26 days ago
“የንባብ ከተማ” የተሰኘ የህጻናት ቲያትር በድምቀት ተመረቀ
#ethiopia | የህፃናትን የንባብ ባህል ለማዳበር ታሳቢ ተደርጎ የተዘጋጀው “የንባብ ከተማ” የተሰኘው አዲስ የህፃናት ቴአትር ዛሬ ረፋድ ላይ ለእይታ በቃ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቲያትር ቤቶች አስተዳደር፣ የህጻናትን እና የወጣቶችን ጥበባዊ ተሰጥኦ ለማሳደግና ታሪክን ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማሸጋገር ዘመናዊ የቲያትር መድረኮችን በስፋት እየተጠቀመ ይገኛል።
የአዲስ አበባ ቲያትር ቤቶች አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተስፋገኘው ለገሠ እንደገለጹት፣ ከተማዋ ዘመናዊ የንባብና የመዝናኛ ቦታዎችን በመገንባት ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራች ነው።
በዚህም መሰረት በቅርቡ ተመርቆ አገልግሎት እየሰጠ በሚገኘው እና ፍላሚንጎ አካባቢ በሚገኘው የህጻናት እና ወጣቶች ቲያትር ቤት ለህጻናት የተዘጋጀ አዲስ ቲያትር በይፋ መመረቁን ጠቅሰው፣ ይህንን መድረክ ለታለመለት አላማ ሙሉ ለሙሉ ለመጠቀም እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
“የንባብ ከተማ” ቴአትር ከሚቀጥለው እሁድ ጀምሮ በቋሚነት ዘወትር እሁድ ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ ለታዳሚዎች እንደሚቀርብ ተገልጿል።
ለህፃናትና ለወላጆች ምቹ በሆነው በዚህ አዳራሽ፣ ከቴአትር በተጨማሪ ማራኪ ሙዚቃዎችና አስተማሪ የታሪክ መርሐግብሮች እንደሚኖሩት ተጠቁሟል።
ጌትነት ተመስገን
📷ከበደ መክብብ
#addisababa #theaterlife #culturalheritage #ethiopianarts #kidstheater #citydevelopment #performingarts #communityengagement
#ethiopia | የህፃናትን የንባብ ባህል ለማዳበር ታሳቢ ተደርጎ የተዘጋጀው “የንባብ ከተማ” የተሰኘው አዲስ የህፃናት ቴአትር ዛሬ ረፋድ ላይ ለእይታ በቃ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቲያትር ቤቶች አስተዳደር፣ የህጻናትን እና የወጣቶችን ጥበባዊ ተሰጥኦ ለማሳደግና ታሪክን ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማሸጋገር ዘመናዊ የቲያትር መድረኮችን በስፋት እየተጠቀመ ይገኛል።
የአዲስ አበባ ቲያትር ቤቶች አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተስፋገኘው ለገሠ እንደገለጹት፣ ከተማዋ ዘመናዊ የንባብና የመዝናኛ ቦታዎችን በመገንባት ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራች ነው።
በዚህም መሰረት በቅርቡ ተመርቆ አገልግሎት እየሰጠ በሚገኘው እና ፍላሚንጎ አካባቢ በሚገኘው የህጻናት እና ወጣቶች ቲያትር ቤት ለህጻናት የተዘጋጀ አዲስ ቲያትር በይፋ መመረቁን ጠቅሰው፣ ይህንን መድረክ ለታለመለት አላማ ሙሉ ለሙሉ ለመጠቀም እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።
“የንባብ ከተማ” ቴአትር ከሚቀጥለው እሁድ ጀምሮ በቋሚነት ዘወትር እሁድ ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ ለታዳሚዎች እንደሚቀርብ ተገልጿል።
ለህፃናትና ለወላጆች ምቹ በሆነው በዚህ አዳራሽ፣ ከቴአትር በተጨማሪ ማራኪ ሙዚቃዎችና አስተማሪ የታሪክ መርሐግብሮች እንደሚኖሩት ተጠቁሟል።
ጌትነት ተመስገን
📷ከበደ መክብብ
#addisababa #theaterlife #culturalheritage #ethiopianarts #kidstheater #citydevelopment #performingarts #communityengagement
5 months ago
ባሕርዳር ለአንጋፋው የጥበብ ሰው ግዮን ዓለምሰገድ የክብር እውቅና ሰጠች
#ethiopia | በኢትዮጵያ የቲያትርና የፊልም ጥበብ ውስጥ ጉልህ አሻራ ያሳረፈውና በትውልድ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ መፍጠር የቻለው አንጋፋው ተዋናይ ግዮን ዓለምሰገድ በባሕርዳር ከተማ ደማቅ የክብርና የእውቅና ተሰጥቷል።
በውቧ የጣና ዳርቻ ከተማ በተከናወነው በዚህ የክብር መርሀግብር ላይ በርካታ የኪነጥበብ ባለሙያዎች ወዳጅ ቤተሰብ በተገኙበት ለከያኒው የሚገባውን አክብሮት ተሰጥቷል።
