6 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ‹‹የሱዳንና የኤርትራ አጋርነት ለአፍሪካ ቀንድና ቀይ ባህር መረጋጋት ከፍተኛ ሚና ይጫወታል፡፡›› ሲሉ በኤርትራ የሱዳን አምባሳደር ገለፁ፡፡ በኤርትራ የሱዳን አምባሳደር የሆኑት ኦሳማ አህመድ አደል ባሪ ዛሬ ባሰራጩት ዘለግ ያለ ፅሁፍ የሁለቱን አገራት ግንኙነት ጠቀሜታ አጉልተው ለማሳየት ጥረዋል፡፡ በሱዳን ሆራይዘን ጋዜጣ ላይ በሰፈረው በዚህ ፅሁፋቸው ‹‹ቀይ ባህርና የአፍሪካ ቀንድ በአሁኑ ጊዜ በፍጥነት በሚለዋወጥ ጂኦፖለቲካዊ ባህርይና በመርከቦች ጉዞ፣ በአቅርቦት ሰንሰለት፣ በነዳጅ ሀብትና በተፈጥሮ ሀብት ላይ በሚደረግ ፉክክር ወሳኝ ምእራፍ ውስጥ ይገኛሉ›› በማለት ጀምረዋል፡፡
አስከትለውም ከዚህ በመነሳት ከክልላዊ አጋርነት በተሻለ ሰፋ ያሉ የደህንነት፣ የልማትና ዘላቂ መረጋጋትን አላማው ያደረገ ስትራቴጂያዊ ጥምረት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል፡፡ አምባሳደሩ ሲቀጥሉም ‹‹ከዚህ አንፃር የሱዳንና ኤርትራ ስትራቴጂያዊ አጋርነት የተረጋጋ ቀጣናዊ የሀይል ሚዛን እንዲኖር የሚያስችል ትልቅ መሰረት ነው›› ያሉ ሲሆን ሁለቱ አገራት በቀይ ባህርና በአፍሪካ ቀንድ ዙሪያ የጋራ ፍላጎት እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹ሱዳን በቀይ ባህር ዳርቻዋ በኩል ሰሜን አፍሪካን ከምስራቅና ከመካከለኛው አፍሪካ ጋር የምታገናኝ ድልድይ ናት፡፡
እንዲሁም ባላት የግብርና፣ የውሀና የማእድን ሀብቶች በቀጠናው ውስጥ ትልቅ የልማት ሞተር ሆና ማገልገል ትችላለች፡፡ በሌላ በኩል ኤርትራ ደግሞ በቀይ ባህር ላይ ልዩ የሆነ ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ ያላት ከመሆኑም በላይ ሰፊ የባህር ዳርቻና ተስፋ ሰጪ ወደቦችን የያዘች ናት፡፡ ስለዚህም እነዚህ ጉዳዮች ኢኮኖሚያዊ ውህደት ለመፍጠርና በቀጠናው ውስጥ የተረጋጋ ፖለቲካ ለመፍጠር ምሰሶ ሆነው ሊያገለግሉ ይችላሉ›› በማለት ገልፀው ሁለቱ አገራት ዘላቂነት ያለውና ረጅም ራእይ የሰነቀ ስትራቴጂያዊ አጋርነት መፍጠራቸውን አስረድተዋል፡፡
አስከትለውም ከዚህ በመነሳት ከክልላዊ አጋርነት በተሻለ ሰፋ ያሉ የደህንነት፣ የልማትና ዘላቂ መረጋጋትን አላማው ያደረገ ስትራቴጂያዊ ጥምረት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል፡፡ አምባሳደሩ ሲቀጥሉም ‹‹ከዚህ አንፃር የሱዳንና ኤርትራ ስትራቴጂያዊ አጋርነት የተረጋጋ ቀጣናዊ የሀይል ሚዛን እንዲኖር የሚያስችል ትልቅ መሰረት ነው›› ያሉ ሲሆን ሁለቱ አገራት በቀይ ባህርና በአፍሪካ ቀንድ ዙሪያ የጋራ ፍላጎት እንዳላቸው ገልፀዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹ሱዳን በቀይ ባህር ዳርቻዋ በኩል ሰሜን አፍሪካን ከምስራቅና ከመካከለኛው አፍሪካ ጋር የምታገናኝ ድልድይ ናት፡፡
እንዲሁም ባላት የግብርና፣ የውሀና የማእድን ሀብቶች በቀጠናው ውስጥ ትልቅ የልማት ሞተር ሆና ማገልገል ትችላለች፡፡ በሌላ በኩል ኤርትራ ደግሞ በቀይ ባህር ላይ ልዩ የሆነ ጂኦግራፊያዊ አቀማመጥ ያላት ከመሆኑም በላይ ሰፊ የባህር ዳርቻና ተስፋ ሰጪ ወደቦችን የያዘች ናት፡፡ ስለዚህም እነዚህ ጉዳዮች ኢኮኖሚያዊ ውህደት ለመፍጠርና በቀጠናው ውስጥ የተረጋጋ ፖለቲካ ለመፍጠር ምሰሶ ሆነው ሊያገለግሉ ይችላሉ›› በማለት ገልፀው ሁለቱ አገራት ዘላቂነት ያለውና ረጅም ራእይ የሰነቀ ስትራቴጂያዊ አጋርነት መፍጠራቸውን አስረድተዋል፡፡
7 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የቻይናው ዚጂን ማይኒንግ (የካናዳውን አላይድ ጎልድን በ4.01 ቢሊዮን ዶላር (5.5 ቢሊዮን የካናዳ ዶላር) ለመግዛት ያደረገው ስምምነት በቻይና እና በኢትዮጵያ መንግስታት ጫና ምክንያት መፍረሱ ተገለጸ።
እ.ኤ.አ. በጥር 2026 የተደረሰው ይህ ስምምነት፣ ዚጂን ማይኒንግ በአላይድ ጎልድ ስር የሚገኙትንና በኮትዲቯር፣ ማሊ እና ኢትዮጵያ (ቤኒሻንጉል ጉሙዝ የሚገኘው የኩርሙክ የወርቅ ማዕድን) ያሉትን ፕሮጀክቶች ሙሉ በሙሉ ጠቅልሎ እንዲገዛ የሚያስችል ነበር። ስምምነቱን የካናዳ እና የአፍሪካ ቀጣናዊ ተቋማት (እንደ ኮሜሳ እና ኤኮዋስ) ቢያጸድቁትም፣ የቻይና ብሔራዊ ልማት እና ማሻሻያ ኮሚሽን (NDRC) የግዢውን ዋጋ እና የማሊን የፖለቲካ አለመረጋጋት በመስጋት ማጽደቅ አልቻለም።
በሌላ በኩል የኢትዮጵያ መንግስት በዚሁ ስምምነት ዙሪያ ከፍተኛ የግብር ጥያቄዎችን ማንሳቱ ለድርድሩ መፍረስ ተጨማሪ ምክንያት ሆኗል። የኢትዮጵያ ገቢዎች ህግ የውጭ ኩባንያዎች የባለቤትነት ለውጥ ሲያደርጉ ከፍተኛ ግብር እንዲከፍሉ ያስገድዳል። በተጨማሪም፣ የኢትዮጵያ መንግስት እንደ ኩርሙክ ያለን ስትራቴጂካዊ የወርቅ ማዕድን በአንድ የቻይና የመንግስት ኩባንያ ስር ብቻ እንዲወድቅ አለመፈለጉ ሌላው ተግዳሮት ነበር።
በእነዚህ ጂኦፖለቲካዊ እና አስተዳደራዊ እንቅፋቶች ምክንያት ሁለቱ ኩባንያዎች ሙሉ ግዥውን ሰርዘዋል። በምትኩ፣ ዚጂን ማይኒንግ 295 ሚሊዮን ዶላር በመክፈል 9.2 በመቶ የአላይድ ጎልድ አክሲዮኖችን (Strategic Equity Stake) ብቻ ለመግዛት ተስማምቷል። ይህ ዜና ከተሰማ በኋላ በቶሮንቶ እና ኒውዮርክ የአክሲዮን ገበያዎች ላይ የአላይድ ጎልድ የአክሲዮን ዋጋ ከ16 በመቶ በላይ አሽቆልቁሏል።
እ.ኤ.አ. በጥር 2026 የተደረሰው ይህ ስምምነት፣ ዚጂን ማይኒንግ በአላይድ ጎልድ ስር የሚገኙትንና በኮትዲቯር፣ ማሊ እና ኢትዮጵያ (ቤኒሻንጉል ጉሙዝ የሚገኘው የኩርሙክ የወርቅ ማዕድን) ያሉትን ፕሮጀክቶች ሙሉ በሙሉ ጠቅልሎ እንዲገዛ የሚያስችል ነበር። ስምምነቱን የካናዳ እና የአፍሪካ ቀጣናዊ ተቋማት (እንደ ኮሜሳ እና ኤኮዋስ) ቢያጸድቁትም፣ የቻይና ብሔራዊ ልማት እና ማሻሻያ ኮሚሽን (NDRC) የግዢውን ዋጋ እና የማሊን የፖለቲካ አለመረጋጋት በመስጋት ማጽደቅ አልቻለም።
በሌላ በኩል የኢትዮጵያ መንግስት በዚሁ ስምምነት ዙሪያ ከፍተኛ የግብር ጥያቄዎችን ማንሳቱ ለድርድሩ መፍረስ ተጨማሪ ምክንያት ሆኗል። የኢትዮጵያ ገቢዎች ህግ የውጭ ኩባንያዎች የባለቤትነት ለውጥ ሲያደርጉ ከፍተኛ ግብር እንዲከፍሉ ያስገድዳል። በተጨማሪም፣ የኢትዮጵያ መንግስት እንደ ኩርሙክ ያለን ስትራቴጂካዊ የወርቅ ማዕድን በአንድ የቻይና የመንግስት ኩባንያ ስር ብቻ እንዲወድቅ አለመፈለጉ ሌላው ተግዳሮት ነበር።
በእነዚህ ጂኦፖለቲካዊ እና አስተዳደራዊ እንቅፋቶች ምክንያት ሁለቱ ኩባንያዎች ሙሉ ግዥውን ሰርዘዋል። በምትኩ፣ ዚጂን ማይኒንግ 295 ሚሊዮን ዶላር በመክፈል 9.2 በመቶ የአላይድ ጎልድ አክሲዮኖችን (Strategic Equity Stake) ብቻ ለመግዛት ተስማምቷል። ይህ ዜና ከተሰማ በኋላ በቶሮንቶ እና ኒውዮርክ የአክሲዮን ገበያዎች ላይ የአላይድ ጎልድ የአክሲዮን ዋጋ ከ16 በመቶ በላይ አሽቆልቁሏል።
8 days ago
የዓለም የወርቅ ፍላጎት 380 ቢሊዮን ዶላር ደረሰ
#ethiopia | የዓለም የወርቅ ገበያ በ2026 ሁለተኛ ሩብ ዓመት ታሪካዊ ምዕራፍ መመዝገቡን የዓለም ወርቅ ምክር ቤት (World Gold Council) አስታውቋል።
በሪፖርቱ መሠረት፣ የወርቅ ፍላጎት በመጠን 1,269 ቶን ላይ የተረጋጋ ሲሆን፣ በከፍተኛ የወርቅ ዋጋ ምክንያት የገበያው ጠቅላላ ዋጋ 380 ቢሊዮን ዶላር በመድረስ አዲስ ታሪካዊ ክብረ ወሰን አስመዝግቧል።
ባለሙያዎች እንደሚገልጹት፣ የወርቅ ዋጋ መጨመር፣ የዓለም አቀፍ ጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች፣ የገንዘብ ገበያ አለመረጋጋት እና ባለሀብቶች ወደ ደህንነት ንብረት (Safe Haven Asset) የሚያደርጉት መሸጋገር የወርቅ ፍላጎትን በእጅጉ አጠናክረዋል።
ሪፖርቱ እንደሚያመለክተው፣ በምዕራብ አፍሪካ ያለው የማዕድን ምርት እድገት ለዓለም የወርቅ አቅርቦት ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጓል። ቡርኪና ፋሶ 17 በመቶ እና ጋና 8 በመቶ የምርት እድገት በማስመዝገብ የወርቅ ምርት ማሳደግ ችለዋል። ይህም የዓለም የወርቅ አቅርቦትን ለማረጋጋት አስፈላጊ ሚና ተጫውቷል።
በሌላ በኩል የዓለም ማዕከላዊ ባንኮች 289 ቶን የወርቅ ግዥ በመፈጸማቸው የገበያውን ፍላጎት ደግፈዋል። ምንም እንኳን በአንዳንድ አገራት የወርቅ ምርት መቀነስ ቢታይም፣ የዓለም አቀፉ ገበያ በአጠቃላይ ጠንካራ መሆኑን ሪፖርቶች ያመለክታሉ።
በወርቅ ገበያ ላይ የሚታየው የዋጋ ንረት የጌጣጌጥ ፍላጎትን እየቀነሰ ቢሆንም፣ የኢንቨስትመንት ፍላጎት በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉን የዓለም ወርቅ ምክር ቤት ገልጿል።
በተለይ የወርቅ ETF ፈንዶች፣ የወርቅ ሳንቲሞች እና የወርቅ አሞሌዎች ላይ የባለሀብቶች ፍላጎት እየጨመረ መሆኑ ተጠቁሟል።
ኢኮኖሚስቶች እንደሚሉት፣ የወርቅ ገበያ በቀጣዮቹ ወራትም በዓለም አቀፍ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች ተፅዕኖ ስር እንደሚቀጥል ይጠበቃል።
በተለይ የማዕከላዊ ባንኮች የወርቅ ክምችት ማሳደግና ባለሀብቶች ወደ ወርቅ የሚያደርጉት መሸጋገር የዋጋ እንቅስቃሴውን ዋና የሚወስኑ ምክንያቶች እንደሚሆኑ ተገልጿል።
#ethiopia | የዓለም የወርቅ ገበያ በ2026 ሁለተኛ ሩብ ዓመት ታሪካዊ ምዕራፍ መመዝገቡን የዓለም ወርቅ ምክር ቤት (World Gold Council) አስታውቋል።
በሪፖርቱ መሠረት፣ የወርቅ ፍላጎት በመጠን 1,269 ቶን ላይ የተረጋጋ ሲሆን፣ በከፍተኛ የወርቅ ዋጋ ምክንያት የገበያው ጠቅላላ ዋጋ 380 ቢሊዮን ዶላር በመድረስ አዲስ ታሪካዊ ክብረ ወሰን አስመዝግቧል።
ባለሙያዎች እንደሚገልጹት፣ የወርቅ ዋጋ መጨመር፣ የዓለም አቀፍ ጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች፣ የገንዘብ ገበያ አለመረጋጋት እና ባለሀብቶች ወደ ደህንነት ንብረት (Safe Haven Asset) የሚያደርጉት መሸጋገር የወርቅ ፍላጎትን በእጅጉ አጠናክረዋል።
ሪፖርቱ እንደሚያመለክተው፣ በምዕራብ አፍሪካ ያለው የማዕድን ምርት እድገት ለዓለም የወርቅ አቅርቦት ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጓል። ቡርኪና ፋሶ 17 በመቶ እና ጋና 8 በመቶ የምርት እድገት በማስመዝገብ የወርቅ ምርት ማሳደግ ችለዋል። ይህም የዓለም የወርቅ አቅርቦትን ለማረጋጋት አስፈላጊ ሚና ተጫውቷል።
በሌላ በኩል የዓለም ማዕከላዊ ባንኮች 289 ቶን የወርቅ ግዥ በመፈጸማቸው የገበያውን ፍላጎት ደግፈዋል። ምንም እንኳን በአንዳንድ አገራት የወርቅ ምርት መቀነስ ቢታይም፣ የዓለም አቀፉ ገበያ በአጠቃላይ ጠንካራ መሆኑን ሪፖርቶች ያመለክታሉ።
በወርቅ ገበያ ላይ የሚታየው የዋጋ ንረት የጌጣጌጥ ፍላጎትን እየቀነሰ ቢሆንም፣ የኢንቨስትመንት ፍላጎት በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉን የዓለም ወርቅ ምክር ቤት ገልጿል።
በተለይ የወርቅ ETF ፈንዶች፣ የወርቅ ሳንቲሞች እና የወርቅ አሞሌዎች ላይ የባለሀብቶች ፍላጎት እየጨመረ መሆኑ ተጠቁሟል።
ኢኮኖሚስቶች እንደሚሉት፣ የወርቅ ገበያ በቀጣዮቹ ወራትም በዓለም አቀፍ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች ተፅዕኖ ስር እንደሚቀጥል ይጠበቃል።
በተለይ የማዕከላዊ ባንኮች የወርቅ ክምችት ማሳደግና ባለሀብቶች ወደ ወርቅ የሚያደርጉት መሸጋገር የዋጋ እንቅስቃሴውን ዋና የሚወስኑ ምክንያቶች እንደሚሆኑ ተገልጿል።
9 days ago
ኢትዮጵያና አዘርባጃን፣ ከዲፕሎማሲ ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ኢትዮጵያና አዘርባጃን ጠንካራ ዲፕሎማሲዊ ግንኙት እየገነቡ መጥተዋል፡፡
በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙት እነዚህ ሁለት ሀገራት የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ኢንቨስትመንት፣ የመከላከያ እና የቴክኖሎጂ ትብብሮችን ወደ ጠንካራና አዲስ ምዕራፍ ለማሳደግ እየሰሩ ናቸው።
ሀገራቱ የሶቪየት ኅብረት መፍረስን ተከትሎ አዘርባጃን ሪፐብሊክ ራሷን የቻለች ሀገር ከሆነች በኋላ ግንኙነታቸውን ቀስ በቀስ እያጠናከሩ መጥተዋል።
ኢትዮጵያና አዘርባጃን ለበርካታ ዓመታት በዘለቀው ግንኙነታቸው የየሀገራቱ ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት ጉብኝቶችን አድርገዋል፡፡
ሕዳር 2017 ዓ.ም አዘርባጃን ባስተናገደችው የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ (ኮፕ29) ለመሳተፍ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ወደ ባኩ ተጉዘው ነበር፡፡
በቆታቸውም የአዘርባጃንን የዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡
እንዲሁም በ2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ 3ኛው የኢትዮ-አዘርባጃን የፖለቲካ ምክክር መድረክ የተካሄደ ሲሆን÷ መድረኩ የሁለቱን ሀገራት የፖለቲካ ትስስር ወደ ከፍተኛ ደረጃ መድረሱን የሚያመላክት ነበር፡፡
በመቀጠልም የካቲት 2018 ዓ.ም ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የባኩ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ አዲስ ምዕራፍ ከፍ አድርጓል።
በዚህ ሳምንት ደግሞ የአዘርባጃን ሪፐብሊክ የፓርላማ አፈ ጉባዔ ሳሂባ ጋፋሮቫ ኢትዮጵያን እየጎበኙ የሚገኙ ሲሆን÷ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ከፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔዎች ጋር መክረዋል፡፡
ኢትዮጵያና አዘርባጃን በታሪክና በጂኦግራፊያዊ አቀማመጣቸው ቢለያዩም በርካታ የጋራ ባህሪያት አሏቸው።
ሁለቱም ጂኦፖለቲካዊ ፉክክር ባሉባቸው ቀጣናዎች ይገኛሉ፤ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ፤ አዘርባጃን ደግሞ በደቡብ ካውካሰስ ክልል፡፡ በየቀጣናቸው ሁለቱም ሀገራት ለሰላምና ደህንነት ቁልፍ ሚና እየተጫወቱ ነው፡፡
በዓለም አቀፍ ፖለቲካም ሁለቱ ሀገራት ከምሥራቅና ከምዕራቡ ዓለማት ጋር ሚዛኑን የጠበቀ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲን ይከተላሉ፡፡
ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን መሠረተ ልማትን፣ ዲጂታል ሽግግርን፣ ኢንዱስትሪን እና የውጭ ኢንቨስትመንትን ለልማትና ዕድገታቸው ትኩረት ሰጥተው እየሰሩባቸው ያሉ ዘርፎች ናቸው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አዘርባጃንን በጎበኙበት ወቅት የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሊየቭ የሀገራቱን ግንኙነት አስመልክተው ሲገልጹ፣ "አጋርነታችን በርካታ ጠቃሚ ጉዳዮችን ያካተተ ነው" ነበር ያሉት።
ሁለቱ ሀገራት በኢኮኖሚ፣ በወታደራዊ፣ በኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂ፣ በአየር ንብረት ለውጥ እና በሌሎች ዘርፎች ግንኙነታቸው እያደገ መምጣቱን መሪዎቹ በተለያዩ ጊዜያት ገልጸዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሊየቭ ብልፅግና ፓርቲ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ማሸነፉን አስመልክቶ በላኩት የደስታ መልዕክት፣ "በአዘርባጃን እና በኢትዮጵያ መካከል ያለው ግንኙነት በአዎንታዊ አቅጣጫ እያደገ መሆኑ የሚያስደስት ነው" በማለት የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት በአዲስ መልክ እየተጠናከረ መምጣቱን አንስተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በጉብኝታቸው ወቅት እንዳሉት÷ ባለፉት ዓመታት ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በአቪዬሽን፣ በኢንዱስትሪ ፓርኮችና በነጻ የንግድ ቀጣናዎች ረገድ የተከናወኑ የጋራ የኢኮኖሚዊ ትብብሮች፣ የሁለቱን ሀገራት አጋርነት እያደገ መምጣት ያመለከተ ነው ብለዋል።
ሁለቱ ሀገራት አንደኛቸው ከሌላኛው በበርካታ ዘርፎች ልምዶችን እየተለዋወጡ ሲሆን÷ ለአብነትም ኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከአዘርባጃኑ አሳን ክድመት (ASAN Khidmet) የመንግሥት ዲጂታል አገልግሎት ልምድ የተወሰደ የዲጂታል አሰራር ሥርዓት ነው።
አዘርባጃን በበኩሏ በኢትዮጵያ በኩል ወደ አፍሪካ ገበያ ለመግባት ጥሩ መደላድል ታገኛለች። በዚህ መልኩ ሁለቱ ሀገራት የጋራ ጥቅምን በማስፋት በዓለም ኢኮኖሚና ጂኦፖለቲካ አወቃቀር ውስጥ ይበልጥ የሚጎለብት አጋርነት ሊገነቡ ይችላሉ።
ሁለቱ ሀገራት የሚጋሯቸው የልማት ርዕይ፣ የመሠረተ ልማት ግንባታ፣ የዲጂታል ሽግግር፣ የኢኮኖሚ ብዝሃነት እና ቀጣናዊ ትብብሮች ግንኙነታቸውን ከፍ ወዳለ ስትራቴጂካዊ አጋርነት የሚያሳድግ ነው።
በቴዎድሮስ ሳህለ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ኢትዮጵያና አዘርባጃን ጠንካራ ዲፕሎማሲዊ ግንኙት እየገነቡ መጥተዋል፡፡
በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙት እነዚህ ሁለት ሀገራት የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ኢንቨስትመንት፣ የመከላከያ እና የቴክኖሎጂ ትብብሮችን ወደ ጠንካራና አዲስ ምዕራፍ ለማሳደግ እየሰሩ ናቸው።
ሀገራቱ የሶቪየት ኅብረት መፍረስን ተከትሎ አዘርባጃን ሪፐብሊክ ራሷን የቻለች ሀገር ከሆነች በኋላ ግንኙነታቸውን ቀስ በቀስ እያጠናከሩ መጥተዋል።
ኢትዮጵያና አዘርባጃን ለበርካታ ዓመታት በዘለቀው ግንኙነታቸው የየሀገራቱ ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት ጉብኝቶችን አድርገዋል፡፡
ሕዳር 2017 ዓ.ም አዘርባጃን ባስተናገደችው የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ (ኮፕ29) ለመሳተፍ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ወደ ባኩ ተጉዘው ነበር፡፡
በቆታቸውም የአዘርባጃንን የዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡
እንዲሁም በ2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ 3ኛው የኢትዮ-አዘርባጃን የፖለቲካ ምክክር መድረክ የተካሄደ ሲሆን÷ መድረኩ የሁለቱን ሀገራት የፖለቲካ ትስስር ወደ ከፍተኛ ደረጃ መድረሱን የሚያመላክት ነበር፡፡
በመቀጠልም የካቲት 2018 ዓ.ም ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የባኩ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ አዲስ ምዕራፍ ከፍ አድርጓል።
በዚህ ሳምንት ደግሞ የአዘርባጃን ሪፐብሊክ የፓርላማ አፈ ጉባዔ ሳሂባ ጋፋሮቫ ኢትዮጵያን እየጎበኙ የሚገኙ ሲሆን÷ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ከፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔዎች ጋር መክረዋል፡፡
ኢትዮጵያና አዘርባጃን በታሪክና በጂኦግራፊያዊ አቀማመጣቸው ቢለያዩም በርካታ የጋራ ባህሪያት አሏቸው።
ሁለቱም ጂኦፖለቲካዊ ፉክክር ባሉባቸው ቀጣናዎች ይገኛሉ፤ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ፤ አዘርባጃን ደግሞ በደቡብ ካውካሰስ ክልል፡፡ በየቀጣናቸው ሁለቱም ሀገራት ለሰላምና ደህንነት ቁልፍ ሚና እየተጫወቱ ነው፡፡
በዓለም አቀፍ ፖለቲካም ሁለቱ ሀገራት ከምሥራቅና ከምዕራቡ ዓለማት ጋር ሚዛኑን የጠበቀ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲን ይከተላሉ፡፡
ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን መሠረተ ልማትን፣ ዲጂታል ሽግግርን፣ ኢንዱስትሪን እና የውጭ ኢንቨስትመንትን ለልማትና ዕድገታቸው ትኩረት ሰጥተው እየሰሩባቸው ያሉ ዘርፎች ናቸው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አዘርባጃንን በጎበኙበት ወቅት የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሊየቭ የሀገራቱን ግንኙነት አስመልክተው ሲገልጹ፣ "አጋርነታችን በርካታ ጠቃሚ ጉዳዮችን ያካተተ ነው" ነበር ያሉት።
ሁለቱ ሀገራት በኢኮኖሚ፣ በወታደራዊ፣ በኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂ፣ በአየር ንብረት ለውጥ እና በሌሎች ዘርፎች ግንኙነታቸው እያደገ መምጣቱን መሪዎቹ በተለያዩ ጊዜያት ገልጸዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሊየቭ ብልፅግና ፓርቲ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ማሸነፉን አስመልክቶ በላኩት የደስታ መልዕክት፣ "በአዘርባጃን እና በኢትዮጵያ መካከል ያለው ግንኙነት በአዎንታዊ አቅጣጫ እያደገ መሆኑ የሚያስደስት ነው" በማለት የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት በአዲስ መልክ እየተጠናከረ መምጣቱን አንስተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በጉብኝታቸው ወቅት እንዳሉት÷ ባለፉት ዓመታት ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በአቪዬሽን፣ በኢንዱስትሪ ፓርኮችና በነጻ የንግድ ቀጣናዎች ረገድ የተከናወኑ የጋራ የኢኮኖሚዊ ትብብሮች፣ የሁለቱን ሀገራት አጋርነት እያደገ መምጣት ያመለከተ ነው ብለዋል።
ሁለቱ ሀገራት አንደኛቸው ከሌላኛው በበርካታ ዘርፎች ልምዶችን እየተለዋወጡ ሲሆን÷ ለአብነትም ኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከአዘርባጃኑ አሳን ክድመት (ASAN Khidmet) የመንግሥት ዲጂታል አገልግሎት ልምድ የተወሰደ የዲጂታል አሰራር ሥርዓት ነው።
አዘርባጃን በበኩሏ በኢትዮጵያ በኩል ወደ አፍሪካ ገበያ ለመግባት ጥሩ መደላድል ታገኛለች። በዚህ መልኩ ሁለቱ ሀገራት የጋራ ጥቅምን በማስፋት በዓለም ኢኮኖሚና ጂኦፖለቲካ አወቃቀር ውስጥ ይበልጥ የሚጎለብት አጋርነት ሊገነቡ ይችላሉ።
ሁለቱ ሀገራት የሚጋሯቸው የልማት ርዕይ፣ የመሠረተ ልማት ግንባታ፣ የዲጂታል ሽግግር፣ የኢኮኖሚ ብዝሃነት እና ቀጣናዊ ትብብሮች ግንኙነታቸውን ከፍ ወዳለ ስትራቴጂካዊ አጋርነት የሚያሳድግ ነው።
በቴዎድሮስ ሳህለ
11 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ባለፈው ዓመት ታይቶ የነበረውን የዋጋ ማረጋጋት ሂደት በመቀልበስ፣ በ2026 የመጀመሪያ አጋማሽ በአፍሪካ ቀዳሚ የሚባሉ ኢኮኖሚዎች ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት እያስተናገዱ መሆኑ ተገለጸ። ለዚህ የዋጋ ንረት ማገርሸት ዋነኛ ምክንያት የሆነው በመካከለኛው ምስራቅ (በተለይም በኢራን) ያለው ግጭት የዓለም የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋን ወደ 100 ዶላር እንዲጠጋ በማድረጉ ነው። አስር ዋና ዋና የአፍሪካ ኢኮኖሚዎችን ባካተተ ጥናት፣ ሁሉም ሀገራት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የዋጋ ግሽበት ጭማሪ አስመዝግበዋል። በዚህም ኢትዮጵያ በ4.1 በመቶ ጭማሪ ቀዳሚ ስትሆን፣ የሰኔ ወር አጠቃላይ የዋጋ ግሽበቷ 13.9 በመቶ ደርሷል። የምግብ ዋጋ ንረቱም ወደ 15.1 በመቶ አሻቅቧል። ከኢትዮጵያ በመቀጠል ግብጽ፣ ኬንያ እና ጋና ከፍተኛ የዋጋ ንረት ያስመዘገቡ ሀገራት ሆነዋል።
ይህ ጂኦፖለቲካዊ ቀውስ የአፍሪካ ኢኮኖሚዎች ለውጫዊ የኃይል አቅርቦት እና የዋጋ መናወጥ ምን ያህል ተጋላጭ እንደሆኑ በድጋሚ ያጋለጠ ነው። የነዳጅ፣ የትራንስፖርት እና የምግብ ዋጋ መናር የሀገራቱን ማዕከላዊ ባንኮች የገንዘብ ፖሊሲያቸውን እንዲያጠብቁ (ለአብነት ያህል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የወለድ መጠኑን ወደ 16 በመቶ እንዳሳደገው) ወይም የጀመሩትን የፖሊሲ ማላላት እንዲያቋርጡ አስገድዷቸዋል። የዓለም ባንክ እንዳስጠነቀቀው፣ መንግስታት የተገደበ ሀብታቸውን ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለመታደግ ካላዋሉ በስተቀር አሁን የተፈጠረው የማክሮ-ኢኮኖሚ ጫና አብዛኛውን ገቢውን ለምግብ እና ኢነርጂ በሚያውቀው ድሃው የህብረተሰብ ክፍል ላይ ከባድ ሸክም በመፍጠር ወደ ከፋ ማህበራዊ ቀውስ ሊያመራ ይችላል።
ይህ ጂኦፖለቲካዊ ቀውስ የአፍሪካ ኢኮኖሚዎች ለውጫዊ የኃይል አቅርቦት እና የዋጋ መናወጥ ምን ያህል ተጋላጭ እንደሆኑ በድጋሚ ያጋለጠ ነው። የነዳጅ፣ የትራንስፖርት እና የምግብ ዋጋ መናር የሀገራቱን ማዕከላዊ ባንኮች የገንዘብ ፖሊሲያቸውን እንዲያጠብቁ (ለአብነት ያህል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የወለድ መጠኑን ወደ 16 በመቶ እንዳሳደገው) ወይም የጀመሩትን የፖሊሲ ማላላት እንዲያቋርጡ አስገድዷቸዋል። የዓለም ባንክ እንዳስጠነቀቀው፣ መንግስታት የተገደበ ሀብታቸውን ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለመታደግ ካላዋሉ በስተቀር አሁን የተፈጠረው የማክሮ-ኢኮኖሚ ጫና አብዛኛውን ገቢውን ለምግብ እና ኢነርጂ በሚያውቀው ድሃው የህብረተሰብ ክፍል ላይ ከባድ ሸክም በመፍጠር ወደ ከፋ ማህበራዊ ቀውስ ሊያመራ ይችላል።
Sponsored by
Surafel
12 days ago
የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምላሽና ቀጣናዊ ፋይዳው
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ባለፉት አስርት ዓመታት በሰላም ማስከበር፣ በግጭት አፈታት፣ በኤሌክትሪክ ኃይል ወጪ ንግድ፣ በቀጣናዊ ትስስር እና በንግድ ትብብር ረገድ ያበረከተችው አስተዋጽኦ ለጎረቤቶቿ ብሎም ለቀጣናው የምትሰጠውን ከፍ ያለ ትኩረት ያሳያል።
ኢትዮጵያ በታሪኳ የትኛውንም ጎረቤት ሀገር ወርራ አታውቅም፡፡ ከጎረቤቶቿ ጋር ያላት ግንኙነት ሰላማዊና በትብብር ላይ የተመሰረተ ሆኖ ቆይቷል፡፡
