6 hours ago
በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ800 በላይ አዳዲስ የቱሪስት መስህቦች ተለይተዋል - የቱሪዝም ሚኒስትር
#ethiopia | በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሦስት ሩብ ዓመታት ኢትዮጵያ በቱሪዝም መስክ የላቀ ገጽታ የገነባችበት እና በርካታ ዓለም አቀፍ መድረኮችን በውጤታማነት ያስተናገደችበት ወቅት መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ ገለጹ።
ሚኒስትሯ ይህንን ያመለከቱት ተቋማቸው በበጀት ዓመቱ ያከናወናቸውን ዋና ዋና ተግባራት ለመገምገም እና በቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ለመወያየት ዛሬ ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከሠራተኞች ጋር ባደረጉት ጠቅላላ ስብሰባ ላይ ነው።
በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት በዓመቱ አዲሱ የቱሪዝም ፖሊሲ መጽደቁ ለዘርፉ ዕድገት ትልቅ መሠረት ጥሏል።
ከግሉ ዘርፍ እና ከክልል መስተዳድሮች ጋር ጠንካራ የሥራ ግንኙነት እንደነበር የገለጹት ሚኒስትሯ፣ አገሪቱን የስብሰባ፣ የጉዞ እና የዝግጅቶች ወይም የማክ ቱሪዝም መዳረሻ አድርጎ ለማስተዋወቅ ሰፊ ጥረት መደረጉንና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ800 በላይ አዳዲስ የቱሪስት መስህቦች መለየታቸውን አብራርተዋል።
በቀጣዩ አንድ ወር ውስጥ የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በውጤታማነት ማጠናቀቅ እንደሚገባ የጠቆሙት ሰላማዊት ካሳ፣ የፈጠራ አቀራረብ ያላቸውን የፕሮሞሽን ሥራዎች ማጠናከር፣ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ማሳደግ እና የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ሪፎርም የዝግጅት ምዕራፍን ማጠናቀቅ በትኩረት እንደሚሠራበት አስገንዝበዋል።
የቱሪዝም መዳረሻዎችና መሠረተ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ስለሺ ግርማ በበኩላቸው፣ ከተለመዱት የቱሪዝም ዓይነቶች በተጨማሪ አዳዲስ አማራጮችን ለይቶ በፖሊሲ ደረጃ ትኩረት እንዲያገኙ ማድረግ መቻሉ የዓመቱ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል።
የማርኬቲንግ እና ፕሮሞሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እንደገና አበበ በበጀት ዓመቱ የተመዘገቡ መልካም ተሞክሮዎችን በማስቀጠልና የታዩ ክፍተቶችን በማረም የዘርፉን ተወዳዳሪነት ይበልጥ ማሳደግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
#tourismethiopia #ethiopiatourism #micetourism #ethiopianheritage #tourismpolicy #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሦስት ሩብ ዓመታት ኢትዮጵያ በቱሪዝም መስክ የላቀ ገጽታ የገነባችበት እና በርካታ ዓለም አቀፍ መድረኮችን በውጤታማነት ያስተናገደችበት ወቅት መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ ገለጹ።
ሚኒስትሯ ይህንን ያመለከቱት ተቋማቸው በበጀት ዓመቱ ያከናወናቸውን ዋና ዋና ተግባራት ለመገምገም እና በቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ለመወያየት ዛሬ ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከሠራተኞች ጋር ባደረጉት ጠቅላላ ስብሰባ ላይ ነው።
በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት በዓመቱ አዲሱ የቱሪዝም ፖሊሲ መጽደቁ ለዘርፉ ዕድገት ትልቅ መሠረት ጥሏል።
ከግሉ ዘርፍ እና ከክልል መስተዳድሮች ጋር ጠንካራ የሥራ ግንኙነት እንደነበር የገለጹት ሚኒስትሯ፣ አገሪቱን የስብሰባ፣ የጉዞ እና የዝግጅቶች ወይም የማክ ቱሪዝም መዳረሻ አድርጎ ለማስተዋወቅ ሰፊ ጥረት መደረጉንና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ800 በላይ አዳዲስ የቱሪስት መስህቦች መለየታቸውን አብራርተዋል።
በቀጣዩ አንድ ወር ውስጥ የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በውጤታማነት ማጠናቀቅ እንደሚገባ የጠቆሙት ሰላማዊት ካሳ፣ የፈጠራ አቀራረብ ያላቸውን የፕሮሞሽን ሥራዎች ማጠናከር፣ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ማሳደግ እና የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ሪፎርም የዝግጅት ምዕራፍን ማጠናቀቅ በትኩረት እንደሚሠራበት አስገንዝበዋል።
የቱሪዝም መዳረሻዎችና መሠረተ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ስለሺ ግርማ በበኩላቸው፣ ከተለመዱት የቱሪዝም ዓይነቶች በተጨማሪ አዳዲስ አማራጮችን ለይቶ በፖሊሲ ደረጃ ትኩረት እንዲያገኙ ማድረግ መቻሉ የዓመቱ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል።
የማርኬቲንግ እና ፕሮሞሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እንደገና አበበ በበጀት ዓመቱ የተመዘገቡ መልካም ተሞክሮዎችን በማስቀጠልና የታዩ ክፍተቶችን በማረም የዘርፉን ተወዳዳሪነት ይበልጥ ማሳደግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
#tourismethiopia #ethiopiatourism #micetourism #ethiopianheritage #tourismpolicy #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
ኢትዮጵያ : የሰው ልጅ መገኛነቷን ዳግም ለዓለም አረጋገጠች
#ethiopia | ኢትዮጵያ አሁንም "የሰው ዘር መገኛ" መሆኗን በሳይንስ ዳግም አረጋገጠች።
በአፋር ስምጥ ሸለቆ በመካከለኛው አዋሽ (ሀሊቢ) አካባቢ በተደረገ የምርምር ፕሮጀክት፣ ከ100 ሺህ ዓመታት በፊት ይኖሩ የነበሩ የጥንታዊ ሆሞ ሳፒየንስ (Homo sapiens) ቅሪተ አካላት እና የድንጋይ መሣሪያዎች መገኘታቸውን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ይፋ አድርጓል።
ግኝቱ በአፍሪካ የሰው ዘር አመጣጥ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ክፍተት የነበረበትን ከ900,000 እስከ 200,000 ዓመታት ያለውን ጊዜ የሚዘክሩ አዳዲስ መረጃዎችን ይዟል።
ጥናቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ባለው የአሜሪካ የሳይንስ ጆርናል (PNAS) ላይ ዛሬ ታትሞ ወጥቷል።
በሺዎች የሚቆጠሩ የድንጋይ መሣሪያዎች መገኘታቸው፣ የሰው ልጅ የቴክኖሎጂ እድገት በወቅቱ ምን ይመስል እንደነበር ትልቅ ማሳያ ሆኗል።
በጥናቱ የተገኙ የእንስሳት ቅሪቶች (ጉሬዛ፣ ዝንጀሮ...) አፋር በወቅቱ ዛሬ እንደምናየው በረሃማ ሳይሆን ለምለምና ጫካማ እንደነበር ያረጋግጣሉ።
በዶ/ር ዮናስ በየነ የተመራውና ከ24 ሀገራት የተውጣጡ ሳይንቲስቶች የተሳተፉበት ይህ ምርምር፣ ለሀገራችን የቱሪዝም ዘርፍና ለታሪክ ጥናት ትልቅ ግብዓት ነው።
ኢትዮጵያ - የሰው ዘር ሁሉ ቤት!