አንጋፋው ባለቅኔና ደራሲ ጌትነት እንየው ለግዮን ዓለምሰገድ የክብር ካባ በማልበስ ለጥበብ የከፈለውን የሕይወት ዘመን መስዋዕትነት ዘክሯል።
ግዮን ዓለምሰገድ በመድረክ ላይ ያለውን ገጸ-ባህሪ በሕይወት የመሳል፣ የድምፅ አጠቃቀምና የሰውነት እንቅስቃሴን በተመጣጣኝ ሁኔታ የማዋሃድ ልዩ ክህሎቱ የሚታወቅ ሲሆን ከትወና ባለፈም ለወጣት ባለሙያዎች መንገድ አሳይና አስተማሪ በመሆን የዘርፉን ዕድገት ሲደግፍ የቆየ የጥበብ አውራ ነው።
ይህ በባሕርዳር ከተማ የተዘጋጀው የምስጋና መርሃ-ግብር እንዲሳካ ስንታየሁ ገብሩ፣ አበባው ደረበ ፣ ቻሌ ማረው ፣ ደሳለኝ ድረስ እና ሌሎች የጥበብ ጓደኞቹ ከባሕርዳር ጥበብ አፍቃሪዎች ጋር በመሆን ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል።
የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ "እንኳን ደስ አለህ" በማለት የማይተካና የማይደፈር የሙያ አበርክቶት እንዳለው ምስክርነታቸውን የሰጡ ሲሆን ይህ አይነቱ በሕይወት እያሉ የመከበር ባህል ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
ጌጡ ተመስገን (Getu Temesgen)
#gionalemseged #bahirdar #ethiopiantheatre #artrecognition #getnetenyew #ethiopianart #tana #lifetimeachievement #cinemaethiopia #culturalheritage
#ethiopia | በኢትዮጵያ የቲያትርና የፊልም ጥበብ ውስጥ ጉልህ አሻራ ያሳረፈውና በትውልድ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ መፍጠር የቻለው አንጋፋው ተዋናይ ግዮን ዓለምሰገድ በባሕርዳር ከተማ ደማቅ የክብርና የእውቅና ተሰጥቷል።
በውቧ የጣና ዳርቻ ከተማ በተከናወነው በዚህ የክብር መርሀግብር ላይ በርካታ የኪነጥበብ ባለሙያዎች ወዳጅ ቤተሰብ በተገኙበት ለከያኒው የሚገባውን አክብሮት ተሰጥቷል።
አንጋፋው ባለቅኔና ደራሲ ጌትነት እንየው ለግዮን ዓለምሰገድ የክብር ካባ በማልበስ ለጥበብ የከፈለውን የሕይወት ዘመን መስዋዕትነት ዘክሯል።
ግዮን ዓለምሰገድ በመድረክ ላይ ያለውን ገጸ-ባህሪ በሕይወት የመሳል፣ የድምፅ አጠቃቀምና የሰውነት እንቅስቃሴን በተመጣጣኝ ሁኔታ የማዋሃድ ልዩ ክህሎቱ የሚታወቅ ሲሆን ከትወና ባለፈም ለወጣት ባለሙያዎች መንገድ አሳይና አስተማሪ በመሆን የዘርፉን ዕድገት ሲደግፍ የቆየ የጥበብ አውራ ነው።
ይህ በባሕርዳር ከተማ የተዘጋጀው የምስጋና መርሃ-ግብር እንዲሳካ ስንታየሁ ገብሩ፣ አበባው ደረበ ፣ ቻሌ ማረው ፣ ደሳለኝ ድረስ እና ሌሎች የጥበብ ጓደኞቹ ከባሕርዳር ጥበብ አፍቃሪዎች ጋር በመሆን ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል።
የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ "እንኳን ደስ አለህ" በማለት የማይተካና የማይደፈር የሙያ አበርክቶት እንዳለው ምስክርነታቸውን የሰጡ ሲሆን ይህ አይነቱ በሕይወት እያሉ የመከበር ባህል ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
ጌጡ ተመስገን (Getu Temesgen)
#gionalemseged #bahirdar #ethiopiantheatre #artrecognition #getnetenyew #ethiopianart #tana #lifetimeachievement #cinemaethiopia #culturalheritage
5 months ago
“እንዛንታ” ትውፊታዊ ቲያትር ተመረቀ
#ethiopia | በባህር ዳር ከተማ በሚገኘው ሙሉዓለም የባህል ማዕከል፣ የኢትዮጵያን ጥንታዊ ትውፊትና የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎችን ጥበባዊ ታሪክ የሚዘክረው “እንዛንታ” የተሰኘው ትውፊታዊ ቲያትር በደመቀ ሁኔታ ተመርቋል።
በምረቃው መርሃ ግብር ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የጥበብ ባለሙያዎችና የኪነ-ጥበብ አፍቃሪዎች ተገኝተው የጥበብ ስራውን ተከታትለዋል።
በምረቃው ወቅት ንግግር ያደረጉት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የባህል፣ ኪነ-ጥበብና ዝክረ-ታሪክ ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ የሺ ካሳ፣ እንዲህ ያሉ ትውፊታዊ ስራዎች የህዝብን ታሪክና ማንነት ጠብቆ ለማቆየት ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።
