4 hours ago
የኦሮሞ ሕዝብ ትግል በአንድ ቦታ የቆመ አይደለም ➡️ https://youtu.be/DVFhZjlaY... #abiyahmed #ethiopia #oromia #obn #ethiopianhistory #gadaasystem #pmabiy
5 hours ago
የኦሮሞ ጀግኖች መሥዕዋትነት ለኢትዮጵያ አንድነት ➡️ https://youtu.be/DVFhZjlaY... #abiyahmed #ethiopia #oromia #obn #ethiopianhistory #gadaasystem #pmabiy
5 months ago
OBN ለኢትዮጲያ ፕሪሚርሊግ 200 ሚሊዮን ብር ይከፍላል:
ክለቦች ስንት ያገኛሉ?
#ethiopia | ከአምስት አመታት ቆይታ በኋላ ከዲኤስቲቪ ሱፐር ስፖርት ጋር የተለያየዉ የኢትዮጲያ ፕሪሚርሊግ አክሲዮን ማህበር ዘንድሮ ፊቱን ወደ ሀገር ዉስጥ የቴሌቪዥን ጣቢያ በማዞር የሊጉን የምስል መብት ለOBN ለሁለት አመት ሸጧል።
OBNየሊጉን የምስል መብት ለሁለት አመት በሁለት መቶ ሚሊዮን ብር እንደገዛዉ ብስራት ራዲዮ ለጉዳዩ ቅርበት ካላቸዉ ሰዎች ሰምቷል።
ይህንንም ተከትሎ ዘንድሮ OBN 100 ሚሊዮን ብር የሚከፍል ሲሆን ክለቦች ከምስል ሽያጩ የሚያገኙት ገንዘብ ከዚህ ቀደም ከነበረዉ በእጂጉ ያነሰ እንደሚሆን ተገምቷል።
ከ100 ሚሊየኑ ዉስጥ ክለቦች ሊያገኙት የሚችሉት ገንዘብ ከግማሽ በታች ሊሆን እንደሚችል ሲተነበይ ምክንያቱ ደግሞ ከሚገኘዉ ገንዘብ ላይ የሊጉ አክሲዮን ማህበር ለዳኞች እና ለልዩ ልዩ ወጪዎች ቀንሶ ተራፊዉን ስለሚያከፋፍል እንደሆነ ታዉቋል።
በአምናዉ የዉድድር ዘመን በሀገሪቱ ከታየዉ ዶላር ጭማሪ ጋር ተያይዞ አክሲዮን ማህበሩ በሊጉ ታሪክ ከፍተኛ የተባለዉን ገንዘብ ለክለቦች ሲያከፋፍል የአምናዉ ሻምፒዮን ኢትዮጲያ መድን 40 ሚሊዮን ብር እንዳገኘ የሚዘነጋ አይደለም።
ዘንድሮ ግን ሻምፒዮን የሚሆነዉ ክለብ ምን አልባትም ከአምስት ሚሊዮን ብር በታች ሊያገኝ እንደሚችል ይገመታል ።
የኢትዮጲያ ፕሪሚርሊግ አክሲዮን ማህበር አምና ከ409 ሚሊዮን ብር በላይ ለ15 ክለቦች ሲያከፋፍል ዘንድሮ ግን ምን አልባትም ለ20 ክለቦች ከ50ሚሊዮን ብር ያነሰ ገንዘብ ያከፋፍላል ተብሎ ይጠበቃል ሲል ብስራት ሬዲዮ ዘግቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
ክለቦች ስንት ያገኛሉ?
