለሙያዎች በዚህ ታሪካዊ ምሽት ላይ ተገኝታችሁ ለአርቲስት ግዮን ዓለምሰገድ ያላችሁን አክብሮት እንድትገልጹ ተጋብዛችኋል።
በባህር ዳር ዩኒሰን ሆቴል ነገ 8:00 ሰዓት ላይ ቀጠሯችን ይሁን!
#getu #ethiopia #bahirdar #art #tribute #gyionalemseged #getnetenyew #unisonhotel #የግዮንመንገድ #ባህርዳር #ጥበብ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
በአርቲስት ግዮን ዓለምሰገድ የክብር ምሽት ነገ በባህር ዳር እንገናኝ
#ethiopia | የጥበብ ባለውለታዎችን ማክበርና እውቅና መስጠት የሰለጠነ ማህበረሰብ መገለጫ ነው። ነገ ቅዳሜ መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ "የግዮን መንገድ" የተሰኘ ልዩ የምስጋናና የእውቅና መርሃ-ግብር በደማቅ ሁኔታ ይካሄዳል።
የዕለቱ ተመስጋኝ፦
አርቲስት ግዮን ዓለምሰገድ
የዕለቱ የክብር እንግዳ፦
አንጋፋውና በቅርቡ ትልቅ ክብር የተሰጠው አርቲስት ጌትነት እንየው
ነገ ቅዳሜ፣ ከቀኑ 8:00 ሰዓት ጀምሮ
ባህር ዳር፣ ዩኒሰን ሆቴል
የጥበብ አፍቃሪዎችና የጥበብ ባለሙያዎች በዚህ ታሪካዊ ምሽት ላይ ተገኝታችሁ ለአርቲስት ግዮን ዓለምሰገድ ያላችሁን አክብሮት እንድትገልጹ ተጋብዛችኋል።
በባህር ዳር ዩኒሰን ሆቴል ነገ 8:00 ሰዓት ላይ ቀጠሯችን ይሁን!
#getu #ethiopia #bahirdar #art #tribute #gyionalemseged #getnetenyew #unisonhotel #የግዮንመንገድ #ባህርዳር #ጥበብ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
3 months ago
“እንዛንታ” ትውፊታዊ ቲያትር ተመረቀ
#ethiopia | በባህር ዳር ከተማ በሚገኘው ሙሉዓለም የባህል ማዕከል፣ የኢትዮጵያን ጥንታዊ ትውፊትና የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎችን ጥበባዊ ታሪክ የሚዘክረው “እንዛንታ” የተሰኘው ትውፊታዊ ቲያትር በደመቀ ሁኔታ ተመርቋል።
በምረቃው መርሃ ግብር ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የጥበብ ባለሙያዎችና የኪነ-ጥበብ አፍቃሪዎች ተገኝተው የጥበብ ስራውን ተከታትለዋል።
በምረቃው ወቅት ንግግር ያደረጉት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የባህል፣ ኪነ-ጥበብና ዝክረ-ታሪክ ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ የሺ ካሳ፣ እንዲህ ያሉ ትውፊታዊ ስራዎች የህዝብን ታሪክና ማንነት ጠብቆ ለማቆየት ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።
ወይዘሮ የሺ አክለውም፣ “እንዛንታ” ቲያትር የክልሉን አልፎም የሀገሪቱን የቆዩ ባህላዊ እሴቶችና የአዝማሪዎችን የጥበብ ጉዞ ለዘመኑ ትውልድ በሚመጥን መልኩ ማቅረቡ ለዘርፉ ትልቅ እመርታ መሆኑን ጠቁመዋል። መንግስት እንዲህ ያሉ ማንነትን የሚገልጹ የጥበብ ስራዎች እንዲስፋፉና ለትውልድ እንዲሸጋገሩ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል የሙሉዓለም የባህል ማዕከል ምክትል ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገብረማርያም ይርጋ በበኩላቸው፣ ማዕከሉ የጥበብ ባለሙያዎች የፈጠራ ስራዎቻቸውን እንዲያቀርቡ ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። “እንዛንታ” ቲያትር በውስጡ የያዘው የታሪክ ጥልቀትና የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ጥበባዊ አበርክቶ፣ ማዕከሉ ለሚያከናውናቸው የባህልና የኪነ-ጥበብ ስራዎች እንደ ትልቅ ግብዓት የሚያገለግል መሆኑን አብራርተዋል።