ወይዘሮ የሺ አክለውም፣ “እንዛንታ” ቲያትር የክልሉን አልፎም የሀገሪቱን የቆዩ ባህላዊ እሴቶችና የአዝማሪዎችን የጥበብ ጉዞ ለዘመኑ ትውልድ በሚመጥን መልኩ ማቅረቡ ለዘርፉ ትልቅ እመርታ መሆኑን ጠቁመዋል። መንግስት እንዲህ ያሉ ማንነትን የሚገልጹ የጥበብ ስራዎች እንዲስፋፉና ለትውልድ እንዲሸጋገሩ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል የሙሉዓለም የባህል ማዕከል ምክትል ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገብረማርያም ይርጋ በበኩላቸው፣ ማዕከሉ የጥበብ ባለሙያዎች የፈጠራ ስራዎቻቸውን እንዲያቀርቡ ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። “እንዛንታ” ቲያትር በውስጡ የያዘው የታሪክ ጥልቀትና የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ጥበባዊ አበርክቶ፣ ማዕከሉ ለሚያከናውናቸው የባህልና የኪነ-ጥበብ ስራዎች እንደ ትልቅ ግብዓት የሚያገለግል መሆኑን አብራርተዋል።
አቶ ገብረማርያም አክለውም፣ ቲያትሩ መመረቁ ብቻ ሳይሆን በቀጣይም ለተመልካች ቀርቦ የባህል ግንባታ ስራውን እንዲያግዝ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል።
ይህ “እንዛንታ” የተሰኘው ትውፊታዊ ቲያትር በታሪክ አወቃቀሩና በአቀራረቡ የባህላዊ ኪነ-ጥበብን እሴት የጠበቀ ሲሆን፣ በተለይም ለጥበብ ስራው እንደ መነሻነት ያገለገሉት የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ታሪክ በጥልቀት የተዳሰሰበት ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#enzanta #barbakanazmaris #bahirdar #ethiopianculture #artdiscussion #mulualemhall #culturalheritage #ethiopiantheatre #traditionalart
#ethiopia | በባህር ዳር ከተማ በሚገኘው ሙሉዓለም የባህል ማዕከል፣ የኢትዮጵያን ጥንታዊ ትውፊትና የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎችን ጥበባዊ ታሪክ የሚዘክረው “እንዛንታ” የተሰኘው ትውፊታዊ ቲያትር በደመቀ ሁኔታ ተመርቋል።
በምረቃው መርሃ ግብር ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የጥበብ ባለሙያዎችና የኪነ-ጥበብ አፍቃሪዎች ተገኝተው የጥበብ ስራውን ተከታትለዋል።
በምረቃው ወቅት ንግግር ያደረጉት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የባህል፣ ኪነ-ጥበብና ዝክረ-ታሪክ ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ ወይዘሮ የሺ ካሳ፣ እንዲህ ያሉ ትውፊታዊ ስራዎች የህዝብን ታሪክና ማንነት ጠብቆ ለማቆየት ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።
ወይዘሮ የሺ አክለውም፣ “እንዛንታ” ቲያትር የክልሉን አልፎም የሀገሪቱን የቆዩ ባህላዊ እሴቶችና የአዝማሪዎችን የጥበብ ጉዞ ለዘመኑ ትውልድ በሚመጥን መልኩ ማቅረቡ ለዘርፉ ትልቅ እመርታ መሆኑን ጠቁመዋል። መንግስት እንዲህ ያሉ ማንነትን የሚገልጹ የጥበብ ስራዎች እንዲስፋፉና ለትውልድ እንዲሸጋገሩ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል የሙሉዓለም የባህል ማዕከል ምክትል ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገብረማርያም ይርጋ በበኩላቸው፣ ማዕከሉ የጥበብ ባለሙያዎች የፈጠራ ስራዎቻቸውን እንዲያቀርቡ ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። “እንዛንታ” ቲያትር በውስጡ የያዘው የታሪክ ጥልቀትና የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ጥበባዊ አበርክቶ፣ ማዕከሉ ለሚያከናውናቸው የባህልና የኪነ-ጥበብ ስራዎች እንደ ትልቅ ግብዓት የሚያገለግል መሆኑን አብራርተዋል።
አቶ ገብረማርያም አክለውም፣ ቲያትሩ መመረቁ ብቻ ሳይሆን በቀጣይም ለተመልካች ቀርቦ የባህል ግንባታ ስራውን እንዲያግዝ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል።
