25 days ago
በምክክር ጉባኤው እንደ ሀገር ሥር የሰደዱ እና ውስብስብ ችግሮች ዙሪያ የጋራ መግባባት እንደሚፈጠር እንጠብቃለን - የባሕር ዳር ከተማ ነዋሪዎች
*****************
ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የምታካሂደው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ እንደ ሀገር ያደሩ እና ለዘመናት የተከማቹ ልዩነቶችን ከማጥበብ ባለፈ አብሮነትን በመገንባት ረገድ አይተኬ ሚና እንዳለው የባሕር ዳር ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።
ምክክር የተለያዩ የተቃርኖ ሐሳቦችን የምናርቅበት፣ ነጣጣይ እና የተሳሳቱ ትርክቶችን የምናርምበት፣ ብሔራዊ አንድነታችንን እና ብሔራዊ ጥቅሞቻችንን የምናስከብርበት የችግሮቻችን ሁሉ ቁልፍ መሣሪያ ስለመሆኑ ነው የገለጹት።
ሀገራችን ኢትዮጵያ ብዙ አስታራቂ እምነቶች፣ የባህል እሴቶች ባለቤት ብትሆንም እርስ በርስ የመነጋገር እና የመወያየት ባህላችን ደካማ በመሆኑ ለብዙ ተግዳሮቶች ስንጋለጥ ቆይተናል ያሉት ነዋሪዎቹ፤ አሁን ላይ ግን እንደ ሀገር በታሪክ አጋጣሚ የምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ ጥያቄዎቻችንን በጠረጴዛ ዙሪያ ለመፍታት የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ እንገኛለን ብለዋል።
ከሐምሌ 8 ጀምሮ የሚካሄደውን የምክክር ጉባኤን በጉጉት እና በተስፋ እንደሚጠብቁትም ተናግረዋል።
በክልሉ በነበረው የአጀንዳ ማሰባሰብ ምዕራፍም የተለያዩ አጀንዳዎችን ለምክክር ኮሚሽኑ ማስረከባቸውን የገለጹት ነዋሪዎቹ፤ ከቀናት በኋላ በሚጀምረው ጉባኤ እንደ ሀገር ሥር የሰደዱ እና ውስብስብ ችግሮችን ጨምሮ ያነሧቸው መሠረታዊ ጥያቄዎች እንደሚመለሱላቸው በተስፋ እንደሚጠብቁ ጠቁመዋል።
ሀገር የምትገነባው በንግግር እና በምክክር በመሆኑ ለዘላቂ ሰላም፣ ለብሔራዊ ትርክት ግንባታ እና ለብሔራዊ ጥቅሞቻችን መከበር በታሪክ አጋጣሚ የተገኘውን ወርቃማ ዕድል በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባም አሳስበዋል።
ለጉባኤው ስኬትም መላው ኢትዮጵያውያን ድጋፋቸውን በቁርጠኝነት እንዲያሳዩ ጥሪ አቅርበዋል።
በተስፋሁን ደስታ
#ethiopia #ebc #nationaldialogue #bahirdar
*****************
ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የምታካሂደው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ እንደ ሀገር ያደሩ እና ለዘመናት የተከማቹ ልዩነቶችን ከማጥበብ ባለፈ አብሮነትን በመገንባት ረገድ አይተኬ ሚና እንዳለው የባሕር ዳር ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።
ምክክር የተለያዩ የተቃርኖ ሐሳቦችን የምናርቅበት፣ ነጣጣይ እና የተሳሳቱ ትርክቶችን የምናርምበት፣ ብሔራዊ አንድነታችንን እና ብሔራዊ ጥቅሞቻችንን የምናስከብርበት የችግሮቻችን ሁሉ ቁልፍ መሣሪያ ስለመሆኑ ነው የገለጹት።
ሀገራችን ኢትዮጵያ ብዙ አስታራቂ እምነቶች፣ የባህል እሴቶች ባለቤት ብትሆንም እርስ በርስ የመነጋገር እና የመወያየት ባህላችን ደካማ በመሆኑ ለብዙ ተግዳሮቶች ስንጋለጥ ቆይተናል ያሉት ነዋሪዎቹ፤ አሁን ላይ ግን እንደ ሀገር በታሪክ አጋጣሚ የምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ ጥያቄዎቻችንን በጠረጴዛ ዙሪያ ለመፍታት የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ እንገኛለን ብለዋል።
ከሐምሌ 8 ጀምሮ የሚካሄደውን የምክክር ጉባኤን በጉጉት እና በተስፋ እንደሚጠብቁትም ተናግረዋል።
በክልሉ በነበረው የአጀንዳ ማሰባሰብ ምዕራፍም የተለያዩ አጀንዳዎችን ለምክክር ኮሚሽኑ ማስረከባቸውን የገለጹት ነዋሪዎቹ፤ ከቀናት በኋላ በሚጀምረው ጉባኤ እንደ ሀገር ሥር የሰደዱ እና ውስብስብ ችግሮችን ጨምሮ ያነሧቸው መሠረታዊ ጥያቄዎች እንደሚመለሱላቸው በተስፋ እንደሚጠብቁ ጠቁመዋል።
ሀገር የምትገነባው በንግግር እና በምክክር በመሆኑ ለዘላቂ ሰላም፣ ለብሔራዊ ትርክት ግንባታ እና ለብሔራዊ ጥቅሞቻችን መከበር በታሪክ አጋጣሚ የተገኘውን ወርቃማ ዕድል በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባም አሳስበዋል።
ለጉባኤው ስኬትም መላው ኢትዮጵያውያን ድጋፋቸውን በቁርጠኝነት እንዲያሳዩ ጥሪ አቅርበዋል።
በተስፋሁን ደስታ
#ethiopia #ebc #nationaldialogue #bahirdar
2 months ago
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ 10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር በባህርዳር ከተማ ሊካሄድ ነው
#ethiopia | የመጀመሪያው የኢትዮጵያ 10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር የፊታችን እሁድ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም በባህርዳር ከተማ በደመቀ ሁኔታ እንደሚካሄድ ተነገረ።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በውድድሩ ቅድመ ዝግጅት ስራዎች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው መግለጫ፣ የፌዴሬሽኑ ከፍተኛ የቴክኒክ ባለሙያዎች ወደ ስፍራው በማቅናት አስፈላጊውን ዝግጅት እያከናወኑ እንደሚገኙ አስታውቋል።
ይህ የውድድር መድረክ በዋናነት አዳዲስ ተተኪ አትሌቶችን ለማፍራትና የውድድር እድሎችን ለመፍጠር ያለመ መሆኑም ተገልጿል።
በዚሁ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ላይ የግል ተሳታፊዎችን ጨምሮ ከ6 የተለያዩ ክለቦች የተውጣጡ 91 አትሌቶች እንደሚሳተፉ ታውቋል። በውድድሩ ከ1ኛ እስከ 8ኛ ያለውን ደረጃ ይዘው ለሚያጠናቅቁ አትሌቶችም የገንዘብ ሽልማት እንደሚበረከትላቸው ተገልጿል።
ይህንን ጋዜጣዊ መግለጫ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የውድድርና ተሳትፎ ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ጊዜ አድነው እና አቶ መሐሪ ነጋሽ በጋራ የሰጡት ሲሆን፣ ውድድሩ በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በቀጥታ ስርጭት ለተመልካች እንደሚተላለፍ ታውቋል።
#ethiopianathletics #bahirdar #streetrace #10krun #ethiopiansport #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የመጀመሪያው የኢትዮጵያ 10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር የፊታችን እሁድ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም በባህርዳር ከተማ በደመቀ ሁኔታ እንደሚካሄድ ተነገረ።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በውድድሩ ቅድመ ዝግጅት ስራዎች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው መግለጫ፣ የፌዴሬሽኑ ከፍተኛ የቴክኒክ ባለሙያዎች ወደ ስፍራው በማቅናት አስፈላጊውን ዝግጅት እያከናወኑ እንደሚገኙ አስታውቋል።
ይህ የውድድር መድረክ በዋናነት አዳዲስ ተተኪ አትሌቶችን ለማፍራትና የውድድር እድሎችን ለመፍጠር ያለመ መሆኑም ተገልጿል።
በዚሁ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ላይ የግል ተሳታፊዎችን ጨምሮ ከ6 የተለያዩ ክለቦች የተውጣጡ 91 አትሌቶች እንደሚሳተፉ ታውቋል። በውድድሩ ከ1ኛ እስከ 8ኛ ያለውን ደረጃ ይዘው ለሚያጠናቅቁ አትሌቶችም የገንዘብ ሽልማት እንደሚበረከትላቸው ተገልጿል።
ይህንን ጋዜጣዊ መግለጫ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የውድድርና ተሳትፎ ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ጊዜ አድነው እና አቶ መሐሪ ነጋሽ በጋራ የሰጡት ሲሆን፣ ውድድሩ በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በቀጥታ ስርጭት ለተመልካች እንደሚተላለፍ ታውቋል።