አቶ ገብረማርያም አክለውም፣ ቲያትሩ መመረቁ ብቻ ሳይሆን በቀጣይም ለተመልካች ቀርቦ የባህል ግንባታ ስራውን እንዲያግዝ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል።
ይህ “እንዛንታ” የተሰኘው ትውፊታዊ ቲያትር በታሪክ አወቃቀሩና በአቀራረቡ የባህላዊ ኪነ-ጥበብን እሴት የጠበቀ ሲሆን፣ በተለይም ለጥበብ ስራው እንደ መነሻነት ያገለገሉት የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ታሪክ በጥልቀት የተዳሰሰበት ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#enzanta #barbakanazmaris #bahirdar #ethiopianculture #artdiscussion #mulualemhall #culturalheritage #ethiopiantheatre #traditionalart
#ethiopia | በባህር ዳር ከተማ በሚገኘው ሙሉዓለም የባህል ማዕከል፣ የኢትዮጵያን ጥንታዊ ትውፊትና የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎችን ጥበባዊ ታሪክ የሚዘክረው “እንዛንታ” የተሰኘው ትውፊታዊ ቲያትር በደመቀ ሁኔታ ተመርቋል።
በምረቃው መርሃ ግብር ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የጥበብ ባለሙያዎችና የኪነ-ጥበብ አፍቃሪዎች ተገኝተው የጥበብ ስራውን ተከታትለዋል።
በምረቃው ወቅት ንግግር ያደረጉት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የባህል፣ ኪነ-ጥበብና ዝክረ-ታሪክ ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ የሺ ካሳ፣ እንዲህ ያሉ ትውፊታዊ ስራዎች የህዝብን ታሪክና ማንነት ጠብቆ ለማቆየት ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።
ወይዘሮ የሺ አክለውም፣ “እንዛንታ” ቲያትር የክልሉን አልፎም የሀገሪቱን የቆዩ ባህላዊ እሴቶችና የአዝማሪዎችን የጥበብ ጉዞ ለዘመኑ ትውልድ በሚመጥን መልኩ ማቅረቡ ለዘርፉ ትልቅ እመርታ መሆኑን ጠቁመዋል። መንግስት እንዲህ ያሉ ማንነትን የሚገልጹ የጥበብ ስራዎች እንዲስፋፉና ለትውልድ እንዲሸጋገሩ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል የሙሉዓለም የባህል ማዕከል ምክትል ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገብረማርያም ይርጋ በበኩላቸው፣ ማዕከሉ የጥበብ ባለሙያዎች የፈጠራ ስራዎቻቸውን እንዲያቀርቡ ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። “እንዛንታ” ቲያትር በውስጡ የያዘው የታሪክ ጥልቀትና የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ጥበባዊ አበርክቶ፣ ማዕከሉ ለሚያከናውናቸው የባህልና የኪነ-ጥበብ ስራዎች እንደ ትልቅ ግብዓት የሚያገለግል መሆኑን አብራርተዋል።
አቶ ገብረማርያም አክለውም፣ ቲያትሩ መመረቁ ብቻ ሳይሆን በቀጣይም ለተመልካች ቀርቦ የባህል ግንባታ ስራውን እንዲያግዝ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል።
ይህ “እንዛንታ” የተሰኘው ትውፊታዊ ቲያትር በታሪክ አወቃቀሩና በአቀራረቡ የባህላዊ ኪነ-ጥበብን እሴት የጠበቀ ሲሆን፣ በተለይም ለጥበብ ስራው እንደ መነሻነት ያገለገሉት የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ታሪክ በጥልቀት የተዳሰሰበት ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#enzanta #barbakanazmaris #bahirdar #ethiopianculture #artdiscussion #mulualemhall #culturalheritage #ethiopiantheatre #traditionalart
3 months ago
የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ጥበባዊ አበርክቶና ተግዳሮቶች ላይ ያተኮረ የጥናት ውይይት ተካሄደ
#ethiopia | በባህር ዳር ከተማ በሚገኘው ሙሉዓለም የባህል ማዕከል ለ“እንዛንታ” ተውኔት እንደ ግብዓት በሆኑት የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ዙሪያ የሚያተኩር የጥናት ውይይት በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በመድረክ ላይ በዋናነት የአዝማሪነትን ሙያዊ እሴት፣ የታሪክ አወቃቀርና በዘርፉ ላይ የሚታዩ ተግዳሮቶችን በጥልቀት ለመመርመር ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
ይህ የጥናት መድረክ በተለይ ለ“እንዛንታ” ተውኔት ስኬት ትልቅ አስተዋጽኦ የነበራቸውን የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ታሪክና ጥበባዊ ጉዞ ለመዘከር እንደ መነሻ ተወስዷል።
በተጨማሪም በውይይቱ ወቅት የባህላዊ ኪነ-ጥበብን እሴት ሳይበረዝ ጠብቆ ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ በሚቻልባቸው ስልቶች ላይ ሰፊ ምክክር ተደርጓል። ይህም ጥበባዊ ቅርሳችንን ከዘመኑ ጋር አዋህዶ ለማስቀጠል የሚደረገውን ጥረት የሚያጠናክር መሆኑ ተገልጿል።
መርሃ ግብሩ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ባሕል፣ ኪነ-ጥበብና ዝክረ-ታሪክ ጽሕፈት ቤት አማካኝነት የተዘጋጀ ሲሆን፣ በውይይቱም ላይ የዘርፉ ባለሙያዎችና የጥበብ አፍቃሪዎች ተገኝተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#enzanta #barbakanazmaris #bahirdar #ethiopianculture #artdiscussion #mulualemhall #culturalheritage #ethiopiantheatre #traditionalart
#ethiopia | በባህር ዳር ከተማ በሚገኘው ሙሉዓለም የባህል ማዕከል ለ“እንዛንታ” ተውኔት እንደ ግብዓት በሆኑት የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ዙሪያ የሚያተኩር የጥናት ውይይት በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በመድረክ ላይ በዋናነት የአዝማሪነትን ሙያዊ እሴት፣ የታሪክ አወቃቀርና በዘርፉ ላይ የሚታዩ ተግዳሮቶችን በጥልቀት ለመመርመር ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
ይህ የጥናት መድረክ በተለይ ለ“እንዛንታ” ተውኔት ስኬት ትልቅ አስተዋጽኦ የነበራቸውን የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ታሪክና ጥበባዊ ጉዞ ለመዘከር እንደ መነሻ ተወስዷል።
በተጨማሪም በውይይቱ ወቅት የባህላዊ ኪነ-ጥበብን እሴት ሳይበረዝ ጠብቆ ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ በሚቻልባቸው ስልቶች ላይ ሰፊ ምክክር ተደርጓል። ይህም ጥበባዊ ቅርሳችንን ከዘመኑ ጋር አዋህዶ ለማስቀጠል የሚደረገውን ጥረት የሚያጠናክር መሆኑ ተገልጿል።
መርሃ ግብሩ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ባሕል፣ ኪነ-ጥበብና ዝክረ-ታሪክ ጽሕፈት ቤት አማካኝነት የተዘጋጀ ሲሆን፣ በውይይቱም ላይ የዘርፉ ባለሙያዎችና የጥበብ አፍቃሪዎች ተገኝተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#enzanta #barbakanazmaris #bahirdar #ethiopianculture #artdiscussion #mulualemhall #culturalheritage #ethiopiantheatre #traditionalart
3 months ago
🎭 "እንዝታ" ትውፊታዊ ቴአትር — በባህር ዳር!