#ethiopia | ከአምስት አመታት ቆይታ በኋላ ከዲኤስቲቪ ሱፐር ስፖርት ጋር የተለያየዉ የኢትዮጲያ ፕሪሚርሊግ አክሲዮን ማህበር ዘንድሮ ፊቱን ወደ ሀገር ዉስጥ የቴሌቪዥን ጣቢያ በማዞር የሊጉን የምስል መብት ለOBN ለሁለት አመት ሸጧል።
OBNየሊጉን የምስል መብት ለሁለት አመት በሁለት መቶ ሚሊዮን ብር እንደገዛዉ ብስራት ራዲዮ ለጉዳዩ ቅርበት ካላቸዉ ሰዎች ሰምቷል።
ይህንንም ተከትሎ ዘንድሮ OBN 100 ሚሊዮን ብር የሚከፍል ሲሆን ክለቦች ከምስል ሽያጩ የሚያገኙት ገንዘብ ከዚህ ቀደም ከነበረዉ በእጂጉ ያነሰ እንደሚሆን ተገምቷል።
ከ100 ሚሊየኑ ዉስጥ ክለቦች ሊያገኙት የሚችሉት ገንዘብ ከግማሽ በታች ሊሆን እንደሚችል ሲተነበይ ምክንያቱ ደግሞ ከሚገኘዉ ገንዘብ ላይ የሊጉ አክሲዮን ማህበር ለዳኞች እና ለልዩ ልዩ ወጪዎች ቀንሶ ተራፊዉን ስለሚያከፋፍል እንደሆነ ታዉቋል።
በአምናዉ የዉድድር ዘመን በሀገሪቱ ከታየዉ ዶላር ጭማሪ ጋር ተያይዞ አክሲዮን ማህበሩ በሊጉ ታሪክ ከፍተኛ የተባለዉን ገንዘብ ለክለቦች ሲያከፋፍል የአምናዉ ሻምፒዮን ኢትዮጲያ መድን 40 ሚሊዮን ብር እንዳገኘ የሚዘነጋ አይደለም።
ዘንድሮ ግን ሻምፒዮን የሚሆነዉ ክለብ ምን አልባትም ከአምስት ሚሊዮን ብር በታች ሊያገኝ እንደሚችል ይገመታል ።
የኢትዮጲያ ፕሪሚርሊግ አክሲዮን ማህበር አምና ከ409 ሚሊዮን ብር በላይ ለ15 ክለቦች ሲያከፋፍል ዘንድሮ ግን ምን አልባትም ለ20 ክለቦች ከ50ሚሊዮን ብር ያነሰ ገንዘብ ያከፋፍላል ተብሎ ይጠበቃል ሲል ብስራት ሬዲዮ ዘግቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
8 months ago
መኮ ቢሊ ሾው የተሰኘ አዝናኝና አስተማሪ የቤተሰብ መዝናኛ ፕሮግራምን በ ኦ ቢ ኤን (OBN)ቴሌቪዥን እና Mako Bili Show ዩቲዩብን ሰብስክራይብ በማድረግ እሁድ ማታ ከ 3:00-4:00 ይከታተሉ ። ምርትና አገልግሎትንም ያስተዋውቁ ።
Sagantaa Mako Bili Show kan itti bohaartaniif irraa Odeeffattan karaa Dilbata Galgala yeroo mara Sa'aatii 3:00- 4:00tti karaa OBN fi Youtube Subscribe gochuun daawwadhaa.
https://youtube.com/makob...
Sagantaa Mako Bili Show kan itti bohaartaniif irraa Odeeffattan karaa Dilbata Galgala yeroo mara Sa'aatii 3:00- 4:00tti karaa OBN fi Youtube Subscribe gochuun daawwadhaa.
https://youtube.com/makob...
8 months ago
ሦስት ኢትዮጵያውያን ተሸላሚ ሆነዋል
#ethiopia | አዲስአበባ በተካሄደው የ 2025 IGAD Secretariat ሚዲያ አዋርድ ሦስት ኢትዮጵያውያን ተሸላሚ ሆነዋል ።
የምንወዳት የምናከብራት የሸገር FM አንጋፋ ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ የሕይወት ዘመን ተሸላሚ ሆናለች ።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎቱ ጌትነት ሸንቁጥ በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ : የኦቢኤኑ ሽመክት ለገሰ ደግሞ በአገርበቀል ቋንቋ ዘርፍ ተሸላሚ ሆነዋል ።
እንኳን ደስ አላችሁ !
#igadmediaaward2025
Three Ethiopians were award winners at the 2025 IGAD Secretariat Media Awards ceremony held here in Addis Ababa.
Our beloved and respected veteran Sheger FM journalist, Meaza Biru, received the Lifetime Achievement Award.
Getnet Shenkute of the Ethiopian News Agency (ENA) won in the Digital Media category, and Shimekit Legese of OBN (Oromia Broadcast Network) won in the Indigenous Language category.