#ethiopianathletics #bahirdar #streetrace #10krun #ethiopiansport #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
በባሕር ዳር የሚንቀሳቀሱ የመኖሪያ ቤት አልሚ አክሲዮን ማኅበራት አሠራራቸውን ዘመናዊ የሚያደርግ አዲስ መተግበሪያ እና ድረገጽ አስገመገሙ
#ethiopia | በቤት ልማት ዘርፍ ላይ የተሰማሩና መቀመጫቸውን በባሕር ዳር ከተማ ያደረጉ አራት የአክሲዮን ማኅበራት፣ አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴያቸውን ወደ ዲጂታል ሥርዓት ለማሸጋገር ያዘጋጁትን አዲስ የቴክኖሎጂ መተግበሪያ በባለሙያዎች አስገምግመዋል።
ዋዜማ፣ ፕላኔት፣ ዋን ሩፍ እና ታውን አፓርትመንት የተባሉት እነዚህ ማኅበራት፣ ለአባላቶቻቸው ዘመናዊ የመኖሪያ ቤቶችን ለመገንባት ተቋቁመው ወደ ሥራ የገቡ ኩባንያዎች ናቸው።
የኩባንያዎቹ መሥራች አቶ ዘላለም እሸቱ በምክክር መድረኩ ላይ እንደተናገሩት፣ አሠራርን በቴክኖሎጂ መደገፍ በአሁኑ ወቅት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ሆኗል። ማኅበራቱ በአገር ውስጥና በውጭ አገር ከሚኖሩ ባለአክሲዮኖች በሚሰበሰብ መዋጮ የሚንቀሳቀሱ በመሆናቸው፣ አዲሱ መተግበሪያ በሥራዎች ላይ ፍጹም ግልጸኝነትን ለመፍጠር ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግ አብራርተዋል።
ቀደም ሲል የነበረው አሠራር የቤት ግንባታ ገቢና ወጪዎችን በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ በሚደረግ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የሚያቀርብ በመሆኑ የመረጃ ክፍተት ይፈጥር ነበር።
አዲሱ የቴክኖሎጂ አማራጭ ግን እያንዳንዱ የገንዘብ እንቅስቃሴ የወቅቱን የገበያ ዋጋ ባገናዘበ ማስረጃ እንዲደገፍ የሚያደርግ ሲሆን፣ ባለአክሲዮኖችም ባሉበት ሆነው መረጃዎችን በቀጥታ መከታተል እንዲችሉ ያስችላቸዋል።
በዕለቱ የተገኙት የክልሉ ንግድ ቢሮ የአክሲዮን ክትትል ባለሙያ አቶ ደሳለኝ ጓንቻ በበኩላቸው፣ በአሁኑ ወቅት የአክሲዮን ማኅበራት ዋነኛ ፈተና የአሠራር ግልጸኝነት ማጣት መሆኑን ጠቅሰው ይህ ጅማሮ ለሌሎችም አርአያ የሚሆንና ትልቅ መፍትሔ ይዞ የመጣ መሆኑን ገልጸዋል።
በምክክር መድረኩ ላይ በባለሙያዎች የተነሱ ጠቃሚ ማሻሻያዎችን በማካተት መተግበሪያው በፍጥነት ወደ ሥራ እንዲገባ መግባባት ላይ ተደርሷል።
#bahirdar #digitaltransformation #realestateethiopia #technology #housingdevelopment #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በቤት ልማት ዘርፍ ላይ የተሰማሩና መቀመጫቸውን በባሕር ዳር ከተማ ያደረጉ አራት የአክሲዮን ማኅበራት፣ አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴያቸውን ወደ ዲጂታል ሥርዓት ለማሸጋገር ያዘጋጁትን አዲስ የቴክኖሎጂ መተግበሪያ በባለሙያዎች አስገምግመዋል።
ዋዜማ፣ ፕላኔት፣ ዋን ሩፍ እና ታውን አፓርትመንት የተባሉት እነዚህ ማኅበራት፣ ለአባላቶቻቸው ዘመናዊ የመኖሪያ ቤቶችን ለመገንባት ተቋቁመው ወደ ሥራ የገቡ ኩባንያዎች ናቸው።
የኩባንያዎቹ መሥራች አቶ ዘላለም እሸቱ በምክክር መድረኩ ላይ እንደተናገሩት፣ አሠራርን በቴክኖሎጂ መደገፍ በአሁኑ ወቅት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ሆኗል። ማኅበራቱ በአገር ውስጥና በውጭ አገር ከሚኖሩ ባለአክሲዮኖች በሚሰበሰብ መዋጮ የሚንቀሳቀሱ በመሆናቸው፣ አዲሱ መተግበሪያ በሥራዎች ላይ ፍጹም ግልጸኝነትን ለመፍጠር ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግ አብራርተዋል።
ቀደም ሲል የነበረው አሠራር የቤት ግንባታ ገቢና ወጪዎችን በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ በሚደረግ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የሚያቀርብ በመሆኑ የመረጃ ክፍተት ይፈጥር ነበር።
አዲሱ የቴክኖሎጂ አማራጭ ግን እያንዳንዱ የገንዘብ እንቅስቃሴ የወቅቱን የገበያ ዋጋ ባገናዘበ ማስረጃ እንዲደገፍ የሚያደርግ ሲሆን፣ ባለአክሲዮኖችም ባሉበት ሆነው መረጃዎችን በቀጥታ መከታተል እንዲችሉ ያስችላቸዋል።
በዕለቱ የተገኙት የክልሉ ንግድ ቢሮ የአክሲዮን ክትትል ባለሙያ አቶ ደሳለኝ ጓንቻ በበኩላቸው፣ በአሁኑ ወቅት የአክሲዮን ማኅበራት ዋነኛ ፈተና የአሠራር ግልጸኝነት ማጣት መሆኑን ጠቅሰው ይህ ጅማሮ ለሌሎችም አርአያ የሚሆንና ትልቅ መፍትሔ ይዞ የመጣ መሆኑን ገልጸዋል።
በምክክር መድረኩ ላይ በባለሙያዎች የተነሱ ጠቃሚ ማሻሻያዎችን በማካተት መተግበሪያው በፍጥነት ወደ ሥራ እንዲገባ መግባባት ላይ ተደርሷል።
#bahirdar #digitaltransformation #realestateethiopia #technology #housingdevelopment #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 months ago
በጣና ዳርቻ ላይ የሚገነባው የቱሪዝም መዳረሻ
#bahirdar #tourismethiopia #midrocinvestmentgroup #laketana #newproject #ethiopiarising #ባሕርዳር #ኢትዮጵያ
Sponsored by
Surafel
3 months ago
የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት አካል የሆነው ግዙፉ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት በባህር ዳር ከተማ ተመረቀ
#ethiopia | በውቧ ባህር ዳር ከተማ በከፍተኛ ወጪ የተገነባው ግዙፉ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ዛሬ ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በታላቅ ስነ ስርዓት ተመርቋል።
በደቡባዊ የጣና ሀይቅ ዳርቻ ላይ ያረፈው ይህ ሪዞርት በጎርጎራ በኩል የተጀመረውን የቱሪዝም ልማት ብርሃን ወደ ሌላኛው የሀይቁ ዳርቻ ያሸጋገረ ግዙፍ ኢንቨስትመንት ነው።
ፕሮጀክቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በገበታ ለሀገር እቅድ አማካኝነት ሁለት የጣና ሀይቅ ዳርቻዎችን በቱሪዝም ለማስተሳሰር የነደፉትን ታላቅ ራዕይ ዳር ያደረሰ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የታሪካዊቷን የጎርጎራ ከተማ ገፅታ ከመቀየር ባለፈ በዐፄ ፋሲለደስ መናገሻ ጎንደር የሚገኙ የቤተ መንግስት ቅርሶችን በከፍተኛ ጥራት በማደስ ለዘላቂ ቱሪዝም ዝግጁ እንዲሆኑ አድርገዋል።
ከዚህም በተጨማሪ ለጎንደር ከተማ የመጠጥ ውሃ እና ለግብርና ልማት የሚውለው የመገጭ ግድብ ግንባታ ለውሃ ቱሪዝም አዲስ እድል ይዞ እየመጣ ይገኛል።
ይህንን መንግስታዊ ራዕይ በግል ኢንቨስትመንት በማገዝ የቤአኢካ እና የእህት ኩባንያዎቹ መስራች አቶ ካሳሁን ምስጋናው የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርትን በ 4.5 ቢሊዮን ብር ወጪ በሁለት አመት ከስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ገንብተው አጠናቀዋል።
ግለሰቡ በጎርጎራ ኢኮ ቱሪዝም ግንባታ እና በጎንደር ቅርሶች ጥገና ላይ የነበራቸውን ውጤታማ ተሳትፎ አሁን ደግሞ በቱሪዝም ኢንዱስትሪው ውስጥ በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ በኩል በስፋት ለመቀጠል ተዘጋጅተዋል።
አቶ ካሳሁን ለእነዚህ ስራዎች ስኬት የፌዴራል እና የክልል መንግስታት እንዲሁም የከተማ አስተዳደሮች ላደረጉላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ወደፊትም የፈለገ ግዮን እና የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርቶች በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ ስር በመሆን ልባችን ኢትዮጵያ ደረጃችን አለም አቀፍ በሚል መሪ ቃል ጥራት ያለው አገልግሎት ለጎብኚዎች እንደሚያቀርቡ ተገልጿል።