ጎረቤቶቿ ሰላም በራቃቸው ጊዜ ሁሉ፣ ሰላም ለማስከበር ቀድማ በመገኘት ትታወቃለች፡፡ ይህንንም በደቡብ ሱዳን፣ በሱዳን፣ በሶማሊያ እንዲሁም ከጎረቤቶቿ ራቅ ብላም በላይቤሪያ፣ በሩዋንዳ፣ በኮንጎ እና በሴራሊዮን በተግባር አስመስክራለች፡፡
በአህጉር ደረጃ ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ቀንበር ሲማቅቁ የነበሩ አፍሪካውያን ወንድም እህቶች ነጻ ለመውጣት የሚያደርጉትን ጥረት በስልጠና፣ በሎጂስቲክስና በዲፕሎማሲ መስክ ጭምር መደገፏ አሌ የማይባል ሃቅ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ዛሬም የልማት ትሩፋቷን ለብቻዋ ዕድገትና ለውጥ የምትጠቀም ሀገር አይደለችም፡፡ ይልቁንም ልማቷን እና ለውጧን በማጋራት እና ለጎረቤቶቿ አብሮ መለወጥ እየሰራች ትገኛለች፡፡
በአፍሪካ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል አምራች ከሆኑ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ፤ ለጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ኤሌክትሪክ እየላከች ነው።
ይህ በአካባቢው የኢንዱስትሪ ልማት፣ የከተማ እድገት እና የህዝብ ኑሮ መሻሻል ላይ ቀጥተኛ አስተዋፅኦ እያደረገ ነው።
በንግድ ረገድም ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና እና የአፍሪካ ህብረት "አጀንዳ 2063" የሚያስቀምጧቸውን የክልላዊ ውህደት ግቦች ለማሳካት የኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች፣ የድንበር ንግድ ማዕከላት እና የትራንስፖርት ኮሪደሮችን በማስፋፋት በቀጣናዊ ትስስር ማደግና መጠናከር ላይ ግዙፍ ኢንቨስትመንት እያካሄደች ነው።
ኢትዮጵያ ለጎረቤቶቿ ሰላምና ደህንነት፣ እድገትና ልማት አበክራ የሰራቻቸው ስራዎች ለቀጣናውና ለሀገራቱ ያላትን አዎንታዊ ሚና በግልፅ ያሳያል። ሀገሪቱ የባህር በር ጥያቄዋ ምላሽ ሲያገኝ ይህ ቀጣናዊ ገንቢ ሚናዋ በምን ያህል መጠን ሊያድግና ሊባዛ እንደሚችል ለመገመት አያዳግትም፡፡
በታሪክ አጋጣሚ የኢትዮጵያ ህዝብ ህጋዊ ስልጣን በሌለው አካል ህጋዊ የባሕር በር ባለቤትነቷን እንድታጣ ተደርጓል፡፡ የመደመር መንግሥት የተፈጸመውን ኢፍትሃዊና ታሪካዊ በደል በሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ የማስመለስ ጥያቄ አቅርቦ የበርካታ ሃያላን ሀገራትን ድጋፍ አግኝቷል፡፡ ኢትዮጵያ በፍጥነት እያደገ ካለው ኢኮኖሚዋና የህዝብ ቁጥሯ አንጻር የባሕር በር አማራጭ ሊኖራት ይገባል።
በ60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የባሕር በር እያለ ኢትዮጵያ ተዘግታ ትኑር የሚል ኢፍትሐዊነት ተቀባይነት የለውም።
የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የንግድ መውጫ መግቢያ ብቻ ሳይሆን፤ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የብሔራዊ ደህንነት እና የጂኦፖለቲካ ስትራቴጂ ቁልፍ ጥያቄ በመሆኑ ጥያቄዋ መልስ እስኪያገኝ አበክራ ትሰራለች፡፡
ኢትዮጵያ የባህር በር ማግኘቷ ጥቅሙ ለእርሷ ብቻ አይደለም። በአፍሪካ ቀንድ እና በጎረቤት ሀገራት ዘንድ ከፍ ያለ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የመፍጠር ሚና ይኖረዋል፡፡
በአካባቢው የንግድ ኮሪደሮች ስለሚፈጠሩ የወደብ አገልግሎት እንዲስፋፋ፣ የተለያዩ የመሰረተ ልማት አውታሮች እንዲገነቡ በማድረግ የንግድ ትስስርና አዳዲስ የስራ ዕድሎች ለመፍጠር ያስችላል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ ከታዳሽ ኃይል የምታመነጨው ኤሌክትሪክ ለቀጣናው በበቂ ሁኔታ ማቅረቧ ኢንዱስትሪዎችን ለማስፋፋትና የካርቦን ልቀትን ለመቀነስ ይረዳል።
ከዚህ ባሻገር የቀጣናዊ ሰላምና ጸጥታን በተመለከተ የጋራ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እያደገ ሲመጣ በሀገራት መካከል ከግጭት ይልቅ ትብብር እንዲጨምር ያደርጋል። ሀገራት በንግድ፣ በኢንቨስትመንት እና በመሠረተ ልማት በተጠናከረ ሁኔታ ሲተሳሰሩ ሰላምን የመጠበቅ ፍላጎታቸውም በዛው ልክ ይጨምራል።
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት የአፍሪካ ህብረት "አጀንዳ 2063" የሚጠይቀውን ቀጣናዊ ትስስር ለማጠናከር፣ የነፃ ንግድ ቀጣና ለመመስረት እና የመሠረተ ልማት ትስስርን ለማሳካት ጠንካራ መሠረት ለመጣል ያግዛል።
በመሆኑም የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ አፋጣኝ መልስ እንዲያገኝ ለማድረግ ሀገራት፣ ዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊ እና ቀጣናዊ ተቋማት ድጋፋቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል፡፡
በቴዎድሮስ ሳህለ
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ባለፉት አስርት ዓመታት በሰላም ማስከበር፣ በግጭት አፈታት፣ በኤሌክትሪክ ኃይል ወጪ ንግድ፣ በቀጣናዊ ትስስር እና በንግድ ትብብር ረገድ ያበረከተችው አስተዋጽኦ ለጎረቤቶቿ ብሎም ለቀጣናው የምትሰጠውን ከፍ ያለ ትኩረት ያሳያል።
ኢትዮጵያ በታሪኳ የትኛውንም ጎረቤት ሀገር ወርራ አታውቅም፡፡ ከጎረቤቶቿ ጋር ያላት ግንኙነት ሰላማዊና በትብብር ላይ የተመሰረተ ሆኖ ቆይቷል፡፡
ጎረቤቶቿ ሰላም በራቃቸው ጊዜ ሁሉ፣ ሰላም ለማስከበር ቀድማ በመገኘት ትታወቃለች፡፡ ይህንንም በደቡብ ሱዳን፣ በሱዳን፣ በሶማሊያ እንዲሁም ከጎረቤቶቿ ራቅ ብላም በላይቤሪያ፣ በሩዋንዳ፣ በኮንጎ እና በሴራሊዮን በተግባር አስመስክራለች፡፡
በአህጉር ደረጃ ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ቀንበር ሲማቅቁ የነበሩ አፍሪካውያን ወንድም እህቶች ነጻ ለመውጣት የሚያደርጉትን ጥረት በስልጠና፣ በሎጂስቲክስና በዲፕሎማሲ መስክ ጭምር መደገፏ አሌ የማይባል ሃቅ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ዛሬም የልማት ትሩፋቷን ለብቻዋ ዕድገትና ለውጥ የምትጠቀም ሀገር አይደለችም፡፡ ይልቁንም ልማቷን እና ለውጧን በማጋራት እና ለጎረቤቶቿ አብሮ መለወጥ እየሰራች ትገኛለች፡፡
በአፍሪካ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል አምራች ከሆኑ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ፤ ለጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ኤሌክትሪክ እየላከች ነው።
ይህ በአካባቢው የኢንዱስትሪ ልማት፣ የከተማ እድገት እና የህዝብ ኑሮ መሻሻል ላይ ቀጥተኛ አስተዋፅኦ እያደረገ ነው።
በንግድ ረገድም ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና እና የአፍሪካ ህብረት "አጀንዳ 2063" የሚያስቀምጧቸውን የክልላዊ ውህደት ግቦች ለማሳካት የኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች፣ የድንበር ንግድ ማዕከላት እና የትራንስፖርት ኮሪደሮችን በማስፋፋት በቀጣናዊ ትስስር ማደግና መጠናከር ላይ ግዙፍ ኢንቨስትመንት እያካሄደች ነው።
ኢትዮጵያ ለጎረቤቶቿ ሰላምና ደህንነት፣ እድገትና ልማት አበክራ የሰራቻቸው ስራዎች ለቀጣናውና ለሀገራቱ ያላትን አዎንታዊ ሚና በግልፅ ያሳያል። ሀገሪቱ የባህር በር ጥያቄዋ ምላሽ ሲያገኝ ይህ ቀጣናዊ ገንቢ ሚናዋ በምን ያህል መጠን ሊያድግና ሊባዛ እንደሚችል ለመገመት አያዳግትም፡፡
በታሪክ አጋጣሚ የኢትዮጵያ ህዝብ ህጋዊ ስልጣን በሌለው አካል ህጋዊ የባሕር በር ባለቤትነቷን እንድታጣ ተደርጓል፡፡ የመደመር መንግሥት የተፈጸመውን ኢፍትሃዊና ታሪካዊ በደል በሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ የማስመለስ ጥያቄ አቅርቦ የበርካታ ሃያላን ሀገራትን ድጋፍ አግኝቷል፡፡ ኢትዮጵያ በፍጥነት እያደገ ካለው ኢኮኖሚዋና የህዝብ ቁጥሯ አንጻር የባሕር በር አማራጭ ሊኖራት ይገባል።
በ60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የባሕር በር እያለ ኢትዮጵያ ተዘግታ ትኑር የሚል ኢፍትሐዊነት ተቀባይነት የለውም።
የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የንግድ መውጫ መግቢያ ብቻ ሳይሆን፤ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የብሔራዊ ደህንነት እና የጂኦፖለቲካ ስትራቴጂ ቁልፍ ጥያቄ በመሆኑ ጥያቄዋ መልስ እስኪያገኝ አበክራ ትሰራለች፡፡
ኢትዮጵያ የባህር በር ማግኘቷ ጥቅሙ ለእርሷ ብቻ አይደለም። በአፍሪካ ቀንድ እና በጎረቤት ሀገራት ዘንድ ከፍ ያለ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የመፍጠር ሚና ይኖረዋል፡፡
በአካባቢው የንግድ ኮሪደሮች ስለሚፈጠሩ የወደብ አገልግሎት እንዲስፋፋ፣ የተለያዩ የመሰረተ ልማት አውታሮች እንዲገነቡ በማድረግ የንግድ ትስስርና አዳዲስ የስራ ዕድሎች ለመፍጠር ያስችላል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ ከታዳሽ ኃይል የምታመነጨው ኤሌክትሪክ ለቀጣናው በበቂ ሁኔታ ማቅረቧ ኢንዱስትሪዎችን ለማስፋፋትና የካርቦን ልቀትን ለመቀነስ ይረዳል።
ከዚህ ባሻገር የቀጣናዊ ሰላምና ጸጥታን በተመለከተ የጋራ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እያደገ ሲመጣ በሀገራት መካከል ከግጭት ይልቅ ትብብር እንዲጨምር ያደርጋል። ሀገራት በንግድ፣ በኢንቨስትመንት እና በመሠረተ ልማት በተጠናከረ ሁኔታ ሲተሳሰሩ ሰላምን የመጠበቅ ፍላጎታቸውም በዛው ልክ ይጨምራል።
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት የአፍሪካ ህብረት "አጀንዳ 2063" የሚጠይቀውን ቀጣናዊ ትስስር ለማጠናከር፣ የነፃ ንግድ ቀጣና ለመመስረት እና የመሠረተ ልማት ትስስርን ለማሳካት ጠንካራ መሠረት ለመጣል ያግዛል።
በመሆኑም የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ አፋጣኝ መልስ እንዲያገኝ ለማድረግ ሀገራት፣ ዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊ እና ቀጣናዊ ተቋማት ድጋፋቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል፡፡
በቴዎድሮስ ሳህለ
12 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ኢራን አሜሪካ ጥቃቷን እስካቆመች ድረስ አጸፋዊ ወታደራዊ እርምጃዎችን እንደምታቆም ማስታወቋን ተከትሎ፣ የዓለም የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ አሽቆልቁሏል። ዓለም አቀፉ የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ በ5 በመቶ በማሽቆልቆል በርሜሉ 91.97 ዶላር የገባ ሲሆን፣ የአሜሪካው ደብሊው ቲ አይ በተመሳሳይ ወደ 84.67 ዶላር ወርዷል። ይህ መርገብ ላለፉት ሁለት ሳምንታት እያሻቀበ የመጣውን የጦርነት ስጋት በተወሰነ መልኩ አቅልሎታል።
የዚህ ጊዜያዊ የተኩስ አቁም መነሻ ግን በአሜሪካ መንግስት በኩል እርስ በርሱ የሚጋጭ ትርክት እንዲፈጠር አድርጓል። የተባበሩት መንግስታት የአሜሪካ አምባሳደር ማይክ ዋልትዝ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ጥቃቱን ያቆሙት "ለዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች ዕድል ለመስጠት" ነው ሲሉ ለፎክስ ኒውስ ተናግረዋል። ይሁን እንጂ የሮይተርስ እና የውስጥ አዋቂዎች መረጃ እንደሚያሳየው፣ ዋሽንግተን ይህንን ውሳኔ ያሳለፈችው የጦር ኃይሉ ሊመታቸው የሚችሉ ኢላማዎች በማለቃቸው እና የአሜሪካ የመሳሪያ ክምችት እየተመናመነ ነው የሚል ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ከአማካሪዎች በመቅረቡ ነው።
በሌላ በኩል ኢራን "ጥቃት በጥቃት" የሚለውን መርህ አጥብቃ ይዛለች። አሜሪካ ካቆመች እኛም እናቆማለን የሚለው መልዕክቷ፣ የተኩስ አቁሙ የተመሰረተው በዲፕሎማሲያዊ ስምምነት ሳይሆን በጊዜያዊ የኃይል ሚዛን መፈተሽ ላይ መሆኑን ያሳያል።
ይህ የጂኦፖለቲካዊ ውጥረት ማብረድ በዓለም ኢኮኖሚ ላይ የፈጠረው ቅጽበታዊ እፎይታ አለ። የኤችኤስቢሲ ስትራቴጂስት ዲራጅ ናሩላ እንዳስገነዘቡት፣ የነዳጅ ዋጋ መናር የአሜሪካ ማዕከላዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲውን ይበልጥ እንዲያጠብ ያስገድደዋል የሚለውን ስጋት አሁን ላይ አርግቦታል። ሆኖም የሁለቱ ሀገራት ሰላም በስስ ገመድ ላይ የተንጠለጠለ እና በማንኛውም ጊዜ ሊቀለበስ የሚችል በመሆኑ፣ የነዳጅ ገበያውም ሆነ የዓለም ኢኮኖሚ አሁንም ከስጋት ቀጠና አልወጡም።
የዚህ ጊዜያዊ የተኩስ አቁም መነሻ ግን በአሜሪካ መንግስት በኩል እርስ በርሱ የሚጋጭ ትርክት እንዲፈጠር አድርጓል። የተባበሩት መንግስታት የአሜሪካ አምባሳደር ማይክ ዋልትዝ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ጥቃቱን ያቆሙት "ለዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች ዕድል ለመስጠት" ነው ሲሉ ለፎክስ ኒውስ ተናግረዋል። ይሁን እንጂ የሮይተርስ እና የውስጥ አዋቂዎች መረጃ እንደሚያሳየው፣ ዋሽንግተን ይህንን ውሳኔ ያሳለፈችው የጦር ኃይሉ ሊመታቸው የሚችሉ ኢላማዎች በማለቃቸው እና የአሜሪካ የመሳሪያ ክምችት እየተመናመነ ነው የሚል ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ከአማካሪዎች በመቅረቡ ነው።
በሌላ በኩል ኢራን "ጥቃት በጥቃት" የሚለውን መርህ አጥብቃ ይዛለች። አሜሪካ ካቆመች እኛም እናቆማለን የሚለው መልዕክቷ፣ የተኩስ አቁሙ የተመሰረተው በዲፕሎማሲያዊ ስምምነት ሳይሆን በጊዜያዊ የኃይል ሚዛን መፈተሽ ላይ መሆኑን ያሳያል።
ይህ የጂኦፖለቲካዊ ውጥረት ማብረድ በዓለም ኢኮኖሚ ላይ የፈጠረው ቅጽበታዊ እፎይታ አለ። የኤችኤስቢሲ ስትራቴጂስት ዲራጅ ናሩላ እንዳስገነዘቡት፣ የነዳጅ ዋጋ መናር የአሜሪካ ማዕከላዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲውን ይበልጥ እንዲያጠብ ያስገድደዋል የሚለውን ስጋት አሁን ላይ አርግቦታል። ሆኖም የሁለቱ ሀገራት ሰላም በስስ ገመድ ላይ የተንጠለጠለ እና በማንኛውም ጊዜ ሊቀለበስ የሚችል በመሆኑ፣ የነዳጅ ገበያውም ሆነ የዓለም ኢኮኖሚ አሁንም ከስጋት ቀጠና አልወጡም።
12 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በጸጥታ እና ጂኦፖለቲካዊ ቀውሶች ምክንያት ከ6 እስከ 7 ዓመታት ገደማ ተጓትቶ የነበረው የኬፊ ጎልድ ኤንድ ኮፐር ኩባንያ 'የቱሉ ካፒ' የወርቅ ማዕድን ፕሮጀክት በመጨረሻም ወደ ግንባታ ምዕራፍ መግባቱ ተገለጸ።
ከአዲስ አበባ 360 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምዕራብ ኢትዮጵያ የሚገኘው ይህ ፕሮጀክት፣ ከ400 ሚሊዮን ዶላር በላይ የፋይናንስ ፓኬጅ የተመደበለት ሲሆን (የኢትዮጵያ መንግስት 20 ሚሊዮን ዶላር በማዋጣት የ17 በመቶ ድርሻ ይዟል)፣ በዓመት 166 ሺህ አውንስ ወርቅ የማምረት አቅም ይኖረዋል። ማዕድን ማውጣቱ ክፍት እና ከመሬት በታች የማውጣት ዘዴዎችን አጣምሮ የሚጠቀም ሲሆን፣ በ2027 መገባደጃ ላይ ስራ ጀምሮ በ2028 ሙሉ የማምረት አቅሙ ላይ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።
የኩባንያው ስራ አስፈፃሚ ሃሪ አናግኖስታራስ-አዳምስ እንዳሉት፤ ይህ "ስትራቴጂካዊ የኢትዮጵያ ፕሮጀክት" አሁን ላይ 1 በመቶ ብቻ ያለውን የማዕድን ዘርፉን የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) አስተዋፅኦ በቀጣዩ አስርት ዓመት ውስጥ ወደ 10 በመቶ ለማሳደግ ለታለመው የመንግስት ዕቅድ ትልቅ ሚና ይጫወታል።
ይሁን እንጂ ኢትዮጵያ ይህንን እጅግ ከፍተኛ ሆነ የኢኮኖሚ ዕቅድ ለማሳካትና ማዕድን ዘርፉን እንደ አውስትራሊያ ለማሳደግ፣ እንደ ቱሉ ካፒ ፕሮጀክት ያጋጠማቸው ዓይነት የጸጥታ መደፍረስና የዓመታት መጓተት ዳግም እንዳይከሰት አስተማማኝ ሰላም ማረጋገጥ ዋነኛ ፈተናዋ ሆኖ ይቀጥላል። ፕሮጀክቱ ትርፋማነቱ (በተለይ አሁን ባለው የዓለም የወርቅ ዋጋ መጨመር) እጅግ አጓጊ ቢሆንም፣ ቀጣይነቱ የሚወሰነው በመሬት ላይ ባለው ፖለቲካዊ እና የጸጥታ መረጋጋት ላይ መሆኑን ባለሙያዎች ለዘ-ሐበሻ ተናግረዋል።
ከአዲስ አበባ 360 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምዕራብ ኢትዮጵያ የሚገኘው ይህ ፕሮጀክት፣ ከ400 ሚሊዮን ዶላር በላይ የፋይናንስ ፓኬጅ የተመደበለት ሲሆን (የኢትዮጵያ መንግስት 20 ሚሊዮን ዶላር በማዋጣት የ17 በመቶ ድርሻ ይዟል)፣ በዓመት 166 ሺህ አውንስ ወርቅ የማምረት አቅም ይኖረዋል። ማዕድን ማውጣቱ ክፍት እና ከመሬት በታች የማውጣት ዘዴዎችን አጣምሮ የሚጠቀም ሲሆን፣ በ2027 መገባደጃ ላይ ስራ ጀምሮ በ2028 ሙሉ የማምረት አቅሙ ላይ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።
የኩባንያው ስራ አስፈፃሚ ሃሪ አናግኖስታራስ-አዳምስ እንዳሉት፤ ይህ "ስትራቴጂካዊ የኢትዮጵያ ፕሮጀክት" አሁን ላይ 1 በመቶ ብቻ ያለውን የማዕድን ዘርፉን የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) አስተዋፅኦ በቀጣዩ አስርት ዓመት ውስጥ ወደ 10 በመቶ ለማሳደግ ለታለመው የመንግስት ዕቅድ ትልቅ ሚና ይጫወታል።
ይሁን እንጂ ኢትዮጵያ ይህንን እጅግ ከፍተኛ ሆነ የኢኮኖሚ ዕቅድ ለማሳካትና ማዕድን ዘርፉን እንደ አውስትራሊያ ለማሳደግ፣ እንደ ቱሉ ካፒ ፕሮጀክት ያጋጠማቸው ዓይነት የጸጥታ መደፍረስና የዓመታት መጓተት ዳግም እንዳይከሰት አስተማማኝ ሰላም ማረጋገጥ ዋነኛ ፈተናዋ ሆኖ ይቀጥላል። ፕሮጀክቱ ትርፋማነቱ (በተለይ አሁን ባለው የዓለም የወርቅ ዋጋ መጨመር) እጅግ አጓጊ ቢሆንም፣ ቀጣይነቱ የሚወሰነው በመሬት ላይ ባለው ፖለቲካዊ እና የጸጥታ መረጋጋት ላይ መሆኑን ባለሙያዎች ለዘ-ሐበሻ ተናግረዋል።
14 days ago
ለባሕር በር ጥያቄው ምላሽ የተደመረ ዕይታና ጽኑ አቋም
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ያስመዘገበችው ፈጣን የኢኮኖሚ እድገትና የልማት ምዕራፎች ሀገሪቱን በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና የዕድገት ማዕከል እንድትሆን አድርገዋታል፡፡
ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላትና ግዙፍ ሰላም አስከባሪ ሠራዊት የገነባችው ሀገር፣ የኢኮኖሚ እጇን በዘላቂነት ለማጽናት እና የሉዓላዊነት ዋስትናዋን ለማረጋገጥ የባሕር በር ተጠቃሚነትን እንደ አንድ የህልውና አጀንዳ አድርጋ በመያዝ ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ገብታለች።
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ከታሪካዊ እውነታዎች፣ ከመልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ እና ከፍትሃዊ የንግድ መርሆዎች ጋር የተያያዘ የብሔራዊ ጥቅም ማዕከል መሆኑ ተደጋግሞ ተገልጿል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) «ማንም ፈለገም አልፈለገም ኢትዮጵያ ተዘግታ አትኖርም» በሚል ያነሱት ሀሳብ የመደመር መንግሥት አጀንዳውን ከነበረበት የመሸፋፈን አባዜ በማውጣት የሀገሪቱ ዋና የጂኦፖለቲካዊ አጀንዳ አድርጎታል፡፡
ፍትሃዊ የባሕር በር ባለቤትነት በቀጣናው ሁለንተናዊ ሰላምን፣ መረጋጋትን እና የኢኮኖሚ ትስስርን ለማረጋገጥ ቁልፍ ሚና የሚጫወት በመሆኑ ጥያቄው በንግግርና በሰላማዊ መንገድ እውን ሊሆን ይገባል።
ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ካለው ልምምድና መርሕ ውጪ በታሪካዊ ስሕተቶች እና ጠላቶች በሸረቡት ፖለቲካዊ ሴራ የባሕር በር አጥታለች።
ለሺህ ዓመታት የባሕር በር ባለቤት የነበረችው ሀገር በ30 ዓመታት አጭር ስሑት ትርክት ምክንያት ከባሕር በር እርቃ እንደማትቀጥልም እርግጥ ሆኗል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የባሕር በር ጉዳይን የብሔራዊ ጥቅም ዋነኛ ማጠንጠኛ ማዕከል እንዲሆንና ኢትዮጵያዊያን በአንድነት እንዲቆሙ ከማድረግ አንጻር የአንበሳውን ድርሻ ተወጥተዋል፡፡
ኢትዮጵያ ፍትሃዊ የባሕር በር ተጠቃሚነትን በምክክርና ሰጥቶ በመቀበል መርሕ ለማረጋገጥ የጀመረችው ጥረትም ዓለም አቀፍ እውቅና እየተቸረው ይገኛል፡፡
ኢትዮጵያ በቀጣናው በተለይም ሽብርተኝነት ከመከላከልና የሰላም ማስከበር ተልዕኮን በስኬት ከማከናወን አንጻር ጉልህ ሚና እየተጫወተች ነው፡፡ ለዚህም የዘመኑን የዋጀ ቴክኖሎጂ የታጠቀ እና አስፈላጊውን ወታደራዊ ግዳጅ መፈጸም የሚችል ግዙፍ መከላከያ ገንብታለች፡፡
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ከሀገር ዳርቻ አልፎ ለቀጣናው ሰላምና መረጋጋት የቆመ የታማኝነትና የጥንካሬ ተምሳሌት መሆኑም ይታወቃል፡፡
ኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘቷም በቀጣናው ያለውን ሰላም በዘላቂነት ለማስፈን ብሎም በሰላም ማስከበር ተልዕኮ ያላትን አፈጻጸም በእጅጉ ያሳድጋል፡፡
በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት የሀገርን ኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን የሚወስን ቁልፍ የብሔራዊ ጥቅምና የሕልውና ጉዳይ መሆኑ እሙን ነው፡፡
በታሪክ አጋጣሚ ታሪካዊ ጠላቶች ኢትዮጵያን ከቀይ ባሕር ለማራቅ የውስጥ ባንዳዎችን በማሰለፍ ጭምር የሸረቡትን ሴራና የተሳሳተ ስሌት ከመሰረቱ ለመናድ የተጀመረው ጥረት በርካታ ውጤቶችን እያስገኘ ነው፡፡
ለባሕር በር ጥያቄው ምላሽ ለማግኘትም ኢትዮጵያውያን በብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ ላይ ያሳዩት የተደመረ ዕይታና ጽኑ አቋም ትልቅ እመርታ ሆኗል፡፡
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ያስመዘገበችው ፈጣን የኢኮኖሚ እድገትና የልማት ምዕራፎች ሀገሪቱን በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና የዕድገት ማዕከል እንድትሆን አድርገዋታል፡፡
ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላትና ግዙፍ ሰላም አስከባሪ ሠራዊት የገነባችው ሀገር፣ የኢኮኖሚ እጇን በዘላቂነት ለማጽናት እና የሉዓላዊነት ዋስትናዋን ለማረጋገጥ የባሕር በር ተጠቃሚነትን እንደ አንድ የህልውና አጀንዳ አድርጋ በመያዝ ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ገብታለች።
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ከታሪካዊ እውነታዎች፣ ከመልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ እና ከፍትሃዊ የንግድ መርሆዎች ጋር የተያያዘ የብሔራዊ ጥቅም ማዕከል መሆኑ ተደጋግሞ ተገልጿል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) «ማንም ፈለገም አልፈለገም ኢትዮጵያ ተዘግታ አትኖርም» በሚል ያነሱት ሀሳብ የመደመር መንግሥት አጀንዳውን ከነበረበት የመሸፋፈን አባዜ በማውጣት የሀገሪቱ ዋና የጂኦፖለቲካዊ አጀንዳ አድርጎታል፡፡
ፍትሃዊ የባሕር በር ባለቤትነት በቀጣናው ሁለንተናዊ ሰላምን፣ መረጋጋትን እና የኢኮኖሚ ትስስርን ለማረጋገጥ ቁልፍ ሚና የሚጫወት በመሆኑ ጥያቄው በንግግርና በሰላማዊ መንገድ እውን ሊሆን ይገባል።
ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ካለው ልምምድና መርሕ ውጪ በታሪካዊ ስሕተቶች እና ጠላቶች በሸረቡት ፖለቲካዊ ሴራ የባሕር በር አጥታለች።
ለሺህ ዓመታት የባሕር በር ባለቤት የነበረችው ሀገር በ30 ዓመታት አጭር ስሑት ትርክት ምክንያት ከባሕር በር እርቃ እንደማትቀጥልም እርግጥ ሆኗል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የባሕር በር ጉዳይን የብሔራዊ ጥቅም ዋነኛ ማጠንጠኛ ማዕከል እንዲሆንና ኢትዮጵያዊያን በአንድነት እንዲቆሙ ከማድረግ አንጻር የአንበሳውን ድርሻ ተወጥተዋል፡፡
ኢትዮጵያ ፍትሃዊ የባሕር በር ተጠቃሚነትን በምክክርና ሰጥቶ በመቀበል መርሕ ለማረጋገጥ የጀመረችው ጥረትም ዓለም አቀፍ እውቅና እየተቸረው ይገኛል፡፡
ኢትዮጵያ በቀጣናው በተለይም ሽብርተኝነት ከመከላከልና የሰላም ማስከበር ተልዕኮን በስኬት ከማከናወን አንጻር ጉልህ ሚና እየተጫወተች ነው፡፡ ለዚህም የዘመኑን የዋጀ ቴክኖሎጂ የታጠቀ እና አስፈላጊውን ወታደራዊ ግዳጅ መፈጸም የሚችል ግዙፍ መከላከያ ገንብታለች፡፡
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ከሀገር ዳርቻ አልፎ ለቀጣናው ሰላምና መረጋጋት የቆመ የታማኝነትና የጥንካሬ ተምሳሌት መሆኑም ይታወቃል፡፡
ኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘቷም በቀጣናው ያለውን ሰላም በዘላቂነት ለማስፈን ብሎም በሰላም ማስከበር ተልዕኮ ያላትን አፈጻጸም በእጅጉ ያሳድጋል፡፡
በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነት የሀገርን ኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን የሚወስን ቁልፍ የብሔራዊ ጥቅምና የሕልውና ጉዳይ መሆኑ እሙን ነው፡፡
በታሪክ አጋጣሚ ታሪካዊ ጠላቶች ኢትዮጵያን ከቀይ ባሕር ለማራቅ የውስጥ ባንዳዎችን በማሰለፍ ጭምር የሸረቡትን ሴራና የተሳሳተ ስሌት ከመሰረቱ ለመናድ የተጀመረው ጥረት በርካታ ውጤቶችን እያስገኘ ነው፡፡
ለባሕር በር ጥያቄው ምላሽ ለማግኘትም ኢትዮጵያውያን በብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ ላይ ያሳዩት የተደመረ ዕይታና ጽኑ አቋም ትልቅ እመርታ ሆኗል፡፡
Sponsored by
Surafel
18 days ago
ወሳኙ የንግድ መስመር ቀይ ባህር !!