ይህ “እንዛንታ” የተሰኘው ትውፊታዊ ቲያትር በታሪክ አወቃቀሩና በአቀራረቡ የባህላዊ ኪነ-ጥበብን እሴት የጠበቀ ሲሆን፣ በተለይም ለጥበብ ስራው እንደ መነሻነት ያገለገሉት የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ታሪክ በጥልቀት የተዳሰሰበት ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#enzanta #barbakanazmaris #bahirdar #ethiopianculture #artdiscussion #mulualemhall #culturalheritage #ethiopiantheatre #traditionalart
5 months ago
የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ጥበባዊ አበርክቶና ተግዳሮቶች ላይ ያተኮረ የጥናት ውይይት ተካሄደ
#ethiopia | በባህር ዳር ከተማ በሚገኘው ሙሉዓለም የባህል ማዕከል ለ“እንዛንታ” ተውኔት እንደ ግብዓት በሆኑት የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ዙሪያ የሚያተኩር የጥናት ውይይት በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በመድረክ ላይ በዋናነት የአዝማሪነትን ሙያዊ እሴት፣ የታሪክ አወቃቀርና በዘርፉ ላይ የሚታዩ ተግዳሮቶችን በጥልቀት ለመመርመር ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
ይህ የጥናት መድረክ በተለይ ለ“እንዛንታ” ተውኔት ስኬት ትልቅ አስተዋጽኦ የነበራቸውን የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ታሪክና ጥበባዊ ጉዞ ለመዘከር እንደ መነሻ ተወስዷል።
በተጨማሪም በውይይቱ ወቅት የባህላዊ ኪነ-ጥበብን እሴት ሳይበረዝ ጠብቆ ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ በሚቻልባቸው ስልቶች ላይ ሰፊ ምክክር ተደርጓል። ይህም ጥበባዊ ቅርሳችንን ከዘመኑ ጋር አዋህዶ ለማስቀጠል የሚደረገውን ጥረት የሚያጠናክር መሆኑ ተገልጿል።
መርሃ ግብሩ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ባሕል፣ ኪነ-ጥበብና ዝክረ-ታሪክ ጽሕፈት ቤት አማካኝነት የተዘጋጀ ሲሆን፣ በውይይቱም ላይ የዘርፉ ባለሙያዎችና የጥበብ አፍቃሪዎች ተገኝተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#enzanta #barbakanazmaris #bahirdar #ethiopianculture #artdiscussion #mulualemhall #culturalheritage #ethiopiantheatre #traditionalart
#ethiopia | በባህር ዳር ከተማ በሚገኘው ሙሉዓለም የባህል ማዕከል ለ“እንዛንታ” ተውኔት እንደ ግብዓት በሆኑት የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ዙሪያ የሚያተኩር የጥናት ውይይት በመካሄድ ላይ ይገኛል።
በመድረክ ላይ በዋናነት የአዝማሪነትን ሙያዊ እሴት፣ የታሪክ አወቃቀርና በዘርፉ ላይ የሚታዩ ተግዳሮቶችን በጥልቀት ለመመርመር ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
ይህ የጥናት መድረክ በተለይ ለ“እንዛንታ” ተውኔት ስኬት ትልቅ አስተዋጽኦ የነበራቸውን የ“ብርቧክስ” አዝማሪዎች ታሪክና ጥበባዊ ጉዞ ለመዘከር እንደ መነሻ ተወስዷል።
በተጨማሪም በውይይቱ ወቅት የባህላዊ ኪነ-ጥበብን እሴት ሳይበረዝ ጠብቆ ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ በሚቻልባቸው ስልቶች ላይ ሰፊ ምክክር ተደርጓል። ይህም ጥበባዊ ቅርሳችንን ከዘመኑ ጋር አዋህዶ ለማስቀጠል የሚደረገውን ጥረት የሚያጠናክር መሆኑ ተገልጿል።
መርሃ ግብሩ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ባሕል፣ ኪነ-ጥበብና ዝክረ-ታሪክ ጽሕፈት ቤት አማካኝነት የተዘጋጀ ሲሆን፣ በውይይቱም ላይ የዘርፉ ባለሙያዎችና የጥበብ አፍቃሪዎች ተገኝተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#enzanta #barbakanazmaris #bahirdar #ethiopianculture #artdiscussion #mulualemhall #culturalheritage #ethiopiantheatre #traditionalart
5 months ago
🎭 "እንዝታ" ትውፊታዊ ቴአትር — በባህር ዳር!