#bahirdar #tanalake #tourismethiopia #beaikainvestment #rodahospitality #development #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በውቧ ባህር ዳር ከተማ በከፍተኛ ወጪ የተገነባው ግዙፉ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ዛሬ ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በታላቅ ስነ ስርዓት ተመርቋል።
በደቡባዊ የጣና ሀይቅ ዳርቻ ላይ ያረፈው ይህ ሪዞርት በጎርጎራ በኩል የተጀመረውን የቱሪዝም ልማት ብርሃን ወደ ሌላኛው የሀይቁ ዳርቻ ያሸጋገረ ግዙፍ ኢንቨስትመንት ነው።
ፕሮጀክቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በገበታ ለሀገር እቅድ አማካኝነት ሁለት የጣና ሀይቅ ዳርቻዎችን በቱሪዝም ለማስተሳሰር የነደፉትን ታላቅ ራዕይ ዳር ያደረሰ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የታሪካዊቷን የጎርጎራ ከተማ ገፅታ ከመቀየር ባለፈ በዐፄ ፋሲለደስ መናገሻ ጎንደር የሚገኙ የቤተ መንግስት ቅርሶችን በከፍተኛ ጥራት በማደስ ለዘላቂ ቱሪዝም ዝግጁ እንዲሆኑ አድርገዋል።
ከዚህም በተጨማሪ ለጎንደር ከተማ የመጠጥ ውሃ እና ለግብርና ልማት የሚውለው የመገጭ ግድብ ግንባታ ለውሃ ቱሪዝም አዲስ እድል ይዞ እየመጣ ይገኛል።
ይህንን መንግስታዊ ራዕይ በግል ኢንቨስትመንት በማገዝ የቤአኢካ እና የእህት ኩባንያዎቹ መስራች አቶ ካሳሁን ምስጋናው የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርትን በ 4.5 ቢሊዮን ብር ወጪ በሁለት አመት ከስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ገንብተው አጠናቀዋል።
ግለሰቡ በጎርጎራ ኢኮ ቱሪዝም ግንባታ እና በጎንደር ቅርሶች ጥገና ላይ የነበራቸውን ውጤታማ ተሳትፎ አሁን ደግሞ በቱሪዝም ኢንዱስትሪው ውስጥ በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ በኩል በስፋት ለመቀጠል ተዘጋጅተዋል።
አቶ ካሳሁን ለእነዚህ ስራዎች ስኬት የፌዴራል እና የክልል መንግስታት እንዲሁም የከተማ አስተዳደሮች ላደረጉላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ወደፊትም የፈለገ ግዮን እና የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርቶች በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ ስር በመሆን ልባችን ኢትዮጵያ ደረጃችን አለም አቀፍ በሚል መሪ ቃል ጥራት ያለው አገልግሎት ለጎብኚዎች እንደሚያቀርቡ ተገልጿል።
#bahirdar #tanalake #tourismethiopia #beaikainvestment #rodahospitality #development #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 months ago
እንዲህ በትብብር ስንሠራ ወደ ብልጽግና የሚያሻግሩ ተግባራትን ማሳካት እንችላለን - ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ
******************
እንደ ፈለገ ጊዮን ኢኮ ሪዞርት ያሉ ግዙፍ የቱሪዝም ፕሮጀክቶች ለክልሉ ተጨማሪ ጸጋ ከመሆናቸውም በላይ የኢትዮጵያን የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ስለመሆናቸው የአማራ ክልል ርዕስ መስተዳድር አረጋ ከበደ ተናገሩ።
በባህር ዳር ከተማ የተገነባው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት በይፋ ተመርቋል።
ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፥ ሪዞርቱ ጥራት፣ ውበትና ምቾትን ከመላበሱ ባሻገር፣ ለታሪካዊው የጣና ሐይቅ ደህንነት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመገንባቱ ለሌሎች መሰል ፕሮጀክቶች እንደ አርአያ የሚጠቀስ መሆኑን አብራርተዋል።
ሪዞርቱ ከመንግሥትና ከግል ባለሀብቱ ጥንካሬ የተገኘ የጋራ ውጤት መሆኑን በመጥቀስ፣ "ሀሳብና ተግባር ሲገናኙ የማይታለፉ የሚመስሉ ፈታኝ ጊዜያትን በትብብር መሻገር እንደሚቻል የታየበት ነው ብለዋል።
ሪዞርቱ ለጎብኚዎች ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ከዘርፉ ማግኘት የሚገባንን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማግኘት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርም ገልጸዋል።
እንደ ርዕሰ መስተዳድሩ ገለጻ፥ የጣና ሐይቅ የኢትዮጵያ ጥንታዊ ሥልጣኔ መገለጫ እንደመሆኑ፣ አሁን ላይ ተግባራዊ እየሆነ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ፖሊሲ ደግሞ ዛሬን ከነገ በማገናኘት የቱሪዝም ሀብቶቻችንን ለትውልድ በሚተርፍ መልኩ ለማልማት ዕድል ፈጥሯል።
እንዲህ በትብብር ሲሥሠራ ወደ ብልጽግና የሚያሻግሩ ተግባራትን ማሳካት እንደሚቻል በመጠቆም፣ ዛሬም ሆነ ነገ ትብብራችንን በማጠናከር ለትውልድ የሚተርፍ አሻራ ማኖር ይገባል ብለዋል።
ከልማትና ከትብብር ውጪ ያለው አማራጭ የጥፋት መንገድ መሆኑን በማስገንዘብ፣ ሁሉም አካላት ለክልሉና ለሀገር ዕድገት በጋራ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል።
በአሸናፊ እንዳለ
#ethiopia #bahirdar #felegegion #resort #ebc
******************
እንደ ፈለገ ጊዮን ኢኮ ሪዞርት ያሉ ግዙፍ የቱሪዝም ፕሮጀክቶች ለክልሉ ተጨማሪ ጸጋ ከመሆናቸውም በላይ የኢትዮጵያን የቱሪዝም ኢንዱስትሪ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩ ስለመሆናቸው የአማራ ክልል ርዕስ መስተዳድር አረጋ ከበደ ተናገሩ።
በባህር ዳር ከተማ የተገነባው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በተገኙበት በይፋ ተመርቋል።
ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፥ ሪዞርቱ ጥራት፣ ውበትና ምቾትን ከመላበሱ ባሻገር፣ ለታሪካዊው የጣና ሐይቅ ደህንነት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመገንባቱ ለሌሎች መሰል ፕሮጀክቶች እንደ አርአያ የሚጠቀስ መሆኑን አብራርተዋል።
ሪዞርቱ ከመንግሥትና ከግል ባለሀብቱ ጥንካሬ የተገኘ የጋራ ውጤት መሆኑን በመጥቀስ፣ "ሀሳብና ተግባር ሲገናኙ የማይታለፉ የሚመስሉ ፈታኝ ጊዜያትን በትብብር መሻገር እንደሚቻል የታየበት ነው ብለዋል።
ሪዞርቱ ለጎብኚዎች ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ከዘርፉ ማግኘት የሚገባንን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማግኘት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርም ገልጸዋል።
እንደ ርዕሰ መስተዳድሩ ገለጻ፥ የጣና ሐይቅ የኢትዮጵያ ጥንታዊ ሥልጣኔ መገለጫ እንደመሆኑ፣ አሁን ላይ ተግባራዊ እየሆነ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ፖሊሲ ደግሞ ዛሬን ከነገ በማገናኘት የቱሪዝም ሀብቶቻችንን ለትውልድ በሚተርፍ መልኩ ለማልማት ዕድል ፈጥሯል።
እንዲህ በትብብር ሲሥሠራ ወደ ብልጽግና የሚያሻግሩ ተግባራትን ማሳካት እንደሚቻል በመጠቆም፣ ዛሬም ሆነ ነገ ትብብራችንን በማጠናከር ለትውልድ የሚተርፍ አሻራ ማኖር ይገባል ብለዋል።
ከልማትና ከትብብር ውጪ ያለው አማራጭ የጥፋት መንገድ መሆኑን በማስገንዘብ፣ ሁሉም አካላት ለክልሉና ለሀገር ዕድገት በጋራ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል።
በአሸናፊ እንዳለ
#ethiopia #bahirdar #felegegion #resort #ebc
4 months ago
ባሕር ዳር፦ ወጣት ብሩክ የሠራው አዲሱ መኪና
#የጥበበኛ እጆች ባለቤት የሆነውና በባሕር ዳር ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ በአውቶ ኤሌክትሪክ ዘርፍ የተመረቀው ወጣት ብሩክ ወንዲፍራው፣ የማይቻል የሚመስለውን በተግባር አሳይቷል።