📷 Abdi Ali Ibrahim
#ethiopia | አዲስአበባ በተካሄደው የ 2025 IGAD Secretariat ሚዲያ አዋርድ ሦስት ኢትዮጵያውያን ተሸላሚ ሆነዋል ።
የምንወዳት የምናከብራት የሸገር FM አንጋፋ ጋዜጠኛ መዓዛ ብሩ የሕይወት ዘመን ተሸላሚ ሆናለች ።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎቱ ጌትነት ሸንቁጥ በዲጂታል ሚዲያ ዘርፍ : የኦቢኤኑ ሽመክት ለገሰ ደግሞ በአገርበቀል ቋንቋ ዘርፍ ተሸላሚ ሆነዋል ።
እንኳን ደስ አላችሁ !
#igadmediaaward2025
Three Ethiopians were award winners at the 2025 IGAD Secretariat Media Awards ceremony held here in Addis Ababa.
Our beloved and respected veteran Sheger FM journalist, Meaza Biru, received the Lifetime Achievement Award.
Getnet Shenkute of the Ethiopian News Agency (ENA) won in the Digital Media category, and Shimekit Legese of OBN (Oromia Broadcast Network) won in the Indigenous Language category.
📷 Abdi Ali Ibrahim
9 months ago
በኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማት የተፈናቀለው ድህነት እንጂ ደሀ አይደለም።
#fastmereja I በጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ የተጀመረው የሸገር ገበታ ኢኒሼቲቭ የአዲስ አበባ ኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ማሳካቱን የአዲስ አበባ ከተማ የከተማ ውበት እና የአረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ ገለፁ።
የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ከተማውን አረንጓዴ ለማድረግ የታቀደውን 30%, ወደ 22% ማሳካቱን ጠቁመዋል።
የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ንፁህ አየር መተንፈስ ፣ ውብ አካባቢ መኖር ፣ የሥራ እድል የፈጠረ ፣ የቦታ ዲሞክራሲ የሰጠ መሆኑን የገለፁት አቶ ግርማ በኮሪደር ልማት ምክንያት ተፈናቀለ የሚባለው ድህነት እንጂ ደሀ አይደለም ብለዋል።
በየኮሪደሩ ዙሪያ የተሰሩት የልጆች መጫወቻ ምን ያህል ለትውልድ እንደታሠበ አመላካችና የትውልድን ራዕይ ያሳካ ነው ብለዋል።
የተሠራው የኮሪደር ልማት የከተማውን 15% የሚሸፍን ቢሆንም በጋራ በራስ አቅም የማልማት ሂደቱ ይቀጥላል ብለዋል።
የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ወጤታማነት የገባቸው የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባላት ለወከሉት ህዝብ መቼ ወደ እኛ ጋር ይደርሳል የሚል ጥያቄ መመለስ ስለሚገባ የተጀመረውን የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ቅድሚያ መጨረስ ይገባል ብለዋል።
Via: OBN
#fastmereja I በጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ የተጀመረው የሸገር ገበታ ኢኒሼቲቭ የአዲስ አበባ ኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ማሳካቱን የአዲስ አበባ ከተማ የከተማ ውበት እና የአረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ ገለፁ።
የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ከተማውን አረንጓዴ ለማድረግ የታቀደውን 30%, ወደ 22% ማሳካቱን ጠቁመዋል።
የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ንፁህ አየር መተንፈስ ፣ ውብ አካባቢ መኖር ፣ የሥራ እድል የፈጠረ ፣ የቦታ ዲሞክራሲ የሰጠ መሆኑን የገለፁት አቶ ግርማ በኮሪደር ልማት ምክንያት ተፈናቀለ የሚባለው ድህነት እንጂ ደሀ አይደለም ብለዋል።
በየኮሪደሩ ዙሪያ የተሰሩት የልጆች መጫወቻ ምን ያህል ለትውልድ እንደታሠበ አመላካችና የትውልድን ራዕይ ያሳካ ነው ብለዋል።
የተሠራው የኮሪደር ልማት የከተማውን 15% የሚሸፍን ቢሆንም በጋራ በራስ አቅም የማልማት ሂደቱ ይቀጥላል ብለዋል።
የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ወጤታማነት የገባቸው የአዲስ አበባ ምክር ቤት አባላት ለወከሉት ህዝብ መቼ ወደ እኛ ጋር ይደርሳል የሚል ጥያቄ መመለስ ስለሚገባ የተጀመረውን የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ቅድሚያ መጨረስ ይገባል ብለዋል።
Via: OBN
9 months ago
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ኢትዮ ሳት ያጋጠመውን የሥርጭት መቋረጥ ችግር ለመቅረፍ "ከባለድርሻ አካላት ጋር እየተሰራው ነው" ሲል አስታውቋል
👉ከድምፂ ወያነ፣ትግራይ ቲቪ እና
OBN በስተቀር በሳተላይት ላይ የሀገር ውስጥ ቴሌዥን ጣቢያዎች ስርጭት ተቋርጣል።
👉ከድምፂ ወያነ፣ትግራይ ቲቪ እና
OBN በስተቀር በሳተላይት ላይ የሀገር ውስጥ ቴሌዥን ጣቢያዎች ስርጭት ተቋርጣል።
Sponsored by
Surafel
10 months ago
የኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግን ማስተላለፍ የጀመረው OBN ሶስት ስህተት ሰርቷል።
📍ቅዱስ ጊዮርጊስ በሌለበት ጨዋታ ስሙን ለመጥራት ሞክሯል።
📍ቅዱስ ጊዮርጊስ ሲጽፉ በትክክል አልጻፉም።
📍 ባለ ሜዳውም ተጋጣሚውም Saint Georgis ተብሏል።
በቀጣዮቹ ጨዋታ ቦታው ላይ ባለሞያ ያስቀምጣሉ ብለን ተስፋ እናደርጋለን።
ኦቢኤን ሰገሌ ዑመታ 🔊
ሜዳውን ግን ሲታደስ ነው ሲታረስ የቆየው?
📍ቅዱስ ጊዮርጊስ በሌለበት ጨዋታ ስሙን ለመጥራት ሞክሯል።
📍ቅዱስ ጊዮርጊስ ሲጽፉ በትክክል አልጻፉም።
📍 ባለ ሜዳውም ተጋጣሚውም Saint Georgis ተብሏል።
በቀጣዮቹ ጨዋታ ቦታው ላይ ባለሞያ ያስቀምጣሉ ብለን ተስፋ እናደርጋለን።
ኦቢኤን ሰገሌ ዑመታ 🔊
ሜዳውን ግን ሲታደስ ነው ሲታረስ የቆየው?
12 months ago
ማን ሊያሸንፍ ይችላል?
#ethiopia | የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በ2018 በ20 ክለቦች መካከል እንደሚካሄድ ይታወቃል። አነጋጋሪው ነገር መቼ ይጀመራል? የሚለው ነገር ነው።
ባለኝ መረጃ መሰረት ሊግ ካምፓኒው ውድድሩን በመስከረም መጨረሻ ወይም በጥቅምት መጀመሪያ ለማስጀመር አስቧል።
የስርጭቱስ ጉዳይ?
DSTV ከሊግ ካምፓኒው ጋር የነበረውን የ5 ዓመት ኮንትራት ጨርሶ ወጥቷል። ስለዚህ በቀጣዩ ዓመት ሊጉ የቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት ይኖረዋል ወይስ አይኖረውም? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ነው።
ባለኝ ተጨባጭ መረጃ መሰረት የቀጥታ ስርጭት ይኖረዋል። ይህንንም በተመለከተ ሊግ ካምፓኒው የዛሬ ወር ገደማ ባወጣው ጨረታ መሰረት አምስት የቴሌቪዥን ጣቢያዎች የጨረታ ሰነዱን ወስደዋል።
እነሱም፦ EBC፣ ፋና፣ OBN፣ አርትስ እና EBS ናቸው።
ሊግ ካምፓኒው የጨረታ ሰነዳቸውን እየመረመረ ሲሆን የ2018 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን የሚያስተላልፈው ቴሌቪዥን ጣቢያ በዚህ ሳምንት መጨረሻ ይታወቃል ተብሎ ይጠበቃል።
እርሶስ ይሄንን የቀጥታ ስርጭት መብት ማን ሊያሸንፍ ይችላል ብለው ያስባሉ?
