6 days ago
መሣሪያን በብዕር የተኩ እጆች፤ የሀገራዊ ምክክር ታሪካዊ ምዕራፍ
***************
የግጭትን መንገድ ትቶ ወደ ሰላማዊ ውይይት በመምጣት በአንድ መድረክ ላይ በእጃቸው መሳሪያ ሳይሆን ብዕርን በመያዝ ሀሳባቸውን ለማስፈር መላው ኢትዮጵያውያን ተገናኝተዋል።
የሀገር ግንባታ መሠረቱ የሚጠነክረው በግጭት ሳይሆን በመደማመጥ፣ እንዲሁም በጋራ በሚገነባ የሀሳብ ራዕይ መሆኑን በማስረፅ።
በዚህ እሳቤ መሠረት ነው የሀገራዊ ምክክር ሂደት "የሁሉም ሀሳብ ለኢትዮጵያ ያስፈልጋል" በሚል መርህ የሁሉንም ድምፅ ለማዳመጥ በር የከፈተው።
ሀገራዊ ምክክር ዓላማው ልክ እንደ ውድድር አሸናፊና ተሸናፊ መለየት ሳይሆን በሕዝቦች ዘንድ የተወከሉ ተወካዮች ተጠናክረው የጋራ መፍትሔ በመፈለግ በሁሉም ውስጥ ኢትዮጵያን አሸናፊ ማድረግ ነው።
ለዚህም ዋና ማሳያ የሆነው ከ4 ሺህ በላይ ተመካካሪዎች በስምንት ዋና ዋና ሀገራዊ አጀንዳዎች ዙሪያ ከመላው ኢትዮጵያ የተወከሉ በቡድን ተከፋፍለው እየተወያዩ ይገኛሉ።
ዓመታትን በትጥቅ ትግል ያሳለፉ ተመካካሪዎች ዛሬ መሣሪያን አስቀምጠው ብዕር በመያዝ ሐሳባቸውን በውይይት እያቀረቡ ይገኛሉ፤ ይህ የሚጠቁመው ምልክት የጦርነትን ኃይል ሳይሆን በመመካከር ችግሮች ሊፈቱ እንደሚችሉ የሚያሳይ ተስፋ ሰጪ ምልክት እና የሰላም መንገድ ለሁሉም ክፍት መሆኑን ያረጋግጣል።
ተመካካሪዎቹ ከ250 አባላት ወደ 50 አባላት፣ በመጨረሻም ወደ 10 አባላት በመከፋፈል ሁሉም ተመካካሪ ያመጣውን የማኅበረሰብ ጥያቄና ሐሳብ ያለ ግፊት፣ ያለ ፍርሃት እና ያለ ተፅዕኖ በነፃነት እንዲያቀርብ ዕድል ተፈጥሮለታል።
ልዩነታቸው ውበታቸው የሆነው የኢትዮጵያውያን ሐሳቦች ሲገናኙ፣ ልዩነቶች ሲከበሩ እና ሁሉም ድምፅ የመደመጥ ዕድል ሲያገኝ፣ የነገዋ ኢትዮጵያ በተስፋ እና በመተማመን የተመሠረተች ትሆናለች። ለዘመናት የቆዩ ቁርሾዎችን በጠረጴዛ ዙሪያ በመፍታት የሰላም ባህልን ማጠናከር የዚህ ሂደት ትልቁ ስኬት ነው።
በዚህ መድረክ ላይ የሚጻፉት ቃላት በወረቀት ላይ ብቻ አይቀሩም፤ ወደ ታሪክ በመሻገር ከአዳራሹ አልፈው የቀጣዮቹን ትውልዶች ሊመሩ የሚችሉ እና ተስፋን፣ ይቅርታን፣ የጋራ ራዕይን የሚተክሉ ናቸው።
በዚህም ሀገር የምትገነባው በዜጎቿ የተረጋጋ ውይይት በመሆኑ ወደ ምክክር መምጣት የድክመት ምልክት ሳይሆን የብስለት፣ የኃላፊነት እና የጋራ የወደፊት ዕጣ ፈንታን በሰላማዊ መንገድ ለመወሰን የተወሰደ ጠንካራ እርምጃ ነው።
መሣሪያን በብዕር የተኩ እጆች የሚጽፉት የአንድ ቡድን ታሪክ አይደለም፤ የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ የወደፊት ምዕራፍን ነው።
በልዩ እሸቱ
#nationaldialogue #peacebuilding #futureethiopia #inclusion #unityindiversity #reconciliation