#ethiopia | በታሪካዊ ትውፊት የተዋቀረውና በብዙዎች ዘንድ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው "እንዝታ" የተሰኘው ትውፊታዊ ቴአትር፣ ነገ መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በታላቅ ድምቀት ለእይታ ይቀርባል።
የጥበብ አፍቃሪዎች ሁሉ በዚህ ልዩ መድረክ ላይ እንዲገኙ ተጋብዘዋል።
የዝግጅቱ ቦታ እና ሰዓት
ቦታ፦ ባህር ዳር ከተማ፣ በሙሉዓለም ባሕል ማዕከል
ቀን፦ ነገ መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም
ደራሲያን፦
ደሳለኝ ድረስ (መረዋ) እና ንብረት ያለው
አዘጋጅ፦ አባይነህ በለጠ
ረዳት አዘጋጅ፦ ህሩይ አበበ
ፕሮዳክሽን ማናጀር፦ ይስማው ዮሐንስ
መብራት፦ ደጉ ሙልጌታ
ስፖት ላይት፦ መንግስቱ መኮንን
መድረክ ግንባታ፦ ሙልጌታ አለኸኝ
ድምጽ ግብዓት፦ በለጠ ወንዴ
አልባሳት እና ቁሳቁስ፦ የዝና አዱኛ
🎭 ተዋንያን
በርካታ ተሰጥኦ ያላቸው ተዋንያን በመድረኩ ላይ ይከሰታሉ፦
ግዮን አለምሰገድ፣ አሳሱሁ መንግሥቱ፣ ይታየው አንዴ፣ ያለምስራ ገድፍ፣ ጊዜኔው አዲስ፣ መማር አለባቸው፣ ስዩም መኮነን፣ አመልማል ተክሉ፣ ብርሃኑ ውብአየሁ፣ ተዋቸው ወረታው፣ አመለወርቅ ወንዲራድ፣ ማስተዋል አድማሱ፣ ይኽነው ባለህ እና ሌሎችም።
ፕሮዳክሽን
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ዝክረ ታሪክ ጽሕፈት ቤት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#enzita #traditionaltheatre #ethiopiantheatre #bahirdar #mulualemculturalcenter #amharaculture #ethiopianarts #ethiopianhistory #culturalheritage #bahirdarevents
#ethiopia | በታሪካዊ ትውፊት የተዋቀረውና በብዙዎች ዘንድ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው "እንዝታ" የተሰኘው ትውፊታዊ ቴአትር፣ ነገ መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም በታላቅ ድምቀት ለእይታ ይቀርባል።
የጥበብ አፍቃሪዎች ሁሉ በዚህ ልዩ መድረክ ላይ እንዲገኙ ተጋብዘዋል።
የዝግጅቱ ቦታ እና ሰዓት
ቦታ፦ ባህር ዳር ከተማ፣ በሙሉዓለም ባሕል ማዕከል
ቀን፦ ነገ መጋቢት 6 ቀን 2018 ዓ.ም
ደራሲያን፦
ደሳለኝ ድረስ (መረዋ) እና ንብረት ያለው
አዘጋጅ፦ አባይነህ በለጠ
ረዳት አዘጋጅ፦ ህሩይ አበበ
ፕሮዳክሽን ማናጀር፦ ይስማው ዮሐንስ
መብራት፦ ደጉ ሙልጌታ
ስፖት ላይት፦ መንግስቱ መኮንን
መድረክ ግንባታ፦ ሙልጌታ አለኸኝ
ድምጽ ግብዓት፦ በለጠ ወንዴ
አልባሳት እና ቁሳቁስ፦ የዝና አዱኛ
🎭 ተዋንያን
በርካታ ተሰጥኦ ያላቸው ተዋንያን በመድረኩ ላይ ይከሰታሉ፦
ግዮን አለምሰገድ፣ አሳሱሁ መንግሥቱ፣ ይታየው አንዴ፣ ያለምስራ ገድፍ፣ ጊዜኔው አዲስ፣ መማር አለባቸው፣ ስዩም መኮነን፣ አመልማል ተክሉ፣ ብርሃኑ ውብአየሁ፣ ተዋቸው ወረታው፣ አመለወርቅ ወንዲራድ፣ ማስተዋል አድማሱ፣ ይኽነው ባለህ እና ሌሎችም።
ፕሮዳክሽን
የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ዝክረ ታሪክ ጽሕፈት ቤት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#enzita #traditionaltheatre #ethiopiantheatre #bahirdar #mulualemculturalcenter #amharaculture #ethiopianarts #ethiopianhistory #culturalheritage #bahirdarevents
Sponsored by
Surafel
7 months ago
የታሪክና የማንነት ጥሪ ከከረዩ ምድር❤
#ethiopia | የኩራትና የጥንታዊው የገዳ ሥርዓት መገለጫ የሆነው ታላቁ የከረዩ "ሚቺሌ ገዳ" የቡታ ሥነ-ሥርዓት እሁድ ታህሳስ 26እና 27 በድምቀት ይከበራል!
፨የከረዩ ገዳ ስርዓት፨
የከረዩ ገዳ ስልጣን ሽግግር፦ የጥበብ፣ የልምድ ልውውጥና የዲሞክራሲ ተምሳሌት!