ጋዜጠኛ ምስጋና ታደሰ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በ2018 በ20 ክለቦች መካከል እንደሚካሄድ ይታወቃል። አነጋጋሪው ነገር መቼ ይጀመራል? የሚለው ነገር ነው።
ባለኝ መረጃ መሰረት ሊግ ካምፓኒው ውድድሩን በመስከረም መጨረሻ ወይም በጥቅምት መጀመሪያ ለማስጀመር አስቧል።
የስርጭቱስ ጉዳይ?
DSTV ከሊግ ካምፓኒው ጋር የነበረውን የ5 ዓመት ኮንትራት ጨርሶ ወጥቷል። ስለዚህ በቀጣዩ ዓመት ሊጉ የቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት ይኖረዋል ወይስ አይኖረውም? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ነው።
ባለኝ ተጨባጭ መረጃ መሰረት የቀጥታ ስርጭት ይኖረዋል። ይህንንም በተመለከተ ሊግ ካምፓኒው የዛሬ ወር ገደማ ባወጣው ጨረታ መሰረት አምስት የቴሌቪዥን ጣቢያዎች የጨረታ ሰነዱን ወስደዋል።
እነሱም፦ EBC፣ ፋና፣ OBN፣ አርትስ እና EBS ናቸው።
ሊግ ካምፓኒው የጨረታ ሰነዳቸውን እየመረመረ ሲሆን የ2018 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን የሚያስተላልፈው ቴሌቪዥን ጣቢያ በዚህ ሳምንት መጨረሻ ይታወቃል ተብሎ ይጠበቃል።
እርሶስ ይሄንን የቀጥታ ስርጭት መብት ማን ሊያሸንፍ ይችላል ብለው ያስባሉ?
ጋዜጠኛ ምስጋና ታደሰ
12 months ago
ማን ሊያሸንፍ ይችላል?
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በ2018 በ20 ክለቦች መካከል እንደሚካሄድ ይታወል። አነጋጋሪው ነገር መቼ ይጀመራል? የሚለው ነገር ነው።
ባለኝ መረጃ መሰረት ሊግ ካምፓኒው ውድድሩን በመስከረም መጨረሻ ወይም በጥቅምት መጀመሪያ ለማስጀመር አስቧል።
የስርጭቱስ ጉዳይ?
DSTV ከሊግ ካምፓኒው ጋር የነበረውን የ5 ዓመት ኮንትራት ጨርሶ ወጥቷል። ስለዚህ በቀጣዩ ዓመት ሊጉ የቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት ይኖረዋል ወይስ አይኖረውም? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ነው።
ባለኝ ተጨባጭ መረጃ መሰረት የቀጥታ ስርጭት ይኖረዋል። ይህንንም በተመለከተ ሊግ ካምፓኒው የዛሬ ወር ገደማ ባወጣው ጨረታ መሰረት አምስት የቴሌቪዥን ጣቢያዎች የጨረታ ሰነዱን ወስደዋል።
እነሱም፦ EBC፣ ፋና፣ OBN፣ አርትስ እና EBS ናቸው።
ሊግ ካምፓኒው የጨረታ ሰነዳቸውን እየመረመረ ሲሆን የ2018 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን የሚያስተላልፈው ቴሌቪዥን ጣቢያ በዚህ ሳምንት መጨረሻ ይታወቃል ተብሎ ይጠበቃል።
እርሶስ ይሄንን የቀጥታ ስርጭት መብት ማን ሊያሸንፍ ይችላል ብለው ያስባሉ?
በጋዜጠኛ ምስጋናው ታደሰ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በ2018 በ20 ክለቦች መካከል እንደሚካሄድ ይታወል። አነጋጋሪው ነገር መቼ ይጀመራል? የሚለው ነገር ነው።
ባለኝ መረጃ መሰረት ሊግ ካምፓኒው ውድድሩን በመስከረም መጨረሻ ወይም በጥቅምት መጀመሪያ ለማስጀመር አስቧል።
የስርጭቱስ ጉዳይ?