በኢራን የሚደገፉት የየመን ሁቲ ኃይሎች የሳውዲ አረቢያ መርከቦች የባሕር እንቅስቃሴ ላይ እገዳ አወጁ።
ቡድኑ እገዳውን ያወጀው ሳውዲ አረቢያ በየመን ላይ "ኢፍትሃዊና ጨቋኝ ከበባ እየጣለች ነው" በሚል ክስ ነው።
የቀይባሕር ዋነኛ መተላለፊያ ባብ አል-መንደብ ሰርጥ ለሳውዲ መርከቦች እንደሚዘጋ ሁቲዎች አስታውቀዋል።
ይህ ከ2022 ጀምሮ በተመድ ድጋፍ ሲቆይ የነበረውን የተኩስ አቁም ስምምነት የሚያዳክም እርምጃ መሆኑ ተጠቁሟል።
እገዳው የመጣው በሁቲዎች ቁጥጥር ስር ባለው የሳና አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ከተፈጸመ ጥቃት በኋላ ነው።
የየመን መንግሥት የኢራና አውሮፕላን እንዳያርፍ ለመከላከል " ጥቃቱን ፈጽሜያለሁ " ቢልም ፤ ሁቲዎች ግን ሳውዲን ተጠያቂ በማድረግ የሚሳይል ጥቃት ከፍተው አሁን ደግሞ የባሕር ላይ እንቅስቃሴ እገዳ አውጀዋል።
ባብ አል-መንደብ ሙሉ በሙሉ ከተዘጋ የዓለም የነዳጅ አቅርቦት እስከ 7 በመቶ ሊቀንስ፤ በቀይ ባሕር የሚካሄደውን የንግድ መጓጓዣ እና የኃይል አቅርቦት በከፍተኛ ሁኔታ ሊያውክ ይችላል።
የየመን ሁቲዎች የባሕር ላይ እንቅስቃሴ እገዳ በቀጠናው እየተባባሰ ካለው የጂኦፖለቲካ ውጥረት ጋር የተያያዘ መሆኑ እየተነገረ ነው።
ኢራን በመሠረተ ልማቶቿ ላይ ለሚፈጸመው የእነ አሜሪካ ወታደራዊ ጥቃት ምላሽ እንዲሆን፣ ሁቲዎች የምዕራባውያንና የባሕረ ሰላጤ ሀገራት የመርከብ መጓጓዣ ወሳኝ መተላለፊያዎችን እንዲያውኩ ሁቲዎችን " ግፊት አድርጋባቸዋለች ም" ተብሏል።
Seledadotio
Seledadotio
በኢራን የሚደገፉት የየመን ሁቲ ኃይሎች የሳውዲ አረቢያ መርከቦች የባሕር እንቅስቃሴ ላይ እገዳ አወጁ።
ቡድኑ እገዳውን ያወጀው ሳውዲ አረቢያ በየመን ላይ "ኢፍትሃዊና ጨቋኝ ከበባ እየጣለች ነው" በሚል ክስ ነው።
የቀይባሕር ዋነኛ መተላለፊያ ባብ አል-መንደብ ሰርጥ ለሳውዲ መርከቦች እንደሚዘጋ ሁቲዎች አስታውቀዋል።
ይህ ከ2022 ጀምሮ በተመድ ድጋፍ ሲቆይ የነበረውን የተኩስ አቁም ስምምነት የሚያዳክም እርምጃ መሆኑ ተጠቁሟል።
እገዳው የመጣው በሁቲዎች ቁጥጥር ስር ባለው የሳና አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ከተፈጸመ ጥቃት በኋላ ነው።
የየመን መንግሥት የኢራና አውሮፕላን እንዳያርፍ ለመከላከል " ጥቃቱን ፈጽሜያለሁ " ቢልም ፤ ሁቲዎች ግን ሳውዲን ተጠያቂ በማድረግ የሚሳይል ጥቃት ከፍተው አሁን ደግሞ የባሕር ላይ እንቅስቃሴ እገዳ አውጀዋል።
ባብ አል-መንደብ ሙሉ በሙሉ ከተዘጋ የዓለም የነዳጅ አቅርቦት እስከ 7 በመቶ ሊቀንስ፤ በቀይ ባሕር የሚካሄደውን የንግድ መጓጓዣ እና የኃይል አቅርቦት በከፍተኛ ሁኔታ ሊያውክ ይችላል።
የየመን ሁቲዎች የባሕር ላይ እንቅስቃሴ እገዳ በቀጠናው እየተባባሰ ካለው የጂኦፖለቲካ ውጥረት ጋር የተያያዘ መሆኑ እየተነገረ ነው።
ኢራን በመሠረተ ልማቶቿ ላይ ለሚፈጸመው የእነ አሜሪካ ወታደራዊ ጥቃት ምላሽ እንዲሆን፣ ሁቲዎች የምዕራባውያንና የባሕረ ሰላጤ ሀገራት የመርከብ መጓጓዣ ወሳኝ መተላለፊያዎችን እንዲያውኩ ሁቲዎችን " ግፊት አድርጋባቸዋለች ም" ተብሏል።
Seledadotio
Seledadotio
23 days ago
በሰማይ ላይ ለሚያንዣብቡ አሞራዎች የማይበተን የኢትዮጵያ አንድነት
*********************
(የዕለቱ መልዕክት)
የኢትዮጵያ ታሪክ የትግል፣ የጽናት እና የጥልቅ ኅብረት ደማቅ ሸራ ነው።
ይህች ሀገር በታሪኳ በርካታ ውጣ ውረዶችን አልፋለች፤ ሆኖም የገዛ ልጆቿ በውስጣዊ አለመግባባት ክፍተት በፈጠሩ ቁጥር፣ ታሪካዊ ጠላቶቿ አጋጣሚውን ሲጠብቁና ሲያደቡ መኖራቸው የዘመናት ሐቅ ነው።
ይህ እውነት ዛሬም መልኩን ቀይሮ፣ በዘመናዊ የጂኦፖለቲካ ትርክት ተጠቅልሎ በደጃፋችን ቆሟል።
ሀገራዊ የልማት ውጥኖችን ስንጀምር፣ ትልልቅ ፕሮጀክቶችን ስንገነባና ከተሞቻችንን ስናዘምን ድምጻቸው የማይሰማ፣ አንዳች አስተዋጽኦ የማያደርጉ የውጭ ኃይሎች፣ በውስጣዊ ልዩነቶች ስንፋጠጥ ግን ከየት መጡ ሳይባሉ የጣልቃ ገብነት እጃቸውን ሲዘረጉ፣ የጥፋት መሣሪያና የፕሮፓጋንዳ ድጋፍ ሲያቀብሉ ማየት የተለመደ ሆኗል።
እንደ ሀገር ትልቁ ፈተናችንና ድክመታችን የሚመነጨው ከራሳችን የውስጥ ክፍተት ነው። ከጉንደት እስከ ጉራ፣ ከዓድዋ እስከ ማይጨው፣ ከካራማራ እስከ ባድመ ያለውን ታሪካችንን ስንፈትሽ፤ ጠላቶቻችን ሁልጊዜም የሚንቀሳቀሱት የእኛን መነታረክ ተከትለው ነው።
ታላቋን ሀገር የጂኦግራፊ እስረኛ ያደረጋት፣ የባለቤትነት መብቷን የነጠቃትና ቀይ ባሕርን የመሰለ ስትራቴጂያዊ ሀብት ያሳጣን ይኸው የውስጥ መከፋፈል ያመጣው የታሪክ ስህተት ነው።
ዛሬም ቢሆን የትኛውም የውስጥ ጉዳይ ቢያከራክረን መፍትሔው በእኛው መካከል በጠረጴዛ ዙሪያ በመነጋገር መፈታት አለበት።
ለውጭ ኃይሎች መጠቀሚያ የሚሆን ቀዳዳ መክፈት፣ በታሪክ ፊት እንክርዳድ ሆኖ ከመታየትና የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ ከመስጠት የተለየ ትርጉም የለውም።
ይህንኑ ጉዳይ አስመልክተው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልዕክት፣ የሀገራችንን ወቅታዊ የፖለቲካ ትርታና የሉዓላዊነት አቋም በጥልቅ የሚያንጸባርቅ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የውጭ ጣልቃ ገብነትን በጠንባሮ አባቶች የከብትና የአሞራ ብሂል በሚገርም አገላለጽ መስለውታል።
"በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ ለሚያንዣብቡ አሞራዎች ያለኝ መልዕክት ከብቱን መርጠን የምንገዛ እኛ ነን፤ የቅርጫውን ባለቤት የምንወስን እኛ ነን፤ የተረፈንን፣ የማንፈልገውን ካልሆነ በቀር የትኛውም አሞራ በጉልበት ከየትኛውም ቅርጫ መደብ ላይ አንዲት ኪሎ ስጋ መውሰድ እንደማይችል ላረጋግጥላቸው እፈልጋለሁ" በማለት የማያወላዳ አቋማቸውን አስረግጠው ተናግረዋል።
ይህ ጥልቅ መልዕክት ኢትዮጵያ የራሷን ዕድል በራሷ የመወሰን ሙሉ መብት እንዳላት እና ማንም በጉልበት ሊነጥቃት የሚችለው ሀብትም ሆነ ጥቅም እንደሌለ የተላለፈ ግልጽ መልዕክት ነው።
በመሆኑም በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የሚያንዣብቡ ዘመናዊ "አሞራዎች" ሊገነዘቡት የሚገባ አንድ ሐቅ አለ። ኢትዮጵያ በቀላሉ የምትበጠስ፣ በውጭ ፕሮፓጋንዳ ጫጫታ የምትዘናጋና ብሔራዊ ጥቅሟን አሳልፋ የምትሰጥ ደካማ ሀገር አይደለችም።
ለዘመናት በማይበጠስ ጠንካራ ገመድ የተሰናሰለች፣ የጸናች ሀገር ናት። የውጭ ኃይሎች የሀገራችንን እውነተኛ የጥንካሬ ታሪክ ወደ ኋላ መለስ ብለው በማንበብ፣ ከጣልቃ ገብነት ምኞታቸው ታቅበው ለጋራ ጥቅም በጋራ ለመሥራት ራሳቸውን ማዘጋጀት አለባቸው።
እኛም ኢትዮጵያውያን፣ የውስጥ ልዩነቶቻችንን በሠለጠነ የውይይት መንገድ እየፈታን፣ ሀገራችንን ከሚያንዣብቡ ታሪካዊ ጠላቶች በኅብረት ልንጠብቃት ግድ ይለናል። ያደፈጠው አሞራ ስሌት የሚከሽፈው፣ የእኛ ውስጣዊ አንድነት ሲጸና ብቻ ነውና።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
*********************
(የዕለቱ መልዕክት)
የኢትዮጵያ ታሪክ የትግል፣ የጽናት እና የጥልቅ ኅብረት ደማቅ ሸራ ነው።
ይህች ሀገር በታሪኳ በርካታ ውጣ ውረዶችን አልፋለች፤ ሆኖም የገዛ ልጆቿ በውስጣዊ አለመግባባት ክፍተት በፈጠሩ ቁጥር፣ ታሪካዊ ጠላቶቿ አጋጣሚውን ሲጠብቁና ሲያደቡ መኖራቸው የዘመናት ሐቅ ነው።
ይህ እውነት ዛሬም መልኩን ቀይሮ፣ በዘመናዊ የጂኦፖለቲካ ትርክት ተጠቅልሎ በደጃፋችን ቆሟል።
ሀገራዊ የልማት ውጥኖችን ስንጀምር፣ ትልልቅ ፕሮጀክቶችን ስንገነባና ከተሞቻችንን ስናዘምን ድምጻቸው የማይሰማ፣ አንዳች አስተዋጽኦ የማያደርጉ የውጭ ኃይሎች፣ በውስጣዊ ልዩነቶች ስንፋጠጥ ግን ከየት መጡ ሳይባሉ የጣልቃ ገብነት እጃቸውን ሲዘረጉ፣ የጥፋት መሣሪያና የፕሮፓጋንዳ ድጋፍ ሲያቀብሉ ማየት የተለመደ ሆኗል።
እንደ ሀገር ትልቁ ፈተናችንና ድክመታችን የሚመነጨው ከራሳችን የውስጥ ክፍተት ነው። ከጉንደት እስከ ጉራ፣ ከዓድዋ እስከ ማይጨው፣ ከካራማራ እስከ ባድመ ያለውን ታሪካችንን ስንፈትሽ፤ ጠላቶቻችን ሁልጊዜም የሚንቀሳቀሱት የእኛን መነታረክ ተከትለው ነው።
ታላቋን ሀገር የጂኦግራፊ እስረኛ ያደረጋት፣ የባለቤትነት መብቷን የነጠቃትና ቀይ ባሕርን የመሰለ ስትራቴጂያዊ ሀብት ያሳጣን ይኸው የውስጥ መከፋፈል ያመጣው የታሪክ ስህተት ነው።
ዛሬም ቢሆን የትኛውም የውስጥ ጉዳይ ቢያከራክረን መፍትሔው በእኛው መካከል በጠረጴዛ ዙሪያ በመነጋገር መፈታት አለበት።
ለውጭ ኃይሎች መጠቀሚያ የሚሆን ቀዳዳ መክፈት፣ በታሪክ ፊት እንክርዳድ ሆኖ ከመታየትና የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ ከመስጠት የተለየ ትርጉም የለውም።
ይህንኑ ጉዳይ አስመልክተው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልዕክት፣ የሀገራችንን ወቅታዊ የፖለቲካ ትርታና የሉዓላዊነት አቋም በጥልቅ የሚያንጸባርቅ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የውጭ ጣልቃ ገብነትን በጠንባሮ አባቶች የከብትና የአሞራ ብሂል በሚገርም አገላለጽ መስለውታል።
"በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ ለሚያንዣብቡ አሞራዎች ያለኝ መልዕክት ከብቱን መርጠን የምንገዛ እኛ ነን፤ የቅርጫውን ባለቤት የምንወስን እኛ ነን፤ የተረፈንን፣ የማንፈልገውን ካልሆነ በቀር የትኛውም አሞራ በጉልበት ከየትኛውም ቅርጫ መደብ ላይ አንዲት ኪሎ ስጋ መውሰድ እንደማይችል ላረጋግጥላቸው እፈልጋለሁ" በማለት የማያወላዳ አቋማቸውን አስረግጠው ተናግረዋል።
ይህ ጥልቅ መልዕክት ኢትዮጵያ የራሷን ዕድል በራሷ የመወሰን ሙሉ መብት እንዳላት እና ማንም በጉልበት ሊነጥቃት የሚችለው ሀብትም ሆነ ጥቅም እንደሌለ የተላለፈ ግልጽ መልዕክት ነው።
በመሆኑም በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የሚያንዣብቡ ዘመናዊ "አሞራዎች" ሊገነዘቡት የሚገባ አንድ ሐቅ አለ። ኢትዮጵያ በቀላሉ የምትበጠስ፣ በውጭ ፕሮፓጋንዳ ጫጫታ የምትዘናጋና ብሔራዊ ጥቅሟን አሳልፋ የምትሰጥ ደካማ ሀገር አይደለችም።
ለዘመናት በማይበጠስ ጠንካራ ገመድ የተሰናሰለች፣ የጸናች ሀገር ናት። የውጭ ኃይሎች የሀገራችንን እውነተኛ የጥንካሬ ታሪክ ወደ ኋላ መለስ ብለው በማንበብ፣ ከጣልቃ ገብነት ምኞታቸው ታቅበው ለጋራ ጥቅም በጋራ ለመሥራት ራሳቸውን ማዘጋጀት አለባቸው።
እኛም ኢትዮጵያውያን፣ የውስጥ ልዩነቶቻችንን በሠለጠነ የውይይት መንገድ እየፈታን፣ ሀገራችንን ከሚያንዣብቡ ታሪካዊ ጠላቶች በኅብረት ልንጠብቃት ግድ ይለናል። ያደፈጠው አሞራ ስሌት የሚከሽፈው፣ የእኛ ውስጣዊ አንድነት ሲጸና ብቻ ነውና።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
24 days ago
የታሪክ ስህተቶችን በማረም ለነገይቱ ጠንካራ ኢትዮጵያ መሠረት የሚጥለው ሀገራዊ ምክክር
*******************
ታሪካዊው የሀገራዊ ምክክር ዋና ጉባኤ በስኬት እንዲጠናቀቅ እና ዘላቂ ውጤት እንዲያመጣ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልዕክት ለውይይቱ መነሻ የሚሆን ጠንካራ እሳቤን ይዟል።
ይህ መልዕክት የኢትዮጵያ የትናንት ሕመም፣ የዛሬ ፈተና እና የነገ ተስፋ በግልጽ የተንጸባረቀበት ነው።
የውስጥ ድክመት እና የውጭ ጣልቃ ገብነት አንደምታ
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሀገራችን ውስጣዊ ክፍተቶች ምክንያት የሚመጡ የውጭ ጣልቃ ገብነቶችን እና የጂኦፖለቲካ አደጋዎችን በምሳሌ አስረድተዋል።
የዚህ መልዕክት ትልቁ አንደምታ ግልጽ ነው፤ እኛ እርስ በርሳችን በውስጥ ጉዳዮቻችን ስንጨቃጨቅ እና ስንወዛገብ፣ የውጭ ኃይሎች መዳከማችንን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም የራሳቸውን ፍላጎትና ጥቅም በላያችን ላይ ይጭናሉ።
ይህን እውነት ለማሳየትም ታሪካዊ ስህተቶቻችንን አስታውሰዋል። ቀደም ባሉ ጊዜያት ልዩነቶቻችንን በውይይት መፍታት አለመቻላችን እና ውስጣዊ አንድነታችን መላላቱ ኢትዮጵያ ቀይ ባሕርን እንድታጣ አድርጓታል።
ይህም በታሪክ "የጂኦግራፊ እስረኛ" እንድንሆን አድርጎናል። የዚህ ታሪካዊ እውነት አንደምታ፣ የውስጥ መከፋፈል የአንድ ትውልድ ስህተት ብቻ ሳይሆን የብዙ ትውልዶችን የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚያጨልም ታሪካዊ ኪሳራ ማስከተሉን ሊያስተምረን ይገባል የሚል ነው።
"እኔ ብቻ" ከሚል ግትርነት ወደ መደማመጥ ባህል
የምክክሩ ስኬት የሚጀምረው ከአስተሳሰብ ለውጥ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ "እኔ ያልኩት ብቻ" በሚል ግትርነት የውይይት ባህልን የመቁረጥ አደገኛ አካሄድ መታረም እንዳለበት አሳስበዋል።
መደማመጥ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ለማስረዳትም የሀገራችንን ሁለት ድንቅ አባበሎች ጠቅሰዋል።
"መልካም ንግግር ከመልካም አልጋ በተሻለ ያሳርፋል" የሚለው የኦሮሞ አባቶች ይትበሃል እና "በአንድ ወገን ቆመህ የሌላውን ችግር መረዳት አትችልምና፣ ተነስተህ ሂድና አድምጥ" የሚለው የአፋሮች ጥልቅ ምክር የዚህ ማሳያ ናቸው።
የነዚህ አባባሎች አንደምታ ቀላልና ግልጽ ነው፤ ሰላም እና መግባባት የሚመጣው በጉልበት ሳይሆን በሃሳብ ልዕልና ነው።
እውነተኛ መግባባት የሚፈጠረው ደግሞ ከራሳችን ጠባብ አጥር ወጥተን የሌላውን ወገን ስሜት፣ ሃሳብ እና ስጋት ለመረዳት ስንሞክር ብቻ ነው።
በአሁኑ ወቅት የተሰበሰቡት 4 ሺህ ተሳታፊዎች ዋነኛ ሥራም ይህን የመደማመጥ ባህል በማዳበር ለሀገራችን ዘላቂ ሕገ-መንግሥታዊ ዋስትና ያለው ሥራ መሥራት ነው።
የውሸት ፕሮፓጋንዳ እና የሀገር ሕልውና
ሌላው ትልቁ መልዕክት፣ ተሳታፊዎች በውሸት ፕሮፓጋንዳዎች እንዳይዘናጉ የቀረበው አደራ ነው። ይህንንም "ቀፎዋን የጣለች ንብ፣ ማር አትሰጥም" በሚል ምሳሌ አስገንዝበዋል።
ሀገር ከሌለች ግለሰባዊም ሆነ ቡድናዊ ሕልውና ሊኖር አይችልም። ማር መሥራት የሚቻለው ቀፎው ሲኖር እና ንቦቹ በጋራ ሲሠሩ ብቻ ነው።
በመሆኑም በሀሰተኛ መረጃዎች እና አሉባልታዎች ተታልለን የጋራ ቀፎአችን የሆነችውን ሀገራችንን ማፍረስ፣ ከሁለት ያጣ እንደሚያደርገን መረዳት ያስፈልጋል።
ወደ አዲሱ የሰላም ሞዴል
ይህ ታሪካዊ የምክክር መድረክ እርስ በርስ በመደማመጥ አሁን ያለውን የዜሮ ድምር ፖለቲካ በምክክር እና መደማመጥ ላይ ወደተመሠረተ ዘላቂ ሰላም እና ልማት ለመለወጥ የተዘጋጀ ትልቅ በር ነው።
የፍትህ እና የዴሞክራሲ ተቋማት ገለልተኛ እንዲሆኑ በማድረግ፣ ኢትዮጵያን ለአፍሪካ ቀንድ እና ለመላው አህጉር አርአያ የሚሆን የሰላም ሞዴል የማድረግ ታላቅ ሀገራዊ ኃላፊነት አሁን በተመካካሪዎቹ እጅ ላይ ይገኛል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #pmabiyahmed #nationaldialogue #peacebuilding #reconciliation #ebc
*******************
ታሪካዊው የሀገራዊ ምክክር ዋና ጉባኤ በስኬት እንዲጠናቀቅ እና ዘላቂ ውጤት እንዲያመጣ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልዕክት ለውይይቱ መነሻ የሚሆን ጠንካራ እሳቤን ይዟል።
ይህ መልዕክት የኢትዮጵያ የትናንት ሕመም፣ የዛሬ ፈተና እና የነገ ተስፋ በግልጽ የተንጸባረቀበት ነው።
የውስጥ ድክመት እና የውጭ ጣልቃ ገብነት አንደምታ
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሀገራችን ውስጣዊ ክፍተቶች ምክንያት የሚመጡ የውጭ ጣልቃ ገብነቶችን እና የጂኦፖለቲካ አደጋዎችን በምሳሌ አስረድተዋል።
የዚህ መልዕክት ትልቁ አንደምታ ግልጽ ነው፤ እኛ እርስ በርሳችን በውስጥ ጉዳዮቻችን ስንጨቃጨቅ እና ስንወዛገብ፣ የውጭ ኃይሎች መዳከማችንን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም የራሳቸውን ፍላጎትና ጥቅም በላያችን ላይ ይጭናሉ።
ይህን እውነት ለማሳየትም ታሪካዊ ስህተቶቻችንን አስታውሰዋል። ቀደም ባሉ ጊዜያት ልዩነቶቻችንን በውይይት መፍታት አለመቻላችን እና ውስጣዊ አንድነታችን መላላቱ ኢትዮጵያ ቀይ ባሕርን እንድታጣ አድርጓታል።
ይህም በታሪክ "የጂኦግራፊ እስረኛ" እንድንሆን አድርጎናል። የዚህ ታሪካዊ እውነት አንደምታ፣ የውስጥ መከፋፈል የአንድ ትውልድ ስህተት ብቻ ሳይሆን የብዙ ትውልዶችን የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚያጨልም ታሪካዊ ኪሳራ ማስከተሉን ሊያስተምረን ይገባል የሚል ነው።
"እኔ ብቻ" ከሚል ግትርነት ወደ መደማመጥ ባህል
የምክክሩ ስኬት የሚጀምረው ከአስተሳሰብ ለውጥ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ "እኔ ያልኩት ብቻ" በሚል ግትርነት የውይይት ባህልን የመቁረጥ አደገኛ አካሄድ መታረም እንዳለበት አሳስበዋል።
መደማመጥ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ለማስረዳትም የሀገራችንን ሁለት ድንቅ አባበሎች ጠቅሰዋል።
"መልካም ንግግር ከመልካም አልጋ በተሻለ ያሳርፋል" የሚለው የኦሮሞ አባቶች ይትበሃል እና "በአንድ ወገን ቆመህ የሌላውን ችግር መረዳት አትችልምና፣ ተነስተህ ሂድና አድምጥ" የሚለው የአፋሮች ጥልቅ ምክር የዚህ ማሳያ ናቸው።
የነዚህ አባባሎች አንደምታ ቀላልና ግልጽ ነው፤ ሰላም እና መግባባት የሚመጣው በጉልበት ሳይሆን በሃሳብ ልዕልና ነው።
እውነተኛ መግባባት የሚፈጠረው ደግሞ ከራሳችን ጠባብ አጥር ወጥተን የሌላውን ወገን ስሜት፣ ሃሳብ እና ስጋት ለመረዳት ስንሞክር ብቻ ነው።
በአሁኑ ወቅት የተሰበሰቡት 4 ሺህ ተሳታፊዎች ዋነኛ ሥራም ይህን የመደማመጥ ባህል በማዳበር ለሀገራችን ዘላቂ ሕገ-መንግሥታዊ ዋስትና ያለው ሥራ መሥራት ነው።
የውሸት ፕሮፓጋንዳ እና የሀገር ሕልውና
ሌላው ትልቁ መልዕክት፣ ተሳታፊዎች በውሸት ፕሮፓጋንዳዎች እንዳይዘናጉ የቀረበው አደራ ነው። ይህንንም "ቀፎዋን የጣለች ንብ፣ ማር አትሰጥም" በሚል ምሳሌ አስገንዝበዋል።
ሀገር ከሌለች ግለሰባዊም ሆነ ቡድናዊ ሕልውና ሊኖር አይችልም። ማር መሥራት የሚቻለው ቀፎው ሲኖር እና ንቦቹ በጋራ ሲሠሩ ብቻ ነው።
በመሆኑም በሀሰተኛ መረጃዎች እና አሉባልታዎች ተታልለን የጋራ ቀፎአችን የሆነችውን ሀገራችንን ማፍረስ፣ ከሁለት ያጣ እንደሚያደርገን መረዳት ያስፈልጋል።
ወደ አዲሱ የሰላም ሞዴል