***************
የግጭትን መንገድ ትቶ ወደ ሰላማዊ ውይይት በመምጣት በአንድ መድረክ ላይ በእጃቸው መሳሪያ ሳይሆን ብዕርን በመያዝ ሀሳባቸውን ለማስፈር መላው ኢትዮጵያውያን ተገናኝተዋል።
የሀገር ግንባታ መሠረቱ የሚጠነክረው በግጭት ሳይሆን በመደማመጥ፣ እንዲሁም በጋራ በሚገነባ የሀሳብ ራዕይ መሆኑን በማስረፅ።
በዚህ እሳቤ መሠረት ነው የሀገራዊ ምክክር ሂደት "የሁሉም ሀሳብ ለኢትዮጵያ ያስፈልጋል" በሚል መርህ የሁሉንም ድምፅ ለማዳመጥ በር የከፈተው።
ሀገራዊ ምክክር ዓላማው ልክ እንደ ውድድር አሸናፊና ተሸናፊ መለየት ሳይሆን በሕዝቦች ዘንድ የተወከሉ ተወካዮች ተጠናክረው የጋራ መፍትሔ በመፈለግ በሁሉም ውስጥ ኢትዮጵያን አሸናፊ ማድረግ ነው።
ለዚህም ዋና ማሳያ የሆነው ከ4 ሺህ በላይ ተመካካሪዎች በስምንት ዋና ዋና ሀገራዊ አጀንዳዎች ዙሪያ ከመላው ኢትዮጵያ የተወከሉ በቡድን ተከፋፍለው እየተወያዩ ይገኛሉ።
ዓመታትን በትጥቅ ትግል ያሳለፉ ተመካካሪዎች ዛሬ መሣሪያን አስቀምጠው ብዕር በመያዝ ሐሳባቸውን በውይይት እያቀረቡ ይገኛሉ፤ ይህ የሚጠቁመው ምልክት የጦርነትን ኃይል ሳይሆን በመመካከር ችግሮች ሊፈቱ እንደሚችሉ የሚያሳይ ተስፋ ሰጪ ምልክት እና የሰላም መንገድ ለሁሉም ክፍት መሆኑን ያረጋግጣል።
ተመካካሪዎቹ ከ250 አባላት ወደ 50 አባላት፣ በመጨረሻም ወደ 10 አባላት በመከፋፈል ሁሉም ተመካካሪ ያመጣውን የማኅበረሰብ ጥያቄና ሐሳብ ያለ ግፊት፣ ያለ ፍርሃት እና ያለ ተፅዕኖ በነፃነት እንዲያቀርብ ዕድል ተፈጥሮለታል።
ልዩነታቸው ውበታቸው የሆነው የኢትዮጵያውያን ሐሳቦች ሲገናኙ፣ ልዩነቶች ሲከበሩ እና ሁሉም ድምፅ የመደመጥ ዕድል ሲያገኝ፣ የነገዋ ኢትዮጵያ በተስፋ እና በመተማመን የተመሠረተች ትሆናለች። ለዘመናት የቆዩ ቁርሾዎችን በጠረጴዛ ዙሪያ በመፍታት የሰላም ባህልን ማጠናከር የዚህ ሂደት ትልቁ ስኬት ነው።
በዚህ መድረክ ላይ የሚጻፉት ቃላት በወረቀት ላይ ብቻ አይቀሩም፤ ወደ ታሪክ በመሻገር ከአዳራሹ አልፈው የቀጣዮቹን ትውልዶች ሊመሩ የሚችሉ እና ተስፋን፣ ይቅርታን፣ የጋራ ራዕይን የሚተክሉ ናቸው።
በዚህም ሀገር የምትገነባው በዜጎቿ የተረጋጋ ውይይት በመሆኑ ወደ ምክክር መምጣት የድክመት ምልክት ሳይሆን የብስለት፣ የኃላፊነት እና የጋራ የወደፊት ዕጣ ፈንታን በሰላማዊ መንገድ ለመወሰን የተወሰደ ጠንካራ እርምጃ ነው።
መሣሪያን በብዕር የተኩ እጆች የሚጽፉት የአንድ ቡድን ታሪክ አይደለም፤ የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ የወደፊት ምዕራፍን ነው።
በልዩ እሸቱ
#nationaldialogue #peacebuilding #futureethiopia #inclusion #unityindiversity #reconciliation
