2 hours ago
ኮሜርሻል ኖሚኒስ 60ኛ ዓመት በዓሉን በሩጫ አጠናቀቀ!
#fastmereja :-በሀገራችን የአውትሶርሲንግ (Outsourcing) ዘርፍ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ የሆነው ኮሜርሻል ኖሚኒስ፣ የምስረታ በዓሉ ማጠቃለያ የሆነውን ታላቅ የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ በዛሬዉ እለት በአዲስ አበባ ከተማ በድምቀት ተካሄደ።
«ለ60 ዓመታት የታማኝነት ጉዞ በጋራ እንሩጥ!» በሚል መሪ ቃል በተካሄደው በዚህ ስፖርታዊ መርሐ-ግብር ላይ የከተማ አስተዳደሩና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ በርካታ ቁጥር ያላቸዉ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።
የኮሜርሻል ኖሚኒስ ዋና ስራ አስኪያጅ ኮማንደር ጥላቸው ፀጋዬ በዕለቱ እንደገለጹት፤ ሩጫው የ60 ዓመታትን የተቋማዊ ቅብብሎሽ ታሪክ ለማስታወስ ብቻ ሳይሆን፣ የተቋሙን ቀጣይ ግዙፍ የ10 እና የ20 ዓመታት የወደፊት ራዕይ ለህዝብ ለማስተዋወቅና የአዲስ አበባን ሰላምና ውበት ለአለም ለማሳየት ያለመ መልቲፕል (በርካታ) ዓላማዎች ያሉት መሆኑን ገልፀዋል።
ዋና ስራ አስኪያጁ አያይዘውም፣ ተቋሙ ከ60 ዓመታት ጉዞ በኋላ ወደፊት በ«ፒኤልሲ» ደረጃ ብቻ ሳይወሰን ወደ ግዙፍ የ«ኮሜርሻል ኖሚኒስ ግሩፕ» ለማደግ ስትራቴጂካዊ እቅዶችን ይዞ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ይፋ አድርገዋል።
ከተጠቀሱት አዳዲስና ግዙፍ ፕሮጀክቶች መካከል የአዋጭነት ጥናቱ የተጠናቀቀው የጋርመንት ፋብሪካ ግንባታ አንዱ ሲሆን፣ ይህም የድርጅቱን ዩኒፎርም ለባሽ ሰራተኞች ፍላጎት በራስ አቅም ለመሸፈንና ምርትን ወደ ውጭ በመላክ የውጭ ምንዛሬ ለማስገኘት የታለመ መሆኑ ነዉ የተገለፀዉ።
በተጨማሪም በደረቅ ቆሻሻ አስተዳደር ዘርፍ በመሰማራት «ከቆሻሻ ወደ ሀብት» ለመቀየር ጥናቶች እየተከናወኑ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅትም ለኮሪደር ልማቱ እገዛ የሚያደርግ በሰአት 60 ኪሎ ሜትር የሚሮጥ ዘመናዊ የፅዳት ማሽን ወደ ስራ መግባቱ የተገለፀ ሲሆን ድርጅቱ የራሱን ይዞታዎች በመጠቀም በሪል ስቴት ዘርፍ በስፋት ለመሳተፍ ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝም ተጠቁሟል።
በአሁኑ ወቅት ኮሜርሻል ኖሚኒስ በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ 30 ቅርንጫፎቹ አማካኝነት ከ40 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል የፈጠረ ሲሆን፣ ከነዚህም ውስጥ 42 በመቶ ያህሉ ሴቶች ናቸው።
ተቋሙ ወደፊት በሚያከናውናቸው አዳዲስ የኢንቨስትመንት ዘርፎች የሰራተኞቹን ቁጥር እስከ 120 ሺህ ለማድረስ እና በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ተወዳዳሪ ሆኖ ለመውጣት እየሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።
#fastmereja :-በሀገራችን የአውትሶርሲንግ (Outsourcing) ዘርፍ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ የሆነው ኮሜርሻል ኖሚኒስ፣ የምስረታ በዓሉ ማጠቃለያ የሆነውን ታላቅ የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ በዛሬዉ እለት በአዲስ አበባ ከተማ በድምቀት ተካሄደ።
«ለ60 ዓመታት የታማኝነት ጉዞ በጋራ እንሩጥ!» በሚል መሪ ቃል በተካሄደው በዚህ ስፖርታዊ መርሐ-ግብር ላይ የከተማ አስተዳደሩና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ በርካታ ቁጥር ያላቸዉ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።
የኮሜርሻል ኖሚኒስ ዋና ስራ አስኪያጅ ኮማንደር ጥላቸው ፀጋዬ በዕለቱ እንደገለጹት፤ ሩጫው የ60 ዓመታትን የተቋማዊ ቅብብሎሽ ታሪክ ለማስታወስ ብቻ ሳይሆን፣ የተቋሙን ቀጣይ ግዙፍ የ10 እና የ20 ዓመታት የወደፊት ራዕይ ለህዝብ ለማስተዋወቅና የአዲስ አበባን ሰላምና ውበት ለአለም ለማሳየት ያለመ መልቲፕል (በርካታ) ዓላማዎች ያሉት መሆኑን ገልፀዋል።
ዋና ስራ አስኪያጁ አያይዘውም፣ ተቋሙ ከ60 ዓመታት ጉዞ በኋላ ወደፊት በ«ፒኤልሲ» ደረጃ ብቻ ሳይወሰን ወደ ግዙፍ የ«ኮሜርሻል ኖሚኒስ ግሩፕ» ለማደግ ስትራቴጂካዊ እቅዶችን ይዞ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ይፋ አድርገዋል።
ከተጠቀሱት አዳዲስና ግዙፍ ፕሮጀክቶች መካከል የአዋጭነት ጥናቱ የተጠናቀቀው የጋርመንት ፋብሪካ ግንባታ አንዱ ሲሆን፣ ይህም የድርጅቱን ዩኒፎርም ለባሽ ሰራተኞች ፍላጎት በራስ አቅም ለመሸፈንና ምርትን ወደ ውጭ በመላክ የውጭ ምንዛሬ ለማስገኘት የታለመ መሆኑ ነዉ የተገለፀዉ።
በተጨማሪም በደረቅ ቆሻሻ አስተዳደር ዘርፍ በመሰማራት «ከቆሻሻ ወደ ሀብት» ለመቀየር ጥናቶች እየተከናወኑ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅትም ለኮሪደር ልማቱ እገዛ የሚያደርግ በሰአት 60 ኪሎ ሜትር የሚሮጥ ዘመናዊ የፅዳት ማሽን ወደ ስራ መግባቱ የተገለፀ ሲሆን ድርጅቱ የራሱን ይዞታዎች በመጠቀም በሪል ስቴት ዘርፍ በስፋት ለመሳተፍ ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝም ተጠቁሟል።
በአሁኑ ወቅት ኮሜርሻል ኖሚኒስ በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ 30 ቅርንጫፎቹ አማካኝነት ከ40 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል የፈጠረ ሲሆን፣ ከነዚህም ውስጥ 42 በመቶ ያህሉ ሴቶች ናቸው።
ተቋሙ ወደፊት በሚያከናውናቸው አዳዲስ የኢንቨስትመንት ዘርፎች የሰራተኞቹን ቁጥር እስከ 120 ሺህ ለማድረስ እና በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ተወዳዳሪ ሆኖ ለመውጣት እየሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።
4 days ago
ቦቆጂ፣ የዓለም አትሌቲክስ ማማ፤ የሻምፒዮኖች መፍለቂያ
#fastmereja I በኢትዮጵያ ስፖርት ታሪክ ውስጥ በቆጂን መዘንጋት የዓለምን የሩጫ ታሪክ እንደ መዘንጋት ይቆጠራል። በአርሲ ዞን፣ ሌሙ እና ቢልቢሎ ወረዳ የምትገኘው በቆጂ ከተማ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ በስሟ የሚታወቁትን አትሌቶች በማፍራት የኢትዮጵያን ስም ከፍ ያደረገች ታላቅ የጀግኖች ማዕከል ናት። በከተማዋ አምባሳደር በጋዜጠኛ አንዱዓለም ጌታቸው አማካኝነት የጎበኘናት ይህች ከተማ፣ ከሩጫ ሜዳ ባሻገር በባህሏ እና በልዩ አቀባበሏ ተወዳጅ መሆኗን አስመስክራለች።
ከአዲስ አበባ ተነስተን አዳማንና አሰላን አቋርጠን ወደ በቆጂ ስንገባ፣ ከተማዋ የምትቀበለን በልዩ አየር ነው። የቆላማው ትኩሳት በአርሲው ብርድ ተተክቶ፣ ንፋሱ እንደ አትሌቶቹ አቀባበል በጋለ ስሜት ይገጥመናል። የሀገር ሽማግሌዎች፣ አባ ገዳዎች፣ ሀዳ ሲንቄዎች እና ከንቲባዋ በባህላዊው አቀባበል "አና ዱፉ" በማለት፣ ጋቢ አልብሰው የጀመሩልን አቀባበል፤ የህዝቡን እንግዳ ተቀባይነትና የክብር መገለጫ ነው። ከንቲባ በርሃኔ ነገሰ እንደገለጹት፣ በቆጂ ለኢትዮጵያ የምታበረክተው አስተዋጽኦ የላቀ በመሆኑ፣ ከተማዋን ለጎብኚዎች ምቹ የማድረግ ስራ በልዩ ትኩረት እየተሰራበት ነው።
የበቆጂ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ የዓለምን የሩጫ ታሪክ የቀየሩ ድንቅ አትሌቶች የተፈጠሩባት፣ የአሸናፊነት መንፈስ የሚነፍስባት የተቀደሰች ምድር ናት። ደራርቱ ቱሉ፣ እጅጋየሁ ዲባባ፣ ጥሩነሽ ዲባባ፣ ገንዘቤ ዲባባ፣ ቀነኒሳ በቀለ፣ ታሪኩ በቀለ፣ እንዲሁም ለሜቻ ግርማ... እነዚህ ስሞች በቆጂን በዓለም የሩጫ ካርታ ላይ ያኖሩ ናቸው። ትምህርት ቤቱ ዛሬም በናፍቆት የተሞላ ነው፤ "የቀድሞ ተማሪዎቼ የት ናችሁ? እኔ ያሳደኳችሁ፣ የኮረኮምኳችሁ የትላንት ልጆቼ፣ መጥታችሁ ጎብኙኝ" እያለ በናፍቆት ይጠባበቃል። ይህ ትምህርት ቤት የዕውቀት ማዕከልነቱ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ለኢትዮጵያ አትሌቲክስ የፈጠረው ፋይዳ ሊዘነጋ የማይችል ታሪካዊ ሃብት ነው።
በቆጂ የሩጫ ብቻ አይደለችም! በከተማዋ እየተካሄደ ያለው የቴኳንዶ ስፖርት እንቅስቃሴ ሌላው የሚያስደንቅ ገጽታ ነው። "ዲ ቤስት ወርልድ ቴኳንዶ" የተባለ ማዕከል፣ በማስተር ደለለኝ አመራር ስር በቆጂን የቴኳንዶ ሻምፒዮኖች መፍለቂያ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት፣ የከተማዋን ስፖርታዊ ብቃት ሁለገብነት ያሳያል። ወጣቶች በሩጫ ብቻ ሳይሆን በሌሎች የትግል ስፖርቶችም ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸው፣ የከተማዋን የስፖርት ስትራቴጂ ትክክለኛነት ያሳያል።
ሌላኛው ትኩረት የሚስብ የጉብኝታችን ክፍል የቦቆጂ ሆስፒታል ነው። ከ500 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወገኖቻችን የጤና እፎይታን እየሰጠ የሚገኘው ይህ ሆስፒታል፣ ከህክምና አገልግሎቱ ባሻገር በውስጥ ግቢው እየተከናወኑ ያሉት የማስዋብ ስራዎች ተጠቃሽ ናቸው። ለህጻናት እና አዋቂዎች የመዝናኛ አገልግሎት የሚሰጡ መናፈሻዎች መገንባታቸው፣ ሆስፒታሉን የከተማዋ የውበት መገለጫ እና ማህበራዊ መስተጋብር የሚፈጠርበት ስፍራ አድርጎታል።
በርካታ አትሌቶችን ያፈራችው ቦቆጂ ስቴዲየም እና የመሮጫ ትራክ የላትም፣ ከታዳጊዎች እስከ አባቶች የህዝቡ ጉጉት ቦቆጂ ስታድየም ተሰርቶ ማየት ሲሆን ይህን የህዝቡ ጉጉት ተመልክተው በተቀናጀ ስራ የቦቆጂን ስታድየም ሰርተው አጠናቀው ለመመረቅ እንደምንሄድ ተስፋ አደርጋለሁ።
በቆጂ የታላቁ ሩጫን በስኬት እንዳስተናገደች ሁሉ፣ የከተማዋን የቱሪዝም አቅም ለመጠቀም እየተደረገ ያለው ጥረት አበረታች ነው። በቀጣይ የቱሪስት ስፍራዎቿን፣ የተፈጥሮ ውበቷን እና ታሪካዊ መዳረሻዎቿን በጥናት በመለየት ለጎብኚዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሰራ ተጠቁሟል። በቆጂ በአየርዋ፣ በታሪኳና በጀግኖቿ የምትወደድ ከተማ ናት፤ ገና ያልተነገረላት ብዙ ምስጢር ስላላት ወደፊት በድጋሜ ተመልሰን የምንጎበኛት ይሆናል።
#fastmereja I በኢትዮጵያ ስፖርት ታሪክ ውስጥ በቆጂን መዘንጋት የዓለምን የሩጫ ታሪክ እንደ መዘንጋት ይቆጠራል። በአርሲ ዞን፣ ሌሙ እና ቢልቢሎ ወረዳ የምትገኘው በቆጂ ከተማ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ በስሟ የሚታወቁትን አትሌቶች በማፍራት የኢትዮጵያን ስም ከፍ ያደረገች ታላቅ የጀግኖች ማዕከል ናት። በከተማዋ አምባሳደር በጋዜጠኛ አንዱዓለም ጌታቸው አማካኝነት የጎበኘናት ይህች ከተማ፣ ከሩጫ ሜዳ ባሻገር በባህሏ እና በልዩ አቀባበሏ ተወዳጅ መሆኗን አስመስክራለች።
ከአዲስ አበባ ተነስተን አዳማንና አሰላን አቋርጠን ወደ በቆጂ ስንገባ፣ ከተማዋ የምትቀበለን በልዩ አየር ነው። የቆላማው ትኩሳት በአርሲው ብርድ ተተክቶ፣ ንፋሱ እንደ አትሌቶቹ አቀባበል በጋለ ስሜት ይገጥመናል። የሀገር ሽማግሌዎች፣ አባ ገዳዎች፣ ሀዳ ሲንቄዎች እና ከንቲባዋ በባህላዊው አቀባበል "አና ዱፉ" በማለት፣ ጋቢ አልብሰው የጀመሩልን አቀባበል፤ የህዝቡን እንግዳ ተቀባይነትና የክብር መገለጫ ነው። ከንቲባ በርሃኔ ነገሰ እንደገለጹት፣ በቆጂ ለኢትዮጵያ የምታበረክተው አስተዋጽኦ የላቀ በመሆኑ፣ ከተማዋን ለጎብኚዎች ምቹ የማድረግ ስራ በልዩ ትኩረት እየተሰራበት ነው።
የበቆጂ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ የዓለምን የሩጫ ታሪክ የቀየሩ ድንቅ አትሌቶች የተፈጠሩባት፣ የአሸናፊነት መንፈስ የሚነፍስባት የተቀደሰች ምድር ናት። ደራርቱ ቱሉ፣ እጅጋየሁ ዲባባ፣ ጥሩነሽ ዲባባ፣ ገንዘቤ ዲባባ፣ ቀነኒሳ በቀለ፣ ታሪኩ በቀለ፣ እንዲሁም ለሜቻ ግርማ... እነዚህ ስሞች በቆጂን በዓለም የሩጫ ካርታ ላይ ያኖሩ ናቸው። ትምህርት ቤቱ ዛሬም በናፍቆት የተሞላ ነው፤ "የቀድሞ ተማሪዎቼ የት ናችሁ? እኔ ያሳደኳችሁ፣ የኮረኮምኳችሁ የትላንት ልጆቼ፣ መጥታችሁ ጎብኙኝ" እያለ በናፍቆት ይጠባበቃል። ይህ ትምህርት ቤት የዕውቀት ማዕከልነቱ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ለኢትዮጵያ አትሌቲክስ የፈጠረው ፋይዳ ሊዘነጋ የማይችል ታሪካዊ ሃብት ነው።
በቆጂ የሩጫ ብቻ አይደለችም! በከተማዋ እየተካሄደ ያለው የቴኳንዶ ስፖርት እንቅስቃሴ ሌላው የሚያስደንቅ ገጽታ ነው። "ዲ ቤስት ወርልድ ቴኳንዶ" የተባለ ማዕከል፣ በማስተር ደለለኝ አመራር ስር በቆጂን የቴኳንዶ ሻምፒዮኖች መፍለቂያ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት፣ የከተማዋን ስፖርታዊ ብቃት ሁለገብነት ያሳያል። ወጣቶች በሩጫ ብቻ ሳይሆን በሌሎች የትግል ስፖርቶችም ውጤታማ እየሆኑ መምጣታቸው፣ የከተማዋን የስፖርት ስትራቴጂ ትክክለኛነት ያሳያል።
ሌላኛው ትኩረት የሚስብ የጉብኝታችን ክፍል የቦቆጂ ሆስፒታል ነው። ከ500 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወገኖቻችን የጤና እፎይታን እየሰጠ የሚገኘው ይህ ሆስፒታል፣ ከህክምና አገልግሎቱ ባሻገር በውስጥ ግቢው እየተከናወኑ ያሉት የማስዋብ ስራዎች ተጠቃሽ ናቸው። ለህጻናት እና አዋቂዎች የመዝናኛ አገልግሎት የሚሰጡ መናፈሻዎች መገንባታቸው፣ ሆስፒታሉን የከተማዋ የውበት መገለጫ እና ማህበራዊ መስተጋብር የሚፈጠርበት ስፍራ አድርጎታል።
በርካታ አትሌቶችን ያፈራችው ቦቆጂ ስቴዲየም እና የመሮጫ ትራክ የላትም፣ ከታዳጊዎች እስከ አባቶች የህዝቡ ጉጉት ቦቆጂ ስታድየም ተሰርቶ ማየት ሲሆን ይህን የህዝቡ ጉጉት ተመልክተው በተቀናጀ ስራ የቦቆጂን ስታድየም ሰርተው አጠናቀው ለመመረቅ እንደምንሄድ ተስፋ አደርጋለሁ።
በቆጂ የታላቁ ሩጫን በስኬት እንዳስተናገደች ሁሉ፣ የከተማዋን የቱሪዝም አቅም ለመጠቀም እየተደረገ ያለው ጥረት አበረታች ነው። በቀጣይ የቱሪስት ስፍራዎቿን፣ የተፈጥሮ ውበቷን እና ታሪካዊ መዳረሻዎቿን በጥናት በመለየት ለጎብኚዎች ምቹ ለማድረግ እንደሚሰራ ተጠቁሟል። በቆጂ በአየርዋ፣ በታሪኳና በጀግኖቿ የምትወደድ ከተማ ናት፤ ገና ያልተነገረላት ብዙ ምስጢር ስላላት ወደፊት በድጋሜ ተመልሰን የምንጎበኛት ይሆናል።
4 days ago
የፈረንሳይ ክዋክብት የታራንጋ አንበሶችን ፈተና አሸነፉ
#ethiopia | በችሎታ እና በጥራት እርስ በእርስ የሚመሳሰሉት ፈረንሳይ እና ሴኔጋል ያደረጉት ተጠባቂ ጨዋታ በፈረንሳይ አሸናፊነት ተጠናቋል።
በሁለቱ ቡድኖች መካከል የነበረው ዋነኛው ልዩነት እንደ ኪሊያን ምባፔ ዓይነት ፈጣንና ገዳይ አጥቂ፣ እንዲሁም በማንኛውም ቅፅበት ጨዋታን መቀየር የሚችሉት እንደ ማይክል ኦሊሴ እና አድሪያን ራቢዮ ያሉ ተፈጥሯዊ የቴክኒክ ክህሎት ያላቸው ኮከቦች በሴኔጋል በኩል አለመኖራቸው ነው።
እነዚህ የፈረንሳይ የፊት መስመር ተጫዋቾች በሰከንዶች ሹልክታ ከሴኔጋሉ ግብ ጠባቂ ኤድዋርድ ሜንዲ ጋር በመገናኘት በደቂቃዎች ውስጥ የጨዋታውን ውጤት መወሰን ችለዋል።
በዚህም ፈረንሳይ ጨዋታውን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት ስታሸንፍ፣ ኪሊያን ምባፔ በጨዋታው ማጠናቀቂያ ላይ ባስቆጠራት አስደናቂ የሮኬት ግብ የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን የምንጊዜውም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ መሆን ችሏል።
ለ65 ደቂቃዎች ያህል በሁለቱ ቡድኖች መካከል የነበረው ብርቱና እልህ አስጨራሽ የአቻነት ትንቅንቅ በመጨረሻም በግል ተጫዋቾች የክህሎት ልዩነት ሊፈታ ችሏል።
የማድሪዱ ኮከብ ኪሊያን ምባፔ በዓለም ዋንጫው መድረክ ላይ በድጋሚ አስደናቂ ብቃቱን አሳይቷል። ሁለቱ ቡድኖች ከሜዳ አቀማመጥ ውጭ በጨዋታ እንቅስቃሴ ረገድ እምብዛም ሰፊ ልዩነት አልነበራቸውም።
በጠንካራ አካል ብቃት፣ ከፍተኛ ሩጫ፣ መውደቅ መነሳትና ፍልሚያ በታየበት በዚህ ዘመናዊ የእግር ኳስ ጨዋታ፣ በታክቲክ የበሰለው ትንቅንቅ እስከ 65ኛው ደቂቃ ድረስ በእኩልነት ቀጥሎ ነበር። ይሁን እንጂ በወሳኙ ሰዓት የፈረንሳይ የክዋክብት ስብስብ ጨዋታውን መለወጥ ችሏል።
የፓሪሱ ኮከብ ምባፔ አስማታዊ ብቃት ፈረንሳይን ለድል ሲያበቃ፣ የታራንጋ አንበሶቹ ሴኔጋል ግን ጨዋታን ለመቀየር ጥቂት ደቂቃዎች ብቻ የሚበቋቸው እንደ ምባፔ፣ ኦሊሴ እና ራቢዮ ያሉ ተጫዋቾች ባለመኖራቸው በመጨረሻ ለመሸነፍ ተገደዋል።
ጨዋታውም በፈረንሳይ 3 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቋል።
#worldcup #francevssenegal #mbappe #football #sportsnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በችሎታ እና በጥራት እርስ በእርስ የሚመሳሰሉት ፈረንሳይ እና ሴኔጋል ያደረጉት ተጠባቂ ጨዋታ በፈረንሳይ አሸናፊነት ተጠናቋል።
በሁለቱ ቡድኖች መካከል የነበረው ዋነኛው ልዩነት እንደ ኪሊያን ምባፔ ዓይነት ፈጣንና ገዳይ አጥቂ፣ እንዲሁም በማንኛውም ቅፅበት ጨዋታን መቀየር የሚችሉት እንደ ማይክል ኦሊሴ እና አድሪያን ራቢዮ ያሉ ተፈጥሯዊ የቴክኒክ ክህሎት ያላቸው ኮከቦች በሴኔጋል በኩል አለመኖራቸው ነው።
እነዚህ የፈረንሳይ የፊት መስመር ተጫዋቾች በሰከንዶች ሹልክታ ከሴኔጋሉ ግብ ጠባቂ ኤድዋርድ ሜንዲ ጋር በመገናኘት በደቂቃዎች ውስጥ የጨዋታውን ውጤት መወሰን ችለዋል።
በዚህም ፈረንሳይ ጨዋታውን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት ስታሸንፍ፣ ኪሊያን ምባፔ በጨዋታው ማጠናቀቂያ ላይ ባስቆጠራት አስደናቂ የሮኬት ግብ የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን የምንጊዜውም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ መሆን ችሏል።
ለ65 ደቂቃዎች ያህል በሁለቱ ቡድኖች መካከል የነበረው ብርቱና እልህ አስጨራሽ የአቻነት ትንቅንቅ በመጨረሻም በግል ተጫዋቾች የክህሎት ልዩነት ሊፈታ ችሏል።
የማድሪዱ ኮከብ ኪሊያን ምባፔ በዓለም ዋንጫው መድረክ ላይ በድጋሚ አስደናቂ ብቃቱን አሳይቷል። ሁለቱ ቡድኖች ከሜዳ አቀማመጥ ውጭ በጨዋታ እንቅስቃሴ ረገድ እምብዛም ሰፊ ልዩነት አልነበራቸውም።
በጠንካራ አካል ብቃት፣ ከፍተኛ ሩጫ፣ መውደቅ መነሳትና ፍልሚያ በታየበት በዚህ ዘመናዊ የእግር ኳስ ጨዋታ፣ በታክቲክ የበሰለው ትንቅንቅ እስከ 65ኛው ደቂቃ ድረስ በእኩልነት ቀጥሎ ነበር። ይሁን እንጂ በወሳኙ ሰዓት የፈረንሳይ የክዋክብት ስብስብ ጨዋታውን መለወጥ ችሏል።
የፓሪሱ ኮከብ ምባፔ አስማታዊ ብቃት ፈረንሳይን ለድል ሲያበቃ፣ የታራንጋ አንበሶቹ ሴኔጋል ግን ጨዋታን ለመቀየር ጥቂት ደቂቃዎች ብቻ የሚበቋቸው እንደ ምባፔ፣ ኦሊሴ እና ራቢዮ ያሉ ተጫዋቾች ባለመኖራቸው በመጨረሻ ለመሸነፍ ተገደዋል።
ጨዋታውም በፈረንሳይ 3 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቋል።
#worldcup #francevssenegal #mbappe #football #sportsnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
5 days ago
"ለ60 አመታት የታማኝነት ጉዞ በጋራ እንሩጥ"
የቤተሰብ፣ የአንድነት ሩጫ!