DSTV ከሊግ ካምፓኒው ጋር የነበረውን የ5 ዓመት ኮንትራት ጨርሶ ወጥቷል። ስለዚህ በቀጣዩ ዓመት ሊጉ የቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት ይኖረዋል ወይስ አይኖረውም? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ነው።
ባለኝ ተጨባጭ መረጃ መሰረት የቀጥታ ስርጭት ይኖረዋል። ይህንንም በተመለከተ ሊግ ካምፓኒው የዛሬ ወር ገደማ ባወጣው ጨረታ መሰረት አምስት የቴሌቪዥን ጣቢያዎች የጨረታ ሰነዱን ወስደዋል።
እነሱም፦ EBC፣ ፋና፣ OBN፣ አርትስ እና EBS ናቸው።
ሊግ ካምፓኒው የጨረታ ሰነዳቸውን እየመረመረ ሲሆን የ2018 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን የሚያስተላልፈው ቴሌቪዥን ጣቢያ በዚህ ሳምንት መጨረሻ ይታወቃል ተብሎ ይጠበቃል።
እርሶስ ይሄንን የቀጥታ ስርጭት መብት ማን ሊያሸንፍ ይችላል ብለው ያስባሉ?
በጋዜጠኛ ምስጋናው ታደሰ
1 year ago
ጀፎረ
#ethiopia | ጉራጌዎችን ታታሪ ጥበበኛ ከሚያሰኟቸው ነገሮች ውስጥ የመንደር አቀያየሳቸውና የሳር ቤት አሠራራቸው ተጠቃሽ ናቸው፡፡
በተለይ ደግሞ ማራኪ የመንደር ገጽታ እንዲኖራቸው ከጥንት ጊዜ ጀምረው የሚታወቁበት የምሕንድስና ጥበብ አስደማሚ ነው፤ ‹ጀፎረ›› ይባላል፡፡
በጉራጊኛ ‹ጀፎረ›› ማለት አውራ መንገድ ማለት ነው፡፡
‹ጀፎረ›› ከመሠረታዊ ጠቀሜታው ባለፈ ለጉራጌ መንደሮች ውበትን በማላበስ የጎላ አስተዋጽኦ አለው፡፡
በጉራጌ የመንደር አመሠራረት ያለ ጀፎረ አይታሰብም፡፡
ጀፎረ አረንጓዴ ሳር የለበሰ እና በሁለት ትይዩ መንደርተኞች መካከል የሚገኝ ሰፊና ማራኪ አውራ መንገድ ነው፡፡
ለአካባቢው ነዋሪዎች መግቢያና መውጫ እንዲሁም መተላለፊያ ሆኖ ያገለግላል፡፡
እስከ 60 ሜትር ድረስ ስፋት ያለው ይኽ የወል መንገድ ከመንገድነት ባሻገር ለተለያዩ ማኅበራዊ ኩነቶች ያገለግላል፡፡
‹ጀፎረ›› ለማኅበረሰቡ እንደሠርግ ያሉ የደስታ፣ እንደለቅሶ ያሉ የሐዘን ማኅበራዊ ሥነ ሥርዓቶች መከወኛ ስፍራም ነው፡፡
በሠርግ ወቅት ሰርገኞች የሚጨፍሩበት፣ አባቶችና እናቶች እንዲሁም የሰፈር አዛውንቶች ልጆቻቸውን መርቀው የሚሰጡበት ቦታ ነው፤ ‹ጀፎረ››፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ‹ጀፎረ›› የተለያዩ ስብሰባዎች፣ እንደ ፈረስ ጉግስና መሰል ባህላዊ ትዕይንቶች የሚካሄዱበትም ነው፡፡
የጉራጌ እረኞች ከብቶቻቸውን የሚያመላልሱበት በዚሁ ‹ጀፎረ›› በተባለው የወል ስፍራ ነው፡፡
በጉራጌ ባህል ‹ጀፎረ›› ወይም ባህላዊ አውራ መንገድን አጥሮ ወደ ግል ማካለል የተወገዘ ተግባር፤ ነውርም ነው።
ይህን ስርዓት ተላላልፎ የተገኘ ግለሰብ ቢኖር በማኅበረሰቡ ዘንድ ተቀባይነት ያጣል፤ ከማንኛውም ማኅበራዊ ግንኙነት ይገለላል፡፡
በጉራጌዎች ዘንድ በየዓመቱ በድምቀት የሚከበረው የዓረፋና የመስቀል በዓል በዚህ የወል ስፍራ ላይ ነው የሚከወነው፡፡