በኢትዮጵያ ቀደምት ታሪክና ባህል ውስጥ ስር የሰደደው የከረዩ ኦሮሞ የገዳ ስልጣን ሽግግር ስነ-ስርዓት ዛሬ በደመቀ ሁኔታ ተጀምሯል። ይህ ለሁለት ሳምንታት የሚዘልቀው ታላቅ ክውን ልዩ የሚያደርገው አንድ ድንቅ ጥበብ አለው፤ እርሱም "የስልጣን መጋራት" ነው።
የከረዩ ገዳ ስርዓት፦ በቡታ ቀላ ስነ-ስርዓት የታሪክና የወግ ትውስታ
የከረዩ ኦሮሞ ህዝብ የ"ቱታ ገዳ ሚቺሌ" ለገዳ ስርዓት እጅግ ቅዱስና ትርጉም ያለው "የቡታ ቀላ" ስነ-ስርዓትን ለማከናወን በሚያደርገው ዝግጅት፤ የራሱን ጥንታዊና ተወላጅ የዲሞክራሲ ስርዓት ጥንካሬ፣ ጽናትና ቀጣይነት በድጋሚ እያረጋገጠ ይገኛል።
ባለፉት ስድስት ዓመታት የገዳ ስልጣንን (ባሊ) በታማኝነት ሲመራ የቆየው የ"ገዳ ሚቺሌ" ትውልድ፣ አሁን ላይ ወሳኝ ወደሆነው የሽግግር ስነ-ስርዓት ምዕራፍ ተሸጋግሯል። ይህ የ"ቡጣ ቀሉ" ስነ-ስርዓት ያለፈውን የአመራር ዘመን መቃኛና ራስን የማደሻ ወቅት ሲሆን፤ በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ሙሉ ስልጣኑን ለሚረከበው ቀጣዩ የገዳ ተረኛ ቡድን ስልጣኑ በሰላም እንዲሸጋገር መሰረት የሚጣልበት ታሪካዊ ክውን ነው።
"ቡጣ ቀሉ" ከመደበኛ ስነ-ስርዓት ባለፈ ተጠያቂነትን፣ የአመራር ቀጣይነትንና ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚሸጋገር መሪነትን የሚወክል ታላቅ ምልክት ነው። ይህም የኦሮሞ ህዝብ ለዲሞክራሲያዊ አስተዳደር፣ ለባህላዊ ማንነትና ለማህበራዊ ስምምነት ያለውን ጥልቅ ቁርጠኝነት የሚያንጸባርቅ ሲሆን፤ እነዚህ እሴቶች የገዳ ስርዓት ለዘመናት ጸንቶ እንዲቆይ ያደረጉ ምሰሶዎች ናቸው።
የከረዩ ማህበረሰብ ለዚህ ታሪካዊ ክስተት በሚዘጋጅበት በዚህ ወቅት፣ ስነ-ስርዓቱ የኦሮሞ ባህል ምን ያህል ጠንካራ መሆኑንና ለሰላም፣ ለአንድነት እንዲሁም ለመልካም አስተዳደር እያበረከተ ያለውን ዘላቂ አስተዋጽኦ ለዓለም የሚያሳይ ህያው ምስክር ነው።
ይህ በሀገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚዲያ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ድንቅ የዲሞክራሲ ትምህርት ቤትም ነው። ይህንን ታሪካዊ ኩነት በቦታው ተገኝታችሁ ለዓለም ለማስተዋወቅ ለምትተጉ በሙሉ ትልቅ ምስጋና ይገባችኋል!
ይህ በዓል የከረዩ ኦሮሞዎች ለዘመናት የጠበቁት፣ ማንነታቸውንና ባህላቸውን ለዓለም የሚያሳዩበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው። ዓመታት ዓመታትን እየተኩ፤ የአባቶቸው ፈር ሳይለቁ የደረሱት የከረዩ አባቶች፣ ዛሬም በኩራት ወደ አባቶቻችን በታሪካዊ መሬት ይጠሩናል።
ሁላችንም በቦታው በመገኘት ባህላቸውን እና ታሪካቸውን እንካፈል!
#ባህላችን የማንነታችን ነፀብራቅ ነው!,የከረዩ ገዳ በዓል፦ የቡታ ሰርግ እና የጎባ (ሥልጣን) ርክክብ!!