የኮሜርሺያል ኖሚኒስ ቤተሰቦች፣ ክቡራን ደንበኞቻችን እና ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት "ለ60 አመታት የታማኝነት ጉዞ በጋራ እንሩጥ" የጎዳና ላይ ሩጫ ሰኔ 14 ቀን 2018 አ.ም ይካሄዳል።
60 አመታትን በታማኝነት ያገለገለው ኮሜርሺያል ኖሚኒስ፣ በደንበኞቹ፣ በእህት ተቋማቱ ፣ በሰራተኞቹ እና በመላው የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ማህበረሰብ መካካል ይበልጥ መቀራረብን ለመፍጠር እና ቤተሰባዊ አንድነትን ለማጠናከር በሚረዳው የ5 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ እንድትሳተፉ በአክብሮት ጋብዘነዎታል።
ቲ-ሸርቶቹን በኮሜርሺያል ኖሚኒስ ዋና መስሪያ ቤት እና አዲስ አበባ በሚገኙ የኮሜርሺያል ቅርንጫፎች ያገኛሉ፡፡
ዋናው መ/ቤት ----------------ስ.ቁ 09 32 15 13 85
መገናኛ ቅርንጫፍ-------------ስ.ቁ 09 13 59 78 11
ቦሌ ቅርንጫፍ-----------------ስ.ቁ 09 13 07 67 12
አራዳ ቅርንጫፍ---------------ስ.ቁ 09 21 85 39 30
ሳሪስ ቅርንጫፍ----------------ስ.ቁ 09 12 08 22 57
የካ ቅርንጫፍ------------------ስ.ቁ 09 10 16 36 06
መርካቶ ቅርንጫፍ------------ስ.ቁ 09 51 10 46 12
ልደታ ቅርንጫፍ---------------ስ.ቁ 09 13 61 23 95
ኮልፌ ቅርንጫፍ---------------ስ.ቁ 09 11 91 76 47
ቂርቆስ ቅርንጫፍ--------------ስ.ቁ 09 11 82 75 69
ቃሊቲ ቅርንጫፍ---------------ስ.ቁ 09 31 27 27 27
የአንድ ቲ-ሸርት ዋጋ 500 ብር ሲሆን ክፍያውን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000770855237 (CN for Event Management) እና በሲቢኢ ብር መክፈል ይቻላል፡፡
የሩጫው መስመር፡- መነሻውን ከአትላስ መኪና መኪና ማቆሚያ አድርጎ ወደ ኡራኤል ቤተ ክርስቲያን አደባባይ ሳይደርስ ወደ ግራ በመታጠፍ ወደ አትላስ ኢንተርናሽናል ሆቴል በመመለስ በቦሌ መድሃኔዓለም ቤተክርስቲያን፣ በሸገር ህንጻ አልፎ መድረሻውን አትላስ መኪና ማቆሚያ ያደርጋል፡፡
የሩጫው መርሀግብር የሚጀምረው ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12፡00 ነው፡፡
ለተጨማሪ መረጃ በ6630 ነጻ የስልክ ጥሪ
ወይም በ 0932151385 እና በ0904032498 ደውለው ማግኘት ይችላሉ
የቤተሰብ፣ የአንድነት ሩጫ!
የኮሜርሺያል ኖሚኒስ ቤተሰቦች፣ ክቡራን ደንበኞቻችን እና ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት "ለ60 አመታት የታማኝነት ጉዞ በጋራ እንሩጥ" የጎዳና ላይ ሩጫ ሰኔ 14 ቀን 2018 አ.ም ይካሄዳል።
60 አመታትን በታማኝነት ያገለገለው ኮሜርሺያል ኖሚኒስ፣ በደንበኞቹ፣ በእህት ተቋማቱ ፣ በሰራተኞቹ እና በመላው የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ማህበረሰብ መካካል ይበልጥ መቀራረብን ለመፍጠር እና ቤተሰባዊ አንድነትን ለማጠናከር በሚረዳው የ5 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ እንድትሳተፉ በአክብሮት ጋብዘነዎታል።
ቲ-ሸርቶቹን በኮሜርሺያል ኖሚኒስ ዋና መስሪያ ቤት እና አዲስ አበባ በሚገኙ የኮሜርሺያል ቅርንጫፎች ያገኛሉ፡፡
ዋናው መ/ቤት ----------------ስ.ቁ 09 32 15 13 85
መገናኛ ቅርንጫፍ-------------ስ.ቁ 09 13 59 78 11
ቦሌ ቅርንጫፍ-----------------ስ.ቁ 09 13 07 67 12
አራዳ ቅርንጫፍ---------------ስ.ቁ 09 21 85 39 30
ሳሪስ ቅርንጫፍ----------------ስ.ቁ 09 12 08 22 57
የካ ቅርንጫፍ------------------ስ.ቁ 09 10 16 36 06
መርካቶ ቅርንጫፍ------------ስ.ቁ 09 51 10 46 12
ልደታ ቅርንጫፍ---------------ስ.ቁ 09 13 61 23 95
ኮልፌ ቅርንጫፍ---------------ስ.ቁ 09 11 91 76 47
ቂርቆስ ቅርንጫፍ--------------ስ.ቁ 09 11 82 75 69
ቃሊቲ ቅርንጫፍ---------------ስ.ቁ 09 31 27 27 27
የአንድ ቲ-ሸርት ዋጋ 500 ብር ሲሆን ክፍያውን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000770855237 (CN for Event Management) እና በሲቢኢ ብር መክፈል ይቻላል፡፡
የሩጫው መስመር፡- መነሻውን ከአትላስ መኪና መኪና ማቆሚያ አድርጎ ወደ ኡራኤል ቤተ ክርስቲያን አደባባይ ሳይደርስ ወደ ግራ በመታጠፍ ወደ አትላስ ኢንተርናሽናል ሆቴል በመመለስ በቦሌ መድሃኔዓለም ቤተክርስቲያን፣ በሸገር ህንጻ አልፎ መድረሻውን አትላስ መኪና ማቆሚያ ያደርጋል፡፡
የሩጫው መርሀግብር የሚጀምረው ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12፡00 ነው፡፡
ለተጨማሪ መረጃ በ6630 ነጻ የስልክ ጥሪ
ወይም በ 0932151385 እና በ0904032498 ደውለው ማግኘት ይችላሉ
Sponsored by
Surafel
7 days ago
የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም እድሳት ተጠናቆ ወደ ውድድር ሊመለስ መሆኑ ተገለጸ
የባሕር ዳር ዓለም ከባህር ዳር ከተማ ስታዲየም በቅርቡ ወደ ስፖርታዊ ውድድሮች እንደሚመለስ የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው አስታወቁ።
ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ይህንን የገለጹት በከተማዋ በደመቀ ሁኔታ በተካሄደው የ1ኛው የኢትዮጵያ 10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር መዝጊያ ስነስርዓት ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ነው።
የስታዲየሙን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ጎሹ እንዳላማው የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም የእድሳት ሥራ በአሁኑ ወቅት እየተጠናቀቀ መሆኑን ጠቁመው፣ ስታዲየሙ በቅርቡ ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ ውድድሮችን ማስተናገድ በሚችልበት ቁመና ላይ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል።
ከተማዋ ያሏትን ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎችና አዳዲስ እየተገነቡ ያሉ መስተንግዶዎችን ያነሱት ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ይህ መሰረተልማት ስታዲየሙንና ባህር ዳርን ሁሉ የተሟላላት ዘመናዊ የቱሪዝምና የስፖርት ከተማ እንደሚያደርጋት ገልጸዋል።
በሌላ በኩል በከተማዋ የተካሄደውን የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር አስመልክቶ ባደረጉት ንግግር ውድድሩ የባሕር ዳር ከተማ አስተማማኝ የሰላም ከተማ መሆኗን በተግባር ያረጋገጠበት መድረክ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ውድድሩ በባሕር ዳር እንዲካሄድ ውሳኔ ላስተላለፉና በቦታው ተገኝተው ለታደሙት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮችም የከተማ አስተዳደሩን ምስጋና አቅርበዋል።
#አሐዱ
የባሕር ዳር ዓለም ከባህር ዳር ከተማ ስታዲየም በቅርቡ ወደ ስፖርታዊ ውድድሮች እንደሚመለስ የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው አስታወቁ።
ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ይህንን የገለጹት በከተማዋ በደመቀ ሁኔታ በተካሄደው የ1ኛው የኢትዮጵያ 10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር መዝጊያ ስነስርዓት ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ነው።
የስታዲየሙን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ጎሹ እንዳላማው የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም የእድሳት ሥራ በአሁኑ ወቅት እየተጠናቀቀ መሆኑን ጠቁመው፣ ስታዲየሙ በቅርቡ ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ ውድድሮችን ማስተናገድ በሚችልበት ቁመና ላይ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል።
ከተማዋ ያሏትን ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎችና አዳዲስ እየተገነቡ ያሉ መስተንግዶዎችን ያነሱት ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ይህ መሰረተልማት ስታዲየሙንና ባህር ዳርን ሁሉ የተሟላላት ዘመናዊ የቱሪዝምና የስፖርት ከተማ እንደሚያደርጋት ገልጸዋል።
በሌላ በኩል በከተማዋ የተካሄደውን የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር አስመልክቶ ባደረጉት ንግግር ውድድሩ የባሕር ዳር ከተማ አስተማማኝ የሰላም ከተማ መሆኗን በተግባር ያረጋገጠበት መድረክ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ውድድሩ በባሕር ዳር እንዲካሄድ ውሳኔ ላስተላለፉና በቦታው ተገኝተው ለታደሙት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮችም የከተማ አስተዳደሩን ምስጋና አቅርበዋል።
#አሐዱ
7 days ago
በቆጂ ከተማ የ2018 ኢትዮ ቴሌኮም ታላቁ ሩጫን በስኬት አጠናቀቀች
#fastmereja I ለአምስተኛ ጊዜ የተካሄደውን 12 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን የ2018 ኢትዮ ቴሌኮም ታላቁ የቦቆጂ ሩጫ በስኬት ተጠናቀቀ።
በቦቆጂ ስታድየም መነሻና መድረሻውን ባደረገው የዛሬው ውድድር በወንዶች የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን አትሌት የሆነው ማሞ ሐጫሉ ቀዳሚ ሲሆን፣ አማን ቃዲ እና አልዬ ቃሲም 2ኛ እና 3ኛ ደረጃን ይዘዋል። በሴቶች ደግሞ የአሰላ አትሌቲክስ ክለብ ተወዳዳሪዋ ማህሌት ካሳሁን ስታሸንፍ፣ ኪያ ፍስሃ እና ድርቤ ኢርኮ ተከታትለው በመግባት የ2ኛ እና 3ኛ ደረጃን ተቆጣጥረዋል።
የ'ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክስ’ ተከታታይ ውድድር አካል በሆነው በዚህ መርሃ ግብር ላይ የ15 ዓመት በታች የታዳጊዎች ሻምፕዮናም የተካሄደ ሲሆን፣ በተጨማሪም የ11 ዓመት በታች እና የህጻናት ውድድሮች ተካሂደዋል።
ከ2500 በላይ የአካባቢው ነዋሪዎች እና ከአዲስ አበባ የተጓዙ ከ70 በላይ ሯጮች የተሳተፉበት ይህ ውድድር በአርሲ አባቶች ምርቃት እና በብሔራዊ መዝሙር ተጀምሯል።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ አቶ መኪዩ ሙሐመድ፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) እና የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሮዛ ቢያ፣ የአርሲ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ኢብራሂም ከድር እና የቦቆጂ ከተማ ከንቲባን ብርሃነ ነገሰ ጨምሮ በርካታ የመንግስት ከፍተኛ ኃላፊዎች በቦታው ተገኝተዋል።
#fastmereja I ለአምስተኛ ጊዜ የተካሄደውን 12 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነውን የ2018 ኢትዮ ቴሌኮም ታላቁ የቦቆጂ ሩጫ በስኬት ተጠናቀቀ።
በቦቆጂ ስታድየም መነሻና መድረሻውን ባደረገው የዛሬው ውድድር በወንዶች የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን አትሌት የሆነው ማሞ ሐጫሉ ቀዳሚ ሲሆን፣ አማን ቃዲ እና አልዬ ቃሲም 2ኛ እና 3ኛ ደረጃን ይዘዋል። በሴቶች ደግሞ የአሰላ አትሌቲክስ ክለብ ተወዳዳሪዋ ማህሌት ካሳሁን ስታሸንፍ፣ ኪያ ፍስሃ እና ድርቤ ኢርኮ ተከታትለው በመግባት የ2ኛ እና 3ኛ ደረጃን ተቆጣጥረዋል።
የ'ልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክስ’ ተከታታይ ውድድር አካል በሆነው በዚህ መርሃ ግብር ላይ የ15 ዓመት በታች የታዳጊዎች ሻምፕዮናም የተካሄደ ሲሆን፣ በተጨማሪም የ11 ዓመት በታች እና የህጻናት ውድድሮች ተካሂደዋል።
ከ2500 በላይ የአካባቢው ነዋሪዎች እና ከአዲስ አበባ የተጓዙ ከ70 በላይ ሯጮች የተሳተፉበት ይህ ውድድር በአርሲ አባቶች ምርቃት እና በብሔራዊ መዝሙር ተጀምሯል።
የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ አቶ መኪዩ ሙሐመድ፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) እና የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሮዛ ቢያ፣ የአርሲ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ኢብራሂም ከድር እና የቦቆጂ ከተማ ከንቲባን ብርሃነ ነገሰ ጨምሮ በርካታ የመንግስት ከፍተኛ ኃላፊዎች በቦታው ተገኝተዋል።
7 days ago
🏃♀️🏃♂️ የ2018 ኢትዮ ቴሌኮም ታላቁ ሩጫ በቦቆጂ በድምቀት ተካሔደ!!