ይህ ታሪካዊ የምክክር መድረክ እርስ በርስ በመደማመጥ አሁን ያለውን የዜሮ ድምር ፖለቲካ በምክክር እና መደማመጥ ላይ ወደተመሠረተ ዘላቂ ሰላም እና ልማት ለመለወጥ የተዘጋጀ ትልቅ በር ነው።
የፍትህ እና የዴሞክራሲ ተቋማት ገለልተኛ እንዲሆኑ በማድረግ፣ ኢትዮጵያን ለአፍሪካ ቀንድ እና ለመላው አህጉር አርአያ የሚሆን የሰላም ሞዴል የማድረግ ታላቅ ሀገራዊ ኃላፊነት አሁን በተመካካሪዎቹ እጅ ላይ ይገኛል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #pmabiyahmed #nationaldialogue #peacebuilding #reconciliation #ebc
27 days ago
መገናኛ ብዙሃን ብሔራዊ ጥቅም በማስጠበቅ ላይ ሊሰሩ ይገባል - መኩሪያ መካሻ (ረ/ፕ)
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መገናኛ ብዙሃን በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ላይ ትኩረት አድርጎ መሥራት ይጠበቅበታል አሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት እና ኮሙኒኬሽን መምህር መኩሪያ መካሻ (ረ/ፕ)።
መኩሪያ መካሻ (ረ/ፕ) ከፋና ፖድካስት ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፥ ጋዜጠኞች የሀገርን ሉዓላዊነትና ክብር በሚያስጠብቁ ብሔራዊ ጥቅሞች ላይ በመሥራት ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል።
የሀገራችን መገናኛ ብዙሃን በቀጣናው ተፅዕኖ ፈጣሪ መሆን አለባቸው ያሉት መምህሩ፥ የሀገርን ጥቅም በማስከበር ረገድ በጂኦፖለቲካዊ ጉዳዮች ገንቢ ሚናን መጫወት አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ማንነትና ታሪክን ለመግለፅ ብሎም ተፅዕኖ ለመፍጠር መገናኛ ብዙሃን ትልቅ አቅም እንዳላቸው ገልጸው፥ ገዢ ትርክት በማስረፅና ልዕለ ኃያል ሀገር በመገንባት ላይ ትኩረት አድርጎ መሥራት እንደሚገባ መክረዋል።
ይህ ወቅት ዲጂታል ሚዲያው ተጽዕኖ እያየለ የመጣበት ጊዜ በመሆኑ ኅብረተሰቡ እውነተኛውን መረጃ ለይቶ መጠቀም እንዲችል መሠረታዊ ትምህርት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።
ለመገናኛ ብዙሃን ውጤታማነት ፈጠራ ወሳኝ መሆኑን የገለጹ ሲሆን፥ የጋዜጠኝነት ስራ ተግባርን ያስቀድማል ሲሉም አብራርተዋል።
በሠራዊት ሸሎ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት እና ኮሙኒኬሽን ትምህርት ከፍል መምህር መኩሪያ መካሻ (ረ/ፕ) ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረጉትን ቆይታ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
https://youtube.com/watch?...
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መገናኛ ብዙሃን በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም ላይ ትኩረት አድርጎ መሥራት ይጠበቅበታል አሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት እና ኮሙኒኬሽን መምህር መኩሪያ መካሻ (ረ/ፕ)።
መኩሪያ መካሻ (ረ/ፕ) ከፋና ፖድካስት ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፥ ጋዜጠኞች የሀገርን ሉዓላዊነትና ክብር በሚያስጠብቁ ብሔራዊ ጥቅሞች ላይ በመሥራት ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል።
የሀገራችን መገናኛ ብዙሃን በቀጣናው ተፅዕኖ ፈጣሪ መሆን አለባቸው ያሉት መምህሩ፥ የሀገርን ጥቅም በማስከበር ረገድ በጂኦፖለቲካዊ ጉዳዮች ገንቢ ሚናን መጫወት አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ማንነትና ታሪክን ለመግለፅ ብሎም ተፅዕኖ ለመፍጠር መገናኛ ብዙሃን ትልቅ አቅም እንዳላቸው ገልጸው፥ ገዢ ትርክት በማስረፅና ልዕለ ኃያል ሀገር በመገንባት ላይ ትኩረት አድርጎ መሥራት እንደሚገባ መክረዋል።
ይህ ወቅት ዲጂታል ሚዲያው ተጽዕኖ እያየለ የመጣበት ጊዜ በመሆኑ ኅብረተሰቡ እውነተኛውን መረጃ ለይቶ መጠቀም እንዲችል መሠረታዊ ትምህርት እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።
ለመገናኛ ብዙሃን ውጤታማነት ፈጠራ ወሳኝ መሆኑን የገለጹ ሲሆን፥ የጋዜጠኝነት ስራ ተግባርን ያስቀድማል ሲሉም አብራርተዋል።
በሠራዊት ሸሎ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት እና ኮሙኒኬሽን ትምህርት ከፍል መምህር መኩሪያ መካሻ (ረ/ፕ) ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረጉትን ቆይታ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
https://youtube.com/watch?...
28 days ago
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ለቀጣናዊ ሰላም
የአፍሪካ ቀንድ በዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ላይ ባለው ስልታዊ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ ሳቢያ ሁልጊዜም የጂኦፖለቲካ ፍላጎቶች መናኸሪያ ነው።
በዚህ ቀጣና ውስጥ ከ130 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ፣ የባህር በር አልባ መሆኗ የራሷን የኢኮኖሚ እድገት ከመገደቡ ባለፈ በቀጣናው መረጋጋት ላይ የራሱ ተጽእኖ አለው።
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት የሀገሪቱን የልማት ጥያቄ ከመመለስ ባለፈ ለአጠቃላይ ቀጣናው ሰላምና ዘላቂ ትስስር ሚናው ወሳኝ ነው።
የፖለቲካ ሳይንስ ሳይንሳዊ እውነታዎች እንደሚያሳዩት፣ ሀገራት በኢኮኖሚ እርስ በርስ የሚኖራቸው ትስስር በጠነከረ ቁጥር በመካከላቸው የመተማመንና የመተባበር መንፈስ በርትቶ የግጭት ዕድል በእጅጉ ይቀንሳል።
በሌላ መልኩ ኢትዮጵያ ቀጥተኛ የባህር በር ካላት የምርት ወጪዋ ይቀንሳል፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮች በሙሉ አቅማቸው ያመርታሉ፣ ሰፊ የሥራ ዕድልም ይፈጠራል።
ኢትዮጵያ ጠንካራ የባህር ኃይል እና የወደብ መዋቅር ሲኖራት፣ በቀጣናው የሚስተዋሉትን የባህር ላይ ወንብድና እና የሽብርተኝነት ስጋቶች ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ ለመከላከል ሰፊ አቅም ይፈጥራል።
ይህ ደግሞ በኤደን ባህረ-ሰላጤ እና በቀይ ባህር አካባቢ ያለውን ህገ-ወጥ ስደት እና የወንጀል ተጋላጭነት ይቀንሳል።
የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በዲፕሎማሲ እና በሰላማዊ መንገድ ምላሽ ካገኘ፣ በሀገሪቱ ላይ የሚፈጠረውን የኢኮኖሚ መታፈን ያስወግዳል። ይህ ደግሞ ስጋት-ወለድ ለሆኑ ግጭቶች በር ይዘጋል።
ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄዋን የምታነሳው የዓለም አቀፍ የባህር ህግን እና የጋራ ልማት መርሆዎችን መሠረት አድርጋ ነው።
ይህ አካሄድ ከሃይል ይልቅ በድርድር እና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ አዲስ የዲፕሎማሲ ባህል በአፍሪካ ቀንድ እንዲዳብር መንገድ ከፍቷል።
በአጠቃላይ፣ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የመላው አፍሪካ ቀንድ የሰላም ዋስትና ነው።
በመሆኑም የባህር በር ጥያቄው መመለስ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያፋጥን እና ዘላቂ ሰላምን የሚያሰፍን ታሪካዊ እርምጃ ነው።
የአፍሪካ ቀንድ በዓለም አቀፍ የንግድ መስመር ላይ ባለው ስልታዊ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ ሳቢያ ሁልጊዜም የጂኦፖለቲካ ፍላጎቶች መናኸሪያ ነው።
በዚህ ቀጣና ውስጥ ከ130 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ፣ የባህር በር አልባ መሆኗ የራሷን የኢኮኖሚ እድገት ከመገደቡ ባለፈ በቀጣናው መረጋጋት ላይ የራሱ ተጽእኖ አለው።
የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት የሀገሪቱን የልማት ጥያቄ ከመመለስ ባለፈ ለአጠቃላይ ቀጣናው ሰላምና ዘላቂ ትስስር ሚናው ወሳኝ ነው።
የፖለቲካ ሳይንስ ሳይንሳዊ እውነታዎች እንደሚያሳዩት፣ ሀገራት በኢኮኖሚ እርስ በርስ የሚኖራቸው ትስስር በጠነከረ ቁጥር በመካከላቸው የመተማመንና የመተባበር መንፈስ በርትቶ የግጭት ዕድል በእጅጉ ይቀንሳል።
በሌላ መልኩ ኢትዮጵያ ቀጥተኛ የባህር በር ካላት የምርት ወጪዋ ይቀንሳል፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮች በሙሉ አቅማቸው ያመርታሉ፣ ሰፊ የሥራ ዕድልም ይፈጠራል።
ኢትዮጵያ ጠንካራ የባህር ኃይል እና የወደብ መዋቅር ሲኖራት፣ በቀጣናው የሚስተዋሉትን የባህር ላይ ወንብድና እና የሽብርተኝነት ስጋቶች ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ ለመከላከል ሰፊ አቅም ይፈጥራል።
ይህ ደግሞ በኤደን ባህረ-ሰላጤ እና በቀይ ባህር አካባቢ ያለውን ህገ-ወጥ ስደት እና የወንጀል ተጋላጭነት ይቀንሳል።
የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በዲፕሎማሲ እና በሰላማዊ መንገድ ምላሽ ካገኘ፣ በሀገሪቱ ላይ የሚፈጠረውን የኢኮኖሚ መታፈን ያስወግዳል። ይህ ደግሞ ስጋት-ወለድ ለሆኑ ግጭቶች በር ይዘጋል።
ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄዋን የምታነሳው የዓለም አቀፍ የባህር ህግን እና የጋራ ልማት መርሆዎችን መሠረት አድርጋ ነው።
ይህ አካሄድ ከሃይል ይልቅ በድርድር እና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ አዲስ የዲፕሎማሲ ባህል በአፍሪካ ቀንድ እንዲዳብር መንገድ ከፍቷል።
በአጠቃላይ፣ የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የመላው አፍሪካ ቀንድ የሰላም ዋስትና ነው።
በመሆኑም የባህር በር ጥያቄው መመለስ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያፋጥን እና ዘላቂ ሰላምን የሚያሰፍን ታሪካዊ እርምጃ ነው።
28 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን መንግስት ላይ እጅግ ከባድ እና ታይቶ የማይታወቅ የጦርነት ማስጠንቀቂያ ሰንዝረዋል። ትራምፕ በትሩዝ ሶሻል ማህበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ባስተላለፉት አስቸኳይ መልዕክት፣ የኢራን መንግስት በሳቸው ላይ ማንኛውንም ዓይነት የግድያ ሙከራ ለማድረግ ቢሞክር አሜሪካ "በሺዎች የሚቆጠሩ" ሚሳይሎችን ወደ ሀገሪቱ እንደምትተኩስ በግልጽ ዝተዋል።
ፕሬዝዳንቱ በዓለም ዙሪያ በሚገነቱ የተለያዩ አቅጣጫዎች የሚነገረውን እና በእርሳቸው ላይ የተደቀነውን የግድያ ስጋት በመጥቀስ፣ በማህበራዊ ሚዲያ መልዕክታቸው ላይ "1000 ሚሳይሎች ተዘጋጅተው ወደ ኢስላማዊቷ የኢራን ሪፐብሊክ ተደቅነዋል፤ የኢራን መንግስት የአሜሪካን ተቀማጭ ፕሬዝዳንት፣ በዚህ ሁኔታ 'እኔን' ለመግደል ወይም የግድያ ሙከራ ለማድረግ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ባስተጋባው ዛቻው ላይ እርምጃ ከወሰደ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ተጨማሪ ሚሳይሎች ወዲያውኑ ይከተላሉ" ሲሉ አስፍረዋል።
አክለውም ትራምፕ ለጦር ኃይሉ አስፈላጊው መመሪያ አስቀድሞ መሰጠቱን ገልጸዋል። የአሜሪካ ጦር ኃይል ለቀጣዩ አንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ እንደ አስፈላጊነቱ ሊራዘም በሚችል ሁኔታ ሁሉንም የኢራን ግዛቶች ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት እና ለማውደም ዝግጁ፣ ፈቃደኛ እና ሙሉ አቅም ያለው መሆኑን አስታውቀዋል። ይህ የፕሬዝዳንቱ ይፋዊ ዛቻ እና በሁለቱ ሀገራት መካከል የተደቀነው ከባድ ወታደራዊ ስጋት ቀጣናዊ ውጥረቱን ወደ አደገኛ ምዕራፍ ሊያሸጋግረው እንደሚችል የጂኦፖለቲካ ባለሙያዎች በስጋት እየገለጹ ይገኛሉ።
ፕሬዝዳንቱ በዓለም ዙሪያ በሚገነቱ የተለያዩ አቅጣጫዎች የሚነገረውን እና በእርሳቸው ላይ የተደቀነውን የግድያ ስጋት በመጥቀስ፣ በማህበራዊ ሚዲያ መልዕክታቸው ላይ "1000 ሚሳይሎች ተዘጋጅተው ወደ ኢስላማዊቷ የኢራን ሪፐብሊክ ተደቅነዋል፤ የኢራን መንግስት የአሜሪካን ተቀማጭ ፕሬዝዳንት፣ በዚህ ሁኔታ 'እኔን' ለመግደል ወይም የግድያ ሙከራ ለማድረግ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ባስተጋባው ዛቻው ላይ እርምጃ ከወሰደ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ተጨማሪ ሚሳይሎች ወዲያውኑ ይከተላሉ" ሲሉ አስፍረዋል።
አክለውም ትራምፕ ለጦር ኃይሉ አስፈላጊው መመሪያ አስቀድሞ መሰጠቱን ገልጸዋል። የአሜሪካ ጦር ኃይል ለቀጣዩ አንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ እንደ አስፈላጊነቱ ሊራዘም በሚችል ሁኔታ ሁሉንም የኢራን ግዛቶች ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት እና ለማውደም ዝግጁ፣ ፈቃደኛ እና ሙሉ አቅም ያለው መሆኑን አስታውቀዋል። ይህ የፕሬዝዳንቱ ይፋዊ ዛቻ እና በሁለቱ ሀገራት መካከል የተደቀነው ከባድ ወታደራዊ ስጋት ቀጣናዊ ውጥረቱን ወደ አደገኛ ምዕራፍ ሊያሸጋግረው እንደሚችል የጂኦፖለቲካ ባለሙያዎች በስጋት እየገለጹ ይገኛሉ።
30 days ago
በምክክሩ የኢትዮጵያ ጠላቶች ሴራ ይከሽፋል!
***********************
የአንድ ሀገር ሉዓላዊነት በድንበሯ ምሰሶዎች እና በጦር ኃይሏ ላይ ብቻ ሳይሆን፣ በሕዝቦቿ ልብ ውስጥ በሚታነጸው የጋራ መግባባት እና በማይናወጠው የአንድነት ዐለት ላይ የቆመ ነው። ታላቋ ኢትዮጵያ፣ የዘመናት ፈተናዎችን ተሻግራ፣ በታሪክ አውሎ ንፋስ ውስጥ አልፋ ዛሬ ላይ የደረሰችው፣ በልጆቿ ደም እና አጥንት በተከፈለ መስዋዕትነት ብቻ ሳይሆን፣ ከልዩነት ማዕበል በላይ በገነነ የውስጥ መተባበር እና የሕብረት ጸጋ ነው። ነገር ግን የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ሀገራችን ቀና ብላ እንዳትራመድ፣ የጋራ ቋንቋ እና አንድ የልብ ትርታ እንዳይኖራት የባቢሎንን የመከፋፈል እርግማን ሲያዘንቡባት ኖረዋል። አንድ ሆነን የብልጽግናን ግንብ እንዳንገነባ ቋንቋችንን በማዘበራረቅ፣ አንዱን ወገን በመደለልና ሌላውን በማግለል ከጥንት ጀምሮ የልዩነት እና የጥላቻ መርዝ ሲግቱን ቆይተዋል።
የጠላቶቻችን ሴራ ጊዜና መልኩን ይቀይራል እንጂ ዓላማው አንድ እና ጥርት ያለ ነው፤ እርሱም ኢትዮጵያን የእርስ በርስ ጦርነት አውድማ ማድረግ፤ ከሁለቱ ውሃዎቿ ማራቅ ነው። ወንድም በወንድሙ ላይ ጠመንጃ እንዲያነሳ፣ እልህ አስጨራሽ እና ትውልድ አምካኝ የእርስ በርስ መተላለቅ ውስጥ እንድንዘፈቅ ጠላቶቻችን ያልሸረቡት አሻጥር፣ ያልቆፈሩት የጥፋት ጉድጓድ አልነበረም። አንዱን ወገን በስውር በማስታጠቅ፣ ሌላውን በማዳከም ለዘመናት በወንድማማቾች ደም ሲነግዱ ኖረዋል። ከዚህም አልፎ የኢትዮጵያን ጂኦፖለቲካዊ ጡንቻ በማዛል፣ ተፈጥሯዊ እና ታሪካዊ የባህር በሯን በማሳጣት፣ የውሃ ላይ እትብቷን በመበጠስ፣ በየብስ እንድትታጠር አድርገዋል። በኢኮኖሚ ደቅቃ፣ በፖለቲካ ተከፋፍላ እንደ ምስጥ በውስጧ በምትበላ ሀገር ላይ የራሳቸውን የባንዳ ዙፋን ለመትከል ያልፈነቀሉት ቋጥኝ አልነበረም።
ሆኖም የኢትዮጵያ የእምቢተኝነት፣ የአልደፈር ባይነት መንፈስ በመከራ ውስጥ የሚጠነክር፣ በእሳት የሚፈተን ወርቅ ነው! ጠላቶቻችን "ተበታተኑ፣ ፈረሱ፣ አከተመላቸው" ሲሉን፣ እኛ ግን ከውድቀታችን አፈር ውስጥ ዳግም እንመዘዛለን። እነሆ የፊታችን ሐምሌ 8 የሚጀመረው ታሪካዊው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የፖለቲካ ስብራታችንን የምንጠግንበት፣ የዘመናት ቁስላችንን በይቅርታ የምናክምበት የሕልውና እና የሉዓላዊነታችን ዋነኛ ምሰሶ ነው። ይህ ጉባዔ ተራ የፖለቲካ ልሂቃን የቃላት ጦርነት የሚደረግበት አውድማ ሳይሆን፣ ኢትዮጵያውያን በአንድ ጣሪያ ስር ተሰባስበው፣ በገዛ ሀገራቸው እጣ ፈንታ ላይ የራሳቸውን የስምምነት ማህተም የሚያኖሩበት የነጻነት መድረክ ነው። ይህ የሰለጠነ ምክክር በራሱ የሉዓላዊነት ትልቅ መገለጫ ነው፤ የውጭ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትን በጽኑ የሚዘጋ፣ የጠላትን ሴራ ከሥሩ የሚነቅል የብሔራዊ መግባባት የጋራ ቃል ኪዳን ነው።
ታሪክ እንደመሰከረው፣ ኢትዮጵያውያን በአንድ ልብ ሲመክሩ እና ሲተባበሩ የውጭ ጠላቶች ሐፍረት ይከናነባሉ። ልዩነቶቻችንን ወደ ጎን ትተን፣ "እኔ" ከሚለው ራስ ወዳድነት ወጥተን "እኛ" በሚል ጽኑ መንፈስ በአንድነት ስንቆም፣ የማይደፈረውን የዓባይን ወንዝ ገድበን ታላቁን የሕዳሴ ግድብ እውን አድርገናል። በተመሳሳይ፣ ከዘመናት የመልክዓ ምድር እስራታችን በጥሰን ለመውጣት፣ ታሪካዊ የባሕር በር እና የወደብ ባለቤትነት መብታችንን ለማረጋገጥ በምናደርገው ፍትሐዊ የዲፕሎማሲ እና የጂኦፖለቲካ ጉዞ፣ ዳግም ብሔራዊ አንድነታችንን ለዓለም እያረጋገጥን ነው። በባቢሎን ሕዝብ ላይ እንደሆነው ጠላት ቋንቋችንን ሊያዘበራርቅ ሲጥር፣ እኛ ግን የልማት፣ የሰላም እና የብልጽግናን አንድ ቋንቋ መናገር ጀምረናል።
በመሆኑም፣ ሐምሌ 8 የሚጠነሰሰው ሀገራዊ ምክክር፣ ኢትዮጵያን ከውስጥ አጽንቶ፣ ከውጭ የሚመጣባትን የጥፋት ማዕበል የሚመክት የማይበገር ጋሻችን ነው። በምክክሩ፣ ለዘመናት የተነዛው የጥላቻ እና የመከፋፈል ትርክት ይከሽፋል፤ በምክክሩ፣ ሀገረ-መንግሥቱን ለማፍረስ የተወጠነው የጠላት ሴራ የሸረሪት ድር ሆኖ ይበጣጠሳል! ዛሬ ከስሜት ፖለቲካ ወጥተን በምክንያት እና በስክነት ስንመክር፣ የዘመናት የኢትዮጵያ ጠላቶች አንገታቸውን ይደፋሉ። የኢትዮጵያ ሕዳሴ በልጆቿ የጠረጴዛ ዙሪያ ምክክር፣ በጥልቅ መከባበር እና በጽኑ አንድነት በዐለት ላይ ተመስርቶ ወደ ፊት ይገሰግሳል። አዎ! በምክክሩ የጠላት ሴራ ይከሽፋል፤ ታላቂቱ ኢትዮጵያም ለዘለዓለም በክብር ጸንታ ትኖራለች!