22 days ago
የታሪክ ስህተቶችን በማረም ለነገይቱ ጠንካራ ኢትዮጵያ መሠረት የሚጥለው ሀገራዊ ምክክር
*******************
ታሪካዊው የሀገራዊ ምክክር ዋና ጉባኤ በስኬት እንዲጠናቀቅ እና ዘላቂ ውጤት እንዲያመጣ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልዕክት ለውይይቱ መነሻ የሚሆን ጠንካራ እሳቤን ይዟል።
ይህ መልዕክት የኢትዮጵያ የትናንት ሕመም፣ የዛሬ ፈተና እና የነገ ተስፋ በግልጽ የተንጸባረቀበት ነው።
የውስጥ ድክመት እና የውጭ ጣልቃ ገብነት አንደምታ
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሀገራችን ውስጣዊ ክፍተቶች ምክንያት የሚመጡ የውጭ ጣልቃ ገብነቶችን እና የጂኦፖለቲካ አደጋዎችን በምሳሌ አስረድተዋል።
የዚህ መልዕክት ትልቁ አንደምታ ግልጽ ነው፤ እኛ እርስ በርሳችን በውስጥ ጉዳዮቻችን ስንጨቃጨቅ እና ስንወዛገብ፣ የውጭ ኃይሎች መዳከማችንን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም የራሳቸውን ፍላጎትና ጥቅም በላያችን ላይ ይጭናሉ።
ይህን እውነት ለማሳየትም ታሪካዊ ስህተቶቻችንን አስታውሰዋል። ቀደም ባሉ ጊዜያት ልዩነቶቻችንን በውይይት መፍታት አለመቻላችን እና ውስጣዊ አንድነታችን መላላቱ ኢትዮጵያ ቀይ ባሕርን እንድታጣ አድርጓታል።
ይህም በታሪክ "የጂኦግራፊ እስረኛ" እንድንሆን አድርጎናል። የዚህ ታሪካዊ እውነት አንደምታ፣ የውስጥ መከፋፈል የአንድ ትውልድ ስህተት ብቻ ሳይሆን የብዙ ትውልዶችን የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚያጨልም ታሪካዊ ኪሳራ ማስከተሉን ሊያስተምረን ይገባል የሚል ነው።
"እኔ ብቻ" ከሚል ግትርነት ወደ መደማመጥ ባህል
የምክክሩ ስኬት የሚጀምረው ከአስተሳሰብ ለውጥ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ "እኔ ያልኩት ብቻ" በሚል ግትርነት የውይይት ባህልን የመቁረጥ አደገኛ አካሄድ መታረም እንዳለበት አሳስበዋል።
መደማመጥ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ለማስረዳትም የሀገራችንን ሁለት ድንቅ አባበሎች ጠቅሰዋል።
"መልካም ንግግር ከመልካም አልጋ በተሻለ ያሳርፋል" የሚለው የኦሮሞ አባቶች ይትበሃል እና "በአንድ ወገን ቆመህ የሌላውን ችግር መረዳት አትችልምና፣ ተነስተህ ሂድና አድምጥ" የሚለው የአፋሮች ጥልቅ ምክር የዚህ ማሳያ ናቸው።
የነዚህ አባባሎች አንደምታ ቀላልና ግልጽ ነው፤ ሰላም እና መግባባት የሚመጣው በጉልበት ሳይሆን በሃሳብ ልዕልና ነው።
እውነተኛ መግባባት የሚፈጠረው ደግሞ ከራሳችን ጠባብ አጥር ወጥተን የሌላውን ወገን ስሜት፣ ሃሳብ እና ስጋት ለመረዳት ስንሞክር ብቻ ነው።