የ12ኪ.ሜ. ርቀት የሸፈነው ውድድር ከ100 በላይ አትሌቶችን፣ ከአዲስ አበባ ከ70 በላይ ተሳታፊዎችንና 2500 የከተማዋ ነዋሪዎችን አሳትፏል።
በተጨማሪም ተተኪዎችን ለማፍራት ያለመውና ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ታዳጊዎችን ያሳተፈው የ15ዓመት በታችና የ11ዓመት በታች ውድድሮች ሲካሔዱ የሕጻናት ውድድርም የዝግጅቱ ተጨማሪ ውበት ነበር።
የአገራችን አትሌቲክስ ለማሳደግና ተተኪዎች ለማፍራት በሚደረገው ጥረት ኩባንያችን ኢትዮ ቴሌኮም ላለፉት 5 ተከታታይ ዓመታት በስያሜ አጋርነት ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር እየሠራ የሚገኝ ሲሆን ወደ ፊትም በአትሌቲክሱ ዘርፍ የምናደርገውን አስተዋጽኦ አጠናክረን እንቀጥላለን።
#ethiotelecomgreatbokojirun #greatethiopianrun #bokoji #telebirr #ethiotelecom
የ12ኪ.ሜ. ርቀት የሸፈነው ውድድር ከ100 በላይ አትሌቶችን፣ ከአዲስ አበባ ከ70 በላይ ተሳታፊዎችንና 2500 የከተማዋ ነዋሪዎችን አሳትፏል።
በተጨማሪም ተተኪዎችን ለማፍራት ያለመውና ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ታዳጊዎችን ያሳተፈው የ15ዓመት በታችና የ11ዓመት በታች ውድድሮች ሲካሔዱ የሕጻናት ውድድርም የዝግጅቱ ተጨማሪ ውበት ነበር።
የአገራችን አትሌቲክስ ለማሳደግና ተተኪዎች ለማፍራት በሚደረገው ጥረት ኩባንያችን ኢትዮ ቴሌኮም ላለፉት 5 ተከታታይ ዓመታት በስያሜ አጋርነት ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር እየሠራ የሚገኝ ሲሆን ወደ ፊትም በአትሌቲክሱ ዘርፍ የምናደርገውን አስተዋጽኦ አጠናክረን እንቀጥላለን።
#ethiotelecomgreatbokojirun #greatethiopianrun #bokoji #telebirr #ethiotelecom
7 days ago
በቆጂ : አትሌት ማሞ ሐጫሉ እና ማህሌት ካሳሁን የድል አክሊል ደፉ
#ethiopia | ለአምስተኛ ጊዜ መነሻና መድረሻውን በቆጂ ስታዲየም ባደረገው የ12 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር በወንዶች ዘርፍ የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ክለብ ተወካይ የሆነው ማሞ ሐጫሉ አንደኛ በመሆን አሸንፏል።
በዚሁ ምድብ አማን ቃዲ እና አልዬ ቃሲም ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን አጠናቀዋል።
በሴቶች ምድብ በተደረገው ፉክክር የአሰላ አትሌቲክስ ክለብ አትሌት ማህሌት ካሳሁን ቀዳሚነቱን ስትይዝ፤ ኪያ ፍስሃ እና ድርቤ ኢርኮ በቅደም ተከተል ሁለተኛና ሶስተኛ በመሆን ተከታትለው ገብተዋል።
የልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክስ ተከታታይ ውድድር አካል በሆነው በዚህ ዝግጅት ላይ ዕድሜያቸው ከ11 እና ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ህጻናት በሁለቱም ጾታ ያደረጉት ተሳትፎ ለውድድሩ የተለየ ድምቀት ሰጥቶት አርፍዷል።
በስፍራው ተገኝተው የክብር እንግዳ የነበሩት የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ መኪዩ ሙሐመድ፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ እንደገና አበበ ዶክተር፣ የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሮዛ ቢያ እና የበቆጂ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ ብርሃኔ ነገሰ ሲሆኑ በርካታ የአካባቢው ነዋሪዎችም ታድመውታል።
በስድስት ከተሞች ላይ የሚካሄደው የልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክስ ውድድር ቀጣይ መርሃ ግብሩን ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም በአርባምንጭ ከተማ የሚያደርግ ሲሆን የፍጻሜው ውድድር ደግሞ ሐምሌ 12 ቀን በታሪካዊቷ ሐረር ከተማ እንደሚጠናቀቅ ታውቋል።
#bekoji #athletics #ethiotelecom #greatethiopianrun #sportnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ለአምስተኛ ጊዜ መነሻና መድረሻውን በቆጂ ስታዲየም ባደረገው የ12 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር በወንዶች ዘርፍ የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ክለብ ተወካይ የሆነው ማሞ ሐጫሉ አንደኛ በመሆን አሸንፏል።
በዚሁ ምድብ አማን ቃዲ እና አልዬ ቃሲም ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን አጠናቀዋል።
በሴቶች ምድብ በተደረገው ፉክክር የአሰላ አትሌቲክስ ክለብ አትሌት ማህሌት ካሳሁን ቀዳሚነቱን ስትይዝ፤ ኪያ ፍስሃ እና ድርቤ ኢርኮ በቅደም ተከተል ሁለተኛና ሶስተኛ በመሆን ተከታትለው ገብተዋል።
የልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክስ ተከታታይ ውድድር አካል በሆነው በዚህ ዝግጅት ላይ ዕድሜያቸው ከ11 እና ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ህጻናት በሁለቱም ጾታ ያደረጉት ተሳትፎ ለውድድሩ የተለየ ድምቀት ሰጥቶት አርፍዷል።
በስፍራው ተገኝተው የክብር እንግዳ የነበሩት የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ መኪዩ ሙሐመድ፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ እንደገና አበበ ዶክተር፣ የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሮዛ ቢያ እና የበቆጂ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ ብርሃኔ ነገሰ ሲሆኑ በርካታ የአካባቢው ነዋሪዎችም ታድመውታል።
በስድስት ከተሞች ላይ የሚካሄደው የልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክስ ውድድር ቀጣይ መርሃ ግብሩን ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም በአርባምንጭ ከተማ የሚያደርግ ሲሆን የፍጻሜው ውድድር ደግሞ ሐምሌ 12 ቀን በታሪካዊቷ ሐረር ከተማ እንደሚጠናቀቅ ታውቋል።
#bekoji #athletics #ethiotelecom #greatethiopianrun #sportnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
7 days ago
ታዋቂዋ የአትሌቶች መፍለቂያ ቦቆጂ ከተማ የልወቅሽ የኢትዮጵያ ክላሲክ 2018 የሩጫ ውድድርን በደመቀ ሁኔታ ማስተናገድ ጀመረች
#ethiopia | የበርካታ የዓለምና የኦሊምፒክ ሻምፒዮኖችን በማፍራት በዓለም አቀፍ ደረጃ በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀሰው የቦቆጂ ከተማ፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በመሆን ያዘጋጀውን ልወቅሽ የኢትዮጵያ ክላሲክ ታላቅ የሩጫ ውድድር በዛሬው ዕለት ማስተናገድ ጀምራለች።
ውድድሩ መነሻና መድረሻውን ታሪካዊው የቦቆጂ ስታዲየም ላይ ያደረገ ሲሆን፣ ከ100 በላይ አንጋፋና ፕሮፌሽናል አትሌቶች፣ ከ2 ሺህ 500 በላይ የቦቆጂ ከተማ ነዋሪዎች እንዲሁም ከአዲስ አበባ የተጓዙ ከ70 በላይ የስፖርቱ አፍቃሪያን ተሳታፊ ሆነዋል።
ይህ ትልቅ ስፖርታዊ መርሃ ግብር የአትሌቲክስ ስፖርትን ለማሳደግ ከሚኖረው ሚና ባሻገር፣ የቦቆጂን ከተማ የቱሪዝም መስህቦችና አቅሞች ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ጎብኝዎች በሰፊው ለማስተዋወቅ ታላቅ ዕድል የፈጠረ ነው።
የመጀመሪያው ምዕራፉ በደብረ ብርሃን ከተማ ተጀምሮ አሁን በቦቆጂ ይፋዊ ጉዞውን የቀጠለው ይህ መርሃ ግብር፣ በኢትዮጵያ የስፖርት ቱሪዝም ልማት ላይ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ክስተት ሆኗል።
በዚህ ደማቅ የማስጀመሪያ ዝግጅት ላይ የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እንደገና አበበ፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ መኪዩ መሀመድ፣ የአርሲ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኢብራሒም ከድር እና የቦቆጂ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ ብርሃኔ ነገሰ ተገኝተዋል።
በተጨማሪም ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የቱሪዝም ዘርፍ ተወካዮች፣ ታዋቂ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችና የብዙኃን መገናኛ ባለሙያዎች በከተማዋ በመገኘት መርሃ ግብሩን ታድመዋል።
#bekoji #ethiopianclassic #greatethiopianrun #sportstourism #tourismethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የበርካታ የዓለምና የኦሊምፒክ ሻምፒዮኖችን በማፍራት በዓለም አቀፍ ደረጃ በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀሰው የቦቆጂ ከተማ፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በመሆን ያዘጋጀውን ልወቅሽ የኢትዮጵያ ክላሲክ ታላቅ የሩጫ ውድድር በዛሬው ዕለት ማስተናገድ ጀምራለች።
ውድድሩ መነሻና መድረሻውን ታሪካዊው የቦቆጂ ስታዲየም ላይ ያደረገ ሲሆን፣ ከ100 በላይ አንጋፋና ፕሮፌሽናል አትሌቶች፣ ከ2 ሺህ 500 በላይ የቦቆጂ ከተማ ነዋሪዎች እንዲሁም ከአዲስ አበባ የተጓዙ ከ70 በላይ የስፖርቱ አፍቃሪያን ተሳታፊ ሆነዋል።
ይህ ትልቅ ስፖርታዊ መርሃ ግብር የአትሌቲክስ ስፖርትን ለማሳደግ ከሚኖረው ሚና ባሻገር፣ የቦቆጂን ከተማ የቱሪዝም መስህቦችና አቅሞች ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ጎብኝዎች በሰፊው ለማስተዋወቅ ታላቅ ዕድል የፈጠረ ነው።
የመጀመሪያው ምዕራፉ በደብረ ብርሃን ከተማ ተጀምሮ አሁን በቦቆጂ ይፋዊ ጉዞውን የቀጠለው ይህ መርሃ ግብር፣ በኢትዮጵያ የስፖርት ቱሪዝም ልማት ላይ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ክስተት ሆኗል።
በዚህ ደማቅ የማስጀመሪያ ዝግጅት ላይ የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር እንደገና አበበ፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ መኪዩ መሀመድ፣ የአርሲ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ኢብራሒም ከድር እና የቦቆጂ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ ብርሃኔ ነገሰ ተገኝተዋል።
በተጨማሪም ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የቱሪዝም ዘርፍ ተወካዮች፣ ታዋቂ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችና የብዙኃን መገናኛ ባለሙያዎች በከተማዋ በመገኘት መርሃ ግብሩን ታድመዋል።
#bekoji #ethiopianclassic #greatethiopianrun #sportstourism #tourismethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
8 days ago
ዛሬ ቀኑ ነው‼️
🎂 ዛሬ የእሱ ቀን ነው፦
በኦሊምፒክ 3 ወርቅ እና 1 ብር ሜዳሊያ
በአለም ሻምፒዮና 5 ወርቅ እና 1 ነሃስ ሜዳሊያ
በአለም ሀገር አቋራጭ 11 ወርቅ እና 1 ብር ሜዳሊያ
በአለም ሜጀር ማራቶን 2 ወርቅ 2 ብር እና 2 ነሀስ ሜዳሊያ
🎂 ዛሬ የጀግናው ቀን ነው፦
የ2004/5 የአለም የአመቱ ምርጥ አትሌት
የ2004/5 የትራክና ፊልድ ኒውስ የአመቱ ምርጥ አትሌት
የየኢኤስፒኤን የ21ኛው ክፍለ ዘመን ቁጥር አንድ አትሌት
ከስድስት በላይ የአለም ክብረወሰኖችን የሰበረ አትሌት
🎂 ዛሬ እለቱ ነው፦
ሱሉልታ ላይ ዘመናዊ ትራክ ያለው
አዲስ አበባ፣ ሱሉልታና አሰላ ላይ የሆቴሎች ባለቤት
ሱሉልታ ለአካባቢው ማህበረሰብ ትምህርት ቤት የከፈተ
በርካታ አብያተ ክርስቲያናትን ያሰራ
በበጎ አድራጎት ተግባራት ቀድሞ የሚገኝ
ታዳጊ አትሌቶችን በገንዘብና በትጥቅ የሚደግፍ
🎂 ዛሬ የእሱ ቅዳሜ ነው፦
ከቤተሰቡ 6 ፍሬዎች መካከል 2ኛ ልጅ የሆነ
3 ወንድምና 2 እህቶች ያሉት
ከባለቤቱ ዳናዊት ገ/እግዚአብሔር 2 ሴት እና 1 ወንድ ልጅ ያፈራ
🎂 ዛሬ የዝምተኛው ገዳይ ቀን ነው፦
በ27 አመታት የሩጫ አለም ቆይታው ከ200 በላይ ውድድሮችን ያደረገ፥ ብሄራዊ መዝሙራችንን በአለም ፊት ደጋግሞ ያዘመረ፥ ሰንደቃችንን ከፍ አድርጎ ያሰቀለ፥ ከአርሲ ዩኒቨርስቲ የክብር ዶክትሬት የተቀበለ፥ በአዲስ ስፖርት ፓርክ የክብር ሃውልት የቆመለት፥ ትውልድ ተሻጋሪ ታሪክ የሰራ
🎂 ዛሬ የቀነኒ ኬኛ እለት ነው
የትዕግስት፣ የቁጭት፣ የፅናት፣ የጥረት፣ የተስፋ፣ የእልህ፣ የልፋት ከዛ የስኬት ተምሳሌት ኢትዮጵያዊው ጀግና አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ዛሬ ቅዳሜ ሰኔ 6/2018 ልደቱ ነው
44 አመት ሞላው🎂
ቀነኒ ኬኛ ለኢትዮጵያ እንኳን ተወለድክላት! መልካም ልደት!
Via: ታምሩ ዓለሙ
🎂 ዛሬ የእሱ ቀን ነው፦
በኦሊምፒክ 3 ወርቅ እና 1 ብር ሜዳሊያ
በአለም ሻምፒዮና 5 ወርቅ እና 1 ነሃስ ሜዳሊያ
በአለም ሀገር አቋራጭ 11 ወርቅ እና 1 ብር ሜዳሊያ
በአለም ሜጀር ማራቶን 2 ወርቅ 2 ብር እና 2 ነሀስ ሜዳሊያ
🎂 ዛሬ የጀግናው ቀን ነው፦
የ2004/5 የአለም የአመቱ ምርጥ አትሌት
የ2004/5 የትራክና ፊልድ ኒውስ የአመቱ ምርጥ አትሌት
የየኢኤስፒኤን የ21ኛው ክፍለ ዘመን ቁጥር አንድ አትሌት
ከስድስት በላይ የአለም ክብረወሰኖችን የሰበረ አትሌት
🎂 ዛሬ እለቱ ነው፦
ሱሉልታ ላይ ዘመናዊ ትራክ ያለው
አዲስ አበባ፣ ሱሉልታና አሰላ ላይ የሆቴሎች ባለቤት
ሱሉልታ ለአካባቢው ማህበረሰብ ትምህርት ቤት የከፈተ
በርካታ አብያተ ክርስቲያናትን ያሰራ
በበጎ አድራጎት ተግባራት ቀድሞ የሚገኝ
ታዳጊ አትሌቶችን በገንዘብና በትጥቅ የሚደግፍ
🎂 ዛሬ የእሱ ቅዳሜ ነው፦
ከቤተሰቡ 6 ፍሬዎች መካከል 2ኛ ልጅ የሆነ
3 ወንድምና 2 እህቶች ያሉት
ከባለቤቱ ዳናዊት ገ/እግዚአብሔር 2 ሴት እና 1 ወንድ ልጅ ያፈራ
🎂 ዛሬ የዝምተኛው ገዳይ ቀን ነው፦
በ27 አመታት የሩጫ አለም ቆይታው ከ200 በላይ ውድድሮችን ያደረገ፥ ብሄራዊ መዝሙራችንን በአለም ፊት ደጋግሞ ያዘመረ፥ ሰንደቃችንን ከፍ አድርጎ ያሰቀለ፥ ከአርሲ ዩኒቨርስቲ የክብር ዶክትሬት የተቀበለ፥ በአዲስ ስፖርት ፓርክ የክብር ሃውልት የቆመለት፥ ትውልድ ተሻጋሪ ታሪክ የሰራ
🎂 ዛሬ የቀነኒ ኬኛ እለት ነው
የትዕግስት፣ የቁጭት፣ የፅናት፣ የጥረት፣ የተስፋ፣ የእልህ፣ የልፋት ከዛ የስኬት ተምሳሌት ኢትዮጵያዊው ጀግና አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ዛሬ ቅዳሜ ሰኔ 6/2018 ልደቱ ነው
44 አመት ሞላው🎂
ቀነኒ ኬኛ ለኢትዮጵያ እንኳን ተወለድክላት! መልካም ልደት!
Via: ታምሩ ዓለሙ
8 days ago
አዲስ አበባ - የዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ የስፖርት ውድድሮች ተመራጭ ከተማ
****************
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለስፖርቱ ዘርፍ በሰጠው ልዩ ትኩረት እና ባከናወናቸው ግዙፍ የስፓርት መሠረተ ልማት ግንባታዎች ምክንያት መዲናዋ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ውድድሮች በስፋት የሚስተናገዱባት ቀዳሚ ተመራጭ የስፖርት ማዕከል መሆን ችላለች።
ባለፉት ዓመታት በከተማዋ የተገነቡት ከ1 ሺህ 580 በላይ የሕዝብ እና የወጣቶች ስፖርት ማዕከላት ማኅበረሰባዊ ተሳትፎን ከማሳደግ ባለፈ ሀገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ለማስተናገድ ትልቅ መሠረት ተጥሏል።
በቅርቡ በታላቅ ድምቀት የተጠናቀቀው እና በመስቀል አደባባይ የተካሄደው 19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶንን ጨምሮ ከተማዋ የተለያዩ ዓለም አቀፍ የብስክሌት፣ የአትሌቲክስ፣ የጎዳና ላይ ሩጫ እና ሌሎች የስፖርት ሁነቶችን በስኬት በማስተናገድ መዲናዋ ምቹ እና ተመሪጭ ከተማ መሆንዋን በተግባር እያሳየች ትገኛለች።
አዲስ አበባ አሁን ላይ የስፖርት ልሂቃን መገናኛ፣ የትላልቅ ውድድሮች እና የደጋፊዎች ድምቀት የምታስተናግድ ደኅንነቷ የተጠበቀ እና ውብ መዲና ሆናለች።
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑት የተቀናጁ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች፣ የወንዝ ዳርቻዎች እና ደረጃቸውን የጠበቁ የስፖርት ማዕከላት መስፋፋት የአዲስ አበባን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ለስፖርት ቱሪዝም ዕድገት ትልቅ አቅም ፈጥረዋል።
ይህ የስፖርት ቱሪዝም ዕድገት ከስፖርታዊ ፋይዳው ባሻገር፣ ለሆቴል ኢንዱስትሪው፣ ለትራንስፖርት ዘርፉ እና ለአካባቢው አነስተኛ እና ጥቃቅን የንግድ አንቀሳቃሾች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ መነቃቃትን ፈጥሯል።
ይህም የከተማ አስተዳደሩ የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እና የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማሳደግ የያዘውን ግብ በከፍተኛ ደረጃ እየደገፈው እንደሚገኝ ከከንቲባ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
#ethiopia #ebc #addisababa #sports
****************
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለስፖርቱ ዘርፍ በሰጠው ልዩ ትኩረት እና ባከናወናቸው ግዙፍ የስፓርት መሠረተ ልማት ግንባታዎች ምክንያት መዲናዋ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ውድድሮች በስፋት የሚስተናገዱባት ቀዳሚ ተመራጭ የስፖርት ማዕከል መሆን ችላለች።
ባለፉት ዓመታት በከተማዋ የተገነቡት ከ1 ሺህ 580 በላይ የሕዝብ እና የወጣቶች ስፖርት ማዕከላት ማኅበረሰባዊ ተሳትፎን ከማሳደግ ባለፈ ሀገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ለማስተናገድ ትልቅ መሠረት ተጥሏል።
በቅርቡ በታላቅ ድምቀት የተጠናቀቀው እና በመስቀል አደባባይ የተካሄደው 19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶንን ጨምሮ ከተማዋ የተለያዩ ዓለም አቀፍ የብስክሌት፣ የአትሌቲክስ፣ የጎዳና ላይ ሩጫ እና ሌሎች የስፖርት ሁነቶችን በስኬት በማስተናገድ መዲናዋ ምቹ እና ተመሪጭ ከተማ መሆንዋን በተግባር እያሳየች ትገኛለች።
አዲስ አበባ አሁን ላይ የስፖርት ልሂቃን መገናኛ፣ የትላልቅ ውድድሮች እና የደጋፊዎች ድምቀት የምታስተናግድ ደኅንነቷ የተጠበቀ እና ውብ መዲና ሆናለች።
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑት የተቀናጁ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች፣ የወንዝ ዳርቻዎች እና ደረጃቸውን የጠበቁ የስፖርት ማዕከላት መስፋፋት የአዲስ አበባን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ለስፖርት ቱሪዝም ዕድገት ትልቅ አቅም ፈጥረዋል።
ይህ የስፖርት ቱሪዝም ዕድገት ከስፖርታዊ ፋይዳው ባሻገር፣ ለሆቴል ኢንዱስትሪው፣ ለትራንስፖርት ዘርፉ እና ለአካባቢው አነስተኛ እና ጥቃቅን የንግድ አንቀሳቃሾች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ መነቃቃትን ፈጥሯል።
ይህም የከተማ አስተዳደሩ የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እና የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማሳደግ የያዘውን ግብ በከፍተኛ ደረጃ እየደገፈው እንደሚገኝ ከከንቲባ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
#ethiopia #ebc #addisababa #sports
Sponsored by
Surafel
8 days ago
አሜሪካ የፓራጓይን ተስፋ አጨለመችው!