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #nationaldialogue #nationalconsensus #socialcontract #ebc
***********************
የአንድ ሀገር ሉዓላዊነት በድንበሯ ምሰሶዎች እና በጦር ኃይሏ ላይ ብቻ ሳይሆን፣ በሕዝቦቿ ልብ ውስጥ በሚታነጸው የጋራ መግባባት እና በማይናወጠው የአንድነት ዐለት ላይ የቆመ ነው። ታላቋ ኢትዮጵያ፣ የዘመናት ፈተናዎችን ተሻግራ፣ በታሪክ አውሎ ንፋስ ውስጥ አልፋ ዛሬ ላይ የደረሰችው፣ በልጆቿ ደም እና አጥንት በተከፈለ መስዋዕትነት ብቻ ሳይሆን፣ ከልዩነት ማዕበል በላይ በገነነ የውስጥ መተባበር እና የሕብረት ጸጋ ነው። ነገር ግን የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ሀገራችን ቀና ብላ እንዳትራመድ፣ የጋራ ቋንቋ እና አንድ የልብ ትርታ እንዳይኖራት የባቢሎንን የመከፋፈል እርግማን ሲያዘንቡባት ኖረዋል። አንድ ሆነን የብልጽግናን ግንብ እንዳንገነባ ቋንቋችንን በማዘበራረቅ፣ አንዱን ወገን በመደለልና ሌላውን በማግለል ከጥንት ጀምሮ የልዩነት እና የጥላቻ መርዝ ሲግቱን ቆይተዋል።
የጠላቶቻችን ሴራ ጊዜና መልኩን ይቀይራል እንጂ ዓላማው አንድ እና ጥርት ያለ ነው፤ እርሱም ኢትዮጵያን የእርስ በርስ ጦርነት አውድማ ማድረግ፤ ከሁለቱ ውሃዎቿ ማራቅ ነው። ወንድም በወንድሙ ላይ ጠመንጃ እንዲያነሳ፣ እልህ አስጨራሽ እና ትውልድ አምካኝ የእርስ በርስ መተላለቅ ውስጥ እንድንዘፈቅ ጠላቶቻችን ያልሸረቡት አሻጥር፣ ያልቆፈሩት የጥፋት ጉድጓድ አልነበረም። አንዱን ወገን በስውር በማስታጠቅ፣ ሌላውን በማዳከም ለዘመናት በወንድማማቾች ደም ሲነግዱ ኖረዋል። ከዚህም አልፎ የኢትዮጵያን ጂኦፖለቲካዊ ጡንቻ በማዛል፣ ተፈጥሯዊ እና ታሪካዊ የባህር በሯን በማሳጣት፣ የውሃ ላይ እትብቷን በመበጠስ፣ በየብስ እንድትታጠር አድርገዋል። በኢኮኖሚ ደቅቃ፣ በፖለቲካ ተከፋፍላ እንደ ምስጥ በውስጧ በምትበላ ሀገር ላይ የራሳቸውን የባንዳ ዙፋን ለመትከል ያልፈነቀሉት ቋጥኝ አልነበረም።
ሆኖም የኢትዮጵያ የእምቢተኝነት፣ የአልደፈር ባይነት መንፈስ በመከራ ውስጥ የሚጠነክር፣ በእሳት የሚፈተን ወርቅ ነው! ጠላቶቻችን "ተበታተኑ፣ ፈረሱ፣ አከተመላቸው" ሲሉን፣ እኛ ግን ከውድቀታችን አፈር ውስጥ ዳግም እንመዘዛለን። እነሆ የፊታችን ሐምሌ 8 የሚጀመረው ታሪካዊው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የፖለቲካ ስብራታችንን የምንጠግንበት፣ የዘመናት ቁስላችንን በይቅርታ የምናክምበት የሕልውና እና የሉዓላዊነታችን ዋነኛ ምሰሶ ነው። ይህ ጉባዔ ተራ የፖለቲካ ልሂቃን የቃላት ጦርነት የሚደረግበት አውድማ ሳይሆን፣ ኢትዮጵያውያን በአንድ ጣሪያ ስር ተሰባስበው፣ በገዛ ሀገራቸው እጣ ፈንታ ላይ የራሳቸውን የስምምነት ማህተም የሚያኖሩበት የነጻነት መድረክ ነው። ይህ የሰለጠነ ምክክር በራሱ የሉዓላዊነት ትልቅ መገለጫ ነው፤ የውጭ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትን በጽኑ የሚዘጋ፣ የጠላትን ሴራ ከሥሩ የሚነቅል የብሔራዊ መግባባት የጋራ ቃል ኪዳን ነው።
ታሪክ እንደመሰከረው፣ ኢትዮጵያውያን በአንድ ልብ ሲመክሩ እና ሲተባበሩ የውጭ ጠላቶች ሐፍረት ይከናነባሉ። ልዩነቶቻችንን ወደ ጎን ትተን፣ "እኔ" ከሚለው ራስ ወዳድነት ወጥተን "እኛ" በሚል ጽኑ መንፈስ በአንድነት ስንቆም፣ የማይደፈረውን የዓባይን ወንዝ ገድበን ታላቁን የሕዳሴ ግድብ እውን አድርገናል። በተመሳሳይ፣ ከዘመናት የመልክዓ ምድር እስራታችን በጥሰን ለመውጣት፣ ታሪካዊ የባሕር በር እና የወደብ ባለቤትነት መብታችንን ለማረጋገጥ በምናደርገው ፍትሐዊ የዲፕሎማሲ እና የጂኦፖለቲካ ጉዞ፣ ዳግም ብሔራዊ አንድነታችንን ለዓለም እያረጋገጥን ነው። በባቢሎን ሕዝብ ላይ እንደሆነው ጠላት ቋንቋችንን ሊያዘበራርቅ ሲጥር፣ እኛ ግን የልማት፣ የሰላም እና የብልጽግናን አንድ ቋንቋ መናገር ጀምረናል።
በመሆኑም፣ ሐምሌ 8 የሚጠነሰሰው ሀገራዊ ምክክር፣ ኢትዮጵያን ከውስጥ አጽንቶ፣ ከውጭ የሚመጣባትን የጥፋት ማዕበል የሚመክት የማይበገር ጋሻችን ነው። በምክክሩ፣ ለዘመናት የተነዛው የጥላቻ እና የመከፋፈል ትርክት ይከሽፋል፤ በምክክሩ፣ ሀገረ-መንግሥቱን ለማፍረስ የተወጠነው የጠላት ሴራ የሸረሪት ድር ሆኖ ይበጣጠሳል! ዛሬ ከስሜት ፖለቲካ ወጥተን በምክንያት እና በስክነት ስንመክር፣ የዘመናት የኢትዮጵያ ጠላቶች አንገታቸውን ይደፋሉ። የኢትዮጵያ ሕዳሴ በልጆቿ የጠረጴዛ ዙሪያ ምክክር፣ በጥልቅ መከባበር እና በጽኑ አንድነት በዐለት ላይ ተመስርቶ ወደ ፊት ይገሰግሳል። አዎ! በምክክሩ የጠላት ሴራ ይከሽፋል፤ ታላቂቱ ኢትዮጵያም ለዘለዓለም በክብር ጸንታ ትኖራለች!
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #nationaldialogue #nationalconsensus #socialcontract #ebc
Sponsored by
Surafel
1 month ago
የመደመር አንቀጽ
የትውልድን ትኩረት የሚሻ አካባቢ
ትውልዱ የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገራትን መመልከቻ መነጽሩ በሦስት ተያያዥነት ባላቸው ነጥቦች ላይ የሚቃኝ ነው።
የመጀመሪያው ለሀገራችን ባለው ቅርበት ነው። በዚህ መልከአ ምድራዊ ቅርበትና ግንኙነት የተነሣ የሃይማኖት፣ የባህል እና የሥልጣኔ መወራረስ ተፈጥሯል።
በአንዱ አካባቢ የተፈጠረ ነገር በሌላው አካባቢ አዎንታዊም ይሁን አሉታዊ ተፅዕኖ ኖሮታል።
ሁለተኛው ያለው መቀራረብ በአዳዲስ ለውጦችንና ከሥተቶች ታጅቦ፤ ይበልጥ እርስ በእርስ እየተሳሰረ የመጣ ጂኦፖለቲካ መፈጠሩ ነው።
በዚህም ውስጥ በጋራ ልንሠራባቸው ወይም የልዩነት ነጥብ ሊሆኑ የሚችሉ፤ እኛም እነርሱ ላይ፡ እነርሱም እኛ ላይ የተለያዩ ፍላጎቶች ያለን መሆኑ ነው።
ሦስተኛው ደግሞ እየተለወጠ ባለው ዓለም ውስጥ፤ ካካበቱት ዐቅም የተነሣ ይበልጥ የተጠናከረ ዓለም አቀፍ ኃይል ሆነው የመውጣት ዕድል ያላቸው መሆኑ ነው።
በአፍሪካ ቀንድና በመካከለኛው ምሥራቅ በተሳሰረ ጂኦፖለቲካ ውስጥ፤ ጠንካራ አካባቢያዊ ኃይል መኖሩን የሚገነዘብ ነው።
የመደመር ትውልድ
ገጽ - 259
የትውልድን ትኩረት የሚሻ አካባቢ
ትውልዱ የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገራትን መመልከቻ መነጽሩ በሦስት ተያያዥነት ባላቸው ነጥቦች ላይ የሚቃኝ ነው።
የመጀመሪያው ለሀገራችን ባለው ቅርበት ነው። በዚህ መልከአ ምድራዊ ቅርበትና ግንኙነት የተነሣ የሃይማኖት፣ የባህል እና የሥልጣኔ መወራረስ ተፈጥሯል።
በአንዱ አካባቢ የተፈጠረ ነገር በሌላው አካባቢ አዎንታዊም ይሁን አሉታዊ ተፅዕኖ ኖሮታል።
ሁለተኛው ያለው መቀራረብ በአዳዲስ ለውጦችንና ከሥተቶች ታጅቦ፤ ይበልጥ እርስ በእርስ እየተሳሰረ የመጣ ጂኦፖለቲካ መፈጠሩ ነው።
በዚህም ውስጥ በጋራ ልንሠራባቸው ወይም የልዩነት ነጥብ ሊሆኑ የሚችሉ፤ እኛም እነርሱ ላይ፡ እነርሱም እኛ ላይ የተለያዩ ፍላጎቶች ያለን መሆኑ ነው።
ሦስተኛው ደግሞ እየተለወጠ ባለው ዓለም ውስጥ፤ ካካበቱት ዐቅም የተነሣ ይበልጥ የተጠናከረ ዓለም አቀፍ ኃይል ሆነው የመውጣት ዕድል ያላቸው መሆኑ ነው።
በአፍሪካ ቀንድና በመካከለኛው ምሥራቅ በተሳሰረ ጂኦፖለቲካ ውስጥ፤ ጠንካራ አካባቢያዊ ኃይል መኖሩን የሚገነዘብ ነው።
የመደመር ትውልድ
ገጽ - 259
1 month ago
ሀምበርግ ላይ በብቸኝነት የተገኙት ኢትዮጵያዊቷ ቤዛ በሻህ የአለምአቀፉን ማህበረሰብ አሳሰቡ‼️
የሆፕ ስፓይና ቢፊዳ እና ሃይድሮሴፋለስ (HOPE-SBH) ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት ወ/ሮ ቤዛ በሻህ ኃይሌ፣ በጀርመን ሀምበርግ በተካሄደው የ2026ቱ የሃምበርግ ዘላቂ ልማት ኮንፈረንስ (Hamburg Sustainability Conference - HSC) በመገኘት በነርቭ ዘንግ አፈጣጠር ችግሮች መከላከል ዙሪያ ዓለም አቀፍ ትኩረት እንዲሰጥ ጥሪ አቀረቡ።
የሃምበርግ ዘላቂ ልማት ኮንፈረንስ በአለም አቀፍ ደረጃ እየጨመረ የመጣውን የጂኦፖለቲካዊ ውጥረት በመሻገር፣ በፖለቲካ፣ በቢዝነስ፣ በሳይንስ እና በሲቪል ማህበረሰብ መሪዎች መካከል አዳዲስ ስምምነቶችን እና አጋርነቶችን ለመፍጠር የተቋቋመ ዓለም አቀፍ መድረክ ነው። ወ/ሮ ቤዛ በኮንፈረንሱ ማዕቀፍ ውስጥ፣ ከጀርመን የኢኮኖሚ ትብብር እና ልማት ፌዴራል ሚኒስትር ወ/ሮ ሬም አላባሊ-ራዶቫን (Reem Alabali Radovan) ንግግር በመቀጠል ዋና ንግግር አድርገዋል።
ወ/ሮ ቤዛ በንግግራቸው ወቅት፣ በሕይወት የመጀመሪያዎቹ 1,000 ቀናት ላይ የተመጣጠነ ምግብን ለማረጋገጥ የሚደረግ ኢንቨስትመንት የእናቶችንና የሕጻናትን ጤና ለማሻሻል ወሳኝ ስትራቴጂ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። በአለም አቀፍ መድረኩ ላይ፤ "ከእያንዳንዱ የምግብ እጥረት አኃዛዊ መረጃ ጀርባ የሚሰቃዩ ሕፃናት እና ቤተሰቦች መኖራቸውን ማስታወስ ይገባል" ብለዋል። በተጨማሪም "የተደበቀ ረሃብ" በመባል የሚታወቀው የንጥረ-ነገር እጥረት (micronutrient deficiencies) በእናቶች እና በሕፃናት ላይ የሚያደርሰውን ዘላቂና ከባድ ተጽዕኖ በዝርዝር አስረድተዋል። ከዚህም ባለፈ፣ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ግለሰቦችን ከመጉዳት በተጨማሪ ለሰው ልጆች ካፒታል፣ ለኢኮኖሚ ዕድገት እና ለዘላቂ ልማት ትልቅ እንቅፋት እንደሚሆን አብራርተዋል። በሕይወት የመጀመሪያዎቹ 1,000 ቀናት የሚደረግ ኢንቨስትመንት ከጤናም በተጨማሪም ለትምህርት ጥራት፣ ለኢኮኖሚ ምርታማነት እና ለዘላቂ ልማት ግቦች ስኬት መሠረት መሆኑን አስገንዝበዋል።
ይህንን አሳሳቢ ችግር ለመቅረፍም፣ ድርጅታቸው ሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች (HOPE-SBH) ላለፉት 10 ዓመታት በትኩረት የሰራባቸውን ዋና ዋና መፍትሄዎች ጠቁመዋል። በተለይም በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ በመተግበር ላይ የሚገኘውን ምግብን በጠቃሚ ንጥረ ነገሮች የማበልጸግ ሥራ በምሳሌነት በማንሳት፤ በሀገር በቀል ጥናትና ምርምር የታገዘውንና ትልቅ ስኬት ያስመዘገበውን ጨውን በአዮዲን እና በፎሊክ አሲድ በጋራ የማበልጸግ ሂደት (Double Salt Fortification) በልዩ አርአያነት አጉልተው አሳይተዋል። ለዚህ ብሔራዊ የፖሊሲ ስኬት መሳካትም የመንግሥት ተቋማት፣ የልማት አጋሮች፣ የግሉ ዘርፍ እና የሲቪል ማኅበረሰብ በቅንጅት መሥራታቸው ወሳኝ ሚና እንደነበረው ገልጸዋል።
ወ/ሮ ቤዛ በማጠቃለያቸው፣ የሃምበርግ ዘላቂ ልማት ኮንፈረንስ እንደሚያንፀባርቀው ሁሉ፣ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ከአጠቃላይ የፖሊሲ ውይይቶች ባለፈ ተጨባጭና ዘላቂ ውጤት ወደሚያመጡ ተግባራዊ አጋርነቶች መሸጋገር እንዳለበት ጥሪያቸውን አቅርበዋል። በሕፃናት የመጀመሪያዎቹ 1,000 ቀናት የተመጣጠነ ምግብ ላይ ኢንቨስት ማድረግ፣ ከማኅበረሰብ ጤና መሻሻል ባለፈ ለትምህርት ጥራት፣ ለኢኮኖሚ ዕድገት እና ለዘላቂ ልማት ዋነኛ መሠረት መሆኑንም ዳግም አረጋግጠዋል።
የሆፕ ስፓይና ቢፊዳ እና ሃይድሮሴፋለስ (HOPE-SBH) ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት ወ/ሮ ቤዛ በሻህ ኃይሌ፣ በጀርመን ሀምበርግ በተካሄደው የ2026ቱ የሃምበርግ ዘላቂ ልማት ኮንፈረንስ (Hamburg Sustainability Conference - HSC) በመገኘት በነርቭ ዘንግ አፈጣጠር ችግሮች መከላከል ዙሪያ ዓለም አቀፍ ትኩረት እንዲሰጥ ጥሪ አቀረቡ።
የሃምበርግ ዘላቂ ልማት ኮንፈረንስ በአለም አቀፍ ደረጃ እየጨመረ የመጣውን የጂኦፖለቲካዊ ውጥረት በመሻገር፣ በፖለቲካ፣ በቢዝነስ፣ በሳይንስ እና በሲቪል ማህበረሰብ መሪዎች መካከል አዳዲስ ስምምነቶችን እና አጋርነቶችን ለመፍጠር የተቋቋመ ዓለም አቀፍ መድረክ ነው። ወ/ሮ ቤዛ በኮንፈረንሱ ማዕቀፍ ውስጥ፣ ከጀርመን የኢኮኖሚ ትብብር እና ልማት ፌዴራል ሚኒስትር ወ/ሮ ሬም አላባሊ-ራዶቫን (Reem Alabali Radovan) ንግግር በመቀጠል ዋና ንግግር አድርገዋል።
ወ/ሮ ቤዛ በንግግራቸው ወቅት፣ በሕይወት የመጀመሪያዎቹ 1,000 ቀናት ላይ የተመጣጠነ ምግብን ለማረጋገጥ የሚደረግ ኢንቨስትመንት የእናቶችንና የሕጻናትን ጤና ለማሻሻል ወሳኝ ስትራቴጂ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። በአለም አቀፍ መድረኩ ላይ፤ "ከእያንዳንዱ የምግብ እጥረት አኃዛዊ መረጃ ጀርባ የሚሰቃዩ ሕፃናት እና ቤተሰቦች መኖራቸውን ማስታወስ ይገባል" ብለዋል። በተጨማሪም "የተደበቀ ረሃብ" በመባል የሚታወቀው የንጥረ-ነገር እጥረት (micronutrient deficiencies) በእናቶች እና በሕፃናት ላይ የሚያደርሰውን ዘላቂና ከባድ ተጽዕኖ በዝርዝር አስረድተዋል። ከዚህም ባለፈ፣ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ግለሰቦችን ከመጉዳት በተጨማሪ ለሰው ልጆች ካፒታል፣ ለኢኮኖሚ ዕድገት እና ለዘላቂ ልማት ትልቅ እንቅፋት እንደሚሆን አብራርተዋል። በሕይወት የመጀመሪያዎቹ 1,000 ቀናት የሚደረግ ኢንቨስትመንት ከጤናም በተጨማሪም ለትምህርት ጥራት፣ ለኢኮኖሚ ምርታማነት እና ለዘላቂ ልማት ግቦች ስኬት መሠረት መሆኑን አስገንዝበዋል።
ይህንን አሳሳቢ ችግር ለመቅረፍም፣ ድርጅታቸው ሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች (HOPE-SBH) ላለፉት 10 ዓመታት በትኩረት የሰራባቸውን ዋና ዋና መፍትሄዎች ጠቁመዋል። በተለይም በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ በመተግበር ላይ የሚገኘውን ምግብን በጠቃሚ ንጥረ ነገሮች የማበልጸግ ሥራ በምሳሌነት በማንሳት፤ በሀገር በቀል ጥናትና ምርምር የታገዘውንና ትልቅ ስኬት ያስመዘገበውን ጨውን በአዮዲን እና በፎሊክ አሲድ በጋራ የማበልጸግ ሂደት (Double Salt Fortification) በልዩ አርአያነት አጉልተው አሳይተዋል። ለዚህ ብሔራዊ የፖሊሲ ስኬት መሳካትም የመንግሥት ተቋማት፣ የልማት አጋሮች፣ የግሉ ዘርፍ እና የሲቪል ማኅበረሰብ በቅንጅት መሥራታቸው ወሳኝ ሚና እንደነበረው ገልጸዋል።
ወ/ሮ ቤዛ በማጠቃለያቸው፣ የሃምበርግ ዘላቂ ልማት ኮንፈረንስ እንደሚያንፀባርቀው ሁሉ፣ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ከአጠቃላይ የፖሊሲ ውይይቶች ባለፈ ተጨባጭና ዘላቂ ውጤት ወደሚያመጡ ተግባራዊ አጋርነቶች መሸጋገር እንዳለበት ጥሪያቸውን አቅርበዋል። በሕፃናት የመጀመሪያዎቹ 1,000 ቀናት የተመጣጠነ ምግብ ላይ ኢንቨስት ማድረግ፣ ከማኅበረሰብ ጤና መሻሻል ባለፈ ለትምህርት ጥራት፣ ለኢኮኖሚ ዕድገት እና ለዘላቂ ልማት ዋነኛ መሠረት መሆኑንም ዳግም አረጋግጠዋል።
1 month ago
የኢትዮጵያ የኢነርጂ ዲፕሎማሲ - ለቀጣናዊ ትሥሥር የተዘረጋ ድልድይ
*************************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ በታሪኳ አዲስ እና ስልታዊ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ይህ ምዕራፍ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በኩራት ከመቁጠር እና ከመቀኘት ባለፈ እነዚያን እምቅ ሀብቶች ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ እና የጂኦፖለቲካ አቅም በመለወጥ ሀገራዊ ልዕልናን ለማረጋገጥ የሚደረግ የታሪክ መታጠፊያ ነው።
ለረጅም ዘመናት በድህነት፣ በዕርዳታ ጥገኝነት እና በውስጥ ስጋቶች ታጥሮ የቆየው የቀድሞው ዲፕሎማሲ ዛሬ በተግባር ተረትቷል። በምትኩም ቀጣናዊ ትሥሥርን የሉዓላዊነት እና የአህጉራዊ መሪነት ማረጋገጫ ያደረገው የመደመር መንግሥት ስልታዊ ራዕይ በተጨባጭ መሬት እየረገጠ ይገኛል።
በተለይም የታዳሽ ኃይል ሀብትን የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ዋና ምሰሶ አድርጎ የመጠቀም ስትራቴጂ፣ የሀገርን የፖለቲካ ተጽዕኖ እና "ለስላሳ ኃይል" (Soft Power) ከፍ ወዳለ ማዕረግ እያሸጋገረው ነው።
ኃይል ለአዳዲስ የቴክኖሎጂ አብዮቶች፣ ለዲጂታል ኢኮኖሚ እና ለሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) መሠረታዊ ግብዓት በሆነበት በዚህ በ21ኛው ክፍለ ዘመን፣ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የኃይል ማዕከል የመሆን ሕልሟን ወደ እውንነት እየቀየረችው ነው።
ይህ እውነታ በወረቀት ላይ በሰፈሩ የይስሙላ ስምምነቶች ሳይሆን፣ በድንበር ተሻጋሪ የኤሌክትሪክ መስመሮች በተግባር የተመሰከረ ሐቅ ነው። ባለፉት ጥቂት የለውጥ ዓመታት የተወሰዱት ቁርጠኛ እርምጃዎች ሱዳን፣ ጅቡቲ እና ኬንያ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ዋነኛ ተጠቃሚዎች እንዲሆኑ አስችለዋል።
የታላቁ የሕዳሴ ግድብ፣ የኮይሻ እና ሌሎች ግዙፍ ፕሮጀክቶች የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ከመሙላት ባለፈ፣ የቀጣናውን የጋራ ዕድገት የሚያረጋግጡ የትሥሥር ድልድዮች ሆነዋል። አሁን ደግሞ ይህ ቁርኝት ወደ ሌሎች ጎረቤት ሀገራት ጭምር መሻገሩ የነገውን ቀጣናዊ ትሥሥር ይበልጥ ብሩህ ያደርገዋል።
ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚደረገው ይህ ዘላቂ ትሥሥር፣ ከንግድ ልውውጥ እና ከገቢ ምንጭነት ባሻገር፣ አንዱ ሀገር ለሌላው የሕልውና ዋስትና የሚሆንበት እና የቀጣናውን ዘላቂ ሰላም በጽኑ መሠረት ላይ የሚገነባ ስልታዊ መሣሪያ መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል።
በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው ረገድም ሀገራችን ከታሪካዊው የልመና አዙሪት ወጥታ በክብር እና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ ፖሊሲን በቁርጠኝነት እየተገበረች ትገኛለች። የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነትን መተግበር፣ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት እና የብሪክስ አባል መሆን የኢትዮጵያን የፋይናንስ እና የኢንቨስትመንት አድማስ በሰፊው ከፍቶታል።
ይህ የፖሊሲ መዋቅር የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ለመቶ ሺዎች ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩ ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶችም በጎረቤት ሀገራት ኢንቨስት በማድረግ አህጉራዊ የኢኮኖሚ አሻራቸውን እንዲያስፋፉ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል።
የኢትዮጵያ የነገ ራዕይ ከአፍሪካ ቀንድ ተሻግሮ እስከ ሰሜን አፍሪካ እና አውሮፓ የሚዘልቅ ታላቅ የኃይል መረብ የመዘርጋት ታላቅ አልሚነት ነው። በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ከውኃ ኃይል በተጨማሪ በፀሐይ፣ በነፋስና በጂኦተርማል ኃይል ላይ የሚደረገው ኢንቨስትመንት የታዳሽ ኃይል ብዝኃነትን በማረጋገጥ፣ ኢትዮጵያን የቀጣናው አስተማማኝ የኃይል "ባንክ" ያደርጋታል።
ይህ ዘላቂ ጉዞ ሀገራችንን ከተረጂነት አዙሪት ሙሉ በሙሉ በማውጣት፣ በዓለም አቀፍ መድረክ በራሷ የምትቆም፣ ክብሯ የተጠበቀ እና የምሥራቅ አፍሪካ የሰላም እና የብልጽግና ፋና እንድትሆን ያደርጋታል።
ምክንያቱም የዚህች ታላቅ ሀገር እውነተኛ እና ዘላቂ ብልጽግና ሊረጋገጥ የሚችለው፣ በራሷ አቅም በልጽጋ ለጎረቤቶቿም የብርሃን እና የዕድገት ዋስትና መሆን ስትችል ብቻ ነው ብለን እናምናለን።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #energy #diplomacy
*************************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ በታሪኳ አዲስ እና ስልታዊ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ይህ ምዕራፍ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በኩራት ከመቁጠር እና ከመቀኘት ባለፈ እነዚያን እምቅ ሀብቶች ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ እና የጂኦፖለቲካ አቅም በመለወጥ ሀገራዊ ልዕልናን ለማረጋገጥ የሚደረግ የታሪክ መታጠፊያ ነው።
ለረጅም ዘመናት በድህነት፣ በዕርዳታ ጥገኝነት እና በውስጥ ስጋቶች ታጥሮ የቆየው የቀድሞው ዲፕሎማሲ ዛሬ በተግባር ተረትቷል። በምትኩም ቀጣናዊ ትሥሥርን የሉዓላዊነት እና የአህጉራዊ መሪነት ማረጋገጫ ያደረገው የመደመር መንግሥት ስልታዊ ራዕይ በተጨባጭ መሬት እየረገጠ ይገኛል።
በተለይም የታዳሽ ኃይል ሀብትን የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ዋና ምሰሶ አድርጎ የመጠቀም ስትራቴጂ፣ የሀገርን የፖለቲካ ተጽዕኖ እና "ለስላሳ ኃይል" (Soft Power) ከፍ ወዳለ ማዕረግ እያሸጋገረው ነው።
ኃይል ለአዳዲስ የቴክኖሎጂ አብዮቶች፣ ለዲጂታል ኢኮኖሚ እና ለሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) መሠረታዊ ግብዓት በሆነበት በዚህ በ21ኛው ክፍለ ዘመን፣ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የኃይል ማዕከል የመሆን ሕልሟን ወደ እውንነት እየቀየረችው ነው።
ይህ እውነታ በወረቀት ላይ በሰፈሩ የይስሙላ ስምምነቶች ሳይሆን፣ በድንበር ተሻጋሪ የኤሌክትሪክ መስመሮች በተግባር የተመሰከረ ሐቅ ነው። ባለፉት ጥቂት የለውጥ ዓመታት የተወሰዱት ቁርጠኛ እርምጃዎች ሱዳን፣ ጅቡቲ እና ኬንያ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ዋነኛ ተጠቃሚዎች እንዲሆኑ አስችለዋል።
የታላቁ የሕዳሴ ግድብ፣ የኮይሻ እና ሌሎች ግዙፍ ፕሮጀክቶች የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ከመሙላት ባለፈ፣ የቀጣናውን የጋራ ዕድገት የሚያረጋግጡ የትሥሥር ድልድዮች ሆነዋል። አሁን ደግሞ ይህ ቁርኝት ወደ ሌሎች ጎረቤት ሀገራት ጭምር መሻገሩ የነገውን ቀጣናዊ ትሥሥር ይበልጥ ብሩህ ያደርገዋል።
ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚደረገው ይህ ዘላቂ ትሥሥር፣ ከንግድ ልውውጥ እና ከገቢ ምንጭነት ባሻገር፣ አንዱ ሀገር ለሌላው የሕልውና ዋስትና የሚሆንበት እና የቀጣናውን ዘላቂ ሰላም በጽኑ መሠረት ላይ የሚገነባ ስልታዊ መሣሪያ መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል።
በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው ረገድም ሀገራችን ከታሪካዊው የልመና አዙሪት ወጥታ በክብር እና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ ፖሊሲን በቁርጠኝነት እየተገበረች ትገኛለች። የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነትን መተግበር፣ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት እና የብሪክስ አባል መሆን የኢትዮጵያን የፋይናንስ እና የኢንቨስትመንት አድማስ በሰፊው ከፍቶታል።
ይህ የፖሊሲ መዋቅር የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ለመቶ ሺዎች ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩ ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶችም በጎረቤት ሀገራት ኢንቨስት በማድረግ አህጉራዊ የኢኮኖሚ አሻራቸውን እንዲያስፋፉ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል።
የኢትዮጵያ የነገ ራዕይ ከአፍሪካ ቀንድ ተሻግሮ እስከ ሰሜን አፍሪካ እና አውሮፓ የሚዘልቅ ታላቅ የኃይል መረብ የመዘርጋት ታላቅ አልሚነት ነው። በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ከውኃ ኃይል በተጨማሪ በፀሐይ፣ በነፋስና በጂኦተርማል ኃይል ላይ የሚደረገው ኢንቨስትመንት የታዳሽ ኃይል ብዝኃነትን በማረጋገጥ፣ ኢትዮጵያን የቀጣናው አስተማማኝ የኃይል "ባንክ" ያደርጋታል።
ይህ ዘላቂ ጉዞ ሀገራችንን ከተረጂነት አዙሪት ሙሉ በሙሉ በማውጣት፣ በዓለም አቀፍ መድረክ በራሷ የምትቆም፣ ክብሯ የተጠበቀ እና የምሥራቅ አፍሪካ የሰላም እና የብልጽግና ፋና እንድትሆን ያደርጋታል።
ምክንያቱም የዚህች ታላቅ ሀገር እውነተኛ እና ዘላቂ ብልጽግና ሊረጋገጥ የሚችለው፣ በራሷ አቅም በልጽጋ ለጎረቤቶቿም የብርሃን እና የዕድገት ዋስትና መሆን ስትችል ብቻ ነው ብለን እናምናለን።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #energy #diplomacy
1 month ago
ሰላም፤ እንደምን አደራችሁ?