በአሁኑ ወቅት የተሰበሰቡት 4 ሺህ ተሳታፊዎች ዋነኛ ሥራም ይህን የመደማመጥ ባህል በማዳበር ለሀገራችን ዘላቂ ሕገ-መንግሥታዊ ዋስትና ያለው ሥራ መሥራት ነው።
የውሸት ፕሮፓጋንዳ እና የሀገር ሕልውና
ሌላው ትልቁ መልዕክት፣ ተሳታፊዎች በውሸት ፕሮፓጋንዳዎች እንዳይዘናጉ የቀረበው አደራ ነው። ይህንንም "ቀፎዋን የጣለች ንብ፣ ማር አትሰጥም" በሚል ምሳሌ አስገንዝበዋል።
ሀገር ከሌለች ግለሰባዊም ሆነ ቡድናዊ ሕልውና ሊኖር አይችልም። ማር መሥራት የሚቻለው ቀፎው ሲኖር እና ንቦቹ በጋራ ሲሠሩ ብቻ ነው።
በመሆኑም በሀሰተኛ መረጃዎች እና አሉባልታዎች ተታልለን የጋራ ቀፎአችን የሆነችውን ሀገራችንን ማፍረስ፣ ከሁለት ያጣ እንደሚያደርገን መረዳት ያስፈልጋል።
ወደ አዲሱ የሰላም ሞዴል
ይህ ታሪካዊ የምክክር መድረክ እርስ በርስ በመደማመጥ አሁን ያለውን የዜሮ ድምር ፖለቲካ በምክክር እና መደማመጥ ላይ ወደተመሠረተ ዘላቂ ሰላም እና ልማት ለመለወጥ የተዘጋጀ ትልቅ በር ነው።
የፍትህ እና የዴሞክራሲ ተቋማት ገለልተኛ እንዲሆኑ በማድረግ፣ ኢትዮጵያን ለአፍሪካ ቀንድ እና ለመላው አህጉር አርአያ የሚሆን የሰላም ሞዴል የማድረግ ታላቅ ሀገራዊ ኃላፊነት አሁን በተመካካሪዎቹ እጅ ላይ ይገኛል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #pmabiyahmed #nationaldialogue #peacebuilding #reconciliation #ebc
*******************
ታሪካዊው የሀገራዊ ምክክር ዋና ጉባኤ በስኬት እንዲጠናቀቅ እና ዘላቂ ውጤት እንዲያመጣ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልዕክት ለውይይቱ መነሻ የሚሆን ጠንካራ እሳቤን ይዟል።
ይህ መልዕክት የኢትዮጵያ የትናንት ሕመም፣ የዛሬ ፈተና እና የነገ ተስፋ በግልጽ የተንጸባረቀበት ነው።
የውስጥ ድክመት እና የውጭ ጣልቃ ገብነት አንደምታ
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሀገራችን ውስጣዊ ክፍተቶች ምክንያት የሚመጡ የውጭ ጣልቃ ገብነቶችን እና የጂኦፖለቲካ አደጋዎችን በምሳሌ አስረድተዋል።
የዚህ መልዕክት ትልቁ አንደምታ ግልጽ ነው፤ እኛ እርስ በርሳችን በውስጥ ጉዳዮቻችን ስንጨቃጨቅ እና ስንወዛገብ፣ የውጭ ኃይሎች መዳከማችንን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም የራሳቸውን ፍላጎትና ጥቅም በላያችን ላይ ይጭናሉ።
ይህን እውነት ለማሳየትም ታሪካዊ ስህተቶቻችንን አስታውሰዋል። ቀደም ባሉ ጊዜያት ልዩነቶቻችንን በውይይት መፍታት አለመቻላችን እና ውስጣዊ አንድነታችን መላላቱ ኢትዮጵያ ቀይ ባሕርን እንድታጣ አድርጓታል።
