Logo
EBC
የመደመር አንቀጽ

የትውልድን ትኩረት የሚሻ አካባቢ

ትውልዱ የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገራትን መመልከቻ መነጽሩ በሦስት ተያያዥነት ባላቸው ነጥቦች ላይ የሚቃኝ ነው።

የመጀመሪያው ለሀገራችን ባለው ቅርበት ነው። በዚህ መልከአ ምድራዊ ቅርበትና ግንኙነት የተነሣ የሃይማኖት፣ የባህል እና የሥልጣኔ መወራረስ ተፈጥሯል።

በአንዱ አካባቢ የተፈጠረ ነገር በሌላው አካባቢ አዎንታዊም ይሁን አሉታዊ ተፅዕኖ ኖሮታል።

ሁለተኛው ያለው መቀራረብ በአዳዲስ ለውጦችንና ከሥተቶች ታጅቦ፤ ይበልጥ እርስ በእርስ እየተሳሰረ የመጣ ጂኦፖለቲካ መፈጠሩ ነው።

በዚህም ውስጥ በጋራ ልንሠራባቸው ወይም የልዩነት ነጥብ ሊሆኑ የሚችሉ፤ እኛም እነርሱ ላይ፡ እነርሱም እኛ ላይ የተለያዩ ፍላጎቶች ያለን መሆኑ ነው።

ሦስተኛው ደግሞ እየተለወጠ ባለው ዓለም ውስጥ፤ ካካበቱት ዐቅም የተነሣ ይበልጥ የተጠናከረ ዓለም አቀፍ ኃይል ሆነው የመውጣት ዕድል ያላቸው መሆኑ ነው።

በአፍሪካ ቀንድና በመካከለኛው ምሥራቅ በተሳሰረ ጂኦፖለቲካ ውስጥ፤ ጠንካራ አካባቢያዊ ኃይል መኖሩን የሚገነዘብ ነው።

የመደመር ትውልድ
ገጽ - 259

1 month ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.