የነገዋን ኢትዮጵያ በጽኑ መሠረት ላይ የማቆም ሉዓላዊ ጉዞ ...
የቅኝ ገዢዎች የአፍሪካን ሕዝቦችን ለማንበርከክ የተጠቀሙበት ዋነኛ መሣሪያ ዘመናዊ የጦር መሣሪያ ብቻ ሳይሆን ሕዝቦችን በመከፋፈል የመግዛት ስትራቴጂ በበርካታ የአፍሪካ ሀገራት ለዘመናት የዘለቀ ትልቅ ማኅበራዊ ስብራትና ጠባሳ ጥሎ አልፏል።
በኢትዮጵያ ላይም ተመሳሳይ የሆነ ሴራ በመስራት ለመከፋፈል የተሞከረ ቢሆንም፤ መንግሥታዊ ሥርዓትን ለሺህ ዓመታት ጠንቅቃ የምታውቀው ኢትዮጵያ ልጆች በጠላት ሴራ ሳይከፋፈሉ ልዩነቶቻቸውን ወደጎን አድርገው በአንድነት በመቆም ሀገራቸውን የነጻነትና የጥቁር ሕዝቦች የትግል ተምሳሌት እንድትሆን አድርገዋል።
በዚህም የአፍሪካ የነጻነት እና የአንድነት ቀንዲል የሆነችው ኢትዮጵያ የጋራ ማንነትን የሚያጠናክር፣ ወንድማማችነትን የሚያጎለብት አሰባሳቢ ትርክት በመገንባት ላይ ትገኛለች።
በዚህ ሂደት የመደመር እሳቤ የተለያዩ አቅሞችንና እሴቶችን ለጋራ ዓላማ ለማሰባብሰብ እንዲሁም የሀገር ውስጥ አንድነትን ለማጠናከር እንደ ሁነኛ መፍትሔ እያገለገለ ይገኛል።
ይህ እሳቤ አቅምን ከመበተን ይልቅ፣ ሀገራዊ ጸጋዎችን ወደ አንድ ማዕከል በማምጣት የጋራ ራዕይን የማሳካት ዓላማ ያለው ሲሆን፤ ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበርና በአፍሪካ ያላትን የመሪነት ሚና ለማጎልበት ወሳኝ መሠረት ነው።
የመደመር መንገድ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ስርዓት በጽኑ መሰረት ላይ እንዲቀመጥ፣ ዘላቂ፣ አካታችና አሳታፊ እንዲሆን እንዲሁም የሁሉም የሆነች ኢትዮጵያን ለመገንባት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
በታሪክና በፖለቲካዊ አመለካከቶች ዙሪያ ያሉ ልዩነቶችን በሰለጠነ ውይይት ለመፍታት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ በታሪክ፣ በፖለቲካና በሀገራዊ ምልክቶች ዙሪያ ያሉ ልዩነቶችን በውይይት ለመፍታት የሚደረገው ጥረት የመደማመጥ ባሕልን እያጠናከረ ነው።
ከዚህ በተጨማሪ የጋራ ማንነትን በተጨባጭ ለመግለጽ የሚያስችሉ እንደ ዓድዋ ድል መታሰቢያ ያሉ ታላላቅ ማዕከላት የሁሉንም ኢትዮጵያውያን የጋራ የነፃነትና የድል ታሪክ የሚያወሱ ፕሮጀክቶች መገንባት የብሔረሰቦችን ባህልና ሥልጣኔ በአንድ ጥላ ሥር በማምጣት hገራዊ ኩራትንና ትስስርን የሚያጎለብት ስራ ተሰርቷል።
እንዲሁም በትምህርት ሥርዓት ውስጥ ጭምር ተማሪዎች ስለ መላው ኢትዮጵያውያን የጋራ እሴቶችና ታሪካዊ ትስስሮች እንዲማሩ የሥርዓተ ትምህርት ማሻሻያዎች እየተደረጉ ይገኛሉ።
የጋራ ትርክት ግንባታ ከውስጥ ሰላም ባለፈ ከሀገራዊ ሕልውና እና ከጂኦፖለቲካዊ ጥንካሬ ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት ያለው በመሆኑ አሰባሳቢ ትርክቶችን እንደ ትልቅ መሣሪያ በመጠቀም የብሔራዊ ጥቅም ማጠንጠኛዎችን የሚያስከብርና በሉዓላዊነት ጉዳይ የማይደራደር ዜጋ ለመቅረጽ እየተሰራ ይገኛል።
በኢትዮጵያ እየተከናወነ የሚገኘው የጋራ ማንነትን የማጠናከር ሥራዎች ልዩነቶችን ውበት አድርጎ በመውሰድ ጠንካራ አንድነት ያለው በአህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ደግሞ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆነ ሀገረ መንግሥት መገንባት ነው።
በመሆኑም የወደፊቱን ሀገራዊ ጉዞ ስኬታማ ለማድረግ ያለፉትን ስኬቶች ማጉላትና የጋራ ትርክትን ማሳደግ የእያንዳንዱ ዜጋ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና የምሁራን ኃላፊነት ሆኖ ይቀጥላል።
አሰባሳቢና ገዢ ትርክት ለማስረጽ የሚዲያ፣ የኮሙኒኬሽንና የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች ሚና ከፍተኛ ሲሆን፤ አብሮነትን የሚያጠናክሩ ሥራዎችን መቅረጽ እንዲሁም አፍራሽ የትርክት ጫናዎችን በእውቀትና በእውነት መመከት ይገባል።
የነገዋን ኢትዮጵያ በጽኑ መሠረት ላይ የማቆም ሉዓላዊ ጉዞ ...
የቅኝ ገዢዎች የአፍሪካን ሕዝቦችን ለማንበርከክ የተጠቀሙበት ዋነኛ መሣሪያ ዘመናዊ የጦር መሣሪያ ብቻ ሳይሆን ሕዝቦችን በመከፋፈል የመግዛት ስትራቴጂ በበርካታ የአፍሪካ ሀገራት ለዘመናት የዘለቀ ትልቅ ማኅበራዊ ስብራትና ጠባሳ ጥሎ አልፏል።
በኢትዮጵያ ላይም ተመሳሳይ የሆነ ሴራ በመስራት ለመከፋፈል የተሞከረ ቢሆንም፤ መንግሥታዊ ሥርዓትን ለሺህ ዓመታት ጠንቅቃ የምታውቀው ኢትዮጵያ ልጆች በጠላት ሴራ ሳይከፋፈሉ ልዩነቶቻቸውን ወደጎን አድርገው በአንድነት በመቆም ሀገራቸውን የነጻነትና የጥቁር ሕዝቦች የትግል ተምሳሌት እንድትሆን አድርገዋል።
በዚህም የአፍሪካ የነጻነት እና የአንድነት ቀንዲል የሆነችው ኢትዮጵያ የጋራ ማንነትን የሚያጠናክር፣ ወንድማማችነትን የሚያጎለብት አሰባሳቢ ትርክት በመገንባት ላይ ትገኛለች።
በዚህ ሂደት የመደመር እሳቤ የተለያዩ አቅሞችንና እሴቶችን ለጋራ ዓላማ ለማሰባብሰብ እንዲሁም የሀገር ውስጥ አንድነትን ለማጠናከር እንደ ሁነኛ መፍትሔ እያገለገለ ይገኛል።
ይህ እሳቤ አቅምን ከመበተን ይልቅ፣ ሀገራዊ ጸጋዎችን ወደ አንድ ማዕከል በማምጣት የጋራ ራዕይን የማሳካት ዓላማ ያለው ሲሆን፤ ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበርና በአፍሪካ ያላትን የመሪነት ሚና ለማጎልበት ወሳኝ መሠረት ነው።
የመደመር መንገድ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ስርዓት በጽኑ መሰረት ላይ እንዲቀመጥ፣ ዘላቂ፣ አካታችና አሳታፊ እንዲሆን እንዲሁም የሁሉም የሆነች ኢትዮጵያን ለመገንባት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
በታሪክና በፖለቲካዊ አመለካከቶች ዙሪያ ያሉ ልዩነቶችን በሰለጠነ ውይይት ለመፍታት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ በታሪክ፣ በፖለቲካና በሀገራዊ ምልክቶች ዙሪያ ያሉ ልዩነቶችን በውይይት ለመፍታት የሚደረገው ጥረት የመደማመጥ ባሕልን እያጠናከረ ነው።
ከዚህ በተጨማሪ የጋራ ማንነትን በተጨባጭ ለመግለጽ የሚያስችሉ እንደ ዓድዋ ድል መታሰቢያ ያሉ ታላላቅ ማዕከላት የሁሉንም ኢትዮጵያውያን የጋራ የነፃነትና የድል ታሪክ የሚያወሱ ፕሮጀክቶች መገንባት የብሔረሰቦችን ባህልና ሥልጣኔ በአንድ ጥላ ሥር በማምጣት hገራዊ ኩራትንና ትስስርን የሚያጎለብት ስራ ተሰርቷል።
እንዲሁም በትምህርት ሥርዓት ውስጥ ጭምር ተማሪዎች ስለ መላው ኢትዮጵያውያን የጋራ እሴቶችና ታሪካዊ ትስስሮች እንዲማሩ የሥርዓተ ትምህርት ማሻሻያዎች እየተደረጉ ይገኛሉ።
የጋራ ትርክት ግንባታ ከውስጥ ሰላም ባለፈ ከሀገራዊ ሕልውና እና ከጂኦፖለቲካዊ ጥንካሬ ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት ያለው በመሆኑ አሰባሳቢ ትርክቶችን እንደ ትልቅ መሣሪያ በመጠቀም የብሔራዊ ጥቅም ማጠንጠኛዎችን የሚያስከብርና በሉዓላዊነት ጉዳይ የማይደራደር ዜጋ ለመቅረጽ እየተሰራ ይገኛል።
በኢትዮጵያ እየተከናወነ የሚገኘው የጋራ ማንነትን የማጠናከር ሥራዎች ልዩነቶችን ውበት አድርጎ በመውሰድ ጠንካራ አንድነት ያለው በአህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ደግሞ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆነ ሀገረ መንግሥት መገንባት ነው።
በመሆኑም የወደፊቱን ሀገራዊ ጉዞ ስኬታማ ለማድረግ ያለፉትን ስኬቶች ማጉላትና የጋራ ትርክትን ማሳደግ የእያንዳንዱ ዜጋ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና የምሁራን ኃላፊነት ሆኖ ይቀጥላል።
አሰባሳቢና ገዢ ትርክት ለማስረጽ የሚዲያ፣ የኮሙኒኬሽንና የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች ሚና ከፍተኛ ሲሆን፤ አብሮነትን የሚያጠናክሩ ሥራዎችን መቅረጽ እንዲሁም አፍራሽ የትርክት ጫናዎችን በእውቀትና በእውነት መመከት ይገባል።
1 month ago
ዶላር ጉዱ ፈላ
#ethiopia | ቻይና በየዓመቱ በሻንጋይ በሚካሄደው የሉጂያዙይ ፎረም ላይ የአሜሪካ ዶላር በዓለም ላይ ያለውን ፍጹም የበላይነት ለመገዳደር የሚያስችላትን አዲስ ስትራቴጂ ይፋ አድርጋለች።
ቤጂንግ ያቀረበቻቸው አዳዲስ እርምጃዎች (RMB) የውጭ ፋይናንስን ማሳደግ ለውጭ ሀገራት ማዕከላዊ ባንኮች አዳዲስ የፋይናንስ አቅርቦቶችን መፍጠር እና የድንበር ተሻጋሪ የንግድ ልውውጦችን ማስፋፋት ላይ ያተኮሩ ናቸው።
ይህ ሂደት ዶላርን በአንድ ጀምበር ሙሉ በሙሉ ለመተካት ሳይሆን የቻይናን እና የሌሎች ሀገራትን በዶላር መዋቅር ላይ ያለውን ጥገኝነት ደረጃ በደረጃ ለመቀነስ ታስቦ በተግባር እየተገነባ ያለ አማራጭ የፋይናንስ ልማት ነው።
ይህ የቤጂንግ እንቅስቃሴ ከገንዘብ ነክ ጉዳይ ይልቅ ትልቅ የጂኦፖለቲካ ፍልሚያ ሲሆን አሜሪካ ላለፉት ሰማንያ ዓመታት በዶላር ኃይል በመጠቀም ስትጠቀምባቸው የነበሩትን እንደ ማዕቀብ መጣልና የዓለምን የካፒታል ፍሰት መቆጣጠር ያሉ የፖለቲካ ተፅዕኖዎችን ለመቀየር ያለመ ነው።
ቻይና ይህንን የአሜሪካን የአንድ ወገን የፋይናንስ የበላይነት ለመገዳደርና ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አዲስ አማራጭ መድረክ ለመፍጠር በአሁኑ ወቅት ከመቼውም ጊዜ በላይ ምቹ ጊዜ ላይ ትገኛለች።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ቻይና በየዓመቱ በሻንጋይ በሚካሄደው የሉጂያዙይ ፎረም ላይ የአሜሪካ ዶላር በዓለም ላይ ያለውን ፍጹም የበላይነት ለመገዳደር የሚያስችላትን አዲስ ስትራቴጂ ይፋ አድርጋለች።
ቤጂንግ ያቀረበቻቸው አዳዲስ እርምጃዎች (RMB) የውጭ ፋይናንስን ማሳደግ ለውጭ ሀገራት ማዕከላዊ ባንኮች አዳዲስ የፋይናንስ አቅርቦቶችን መፍጠር እና የድንበር ተሻጋሪ የንግድ ልውውጦችን ማስፋፋት ላይ ያተኮሩ ናቸው።
ይህ ሂደት ዶላርን በአንድ ጀምበር ሙሉ በሙሉ ለመተካት ሳይሆን የቻይናን እና የሌሎች ሀገራትን በዶላር መዋቅር ላይ ያለውን ጥገኝነት ደረጃ በደረጃ ለመቀነስ ታስቦ በተግባር እየተገነባ ያለ አማራጭ የፋይናንስ ልማት ነው።
ይህ የቤጂንግ እንቅስቃሴ ከገንዘብ ነክ ጉዳይ ይልቅ ትልቅ የጂኦፖለቲካ ፍልሚያ ሲሆን አሜሪካ ላለፉት ሰማንያ ዓመታት በዶላር ኃይል በመጠቀም ስትጠቀምባቸው የነበሩትን እንደ ማዕቀብ መጣልና የዓለምን የካፒታል ፍሰት መቆጣጠር ያሉ የፖለቲካ ተፅዕኖዎችን ለመቀየር ያለመ ነው።
ቻይና ይህንን የአሜሪካን የአንድ ወገን የፋይናንስ የበላይነት ለመገዳደርና ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አዲስ አማራጭ መድረክ ለመፍጠር በአሁኑ ወቅት ከመቼውም ጊዜ በላይ ምቹ ጊዜ ላይ ትገኛለች።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) አፍሪካውያን ሀገራት እርስ በእርስ ለሚያደርጉት የንግድ ልውውጥ በውጭ ምንዛሬ (በተለይም በዶላር እና ዩሮ) ላይ ያላቸውን ጥገኝነት ለመቀነስ፣ የፓን-አፍሪካ የክፍያ እና ማቋቋሚያ ስርዓትን (PAPSS) አጠቃቀም በከፍተኛ ፍጥነት እያሳደጉ መሆኑን የአፍሪካ ኤክስፖርት-ኢምፖርት ባንክ የ2026 ሪፖርት አጋለጠ። ይህ የክፍያ ስርዓት ሀገራቱ በራሳቸው የሀገር ውስጥ ገንዘብ ቀጥታ ግብይት እንዲፈጽሙ በማስቻል፣ የውጭ ባንኮችን ጣልቃ ገብነት እና የግብይት ወጪን በእጅጉ የቀነሰ መሆኑ ተጠቁሟል።
ባንኩ ይህንን የዲጂታል ክፍያ መሰረተ ልማት ማስፋፋት አስቸኳይ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው ያለው፣ አሁን ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ እየታየ ያለውን የጂኦፖለቲካዊ ውጥረት እና የንግድ ጥበቃ ፖሊሲዎችን ታሳቢ በማድረግ ነው። በተለይም በአዲሱ የአሜሪካ አስተዳደር የንግድ ፖሊሲ ላይ የታየውን ለውጥ ተከትሎ በ57 የአፍሪካ ሀገራት ላይ የታሪፍ ጭማሪ (በሌሴቶ ላይ እስከ 50 በመቶ የደረሰ) መጣሉ፣ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሀገራት የጨርቃጨርቅ ኤክስፖርት ገበያ ላይ ከፍተኛ ጫና እያንዣበበ መሆኑን ሪፖርቱ አትቷል። የአጎዋ (AGOA) ተጠቃሚ ሀገራትም ቢሆኑ ከተጨማሪው የ10 በመቶ ታሪፍ ጫና ማምለጥ አልቻሉም። ከዚህም በተጨማሪ በቀይ ባህር አካባቢ ያለው አለመረጋጋት፣ አፍሪካ የራሷን የውስጥ ንግድ ትስስር እንድታጠናክር አስገዳጅ ሁኔታ ፈጥሯል።
ምንም እንኳን የአፍሪካ አጠቃላይ የዓለም አቀፍ ንግድ ድርሻ አሁንም ዝቅተኛ (3.1 በመቶ) ቢሆንም፣ በ2025 የአፍሪካ የውስጥ እርስ በእርስ ንግድ በ5.47 በመቶ በማደግ ወደ 213.8 ቢሊዮን ዶላር ከፍ ማለቱ ተመዝግቧል። ለዚህ ዕድገት ኢትዮጵያ፣ ዩጋንዳ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ዛምቢያ እና ደቡብ አፍሪካ ግንባር ቀደም ሚና ተጫውተዋል።
ሪፖርቱ አክሎም፣ የአፍሪካ ሀገራት አሁን ላይ ከገጠማቸው የታሪፍ ጫና፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እና የውጭ ተጽዕኖ ለማምለጥ፣ ንግዳቸውን ይበልጥ ወደ ብሪክስ ሀገራት ማለትም ወደ ቻይና፣ ህንድ፣ ብራዚል እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በማዞር አማራጭ ገበያዎችን መፍጠር እንዳለባቸው አጥብቆ መክሯል።
ባንኩ ይህንን የዲጂታል ክፍያ መሰረተ ልማት ማስፋፋት አስቸኳይ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው ያለው፣ አሁን ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ እየታየ ያለውን የጂኦፖለቲካዊ ውጥረት እና የንግድ ጥበቃ ፖሊሲዎችን ታሳቢ በማድረግ ነው። በተለይም በአዲሱ የአሜሪካ አስተዳደር የንግድ ፖሊሲ ላይ የታየውን ለውጥ ተከትሎ በ57 የአፍሪካ ሀገራት ላይ የታሪፍ ጭማሪ (በሌሴቶ ላይ እስከ 50 በመቶ የደረሰ) መጣሉ፣ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሀገራት የጨርቃጨርቅ ኤክስፖርት ገበያ ላይ ከፍተኛ ጫና እያንዣበበ መሆኑን ሪፖርቱ አትቷል። የአጎዋ (AGOA) ተጠቃሚ ሀገራትም ቢሆኑ ከተጨማሪው የ10 በመቶ ታሪፍ ጫና ማምለጥ አልቻሉም። ከዚህም በተጨማሪ በቀይ ባህር አካባቢ ያለው አለመረጋጋት፣ አፍሪካ የራሷን የውስጥ ንግድ ትስስር እንድታጠናክር አስገዳጅ ሁኔታ ፈጥሯል።
ምንም እንኳን የአፍሪካ አጠቃላይ የዓለም አቀፍ ንግድ ድርሻ አሁንም ዝቅተኛ (3.1 በመቶ) ቢሆንም፣ በ2025 የአፍሪካ የውስጥ እርስ በእርስ ንግድ በ5.47 በመቶ በማደግ ወደ 213.8 ቢሊዮን ዶላር ከፍ ማለቱ ተመዝግቧል። ለዚህ ዕድገት ኢትዮጵያ፣ ዩጋንዳ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ዛምቢያ እና ደቡብ አፍሪካ ግንባር ቀደም ሚና ተጫውተዋል።
ሪፖርቱ አክሎም፣ የአፍሪካ ሀገራት አሁን ላይ ከገጠማቸው የታሪፍ ጫና፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እና የውጭ ተጽዕኖ ለማምለጥ፣ ንግዳቸውን ይበልጥ ወደ ብሪክስ ሀገራት ማለትም ወደ ቻይና፣ ህንድ፣ ብራዚል እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በማዞር አማራጭ ገበያዎችን መፍጠር እንዳለባቸው አጥብቆ መክሯል።
2 months ago
ከ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ማግስት፦ የነገዋ ኢትዮጵያ አቅጣጫ እና ከመንግሥት የሚጠበቁ ኃላፊነቶች
***************************
የዘንድሮው 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዞ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ታሪካዊ ምዕራፍ ነው።
ምርጫውን አሸንፎ መንግሥት የሚመሰርተው ፓርቲ የሕዝብን አደራ ተቀብሎ ሀገራችንን ወደ ተሻለ ምዕራፍ የማሻገር ከባድ ኃገራዊ ኃላፊነት ይወድቅበታል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተለያዩ መድረኮች ባስተላለፏቸው መልዕክቶች፣ የፓርላማውን አብላጫ ድምጽ በማግኘት መንግሥት የሚመሰርተው ፓርቲ ድርብ ኃላፊነት እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።
ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሻገር የተጀመሩ እና በዕቅድ የተያዙ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን በተሻለ ሁኔታ መፈጸም ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው። ከእነዚህ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፡-
ሰብዓዊነትን ማዕከል ያደረገ አመራር እና የጸጥታ ተቋማት ግንባታ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ "ሰብዓዊነትን ማዕከል ያደረገ አመራር" አስፈላጊነትን ደጋግመው አንስተዋል።
አዲስ የሚመሰረተው መንግሥትም ይህን መርህ በተግባር በመተርጎም የዜጎችን ደኅንነት እና ሰላም ማስቀደም ይጠበቅበታል።
የጸጥታ እና የደኅንነት ተቋማትን ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ የሆኑ፣ ዘመናዊ እና ሕዝብን የሚያገለግሉ አድርጎ የመገንባቱ የሪፎርም ሥራ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ሲሠራ ቆይቷል። ይህ አሁንም ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
የዜጎች ደኅንነት በእኩልነት ሲረጋገጥ እና የጸጥታ መዋቅሩ የሁሉንም ኢትዮጵያዊ መብት ለማስጠበቅ ሲቆም ብቻ ሀገራዊ መረጋጋትን እና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ማሳካት ይቻላል።
ጎረቤትን ያስቀደመ ዲፕሎማሲ እና ቀጣናዊ ትስስር
በውጭ ግንኙነት ረገድ አሸናፊው ፓርቲ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስጠብቅ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ሥራ መሥራት ይኖርበታል።
መንግሥት የሚከተለውን ጎረቤት ተኮር የዲፕሎማሲ ስትራቴጂ ይበልጥ በማጠናከር ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስር ውስጥ ያላትን የመሪነት ሚና ማስቀጠል ይጠበቅበታል።
ከዚህም ባሻገር ለመካከለኛው ምሥራቅ እና ለባሕረ ሰላጤው ጂኦፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች የቅርብ ትኩረት ሊሰጥ ይገባል።
በቀጣናው ሊፈጠሩ የሚችሉ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎችን የሚቋቋም ሚዛናዊ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲን መተግበር በቀጣይ ከመንግሥት የሚጠበቅ ወሳኝ ኃላፊነት ነው።
የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ
አዲስ የሚመሰረተው መንግሥት ሌላው ትልቅ ኃላፊነት ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትን ማረጋገጥ ነው።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርን በማስፋት የኢትዮጵያን የደን ሽፋን ከማሳደግ ባለፈ፣ ሀገራችን ከካርበን ንግድ ተጠቃሚ የምትሆንበትን "የአረንጓዴ ወርቅ" የኢኮኖሚ ሥርዓት መገንባት ይገባዋል።
ይህ አካሄድ የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባሻገር፣ አዲስ የውጭ ምንዛሬ ማስገኛ አቅም በመፍጠር የዜጎችን ተጠቃሚነት ያረጋግጣል።
የሀገራዊ ምክክር ውጤትን ተግባራዊ ማድረግ
አዲሱ መንግሥት ትልቅ ትኩረት ሊሰጣቸው ከሚገቡ ጉዳዮች መካከል የሀገራዊ ምክክሩን ውጤት ተቀብሎ ወደ ተግባር መቀየር ቀዳሚው ነው።
የምክክሩ ውጤት የነገዋን የበለጸገች እና የተረጋጋች ኢትዮጵያን ለመገንባት ጠንካራ መሰረት የሚጥል ነው።
የምክክሩ ውጤት የሕግ የበላይነት የነገሰባት፣ ሰብዓዊ መብቶች ይበልጥ የሚከበሩባት እና የተጠናከረ የፍትሕ ሥርዓት የተረጋገጠባት ሀገር ለመገንባት ወሳኝ ግብዓት ነው።
የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም
ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ውጤታማነቱ እየታየ ይገኛል። በዚህም ኢትዮጵያ በዘንድሮው በጀት ዓመት ማጠቃለያ የ10.2 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት እንደምታስመዘግብ ይጠበቃል።
የመንግሥት ቀጣዩ ዋና ሥራ ይህ ዕድገት ወደ እያንዳንዱ ዜጋ ሕይወት እንዲወርድ ማድረግ ነው።
ለዚህም የዋጋ ንረትን መቆጣጠር፣ የኑሮ ውድነትን ማቃለል እና የውጭ ብድር ጫናን ማስተካከል ከአዲሱ መንግሥት የሚጠበቁ እና ፈጣን ምላሽ የሚሹ አንገብጋቢ የቤት ሥራዎች ናቸው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopia #economicreform #macroeconomy #diplomacy #greenlegacy #ebc
***************************
የዘንድሮው 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዞ ውስጥ ትልቅ ትርጉም ያለው ታሪካዊ ምዕራፍ ነው።
ምርጫውን አሸንፎ መንግሥት የሚመሰርተው ፓርቲ የሕዝብን አደራ ተቀብሎ ሀገራችንን ወደ ተሻለ ምዕራፍ የማሻገር ከባድ ኃገራዊ ኃላፊነት ይወድቅበታል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተለያዩ መድረኮች ባስተላለፏቸው መልዕክቶች፣ የፓርላማውን አብላጫ ድምጽ በማግኘት መንግሥት የሚመሰርተው ፓርቲ ድርብ ኃላፊነት እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።
ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሻገር የተጀመሩ እና በዕቅድ የተያዙ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን በተሻለ ሁኔታ መፈጸም ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው። ከእነዚህ ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፡-
ሰብዓዊነትን ማዕከል ያደረገ አመራር እና የጸጥታ ተቋማት ግንባታ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ "ሰብዓዊነትን ማዕከል ያደረገ አመራር" አስፈላጊነትን ደጋግመው አንስተዋል።
አዲስ የሚመሰረተው መንግሥትም ይህን መርህ በተግባር በመተርጎም የዜጎችን ደኅንነት እና ሰላም ማስቀደም ይጠበቅበታል።
የጸጥታ እና የደኅንነት ተቋማትን ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ የሆኑ፣ ዘመናዊ እና ሕዝብን የሚያገለግሉ አድርጎ የመገንባቱ የሪፎርም ሥራ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ሲሠራ ቆይቷል። ይህ አሁንም ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
የዜጎች ደኅንነት በእኩልነት ሲረጋገጥ እና የጸጥታ መዋቅሩ የሁሉንም ኢትዮጵያዊ መብት ለማስጠበቅ ሲቆም ብቻ ሀገራዊ መረጋጋትን እና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን ማሳካት ይቻላል።
ጎረቤትን ያስቀደመ ዲፕሎማሲ እና ቀጣናዊ ትስስር
በውጭ ግንኙነት ረገድ አሸናፊው ፓርቲ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያስጠብቅ ጠንካራ የዲፕሎማሲ ሥራ መሥራት ይኖርበታል።
መንግሥት የሚከተለውን ጎረቤት ተኮር የዲፕሎማሲ ስትራቴጂ ይበልጥ በማጠናከር ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ትስስር ውስጥ ያላትን የመሪነት ሚና ማስቀጠል ይጠበቅበታል።
ከዚህም ባሻገር ለመካከለኛው ምሥራቅ እና ለባሕረ ሰላጤው ጂኦፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች የቅርብ ትኩረት ሊሰጥ ይገባል።
በቀጣናው ሊፈጠሩ የሚችሉ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎችን የሚቋቋም ሚዛናዊ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲን መተግበር በቀጣይ ከመንግሥት የሚጠበቅ ወሳኝ ኃላፊነት ነው።
የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ
አዲስ የሚመሰረተው መንግሥት ሌላው ትልቅ ኃላፊነት ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትን ማረጋገጥ ነው።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርን በማስፋት የኢትዮጵያን የደን ሽፋን ከማሳደግ ባለፈ፣ ሀገራችን ከካርበን ንግድ ተጠቃሚ የምትሆንበትን "የአረንጓዴ ወርቅ" የኢኮኖሚ ሥርዓት መገንባት ይገባዋል።
ይህ አካሄድ የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባሻገር፣ አዲስ የውጭ ምንዛሬ ማስገኛ አቅም በመፍጠር የዜጎችን ተጠቃሚነት ያረጋግጣል።
የሀገራዊ ምክክር ውጤትን ተግባራዊ ማድረግ
አዲሱ መንግሥት ትልቅ ትኩረት ሊሰጣቸው ከሚገቡ ጉዳዮች መካከል የሀገራዊ ምክክሩን ውጤት ተቀብሎ ወደ ተግባር መቀየር ቀዳሚው ነው።
የምክክሩ ውጤት የነገዋን የበለጸገች እና የተረጋጋች ኢትዮጵያን ለመገንባት ጠንካራ መሰረት የሚጥል ነው።
የምክክሩ ውጤት የሕግ የበላይነት የነገሰባት፣ ሰብዓዊ መብቶች ይበልጥ የሚከበሩባት እና የተጠናከረ የፍትሕ ሥርዓት የተረጋገጠባት ሀገር ለመገንባት ወሳኝ ግብዓት ነው።
የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም
ኢትዮጵያ የተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ውጤታማነቱ እየታየ ይገኛል። በዚህም ኢትዮጵያ በዘንድሮው በጀት ዓመት ማጠቃለያ የ10.2 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት እንደምታስመዘግብ ይጠበቃል።
የመንግሥት ቀጣዩ ዋና ሥራ ይህ ዕድገት ወደ እያንዳንዱ ዜጋ ሕይወት እንዲወርድ ማድረግ ነው።
ለዚህም የዋጋ ንረትን መቆጣጠር፣ የኑሮ ውድነትን ማቃለል እና የውጭ ብድር ጫናን ማስተካከል ከአዲሱ መንግሥት የሚጠበቁ እና ፈጣን ምላሽ የሚሹ አንገብጋቢ የቤት ሥራዎች ናቸው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopia #economicreform #macroeconomy #diplomacy #greenlegacy #ebc
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ከወንበር በላይ ሀገር !