ይህም በታሪክ "የጂኦግራፊ እስረኛ" እንድንሆን አድርጎናል። የዚህ ታሪካዊ እውነት አንደምታ፣ የውስጥ መከፋፈል የአንድ ትውልድ ስህተት ብቻ ሳይሆን የብዙ ትውልዶችን የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚያጨልም ታሪካዊ ኪሳራ ማስከተሉን ሊያስተምረን ይገባል የሚል ነው።
"እኔ ብቻ" ከሚል ግትርነት ወደ መደማመጥ ባህል
የምክክሩ ስኬት የሚጀምረው ከአስተሳሰብ ለውጥ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ "እኔ ያልኩት ብቻ" በሚል ግትርነት የውይይት ባህልን የመቁረጥ አደገኛ አካሄድ መታረም እንዳለበት አሳስበዋል።
መደማመጥ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ለማስረዳትም የሀገራችንን ሁለት ድንቅ አባበሎች ጠቅሰዋል።
"መልካም ንግግር ከመልካም አልጋ በተሻለ ያሳርፋል" የሚለው የኦሮሞ አባቶች ይትበሃል እና "በአንድ ወገን ቆመህ የሌላውን ችግር መረዳት አትችልምና፣ ተነስተህ ሂድና አድምጥ" የሚለው የአፋሮች ጥልቅ ምክር የዚህ ማሳያ ናቸው።
የነዚህ አባባሎች አንደምታ ቀላልና ግልጽ ነው፤ ሰላም እና መግባባት የሚመጣው በጉልበት ሳይሆን በሃሳብ ልዕልና ነው።
እውነተኛ መግባባት የሚፈጠረው ደግሞ ከራሳችን ጠባብ አጥር ወጥተን የሌላውን ወገን ስሜት፣ ሃሳብ እና ስጋት ለመረዳት ስንሞክር ብቻ ነው።
በአሁኑ ወቅት የተሰበሰቡት 4 ሺህ ተሳታፊዎች ዋነኛ ሥራም ይህን የመደማመጥ ባህል በማዳበር ለሀገራችን ዘላቂ ሕገ-መንግሥታዊ ዋስትና ያለው ሥራ መሥራት ነው።
የውሸት ፕሮፓጋንዳ እና የሀገር ሕልውና
ሌላው ትልቁ መልዕክት፣ ተሳታፊዎች በውሸት ፕሮፓጋንዳዎች እንዳይዘናጉ የቀረበው አደራ ነው። ይህንንም "ቀፎዋን የጣለች ንብ፣ ማር አትሰጥም" በሚል ምሳሌ አስገንዝበዋል።
ሀገር ከሌለች ግለሰባዊም ሆነ ቡድናዊ ሕልውና ሊኖር አይችልም። ማር መሥራት የሚቻለው ቀፎው ሲኖር እና ንቦቹ በጋራ ሲሠሩ ብቻ ነው።
በመሆኑም በሀሰተኛ መረጃዎች እና አሉባልታዎች ተታልለን የጋራ ቀፎአችን የሆነችውን ሀገራችንን ማፍረስ፣ ከሁለት ያጣ እንደሚያደርገን መረዳት ያስፈልጋል።
ወደ አዲሱ የሰላም ሞዴል
ይህ ታሪካዊ የምክክር መድረክ እርስ በርስ በመደማመጥ አሁን ያለውን የዜሮ ድምር ፖለቲካ በምክክር እና መደማመጥ ላይ ወደተመሠረተ ዘላቂ ሰላም እና ልማት ለመለወጥ የተዘጋጀ ትልቅ በር ነው።
የፍትህ እና የዴሞክራሲ ተቋማት ገለልተኛ እንዲሆኑ በማድረግ፣ ኢትዮጵያን ለአፍሪካ ቀንድ እና ለመላው አህጉር አርአያ የሚሆን የሰላም ሞዴል የማድረግ ታላቅ ሀገራዊ ኃላፊነት አሁን በተመካካሪዎቹ እጅ ላይ ይገኛል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #pmabiyahmed #nationaldialogue #peacebuilding #reconciliation #ebc