#getu #humanorigins #ethiopiacradleofmankind #archaeologynews #afardepression #homosapiens #scientificdiscovery #yonasbeyene #ethiopianheritage #አፋር #አርኪዮሎጂ #ኢትዮጵያ #የሰውዘርመገኛ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | ኢትዮጵያ አሁንም "የሰው ዘር መገኛ" መሆኗን በሳይንስ ዳግም አረጋገጠች።
በአፋር ስምጥ ሸለቆ በመካከለኛው አዋሽ (ሀሊቢ) አካባቢ በተደረገ የምርምር ፕሮጀክት፣ ከ100 ሺህ ዓመታት በፊት ይኖሩ የነበሩ የጥንታዊ ሆሞ ሳፒየንስ (Homo sapiens) ቅሪተ አካላት እና የድንጋይ መሣሪያዎች መገኘታቸውን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ይፋ አድርጓል።
ግኝቱ በአፍሪካ የሰው ዘር አመጣጥ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ክፍተት የነበረበትን ከ900,000 እስከ 200,000 ዓመታት ያለውን ጊዜ የሚዘክሩ አዳዲስ መረጃዎችን ይዟል።
ጥናቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ባለው የአሜሪካ የሳይንስ ጆርናል (PNAS) ላይ ዛሬ ታትሞ ወጥቷል።
በሺዎች የሚቆጠሩ የድንጋይ መሣሪያዎች መገኘታቸው፣ የሰው ልጅ የቴክኖሎጂ እድገት በወቅቱ ምን ይመስል እንደነበር ትልቅ ማሳያ ሆኗል።
በጥናቱ የተገኙ የእንስሳት ቅሪቶች (ጉሬዛ፣ ዝንጀሮ...) አፋር በወቅቱ ዛሬ እንደምናየው በረሃማ ሳይሆን ለምለምና ጫካማ እንደነበር ያረጋግጣሉ።
በዶ/ር ዮናስ በየነ የተመራውና ከ24 ሀገራት የተውጣጡ ሳይንቲስቶች የተሳተፉበት ይህ ምርምር፣ ለሀገራችን የቱሪዝም ዘርፍና ለታሪክ ጥናት ትልቅ ግብዓት ነው።
ኢትዮጵያ - የሰው ዘር ሁሉ ቤት!
#getu #humanorigins #ethiopiacradleofmankind #archaeologynews #afardepression #homosapiens #scientificdiscovery #yonasbeyene #ethiopianheritage #አፋር #አርኪዮሎጂ #ኢትዮጵያ #የሰውዘርመገኛ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
5 months ago
🍽️ ክትፎን ጨምሮ አራት የጉራጌ ዕሴቶች ወደ ዩኔስኮ (UNESCO) ሊያመሩ ነው
#ethiopia | የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ፣ ታዋቂውን የጉራጌ ክትፎን ጨምሮ አራት የጉራጌ ባህላዊ እሴቶችን በዓለም የማይዳሰሱ ቅርሶች ዝርዝር ውስጥ ለማስመዝገብ ጥናት መጀመሩን አስታወቀ።
🥩 ክትፎ፦ ከምግብነት በላይ የሆነ የማንነት መገለጫ
የጉራጌ ክትፎ በዩኔስኮ ቅድሚያ ከተሰጣቸው እሴቶች መካከል ቀዳሚው ነው። ክትፎ ለጉራጌ ማህበረሰብ ምግብ ብቻ ሳይሆን የእንግዳ መቀበያ፣ የማህበራዊ ትስስር እና የጥበብ መገለጫ ነው። በአሁኑ ወቅት የክትፎ አዘገጃጀት፣ ከቆጮ፣ ከሚጥሚጣ እና ከንጥር ቅቤ ጋር ያለው ቁርኝት በጥልቀት እየተጠና ይገኛል።
📜 ሊመዘገቡ የታጩት አራት የኩራት ምንጮች፦
* የክትፎ አዘገጃጀት ጥበብ፦ ልዩ የሆነው የማክተፍ፣ የቅመማ ቅመም አጠቃቀምና የማቅረብ ስነስርዓት።
* ባህላዊ የክብ ቤት አሰራር፦ ያለ ሚስማር የሚገነባውና ለዘመናት የሚቆየው፣ የምህንድስና ጥበብ የታየበት የቤት አሰራር።
* የጎርደና የዳኝነት ስርአት፦ ለማህበራዊ ሰላምና ፍትህ የሚጠቀሙበት ጥንታዊና ውጤታማ የዳኝነት ስርዓት።
* የጀፎረ (መንደር) አወቃቀር፦ ለጋራ መስተጋብር በሚመች መልኩ የሚሰሩ ሰፋፊ መንገዶችና ማራኪ የመንደር አቀማመጥ።
📍 የጥናቱ ሂደት ምን ደረጃ ላይ ይገኛል?