የምርጫ ቦርድ የዘንድሮውን ሀገራዊ ምርጫ ውጤት ይፋ ውጤት የሀገሪቱን የፖለቲካ ካርታ ግልጽ አድርጎታል። ገዥው ብልጽግና ፓርቲ አብላጫውን ወንበር ወስዷል፤ ሀገራችንም ወደ ሌላ አዲስ የፖለቲካ ምዕራፍ ተሻግራለች።
ኢዜማ የለፋውን እና የደከመበትን ያህል ባይሆንም 86 ወንበሮችን አሸንፏል (13ቱ በፌደራል ፓርላማ፣ 73ቱ በክልል ምክር ቤቶች) በዚህ ውጤቱ ኢዜማ በፓርላማው ውስጥ ዋነኛው ተፎካካሪና አማራጭ ድምፅ ሆኖ ወጥቷል። ለመሆኑ ይህ ውጤት የለፋንለትና የተመኘነው ያህል ነው? ፈጽሞ አይደለም። ታዲያ በቀላሉ የምናጣጥለው እና ፋይዳቢስ የሚባልስ ነው? በፍጹም!
ፖለቲካ እንደ ሎተሪ ዕጣ በአንድ ጀምበር ሁሉንም እድል ጠራርጎ የሚወሰድበት ወይንም በተቃራኒው ሁሉንም ተበልቶ በባዶ እጅ እየቆዘሙ አንገት ደፍቶ ወደቤት የሚኬድበት የዕድል ጨዋታ አይደለም። ለኢዜማ 86 ወንበሮች በማሸነፍ፣ ጠንካራ መዋቅርን ለመሥራት እና ቀጣዩ ምርጫ እስኪደርስ መላውን አባላት በንቃት የሚያሳትፍ በርካታ የቤት ሥራ ይዞ መውጣትም በፖለቲካ ዐይን ተጨማሪ የዴሞክራሲ እርምጃ ነው።
ከእኛ ጋር ተፎካካሪ የነበሩ፤ የሕዝብ አመኔታ እና ድምጽ ሲያጡ እና እንዳለሙት ውጤት ሳይቀናቸው ሲቀር፣ የሌላውን ድካምና ውጤት ለማጣጣል እና ስም ለመለጠፍ የሚሮጡትን "አንዳንድ የተቃውሞ ነዋሪዎች" ስናይ... "ያጣ ለማኝ ተሳድቦ ይሄዳል" ከሚለው ነባር የሀገራችን ብሂል የተሻለ ምን ማስተማሪያ ሊገኝላቸው ይችላል?
ሌሎች ደግሞ አሉ። ዓላማቸው ከዓላማችን፤ መንገዳቸውም ከመንገዳችን ስላልገጠመ ብቻ ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ተጥደው ሲረግሙን ውለው ሲረግሙን በማደራቸው ፖለቲካ የተነተኑ የሚመስላቸው የቁራ ጯሂዎች! የተለመደው ቁርጥ ያለ መልሳቸን “ያዋጣል በምትሉት መንገድ ሂዱ! የእኛን መንገድ ለእኛ ተዉልን” የሚል ይሆናል። ዳር ቆመው ሰባራ ሳንቲም ሳያዋጡ ተዓምር ለሚናፍቁ የሰነፍ ቅምጥሎችና ‘የሶሻል ሚዲያ አርበኞች’ መልካም የምኞት ጊዜ ይሁንላቸው ከማለት ውጪስ ምን ይባላል?
እኛ ኢዜማውያን ግን ዲሞክራሲ የሚገነባው እጅጌን ሰብስቦ እና ቆፍጠን ብሎ መሬት ላይ ሥራ በመሥራት መሆኑን ስለምናምን ከባለፈው የምርጫ ተሳትፎአችን በብዙ እጥፍ የጨመረውን ውጤት በጸጋ ተቀብለን እና የሕዝብ ድምጽ አክብረን በጨዋነት እና በስለጠነ ዘመናዊ ፖለቲካ ተሳትፎ ወደፊት እንራመዳለን። በውድድር ውስጥ ማሸነፍን ብቻ ሳይሆን፣ ተሸንፎም ትልቁን ሀገራዊ ስዕል ማየት መቻል የፖለቲካ ብስለት መለኪያ ነውና።
አሁን የምርጫው አጀንዳ ከሞላ ጎደል ተጠናቅቋል፤ አሸናፊዎች ወደየምክር ቤቶቻቸው፤ የተቀረነውም ወደየ እለታዊ ተግባራችን እንመለሳለን። ሀገርን ማገልገል በምክር ቤቶች ተሳትፎ ብቻ አይወሰንም። የሀገር ግንባታ በምርምር ማዕከላት፣ በዩኒቨርሲቲዎች፣ በሙያ ማኅበራት፤ በሲቪክ መድረኮች፣ በልዩ ልዩ የማኅበረሰብ ከገልግሎቶች ውስጥ ይቀጥላል።
… እንዲያውም ሁሉም ሰው በድንገት የሕገ-መንግስት ተንታኝ፣ የጂኦፖለቲካው ነብይ፣ የፌደራሊዝም ሐዋርያ በሚሆንበት በዚያ ድራማዊ የቡና ጠረጴዛ ውይይት ውስጥ ጭምር ሕይወት እንደወትሮው ይቀጥላል።
እስካሁን የተጓዝንበትን ለሀገር እና ለወገን የሚጠቅም የፖለቲካ ተሳትፎን በኩራት እያከበርን፤ አሁን ደግሞ የፓርቲ ማሊያችንን አውልቀን፣ የሙያ ጃኬታችንን ለብሰን ወደ ዋናው ሥራችን ብንመለስ ምን ይለናል? የሽሚዞቻችን እጅጌ ስብስበን "ዳዬ ወደሥራ!" ብለናል።
እግረመንገድም ከአድካሚው እና እንደ ልቅሶ ቤት አግዳሚ ወንበር ከሊቅ እስከ ደቂቅ አኩል ተኮልኩሎ ከፊሉ ሲራገም ከፊሉ ሲመርቅ ከሚውልበት የማኅበራዊ ሚዲያ መድረክም እስከውዲያኛውም ባይሆንም እረፍት መውጣት ተገቢ አይደለም ትላላቸሁ?
መልክም ጊዜ !
(አርኪቴክት ዮሐንስ መኮንን የኢዜማ ከፍተኛ አመራር)
#ኢትዮጵያ #ኢዜማ #ሀገርግንባታ #ምርጫ2018 #ዲሞክራሲ
የምርጫ ቦርድ የዘንድሮውን ሀገራዊ ምርጫ ውጤት ይፋ ውጤት የሀገሪቱን የፖለቲካ ካርታ ግልጽ አድርጎታል። ገዥው ብልጽግና ፓርቲ አብላጫውን ወንበር ወስዷል፤ ሀገራችንም ወደ ሌላ አዲስ የፖለቲካ ምዕራፍ ተሻግራለች።
ኢዜማ የለፋውን እና የደከመበትን ያህል ባይሆንም 86 ወንበሮችን አሸንፏል (13ቱ በፌደራል ፓርላማ፣ 73ቱ በክልል ምክር ቤቶች) በዚህ ውጤቱ ኢዜማ በፓርላማው ውስጥ ዋነኛው ተፎካካሪና አማራጭ ድምፅ ሆኖ ወጥቷል። ለመሆኑ ይህ ውጤት የለፋንለትና የተመኘነው ያህል ነው? ፈጽሞ አይደለም። ታዲያ በቀላሉ የምናጣጥለው እና ፋይዳቢስ የሚባልስ ነው? በፍጹም!
ፖለቲካ እንደ ሎተሪ ዕጣ በአንድ ጀምበር ሁሉንም እድል ጠራርጎ የሚወሰድበት ወይንም በተቃራኒው ሁሉንም ተበልቶ በባዶ እጅ እየቆዘሙ አንገት ደፍቶ ወደቤት የሚኬድበት የዕድል ጨዋታ አይደለም። ለኢዜማ 86 ወንበሮች በማሸነፍ፣ ጠንካራ መዋቅርን ለመሥራት እና ቀጣዩ ምርጫ እስኪደርስ መላውን አባላት በንቃት የሚያሳትፍ በርካታ የቤት ሥራ ይዞ መውጣትም በፖለቲካ ዐይን ተጨማሪ የዴሞክራሲ እርምጃ ነው።
ከእኛ ጋር ተፎካካሪ የነበሩ፤ የሕዝብ አመኔታ እና ድምጽ ሲያጡ እና እንዳለሙት ውጤት ሳይቀናቸው ሲቀር፣ የሌላውን ድካምና ውጤት ለማጣጣል እና ስም ለመለጠፍ የሚሮጡትን "አንዳንድ የተቃውሞ ነዋሪዎች" ስናይ... "ያጣ ለማኝ ተሳድቦ ይሄዳል" ከሚለው ነባር የሀገራችን ብሂል የተሻለ ምን ማስተማሪያ ሊገኝላቸው ይችላል?
ሌሎች ደግሞ አሉ። ዓላማቸው ከዓላማችን፤ መንገዳቸውም ከመንገዳችን ስላልገጠመ ብቻ ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ተጥደው ሲረግሙን ውለው ሲረግሙን በማደራቸው ፖለቲካ የተነተኑ የሚመስላቸው የቁራ ጯሂዎች! የተለመደው ቁርጥ ያለ መልሳቸን “ያዋጣል በምትሉት መንገድ ሂዱ! የእኛን መንገድ ለእኛ ተዉልን” የሚል ይሆናል። ዳር ቆመው ሰባራ ሳንቲም ሳያዋጡ ተዓምር ለሚናፍቁ የሰነፍ ቅምጥሎችና ‘የሶሻል ሚዲያ አርበኞች’ መልካም የምኞት ጊዜ ይሁንላቸው ከማለት ውጪስ ምን ይባላል?
እኛ ኢዜማውያን ግን ዲሞክራሲ የሚገነባው እጅጌን ሰብስቦ እና ቆፍጠን ብሎ መሬት ላይ ሥራ በመሥራት መሆኑን ስለምናምን ከባለፈው የምርጫ ተሳትፎአችን በብዙ እጥፍ የጨመረውን ውጤት በጸጋ ተቀብለን እና የሕዝብ ድምጽ አክብረን በጨዋነት እና በስለጠነ ዘመናዊ ፖለቲካ ተሳትፎ ወደፊት እንራመዳለን። በውድድር ውስጥ ማሸነፍን ብቻ ሳይሆን፣ ተሸንፎም ትልቁን ሀገራዊ ስዕል ማየት መቻል የፖለቲካ ብስለት መለኪያ ነውና።
አሁን የምርጫው አጀንዳ ከሞላ ጎደል ተጠናቅቋል፤ አሸናፊዎች ወደየምክር ቤቶቻቸው፤ የተቀረነውም ወደየ እለታዊ ተግባራችን እንመለሳለን። ሀገርን ማገልገል በምክር ቤቶች ተሳትፎ ብቻ አይወሰንም። የሀገር ግንባታ በምርምር ማዕከላት፣ በዩኒቨርሲቲዎች፣ በሙያ ማኅበራት፤ በሲቪክ መድረኮች፣ በልዩ ልዩ የማኅበረሰብ ከገልግሎቶች ውስጥ ይቀጥላል።
… እንዲያውም ሁሉም ሰው በድንገት የሕገ-መንግስት ተንታኝ፣ የጂኦፖለቲካው ነብይ፣ የፌደራሊዝም ሐዋርያ በሚሆንበት በዚያ ድራማዊ የቡና ጠረጴዛ ውይይት ውስጥ ጭምር ሕይወት እንደወትሮው ይቀጥላል።
እስካሁን የተጓዝንበትን ለሀገር እና ለወገን የሚጠቅም የፖለቲካ ተሳትፎን በኩራት እያከበርን፤ አሁን ደግሞ የፓርቲ ማሊያችንን አውልቀን፣ የሙያ ጃኬታችንን ለብሰን ወደ ዋናው ሥራችን ብንመለስ ምን ይለናል? የሽሚዞቻችን እጅጌ ስብስበን "ዳዬ ወደሥራ!" ብለናል።
እግረመንገድም ከአድካሚው እና እንደ ልቅሶ ቤት አግዳሚ ወንበር ከሊቅ እስከ ደቂቅ አኩል ተኮልኩሎ ከፊሉ ሲራገም ከፊሉ ሲመርቅ ከሚውልበት የማኅበራዊ ሚዲያ መድረክም እስከውዲያኛውም ባይሆንም እረፍት መውጣት ተገቢ አይደለም ትላላቸሁ?
መልክም ጊዜ !
(አርኪቴክት ዮሐንስ መኮንን የኢዜማ ከፍተኛ አመራር)
#ኢትዮጵያ #ኢዜማ #ሀገርግንባታ #ምርጫ2018 #ዲሞክራሲ
2 months ago
የመደመር አንቀጽ
*************
ኢትዮጵያ ከጥንት ጀምራ በባሕሩ ዳር የተፈጠረች፤ ዕጣ ፈንታዋም ከባሕሩ ጋር የተቆራኘ ሀገር ናት። በቀይ ባሕር ላይ የነበራት ይዞታ፤ ኢትዮጵያን ጠንካራና በጂኦፖለቲካው ውስጥ ተፈላጊ ሀገር ያደርጋት ነበር።
ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ላይየነበራት ይዞታ እየሟሸሸ ሲመጣና፤ በመጨረሻም ሸቀጧን የምታራግፍበት ኩርማን ወደብ እንኳን ማግኘት ያልቻለችበት የታሪክ ሁኔታ ሲፈጠር ኢትዮጵያ በጂኦፖለቲካው ላይ የነበራት ሚና ኮሰመነ፡፡
ኢትዮጵያ በየትኛውም ዓይነት ሁኔታ ከቀይ ባሕር ስትርቅ የምትሟሽሽ፤ ለቀይ ባሕር ስትቀርብ ደግሞ ገናና የምትሆን ሀገር መሆኗን ታሳቢ ያደረጉ አሻጥሮች የዛሬውን እውነታ ሊፈጥሩ ችለዋል።
የአፍሪካ ቀንድ ምንም እንኳን ወሳኝ የጂኦፖለቲካ ሥፍራ ላይ የሚገኝ ቀጣና ቢሆንም፤ በቀጣናው ላይ ያሉት ሀገራት በግጭትና የእርስ በርስ ጦርነት የሚታመሱ፤ ፖለቲካዊ መረጋጋት የሌለባቸው በመሆኑ፤ ደካማና ዘላቂ ጥቅማቸውን ማስከበር የማይችሉ ሆነዋል።
በአንጻሩ ከባሕሩ በሌላው ጎን የሚገኙት የገልፍ ሀገራት፤ በኢኮኖሚ የፈረጠሙ በመሆናቸው፤ ለቀንዱ ሀገራት ጊዜያዊ ጥቅም በመስጠት ብቻ፤ ዘላቂ የሆነና የበላይነታቸውን የሚያረጋግጥ ጥቅም ከቀንዱ እንዲያገኙ አድርጓቸዋል።
የመደመር ትውልድ
ገጽ - 71
#ethiopianbroadcastingcorporation #ethiopia #ኢትዮጵያ ባሕርበር
*************
ኢትዮጵያ ከጥንት ጀምራ በባሕሩ ዳር የተፈጠረች፤ ዕጣ ፈንታዋም ከባሕሩ ጋር የተቆራኘ ሀገር ናት። በቀይ ባሕር ላይ የነበራት ይዞታ፤ ኢትዮጵያን ጠንካራና በጂኦፖለቲካው ውስጥ ተፈላጊ ሀገር ያደርጋት ነበር።
ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ላይየነበራት ይዞታ እየሟሸሸ ሲመጣና፤ በመጨረሻም ሸቀጧን የምታራግፍበት ኩርማን ወደብ እንኳን ማግኘት ያልቻለችበት የታሪክ ሁኔታ ሲፈጠር ኢትዮጵያ በጂኦፖለቲካው ላይ የነበራት ሚና ኮሰመነ፡፡
ኢትዮጵያ በየትኛውም ዓይነት ሁኔታ ከቀይ ባሕር ስትርቅ የምትሟሽሽ፤ ለቀይ ባሕር ስትቀርብ ደግሞ ገናና የምትሆን ሀገር መሆኗን ታሳቢ ያደረጉ አሻጥሮች የዛሬውን እውነታ ሊፈጥሩ ችለዋል።
የአፍሪካ ቀንድ ምንም እንኳን ወሳኝ የጂኦፖለቲካ ሥፍራ ላይ የሚገኝ ቀጣና ቢሆንም፤ በቀጣናው ላይ ያሉት ሀገራት በግጭትና የእርስ በርስ ጦርነት የሚታመሱ፤ ፖለቲካዊ መረጋጋት የሌለባቸው በመሆኑ፤ ደካማና ዘላቂ ጥቅማቸውን ማስከበር የማይችሉ ሆነዋል።
በአንጻሩ ከባሕሩ በሌላው ጎን የሚገኙት የገልፍ ሀገራት፤ በኢኮኖሚ የፈረጠሙ በመሆናቸው፤ ለቀንዱ ሀገራት ጊዜያዊ ጥቅም በመስጠት ብቻ፤ ዘላቂ የሆነና የበላይነታቸውን የሚያረጋግጥ ጥቅም ከቀንዱ እንዲያገኙ አድርጓቸዋል።
የመደመር ትውልድ
ገጽ - 71
#ethiopianbroadcastingcorporation #ethiopia #ኢትዮጵያ ባሕርበር
2 months ago
ያልተነገረው የአረንጓዴ ዐሻራ ጂኦፖለቲካዊ እና ማክሮ-ኢኮኖሚክ ጉልበት
*******************
ለኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የሀገር ሕልውናን የመታደግ፣ የሀገራዊ ደኅንነትን የማረጋገጥ እና የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን የማስከበር ቁልፍ ስትራቴጂ ነው።
ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት እና አብዛኛው ዜጋዋ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በዝናብ ጥገኝነት ላይ በቆመ ግብርና በምተዳደርባት ሀገር፣ የአፈር መሸርሸር እና የመሬት መራቆት ተራ የተፈጥሮ ክስተቶች አይደሉም፤ ይልቁንም የሕዝብን የምግብ ዋስትና የሚያናጉ፣ ማህበራዊ መረጋጋትን የሚፈትኑ የደህንነት ስጋቶች ናቸው።
በየዓመቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ቶን ለም አፈር በጎርፍ እና በንፋስ እየተጠረገ መሄዱ የኢኮኖሚውን መሠረት የሚንድ በመሆኑ፣ ይህንን አውዳሚ ሂደት በአረንጓዴ ዐሻራ አማካኝነት ለመቀልበስ መነሣት የሀገርን ዘላቂ ሕልውና ከጥፋት የመታደግ የታሪክ ግዴታ ተደርጎ ሊወሰድ ይገባል።
ይህ መጠነ-ሰፊ የአረንጓዴ ልማት ንቅናቄ ከሀገር ውስጥ አልፎ ቀጣናዊ እና ጂኦፖለቲካዊ ፋይዳው እጅግ የጎላ ነው።
በተፈጥሮ መራቆት ምክንያት የሚከሰተውን የተፋሰሶች መድረቅ በመከላከል እና የከርሰ-ምድር ውኃን በከፍተኛ ሁኔታ በማበልጸግ ረገድ የአረንጓዴ ዐሻራ ሚና ወደር የለውም።
ይህ የውኃ ሀብት ጥበቃ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ድንበር ተሻጋሪ ወንዞችን ለሚጋሩ የጎረቤት ሀገራት ጭምር የውኃ ደኅንነትን እና አስተማማኝነትን የሚያረጋግጥ ትልቅ ዋስትናም ነው።
በአፍሪካ ቀንድ እና በናይል ተፋሰስ አካባቢ የሚታየውን የውኃ እጥረት ስጋት በመቅረፍ፣ ሀገራት በውኃ ሀብት አጠቃቀም ዙሪያ ወደ ግጭት እና አለመግባባት ከማምራት ይልቅ በጋራ ልማት እና በትብብር ላይ የተመሠረተ ዲፕሎማሲ እንዲከተሉ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።
በመሆኑም የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ ልማት በቀጣናው ያለውን ሰላም እና ጂኦፖለቲካዊ መረጋጋት በቀጥታ የሚወስን የሰላም ስትራቴጂ ሆኖ ያገለግላል።
በተጨማሪም የሀገራችንን የማክሮ-ኢኮኖሚ መዋቅር ወደ ላቀ እና የማይበገር ደረጃ ለማሸጋገር በሚደረገው ጥረት ውስጥ፣ ይህ አረንጓዴ ኢኮኖሚ የራሱን ጉልህ ዐሻራ እያሳረፈ ይገኛል።
የአካባቢ ጥበቃ ሥራው የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባለፈ፣ በመቶ ሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች በተለይም ደግሞ በማኅበረሰቡ ውስጥ በኢኮኖሚ ተጋላጭ ለሆኑት ወጣቶች እና ሴቶች ሰፊ የሥራ ዕድልን መፍጠር ችሏል።
ይህ ከችግኝ መኮትኮት እስከ ደን ጥበቃ እና ልማት የተዘረጋው የሥራ ዕድል፣ የዜጎችን ዕለታዊ ገቢ ከማሻሻሉም በላይ የሀገራዊ የምጣኔ-ሀብት መቋቋም አቅምን የሚገነባ ጠንካራ ምሰሶ ሆኗል።
በመሆኑም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የአካባቢ ጥበቃን፣ የኢኮኖሚ ዕድገትን እና የጂኦፖለቲካ መረጋጋትን በጋራ በማስተሳሰር የነገዋን የበለጸገች እና ሉዓላዊነቷ የተከበረ ኢትዮጵያን ለመገንባት የተነደፈ ሥልታዊ እና አርቆ አሳቢ የፖሊሲ ምላሽ ነው።
በበረከት ሽመልስ
#ethiopia #ebc #greenlegacy #success
*******************
ለኢትዮጵያ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የሀገር ሕልውናን የመታደግ፣ የሀገራዊ ደኅንነትን የማረጋገጥ እና የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን የማስከበር ቁልፍ ስትራቴጂ ነው።
ከ130 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት እና አብዛኛው ዜጋዋ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በዝናብ ጥገኝነት ላይ በቆመ ግብርና በምተዳደርባት ሀገር፣ የአፈር መሸርሸር እና የመሬት መራቆት ተራ የተፈጥሮ ክስተቶች አይደሉም፤ ይልቁንም የሕዝብን የምግብ ዋስትና የሚያናጉ፣ ማህበራዊ መረጋጋትን የሚፈትኑ የደህንነት ስጋቶች ናቸው።
በየዓመቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ቶን ለም አፈር በጎርፍ እና በንፋስ እየተጠረገ መሄዱ የኢኮኖሚውን መሠረት የሚንድ በመሆኑ፣ ይህንን አውዳሚ ሂደት በአረንጓዴ ዐሻራ አማካኝነት ለመቀልበስ መነሣት የሀገርን ዘላቂ ሕልውና ከጥፋት የመታደግ የታሪክ ግዴታ ተደርጎ ሊወሰድ ይገባል።
ይህ መጠነ-ሰፊ የአረንጓዴ ልማት ንቅናቄ ከሀገር ውስጥ አልፎ ቀጣናዊ እና ጂኦፖለቲካዊ ፋይዳው እጅግ የጎላ ነው።
በተፈጥሮ መራቆት ምክንያት የሚከሰተውን የተፋሰሶች መድረቅ በመከላከል እና የከርሰ-ምድር ውኃን በከፍተኛ ሁኔታ በማበልጸግ ረገድ የአረንጓዴ ዐሻራ ሚና ወደር የለውም።
ይህ የውኃ ሀብት ጥበቃ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ድንበር ተሻጋሪ ወንዞችን ለሚጋሩ የጎረቤት ሀገራት ጭምር የውኃ ደኅንነትን እና አስተማማኝነትን የሚያረጋግጥ ትልቅ ዋስትናም ነው።
በአፍሪካ ቀንድ እና በናይል ተፋሰስ አካባቢ የሚታየውን የውኃ እጥረት ስጋት በመቅረፍ፣ ሀገራት በውኃ ሀብት አጠቃቀም ዙሪያ ወደ ግጭት እና አለመግባባት ከማምራት ይልቅ በጋራ ልማት እና በትብብር ላይ የተመሠረተ ዲፕሎማሲ እንዲከተሉ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።
በመሆኑም የኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ ልማት በቀጣናው ያለውን ሰላም እና ጂኦፖለቲካዊ መረጋጋት በቀጥታ የሚወስን የሰላም ስትራቴጂ ሆኖ ያገለግላል።
በተጨማሪም የሀገራችንን የማክሮ-ኢኮኖሚ መዋቅር ወደ ላቀ እና የማይበገር ደረጃ ለማሸጋገር በሚደረገው ጥረት ውስጥ፣ ይህ አረንጓዴ ኢኮኖሚ የራሱን ጉልህ ዐሻራ እያሳረፈ ይገኛል።
የአካባቢ ጥበቃ ሥራው የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባለፈ፣ በመቶ ሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች በተለይም ደግሞ በማኅበረሰቡ ውስጥ በኢኮኖሚ ተጋላጭ ለሆኑት ወጣቶች እና ሴቶች ሰፊ የሥራ ዕድልን መፍጠር ችሏል።
ይህ ከችግኝ መኮትኮት እስከ ደን ጥበቃ እና ልማት የተዘረጋው የሥራ ዕድል፣ የዜጎችን ዕለታዊ ገቢ ከማሻሻሉም በላይ የሀገራዊ የምጣኔ-ሀብት መቋቋም አቅምን የሚገነባ ጠንካራ ምሰሶ ሆኗል።
በመሆኑም የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር የአካባቢ ጥበቃን፣ የኢኮኖሚ ዕድገትን እና የጂኦፖለቲካ መረጋጋትን በጋራ በማስተሳሰር የነገዋን የበለጸገች እና ሉዓላዊነቷ የተከበረ ኢትዮጵያን ለመገንባት የተነደፈ ሥልታዊ እና አርቆ አሳቢ የፖሊሲ ምላሽ ነው።
በበረከት ሽመልስ
#ethiopia #ebc #greenlegacy #success
2 months ago
ቤጂንግ የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎች ሙሉ በሙሉ እንዲወድሙ ጥሪ አቀረበች
#ethiopia | በከፍተኛ የጂኦፖለቲካዊ መግለጫ፣ ቻይና ለዓለም አቀፍ ሰላም መረጋገጥ እና ለሦስተኛው የዓለም ጦርነት መከላከል ብቸኛው መንገድ አጠቃላይ የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎችን ማስወገድ መሆኑን በይፋ አስታወቀች። የቻይና ባለሥልጣናት እንደ አሜሪካ ያሉ ታላላቅ ኃያላን ሀገራት እና የእስራኤልን ተሳትፎ የሚያካትተው የመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ተዋናዮች የኒውክሌር ዛቻዎችን በአስቸኳይ ማቆም እና ሙሉ በሙሉ ወደ ዲ-ኤስካሌሽን (ውጥረትን ወደ መቀነስ) ማምራት እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።
ይሁን እንጂ ቤጂንግ ይህንን ዓለም አቀፋዊ ለውጥ በይፋ ብታስተዋውቅም፣ ተቺዎች ቻይና እራሷ የራሷን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ ክምችት በከፍተኛ ፍጥነት እያሳደገች መሆኑን በስፋት እየነቀፉ ይገኛሉ። እ.ኤ.አ. በ2026 የዓለም አቀፍ የኒውክሌር ወጪ ከፍተኛ ታሪካዊ ደረጃ ላይ በደረሰበት በዚህ ወቅት፣ የጦር መሣሪያዎችን ማስወገድ ተፈጻሚ ሊሆን የሚችል እውነተኛ ግብ ነው ወይስ ፈጽሞ የማይሳካ ምናባዊ ምኞት? የሚለው ክርክር ዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ በሁለት መከፈሉን ቀጥሏል።
እንደ መናኸሪያ ኤፍ ኤም ዘገባ በኒውክሌር ጦር መሣሪያዎች ሙሉ በሙሉ መጥፋት የዓለም ሰላም ይረጋገጣል ብለው ያምናሉ ወይስ አሁን ያለው የጦር መሣሪያ እሽቅድምድም የማይቀር ነው?