ጨዋታው ከጀመረበት የመጀመሪያ ደቂቃ አንስቶ አሜሪካ ፓራጓይን እንደ ማዕበል ጠራርጋ በመውሰድ ሜዳ ላይ ምንም ዕድል አልሰጠቻትም!
የተጫዋቾቹ ፍጥነት፣ ኳስ የሚያቀባብሉበት ጥበብ እና በመካከላቸው ያለው የመግባባት ደረጃ እጅግ የሚያስደንቅ ነው። ከሁሉም በላይ ደግሞ በጨዋታው ውስጥ የሚጠቀሙበትን ፎርሜሽን በነጻነት እና በፍጥነት የሚቀይሩበት መንገድ አስገራሚ ነው።
ይህ ትልቅ የዓለም ዋንጫ መድረክ ፓራጓይን በድንጋጤ እንድትዋጥ አድርጓታል ሊባል ቢችልም፣ እውነታው ግን አሜሪካ ከጠበቅነው በላይ ብቃቷን አሳድጋ መቅረቧ ነው! ሁሉም የአሜሪካ ተጫዋቾች በከፍተኛ በራስ መተማመን እና ቆራጥነት እየተጫወቱ ነው፤ እያንዳንዱ ተጫዋች የራሱን ሚና ጠንቅቆ ከማወቁም በላይ፣ ለቡድን አጋሮቹ ክፍት ቦታዎችን ለመፍጠር የሚያደርገው ትክክለኛ ሩጫ የሚደነቅ ነው። በዚህ ሁኔታ ከቀጠሉ የመጨረሻው ውጤት ምን ሊሆን እንደሚችል መገመት ይከብዳል!
እስካሁን ያየነው የ45 ደቂቃ ጨዋታቸውን ብቻ ቢሆንም፣ ይህ 45 ደቂቃ ግን በእግር ኳስ አፍቃሪው ዘንድ በቀላሉ የማይረሳ እና እጅግ አስደናቂ ሆኖ አልፏል።
ጨዋታው ከጀመረበት የመጀመሪያ ደቂቃ አንስቶ አሜሪካ ፓራጓይን እንደ ማዕበል ጠራርጋ በመውሰድ ሜዳ ላይ ምንም ዕድል አልሰጠቻትም!
የተጫዋቾቹ ፍጥነት፣ ኳስ የሚያቀባብሉበት ጥበብ እና በመካከላቸው ያለው የመግባባት ደረጃ እጅግ የሚያስደንቅ ነው። ከሁሉም በላይ ደግሞ በጨዋታው ውስጥ የሚጠቀሙበትን ፎርሜሽን በነጻነት እና በፍጥነት የሚቀይሩበት መንገድ አስገራሚ ነው።
ይህ ትልቅ የዓለም ዋንጫ መድረክ ፓራጓይን በድንጋጤ እንድትዋጥ አድርጓታል ሊባል ቢችልም፣ እውነታው ግን አሜሪካ ከጠበቅነው በላይ ብቃቷን አሳድጋ መቅረቧ ነው! ሁሉም የአሜሪካ ተጫዋቾች በከፍተኛ በራስ መተማመን እና ቆራጥነት እየተጫወቱ ነው፤ እያንዳንዱ ተጫዋች የራሱን ሚና ጠንቅቆ ከማወቁም በላይ፣ ለቡድን አጋሮቹ ክፍት ቦታዎችን ለመፍጠር የሚያደርገው ትክክለኛ ሩጫ የሚደነቅ ነው። በዚህ ሁኔታ ከቀጠሉ የመጨረሻው ውጤት ምን ሊሆን እንደሚችል መገመት ይከብዳል!
እስካሁን ያየነው የ45 ደቂቃ ጨዋታቸውን ብቻ ቢሆንም፣ ይህ 45 ደቂቃ ግን በእግር ኳስ አፍቃሪው ዘንድ በቀላሉ የማይረሳ እና እጅግ አስደናቂ ሆኖ አልፏል።
9 days ago
የስልሳ ዓመታት የታማኝነት ጉዞን የሚዘክር የቤተሰብ እና የአንድነት የጎዳና ላይ ሩጫ ሊካሄድ ነው
#ethiopia | ኮሜርሺያል ኖሚኒስ የስልሳ ዓመታት የሥራ ጉዞውን እና የቆየ የታማኝነት አገልግሎቱን ምክንያት በማድረግ ያዘጋጀው የጎዳና ላይ ሩጫ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል።
በተቋሙ አዘጋጅነት የሚከናወነው በዚህ የ5 ኪሎ ሜትር የነፃነት እና የአንድነት መርሃ ግብር ላይ የድርጅቱ ሠራተኞች፣ ደንበኞች፣ አጋር ድርጅቶች እና የባለድርሻ አካላት በጋራ ይሳተፋሉ።
የዝግጅቱ ዋና ዓላማ በተጠቃሚው ማህበረሰብ፣ በሠራተኞች እና በደንበኞች መካከል ያለውን ማህበራዊ ትስስር ይበልጥ ማጠናከር እና ቤተሰባዊ መቀራረብን መፍጠር ነው።
ለሩጫው የተዘጋጁ ቲሸርቶችን በኮሜርሺያል ኖሚኒስ ዋና መሥሪያ ቤት እና በአዲስ አበባ በሚገኙ በተመረጡ ቅርንጫፎች ማግኘት ይቻላል።
እያንዳንዱ ቲሸርት በ500 ብር የሚሸጥ ሲሆን፣ ክፍያውን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር 1000770855237 (CN for Event Management) ወይም በሲቢኢ ብር መፈጸም ይቻላል።
ቲሸርቶቹን ለማግኘት እና መረጃ ለመጠየቅ በሚከተሉት የቅርንጫፍ ስልክ ቁጥሮች ማነጋገር ይቻላል
ዋና መሥሪያ ቤት +251-932-151385
መገናኛ ቅርንጫፍ +251-913-597811
ቦሌ ቅርንጫፍ +251-913-076712
አራዳ ቅርንጫፍ +251-921-853930
ሳሪስ ቅርንጫፍ +251-912-082257
የካ ቅርንጫፍ +251-910-163606
መርካቶ ቅርንጫፍ +251-951-104612
ልደታ ቅርንጫፍ +251-913-612395
ኮልፌ ቅርንጫፍ +251-911-917647
ቂርቆስ ቅርንጫፍ +251-911-827569
ቃሊቲ ቅርንጫፍ +251-931-272727
የሩጫው መነሻ መስመር ከአትላስ መኪና ማቆሚያ ተነስቶ ወደ ኡራኤል ቤተክርስቲያን አደባባይ ከመድረሱ በፊት ወደ ግራ በመታጠፍ ወደ አትላስ ኢንተርናሽናል ሆቴል ያመራል።
በመቀጠልም በቦሌ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን እና በሸገር ሕንፃ አጠገብ አልፎ መድረሻውን ድጋሚ በአትላስ መኪና ማቆሚያ ያደርጋል።
ይህ ታላቅ ስፖርታዊ መርሃ ግብር ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ የሚከናወን ይሆናል።
ለተጨማሪ ማብራሪያ
በ6630 ነፃ የስልክ መስመር
ወይም
በ0932151385 እና በ0904032498
ደውሎ መረዳት ይቻላል።
#commercialnominees #familyrun #healthylifestyle #running #community #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ኮሜርሺያል ኖሚኒስ የስልሳ ዓመታት የሥራ ጉዞውን እና የቆየ የታማኝነት አገልግሎቱን ምክንያት በማድረግ ያዘጋጀው የጎዳና ላይ ሩጫ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል።
በተቋሙ አዘጋጅነት የሚከናወነው በዚህ የ5 ኪሎ ሜትር የነፃነት እና የአንድነት መርሃ ግብር ላይ የድርጅቱ ሠራተኞች፣ ደንበኞች፣ አጋር ድርጅቶች እና የባለድርሻ አካላት በጋራ ይሳተፋሉ።
የዝግጅቱ ዋና ዓላማ በተጠቃሚው ማህበረሰብ፣ በሠራተኞች እና በደንበኞች መካከል ያለውን ማህበራዊ ትስስር ይበልጥ ማጠናከር እና ቤተሰባዊ መቀራረብን መፍጠር ነው።
ለሩጫው የተዘጋጁ ቲሸርቶችን በኮሜርሺያል ኖሚኒስ ዋና መሥሪያ ቤት እና በአዲስ አበባ በሚገኙ በተመረጡ ቅርንጫፎች ማግኘት ይቻላል።
እያንዳንዱ ቲሸርት በ500 ብር የሚሸጥ ሲሆን፣ ክፍያውን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር 1000770855237 (CN for Event Management) ወይም በሲቢኢ ብር መፈጸም ይቻላል።
ቲሸርቶቹን ለማግኘት እና መረጃ ለመጠየቅ በሚከተሉት የቅርንጫፍ ስልክ ቁጥሮች ማነጋገር ይቻላል
ዋና መሥሪያ ቤት +251-932-151385
መገናኛ ቅርንጫፍ +251-913-597811
ቦሌ ቅርንጫፍ +251-913-076712
አራዳ ቅርንጫፍ +251-921-853930
ሳሪስ ቅርንጫፍ +251-912-082257
የካ ቅርንጫፍ +251-910-163606
መርካቶ ቅርንጫፍ +251-951-104612
ልደታ ቅርንጫፍ +251-913-612395
ኮልፌ ቅርንጫፍ +251-911-917647
ቂርቆስ ቅርንጫፍ +251-911-827569
ቃሊቲ ቅርንጫፍ +251-931-272727
የሩጫው መነሻ መስመር ከአትላስ መኪና ማቆሚያ ተነስቶ ወደ ኡራኤል ቤተክርስቲያን አደባባይ ከመድረሱ በፊት ወደ ግራ በመታጠፍ ወደ አትላስ ኢንተርናሽናል ሆቴል ያመራል።
በመቀጠልም በቦሌ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን እና በሸገር ሕንፃ አጠገብ አልፎ መድረሻውን ድጋሚ በአትላስ መኪና ማቆሚያ ያደርጋል።
ይህ ታላቅ ስፖርታዊ መርሃ ግብር ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ የሚከናወን ይሆናል።
ለተጨማሪ ማብራሪያ
በ6630 ነፃ የስልክ መስመር
ወይም
በ0932151385 እና በ0904032498
ደውሎ መረዳት ይቻላል።
#commercialnominees #familyrun #healthylifestyle #running #community #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
9 days ago
ቦቆጂ ዝግጁ⁉️
የአገራችን አትሌቶች መፍለቂያ በሆነችው በቆጂ የሚካሔደው #ኢትዮ_ቴሌኮም_ታላቁ_ቦቆጂ_ሩጫ ሁለት ቀናት ብቻ ቀርተውታል!
እሑድ ቦቆጂ እንገናኝ!
#ethiotelecom #greatethiopiarun #bokoji #telebirr #digitalafrica #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
የአገራችን አትሌቶች መፍለቂያ በሆነችው በቆጂ የሚካሔደው #ኢትዮ_ቴሌኮም_ታላቁ_ቦቆጂ_ሩጫ ሁለት ቀናት ብቻ ቀርተውታል!
እሑድ ቦቆጂ እንገናኝ!
#ethiotelecom #greatethiopiarun #bokoji #telebirr #digitalafrica #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
9 days ago
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ 10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር በባህርዳር ከተማ ሊካሄድ ነው
#ethiopia | የመጀመሪያው የኢትዮጵያ 10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር የፊታችን እሁድ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም በባህርዳር ከተማ በደመቀ ሁኔታ እንደሚካሄድ ተነገረ።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በውድድሩ ቅድመ ዝግጅት ስራዎች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው መግለጫ፣ የፌዴሬሽኑ ከፍተኛ የቴክኒክ ባለሙያዎች ወደ ስፍራው በማቅናት አስፈላጊውን ዝግጅት እያከናወኑ እንደሚገኙ አስታውቋል።
ይህ የውድድር መድረክ በዋናነት አዳዲስ ተተኪ አትሌቶችን ለማፍራትና የውድድር እድሎችን ለመፍጠር ያለመ መሆኑም ተገልጿል።
በዚሁ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ላይ የግል ተሳታፊዎችን ጨምሮ ከ6 የተለያዩ ክለቦች የተውጣጡ 91 አትሌቶች እንደሚሳተፉ ታውቋል። በውድድሩ ከ1ኛ እስከ 8ኛ ያለውን ደረጃ ይዘው ለሚያጠናቅቁ አትሌቶችም የገንዘብ ሽልማት እንደሚበረከትላቸው ተገልጿል።
ይህንን ጋዜጣዊ መግለጫ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የውድድርና ተሳትፎ ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ጊዜ አድነው እና አቶ መሐሪ ነጋሽ በጋራ የሰጡት ሲሆን፣ ውድድሩ በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በቀጥታ ስርጭት ለተመልካች እንደሚተላለፍ ታውቋል።
#ethiopianathletics #bahirdar #streetrace #10krun #ethiopiansport #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የመጀመሪያው የኢትዮጵያ 10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር የፊታችን እሁድ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም በባህርዳር ከተማ በደመቀ ሁኔታ እንደሚካሄድ ተነገረ።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በውድድሩ ቅድመ ዝግጅት ስራዎች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው መግለጫ፣ የፌዴሬሽኑ ከፍተኛ የቴክኒክ ባለሙያዎች ወደ ስፍራው በማቅናት አስፈላጊውን ዝግጅት እያከናወኑ እንደሚገኙ አስታውቋል።
ይህ የውድድር መድረክ በዋናነት አዳዲስ ተተኪ አትሌቶችን ለማፍራትና የውድድር እድሎችን ለመፍጠር ያለመ መሆኑም ተገልጿል።
በዚሁ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ላይ የግል ተሳታፊዎችን ጨምሮ ከ6 የተለያዩ ክለቦች የተውጣጡ 91 አትሌቶች እንደሚሳተፉ ታውቋል። በውድድሩ ከ1ኛ እስከ 8ኛ ያለውን ደረጃ ይዘው ለሚያጠናቅቁ አትሌቶችም የገንዘብ ሽልማት እንደሚበረከትላቸው ተገልጿል።
ይህንን ጋዜጣዊ መግለጫ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የውድድርና ተሳትፎ ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ጊዜ አድነው እና አቶ መሐሪ ነጋሽ በጋራ የሰጡት ሲሆን፣ ውድድሩ በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በቀጥታ ስርጭት ለተመልካች እንደሚተላለፍ ታውቋል።
#ethiopianathletics #bahirdar #streetrace #10krun #ethiopiansport #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Sponsored by
Surafel
9 days ago
የካንሰር ታማሚ ህፃናትን ለመደገፍ ያለመ የጎዳና ሩጫና የደም ልገሳ ሊደረግ ነው
#ethiopia | የተስፋ አዲስ ልጆቻቸውን በካንሰር ያጡ ወላጆች እና በጎ ፈቃደኞች፣ ህክምናው ተደራሽ እንዲሆን በማሰብ ከዛሬ 14 ዓመት በፊት የጀመሩት የበጎ አድራጎት ነው። ዋናው ግቡም ልጆቻቸውን ለማሳከም በብዙ የህክምና ውጣ ውረድ ውስጥ ያለፉ ወላጆች፣ ሌሎችም ተመሳሳይ ሁኔታ ውስጥ ያሉትን ለመርዳት በማሰብ ነው። ምንም አይነት ገቢ ወይም ሃብት ያልነበረው ይህ ተስፋ አዲስ፣ በትናንሽ ነገሮች ነበር ጅማሮውን ያደረገው ። ከዚያም ቀስ በቀስ በማደግ፣ አሁን ወደ ሰባት ሆስፒታሎች የበጎ ፍቃድ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
ታዲያ ይህን አገልገሎት ይበልጥ ለማስፋት ይረዳ ዘንድ ፣ "ተስፋ አዲስ" የበጎ አድራጎት ድርጅት ከአራራይ ፕሮሞሽን ጋር በመተባበር የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ሩጫ እና የደም ልገሳ መርሐ ግብር አዘጋጅቷል።
የአራራይ ፕሮሞሽን ስራ አስኪያጅ ፣ ወጣት ክብሮም ሃብቱ (ጆን)፣ የካንሰር ታማሚ ህፃናት ህክምና ብዙ ደም እንደሚጠይቅ ገልፀው፣ ህብረተሰቡ ደም በመለገስ እና በሩጫው በመሳተፍ ለህፃናቱ ተስፋ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበዋል። የፕሮግራሙ ብራንድ አምባሳደር የሆነው ቲክቶከር ቅዱስ አማኑኤልም፣ ተከታዮቹ በዚህ ቅዱስ ዓላማ ላይ ከጎኑ እንዲቆሙ እና ደም በመለገስ ለህፃናቱ እንዲደርሱ ጥሪውን አስተላልፏል።
የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ሩጫው አስተባባሪ እና የአራራይ ፕሮሞሽን ምክትል ስራስካያጅ፣ ወጣት መሃመድ ንጉስ እንደገለፀው፣ ሩጫው የሚካሄደው ሐምሌ 12 /2018 ዓ.ም ሲሆን መነሻው አትላስ አደባባይ ፤በውሃ ልማት አድርጎ መዳረሻውን አትላስ አደባባይ ያደርጋል።
ለሩጫው የሚሆኑ ቲሸርቶች በተስፋ አዲስ የካንሰር ህፃናት ድርጅት ይገኛሉ።
ለበለጠ መረጃ፡
መሐመድ፡ 0920875941
ጆን፡ 0914777751
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የተስፋ አዲስ ልጆቻቸውን በካንሰር ያጡ ወላጆች እና በጎ ፈቃደኞች፣ ህክምናው ተደራሽ እንዲሆን በማሰብ ከዛሬ 14 ዓመት በፊት የጀመሩት የበጎ አድራጎት ነው። ዋናው ግቡም ልጆቻቸውን ለማሳከም በብዙ የህክምና ውጣ ውረድ ውስጥ ያለፉ ወላጆች፣ ሌሎችም ተመሳሳይ ሁኔታ ውስጥ ያሉትን ለመርዳት በማሰብ ነው። ምንም አይነት ገቢ ወይም ሃብት ያልነበረው ይህ ተስፋ አዲስ፣ በትናንሽ ነገሮች ነበር ጅማሮውን ያደረገው ። ከዚያም ቀስ በቀስ በማደግ፣ አሁን ወደ ሰባት ሆስፒታሎች የበጎ ፍቃድ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
ታዲያ ይህን አገልገሎት ይበልጥ ለማስፋት ይረዳ ዘንድ ፣ "ተስፋ አዲስ" የበጎ አድራጎት ድርጅት ከአራራይ ፕሮሞሽን ጋር በመተባበር የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ሩጫ እና የደም ልገሳ መርሐ ግብር አዘጋጅቷል።
የአራራይ ፕሮሞሽን ስራ አስኪያጅ ፣ ወጣት ክብሮም ሃብቱ (ጆን)፣ የካንሰር ታማሚ ህፃናት ህክምና ብዙ ደም እንደሚጠይቅ ገልፀው፣ ህብረተሰቡ ደም በመለገስ እና በሩጫው በመሳተፍ ለህፃናቱ ተስፋ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበዋል። የፕሮግራሙ ብራንድ አምባሳደር የሆነው ቲክቶከር ቅዱስ አማኑኤልም፣ ተከታዮቹ በዚህ ቅዱስ ዓላማ ላይ ከጎኑ እንዲቆሙ እና ደም በመለገስ ለህፃናቱ እንዲደርሱ ጥሪውን አስተላልፏል።
የ5 ኪሎ ሜትር የጎዳና ሩጫው አስተባባሪ እና የአራራይ ፕሮሞሽን ምክትል ስራስካያጅ፣ ወጣት መሃመድ ንጉስ እንደገለፀው፣ ሩጫው የሚካሄደው ሐምሌ 12 /2018 ዓ.ም ሲሆን መነሻው አትላስ አደባባይ ፤በውሃ ልማት አድርጎ መዳረሻውን አትላስ አደባባይ ያደርጋል።
ለሩጫው የሚሆኑ ቲሸርቶች በተስፋ አዲስ የካንሰር ህፃናት ድርጅት ይገኛሉ።
ለበለጠ መረጃ፡
መሐመድ፡ 0920875941
ጆን፡ 0914777751
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
10 days ago
የዓለም ዋንጫ እና አርሲ ሱዴ
ሰዓቱ ምሽት ነው። አየሩ በአርሲ ሱዴ ቀዝቃዛ ንፋስ ታጅቦ በናፍቆት ይሞቃል። ዛሬ ዓለም በሜክሲኮ፣ አሜሪካ እና ካናዳ አስተናጋጅነት ለሚጀመረው የዓለም ዋንጫ በዝግጅት ላይ ሳለች፣ የእኔ ትውስታ ግን ከሃያ ዓመታት በፊት ወደ ነበረችው ኩላ ከተማ ያንገላታኛል።
ያ ዘመን... ቴሌቪዥን በየቤቱ አልነበረም። የኢቲቪ እሁድ መዝናኛን ለመመልከት 50 ሳንቲም በእጅ ይዞ፣ በአንድ ትልቅ ስክሪን ፊት ለፊት ተሰባስቦ የመታየት ጣፋጭ ድካም የነበረበት ዘመን ነበር።
ኩላ፣ ያቺ ትንሽዬ የወረዳ ከተማ፤ ከመኪና ወርደህ "የእከሌ ቤት የት ነው?" ብለህ ብትጠይቅ፣ ከመንገድ ዳር የሚጫወቱት ህፃናት "እኔ ላሳይህ!" ብለው የሚሻሙልህ፣ እያንዳንዱ ነዋሪ የአንዳችንን ማንነት የሚያውቅባት የሞቀች ከተማ። በዚያን ዘመን መብራት የሚባል ነገር አልነበረም። ጨለማውን የሚገፈው የአፍወርቅ እና የዲደዓ ቪዲዮ ቤቶች ጄኔሬተር ድምፅ ብቻ ነበር። ማታ ማታ የውጪ ፊልሞችን፣ በዓል ሲመጣም የኢቲቪን ፕሮግራሞች በነጻም እያስከፈሉ ያሳዩን ነበር። በተለይ የስቅለት ለሊት ቪዲዮ... ያ ድባብ ዛሬም ድረስ በአይኔ ይደቀናል።
የሩጫ ውድድር፣ ዓለም ዋንጫ እና አፍሪካ ዋንጫ ሲመጣ ደግሞ ከተማዋ ትናወጣለች! የአፍወርቅ እና የዲደዓ ቪዲዮ ቤቶች በሰው ተጨናንቀው የትንፋሽ እስራት ይፈጠራል። በስሜት መጮህ፣ በጎል መዝለል፣ በሽንፈት ማዘን... ያ ሁሉ ስሜት የጋራ ነበር። አንዳንድ ጊዜ የተመልካቹ ብዛት ሲበዛ፣ የወረዳው መስተዳደር ጽ/ቤት ጄኔሬተር በማንሳት የራሱን በር ለህዝቡ ይከፍት ነበር። ያኔ፣ በአንድ ስክሪን ፊት የተሰባሰበው የኩላ ወጣት እና ታዳጊ፣ እንደ አንድ ቤተሰብ ነበር የሚሰማው።
ዛሬ ግን ዘመኑ ተቀይሯል። ዓለም ዋንጫው በቴክኖሎጂው ዓለም ተውቦ፣ በእጅ ስልክ ስክሪን እየተመለከትን ነው። ርቀቶች ተሰርዘዋል።
የዛሬይቱ ኩላ ምን ትመስል ይሆን? በየቪዲዮ ቤቱ ትከሻ ለትከሻ ተያይዘን የዓለም ዋንጫን ስንመለከት የነበርን ታዳጊዎች ዛሬ የት ደረስን? ምናልባት አንዳንዶቻችን በአሰላ፣ በአዳማ፣ በአዲስ አበባ፣ አንዳችን በውጪ አገር፣ አንዳችንም በኩላ የልጅነት ትዝታችንን እየናፈቅን በየስልካችን ስንመለከት ይሆን?