በበዓሉ ልጃገረዶችና ጎረምሶች ከሥነ ሥርዓቱ በኋላ ባህላዊ ጨዋታዎችን የሚጫወቱበት ስፍራም ነው፤ ‹ጀፎረ››፡፡
‹ጀፎረ›› በአሁን ወቅት የሃገሪቷን ማህበረሰብ ቀልብ ስቦ የከተማና የገጠር ኮሪደር ምሳሌ ሆኗል።
የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች ‹ጀፎረ››ን ለመጎብኘት ወደ ጉራጌዎች ምድር ማቅናታቸው በህዝቡ ዘንድ ደስታን ፈጥሯል።
OBN
#ethiopia | ጉራጌዎችን ታታሪ ጥበበኛ ከሚያሰኟቸው ነገሮች ውስጥ የመንደር አቀያየሳቸውና የሳር ቤት አሠራራቸው ተጠቃሽ ናቸው፡፡
በተለይ ደግሞ ማራኪ የመንደር ገጽታ እንዲኖራቸው ከጥንት ጊዜ ጀምረው የሚታወቁበት የምሕንድስና ጥበብ አስደማሚ ነው፤ ‹ጀፎረ›› ይባላል፡፡
በጉራጊኛ ‹ጀፎረ›› ማለት አውራ መንገድ ማለት ነው፡፡
‹ጀፎረ›› ከመሠረታዊ ጠቀሜታው ባለፈ ለጉራጌ መንደሮች ውበትን በማላበስ የጎላ አስተዋጽኦ አለው፡፡
በጉራጌ የመንደር አመሠራረት ያለ ጀፎረ አይታሰብም፡፡
ጀፎረ አረንጓዴ ሳር የለበሰ እና በሁለት ትይዩ መንደርተኞች መካከል የሚገኝ ሰፊና ማራኪ አውራ መንገድ ነው፡፡
ለአካባቢው ነዋሪዎች መግቢያና መውጫ እንዲሁም መተላለፊያ ሆኖ ያገለግላል፡፡
እስከ 60 ሜትር ድረስ ስፋት ያለው ይኽ የወል መንገድ ከመንገድነት ባሻገር ለተለያዩ ማኅበራዊ ኩነቶች ያገለግላል፡፡
‹ጀፎረ›› ለማኅበረሰቡ እንደሠርግ ያሉ የደስታ፣ እንደለቅሶ ያሉ የሐዘን ማኅበራዊ ሥነ ሥርዓቶች መከወኛ ስፍራም ነው፡፡
በሠርግ ወቅት ሰርገኞች የሚጨፍሩበት፣ አባቶችና እናቶች እንዲሁም የሰፈር አዛውንቶች ልጆቻቸውን መርቀው የሚሰጡበት ቦታ ነው፤ ‹ጀፎረ››፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ‹ጀፎረ›› የተለያዩ ስብሰባዎች፣ እንደ ፈረስ ጉግስና መሰል ባህላዊ ትዕይንቶች የሚካሄዱበትም ነው፡፡
የጉራጌ እረኞች ከብቶቻቸውን የሚያመላልሱበት በዚሁ ‹ጀፎረ›› በተባለው የወል ስፍራ ነው፡፡
በጉራጌ ባህል ‹ጀፎረ›› ወይም ባህላዊ አውራ መንገድን አጥሮ ወደ ግል ማካለል የተወገዘ ተግባር፤ ነውርም ነው።
ይህን ስርዓት ተላላልፎ የተገኘ ግለሰብ ቢኖር በማኅበረሰቡ ዘንድ ተቀባይነት ያጣል፤ ከማንኛውም ማኅበራዊ ግንኙነት ይገለላል፡፡
በጉራጌዎች ዘንድ በየዓመቱ በድምቀት የሚከበረው የዓረፋና የመስቀል በዓል በዚህ የወል ስፍራ ላይ ነው የሚከወነው፡፡
በበዓሉ ልጃገረዶችና ጎረምሶች ከሥነ ሥርዓቱ በኋላ ባህላዊ ጨዋታዎችን የሚጫወቱበት ስፍራም ነው፤ ‹ጀፎረ››፡፡
‹ጀፎረ›› በአሁን ወቅት የሃገሪቷን ማህበረሰብ ቀልብ ስቦ የከተማና የገጠር ኮሪደር ምሳሌ ሆኗል።
የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች ‹ጀፎረ››ን ለመጎብኘት ወደ ጉራጌዎች ምድር ማቅናታቸው በህዝቡ ዘንድ ደስታን ፈጥሯል።
OBN
Comments