የመምሪያው ኃላፊ ወይዘሮ መሰረት አመረጋ እንደገለጹት፣ ለኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን የቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቷል። ጥናቱ እንደተጠናቀቀ ሰነዱ በቀጥታ በፈረንሳይ ፓሪስ ለሚገኘው የዩኔስኮ ዋና መስሪያ ቤት ለውሳኔ ይላካል።
ከዚህ በተጨማሪ በዞኑ የሚገኙ ዕድሜ ጠገብ መስጂዶች፣ ጥንታዊ ኪታቦች፣ ገዳማትና ታሪካዊ ዋሻዎች ለቱሪስት መስህብነት እንዲውሉ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ጉራጌ #ክትፎ #ዩኔስኮ #ቅርስ #ኢትዮጵያ #ባህል #ቱሪዝም #የጉራጌባህል #gurage #kitfo #unesco #ethiopianheritage #tourismethiopia
#ethiopia | የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ፣ ታዋቂውን የጉራጌ ክትፎን ጨምሮ አራት የጉራጌ ባህላዊ እሴቶችን በዓለም የማይዳሰሱ ቅርሶች ዝርዝር ውስጥ ለማስመዝገብ ጥናት መጀመሩን አስታወቀ።
🥩 ክትፎ፦ ከምግብነት በላይ የሆነ የማንነት መገለጫ
የጉራጌ ክትፎ በዩኔስኮ ቅድሚያ ከተሰጣቸው እሴቶች መካከል ቀዳሚው ነው። ክትፎ ለጉራጌ ማህበረሰብ ምግብ ብቻ ሳይሆን የእንግዳ መቀበያ፣ የማህበራዊ ትስስር እና የጥበብ መገለጫ ነው። በአሁኑ ወቅት የክትፎ አዘገጃጀት፣ ከቆጮ፣ ከሚጥሚጣ እና ከንጥር ቅቤ ጋር ያለው ቁርኝት በጥልቀት እየተጠና ይገኛል።
📜 ሊመዘገቡ የታጩት አራት የኩራት ምንጮች፦
* የክትፎ አዘገጃጀት ጥበብ፦ ልዩ የሆነው የማክተፍ፣ የቅመማ ቅመም አጠቃቀምና የማቅረብ ስነስርዓት።
* ባህላዊ የክብ ቤት አሰራር፦ ያለ ሚስማር የሚገነባውና ለዘመናት የሚቆየው፣ የምህንድስና ጥበብ የታየበት የቤት አሰራር።
* የጎርደና የዳኝነት ስርአት፦ ለማህበራዊ ሰላምና ፍትህ የሚጠቀሙበት ጥንታዊና ውጤታማ የዳኝነት ስርዓት።
* የጀፎረ (መንደር) አወቃቀር፦ ለጋራ መስተጋብር በሚመች መልኩ የሚሰሩ ሰፋፊ መንገዶችና ማራኪ የመንደር አቀማመጥ።
📍 የጥናቱ ሂደት ምን ደረጃ ላይ ይገኛል?
የመምሪያው ኃላፊ ወይዘሮ መሰረት አመረጋ እንደገለጹት፣ ለኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን የቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቷል። ጥናቱ እንደተጠናቀቀ ሰነዱ በቀጥታ በፈረንሳይ ፓሪስ ለሚገኘው የዩኔስኮ ዋና መስሪያ ቤት ለውሳኔ ይላካል።
ከዚህ በተጨማሪ በዞኑ የሚገኙ ዕድሜ ጠገብ መስጂዶች፣ ጥንታዊ ኪታቦች፣ ገዳማትና ታሪካዊ ዋሻዎች ለቱሪስት መስህብነት እንዲውሉ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ጉራጌ #ክትፎ #ዩኔስኮ #ቅርስ #ኢትዮጵያ #ባህል #ቱሪዝም #የጉራጌባህል #gurage #kitfo #unesco #ethiopianheritage #tourismethiopia
Comments