#ethiopia | በታሪካዊ ትውፊት የተዋቀረውና በብዙዎች ዘንድ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው "እንዝታ" የተሰኘው ትውፊታዊ ቴአትር፣ ነገ መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በታላቅ ድምቀት ለእይታ ይቀርባል።
የጥበብ አፍቃሪዎች ሁሉ በዚህ ልዩ መድረክ ላይ እንዲገኙ ተጋብዘዋል።
የዝግጅቱ ቦታ እና ሰዓት
ቦታ፦ ባህር ዳር ከተማ፣ በሙሉዓለም ባሕል ማዕከል
ቀን፦ ነገ መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም
ደራሲያን፦
ደሳለኝ ድረስ (መረዋ) እና ንብረት ያለው
አዘጋጅ፦ አባይነህ በለጠ
ረዳት አዘጋጅ፦ ህሩይ አበበ
ፕሮዳክሽን ማናጀር፦ ይስማው ዮሐንስ
መብራት፦ ደጉ ሙልጌታ
ስፖት ላይት፦ መንግስቱ መኮንን
መድረክ ግንባታ፦ ሙልጌታ አለኸኝ
ድምጽ ግብዓት፦ በለጠ ወንዴ
አልባሳት እና ቁሳቁስ፦ የዝና አዱኛ
🎭 ተዋንያን
በርካታ ተሰጥኦ ያላቸው ተዋንያን በመድረኩ ላይ ይከሰታሉ፦
ግዮን አለምሰገድ፣ አሳሱሁ መንግሥቱ፣ ይታየው አንዴ፣ ያለምስራ ገድፍ፣ ጊዜኔው አዲስ፣ መማር አለባቸው፣ ስዩም መኮነን፣ አመልማል ተክሉ፣ ብርሃኑ ውብአየሁ፣ ተዋቸው ወረታው፣ አመለወርቅ ወንዲራድ፣ ማስተዋል አድማሱ፣ ይኽነው ባለህ እና ሌሎችም።
ፕሮዳክሽን
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ዝክረ ታሪክ ጽሕፈት ቤት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#enzita #traditionaltheatre #ethiopiantheatre #bahirdar #mulualemculturalcenter #amharaculture #ethiopianarts #ethiopianhistory #culturalheritage #bahirdarevents
#ethiopia | በታሪካዊ ትውፊት የተዋቀረውና በብዙዎች ዘንድ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው "እንዝታ" የተሰኘው ትውፊታዊ ቴአትር፣ ነገ መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በታላቅ ድምቀት ለእይታ ይቀርባል።
የጥበብ አፍቃሪዎች ሁሉ በዚህ ልዩ መድረክ ላይ እንዲገኙ ተጋብዘዋል።
የዝግጅቱ ቦታ እና ሰዓት
ቦታ፦ ባህር ዳር ከተማ፣ በሙሉዓለም ባሕል ማዕከል
ቀን፦ ነገ መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም
ደራሲያን፦
ደሳለኝ ድረስ (መረዋ) እና ንብረት ያለው
አዘጋጅ፦ አባይነህ በለጠ
ረዳት አዘጋጅ፦ ህሩይ አበበ
ፕሮዳክሽን ማናጀር፦ ይስማው ዮሐንስ
መብራት፦ ደጉ ሙልጌታ
ስፖት ላይት፦ መንግስቱ መኮንን
መድረክ ግንባታ፦ ሙልጌታ አለኸኝ
ድምጽ ግብዓት፦ በለጠ ወንዴ
አልባሳት እና ቁሳቁስ፦ የዝና አዱኛ
🎭 ተዋንያን
በርካታ ተሰጥኦ ያላቸው ተዋንያን በመድረኩ ላይ ይከሰታሉ፦
ግዮን አለምሰገድ፣ አሳሱሁ መንግሥቱ፣ ይታየው አንዴ፣ ያለምስራ ገድፍ፣ ጊዜኔው አዲስ፣ መማር አለባቸው፣ ስዩም መኮነን፣ አመልማል ተክሉ፣ ብርሃኑ ውብአየሁ፣ ተዋቸው ወረታው፣ አመለወርቅ ወንዲራድ፣ ማስተዋል አድማሱ፣ ይኽነው ባለህ እና ሌሎችም።
ፕሮዳክሽን
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ዝክረ ታሪክ ጽሕፈት ቤት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#enzita #traditionaltheatre #ethiopiantheatre #bahirdar #mulualemculturalcenter #amharaculture #ethiopianarts #ethiopianhistory #culturalheritage #bahirdarevents
3 months ago
⛪ የአዲስ ዘመን ደብረ ደናግል ቅድስት ሐናን አብረን እናልማ!