ከዚህ ቀደም የተለያዩ የኢንዱስትሪ ማሽኖችን የሠራው ብሩክ፣ አሁን ደግሞ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ጥሬ ዕቃዎች የተሠራች ባለ አራት እግር መኪና ይፋ አድርጓል።
የተሽከርካሪዋ ልዩ መገለጫዎች
ሞተር
ባለ 300 ሲሲ (CC) ሞተር የተገጠመላት።
አቅም
በአንድ ጊዜ 4 ሰዎችን የመጫን አቅም ያላትና ከባጃጅ የተሻለ ፍጥነት የምትጓዝ።
ክብደት
ከ400 ኪሎ ግራም በላይ ክብደት አላት።
ወጪ
ለመሥራት ከ350 ሺህ ብር በላይ ወጪ ተደርጎባታል።
የብሩክ ትልቅ ራዕይ
የብሩክ ህልም መኪና ሠርቶ ማሳየት ብቻ አይደለም። በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ከውጭ የሚገቡ ተሽከርካሪዎችን በሀገር ውስጥ በጥራት ማምረት እና ለብዙ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር ነው። ድጋፍ ካገኘ ደግሞ በቀጣይ በኤሌክትሪክ የሚሠሩ ዘመናዊ ተሽከርካሪዎችን የማምረት ትልቅ ዕቅድ አለው።
የነገዋ ኢትዮጵያ ከመግዛት ወጥታ ወደ ማምረት የምትገባው በእንዲህ ያሉ ጀግኖች እጅ ነው።
#ቴዎድሮስ ደሴ ( አሚኮ)
#getu #innovationethiopia #bahirdar #techhero #madeinethiopia #engineeringexcellence #youthempowerment #ethiopiadecides #automotiveinnovation #ባሕርዳር #ፈጠራ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#የጥበበኛ እጆች ባለቤት የሆነውና በባሕር ዳር ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ በአውቶ ኤሌክትሪክ ዘርፍ የተመረቀው ወጣት ብሩክ ወንዲፍራው፣ የማይቻል የሚመስለውን በተግባር አሳይቷል።
ከዚህ ቀደም የተለያዩ የኢንዱስትሪ ማሽኖችን የሠራው ብሩክ፣ አሁን ደግሞ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ጥሬ ዕቃዎች የተሠራች ባለ አራት እግር መኪና ይፋ አድርጓል።
የተሽከርካሪዋ ልዩ መገለጫዎች
ሞተር
ባለ 300 ሲሲ (CC) ሞተር የተገጠመላት።
አቅም
በአንድ ጊዜ 4 ሰዎችን የመጫን አቅም ያላትና ከባጃጅ የተሻለ ፍጥነት የምትጓዝ።
ክብደት
ከ400 ኪሎ ግራም በላይ ክብደት አላት።
ወጪ
ለመሥራት ከ350 ሺህ ብር በላይ ወጪ ተደርጎባታል።
የብሩክ ትልቅ ራዕይ
የብሩክ ህልም መኪና ሠርቶ ማሳየት ብቻ አይደለም። በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ከውጭ የሚገቡ ተሽከርካሪዎችን በሀገር ውስጥ በጥራት ማምረት እና ለብዙ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር ነው። ድጋፍ ካገኘ ደግሞ በቀጣይ በኤሌክትሪክ የሚሠሩ ዘመናዊ ተሽከርካሪዎችን የማምረት ትልቅ ዕቅድ አለው።
የነገዋ ኢትዮጵያ ከመግዛት ወጥታ ወደ ማምረት የምትገባው በእንዲህ ያሉ ጀግኖች እጅ ነው።
#ቴዎድሮስ ደሴ ( አሚኮ)
#getu #innovationethiopia #bahirdar #techhero #madeinethiopia #engineeringexcellence #youthempowerment #ethiopiadecides #automotiveinnovation #ባሕርዳር #ፈጠራ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
5 months ago
ባሕርዳር ለአንጋፋው የጥበብ ሰው ግዮን ዓለምሰገድ የክብር እውቅና ሰጠች
#ethiopia | በኢትዮጵያ የቲያትርና የፊልም ጥበብ ውስጥ ጉልህ አሻራ ያሳረፈውና በትውልድ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ መፍጠር የቻለው አንጋፋው ተዋናይ ግዮን ዓለምሰገድ በባሕርዳር ከተማ ደማቅ የክብርና የእውቅና ተሰጥቷል።
በውቧ የጣና ዳርቻ ከተማ በተከናወነው በዚህ የክብር መርሀግብር ላይ በርካታ የኪነጥበብ ባለሙያዎች ወዳጅ ቤተሰብ በተገኙበት ለከያኒው የሚገባውን አክብሮት ተሰጥቷል።
አንጋፋው ባለቅኔና ደራሲ ጌትነት እንየው ለግዮን ዓለምሰገድ የክብር ካባ በማልበስ ለጥበብ የከፈለውን የሕይወት ዘመን መስዋዕትነት ዘክሯል።
ግዮን ዓለምሰገድ በመድረክ ላይ ያለውን ገጸ-ባህሪ በሕይወት የመሳል፣ የድምፅ አጠቃቀምና የሰውነት እንቅስቃሴን በተመጣጣኝ ሁኔታ የማዋሃድ ልዩ ክህሎቱ የሚታወቅ ሲሆን ከትወና ባለፈም ለወጣት ባለሙያዎች መንገድ አሳይና አስተማሪ በመሆን የዘርፉን ዕድገት ሲደግፍ የቆየ የጥበብ አውራ ነው።
ይህ በባሕርዳር ከተማ የተዘጋጀው የምስጋና መርሃ-ግብር እንዲሳካ ስንታየሁ ገብሩ፣ አበባው ደረበ ፣ ቻሌ ማረው ፣ ደሳለኝ ድረስ እና ሌሎች የጥበብ ጓደኞቹ ከባሕርዳር ጥበብ አፍቃሪዎች ጋር በመሆን ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል።
የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ "እንኳን ደስ አለህ" በማለት የማይተካና የማይደፈር የሙያ አበርክቶት እንዳለው ምስክርነታቸውን የሰጡ ሲሆን ይህ አይነቱ በሕይወት እያሉ የመከበር ባህል ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
ጌጡ ተመስገን (Getu Temesgen)
#gionalemseged #bahirdar #ethiopiantheatre #artrecognition #getnetenyew #ethiopianart #tana #lifetimeachievement #cinemaethiopia #culturalheritage
#ethiopia | በኢትዮጵያ የቲያትርና የፊልም ጥበብ ውስጥ ጉልህ አሻራ ያሳረፈውና በትውልድ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ መፍጠር የቻለው አንጋፋው ተዋናይ ግዮን ዓለምሰገድ በባሕርዳር ከተማ ደማቅ የክብርና የእውቅና ተሰጥቷል።
በውቧ የጣና ዳርቻ ከተማ በተከናወነው በዚህ የክብር መርሀግብር ላይ በርካታ የኪነጥበብ ባለሙያዎች ወዳጅ ቤተሰብ በተገኙበት ለከያኒው የሚገባውን አክብሮት ተሰጥቷል።
አንጋፋው ባለቅኔና ደራሲ ጌትነት እንየው ለግዮን ዓለምሰገድ የክብር ካባ በማልበስ ለጥበብ የከፈለውን የሕይወት ዘመን መስዋዕትነት ዘክሯል።
ግዮን ዓለምሰገድ በመድረክ ላይ ያለውን ገጸ-ባህሪ በሕይወት የመሳል፣ የድምፅ አጠቃቀምና የሰውነት እንቅስቃሴን በተመጣጣኝ ሁኔታ የማዋሃድ ልዩ ክህሎቱ የሚታወቅ ሲሆን ከትወና ባለፈም ለወጣት ባለሙያዎች መንገድ አሳይና አስተማሪ በመሆን የዘርፉን ዕድገት ሲደግፍ የቆየ የጥበብ አውራ ነው።
ይህ በባሕርዳር ከተማ የተዘጋጀው የምስጋና መርሃ-ግብር እንዲሳካ ስንታየሁ ገብሩ፣ አበባው ደረበ ፣ ቻሌ ማረው ፣ ደሳለኝ ድረስ እና ሌሎች የጥበብ ጓደኞቹ ከባሕርዳር ጥበብ አፍቃሪዎች ጋር በመሆን ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል።
የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ "እንኳን ደስ አለህ" በማለት የማይተካና የማይደፈር የሙያ አበርክቶት እንዳለው ምስክርነታቸውን የሰጡ ሲሆን ይህ አይነቱ በሕይወት እያሉ የመከበር ባህል ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
ጌጡ ተመስገን (Getu Temesgen)
#gionalemseged #bahirdar #ethiopiantheatre #artrecognition #getnetenyew #ethiopianart #tana #lifetimeachievement #cinemaethiopia #culturalheritage
5 months ago
ያከበሩት ያከብራል
በአርቲስት ግዮን ዓለምሰገድ የክብር ምሽት ነገ በባህር ዳር እንገናኝ
#ethiopia | የጥበብ ባለውለታዎችን ማክበርና እውቅና መስጠት የሰለጠነ ማህበረሰብ መገለጫ ነው። ነገ ቅዳሜ መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ "የግዮን መንገድ" የተሰኘ ልዩ የምስጋናና የእውቅና መርሃ-ግብር በደማቅ ሁኔታ ይካሄዳል።
የዕለቱ ተመስጋኝ፦
አርቲስት ግዮን ዓለምሰገድ
የዕለቱ የክብር እንግዳ፦
አንጋፋውና በቅርቡ ትልቅ ክብር የተሰጠው አርቲስት ጌትነት እንየው
ነገ ቅዳሜ፣ ከቀኑ 8:00 ሰዓት ጀምሮ
ባህር ዳር፣ ዩኒሰን ሆቴል
የጥበብ አፍቃሪዎችና የጥበብ ባለሙያዎች በዚህ ታሪካዊ ምሽት ላይ ተገኝታችሁ ለአርቲስት ግዮን ዓለምሰገድ ያላችሁን አክብሮት እንድትገልጹ ተጋብዛችኋል።
በባህር ዳር ዩኒሰን ሆቴል ነገ 8:00 ሰዓት ላይ ቀጠሯችን ይሁን!