የከረዩ ኦሮሞ ጠንካራ ታሪክ፣ ባህል እና የገዳ ሥርዓት ያለው ማህበረሰብ ነው። ይህ በዓል የአንድነቱ፣ የጀግንነቱ እና የማንነቱ መገለጫ ነው።
የመከበሪያ ቦታ፦ ተሬ ሌዲ (Tarree Leedii) የሚጪሌ ገዳ የሥርዓት አፈፃፀም መርሃ ግብር (ከታህሳስ 16 - 26)
ከታህሳስ 16/2018ዓ.ም ጀምሮ የሚጪሌ ገዳ አባላት ተሬ ሌዲ ላይ ሠፍረዋል።
በአባ ቦኩ አዳራሽ (ጋልማ) ውስጥ እሳት ይለኩሳሉ።
የምርቃት እና የአርዳጋ (የመስዋዕት) ሥነ-ሥርዓት ያከናውናሉ።
ግመሎችን በታላቅነት ቅደም ተከተል ይፈታሉ።
ሁፌና ተራራ ላይ የከተሪ እንጨት ያቃጥላሉ፣ ኮርማም ያርዳሉ።
2. የከራ (የደጅ) ሥነ-ሥርዓት (ታህሳስ 17)፦
በአባ ቦኩ ደጅ ላይ ዱላቻ (ጥቁር ላም) ያርዳሉ።
ለአባ ቦኩ እሳት እና ለአርዳጋው ጠባቂዎችን ይመድባሉ።
3. አዳራሽ መገንባት (ታህሳስ 18 - 20)፦
የአባ ቦኩን አዳራሽ (ጋልማ) ይገነባሉ።
የእንግዳ ማረፊያ (ዳሳ)፣ የላም እና የግመል በረት ይሠራሉ።
4. ፀሎት እና ውይይት (ታህሳስ 20 - 25)፦
ወደ ተራራ እና ወደ ወንዝ በመሄድ አምላክን (ዋቃን) ሰላም እንዲሰጣቸው ይለምናሉ።
ስለ ገዳው እና ስለ እንግዶች አቀባበል ልዩ ልዩ ውይይቶችን (ገሪ) ያደርጋሉ።
የአካባቢውን ሰላም የሚያውጅ አዋጅ ያውጃሉ።
5. የማጠቃለያ ቀን (ታህሳስ 26)፦
ረፋድ፦ ሂዲ (ለሥርዓቱ የሚፈለግ ዕቃ) ያዘጋጃሉ፣ ቢቲማ (የኋላ ደጅ) ይገነባሉ።
ከሰዓት በኋላ፦ የጋልማው አባት (አባ ጋልማ) ገቢ የሚያመጡ ሰዎችን ይቀበላሉ።
ምሽት፦ የቡታ ሰርግ ሥነ-ሥርዓት ሳይመሽ ይጀመራል።
ማጠቃለያ፦
ታህሳስ 27 ቀን የባሊ (የሥልጣን) ርክክብ ወይም የጎባ ሥነ-ሥርዓት በመከናወን በዓሉ ይጠናቀቃል።
በሄሎ መተሐራ
#fentale #metahara #kereyu #gada #oromia #culturalheritage #oromia Culture and Tourism Bureau #oromia Tourism Commission
#ethiopia | የኩራትና የጥንታዊው የገዳ ሥርዓት መገለጫ የሆነው ታላቁ የከረዩ "ሚቺሌ ገዳ" የቡታ ሥነ-ሥርዓት እሁድ ታህሳስ 26እና 27 በድምቀት ይከበራል!
፨የከረዩ ገዳ ስርዓት፨
የከረዩ ገዳ ስልጣን ሽግግር፦ የጥበብ፣ የልምድ ልውውጥና የዲሞክራሲ ተምሳሌት!
በኢትዮጵያ ቀደምት ታሪክና ባህል ውስጥ ስር የሰደደው የከረዩ ኦሮሞ የገዳ ስልጣን ሽግግር ስነ-ስርዓት ዛሬ በደመቀ ሁኔታ ተጀምሯል። ይህ ለሁለት ሳምንታት የሚዘልቀው ታላቅ ክውን ልዩ የሚያደርገው አንድ ድንቅ ጥበብ አለው፤ እርሱም "የስልጣን መጋራት" ነው።
የከረዩ ገዳ ስርዓት፦ በቡታ ቀላ ስነ-ስርዓት የታሪክና የወግ ትውስታ
የከረዩ ኦሮሞ ህዝብ የ"ቱታ ገዳ ሚቺሌ" ለገዳ ስርዓት እጅግ ቅዱስና ትርጉም ያለው "የቡታ ቀላ" ስነ-ስርዓትን ለማከናወን በሚያደርገው ዝግጅት፤ የራሱን ጥንታዊና ተወላጅ የዲሞክራሲ ስርዓት ጥንካሬ፣ ጽናትና ቀጣይነት በድጋሚ እያረጋገጠ ይገኛል።
ባለፉት ስድስት ዓመታት የገዳ ስልጣንን (ባሊ) በታማኝነት ሲመራ የቆየው የ"ገዳ ሚቺሌ" ትውልድ፣ አሁን ላይ ወሳኝ ወደሆነው የሽግግር ስነ-ስርዓት ምዕራፍ ተሸጋግሯል። ይህ የ"ቡጣ ቀሉ" ስነ-ስርዓት ያለፈውን የአመራር ዘመን መቃኛና ራስን የማደሻ ወቅት ሲሆን፤ በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ሙሉ ስልጣኑን ለሚረከበው ቀጣዩ የገዳ ተረኛ ቡድን ስልጣኑ በሰላም እንዲሸጋገር መሰረት የሚጣልበት ታሪካዊ ክውን ነው።
"ቡጣ ቀሉ" ከመደበኛ ስነ-ስርዓት ባለፈ ተጠያቂነትን፣ የአመራር ቀጣይነትንና ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚሸጋገር መሪነትን የሚወክል ታላቅ ምልክት ነው። ይህም የኦሮሞ ህዝብ ለዲሞክራሲያዊ አስተዳደር፣ ለባህላዊ ማንነትና ለማህበራዊ ስምምነት ያለውን ጥልቅ ቁርጠኝነት የሚያንጸባርቅ ሲሆን፤ እነዚህ እሴቶች የገዳ ስርዓት ለዘመናት ጸንቶ እንዲቆይ ያደረጉ ምሰሶዎች ናቸው።
የከረዩ ማህበረሰብ ለዚህ ታሪካዊ ክስተት በሚዘጋጅበት በዚህ ወቅት፣ ስነ-ስርዓቱ የኦሮሞ ባህል ምን ያህል ጠንካራ መሆኑንና ለሰላም፣ ለአንድነት እንዲሁም ለመልካም አስተዳደር እያበረከተ ያለውን ዘላቂ አስተዋጽኦ ለዓለም የሚያሳይ ህያው ምስክር ነው።
ይህ በሀገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚዲያ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ድንቅ የዲሞክራሲ ትምህርት ቤትም ነው። ይህንን ታሪካዊ ኩነት በቦታው ተገኝታችሁ ለዓለም ለማስተዋወቅ ለምትተጉ በሙሉ ትልቅ ምስጋና ይገባችኋል!