በዐቢይ ጾም ወቅት የሚደረግ ታላቅ የበረከት ጥሪ!
ጥንታዊቷና ታሪካዊቷ የአዲስ ዘመን ደብረ ደናግል ቅድስት ሐና ካቴድራል በ837 ዓ.ም የተመሠረተችና የታሪክ አሻራ ያረፈባት ቅድስት ስፍራ ናት።
በአሁኑ ወቅት ካቴድራሏን በራስ አገዝ ልማት በማጠናከር፣ ታላቅ የሃይማኖትና የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ ሰፊ የልማት እንቅስቃሴ እየተከናወነ ይገኛል።
ይህንን የተጀመረ የተቀደሰ የልማት ሥራ ዳር ለማድረስ፣ በመጪው እሁድ በሚካሄደው የገቢ ማሰባሰቢያና የወንጌል መርሃ-ግብር ላይ እንድትገኙ ጥሪ ቀርቦላችኋል።
እሁድ፣ መጋቢት 13 ቀን 2018 ዓ.ም.
ከጠዋቱ 7:30 ሰዓት ጀምሮ
*ባሕር ዳር፤ ሰላም አድርጊው ማርያም ቤተክርስቲያን።
የትምህርተ ወንጌል ስርጭት እና የልማት ገቢ ማሰባሰቢያ።
የበረከቱ ተካፋይ ለመሆን (ድጋፍ ለማድረግ)
በአካል መገኘት ለማትችሉና ከሩቅ ሆናችሁ ለእናታችን ለቅድስት ሐና ቤት አሻራችሁን ማሳረፍ ለምትፈልጉ ሁሉ፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
የአካውንት ቁጥር፦ 1000709139634
አዘጋጅ፦
የባሕር ዳር አስተባባሪ ኮሚቴ
✨ እኛም ለቤታችን፣ እኛም ለእናታችን!
ይህ ጥንታዊ ቅርስና መንፈሳዊ ማዕከል ተጠግኖና ለምቶ ለትውልድ እንዲተላለፍ የሚደረገው ጥረት የሁላችንንም እገዛ ይሻል።
በጾም ወቅት የሚደረግ ምጽዋትና በጎ ተግባር ደግሞ ድርብ በረከት አለው።
#ቅድስትሐና #አዲስዘመን #ባሕርዳር #ኢትዮጵያ #ኦርቶዶክስ #የበረከትጥሪ #ethiopia #sainthanna #addiszemen #bahirdar #cbe #getu #temesgen #getutemesgen #ጌጡ #ተመስገን #ጌጡተመስገን
በዐቢይ ጾም ወቅት የሚደረግ ታላቅ የበረከት ጥሪ!
ጥንታዊቷና ታሪካዊቷ የአዲስ ዘመን ደብረ ደናግል ቅድስት ሐና ካቴድራል በ837 ዓ.ም የተመሠረተችና የታሪክ አሻራ ያረፈባት ቅድስት ስፍራ ናት።
በአሁኑ ወቅት ካቴድራሏን በራስ አገዝ ልማት በማጠናከር፣ ታላቅ የሃይማኖትና የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ ሰፊ የልማት እንቅስቃሴ እየተከናወነ ይገኛል።
ይህንን የተጀመረ የተቀደሰ የልማት ሥራ ዳር ለማድረስ፣ በመጪው እሁድ በሚካሄደው የገቢ ማሰባሰቢያና የወንጌል መርሃ-ግብር ላይ እንድትገኙ ጥሪ ቀርቦላችኋል።
እሁድ፣ መጋቢት 13 ቀን 2018 ዓ.ም.