ወይ ጊዜ! ያ የጋራ ትዝታ፣ ያ የተሰባሰበ ደስታ ዛሬም በልቤ ውስጥ የከበረ ቦታ አለው። ዛሬ ዓለም ዋንጫ ሲጀመር፣ ከሁሉም በላይ የናፈቀኝ ያ በኩላ ከተማ የነበረው የቡድን መንፈስ እና ያ የዋህ የልጅነት ደስታ ነው።
የት ናችሁ የልጅነት ጓደኞቼ? ያ የኩላ ምሽት፣ ያ የዓለም ዋንጫ ወኔ ዛሬም ትዝ ይላችሁ ይሆን?
ሰዓቱ ምሽት ነው። አየሩ በአርሲ ሱዴ ቀዝቃዛ ንፋስ ታጅቦ በናፍቆት ይሞቃል። ዛሬ ዓለም በሜክሲኮ፣ አሜሪካ እና ካናዳ አስተናጋጅነት ለሚጀመረው የዓለም ዋንጫ በዝግጅት ላይ ሳለች፣ የእኔ ትውስታ ግን ከሃያ ዓመታት በፊት ወደ ነበረችው ኩላ ከተማ ያንገላታኛል።
ያ ዘመን... ቴሌቪዥን በየቤቱ አልነበረም። የኢቲቪ እሁድ መዝናኛን ለመመልከት 50 ሳንቲም በእጅ ይዞ፣ በአንድ ትልቅ ስክሪን ፊት ለፊት ተሰባስቦ የመታየት ጣፋጭ ድካም የነበረበት ዘመን ነበር።
ኩላ፣ ያቺ ትንሽዬ የወረዳ ከተማ፤ ከመኪና ወርደህ "የእከሌ ቤት የት ነው?" ብለህ ብትጠይቅ፣ ከመንገድ ዳር የሚጫወቱት ህፃናት "እኔ ላሳይህ!" ብለው የሚሻሙልህ፣ እያንዳንዱ ነዋሪ የአንዳችንን ማንነት የሚያውቅባት የሞቀች ከተማ። በዚያን ዘመን መብራት የሚባል ነገር አልነበረም። ጨለማውን የሚገፈው የአፍወርቅ እና የዲደዓ ቪዲዮ ቤቶች ጄኔሬተር ድምፅ ብቻ ነበር። ማታ ማታ የውጪ ፊልሞችን፣ በዓል ሲመጣም የኢቲቪን ፕሮግራሞች በነጻም እያስከፈሉ ያሳዩን ነበር። በተለይ የስቅለት ለሊት ቪዲዮ... ያ ድባብ ዛሬም ድረስ በአይኔ ይደቀናል።
የሩጫ ውድድር፣ ዓለም ዋንጫ እና አፍሪካ ዋንጫ ሲመጣ ደግሞ ከተማዋ ትናወጣለች! የአፍወርቅ እና የዲደዓ ቪዲዮ ቤቶች በሰው ተጨናንቀው የትንፋሽ እስራት ይፈጠራል። በስሜት መጮህ፣ በጎል መዝለል፣ በሽንፈት ማዘን... ያ ሁሉ ስሜት የጋራ ነበር። አንዳንድ ጊዜ የተመልካቹ ብዛት ሲበዛ፣ የወረዳው መስተዳደር ጽ/ቤት ጄኔሬተር በማንሳት የራሱን በር ለህዝቡ ይከፍት ነበር። ያኔ፣ በአንድ ስክሪን ፊት የተሰባሰበው የኩላ ወጣት እና ታዳጊ፣ እንደ አንድ ቤተሰብ ነበር የሚሰማው።
ዛሬ ግን ዘመኑ ተቀይሯል። ዓለም ዋንጫው በቴክኖሎጂው ዓለም ተውቦ፣ በእጅ ስልክ ስክሪን እየተመለከትን ነው። ርቀቶች ተሰርዘዋል።
የዛሬይቱ ኩላ ምን ትመስል ይሆን? በየቪዲዮ ቤቱ ትከሻ ለትከሻ ተያይዘን የዓለም ዋንጫን ስንመለከት የነበርን ታዳጊዎች ዛሬ የት ደረስን? ምናልባት አንዳንዶቻችን በአሰላ፣ በአዳማ፣ በአዲስ አበባ፣ አንዳችን በውጪ አገር፣ አንዳችንም በኩላ የልጅነት ትዝታችንን እየናፈቅን በየስልካችን ስንመለከት ይሆን?
ወይ ጊዜ! ያ የጋራ ትዝታ፣ ያ የተሰባሰበ ደስታ ዛሬም በልቤ ውስጥ የከበረ ቦታ አለው። ዛሬ ዓለም ዋንጫ ሲጀመር፣ ከሁሉም በላይ የናፈቀኝ ያ በኩላ ከተማ የነበረው የቡድን መንፈስ እና ያ የዋህ የልጅነት ደስታ ነው።
የት ናችሁ የልጅነት ጓደኞቼ? ያ የኩላ ምሽት፣ ያ የዓለም ዋንጫ ወኔ ዛሬም ትዝ ይላችሁ ይሆን?
11 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት አማኑኤል ማክሮን፣ የግብፅ፣ የሳዑዲ ዓረቢያ፣ የኳታር እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ መሪዎች በሚቀጥለው ሳምንት በፈረንሳይ በሚካሄደው የጂ-7 ጉባኤ ላይ እንደ ክብር እንግድነት እንዲሳተፉ መጋበዛቸውን አስታወቁ።
የዘንድሮው የጂ-7 ጉባኤ ዋነኛ ትኩረት በኢራን እና በምዕራባውያን መካከል ያለውን ውጥረት በድርድር ለመቋጨት በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ያተኩራል ተብሎ ይጠበቃል። በተለይም በሆርሙዝ የባህር ሰላጤ አካባቢ እየተፈጠሩ ያሉ የደህንነት መስተጓጎሎች እና ጥቃቶች፣ በቀጠናው እና በዓለም አቀፍ ኢኮኖሚ ላይ እያደረሱት ያለውን አሉታዊ ተጽዕኖ መሪዎቹ በዝርዝር ይመክሩበታል።
ኤኤፍፒ እንደዘገበው ከሆነ ፕሬዝዳንት ማክሮን በሆርሙዝ አካባቢ የሚስተዋለው የነዳጅ ማጓጓዣ መስተጓጎል የነዳጅ ዋጋ እንዲንር በማድረግ፣ በዓለም አቀፍ ኢኮኖሚ ላይ "ቀጥተኛ እና ከባድ ተጽዕኖ" እየፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል። የነዚህ አራት ታላላቅ የአረብ ሀገራት መሪዎች በጉባኤው መሳተፍ፣ ኢራንን ለማግለል ከሚደረገው ጥረት ባለፈ፣ በቀጠናው የተረጋጋ የነዳጅ አቅርቦት እንዲኖር ለማስቻል የሚደረገውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት የበለጠ ወሳኝ ያደርገዋል።
ይህ ውሳኔ በተለይም ኢራን በክልሉ አገራት ላይ የምታደርሰውን ጥቃት ተከትሎ፣ አረብ ሀገራት ከምዕራባውያን ጋር ያላቸውን የደህንነት ጥምረት ለማጠናከር እየወሰዱት ያለውን እርምጃ በግልጽ የሚያሳይ ነው። የኢራን ጉዳይ በጂ-7 መድረክ ላይ በከፍተኛ ደረጃ መነሳቱ፣ የዓለም ኃያላን አገራት በኢራን ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ያላቸውን ስጋት እና የቀጠናውን ሰላም ለመመለስ የጋራ አቋም ለመያዝ እያደረጉት ያለውን ከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ ሩጫ ያሳያል።
የዘንድሮው የጂ-7 ጉባኤ ዋነኛ ትኩረት በኢራን እና በምዕራባውያን መካከል ያለውን ውጥረት በድርድር ለመቋጨት በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ያተኩራል ተብሎ ይጠበቃል። በተለይም በሆርሙዝ የባህር ሰላጤ አካባቢ እየተፈጠሩ ያሉ የደህንነት መስተጓጎሎች እና ጥቃቶች፣ በቀጠናው እና በዓለም አቀፍ ኢኮኖሚ ላይ እያደረሱት ያለውን አሉታዊ ተጽዕኖ መሪዎቹ በዝርዝር ይመክሩበታል።
ኤኤፍፒ እንደዘገበው ከሆነ ፕሬዝዳንት ማክሮን በሆርሙዝ አካባቢ የሚስተዋለው የነዳጅ ማጓጓዣ መስተጓጎል የነዳጅ ዋጋ እንዲንር በማድረግ፣ በዓለም አቀፍ ኢኮኖሚ ላይ "ቀጥተኛ እና ከባድ ተጽዕኖ" እየፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል። የነዚህ አራት ታላላቅ የአረብ ሀገራት መሪዎች በጉባኤው መሳተፍ፣ ኢራንን ለማግለል ከሚደረገው ጥረት ባለፈ፣ በቀጠናው የተረጋጋ የነዳጅ አቅርቦት እንዲኖር ለማስቻል የሚደረገውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት የበለጠ ወሳኝ ያደርገዋል።
ይህ ውሳኔ በተለይም ኢራን በክልሉ አገራት ላይ የምታደርሰውን ጥቃት ተከትሎ፣ አረብ ሀገራት ከምዕራባውያን ጋር ያላቸውን የደህንነት ጥምረት ለማጠናከር እየወሰዱት ያለውን እርምጃ በግልጽ የሚያሳይ ነው። የኢራን ጉዳይ በጂ-7 መድረክ ላይ በከፍተኛ ደረጃ መነሳቱ፣ የዓለም ኃያላን አገራት በኢራን ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ያላቸውን ስጋት እና የቀጠናውን ሰላም ለመመለስ የጋራ አቋም ለመያዝ እያደረጉት ያለውን ከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ ሩጫ ያሳያል።
14 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በአሁኑ ወቅት በትንሿ አርሜኒያ ዙሪያ ዓለም አቀፋዊ ይዘት ያለው እጅግ ግዙፍ የጂኦፖለቲካዊ ማዕበል እያንዣበበ ይገኛል። በዚህ ማዕበል ውስጥ የአርሜኒያ ከሩሲያ፣ ከአውሮፓ፣ እና ከአሜሪካ ጋር ያላት ግንኙነት ብቻ ሳይሆን፣ ከቅርብ ጎረቤቶቿ ከሆኑት ከኢራን፣ ከአዘርባጃን እና ከቱርክ ጋር ያላት የወደፊት እጣ ፈንታም ከፍተኛ ፈተና ውስጥ ወድቋል።
ዛሬ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ትኩረት ያረፈው በቅርቡ በአርሜኒያ እና በአሜሪካ መካከል በተፈረሙት የመግባቢያ ሰነዶች ላይ ነው። እነዚህ ሰነዶች እንደተለመዱት የዲፕሎማሲያዊ የዕለት ተዕለት ስምምነቶች የሚታለፉ አይደሉም። የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ የፊርማ ስነ-ስርዓቱን ለመታደም በአካል ወደ አርሜኒያ መጓዛቸው፣ ጉዳዩ ለአሜሪካ መንግስት ምን ያህል ከፍተኛ ስትራቴጂካዊ ክብደት እንዳለው በግልጽ ያሳያል። የደቡብ ካውካሰስ፣ የመካከለኛው እስያ፣ የፋርስ ባሕረ ሰላጤ፣ እንዲሁም የአውሮፓ ህብረት፣ እስራኤል እና ቱርክ ከፍተኛ ተጽዕኖ የሚፈጥሩበት የምስራቃዊ ሜዲትራኒያን ቀጠና ውስብስብ ታሪካዊ እና ወቅታዊ ክስተቶች ቀስ በቀስ አዲስ መልክ እየያዙ ነው።
በዚህ ሰፊ ቀጠና ውስጥ ተበታትነው የሚገኙ ስትራቴጂካዊ የማዕድን እና የትራንስፖርት መስመሮች በድጋሚ የዓለም ኃያላን ትኩረት ማዕከል ሆነዋል። ከእነዚህም መካከል በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀሰው የአርሜኒያዋ የሲዩኒክ ግዛት ናት። ይህች ግዛት ከሞሊብዲነም እና ዩራኒየም አንስቶ እስከ ወርቅ የሚደርሱ እጅግ ውድ እና ወሳኝ የሆኑ የማዕድን ክምችቶች መገኛ ናት። ይህ ሀብት ከሶቪየት ህብረት ዘመን ጀምሮ የሚታወቅ ቢሆንም፣ ዛሬ ላይ የፈጠረው መነቃቃት ግን የተለየ ነው።
በአሁኑ የከፍተኛ ወታደራዊ ውድድር እና የመከላከያ ኢንዱስትሪ መስፋፋት ዘመን፣ ሀገራት ከሴሚኮንዳክተሮች ከብርቅዬ የምድር ማዕድናት እና ለመከላከያ ኢንዱስትሪ ወሳኝ ከሆኑ ጥሬ እቃዎች ጋር የተያያዘ ማንኛውንም ሀብት ለመቆጣጠር በከፍተኛ ሩጫ ላይ ይገኛሉ። መንግስታት ቀጣዩን ትውልድ ስትራቴጂካዊ ኢንዱስትሪዎች የሚያንቀሳቅሱ ሀብቶች ላይ የበላይነት ለማግኘት ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ነው። ከዚህ በተጨማሪም አሁን እየተካሄደ ያለውን የዓለም አቀፍ የኢነርጂ ስርዓቶች ሽግግር ስንመለከት፣ አርሜኒያ ለእነዚህ የቴክኖሎጂ ሽግግሮች መሠረት የሆኑ በርካታ ወሳኝ ማዕድናት ምንጭ ሆና ብቅ ብላለች።
የሲዩኒክ ግዛት ከሶቪየት ዘመን ጀምሮ በእነዚህ ሀብቶቿ ትታወቃለች። ክልሉ በማዕድን ማውጫዎች፣ በክፍት የማዕድን ቁፋሮዎች እና በማቀነባበሪያ ፋሲሊቲዎች የተሞላ ነው። በታሪክ እነዚህ ሀብቶች በኢራን ድንበር እና በአራስ ወንዝ ዳርቻ በሚያልፍ የባቡር መስመር አማካኝነት ከሰፊው የሶቪየት ትራንስፖርት አውታር ጋር የተገናኙ ነበሩ። ዛሬ ላይ "የዛንጌዙር ኮሪደር" ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ከምንጊዜውም በላይ የጎላውም በዚሁ ምክንያት ነው።
ከዚህ ቀጠና በቅርብ ርቀት የሚገኘው እና ከ1952 ጀምሮ ስራ ላይ ያለው የዛንጌዙር የመዳብ እና የሞሊብዲነም ማቀነባበሪያ፣ እንዲሁም በሰሜን በኩል የሚገኘው የአጋራክ ማቀነባበሪያ እስከ ዛሬም ሙሉ በሙሉ አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ። የከፍተኛ ጂኦፖለቲካዊ እና ስትራቴጂካዊ ሎጂስቲክስ እይታን ስንመረምር፣ ከአስርት ዓመታት በፊት ፈርሶ አሁን ዳግም እየተገነባ ያለው የ43 ኪሎ ሜትር የባቡር መስመር፣ ከዓለም የሞሊብዲነም ክምችት ውስጥ ሰባት በመቶ ወደሚሆነው ሀብት የሚያደርስ ቁልፍ በር ነው። ሞሊብዲነም ለሚሳኤል ምርት፣ ለኑክሌር ኢነርጂ እና ለሴሚኮንዳክተር ማምረቻ እጅግ አስፈላጊ የሆነ ማዕድን ነው። ይህ ባይሆን ኖሮ፣ ዋሽንግተን ከ35 ዓመታት በፊት ለፈረሰ አጭር የባቡር መስመር ይህን ያህል ከፍተኛ ትኩረት የምትሰጥበት ምንም ዓይነት ሎጂካዊ ምክንያት አይኖርም ነበር።
የካስፒያንን ቀጠና ከቱርክ ጋር የሚያገናኘው ይህ የባቡር መስመር ለዩናይትድ ስቴትስ የነበረው ስትራቴጂካዊ ፋይዳ ውስን ነበር። አሁን የተለወጠው መንገዱ ራሱ ሳይሆን፣ ሊያጓጓዘው የሚችለው የካርጎ (ጭነት) ዓይነት ነው። የእነዚህ ማዕድናት ተፈጥሮ እና እሴት የመስመሩን አስፈላጊነት በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል። በዚህ የማዕድን ቀጠና ላይ ያለውን ተጽዕኖ የማጣት አደጋ ለአሜሪካ መንግስት እጅግ ግልጽ በመሆኑ፣ የትራምፕ አስተዳደር በክልሉ ከሚመረቱ የኢንዱስትሪ ውጤቶች ላይ የራሱን ድርሻ ለማረጋገጥ ፈጣን እንቅስቃሴ አድርጓል። በዚህም "የትራምፕ የሰላም እና የብልጽግና መስመር" የሚባለው ጽንሰ-ሀሳብ ብቅ ብሏል። በዛሬው ሁከት በበዛበት ዓለም፣ የዩራኒየም እና የሞሊብዲነም ተደራሽነት ከሌለ ሰላም እና ብልጽግና ብቻውን ትርጉም አልባ ነው።
በአሜሪካ እና በአርሜኒያ የመግባቢያ ሰነድ ውስጥ "የወጪ ንግድ ቁጥጥሮች" የሚለው ሐረግ በተደጋጋሚ ተጠቅሷል። የወጪ ንግድ ቁጥጥሮች ከሴሚኮንዳክተሮች ጋር አብረው በሚነሱበት በማንኛውም ጊዜ፣ ውይይቱ ወዲያውኑ ለሲቪልም ሆነ ለወታደራዊ አገልግሎት ወደሚውሉ ቴክኖሎጂዎች እና ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ወዳላቸው ማዕድናት መዞሩ አይቀርም።
ይህ በአርሜኒያ እየተካሄደ ያለው የአሜሪካ የጂኦፖለቲካዊ እርምጃ፣ እስራኤል ለዓመታት በዚሁ የካውካሰስ ቀጠና፣ በተለይም በአዘርባጃን ላይ ስትከተለው ከነበረው ስትራቴጂ ጋር እጅግ ተመሳሳይነት አለው። እስራኤል በአርሜኒያ የረጅም ጊዜ ባላንጣ በሆነችው አዘርባጃን ላይ ያላት ተጽዕኖ በዘመናዊው የጂኦፖለቲካ ታሪክ ውስጥ እጅግ ስኬታማ ከሚባሉ የጥቅም ልውውጦች አንዱ ነው።
እስራኤል ለአዘርባጃን እጅግ ዘመናዊ የሆኑ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን፣ የአየር መከላከያ ስርዓቶችን እና ሌሎች የጦር መሳሪያዎችን በስፋት ታቀርባለች። እነዚህ መሳሪያዎች አዘርባጃን በናጎርኖ-ካራባክ ጦርነት ላይ በአርሜኒያ ላይ የበላይነት እንድትቀዳጅ ትልቁን ሚና ተጫውተዋል። በምላሹ ደግሞ፣ እስራኤል ከጠቅላላ የነዳጅ ፍጆታዋ ውስጥ 40 በመቶ የሚሆነውን ከአዘርባጃን ታገኛለች። ሆኖም ከነዳጅ በላይ ለእስራኤል ወሳኝ የሆነው የጂኦፖለቲካዊ ትርፍ፣ አዘርባጃን ከኢራን ጋር ያላትን ሰፊ ድንበር ተጠቅማ በኢራን ላይ የምታደርገውን የስለላ እና የወታደራዊ ክትትል አቅም ማሳደጓ ነው።
ልክ አሜሪካ አሁን አርሜኒያን ተጠቅማ በኢራን ሰሜናዊ ድንበር ላይ ስትራቴጂካዊ የኢኮኖሚ እና የወታደራዊ ተጽዕኖ ለመፍጠር እንደምትሞክረው ሁሉ፣ እስራኤል አዘርባጃንን እንደ መከላከያ ግድግዳ እና እንደ መረጃ መሰብሰቢያ ማዕከል ስትጠቀምባት ቆይታለች። ከዚህም በተጨማሪ፣ እስራኤል በመካከለኛው ምስራቅ አሜሪካን በማስተባበር ለመገንባት ያቀደችው የህንድ-መካከለኛው ምስራቅ-አውሮፓ የኢኮኖሚ ኮሪደር የንግድ መስመር፣ ልክ እንደ ዛንጌዙር ኮሪደር ሁሉ የትራንስፖርት መስመርን ከጂኦፖለቲካዊ የጸጥታ ዋስትና እና የሀብት ቁጥጥር ጋር የማስተሳሰር ስትራቴጂ ነው። የዓለም ኃያላን እና እንደ እስራኤል ያሉ ቀጠናዊ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የትራንስፖርት ኮሪደሮችን እና የማዕድን ክምችቶችን ጠላቶቻቸውን ለመክበብ እና ብሔራዊ ደህንነታቸውን ለማረጋገጥ እንዴት እንደሚጠቀሙበት ይህ ግልጽ ማሳያ ነው።