ይህ በዓል የከረዩ ኦሮሞዎች ለዘመናት የጠበቁት፣ ማንነታቸውንና ባህላቸውን ለዓለም የሚያሳዩበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው። ዓመታት ዓመታትን እየተኩ፤ የአባቶቸው ፈር ሳይለቁ የደረሱት የከረዩ አባቶች፣ ዛሬም በኩራት ወደ አባቶቻችን በታሪካዊ መሬት ይጠሩናል።
ሁላችንም በቦታው በመገኘት ባህላቸውን እና ታሪካቸውን እንካፈል!
#ባህላችን የማንነታችን ነፀብራቅ ነው!,የከረዩ ገዳ በዓል፦ የቡታ ሰርግ እና የጎባ (ሥልጣን) ርክክብ!!
የከረዩ ኦሮሞ ጠንካራ ታሪክ፣ ባህል እና የገዳ ሥርዓት ያለው ማህበረሰብ ነው። ይህ በዓል የአንድነቱ፣ የጀግንነቱ እና የማንነቱ መገለጫ ነው።
የመከበሪያ ቦታ፦ ተሬ ሌዲ (Tarree Leedii) የሚጪሌ ገዳ የሥርዓት አፈፃፀም መርሃ ግብር (ከታህሳስ 16 - 26)
ከታህሳስ 16/2018ዓ.ም ጀምሮ የሚጪሌ ገዳ አባላት ተሬ ሌዲ ላይ ሠፍረዋል።
በአባ ቦኩ አዳራሽ (ጋልማ) ውስጥ እሳት ይለኩሳሉ።
የምርቃት እና የአርዳጋ (የመስዋዕት) ሥነ-ሥርዓት ያከናውናሉ።
ግመሎችን በታላቅነት ቅደም ተከተል ይፈታሉ።
ሁፌና ተራራ ላይ የከተሪ እንጨት ያቃጥላሉ፣ ኮርማም ያርዳሉ።
2. የከራ (የደጅ) ሥነ-ሥርዓት (ታህሳስ 17)፦
በአባ ቦኩ ደጅ ላይ ዱላቻ (ጥቁር ላም) ያርዳሉ።
ለአባ ቦኩ እሳት እና ለአርዳጋው ጠባቂዎችን ይመድባሉ።
3. አዳራሽ መገንባት (ታህሳስ 18 - 20)፦
የአባ ቦኩን አዳራሽ (ጋልማ) ይገነባሉ።
የእንግዳ ማረፊያ (ዳሳ)፣ የላም እና የግመል በረት ይሠራሉ።
4. ፀሎት እና ውይይት (ታህሳስ 20 - 25)፦
ወደ ተራራ እና ወደ ወንዝ በመሄድ አምላክን (ዋቃን) ሰላም እንዲሰጣቸው ይለምናሉ።
ስለ ገዳው እና ስለ እንግዶች አቀባበል ልዩ ልዩ ውይይቶችን (ገሪ) ያደርጋሉ።
የአካባቢውን ሰላም የሚያውጅ አዋጅ ያውጃሉ።
5. የማጠቃለያ ቀን (ታህሳስ 26)፦
ረፋድ፦ ሂዲ (ለሥርዓቱ የሚፈለግ ዕቃ) ያዘጋጃሉ፣ ቢቲማ (የኋላ ደጅ) ይገነባሉ።
ከሰዓት በኋላ፦ የጋልማው አባት (አባ ጋልማ) ገቢ የሚያመጡ ሰዎችን ይቀበላሉ።
ምሽት፦ የቡታ ሰርግ ሥነ-ሥርዓት ሳይመሽ ይጀመራል።
ማጠቃለያ፦
ታህሳስ 27 ቀን የባሊ (የሥልጣን) ርክክብ ወይም የጎባ ሥነ-ሥርዓት በመከናወን በዓሉ ይጠናቀቃል።
በሄሎ መተሐራ
#fentale #metahara #kereyu #gada #oromia #culturalheritage #oromia Culture and Tourism Bureau #oromia Tourism Commission
Comments