ከጠዋቱ 7:30 ሰዓት ጀምሮ
*ባሕር ዳር፤ ሰላም አድርጊው ማርያም ቤተክርስቲያን።
የትምህርተ ወንጌል ስርጭት እና የልማት ገቢ ማሰባሰቢያ።
የበረከቱ ተካፋይ ለመሆን (ድጋፍ ለማድረግ)
በአካል መገኘት ለማትችሉና ከሩቅ ሆናችሁ ለእናታችን ለቅድስት ሐና ቤት አሻራችሁን ማሳረፍ ለምትፈልጉ ሁሉ፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
የአካውንት ቁጥር፦ 1000709139634
አዘጋጅ፦
የባሕር ዳር አስተባባሪ ኮሚቴ
✨ እኛም ለቤታችን፣ እኛም ለእናታችን!
ይህ ጥንታዊ ቅርስና መንፈሳዊ ማዕከል ተጠግኖና ለምቶ ለትውልድ እንዲተላለፍ የሚደረገው ጥረት የሁላችንንም እገዛ ይሻል።
በጾም ወቅት የሚደረግ ምጽዋትና በጎ ተግባር ደግሞ ድርብ በረከት አለው።
#ቅድስትሐና #አዲስዘመን #ባሕርዳር #ኢትዮጵያ #ኦርቶዶክስ #የበረከትጥሪ #ethiopia #sainthanna #addiszemen #bahirdar #cbe #getu #temesgen #getutemesgen #ጌጡ #ተመስገን #ጌጡተመስገን
3 months ago
የበላይነህ ክንዴ ግሩፕ "ሂልተን ባህር ዳር" ግንባታ ተጠናክሮ ቀጥሏል
#ethiopia | ታዋቂው የንግድ ተቋም በላይነህ ክንዴ ግሩፕ (BKG) በአማራ ክልል ርዕሰ መዲና ባህር ዳር ከተማ እያስገነባ የሚገኘው የ"ሂልተን ባህር ዳር" ሆቴል ግንባታ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ። ግሩፑ ሆቴሉን በአጭር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት የሚያስችሉ የሥራ ሂደቶች ውጤት እያሳዩ መሆኑን ገልጿል።
የግሩፑ ተከታታይ ስኬቶች
በላይነህ ክንዴ ግሩፕ በኢንቨስትመንት ዘርፍ ያለውን ተነሳሽነት በተግባር እያሳየ የሚገኝ ሲሆን፣ በቅርቡ የሚከተሉትን መጠነ ሰፊ ፕሮጀክቶች መያዙ ይታወቃል፡
* ሎጎ ሀይቅ ሪዞርት፡ በቅርቡ ግንባታው በጥራትና በፍጥነት ተጠናቆ ለምረቃ የበቃው ይህ ሪዞርት፣ የግሩፑን የአፈጻጸም ብቃት ማሳያ ሆኗል።
* አዳማ ራስ ሆቴል፡ በባህር ዳሩ ፕሮጀክት ጎን ለጎን፣ በአዳማ ከተማ የሚገኘውን የአዳማ ራስ ሆቴል የማጠናቀቂያ ሥራዎችን በከፍተኛ ትኩረት እያከናወነ ይገኛል።
ይህ በባህር ዳር እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ሆቴል፣ ከተማዋ ያላትን የቱሪስት መስህብነት ይበልጥ ከማሳደጉም በላይ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiopia #bahirdar #hiltonbahirdar #aradafm #belaynehkindegroup #investment #tourismethiopia #development
#ethiopia | ታዋቂው የንግድ ተቋም በላይነህ ክንዴ ግሩፕ (BKG) በአማራ ክልል ርዕሰ መዲና ባህር ዳር ከተማ እያስገነባ የሚገኘው የ"ሂልተን ባህር ዳር" ሆቴል ግንባታ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ። ግሩፑ ሆቴሉን በአጭር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት የሚያስችሉ የሥራ ሂደቶች ውጤት እያሳዩ መሆኑን ገልጿል።
የግሩፑ ተከታታይ ስኬቶች
በላይነህ ክንዴ ግሩፕ በኢንቨስትመንት ዘርፍ ያለውን ተነሳሽነት በተግባር እያሳየ የሚገኝ ሲሆን፣ በቅርቡ የሚከተሉትን መጠነ ሰፊ ፕሮጀክቶች መያዙ ይታወቃል፡
* ሎጎ ሀይቅ ሪዞርት፡ በቅርቡ ግንባታው በጥራትና በፍጥነት ተጠናቆ ለምረቃ የበቃው ይህ ሪዞርት፣ የግሩፑን የአፈጻጸም ብቃት ማሳያ ሆኗል።
* አዳማ ራስ ሆቴል፡ በባህር ዳሩ ፕሮጀክት ጎን ለጎን፣ በአዳማ ከተማ የሚገኘውን የአዳማ ራስ ሆቴል የማጠናቀቂያ ሥራዎችን በከፍተኛ ትኩረት እያከናወነ ይገኛል።
ይህ በባህር ዳር እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ሆቴል፣ ከተማዋ ያላትን የቱሪስት መስህብነት ይበልጥ ከማሳደጉም በላይ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiopia #bahirdar #hiltonbahirdar #aradafm #belaynehkindegroup #investment #tourismethiopia #development
Sponsored by
Surafel
4 months ago
🌿 እንኳን ለሰባር ጊዮርጊስ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! 🌿
"ባሕር ዳር በጊዮርጊስ በረከት ደምቃለች!"