ለዓመታት በአርሜኒያ እና አዘርባጃን መካከል የነበረው ውጥረት በክልሉ ሰፊ የአሜሪካ የጸጥታ ስትራቴጂ እንዳይዘረጋ እንቅፋት ሆኖ ቆይቷል። አሁን ግን ሁለቱም ሀገራት በኢራን ድንበር ላይ ያለውን ሁኔታ በአንድ የጋራ መነጽር መመልከት ግድ ብሏቸዋል። በአሜሪካ አደራዳሪነት በተፈጠረው ማዕቀፍ ውስጥ በተግባር በአንድ ጀልባ ላይ ተሳፍረዋል።
የማዕድን ሀብቶቹ ባለቤትነት በመጨረሻ የአሜሪካ ወይም የአውሮፓ ኩባንያዎች ሊሆን ይችላል። ነገር ግን አውሮፓ በደቡብ ካውካሰስ ሎጂስቲክስ ላይ ያላት ፍላጎት አሜሪካ በዩራኒየም እና ሞሊብዲነም ላይ ካላት ፍላጎት ያነሰ አይደለም። የአርሜኒያን ጥሬ እቃዎች የሚያቀነባብሩ ፋሲሊቲዎች እንደ ሎጂስቲክሱ አቅጣጫ ሊዘዋወሩ ይችላሉ፣ ነገር ግን በራሱ በማዕድን መሰረቱ ላይ ያለው ቁጥጥር ከአሜሪካ ተሳትፎ ጋር በጥብቅ የተቆራኘ ሆኖ ይቀጥላል። ይሄው እውነታ በኢነርጂ መሠረተ ልማት እና በግዙፍ የመረጃ ስርዓቶችም ላይ ይሰራል።
አርሜኒያ በአሁኑ ወቅት እንደ አሜሪካ፣ ፈረንሳይ እና ሩሲያ ባሉ ጥቂት ሀገራት ብቻ በበላይነት የተያዘውን አነስተኛ የሞዱላር ኑክሌር ሪአክተሮች ግንባታ ለማካሄድ በንቃት እየተወያየች ትገኛለች። በተመሳሳይ ጊዜ ከአሮጌዋ አጋሯ ከሩሲያ ጋር ያላት ግንኙነት በፍጥነት እያሽቆለቆለ ነው። የዛንጌዙር ኮሪደር ወደ ቱርክ ከሚዘልቁ የትራንስፖርት አውታሮች ጋር መገናኘቱ አይቀሬ ሲሆን፣ አርሜኒያ ከባቡር መስመሩ ጎን ለጎን የሚጓዝ አዲስ አውራ ጎዳና ለማገንባት አቅዳለች። አውሮፓ ደቡብ ካውካሰስን እንደ መሸጋገሪያ መስመር እና እንደ ወሳኝ ጥሬ ዕቃዎች ምንጭ አድርጋ ለመጠቀም ከፍተኛ ጉጉት አላት።
በዋሽንግተን እና በቴህራን መካከል ሊኖር ከሚችለው መግባባት አኳያ ሲታይ፣ ኢራን የአርሜኒያ ዩራኒየም እና ሞሊብዲነም ለአሜሪካ እና ለአውሮፓ ህብረት ያላቸውን ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ሙሉ በሙሉ ተገንዝባለች። ግምገማው ትክክል ከሆነ፣ በፋርስ ባሕረ ሰላጤ አካባቢ የተፈጠረው ግጭት ውሎ አድሮ ሊረግብ እንደሚችል ተስፋ ለማድረግ የሚያስችል በቂ ምክንያት ሊኖር ይችላል። ግጭቱ የሚቀጥል ከሆነ ግን፣ ዩናይትድ ስቴትስ በሲዩኒክ እና በአካባቢው ግዛቶች ላይ ወታደራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ምሽግ ለመመስረት፣ እንዲሁም ይህን ቀጠና የዋሽንግተን የዩራሲያ ተጽዕኖ ማዕከል ለማድረግ የምታደርገው ጥረት እጅግ አስቸጋሪ ይሆናል። ይህ ሁሉ የሚሆነው ግን በድርድር የሚመጣ መፍትሄ አሁንም የሚቻል ከሆነ ብቻ ነው።
በትንሿ አርሜኒያ ላይ እየተደረገ ያለው የጂኦፖለቲካዊ ቁማር ዋጋ ከዚህ በላይ ሊጨምር የማይችልበት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል።
የዓለም ኃያላን ሀገራት በታዳጊ እና ትናንሽ ሀገራት ላይ ያላቸውን የጂኦፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ተጽዕኖ በተመለከተ፣ ከዚህ ጽሁፍ በመነሳት የትኛው የኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ ሀብት ወይም የትራንስፖርት ኮሪደር አወቃቀር ወደፊት ተመሳሳይ ዓለም አቀፋዊ የፉክክር ማዕከል ሊሆን ይችላል ብለው ያስባሉ?
ዛሬ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ትኩረት ያረፈው በቅርቡ በአርሜኒያ እና በአሜሪካ መካከል በተፈረሙት የመግባቢያ ሰነዶች ላይ ነው። እነዚህ ሰነዶች እንደተለመዱት የዲፕሎማሲያዊ የዕለት ተዕለት ስምምነቶች የሚታለፉ አይደሉም። የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ የፊርማ ስነ-ስርዓቱን ለመታደም በአካል ወደ አርሜኒያ መጓዛቸው፣ ጉዳዩ ለአሜሪካ መንግስት ምን ያህል ከፍተኛ ስትራቴጂካዊ ክብደት እንዳለው በግልጽ ያሳያል። የደቡብ ካውካሰስ፣ የመካከለኛው እስያ፣ የፋርስ ባሕረ ሰላጤ፣ እንዲሁም የአውሮፓ ህብረት፣ እስራኤል እና ቱርክ ከፍተኛ ተጽዕኖ የሚፈጥሩበት የምስራቃዊ ሜዲትራኒያን ቀጠና ውስብስብ ታሪካዊ እና ወቅታዊ ክስተቶች ቀስ በቀስ አዲስ መልክ እየያዙ ነው።
በዚህ ሰፊ ቀጠና ውስጥ ተበታትነው የሚገኙ ስትራቴጂካዊ የማዕድን እና የትራንስፖርት መስመሮች በድጋሚ የዓለም ኃያላን ትኩረት ማዕከል ሆነዋል። ከእነዚህም መካከል በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀሰው የአርሜኒያዋ የሲዩኒክ ግዛት ናት። ይህች ግዛት ከሞሊብዲነም እና ዩራኒየም አንስቶ እስከ ወርቅ የሚደርሱ እጅግ ውድ እና ወሳኝ የሆኑ የማዕድን ክምችቶች መገኛ ናት። ይህ ሀብት ከሶቪየት ህብረት ዘመን ጀምሮ የሚታወቅ ቢሆንም፣ ዛሬ ላይ የፈጠረው መነቃቃት ግን የተለየ ነው።
በአሁኑ የከፍተኛ ወታደራዊ ውድድር እና የመከላከያ ኢንዱስትሪ መስፋፋት ዘመን፣ ሀገራት ከሴሚኮንዳክተሮች ከብርቅዬ የምድር ማዕድናት እና ለመከላከያ ኢንዱስትሪ ወሳኝ ከሆኑ ጥሬ እቃዎች ጋር የተያያዘ ማንኛውንም ሀብት ለመቆጣጠር በከፍተኛ ሩጫ ላይ ይገኛሉ። መንግስታት ቀጣዩን ትውልድ ስትራቴጂካዊ ኢንዱስትሪዎች የሚያንቀሳቅሱ ሀብቶች ላይ የበላይነት ለማግኘት ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ነው። ከዚህ በተጨማሪም አሁን እየተካሄደ ያለውን የዓለም አቀፍ የኢነርጂ ስርዓቶች ሽግግር ስንመለከት፣ አርሜኒያ ለእነዚህ የቴክኖሎጂ ሽግግሮች መሠረት የሆኑ በርካታ ወሳኝ ማዕድናት ምንጭ ሆና ብቅ ብላለች።
የሲዩኒክ ግዛት ከሶቪየት ዘመን ጀምሮ በእነዚህ ሀብቶቿ ትታወቃለች። ክልሉ በማዕድን ማውጫዎች፣ በክፍት የማዕድን ቁፋሮዎች እና በማቀነባበሪያ ፋሲሊቲዎች የተሞላ ነው። በታሪክ እነዚህ ሀብቶች በኢራን ድንበር እና በአራስ ወንዝ ዳርቻ በሚያልፍ የባቡር መስመር አማካኝነት ከሰፊው የሶቪየት ትራንስፖርት አውታር ጋር የተገናኙ ነበሩ። ዛሬ ላይ "የዛንጌዙር ኮሪደር" ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ከምንጊዜውም በላይ የጎላውም በዚሁ ምክንያት ነው።
ከዚህ ቀጠና በቅርብ ርቀት የሚገኘው እና ከ1952 ጀምሮ ስራ ላይ ያለው የዛንጌዙር የመዳብ እና የሞሊብዲነም ማቀነባበሪያ፣ እንዲሁም በሰሜን በኩል የሚገኘው የአጋራክ ማቀነባበሪያ እስከ ዛሬም ሙሉ በሙሉ አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ። የከፍተኛ ጂኦፖለቲካዊ እና ስትራቴጂካዊ ሎጂስቲክስ እይታን ስንመረምር፣ ከአስርት ዓመታት በፊት ፈርሶ አሁን ዳግም እየተገነባ ያለው የ43 ኪሎ ሜትር የባቡር መስመር፣ ከዓለም የሞሊብዲነም ክምችት ውስጥ ሰባት በመቶ ወደሚሆነው ሀብት የሚያደርስ ቁልፍ በር ነው። ሞሊብዲነም ለሚሳኤል ምርት፣ ለኑክሌር ኢነርጂ እና ለሴሚኮንዳክተር ማምረቻ እጅግ አስፈላጊ የሆነ ማዕድን ነው። ይህ ባይሆን ኖሮ፣ ዋሽንግተን ከ35 ዓመታት በፊት ለፈረሰ አጭር የባቡር መስመር ይህን ያህል ከፍተኛ ትኩረት የምትሰጥበት ምንም ዓይነት ሎጂካዊ ምክንያት አይኖርም ነበር።
የካስፒያንን ቀጠና ከቱርክ ጋር የሚያገናኘው ይህ የባቡር መስመር ለዩናይትድ ስቴትስ የነበረው ስትራቴጂካዊ ፋይዳ ውስን ነበር። አሁን የተለወጠው መንገዱ ራሱ ሳይሆን፣ ሊያጓጓዘው የሚችለው የካርጎ (ጭነት) ዓይነት ነው። የእነዚህ ማዕድናት ተፈጥሮ እና እሴት የመስመሩን አስፈላጊነት በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል። በዚህ የማዕድን ቀጠና ላይ ያለውን ተጽዕኖ የማጣት አደጋ ለአሜሪካ መንግስት እጅግ ግልጽ በመሆኑ፣ የትራምፕ አስተዳደር በክልሉ ከሚመረቱ የኢንዱስትሪ ውጤቶች ላይ የራሱን ድርሻ ለማረጋገጥ ፈጣን እንቅስቃሴ አድርጓል። በዚህም "የትራምፕ የሰላም እና የብልጽግና መስመር" የሚባለው ጽንሰ-ሀሳብ ብቅ ብሏል። በዛሬው ሁከት በበዛበት ዓለም፣ የዩራኒየም እና የሞሊብዲነም ተደራሽነት ከሌለ ሰላም እና ብልጽግና ብቻውን ትርጉም አልባ ነው።
በአሜሪካ እና በአርሜኒያ የመግባቢያ ሰነድ ውስጥ "የወጪ ንግድ ቁጥጥሮች" የሚለው ሐረግ በተደጋጋሚ ተጠቅሷል። የወጪ ንግድ ቁጥጥሮች ከሴሚኮንዳክተሮች ጋር አብረው በሚነሱበት በማንኛውም ጊዜ፣ ውይይቱ ወዲያውኑ ለሲቪልም ሆነ ለወታደራዊ አገልግሎት ወደሚውሉ ቴክኖሎጂዎች እና ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ወዳላቸው ማዕድናት መዞሩ አይቀርም።
ይህ በአርሜኒያ እየተካሄደ ያለው የአሜሪካ የጂኦፖለቲካዊ እርምጃ፣ እስራኤል ለዓመታት በዚሁ የካውካሰስ ቀጠና፣ በተለይም በአዘርባጃን ላይ ስትከተለው ከነበረው ስትራቴጂ ጋር እጅግ ተመሳሳይነት አለው። እስራኤል በአርሜኒያ የረጅም ጊዜ ባላንጣ በሆነችው አዘርባጃን ላይ ያላት ተጽዕኖ በዘመናዊው የጂኦፖለቲካ ታሪክ ውስጥ እጅግ ስኬታማ ከሚባሉ የጥቅም ልውውጦች አንዱ ነው።
እስራኤል ለአዘርባጃን እጅግ ዘመናዊ የሆኑ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን፣ የአየር መከላከያ ስርዓቶችን እና ሌሎች የጦር መሳሪያዎችን በስፋት ታቀርባለች። እነዚህ መሳሪያዎች አዘርባጃን በናጎርኖ-ካራባክ ጦርነት ላይ በአርሜኒያ ላይ የበላይነት እንድትቀዳጅ ትልቁን ሚና ተጫውተዋል። በምላሹ ደግሞ፣ እስራኤል ከጠቅላላ የነዳጅ ፍጆታዋ ውስጥ 40 በመቶ የሚሆነውን ከአዘርባጃን ታገኛለች። ሆኖም ከነዳጅ በላይ ለእስራኤል ወሳኝ የሆነው የጂኦፖለቲካዊ ትርፍ፣ አዘርባጃን ከኢራን ጋር ያላትን ሰፊ ድንበር ተጠቅማ በኢራን ላይ የምታደርገውን የስለላ እና የወታደራዊ ክትትል አቅም ማሳደጓ ነው።
ልክ አሜሪካ አሁን አርሜኒያን ተጠቅማ በኢራን ሰሜናዊ ድንበር ላይ ስትራቴጂካዊ የኢኮኖሚ እና የወታደራዊ ተጽዕኖ ለመፍጠር እንደምትሞክረው ሁሉ፣ እስራኤል አዘርባጃንን እንደ መከላከያ ግድግዳ እና እንደ መረጃ መሰብሰቢያ ማዕከል ስትጠቀምባት ቆይታለች። ከዚህም በተጨማሪ፣ እስራኤል በመካከለኛው ምስራቅ አሜሪካን በማስተባበር ለመገንባት ያቀደችው የህንድ-መካከለኛው ምስራቅ-አውሮፓ የኢኮኖሚ ኮሪደር የንግድ መስመር፣ ልክ እንደ ዛንጌዙር ኮሪደር ሁሉ የትራንስፖርት መስመርን ከጂኦፖለቲካዊ የጸጥታ ዋስትና እና የሀብት ቁጥጥር ጋር የማስተሳሰር ስትራቴጂ ነው። የዓለም ኃያላን እና እንደ እስራኤል ያሉ ቀጠናዊ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የትራንስፖርት ኮሪደሮችን እና የማዕድን ክምችቶችን ጠላቶቻቸውን ለመክበብ እና ብሔራዊ ደህንነታቸውን ለማረጋገጥ እንዴት እንደሚጠቀሙበት ይህ ግልጽ ማሳያ ነው።
ለዓመታት በአርሜኒያ እና አዘርባጃን መካከል የነበረው ውጥረት በክልሉ ሰፊ የአሜሪካ የጸጥታ ስትራቴጂ እንዳይዘረጋ እንቅፋት ሆኖ ቆይቷል። አሁን ግን ሁለቱም ሀገራት በኢራን ድንበር ላይ ያለውን ሁኔታ በአንድ የጋራ መነጽር መመልከት ግድ ብሏቸዋል። በአሜሪካ አደራዳሪነት በተፈጠረው ማዕቀፍ ውስጥ በተግባር በአንድ ጀልባ ላይ ተሳፍረዋል።
የማዕድን ሀብቶቹ ባለቤትነት በመጨረሻ የአሜሪካ ወይም የአውሮፓ ኩባንያዎች ሊሆን ይችላል። ነገር ግን አውሮፓ በደቡብ ካውካሰስ ሎጂስቲክስ ላይ ያላት ፍላጎት አሜሪካ በዩራኒየም እና ሞሊብዲነም ላይ ካላት ፍላጎት ያነሰ አይደለም። የአርሜኒያን ጥሬ እቃዎች የሚያቀነባብሩ ፋሲሊቲዎች እንደ ሎጂስቲክሱ አቅጣጫ ሊዘዋወሩ ይችላሉ፣ ነገር ግን በራሱ በማዕድን መሰረቱ ላይ ያለው ቁጥጥር ከአሜሪካ ተሳትፎ ጋር በጥብቅ የተቆራኘ ሆኖ ይቀጥላል። ይሄው እውነታ በኢነርጂ መሠረተ ልማት እና በግዙፍ የመረጃ ስርዓቶችም ላይ ይሰራል።
አርሜኒያ በአሁኑ ወቅት እንደ አሜሪካ፣ ፈረንሳይ እና ሩሲያ ባሉ ጥቂት ሀገራት ብቻ በበላይነት የተያዘውን አነስተኛ የሞዱላር ኑክሌር ሪአክተሮች ግንባታ ለማካሄድ በንቃት እየተወያየች ትገኛለች። በተመሳሳይ ጊዜ ከአሮጌዋ አጋሯ ከሩሲያ ጋር ያላት ግንኙነት በፍጥነት እያሽቆለቆለ ነው። የዛንጌዙር ኮሪደር ወደ ቱርክ ከሚዘልቁ የትራንስፖርት አውታሮች ጋር መገናኘቱ አይቀሬ ሲሆን፣ አርሜኒያ ከባቡር መስመሩ ጎን ለጎን የሚጓዝ አዲስ አውራ ጎዳና ለማገንባት አቅዳለች። አውሮፓ ደቡብ ካውካሰስን እንደ መሸጋገሪያ መስመር እና እንደ ወሳኝ ጥሬ ዕቃዎች ምንጭ አድርጋ ለመጠቀም ከፍተኛ ጉጉት አላት።
በዋሽንግተን እና በቴህራን መካከል ሊኖር ከሚችለው መግባባት አኳያ ሲታይ፣ ኢራን የአርሜኒያ ዩራኒየም እና ሞሊብዲነም ለአሜሪካ እና ለአውሮፓ ህብረት ያላቸውን ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ሙሉ በሙሉ ተገንዝባለች። ግምገማው ትክክል ከሆነ፣ በፋርስ ባሕረ ሰላጤ አካባቢ የተፈጠረው ግጭት ውሎ አድሮ ሊረግብ እንደሚችል ተስፋ ለማድረግ የሚያስችል በቂ ምክንያት ሊኖር ይችላል። ግጭቱ የሚቀጥል ከሆነ ግን፣ ዩናይትድ ስቴትስ በሲዩኒክ እና በአካባቢው ግዛቶች ላይ ወታደራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ምሽግ ለመመስረት፣ እንዲሁም ይህን ቀጠና የዋሽንግተን የዩራሲያ ተጽዕኖ ማዕከል ለማድረግ የምታደርገው ጥረት እጅግ አስቸጋሪ ይሆናል። ይህ ሁሉ የሚሆነው ግን በድርድር የሚመጣ መፍትሄ አሁንም የሚቻል ከሆነ ብቻ ነው።
በትንሿ አርሜኒያ ላይ እየተደረገ ያለው የጂኦፖለቲካዊ ቁማር ዋጋ ከዚህ በላይ ሊጨምር የማይችልበት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል።
የዓለም ኃያላን ሀገራት በታዳጊ እና ትናንሽ ሀገራት ላይ ያላቸውን የጂኦፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ተጽዕኖ በተመለከተ፣ ከዚህ ጽሁፍ በመነሳት የትኛው የኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ ሀብት ወይም የትራንስፖርት ኮሪደር አወቃቀር ወደፊት ተመሳሳይ ዓለም አቀፋዊ የፉክክር ማዕከል ሊሆን ይችላል ብለው ያስባሉ?