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በከፍተኛ የጂኦፖለቲካዊ መግለጫ፣ ቻይና ለዓለም አቀፍ ሰላም መረጋገጥ እና ለሦስተኛው የዓለም ጦርነት መከላከል ብቸኛው መንገድ አጠቃላይ የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎችን ማስወገድ መሆኑን በይፋ አስታወቀች። የቻይና ባለሥልጣናት እንደ አሜሪካ ያሉ ታላላቅ ኃያላን ሀገራት እና የእስራኤልን ተሳትፎ የሚያካትተው የመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ተዋናዮች የኒውክሌር ዛቻዎችን በአስቸኳይ ማቆም እና ሙሉ በሙሉ ወደ ዲ-ኤስካሌሽን (ውጥረትን ወደ መቀነስ) ማምራት እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።
ይሁን እንጂ ቤጂንግ ይህንን ዓለም አቀፋዊ ለውጥ በይፋ ብታስተዋውቅም፣ ተቺዎች ቻይና እራሷ የራሷን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ ክምችት በከፍተኛ ፍጥነት እያሳደገች መሆኑን በስፋት እየነቀፉ ይገኛሉ። እ.ኤ.አ. በ2026 የዓለም አቀፍ የኒውክሌር ወጪ ከፍተኛ ታሪካዊ ደረጃ ላይ በደረሰበት በዚህ ወቅት፣ የጦር መሣሪያዎችን ማስወገድ ተፈጻሚ ሊሆን የሚችል እውነተኛ ግብ ነው ወይስ ፈጽሞ የማይሳካ ምናባዊ ምኞት? የሚለው ክርክር ዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ በሁለት መከፈሉን ቀጥሏል።
እንደ መናኸሪያ ኤፍ ኤም ዘገባ በኒውክሌር ጦር መሣሪያዎች ሙሉ በሙሉ መጥፋት የዓለም ሰላም ይረጋገጣል ብለው ያምናሉ ወይስ አሁን ያለው የጦር መሣሪያ እሽቅድምድም የማይቀር ነው?
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Sponsored by
Surafel
2 months ago
በመካከለኛው ምስራቅ ቀውስ ሳቢያ የዓለም ኢኮኖሚ ዕድገት ሊቀንስ ይችላል
**********************
በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣው ጂኦፖለቲካዊ ቀውስ የዓለምን ኢኮኖሚ ክፉኛ እየናጠው እንደሚገኝ ተጠቁሟል። የዓለም ባንክ እና ዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) በአወጡት የኢኮኖሚ ትንበያ ሪፖርት፣ በግጭቱ ሳቢያ በተፈጠረው አለመረጋጋት ምክንያት እ.አ.አ. በ2026 የዓለም ኢኮኖሚ ዕድገት ሊቀንስ እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
የዓለም ባንክ ቀደም ሲል አስቀምጦት የነበረውን የ2026 የዓለም ኢኮኖሚ ዕድገት ግምት ወደ 2.5 በመቶ ዝቅ አድርጎታል።
ይሁን እንጂ የግጭቱ መባባስ የኃይል አቅርቦት መስተጓጎልን ካስከተለና የፋይናንስ ገበያው ውጥረት ውስጥ ከገባ፣ ዕድገቱ እስከ 1.3 በመቶ ድረስ ሊወርድ እንደሚችል ባንኩ ጠቁሟል። ይህም ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወዲህ ዓለም ላይ የሚከሰት ዝቅተኛው የዕድገት ምጣኔ ይሆናል ተብሎ ተገምቷል።
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት በበኩሉ፣ የመካከለኛው ምስራቅ ግጭት የዋጋ ንረትን እያባባሰ መሆኑን አመልክቷል።
በችግሩ ምክንያት የሚከሰተው የነዳጅ ዋጋ መጨመር የሸቀጦችን ዋጋ በ22 በመቶ ያሳድገዋል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ ይህ ሁኔታ በተለይ ነዳጅ ወደ ሀገር ውስጥ በሚያስገቡ ሀገራት ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ይገኛል።
በሌላ በኩል በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂ ላይ በአሁኑ ወቅት እየተደረገ ያለው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን መልሶ ሊያነቃቃውና ለምርታማነት መጨመር ትልቅ ድጋፍ ሊሆን እንደሚችል ተስፋ ተጥሎበታል።
የዓለም ባንክና አይኤምኤፍ መጪውን የኢኮኖሚ ፈተና ለመቋቋም ሀገራት በኢነርጂ እና በምግብ ዋስትና ዙሪያ በጋራ እንዲሰሩ አሳስበዋል።
በላሉ ኢታላ
#ethiopianbroadcastingcorporation #world #economy
**********************
በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣው ጂኦፖለቲካዊ ቀውስ የዓለምን ኢኮኖሚ ክፉኛ እየናጠው እንደሚገኝ ተጠቁሟል። የዓለም ባንክ እና ዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) በአወጡት የኢኮኖሚ ትንበያ ሪፖርት፣ በግጭቱ ሳቢያ በተፈጠረው አለመረጋጋት ምክንያት እ.አ.አ. በ2026 የዓለም ኢኮኖሚ ዕድገት ሊቀንስ እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
የዓለም ባንክ ቀደም ሲል አስቀምጦት የነበረውን የ2026 የዓለም ኢኮኖሚ ዕድገት ግምት ወደ 2.5 በመቶ ዝቅ አድርጎታል።
ይሁን እንጂ የግጭቱ መባባስ የኃይል አቅርቦት መስተጓጎልን ካስከተለና የፋይናንስ ገበያው ውጥረት ውስጥ ከገባ፣ ዕድገቱ እስከ 1.3 በመቶ ድረስ ሊወርድ እንደሚችል ባንኩ ጠቁሟል። ይህም ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወዲህ ዓለም ላይ የሚከሰት ዝቅተኛው የዕድገት ምጣኔ ይሆናል ተብሎ ተገምቷል።
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት በበኩሉ፣ የመካከለኛው ምስራቅ ግጭት የዋጋ ንረትን እያባባሰ መሆኑን አመልክቷል።
በችግሩ ምክንያት የሚከሰተው የነዳጅ ዋጋ መጨመር የሸቀጦችን ዋጋ በ22 በመቶ ያሳድገዋል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ ይህ ሁኔታ በተለይ ነዳጅ ወደ ሀገር ውስጥ በሚያስገቡ ሀገራት ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ይገኛል።
በሌላ በኩል በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂ ላይ በአሁኑ ወቅት እየተደረገ ያለው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን መልሶ ሊያነቃቃውና ለምርታማነት መጨመር ትልቅ ድጋፍ ሊሆን እንደሚችል ተስፋ ተጥሎበታል።
የዓለም ባንክና አይኤምኤፍ መጪውን የኢኮኖሚ ፈተና ለመቋቋም ሀገራት በኢነርጂ እና በምግብ ዋስትና ዙሪያ በጋራ እንዲሰሩ አሳስበዋል።
በላሉ ኢታላ
#ethiopianbroadcastingcorporation #world #economy
2 months ago
ከኢኮኖሚ ዋስትና እስከ ቀጣናዊ ተሰሚነት፦ የባሕር በር ፍላጎት እና የኢትዮጵያ ስትራቴጂያዊ ጥቅሞች
************************
አንድ ሀገር የባሕር በር ማግኘቱ ከቀላል የንግድ ልውውጥ ባለፈ፣ የፖለቲካ ነፃነቱ፣ የኢኮኖሚ ዋስትናው እና የብሔራዊ ደኅንነቱ ማረጋገጫ ነው።
ኢትዮጵያ ካላት ግዙፍ የሕዝብ ቁጥር እና ፈጣን ዕድገት እያስመዘገበ ከሚገኘው ኢኮኖሚዋ አንጻር፣ ቀጥተኛ የባሕር በር ማጣቷ በሉዓላዊነቷ እና በረጅም ጊዜ ስትራቴጂያዊ ጥቅሟ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ አለው።
በመሆኑም የባሕር በር ጥያቄ የቅንጦት ጉዳይ ሳይሆን፣ የሀገራችንን ቀጣይነት ለማረጋገጥ እና ብሔራዊ ጥቅማችንን ለማስጠበቅ ያለመ የሕልውና ጉዳይ ነው።
ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የወጪ እና ገቢ ንግዷን በአንድ ወደብ ብቻ ማካሄዷ ለከፍተኛ ጂኦፖለቲካዊ ስጋት እና ለሎጂስቲክስ መስተጓጎል ተጋላጭ አድርጓታል።
የጅቡቲ ወደብን ለመጠቀም በየዓመቱ የምታወጣው ከ1.5 እስከ 2 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ የውጭ ምንዛሬ በሀገራችን የማክሮ-ኢኮኖሚ መረጋጋት፣ በምርቶች የትርፍ ህዳግ እና በዜጎች የኑሮ ውድነት ላይ ቀጥተኛ ጫና እያሳደረ ይገኛል።
ስለሆነም የራስን የባሕር በር ወይም አስተማማኝ እና ዘላቂ የወደብ አማራጮችን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ማግኘት የሀገር ውስጥ ገበያን ከማረጋጋቱም በላይ፣ ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚኖረንን የኢኮኖሚ ትስስር እና የኃይል ሚዛን በብልሃት ለመምራት ያስችላል።
ሀገራችን እየተገበረችው ላለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና ከግብርና መር ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለጀመረችው ሽግግር ስኬት በተለይም እንደ "ኢትዮጵያ ታምርት" ላሉ ብሔራዊ ንቅናቄዎች ውጤታማነት ቀልጣፋና ተደራሽ የሎጂስቲክስ መስመር መኖሩ ወሳኝ ነው።
የባሕር በር ባለቤትነት የሀገር ውስጥ አምራቾች የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶቻቸውን በፈጣን ሂደት እና በተመጣጣኝ ወጪ በቀጥታ ወደ ዓለም ገበያ እንዲልኩ ሰፊ ዕድል ይፈጥራል።
ይህ ተወዳዳሪነት ደግሞ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን በስፋት ለመሳብ፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን የማምረት አቅም ለማሳደግ እና የሀገራችንን የውጭ ምንዛሬ ገቢ በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ አስተማማኝ ዋስትና ይሆናል።
የባሕር በር መኖር ከኢኮኖሚ ጠቀሜታው ባሻገር ብሔራዊ ደኅንነትን ለማስጠበቅ እና በቀጣናው አስተማማኝ ሰላም ለመገንባት ቁልፍ መሣሪያ ነው።
ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር እና በኤደን ባሕረ ሰላጤ አቅራቢያ የሚስተዋሉ የፀጥታ ስጋቶችን፣ የባሕር ላይ ወንበዴነትን እና የዓለም አቀፍ ኃይሎችን የጂኦፖለቲካ ሽኩቻ ለመመከት ዘመናዊ የባሕር ኃይል በከፍተኛ የሰው ኃይል እና ቴክኖሎጂ መልሳ ገንብታለች።
አስተማማኝ የባሕር በር ማግኘት የባሕር ኃይሉን ስምሪት ውጤታማ በማድረግ፣ ሀገራችን በምሥራቅ አፍሪካ እና በቀይ ባሕር የደኅንነት መዋቅር ያላትን ተሰሚነት፣ የድርድር አቅም እና የሰላም አስከባሪነት ሚና በእጅጉ ከፍ ያደርገዋል።
የባሕር በር ጉዳይ የአጭር ጊዜ የፖለቲካ አጀንዳ ሳይሆን፣ ከትውልድ ትውልድ የሚሻገር የኢትዮጵያ የብሔራዊ ጥቅም ማዕቀፍ ነው።
ሀገራችን በዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች፣ በጋራ ልማት መርሆዎች፣ በሰላማዊ ድርድር እና በሕጋዊ መንገዶች የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት የኢኮኖሚ ጥገኝነትን ለመቀነስ፣ የንግድ መስመሮችን ለማስፋፋት እና የተሟላ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚደረግ ታሪካዊ እና ስትራቴጂያዊ ሂደት ነው።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #seaaccess #redsea #geopolitics #hornofafrica #nationalsecurity #ebc
************************
አንድ ሀገር የባሕር በር ማግኘቱ ከቀላል የንግድ ልውውጥ ባለፈ፣ የፖለቲካ ነፃነቱ፣ የኢኮኖሚ ዋስትናው እና የብሔራዊ ደኅንነቱ ማረጋገጫ ነው።
ኢትዮጵያ ካላት ግዙፍ የሕዝብ ቁጥር እና ፈጣን ዕድገት እያስመዘገበ ከሚገኘው ኢኮኖሚዋ አንጻር፣ ቀጥተኛ የባሕር በር ማጣቷ በሉዓላዊነቷ እና በረጅም ጊዜ ስትራቴጂያዊ ጥቅሟ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ አለው።
በመሆኑም የባሕር በር ጥያቄ የቅንጦት ጉዳይ ሳይሆን፣ የሀገራችንን ቀጣይነት ለማረጋገጥ እና ብሔራዊ ጥቅማችንን ለማስጠበቅ ያለመ የሕልውና ጉዳይ ነው።
ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የወጪ እና ገቢ ንግዷን በአንድ ወደብ ብቻ ማካሄዷ ለከፍተኛ ጂኦፖለቲካዊ ስጋት እና ለሎጂስቲክስ መስተጓጎል ተጋላጭ አድርጓታል።
የጅቡቲ ወደብን ለመጠቀም በየዓመቱ የምታወጣው ከ1.5 እስከ 2 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ የውጭ ምንዛሬ በሀገራችን የማክሮ-ኢኮኖሚ መረጋጋት፣ በምርቶች የትርፍ ህዳግ እና በዜጎች የኑሮ ውድነት ላይ ቀጥተኛ ጫና እያሳደረ ይገኛል።
ስለሆነም የራስን የባሕር በር ወይም አስተማማኝ እና ዘላቂ የወደብ አማራጮችን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ማግኘት የሀገር ውስጥ ገበያን ከማረጋጋቱም በላይ፣ ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚኖረንን የኢኮኖሚ ትስስር እና የኃይል ሚዛን በብልሃት ለመምራት ያስችላል።
ሀገራችን እየተገበረችው ላለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና ከግብርና መር ወደ ኢንዱስትሪ መር ኢኮኖሚ ለጀመረችው ሽግግር ስኬት በተለይም እንደ "ኢትዮጵያ ታምርት" ላሉ ብሔራዊ ንቅናቄዎች ውጤታማነት ቀልጣፋና ተደራሽ የሎጂስቲክስ መስመር መኖሩ ወሳኝ ነው።
የባሕር በር ባለቤትነት የሀገር ውስጥ አምራቾች የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶቻቸውን በፈጣን ሂደት እና በተመጣጣኝ ወጪ በቀጥታ ወደ ዓለም ገበያ እንዲልኩ ሰፊ ዕድል ይፈጥራል።
ይህ ተወዳዳሪነት ደግሞ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን በስፋት ለመሳብ፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን የማምረት አቅም ለማሳደግ እና የሀገራችንን የውጭ ምንዛሬ ገቢ በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ አስተማማኝ ዋስትና ይሆናል።
የባሕር በር መኖር ከኢኮኖሚ ጠቀሜታው ባሻገር ብሔራዊ ደኅንነትን ለማስጠበቅ እና በቀጣናው አስተማማኝ ሰላም ለመገንባት ቁልፍ መሣሪያ ነው።
ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር እና በኤደን ባሕረ ሰላጤ አቅራቢያ የሚስተዋሉ የፀጥታ ስጋቶችን፣ የባሕር ላይ ወንበዴነትን እና የዓለም አቀፍ ኃይሎችን የጂኦፖለቲካ ሽኩቻ ለመመከት ዘመናዊ የባሕር ኃይል በከፍተኛ የሰው ኃይል እና ቴክኖሎጂ መልሳ ገንብታለች።
አስተማማኝ የባሕር በር ማግኘት የባሕር ኃይሉን ስምሪት ውጤታማ በማድረግ፣ ሀገራችን በምሥራቅ አፍሪካ እና በቀይ ባሕር የደኅንነት መዋቅር ያላትን ተሰሚነት፣ የድርድር አቅም እና የሰላም አስከባሪነት ሚና በእጅጉ ከፍ ያደርገዋል።
የባሕር በር ጉዳይ የአጭር ጊዜ የፖለቲካ አጀንዳ ሳይሆን፣ ከትውልድ ትውልድ የሚሻገር የኢትዮጵያ የብሔራዊ ጥቅም ማዕቀፍ ነው።
ሀገራችን በዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች፣ በጋራ ልማት መርሆዎች፣ በሰላማዊ ድርድር እና በሕጋዊ መንገዶች የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት የኢኮኖሚ ጥገኝነትን ለመቀነስ፣ የንግድ መስመሮችን ለማስፋፋት እና የተሟላ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚደረግ ታሪካዊ እና ስትራቴጂያዊ ሂደት ነው።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #seaaccess #redsea #geopolitics #hornofafrica #nationalsecurity #ebc
2 months ago
የቢሊየነሩ የፅሁፍ ስህተት ውዝግብ አስነሳ፤ የኢራን ቆንስላ ለኢሎን ማስክ “ተጨማሪ ትምህርት ያስፈልግሃል!” ሲል መለሰለት
የኤክስ (X) ባለቤትና ታዋቂው ቢሊየነር ኢሎን ማስክ በስትራቴጂካዊው የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ ስያሜ ዙሪያ በገጹ ላይ ያሰፈረው ታሪካዊ ትንታኔ እና የቋንቋ አጠቃቀም ስህተት ዓለም አቀፍ መነጋገሪያ ሆኗል።
ኢሎን ማስክ ትናንት በይፋዊ የማህበራዊ ሚዲያ ገጹ ላይ ባስተላለፈው አጭር መልዕክት፥ “የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤዎች (Straits of Hormuz) ስያሜያቸውን ያገኙት በዞራስትሪያኒዝም እምነት ውስጥ ‘አሁራ ማዝዳ’ ከተባለው ዋነኛ አምላክ ነው” የሚል የራሱን ታሪካዊ ምልከታ አጋርቶ ነበር። ይህ የቢሊየነሩ ፅሁፍ በአጭር ሰዓታት ውስጥ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ትኩረት የሳበ ቢሆንም፣ ከኢራን መንግስት ወገን ግን ጠንከር ያለ ምላሽ አስተናግዷል።
በህንድ ሙምባይ የሚገኘው የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ ጠቅላይ ቆንስላ ጽሕፈት ቤት የኢሎን ማስክን ስህተት በይፋዊ ገጹ ላይ በግልጽ በማረም ምላሽ የሰጠ ሲሆን፥ “ኢሎን፤ ጥሩ ጅምር ነው፤ ነገር ግን ተጨማሪ ትምህርት ያስፈልግሃል” ሲል በይፋ አፌዝበታል።
ቆንስላው በማስተካከያው ላይ እንደገለጸው፥ በመጀመሪያ ደረጃ ማስክ የተጠቀመው “Straits” (ባህረ ሰላጤዎች) የሚለው የብዙ ቁጥር አገላለጽ ስህተት መሆኑንና ትክክለኛው ዓለም አቀፍ ስያሜ በአንድ ቁጥር “Strait of Hormuz” (የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ) መባል እንዳለበት ጠቁሟል። በተጨማሪም ቢሊየነሩ ስለ ፋርስ (ፐርሺያ) ስልጣኔ፣ ታሪክ እና ስለ ስፍራው ጥንታዊ አመጣጥ ይበልጥ በጥንቃቄ እንዲያጠና መክሯል።
ይህ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የተቀሰቀሰው የቃላት ምልልስ በአሁኑ ወቅት በሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ አካባቢ ካለው ከፍተኛ ወታደራዊ ውጥረት እና ከቀጣናው ጂኦፖለቲካዊ ሁኔታ ጋር ተዳምሮ በዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን ዘንድ ትልቅ የዜና አጀንዳ ሆኖ ቀርቧል።
Seledadotio
Seledadotio
የኤክስ (X) ባለቤትና ታዋቂው ቢሊየነር ኢሎን ማስክ በስትራቴጂካዊው የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ ስያሜ ዙሪያ በገጹ ላይ ያሰፈረው ታሪካዊ ትንታኔ እና የቋንቋ አጠቃቀም ስህተት ዓለም አቀፍ መነጋገሪያ ሆኗል።
ኢሎን ማስክ ትናንት በይፋዊ የማህበራዊ ሚዲያ ገጹ ላይ ባስተላለፈው አጭር መልዕክት፥ “የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤዎች (Straits of Hormuz) ስያሜያቸውን ያገኙት በዞራስትሪያኒዝም እምነት ውስጥ ‘አሁራ ማዝዳ’ ከተባለው ዋነኛ አምላክ ነው” የሚል የራሱን ታሪካዊ ምልከታ አጋርቶ ነበር። ይህ የቢሊየነሩ ፅሁፍ በአጭር ሰዓታት ውስጥ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ትኩረት የሳበ ቢሆንም፣ ከኢራን መንግስት ወገን ግን ጠንከር ያለ ምላሽ አስተናግዷል።
በህንድ ሙምባይ የሚገኘው የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ ጠቅላይ ቆንስላ ጽሕፈት ቤት የኢሎን ማስክን ስህተት በይፋዊ ገጹ ላይ በግልጽ በማረም ምላሽ የሰጠ ሲሆን፥ “ኢሎን፤ ጥሩ ጅምር ነው፤ ነገር ግን ተጨማሪ ትምህርት ያስፈልግሃል” ሲል በይፋ አፌዝበታል።
ቆንስላው በማስተካከያው ላይ እንደገለጸው፥ በመጀመሪያ ደረጃ ማስክ የተጠቀመው “Straits” (ባህረ ሰላጤዎች) የሚለው የብዙ ቁጥር አገላለጽ ስህተት መሆኑንና ትክክለኛው ዓለም አቀፍ ስያሜ በአንድ ቁጥር “Strait of Hormuz” (የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ) መባል እንዳለበት ጠቁሟል። በተጨማሪም ቢሊየነሩ ስለ ፋርስ (ፐርሺያ) ስልጣኔ፣ ታሪክ እና ስለ ስፍራው ጥንታዊ አመጣጥ ይበልጥ በጥንቃቄ እንዲያጠና መክሯል።
ይህ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የተቀሰቀሰው የቃላት ምልልስ በአሁኑ ወቅት በሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ አካባቢ ካለው ከፍተኛ ወታደራዊ ውጥረት እና ከቀጣናው ጂኦፖለቲካዊ ሁኔታ ጋር ተዳምሮ በዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን ዘንድ ትልቅ የዜና አጀንዳ ሆኖ ቀርቧል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
Comments