በውቢቷ የባሕር ዳር ከተማ የሚከበረው የሰባር ጊዮርጊስ ዓመታዊ ክብረ በዓል በታላቅ ድምቀት እና መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓት እየተከናወነ ይገኛል።
🌊 ልዩ ድባብ:
በአባቶች ቡራኬ እና በያሬዳዊ ዜማ የታጀበው ይህ ክብረ በዓል፤ በተለይም በጣና ሐይቅ አካባቢ የተደረገው የመባረክ ሥርዓት ለበዓሉ ልዩ ድምቀት ሰጥቶታል።
አሁን ላይ ታቦተ ሕጉ በምእመናን አጀብ እና በዝማሬ ታጅቦ ወደ መንበሩ በመመለስ ላይ ይገኛል።
የሰባር ጊዮርጊስ ረድኤት እና በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን!
ለወዳጅዎ ሼር በማድረግ የበረከቱ ተካፋይ ያድርጉ።
#bahirdar #sebargiyorgis #orthodox #tana #ethiopia #saintgeorge #feast
"ባሕር ዳር በጊዮርጊስ በረከት ደምቃለች!"
በውቢቷ የባሕር ዳር ከተማ የሚከበረው የሰባር ጊዮርጊስ ዓመታዊ ክብረ በዓል በታላቅ ድምቀት እና መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓት እየተከናወነ ይገኛል።
🌊 ልዩ ድባብ:
በአባቶች ቡራኬ እና በያሬዳዊ ዜማ የታጀበው ይህ ክብረ በዓል፤ በተለይም በጣና ሐይቅ አካባቢ የተደረገው የመባረክ ሥርዓት ለበዓሉ ልዩ ድምቀት ሰጥቶታል።
አሁን ላይ ታቦተ ሕጉ በምእመናን አጀብ እና በዝማሬ ታጅቦ ወደ መንበሩ በመመለስ ላይ ይገኛል።
የሰባር ጊዮርጊስ ረድኤት እና በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን!
ለወዳጅዎ ሼር በማድረግ የበረከቱ ተካፋይ ያድርጉ።
#bahirdar #sebargiyorgis #orthodox #tana #ethiopia #saintgeorge #feast
4 months ago
🛶 የጣናዋ ንግሥት!