15 days ago
የኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል በሮምና ሞስኮ...
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሳምንቱ በሮም እና በሞስኮ በተካሄዱ ውድድሮች ላይ በበላይነት አጠናቅቀዋል።
በሩሲያ ሞስኮ በተካሄደውና በዓለም አትሌቲክስ የኤፍ ደረጃ በተሰጠው የ2026 የዝናሜንስኪ ወንድማማቾች መታሰቢያ የአትሌቲክስ ውድድር የኢትዮጵያ አትሌቶች የበላይነት በመያዝ ውድድሩን በታላቅ ድል ማጠናቀቅ ችለዋል።
በሴቶች የ1 ሺህ 500 ሜትር ውድድር አትሌት ብርቄ ኃይሎም 1ኛ በመሆን ማጠናቀቅ ስትችል÷ አትሌት ሳሮን በርሃ ደግሞ 2ኛ ደረጃን ይዛለች።
አትሌት ደስታ ታደለ 5ኛ፣ አትሌት ሲፈን ዳገታ 8ኛ ፣ አትሌት በሻቱ ጌታ 9ኛ እና አትሌት ቤተልሔም ሙላት 15ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቅቀዋል።
የሴቶች 10 ሺህ ሜትር ውድድር አትሌት ፈንታዬ ጫኔ በአንደኝነት ስታሸንፍ÷ አትሌት ቤተልሔም ኦላና 2ኛ ወጥታለች።
አትሌት ሰላማዊት ሻምበል 4ኛ እንዲሁም አትሌት ትርንጎ ታዳለ 6ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቅቀዋል።
በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል አትሌት ብርቱካን ገዳሙ ፈጣን ፉክክር በተደረገበት የሩጫ መድረክ ርቀቱን 2ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቅቃለች።
በ800 ሜትር አትሌት ሀብታም ገበየሁ 6ኛ ደረጃን መያዝ ችላለች።
በወንዶች የ10 ሺህ ሜትር ውድድር ላይ አትሌት እዮብ ስመኝ በበላይነት ጨርሷል፡፡
በዚሁ ውድድር ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ሽመልስ ንጉሴ 3ኛ ደረጃን በመያዝ ፈፅሟል።
የወንዶች 3 ሺህ ሜትር መሰናክል አትሌት ዲንቃ ፍቃዱ 1ኛ በመሆን ሲያሸንፍ÷ አትሌት ሂርኮ ኃይሉ 3ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቅቋል።
የ2026 ዳይመንድ ሊግ 4ኛ መዳረሻ በሆነው የሮሙ የሴቶች 5 ሺህ ሜትር ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የመጀመሪያዎቹን ሰባት ደረጃዎች በመቆጣጠር ጨርሰዋል፡፡
አትሌት ልቅና አምባው 14፡18፡41 የሆነ የወቅቱን ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ ባለድል ሆናለች።
FBC
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሳምንቱ በሮም እና በሞስኮ በተካሄዱ ውድድሮች ላይ በበላይነት አጠናቅቀዋል።
በሩሲያ ሞስኮ በተካሄደውና በዓለም አትሌቲክስ የኤፍ ደረጃ በተሰጠው የ2026 የዝናሜንስኪ ወንድማማቾች መታሰቢያ የአትሌቲክስ ውድድር የኢትዮጵያ አትሌቶች የበላይነት በመያዝ ውድድሩን በታላቅ ድል ማጠናቀቅ ችለዋል።
በሴቶች የ1 ሺህ 500 ሜትር ውድድር አትሌት ብርቄ ኃይሎም 1ኛ በመሆን ማጠናቀቅ ስትችል÷ አትሌት ሳሮን በርሃ ደግሞ 2ኛ ደረጃን ይዛለች።
አትሌት ደስታ ታደለ 5ኛ፣ አትሌት ሲፈን ዳገታ 8ኛ ፣ አትሌት በሻቱ ጌታ 9ኛ እና አትሌት ቤተልሔም ሙላት 15ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቅቀዋል።
የሴቶች 10 ሺህ ሜትር ውድድር አትሌት ፈንታዬ ጫኔ በአንደኝነት ስታሸንፍ÷ አትሌት ቤተልሔም ኦላና 2ኛ ወጥታለች።
አትሌት ሰላማዊት ሻምበል 4ኛ እንዲሁም አትሌት ትርንጎ ታዳለ 6ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቅቀዋል።
በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል አትሌት ብርቱካን ገዳሙ ፈጣን ፉክክር በተደረገበት የሩጫ መድረክ ርቀቱን 2ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቅቃለች።
በ800 ሜትር አትሌት ሀብታም ገበየሁ 6ኛ ደረጃን መያዝ ችላለች።
በወንዶች የ10 ሺህ ሜትር ውድድር ላይ አትሌት እዮብ ስመኝ በበላይነት ጨርሷል፡፡
በዚሁ ውድድር ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ሽመልስ ንጉሴ 3ኛ ደረጃን በመያዝ ፈፅሟል።
የወንዶች 3 ሺህ ሜትር መሰናክል አትሌት ዲንቃ ፍቃዱ 1ኛ በመሆን ሲያሸንፍ÷ አትሌት ሂርኮ ኃይሉ 3ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቅቋል።
የ2026 ዳይመንድ ሊግ 4ኛ መዳረሻ በሆነው የሮሙ የሴቶች 5 ሺህ ሜትር ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የመጀመሪያዎቹን ሰባት ደረጃዎች በመቆጣጠር ጨርሰዋል፡፡
አትሌት ልቅና አምባው 14፡18፡41 የሆነ የወቅቱን ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ ባለድል ሆናለች።
FBC
17 days ago
ማስታወቂያ
"ለ60 ዓመታት የታማኝነት ጉዞ በጋራ እንሩጥ" የቤተሰብ፣ የአንድነት ሩጫ!
የኮሜርሺያል ኖሚኒስ ቤተሰቦች፣ ክቡራን ደንበኞቻችን እና ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት "ለ60 ዓመታት የታማኝነት ጉዞ በጋራ እንሩጥ" የጎዳና ላይ ሩጫ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል።
60 ዓመታትን በታማኝነት ያገለገለው ኮሜርሺያል ኖሚኒስ፣ በደንበኞቹ፣ በእህት ተቋማቱ ፣ በሰራተኞቹ እና በመላው የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ማህበረሰብ መካከል ይበልጥ መቀራረብን ለመፍጠር እና ቤተሰባዊ አንድነትን ለማጠናከር በሚረዳው የ5 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ እንድትሳተፉ በአክብሮት ጋብዘንዎታል።
የመሮጫ ቲ-ሸርቶቹን በኮሜርሺያል ኖሚኒስ ዋና መስሪያ ቤት እና ቅርንጫፎች ያገኛሉ።
ለተጨማሪ መረጃ በ6630 ነጻ የስልክ ጥሪ ወይም በ 0932151385 እና በ0904032498 ደውለው ማግኘት ይችላሉ
"ለ60 ዓመታት የታማኝነት ጉዞ በጋራ እንሩጥ" የቤተሰብ፣ የአንድነት ሩጫ!
የኮሜርሺያል ኖሚኒስ ቤተሰቦች፣ ክቡራን ደንበኞቻችን እና ባለድርሻ አካላት የሚሳተፉበት "ለ60 ዓመታት የታማኝነት ጉዞ በጋራ እንሩጥ" የጎዳና ላይ ሩጫ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል።
60 ዓመታትን በታማኝነት ያገለገለው ኮሜርሺያል ኖሚኒስ፣ በደንበኞቹ፣ በእህት ተቋማቱ ፣ በሰራተኞቹ እና በመላው የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ማህበረሰብ መካከል ይበልጥ መቀራረብን ለመፍጠር እና ቤተሰባዊ አንድነትን ለማጠናከር በሚረዳው የ5 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ እንድትሳተፉ በአክብሮት ጋብዘንዎታል።
የመሮጫ ቲ-ሸርቶቹን በኮሜርሺያል ኖሚኒስ ዋና መስሪያ ቤት እና ቅርንጫፎች ያገኛሉ።
ለተጨማሪ መረጃ በ6630 ነጻ የስልክ ጥሪ ወይም በ 0932151385 እና በ0904032498 ደውለው ማግኘት ይችላሉ
18 days ago
🏃♀️➡️🏃♂️➡️ የ2018 ዓ.ም ኢትዮ ቴሌኮም ታላቁ ቦቆጂ ሩጫ ቲሸርት በቴሌብር!
ሰኔ 07 ቀን 2018 ዓ.ም የጀግኖች አትሌቶች መፍለቂያ በሆነችው ቦቆጂ ይካሔዳል፤ የመሮጫ ቲሸርቱን በቀላሉ በቴሌብር በመግዛት ይሳተፉ።
👉 በኢትዮ ቴሌኮም ቦቆጂ ቅርንጫፍ፣ በንግድ ባንክ ዋና ቅርንጫፍ ፊት ለፊት እንዲሁም በከተማው አስተዳደር ያገኙታል።
*127# ደውለን ወይም ቴሌብር ሱፐርአፕን
https://bit.ly/telebirr_Su... ጭነን ስንሳተፍ እንዲህ ነን
#ደንበኛ_ስንሆን_እንዲህ_ነን #ስንመዘገብ_እንዲህ_ነን #ስንጭን_እንዲህ_ነን #ስናስጀምር_እንዲህ_ነን
ሰኔ 07 ቀን 2018 ዓ.ም የጀግኖች አትሌቶች መፍለቂያ በሆነችው ቦቆጂ ይካሔዳል፤ የመሮጫ ቲሸርቱን በቀላሉ በቴሌብር በመግዛት ይሳተፉ።
👉 በኢትዮ ቴሌኮም ቦቆጂ ቅርንጫፍ፣ በንግድ ባንክ ዋና ቅርንጫፍ ፊት ለፊት እንዲሁም በከተማው አስተዳደር ያገኙታል።
*127# ደውለን ወይም ቴሌብር ሱፐርአፕን
https://bit.ly/telebirr_Su... ጭነን ስንሳተፍ እንዲህ ነን
#ደንበኛ_ስንሆን_እንዲህ_ነን #ስንመዘገብ_እንዲህ_ነን #ስንጭን_እንዲህ_ነን #ስናስጀምር_እንዲህ_ነን
20 days ago
የሞሮኮው የዳይመንድ ሊግ ውድድር የኢትዮጵያውያን አትሌቶች ስኬት ታይቶበታል
#ethiopia | በሞሮኮ ራባት በተካሄደው ሶስተኛው የዳይመንድ ሊግ የራንዌይ ውድድር ላይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑካን ቡድን አባላት ከፍተኛ ድል እና አንጸባራቂ ውጤት አስመዝግበዋል።
በሴቶች የ1 ሺህ 500 ሜትር የሩጫ ውድድር አትሌት ፍሬወይኒ ሀይሉ ርቀቱን በ3 ደቂቃ ከ58 ሰከንድ ከ25 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት በአንደኝነት ስታጠናቅቅ፣ አትሌት ሐረገወይን ካልአዩ ደግሞ በ3 ደቂቃ ከ59 ሰከንድ ከ28 ማይክሮ ሰከንድ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ የሀገራቸውን የበላይነት በጋራ አስጠብቀዋል።
በተጨማሪም በሴቶች የ800 ሜትር ፉክክር አትሌት ፅጌ ድጉማ በ1 ደቂቃ ከ57 ሰከንድ ከ24 ማይክሮ ሰከንድ ፈጣን ጊዜ ሁለተኛ በመሆን አበረታች ውጤት ያስመዘገበች ሲሆን፣ አትሌት ንግስት ጌታቸው ደግሞ በ1 ደቂቃ ከ58 ሰከንድ ከ58 ማይክሮ ሰከንድ 11ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቃለች።
በወንዶች የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ውድድር ላይ የተሳተፈው አትሌት ሳሙኤል ፍሬው የራሱን የዓመቱን ምርጥ ሰዓት በ8 ደቂቃ ከ12 ሰከንድ ከ55 ማይክሮ ሰከንድ በማሻሻል ውድድሩን በ12ኛነት ፈጽሟል።
#athletics #diamondleague #rabat #running #sport #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በሞሮኮ ራባት በተካሄደው ሶስተኛው የዳይመንድ ሊግ የራንዌይ ውድድር ላይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑካን ቡድን አባላት ከፍተኛ ድል እና አንጸባራቂ ውጤት አስመዝግበዋል።
በሴቶች የ1 ሺህ 500 ሜትር የሩጫ ውድድር አትሌት ፍሬወይኒ ሀይሉ ርቀቱን በ3 ደቂቃ ከ58 ሰከንድ ከ25 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት በአንደኝነት ስታጠናቅቅ፣ አትሌት ሐረገወይን ካልአዩ ደግሞ በ3 ደቂቃ ከ59 ሰከንድ ከ28 ማይክሮ ሰከንድ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ የሀገራቸውን የበላይነት በጋራ አስጠብቀዋል።
በተጨማሪም በሴቶች የ800 ሜትር ፉክክር አትሌት ፅጌ ድጉማ በ1 ደቂቃ ከ57 ሰከንድ ከ24 ማይክሮ ሰከንድ ፈጣን ጊዜ ሁለተኛ በመሆን አበረታች ውጤት ያስመዘገበች ሲሆን፣ አትሌት ንግስት ጌታቸው ደግሞ በ1 ደቂቃ ከ58 ሰከንድ ከ58 ማይክሮ ሰከንድ 11ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቃለች።
በወንዶች የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ውድድር ላይ የተሳተፈው አትሌት ሳሙኤል ፍሬው የራሱን የዓመቱን ምርጥ ሰዓት በ8 ደቂቃ ከ12 ሰከንድ ከ55 ማይክሮ ሰከንድ በማሻሻል ውድድሩን በ12ኛነት ፈጽሟል።
#athletics #diamondleague #rabat #running #sport #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
28 days ago
አትሌት አበባ አረጋዊ በኦታዋ ማራቶን አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ጻፈች
#ethiopia | በአንድ ወቅት በ1,500 ሜትር የሩጫ ውድድር ላይ በነበራት ተደጋጋሚ ስኬት የርቀቱ ልዩ ባለሙያ በመባል የምትታወቀው ኢትዮጵያዊቷ አትሌት አበባ አረጋዊ የ2026 የኦታዋ ማራቶንን በሴቶች ዘርፍ በአንደኝነት አጠናቃለች።
በዚሁ ውድድር ላይ ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ኩፍቱ ታሂር በ2 ሰዓት ከ25 ደቂቃ ከ33 ሰከንድ ሁለተኛ ሆና ስታጠናቅቅ ኬንያዊቷ ቤቲ ቺፕኮሪር ደግሞ በ2 ሰዓት ከ25 ደቂቃ ከ51 ሰከንድ ሦስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።
በውድድሩ ላይ የተሳተፉት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች መሰረት በለጠ 4ኛ፣ መስከረም አሰፋ 5ኛ፣ መሰረት ደከቦ 7ኛ እንዲሁም ታደለች በቀለ 10ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን ፈጽመዋል።
በ2012 የለንደን ኦሎምፒክ የትውልድ ሀገሯን ኢትዮጵያን ወክላ በ1,500 ሜትር የብር ሜዳሊያ ያገኘችውና በ2013 የሞስኮ አለም ሻምፒዮና የወርቅ ሜዳሊያ ያሸነፈችው አበባ አረጋዊ በ2014 የቤት ውስጥ አለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ደግሞ ስዊድንን ወክላ የወርቅ ሜዳሊያ ማግኘቷ ይታወሳል።
የሁለት ጊዜ የዳይመንድ ሊግ አሸናፊዋ አትሌት አበባ አረጋዊ ከዚህ የድል ጉዞዋ በኋላ በሰጠችው አስተያየት ለኦታዋ ማራቶን ከፍተኛ ዝግጅት ማድረጓንና በማሸነፏም ታላቅ ደስታ እንደተሰማት ገልጻለች።
ትውልደ ኢትዮጵያዊቷና ስዊድናዊቷ አትሌት አበባ አረጋዊ የኦታዋ ማራቶንን ለማሸነፍ የፈጀባት ጊዜ 2 ሰዓት ከ23 ደቂቃ ከ12 ሰከንድ ነው።
የኢትዮጵያ አትሌቶች ማህበር ፕሬዝዳንትና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የሆነው ባለቤቷ አትሌት የማነ ፀጋይም በ2014 እና በ2018 የካናዳን የቦታው ሪከርድ በመስበር ማሸነፉ ይታወሳል።
ይህ አጋጣሚ ባልና ሚስቱ የኦታዋ ማራቶንን በተለያዩ አመታት በማሸነፍ አዲስ ታሪክ በጋራ እንዲጽፉ አድርጓቸዋል።
✍️ በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ (ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል
#marathon #ottawamarathon #athletics #running #sportnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
)
#ethiopia | በአንድ ወቅት በ1,500 ሜትር የሩጫ ውድድር ላይ በነበራት ተደጋጋሚ ስኬት የርቀቱ ልዩ ባለሙያ በመባል የምትታወቀው ኢትዮጵያዊቷ አትሌት አበባ አረጋዊ የ2026 የኦታዋ ማራቶንን በሴቶች ዘርፍ በአንደኝነት አጠናቃለች።
በዚሁ ውድድር ላይ ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ኩፍቱ ታሂር በ2 ሰዓት ከ25 ደቂቃ ከ33 ሰከንድ ሁለተኛ ሆና ስታጠናቅቅ ኬንያዊቷ ቤቲ ቺፕኮሪር ደግሞ በ2 ሰዓት ከ25 ደቂቃ ከ51 ሰከንድ ሦስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።
በውድድሩ ላይ የተሳተፉት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች መሰረት በለጠ 4ኛ፣ መስከረም አሰፋ 5ኛ፣ መሰረት ደከቦ 7ኛ እንዲሁም ታደለች በቀለ 10ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን ፈጽመዋል።