#getu #ethiopia #bahirdar #art #tribute #gyionalemseged #getnetenyew #unisonhotel #የግዮንመንገድ #ባህርዳር #ጥበብ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
በአርቲስት ግዮን ዓለምሰገድ የክብር ምሽት ነገ በባህር ዳር እንገናኝ
#ethiopia | የጥበብ ባለውለታዎችን ማክበርና እውቅና መስጠት የሰለጠነ ማህበረሰብ መገለጫ ነው። ነገ ቅዳሜ መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ "የግዮን መንገድ" የተሰኘ ልዩ የምስጋናና የእውቅና መርሃ-ግብር በደማቅ ሁኔታ ይካሄዳል።
የዕለቱ ተመስጋኝ፦
አርቲስት ግዮን ዓለምሰገድ
የዕለቱ የክብር እንግዳ፦
አንጋፋውና በቅርቡ ትልቅ ክብር የተሰጠው አርቲስት ጌትነት እንየው
ነገ ቅዳሜ፣ ከቀኑ 8:00 ሰዓት ጀምሮ
ባህር ዳር፣ ዩኒሰን ሆቴል
የጥበብ አፍቃሪዎችና የጥበብ ባለሙያዎች በዚህ ታሪካዊ ምሽት ላይ ተገኝታችሁ ለአርቲስት ግዮን ዓለምሰገድ ያላችሁን አክብሮት እንድትገልጹ ተጋብዛችኋል።
በባህር ዳር ዩኒሰን ሆቴል ነገ 8:00 ሰዓት ላይ ቀጠሯችን ይሁን!
#getu #ethiopia #bahirdar #art #tribute #gyionalemseged #getnetenyew #unisonhotel #የግዮንመንገድ #ባህርዳር #ጥበብ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
5 months ago
“እንዛንታ” ትውፊታዊ ቲያትር ተመረቀ
#ethiopia | በባህር ዳር ከተማ በሚገኘው ሙሉዓለም የባህል ማዕከል፣ የኢትዮጵያን ጥንታዊ ትውፊትና የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎችን ጥበባዊ ታሪክ የሚዘክረው “እንዛንታ” የተሰኘው ትውፊታዊ ቲያትር በደመቀ ሁኔታ ተመርቋል።
በምረቃው መርሃ ግብር ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የጥበብ ባለሙያዎችና የኪነ-ጥበብ አፍቃሪዎች ተገኝተው የጥበብ ስራውን ተከታትለዋል።
በምረቃው ወቅት ንግግር ያደረጉት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የባህል፣ ኪነ-ጥበብና ዝክረ-ታሪክ ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ የሺ ካሳ፣ እንዲህ ያሉ ትውፊታዊ ስራዎች የህዝብን ታሪክና ማንነት ጠብቆ ለማቆየት ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።
ወይዘሮ የሺ አክለውም፣ “እንዛንታ” ቲያትር የክልሉን አልፎም የሀገሪቱን የቆዩ ባህላዊ እሴቶችና የአዝማሪዎችን የጥበብ ጉዞ ለዘመኑ ትውልድ በሚመጥን መልኩ ማቅረቡ ለዘርፉ ትልቅ እመርታ መሆኑን ጠቁመዋል። መንግስት እንዲህ ያሉ ማንነትን የሚገልጹ የጥበብ ስራዎች እንዲስፋፉና ለትውልድ እንዲሸጋገሩ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል የሙሉዓለም የባህል ማዕከል ምክትል ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገብረማርያም ይርጋ በበኩላቸው፣ ማዕከሉ የጥበብ ባለሙያዎች የፈጠራ ስራዎቻቸውን እንዲያቀርቡ ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። “እንዛንታ” ቲያትር በውስጡ የያዘው የታሪክ ጥልቀትና የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ጥበባዊ አበርክቶ፣ ማዕከሉ ለሚያከናውናቸው የባህልና የኪነ-ጥበብ ስራዎች እንደ ትልቅ ግብዓት የሚያገለግል መሆኑን አብራርተዋል።
አቶ ገብረማርያም አክለውም፣ ቲያትሩ መመረቁ ብቻ ሳይሆን በቀጣይም ለተመልካች ቀርቦ የባህል ግንባታ ስራውን እንዲያግዝ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል።
ይህ “እንዛንታ” የተሰኘው ትውፊታዊ ቲያትር በታሪክ አወቃቀሩና በአቀራረቡ የባህላዊ ኪነ-ጥበብን እሴት የጠበቀ ሲሆን፣ በተለይም ለጥበብ ስራው እንደ መነሻነት ያገለገሉት የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ታሪክ በጥልቀት የተዳሰሰበት ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#enzanta #barbakanazmaris #bahirdar #ethiopianculture #artdiscussion #mulualemhall #culturalheritage #ethiopiantheatre #traditionalart
#ethiopia | በባህር ዳር ከተማ በሚገኘው ሙሉዓለም የባህል ማዕከል፣ የኢትዮጵያን ጥንታዊ ትውፊትና የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎችን ጥበባዊ ታሪክ የሚዘክረው “እንዛንታ” የተሰኘው ትውፊታዊ ቲያትር በደመቀ ሁኔታ ተመርቋል።
በምረቃው መርሃ ግብር ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የጥበብ ባለሙያዎችና የኪነ-ጥበብ አፍቃሪዎች ተገኝተው የጥበብ ስራውን ተከታትለዋል።
በምረቃው ወቅት ንግግር ያደረጉት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የባህል፣ ኪነ-ጥበብና ዝክረ-ታሪክ ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ የሺ ካሳ፣ እንዲህ ያሉ ትውፊታዊ ስራዎች የህዝብን ታሪክና ማንነት ጠብቆ ለማቆየት ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።
ወይዘሮ የሺ አክለውም፣ “እንዛንታ” ቲያትር የክልሉን አልፎም የሀገሪቱን የቆዩ ባህላዊ እሴቶችና የአዝማሪዎችን የጥበብ ጉዞ ለዘመኑ ትውልድ በሚመጥን መልኩ ማቅረቡ ለዘርፉ ትልቅ እመርታ መሆኑን ጠቁመዋል። መንግስት እንዲህ ያሉ ማንነትን የሚገልጹ የጥበብ ስራዎች እንዲስፋፉና ለትውልድ እንዲሸጋገሩ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል የሙሉዓለም የባህል ማዕከል ምክትል ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገብረማርያም ይርጋ በበኩላቸው፣ ማዕከሉ የጥበብ ባለሙያዎች የፈጠራ ስራዎቻቸውን እንዲያቀርቡ ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። “እንዛንታ” ቲያትር በውስጡ የያዘው የታሪክ ጥልቀትና የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ጥበባዊ አበርክቶ፣ ማዕከሉ ለሚያከናውናቸው የባህልና የኪነ-ጥበብ ስራዎች እንደ ትልቅ ግብዓት የሚያገለግል መሆኑን አብራርተዋል።
አቶ ገብረማርያም አክለውም፣ ቲያትሩ መመረቁ ብቻ ሳይሆን በቀጣይም ለተመልካች ቀርቦ የባህል ግንባታ ስራውን እንዲያግዝ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል።
ይህ “እንዛንታ” የተሰኘው ትውፊታዊ ቲያትር በታሪክ አወቃቀሩና በአቀራረቡ የባህላዊ ኪነ-ጥበብን እሴት የጠበቀ ሲሆን፣ በተለይም ለጥበብ ስራው እንደ መነሻነት ያገለገሉት የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ታሪክ በጥልቀት የተዳሰሰበት ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#enzanta #barbakanazmaris #bahirdar #ethiopianculture #artdiscussion #mulualemhall #culturalheritage #ethiopiantheatre #traditionalart
5 months ago
የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ጥበባዊ አበርክቶና ተግዳሮቶች ላይ ያተኮረ የጥናት ውይይት ተካሄደ