የ55 ዓመቷ "ታንኳ ቀዛፊ" እና የሁለት ጊዜ የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ! 🥇
#ethiopia | "ታንኳ ለኔ ሕይወት ነው! እህትና ወንድሞቼን ያሳደግኩበት፤ ልጄን ያስተማርኩበት ባለውለታዬ ነው" - ወ/ሮ ፀሐይነሽ ጀምበር
ባሕር ዳር ከምትታወቅባቸው ልዩ እሴቶች መካከል ከፓፒረስ (ደንገል) የሚሰራው "ታንኳ" አንዱ ነው። ታንኳ ለቱሪስቶች የፎቶ ጌጥ ቢሆንም፤ እንደ ወይዘሮ ፀሐይነሽ ጀምበር ላሉት ግን የሕይወት እስትንፋስ ነው።
የወይዘሮ ፀሐይነሽ አስደናቂ ታሪክ:
🌊 የልጅነት ሸክም:
ገና በ15 ዓመታቸው ወላጆቻቸውን በሞት ሲነጠቁ፤ ታንኳ እየቀዘፉ እንጨትና ጨፌ ወደ ባሕር ዳር በማጓጓዝ ታናናሽ ወንድም እና እህቶቻቸውን አሳድገዋል።
🌊 የቤተሰብ ምሰሶ:
ባለቤታቸውን በሞት ሲያጡም አልተሸነፉም! ጣናን እና አባይን እየገመሱ በአንዲት ልጃቸው ምክንያት ተስፋ ሳይቆርጡ ኑሮን አሸንፈዋል።
🌊 የውድድር ጀግና:
በባሕር ዳር ፌስቲባል ላይ በታንኳ ቀዘፋ ውድድር የሁለት ጊዜ (የአንደኝነት እና የሁለተኛነት) የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ ናቸው።
"ልጄ አንድ ቢሆንም ያለ ማንም እገዛ ትምህርት ቤት የሚመላለሰው ታንኳ እየቀዘፈ ነው" የሚሉት እኚህ ጠንካራ እናት፤ የታንኳ ቀዘፋ ሙያን ለትውልድ እያስተላለፉ ይገኛሉ።
የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደርም ታንኳን እንደ ብስክሌት የከተማዋ መለያ (Brand) ለማድረግ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።
ለእኚህ ጀግና እናት ክብር ይገባቸዋል! 👏❤️
ሮዛ የሻነህ (አሚኮ)
#bahirdar #laketana #tankua #strongwoman #ethiopianculture #tourism #amhara #inspiration
የ55 ዓመቷ "ታንኳ ቀዛፊ" እና የሁለት ጊዜ የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ! 🥇
#ethiopia | "ታንኳ ለኔ ሕይወት ነው! እህትና ወንድሞቼን ያሳደግኩበት፤ ልጄን ያስተማርኩበት ባለውለታዬ ነው" - ወ/ሮ ፀሐይነሽ ጀምበር
ባሕር ዳር ከምትታወቅባቸው ልዩ እሴቶች መካከል ከፓፒረስ (ደንገል) የሚሰራው "ታንኳ" አንዱ ነው። ታንኳ ለቱሪስቶች የፎቶ ጌጥ ቢሆንም፤ እንደ ወይዘሮ ፀሐይነሽ ጀምበር ላሉት ግን የሕይወት እስትንፋስ ነው።
የወይዘሮ ፀሐይነሽ አስደናቂ ታሪክ:
🌊 የልጅነት ሸክም:
ገና በ15 ዓመታቸው ወላጆቻቸውን በሞት ሲነጠቁ፤ ታንኳ እየቀዘፉ እንጨትና ጨፌ ወደ ባሕር ዳር በማጓጓዝ ታናናሽ ወንድም እና እህቶቻቸውን አሳድገዋል።
🌊 የቤተሰብ ምሰሶ:
ባለቤታቸውን በሞት ሲያጡም አልተሸነፉም! ጣናን እና አባይን እየገመሱ በአንዲት ልጃቸው ምክንያት ተስፋ ሳይቆርጡ ኑሮን አሸንፈዋል።
🌊 የውድድር ጀግና:
በባሕር ዳር ፌስቲባል ላይ በታንኳ ቀዘፋ ውድድር የሁለት ጊዜ (የአንደኝነት እና የሁለተኛነት) የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ ናቸው።
"ልጄ አንድ ቢሆንም ያለ ማንም እገዛ ትምህርት ቤት የሚመላለሰው ታንኳ እየቀዘፈ ነው" የሚሉት እኚህ ጠንካራ እናት፤ የታንኳ ቀዘፋ ሙያን ለትውልድ እያስተላለፉ ይገኛሉ።
የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደርም ታንኳን እንደ ብስክሌት የከተማዋ መለያ (Brand) ለማድረግ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።
ለእኚህ ጀግና እናት ክብር ይገባቸዋል! 👏❤️
ሮዛ የሻነህ (አሚኮ)
#bahirdar #laketana #tankua #strongwoman #ethiopianculture #tourism #amhara #inspiration