2 months ago
u121du12adu1275u120d u1320u1245u120bu12ed u121au1292u1235u1275u122d u1270u1218u1235u1308u1295 u1325u1229u1290u1205 u1260u121du1235u122bu1245 u1210u1228u122du130c u130bu122b u1219u1208u1273 u12ebu12f0u1228u1309u1275 u1309u1265u129du1275
#ebc #ethiopia #reconciliationu200b #historylessons #medemer #nationaldialogue #u1210u1228u122du130c ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በምስራቅ ሐረርጌ ጋራ ሙለታ ያደረጉት ጉብኝት
#ebc #ethiopia #reconciliation #historylessons #medemer #nationaldialogue #ሐረርጌ
8 months ago
✨ እርቅ ከእራስ ለስኬታማ ሕይወት
Self Reconciliation for a Successful Life
🎉 አራተኛ ዓመት እናከብራለን!
👤 አዘጋጅ:
• ፍጹም አጥናፈወርቅ ኪ/ማርያም
🎤 የመድረክ መሪ:
• ታፈሰ ሣህሌ
🎓 የእለቱ አስተማሪ እንግዶች:
• 🎭 አዳነች ወ/ገብርኤል — አርቲስት
• 🎬 ናሁሰናይ ግርማ — የኤውብ መስራች እና ዳይሬክተር
• 🎓 ፕሮፌሰር ፖኖስ ሀዘንድርያስ — የለባዊ ኢንተርናሸናል ት/ቤት መስራች እና ዳይሬክተር
• 💡 እቴነሽ ወንድሙ — የብርሀን ለሕጻናት መስራች እና ዳይሬክተር
💵 የመግቢያ ዋጋ: 300 ብር ብቻ!
📅 ቀን:
• ታህሣስ 11 ቀን 2018 ዓ.ም.
⏰ ሰዓት:
• ከሰዓት 10:30 — 1:30
🏨 ቦታ:
• በአዶር አዲስ ሆቴል
📍 አድራሻ:
• ከአትላስ ወረድ ብሎ — አውሮፓ ሕብረት ፊት ለፊት
• ደስአለኝ ሆቴል አጠገብ
Self Reconciliation for a Successful Life
🎉 አራተኛ ዓመት እናከብራለን!
👤 አዘጋጅ:
• ፍጹም አጥናፈወርቅ ኪ/ማርያም
🎤 የመድረክ መሪ:
• ታፈሰ ሣህሌ
🎓 የእለቱ አስተማሪ እንግዶች:
• 🎭 አዳነች ወ/ገብርኤል — አርቲስት
• 🎬 ናሁሰናይ ግርማ — የኤውብ መስራች እና ዳይሬክተር
• 🎓 ፕሮፌሰር ፖኖስ ሀዘንድርያስ — የለባዊ ኢንተርናሸናል ት/ቤት መስራች እና ዳይሬክተር
• 💡 እቴነሽ ወንድሙ — የብርሀን ለሕጻናት መስራች እና ዳይሬክተር
💵 የመግቢያ ዋጋ: 300 ብር ብቻ!
📅 ቀን:
• ታህሣስ 11 ቀን 2018 ዓ.ም.
⏰ ሰዓት:
• ከሰዓት 10:30 — 1:30
🏨 ቦታ:
• በአዶር አዲስ ሆቴል
📍 አድራሻ:
• ከአትላስ ወረድ ብሎ — አውሮፓ ሕብረት ፊት ለፊት
• ደስአለኝ ሆቴል አጠገብ
Comments