#ethiopia | በባህር ዳር ከተማ በሚገኘው ሙሉዓለም የባህል ማዕከል ለ“እንዛንታ” ተውኔት እንደ ግብዓት በሆኑት የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ዙሪያ የሚያተኩር የጥናት ውይይት በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በመድረክ ላይ በዋናነት የአዝማሪነትን ሙያዊ እሴት፣ የታሪክ አወቃቀርና በዘርፉ ላይ የሚታዩ ተግዳሮቶችን በጥልቀት ለመመርመር ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
ይህ የጥናት መድረክ በተለይ ለ“እንዛንታ” ተውኔት ስኬት ትልቅ አስተዋጽኦ የነበራቸውን የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ታሪክና ጥበባዊ ጉዞ ለመዘከር እንደ መነሻ ተወስዷል።
በተጨማሪም በውይይቱ ወቅት የባህላዊ ኪነ-ጥበብን እሴት ሳይበረዝ ጠብቆ ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ በሚቻልባቸው ስልቶች ላይ ሰፊ ምክክር ተደርጓል። ይህም ጥበባዊ ቅርሳችንን ከዘመኑ ጋር አዋህዶ ለማስቀጠል የሚደረገውን ጥረት የሚያጠናክር መሆኑ ተገልጿል።
መርሃ ግብሩ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ባሕል፣ ኪነ-ጥበብና ዝክረ-ታሪክ ጽሕፈት ቤት አማካኝነት የተዘጋጀ ሲሆን፣ በውይይቱም ላይ የዘርፉ ባለሙያዎችና የጥበብ አፍቃሪዎች ተገኝተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#enzanta #barbakanazmaris #bahirdar #ethiopianculture #artdiscussion #mulualemhall #culturalheritage #ethiopiantheatre #traditionalart
#ethiopia | በባህር ዳር ከተማ በሚገኘው ሙሉዓለም የባህል ማዕከል ለ“እንዛንታ” ተውኔት እንደ ግብዓት በሆኑት የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ዙሪያ የሚያተኩር የጥናት ውይይት በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በመድረክ ላይ በዋናነት የአዝማሪነትን ሙያዊ እሴት፣ የታሪክ አወቃቀርና በዘርፉ ላይ የሚታዩ ተግዳሮቶችን በጥልቀት ለመመርመር ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
ይህ የጥናት መድረክ በተለይ ለ“እንዛንታ” ተውኔት ስኬት ትልቅ አስተዋጽኦ የነበራቸውን የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ታሪክና ጥበባዊ ጉዞ ለመዘከር እንደ መነሻ ተወስዷል።
በተጨማሪም በውይይቱ ወቅት የባህላዊ ኪነ-ጥበብን እሴት ሳይበረዝ ጠብቆ ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ በሚቻልባቸው ስልቶች ላይ ሰፊ ምክክር ተደርጓል። ይህም ጥበባዊ ቅርሳችንን ከዘመኑ ጋር አዋህዶ ለማስቀጠል የሚደረገውን ጥረት የሚያጠናክር መሆኑ ተገልጿል።
መርሃ ግብሩ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ባሕል፣ ኪነ-ጥበብና ዝክረ-ታሪክ ጽሕፈት ቤት አማካኝነት የተዘጋጀ ሲሆን፣ በውይይቱም ላይ የዘርፉ ባለሙያዎችና የጥበብ አፍቃሪዎች ተገኝተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#enzanta #barbakanazmaris #bahirdar #ethiopianculture #artdiscussion #mulualemhall #culturalheritage #ethiopiantheatre #traditionalart
Sponsored by
Surafel
5 months ago
🎭 "እንዝታ" ትውፊታዊ ቴአትር — በባህር ዳር!
#ethiopia | በታሪካዊ ትውፊት የተዋቀረውና በብዙዎች ዘንድ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው "እንዝታ" የተሰኘው ትውፊታዊ ቴአትር፣ ነገ መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በታላቅ ድምቀት ለእይታ ይቀርባል።
የጥበብ አፍቃሪዎች ሁሉ በዚህ ልዩ መድረክ ላይ እንዲገኙ ተጋብዘዋል።
የዝግጅቱ ቦታ እና ሰዓት
ቦታ፦ ባህር ዳር ከተማ፣ በሙሉዓለም ባሕል ማዕከል
ቀን፦ ነገ መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም
ደራሲያን፦
ደሳለኝ ድረስ (መረዋ) እና ንብረት ያለው
አዘጋጅ፦ አባይነህ በለጠ
ረዳት አዘጋጅ፦ ህሩይ አበበ
ፕሮዳክሽን ማናጀር፦ ይስማው ዮሐንስ
መብራት፦ ደጉ ሙልጌታ
ስፖት ላይት፦ መንግስቱ መኮንን
መድረክ ግንባታ፦ ሙልጌታ አለኸኝ
ድምጽ ግብዓት፦ በለጠ ወንዴ
አልባሳት እና ቁሳቁስ፦ የዝና አዱኛ
🎭 ተዋንያን
በርካታ ተሰጥኦ ያላቸው ተዋንያን በመድረኩ ላይ ይከሰታሉ፦
ግዮን አለምሰገድ፣ አሳሱሁ መንግሥቱ፣ ይታየው አንዴ፣ ያለምስራ ገድፍ፣ ጊዜኔው አዲስ፣ መማር አለባቸው፣ ስዩም መኮነን፣ አመልማል ተክሉ፣ ብርሃኑ ውብአየሁ፣ ተዋቸው ወረታው፣ አመለወርቅ ወንዲራድ፣ ማስተዋል አድማሱ፣ ይኽነው ባለህ እና ሌሎችም።
ፕሮዳክሽን
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ዝክረ ታሪክ ጽሕፈት ቤት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#enzita #traditionaltheatre #ethiopiantheatre #bahirdar #mulualemculturalcenter #amharaculture #ethiopianarts #ethiopianhistory #culturalheritage #bahirdarevents
#ethiopia | በታሪካዊ ትውፊት የተዋቀረውና በብዙዎች ዘንድ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው "እንዝታ" የተሰኘው ትውፊታዊ ቴአትር፣ ነገ መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በታላቅ ድምቀት ለእይታ ይቀርባል።
የጥበብ አፍቃሪዎች ሁሉ በዚህ ልዩ መድረክ ላይ እንዲገኙ ተጋብዘዋል።
የዝግጅቱ ቦታ እና ሰዓት
ቦታ፦ ባህር ዳር ከተማ፣ በሙሉዓለም ባሕል ማዕከል
ቀን፦ ነገ መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም
ደራሲያን፦
ደሳለኝ ድረስ (መረዋ) እና ንብረት ያለው
አዘጋጅ፦ አባይነህ በለጠ
ረዳት አዘጋጅ፦ ህሩይ አበበ
ፕሮዳክሽን ማናጀር፦ ይስማው ዮሐንስ
መብራት፦ ደጉ ሙልጌታ
ስፖት ላይት፦ መንግስቱ መኮንን
መድረክ ግንባታ፦ ሙልጌታ አለኸኝ
ድምጽ ግብዓት፦ በለጠ ወንዴ
አልባሳት እና ቁሳቁስ፦ የዝና አዱኛ
🎭 ተዋንያን
በርካታ ተሰጥኦ ያላቸው ተዋንያን በመድረኩ ላይ ይከሰታሉ፦
ግዮን አለምሰገድ፣ አሳሱሁ መንግሥቱ፣ ይታየው አንዴ፣ ያለምስራ ገድፍ፣ ጊዜኔው አዲስ፣ መማር አለባቸው፣ ስዩም መኮነን፣ አመልማል ተክሉ፣ ብርሃኑ ውብአየሁ፣ ተዋቸው ወረታው፣ አመለወርቅ ወንዲራድ፣ ማስተዋል አድማሱ፣ ይኽነው ባለህ እና ሌሎችም።
ፕሮዳክሽን
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ዝክረ ታሪክ ጽሕፈት ቤት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#enzita #traditionaltheatre #ethiopiantheatre #bahirdar #mulualemculturalcenter #amharaculture #ethiopianarts #ethiopianhistory #culturalheritage #bahirdarevents
5 months ago
⛪ የአዲስ ዘመን ደብረ ደናግል ቅድስት ሐናን አብረን እናልማ!
በዐቢይ ጾም ወቅት የሚደረግ ታላቅ የበረከት ጥሪ!
ጥንታዊቷና ታሪካዊቷ የአዲስ ዘመን ደብረ ደናግል ቅድስት ሐና ካቴድራል በ837 ዓ.ም የተመሠረተችና የታሪክ አሻራ ያረፈባት ቅድስት ስፍራ ናት።
በአሁኑ ወቅት ካቴድራሏን በራስ አገዝ ልማት በማጠናከር፣ ታላቅ የሃይማኖትና የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ ሰፊ የልማት እንቅስቃሴ እየተከናወነ ይገኛል።
ይህንን የተጀመረ የተቀደሰ የልማት ሥራ ዳር ለማድረስ፣ በመጪው እሁድ በሚካሄደው የገቢ ማሰባሰቢያና የወንጌል መርሃ-ግብር ላይ እንድትገኙ ጥሪ ቀርቦላችኋል።
እሁድ፣ መጋቢት 13 ቀን 2018 ዓ.ም.
ከጠዋቱ 7:30 ሰዓት ጀምሮ
*ባሕር ዳር፤ ሰላም አድርጊው ማርያም ቤተክርስቲያን።
የትምህርተ ወንጌል ስርጭት እና የልማት ገቢ ማሰባሰቢያ።
የበረከቱ ተካፋይ ለመሆን (ድጋፍ ለማድረግ)
በአካል መገኘት ለማትችሉና ከሩቅ ሆናችሁ ለእናታችን ለቅድስት ሐና ቤት አሻራችሁን ማሳረፍ ለምትፈልጉ ሁሉ፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
የአካውንት ቁጥር፦ 1000709139634
አዘጋጅ፦
የባሕር ዳር አስተባባሪ ኮሚቴ
✨ እኛም ለቤታችን፣ እኛም ለእናታችን!
ይህ ጥንታዊ ቅርስና መንፈሳዊ ማዕከል ተጠግኖና ለምቶ ለትውልድ እንዲተላለፍ የሚደረገው ጥረት የሁላችንንም እገዛ ይሻል።
በጾም ወቅት የሚደረግ ምጽዋትና በጎ ተግባር ደግሞ ድርብ በረከት አለው።
#ቅድስትሐና #አዲስዘመን #ባሕርዳር #ኢትዮጵያ #ኦርቶዶክስ #የበረከትጥሪ #ethiopia #sainthanna #addiszemen #bahirdar #cbe #getu #temesgen #getutemesgen #ጌጡ #ተመስገን #ጌጡተመስገን
በዐቢይ ጾም ወቅት የሚደረግ ታላቅ የበረከት ጥሪ!
ጥንታዊቷና ታሪካዊቷ የአዲስ ዘመን ደብረ ደናግል ቅድስት ሐና ካቴድራል በ837 ዓ.ም የተመሠረተችና የታሪክ አሻራ ያረፈባት ቅድስት ስፍራ ናት።
በአሁኑ ወቅት ካቴድራሏን በራስ አገዝ ልማት በማጠናከር፣ ታላቅ የሃይማኖትና የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ ሰፊ የልማት እንቅስቃሴ እየተከናወነ ይገኛል።
ይህንን የተጀመረ የተቀደሰ የልማት ሥራ ዳር ለማድረስ፣ በመጪው እሁድ በሚካሄደው የገቢ ማሰባሰቢያና የወንጌል መርሃ-ግብር ላይ እንድትገኙ ጥሪ ቀርቦላችኋል።
እሁድ፣ መጋቢት 13 ቀን 2018 ዓ.ም.
ከጠዋቱ 7:30 ሰዓት ጀምሮ
*ባሕር ዳር፤ ሰላም አድርጊው ማርያም ቤተክርስቲያን።
የትምህርተ ወንጌል ስርጭት እና የልማት ገቢ ማሰባሰቢያ።
የበረከቱ ተካፋይ ለመሆን (ድጋፍ ለማድረግ)
በአካል መገኘት ለማትችሉና ከሩቅ ሆናችሁ ለእናታችን ለቅድስት ሐና ቤት አሻራችሁን ማሳረፍ ለምትፈልጉ ሁሉ፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
የአካውንት ቁጥር፦ 1000709139634
አዘጋጅ፦
የባሕር ዳር አስተባባሪ ኮሚቴ
✨ እኛም ለቤታችን፣ እኛም ለእናታችን!
ይህ ጥንታዊ ቅርስና መንፈሳዊ ማዕከል ተጠግኖና ለምቶ ለትውልድ እንዲተላለፍ የሚደረገው ጥረት የሁላችንንም እገዛ ይሻል።
በጾም ወቅት የሚደረግ ምጽዋትና በጎ ተግባር ደግሞ ድርብ በረከት አለው።
#ቅድስትሐና #አዲስዘመን #ባሕርዳር #ኢትዮጵያ #ኦርቶዶክስ #የበረከትጥሪ #ethiopia #sainthanna #addiszemen #bahirdar #cbe #getu #temesgen #getutemesgen #ጌጡ #ተመስገን #ጌጡተመስገን
5 months ago
የበላይነህ ክንዴ ግሩፕ "ሂልተን ባህር ዳር" ግንባታ ተጠናክሮ ቀጥሏል
#ethiopia | ታዋቂው የንግድ ተቋም በላይነህ ክንዴ ግሩፕ (BKG) በአማራ ክልል ርዕሰ መዲና ባህር ዳር ከተማ እያስገነባ የሚገኘው የ"ሂልተን ባህር ዳር" ሆቴል ግንባታ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ። ግሩፑ ሆቴሉን በአጭር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት የሚያስችሉ የሥራ ሂደቶች ውጤት እያሳዩ መሆኑን ገልጿል።
የግሩፑ ተከታታይ ስኬቶች
በላይነህ ክንዴ ግሩፕ በኢንቨስትመንት ዘርፍ ያለውን ተነሳሽነት በተግባር እያሳየ የሚገኝ ሲሆን፣ በቅርቡ የሚከተሉትን መጠነ ሰፊ ፕሮጀክቶች መያዙ ይታወቃል፡
* ሎጎ ሀይቅ ሪዞርት፡ በቅርቡ ግንባታው በጥራትና በፍጥነት ተጠናቆ ለምረቃ የበቃው ይህ ሪዞርት፣ የግሩፑን የአፈጻጸም ብቃት ማሳያ ሆኗል።
* አዳማ ራስ ሆቴል፡ በባህር ዳሩ ፕሮጀክት ጎን ለጎን፣ በአዳማ ከተማ የሚገኘውን የአዳማ ራስ ሆቴል የማጠናቀቂያ ሥራዎችን በከፍተኛ ትኩረት እያከናወነ ይገኛል።
ይህ በባህር ዳር እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ሆቴል፣ ከተማዋ ያላትን የቱሪስት መስህብነት ይበልጥ ከማሳደጉም በላይ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiopia #bahirdar #hiltonbahirdar #aradafm #belaynehkindegroup #investment #tourismethiopia #development
#ethiopia | ታዋቂው የንግድ ተቋም በላይነህ ክንዴ ግሩፕ (BKG) በአማራ ክልል ርዕሰ መዲና ባህር ዳር ከተማ እያስገነባ የሚገኘው የ"ሂልተን ባህር ዳር" ሆቴል ግንባታ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ። ግሩፑ ሆቴሉን በአጭር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት የሚያስችሉ የሥራ ሂደቶች ውጤት እያሳዩ መሆኑን ገልጿል።
የግሩፑ ተከታታይ ስኬቶች
በላይነህ ክንዴ ግሩፕ በኢንቨስትመንት ዘርፍ ያለውን ተነሳሽነት በተግባር እያሳየ የሚገኝ ሲሆን፣ በቅርቡ የሚከተሉትን መጠነ ሰፊ ፕሮጀክቶች መያዙ ይታወቃል፡
* ሎጎ ሀይቅ ሪዞርት፡ በቅርቡ ግንባታው በጥራትና በፍጥነት ተጠናቆ ለምረቃ የበቃው ይህ ሪዞርት፣ የግሩፑን የአፈጻጸም ብቃት ማሳያ ሆኗል።
* አዳማ ራስ ሆቴል፡ በባህር ዳሩ ፕሮጀክት ጎን ለጎን፣ በአዳማ ከተማ የሚገኘውን የአዳማ ራስ ሆቴል የማጠናቀቂያ ሥራዎችን በከፍተኛ ትኩረት እያከናወነ ይገኛል።
ይህ በባህር ዳር እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ሆቴል፣ ከተማዋ ያላትን የቱሪስት መስህብነት ይበልጥ ከማሳደጉም በላይ ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiopia #bahirdar #hiltonbahirdar #aradafm #belaynehkindegroup #investment #tourismethiopia #development
6 months ago
🌿 እንኳን ለሰባር ጊዮርጊስ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! 🌿
"ባሕር ዳር በጊዮርጊስ በረከት ደምቃለች!"
በውቢቷ የባሕር ዳር ከተማ የሚከበረው የሰባር ጊዮርጊስ ዓመታዊ ክብረ በዓል በታላቅ ድምቀት እና መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓት እየተከናወነ ይገኛል።
🌊 ልዩ ድባብ:
በአባቶች ቡራኬ እና በያሬዳዊ ዜማ የታጀበው ይህ ክብረ በዓል፤ በተለይም በጣና ሐይቅ አካባቢ የተደረገው የመባረክ ሥርዓት ለበዓሉ ልዩ ድምቀት ሰጥቶታል።
አሁን ላይ ታቦተ ሕጉ በምእመናን አጀብ እና በዝማሬ ታጅቦ ወደ መንበሩ በመመለስ ላይ ይገኛል።
የሰባር ጊዮርጊስ ረድኤት እና በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን!
ለወዳጅዎ ሼር በማድረግ የበረከቱ ተካፋይ ያድርጉ።
#bahirdar #sebargiyorgis #orthodox #tana #ethiopia #saintgeorge #feast
"ባሕር ዳር በጊዮርጊስ በረከት ደምቃለች!"
በውቢቷ የባሕር ዳር ከተማ የሚከበረው የሰባር ጊዮርጊስ ዓመታዊ ክብረ በዓል በታላቅ ድምቀት እና መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓት እየተከናወነ ይገኛል።
🌊 ልዩ ድባብ:
በአባቶች ቡራኬ እና በያሬዳዊ ዜማ የታጀበው ይህ ክብረ በዓል፤ በተለይም በጣና ሐይቅ አካባቢ የተደረገው የመባረክ ሥርዓት ለበዓሉ ልዩ ድምቀት ሰጥቶታል።
አሁን ላይ ታቦተ ሕጉ በምእመናን አጀብ እና በዝማሬ ታጅቦ ወደ መንበሩ በመመለስ ላይ ይገኛል።
የሰባር ጊዮርጊስ ረድኤት እና በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን!
ለወዳጅዎ ሼር በማድረግ የበረከቱ ተካፋይ ያድርጉ።
#bahirdar #sebargiyorgis #orthodox #tana #ethiopia #saintgeorge #feast
Sponsored by
Surafel
6 months ago
🛶 የጣናዋ ንግሥት!
የ55 ዓመቷ "ታንኳ ቀዛፊ" እና የሁለት ጊዜ የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ! 🥇
#ethiopia | "ታንኳ ለኔ ሕይወት ነው! እህትና ወንድሞቼን ያሳደግኩበት፤ ልጄን ያስተማርኩበት ባለውለታዬ ነው" - ወ/ሮ ፀሐይነሽ ጀምበር
ባሕር ዳር ከምትታወቅባቸው ልዩ እሴቶች መካከል ከፓፒረስ (ደንገል) የሚሰራው "ታንኳ" አንዱ ነው። ታንኳ ለቱሪስቶች የፎቶ ጌጥ ቢሆንም፤ እንደ ወይዘሮ ፀሐይነሽ ጀምበር ላሉት ግን የሕይወት እስትንፋስ ነው።
የወይዘሮ ፀሐይነሽ አስደናቂ ታሪክ:
🌊 የልጅነት ሸክም:
ገና በ15 ዓመታቸው ወላጆቻቸውን በሞት ሲነጠቁ፤ ታንኳ እየቀዘፉ እንጨትና ጨፌ ወደ ባሕር ዳር በማጓጓዝ ታናናሽ ወንድም እና እህቶቻቸውን አሳድገዋል።
🌊 የቤተሰብ ምሰሶ:
ባለቤታቸውን በሞት ሲያጡም አልተሸነፉም! ጣናን እና አባይን እየገመሱ በአንዲት ልጃቸው ምክንያት ተስፋ ሳይቆርጡ ኑሮን አሸንፈዋል።
🌊 የውድድር ጀግና:
በባሕር ዳር ፌስቲባል ላይ በታንኳ ቀዘፋ ውድድር የሁለት ጊዜ (የአንደኝነት እና የሁለተኛነት) የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ ናቸው።
"ልጄ አንድ ቢሆንም ያለ ማንም እገዛ ትምህርት ቤት የሚመላለሰው ታንኳ እየቀዘፈ ነው" የሚሉት እኚህ ጠንካራ እናት፤ የታንኳ ቀዘፋ ሙያን ለትውልድ እያስተላለፉ ይገኛሉ።
የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደርም ታንኳን እንደ ብስክሌት የከተማዋ መለያ (Brand) ለማድረግ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።
ለእኚህ ጀግና እናት ክብር ይገባቸዋል! 👏❤️
ሮዛ የሻነህ (አሚኮ)
#bahirdar #laketana #tankua #strongwoman #ethiopianculture #tourism #amhara #inspiration
የ55 ዓመቷ "ታንኳ ቀዛፊ" እና የሁለት ጊዜ የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ! 🥇
#ethiopia | "ታንኳ ለኔ ሕይወት ነው! እህትና ወንድሞቼን ያሳደግኩበት፤ ልጄን ያስተማርኩበት ባለውለታዬ ነው" - ወ/ሮ ፀሐይነሽ ጀምበር
ባሕር ዳር ከምትታወቅባቸው ልዩ እሴቶች መካከል ከፓፒረስ (ደንገል) የሚሰራው "ታንኳ" አንዱ ነው። ታንኳ ለቱሪስቶች የፎቶ ጌጥ ቢሆንም፤ እንደ ወይዘሮ ፀሐይነሽ ጀምበር ላሉት ግን የሕይወት እስትንፋስ ነው።
የወይዘሮ ፀሐይነሽ አስደናቂ ታሪክ:
🌊 የልጅነት ሸክም:
ገና በ15 ዓመታቸው ወላጆቻቸውን በሞት ሲነጠቁ፤ ታንኳ እየቀዘፉ እንጨትና ጨፌ ወደ ባሕር ዳር በማጓጓዝ ታናናሽ ወንድም እና እህቶቻቸውን አሳድገዋል።
🌊 የቤተሰብ ምሰሶ:
ባለቤታቸውን በሞት ሲያጡም አልተሸነፉም! ጣናን እና አባይን እየገመሱ በአንዲት ልጃቸው ምክንያት ተስፋ ሳይቆርጡ ኑሮን አሸንፈዋል።
🌊 የውድድር ጀግና:
በባሕር ዳር ፌስቲባል ላይ በታንኳ ቀዘፋ ውድድር የሁለት ጊዜ (የአንደኝነት እና የሁለተኛነት) የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊ ናቸው።
"ልጄ አንድ ቢሆንም ያለ ማንም እገዛ ትምህርት ቤት የሚመላለሰው ታንኳ እየቀዘፈ ነው" የሚሉት እኚህ ጠንካራ እናት፤ የታንኳ ቀዘፋ ሙያን ለትውልድ እያስተላለፉ ይገኛሉ።
የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደርም ታንኳን እንደ ብስክሌት የከተማዋ መለያ (Brand) ለማድረግ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።
ለእኚህ ጀግና እናት ክብር ይገባቸዋል! 👏❤️
ሮዛ የሻነህ (አሚኮ)
#bahirdar #laketana #tankua #strongwoman #ethiopianculture #tourism #amhara #inspiration
Comments