በ2012 የለንደን ኦሎምፒክ የትውልድ ሀገሯን ኢትዮጵያን ወክላ በ1,500 ሜትር የብር ሜዳሊያ ያገኘችውና በ2013 የሞስኮ አለም ሻምፒዮና የወርቅ ሜዳሊያ ያሸነፈችው አበባ አረጋዊ በ2014 የቤት ውስጥ አለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ደግሞ ስዊድንን ወክላ የወርቅ ሜዳሊያ ማግኘቷ ይታወሳል።
የሁለት ጊዜ የዳይመንድ ሊግ አሸናፊዋ አትሌት አበባ አረጋዊ ከዚህ የድል ጉዞዋ በኋላ በሰጠችው አስተያየት ለኦታዋ ማራቶን ከፍተኛ ዝግጅት ማድረጓንና በማሸነፏም ታላቅ ደስታ እንደተሰማት ገልጻለች።
ትውልደ ኢትዮጵያዊቷና ስዊድናዊቷ አትሌት አበባ አረጋዊ የኦታዋ ማራቶንን ለማሸነፍ የፈጀባት ጊዜ 2 ሰዓት ከ23 ደቂቃ ከ12 ሰከንድ ነው።
የኢትዮጵያ አትሌቶች ማህበር ፕሬዝዳንትና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የሆነው ባለቤቷ አትሌት የማነ ፀጋይም በ2014 እና በ2018 የካናዳን የቦታው ሪከርድ በመስበር ማሸነፉ ይታወሳል።
ይህ አጋጣሚ ባልና ሚስቱ የኦታዋ ማራቶንን በተለያዩ አመታት በማሸነፍ አዲስ ታሪክ በጋራ እንዲጽፉ አድርጓቸዋል።
✍️ በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ (ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል
#marathon #ottawamarathon #athletics #running #sportnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
)
28 days ago
ሜሪ ጆይን ለማገዝ የእግር ጉዞ ተደረገ
ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ "ኩላሊት ጤና፣ ህይወት ተስፋ" በሚል መሪ ቃል የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የገቢ ማሰባሰቢያ የሩጫ መርሀ ግብር አዘጋጀ።
እሁድ ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም መነሻውን ካዛንችስ ዑራዔል በአዲሱ መንገድ ወደ ወሎ ሰፈር የሚወስደው መንገድ ላይ ከጠዋቱ 2 ሰዓት ጀምሮ ሩጫው የተጀመረ ሲሆን ከ7000 በላይ ሰዎችም ተሳትፈዋል።
በዕለቱ' የኩላሊት ጤና ጉዳይ ያገባኛል ከሜሪጆይ ጋር እቆማለሁ' ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ልዩ ልዩ ህብረ-ዝማሬዎችን እየዘመሩ ለሩጫው ትልቅ ድምቀት ሰጥተውት ነበር።
በሩጫ ወይም በአጭር የእግር ጉዞው ላይ ያገኘናቸው ተሳታፊዎች እንደነገሩን እንዲህ ዓይነት መርሀ- ግብሮች ህብረተሰቡን የማሰባሰብ አቅም ያላቸው በመሆኑ በኩላሊት ጤና ጉዳይ ላይ በቀላሉ ግንዛቤ ለመፍጠር ያስችላል ብለዋል።
ወይዘሮ ጠይባ ሀሠን የስደተኞችና ተመለሾች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር በሩጫ መርሀ ግብሩ ላይ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን የግንዛቤ ማስጨበጡ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም ተናግረዋል።
ወይዘሮ ቆንጂች ደበላ የአዲስ አበባ የሴቶችና የህፃናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ፣የኢትዮጵያ የሴቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ዶክተር አፎሚያ አበበ፣ የተለያዩ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ፣ እና የሜሪ ጆይ የቦርድ አባላት በሩጫ መርሀ ግብሩ ላይ በክብር እንግድነት መገኘታቸው ታውቋል።
የመከላከያ የማርሽ ቡድን አባላት የኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር ከተዘመረ በኃላ ከፊት ሆነው የእግር ጉዞውን ያስጀመሩ ሲሆን ተሳታፊዎችም እነርሱን በመከተል ነበር የእግር ጉዞውን ያደረጉት።
በዚህ መርሀ ግብር ላይ የኢትዮሪልስቴት አልሚዎች ማህበር፣የዋሪት፣ የዳሸን ባንክ፣ የህብረት ባንክ ሌሎችም ተቋማት ድጋፍ በማድረግ ለመርሀ ግብሩ መሳካት የበኩላቸውን አድርገዋል።
በሩጫ መርሀ ግብሩ ላይ የታደሙት ሲስተር ዘቢደር ዘውዴ ፣ ከ10,000 ሰዎች በላይ ቲሸርት ገዝተው ድጋፍ ያደረጉ መሆኑን ገልፀው 7000 ሰዎች በሩጫው ላይ መሳተፋቸው ለሜሪ ጆይ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልፀዋል።
በተመሳሳይ መልኩ ሌላ የግንዛቤ ማስጨበጫ የሩጫ መርሀ -ግብር በሀዋሣ ከተማ እንደሚደረግ ይህም በአገር አቀፍ ደረጃ እየተደረገ ያለውን ስለ ኩላሊት የማስተማር ዘመቻ ከፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ በ1986 ዓ.ም. በህግ የተቋቋመ ሀገር በቀል በጎ አድራጎት ድርጅት ሲሆን ከ3 አሰርት ዓመታት በላይ በተለያዩ ክልሎች የተቀናጀ የልማት እና ሰብዓዊ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡
ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ በመንግስት፤ የግሉ ዘርፍ እና በማህበረሰቡ ከፍተኛ ድጋፍ የጤና አገልግሎቱን ለማጠናከር እና ማህበረሰቡን በተሻለ ሁኔታ ለማገልገል የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ የሆስፒታል ግንባታ ስራዎችን በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች እያጠናከረ የሚገኝ ሲሆን በተለይም ለኩላሊት ጤና ችግሮች ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የኩላሊት እጥበት ህክምና ማዕከላት በሃዋሳ፤ በአዲስ አበባ እና አርባ ምንጭ ከተሞች አገልግሎት በመስጠት ላይ ናቸው፡፡ በተመሳሳይ በቅርቡ አገልግሎቱን በደብረ ብርሃን ከተማ ለመጀመር ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ፡፡ ይህንን አገልግሎት በሌሎች ከተሞች ለማስፋፋት እና ለማስቀጠል ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡
የዚህን መርሀ ግብር የሚድያ ማስተባበር ሥራ ያከናወነው ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን (ዕዝራ እጅጉ ) እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።
ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ "ኩላሊት ጤና፣ ህይወት ተስፋ" በሚል መሪ ቃል የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የገቢ ማሰባሰቢያ የሩጫ መርሀ ግብር አዘጋጀ።
እሁድ ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም መነሻውን ካዛንችስ ዑራዔል በአዲሱ መንገድ ወደ ወሎ ሰፈር የሚወስደው መንገድ ላይ ከጠዋቱ 2 ሰዓት ጀምሮ ሩጫው የተጀመረ ሲሆን ከ7000 በላይ ሰዎችም ተሳትፈዋል።
በዕለቱ' የኩላሊት ጤና ጉዳይ ያገባኛል ከሜሪጆይ ጋር እቆማለሁ' ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ልዩ ልዩ ህብረ-ዝማሬዎችን እየዘመሩ ለሩጫው ትልቅ ድምቀት ሰጥተውት ነበር።
በሩጫ ወይም በአጭር የእግር ጉዞው ላይ ያገኘናቸው ተሳታፊዎች እንደነገሩን እንዲህ ዓይነት መርሀ- ግብሮች ህብረተሰቡን የማሰባሰብ አቅም ያላቸው በመሆኑ በኩላሊት ጤና ጉዳይ ላይ በቀላሉ ግንዛቤ ለመፍጠር ያስችላል ብለዋል።
ወይዘሮ ጠይባ ሀሠን የስደተኞችና ተመለሾች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር በሩጫ መርሀ ግብሩ ላይ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን የግንዛቤ ማስጨበጡ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም ተናግረዋል።
ወይዘሮ ቆንጂች ደበላ የአዲስ አበባ የሴቶችና የህፃናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ፣የኢትዮጵያ የሴቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ዶክተር አፎሚያ አበበ፣ የተለያዩ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ፣ እና የሜሪ ጆይ የቦርድ አባላት በሩጫ መርሀ ግብሩ ላይ በክብር እንግድነት መገኘታቸው ታውቋል።
የመከላከያ የማርሽ ቡድን አባላት የኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር ከተዘመረ በኃላ ከፊት ሆነው የእግር ጉዞውን ያስጀመሩ ሲሆን ተሳታፊዎችም እነርሱን በመከተል ነበር የእግር ጉዞውን ያደረጉት።
በዚህ መርሀ ግብር ላይ የኢትዮሪልስቴት አልሚዎች ማህበር፣የዋሪት፣ የዳሸን ባንክ፣ የህብረት ባንክ ሌሎችም ተቋማት ድጋፍ በማድረግ ለመርሀ ግብሩ መሳካት የበኩላቸውን አድርገዋል።
በሩጫ መርሀ ግብሩ ላይ የታደሙት ሲስተር ዘቢደር ዘውዴ ፣ ከ10,000 ሰዎች በላይ ቲሸርት ገዝተው ድጋፍ ያደረጉ መሆኑን ገልፀው 7000 ሰዎች በሩጫው ላይ መሳተፋቸው ለሜሪ ጆይ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልፀዋል።
በተመሳሳይ መልኩ ሌላ የግንዛቤ ማስጨበጫ የሩጫ መርሀ -ግብር በሀዋሣ ከተማ እንደሚደረግ ይህም በአገር አቀፍ ደረጃ እየተደረገ ያለውን ስለ ኩላሊት የማስተማር ዘመቻ ከፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ በ1986 ዓ.ም. በህግ የተቋቋመ ሀገር በቀል በጎ አድራጎት ድርጅት ሲሆን ከ3 አሰርት ዓመታት በላይ በተለያዩ ክልሎች የተቀናጀ የልማት እና ሰብዓዊ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡
ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ በመንግስት፤ የግሉ ዘርፍ እና በማህበረሰቡ ከፍተኛ ድጋፍ የጤና አገልግሎቱን ለማጠናከር እና ማህበረሰቡን በተሻለ ሁኔታ ለማገልገል የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ የሆስፒታል ግንባታ ስራዎችን በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች እያጠናከረ የሚገኝ ሲሆን በተለይም ለኩላሊት ጤና ችግሮች ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የኩላሊት እጥበት ህክምና ማዕከላት በሃዋሳ፤ በአዲስ አበባ እና አርባ ምንጭ ከተሞች አገልግሎት በመስጠት ላይ ናቸው፡፡ በተመሳሳይ በቅርቡ አገልግሎቱን በደብረ ብርሃን ከተማ ለመጀመር ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ፡፡ ይህንን አገልግሎት በሌሎች ከተሞች ለማስፋፋት እና ለማስቀጠል ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡
የዚህን መርሀ ግብር የሚድያ ማስተባበር ሥራ ያከናወነው ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን (ዕዝራ እጅጉ ) እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።
Sponsored by
Surafel
28 days ago
"በዐይኔ በብረቱ ...!"
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዓለም ማህበራዊ ጉዷንም፣ ገዷንም በድሯ ሸምና የሰው ልጅ የደረሰበትን ታላላቅ አብዮቶች ታስመለክተን ይዛለች ።
ይህ የዲጂታሉ ዘመን፣ አዲስ መስኮት ነው።
የዓለምን ታሪክ ሰፊ ንዋይ፣ ብዙ የሰው ኃይል እና ጊዜ በልቶ የመንገር ሩጫ በዚህ የመስኮት አቋራጭ በግለሰቦች ስልክና ካሜራ መዳፍ ላይ እየወደቀ ነው።
የማህበራዊ ትስስር ሜዳው ከትናንት ዛሬ፣ ከዛሬም ነገ ትተው ቢሄዱ ቆሞ አይጠብቅም። በዐይን ጥቅሻ ፈትለክ ነው። ለውጡ ፈጣን፣ ተለዋዋጭነቱ ነቅተው እንደ ቴኒስ ዳኛ ወዲህ ወዲያ አንገትዎን የሚነቀንቅ ሆኗል።
ወደ ምድረ ቀደምት ኢትዮጵያ የካሜራ ሌንሳቸውንና በሚሊየን የሚከተሏቸውን ዐይን ይዘው የሚመጡ የመስኮቱ ዘዋሪዎች ለኢትዮጵያ አዲስ ነጋሪት የሚጎስሙ ናቸው።
በሚሊየን የሚቆጠሩ ተከታዮቻቸው በየሰከንዱ ለሚለቀቁ ይዘቶች ሲሉ ዐይንና ጆሯቸውን በእነዚህ የዘዋሪዎች ዳና ላይ አድርገዋል።
ምክንያቱም ዓለም የዲጂታል ዝመና አብዮቷ ላይ ወደ ፊት እንጂ የኋልዮች ዳራዋን ለመመልከት አፍታም የላትም፤ ተከታዮቻቸውም ጊዜ የለቸውም። አጭር፣ ፈጣን፣ አዲስ ይናፍቃሉ።
የአሜሪካው ታዋቂ የቀጥታ ስርጭት አቅራቢ አይሾው ስፒድ፣ እንዲሁም ከ19 ሚሊየን በላይ የቲክቶክ ተከታዮች ያሉት የዲጂታል ዜና አቅራቢው ዲላን ፔጅ ወደ አዲስ አበባ መምጣት ኢትዮጵያ በአፍሪካ የዲጂታል ዲፕሎማሲና የቱሪዝም ስበት ማዕከል እየሆነች መምጣቷን የሚያሳይ ትልቅ የጂኦፖለቲካዊና የማኅበራዊ ሚዲያ ለውጥ ማሳያ ነው።
ቀድሞ በኢትዮጵያ ፍቅር የወደቀው ብሪታኒያዊው የቲክቶክ ዜና አቅራቢ ዲላን ፔጅ ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታና ስለ ኢትዮጵያውያን የአንድነት መንፈስ በአዎንታ በመዘገብ መንፈሱ ከአካሉ ቀድሞ አዲስ አበባ ከደረሰ ከርሟል።
ይህ ፕሮጀክት በውጭ ዕዳ ሳይሆን በሕዝብ ቦንድና በላብ የተገነባ ነው በማለት አጉልቶ አሳይቷል።
ግድቡንም “በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት የሚቀይረው የአፍሪካ የብርሃን ተስፋ” በማለት ለዓለም ማስተዋወቁን አንረሳም።
ዲላን በርካታ ቀናትን የሚወስደውን ታላቁን ጉዞዬን፣ በቅኝ ግዛት ባልተገዛችው ሀገር ኢትዮጵያ ጀምሬያለሁ በማለት ወደ አዲስ አበባ ሲገባ ይዞት የመጣው የካሜራ ሌንስ የኢትዮጵያን ጥንታዊነት ብቻ ሳይሆን አዲሱን የቴክኖሎጂ ምዕራፍም ጭምር የገለጠ ሆኗል።
በአዲስ አበባ ቆይታው የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን በጎበኘበት ወቅት፥ ይህን በቴክኖሎጂ የተቃኘ ቦታ ሳየው ተደምሜያለሁ፤ አፍሪካ ተቀይራለች፣ አዲሱን ገፅታዋን ለዓለም የሚያሳይ ቦታ ሆኖ አግኝቼዋለሁ ብሏል።
አዲስ አበባ በቅርቡ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡና በጥምረት ከ470 ሚሊየን በላይ ተከታዮች ያሏቸው ከ200 በላይ የዲጂታል ፈጣሪዎች የተሳተፉበትን የአፍሪካ ማኅበራዊ ሚዲያ ተፅእኖ ፈጣሪዎች ጉባኤን ማስተናገዷ የይዘት ፈጣሪዎች የዲፕሎማሲ ዋና ከተማ አድርጓታል።
በጉባኤው ላይ በቀረቡ መረጃዎች መሠረት ስለ አፍሪካ የሚሰራጩ የተዛቡና አሉታዊ ትረካዎች በአህጉሪቱ ላይ በየዓመቱ እስከ 4 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር የሚደርስ የኢኮኖሚ ኪሳራ ያደርሳሉ።
ዲላን ፔጅ እና መሰል የይዘት ፈጣሪዎች ይህንን የተዛባ ምስል ለመስበር 'ሳይነገራችሁ በዓይናችሁ እዩት' በሚል መርህ እየመጡ ነው።
የዲላን ፔጅ ጉዞ ስኬታማ እንዲሆን እንደ አዶናይ ያሉ የሀገር ውስጥ ይዘት ፈጣሪዎች የተጫወቱት ሚና ከፍተኛ ነው።
የተጽእኖ ፈጣሪዎች ጉብኝት የዲጂታል ዲፕሎማሲና የሀገር ገፅታ ግንባታ ወሳኝ ተግባር ሲሆን፥ የወቅቱ የሀያላን ሀገራት ፉክክር ገር ኃይል መሆኑን ላጤነ ዲፕሎማሲው ይገለጥለታል።
ገር ዲፕሎማሲ ሰዎችን ሳያስገድዱ፣ ወደውና ፈቅደው አንተ የምትፈልገውን ነገር እንዲያደርጉ የማድረግ ብቃት መሆኑን የጽንሰ ሀሳቡ ፈጣሪ አሜሪካዊው ጆሴፍ ናይ ያስረዳሉ።
ለጆሴፍ ምስጋና ይግባውና ሀገራት ከጦር መሳሪያ እሽቅድምድሞሽ ወደ ለስላሳው አቀራረብ ፊታቸውን እንዲያዞሩ አድርጓል።
ከአሜሪካ ገር መንገዶች መካከል ሆሊውድ፣ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ብራንዶች (አፕል, ጎግል, ማይክሮሶፍት)፣ ምግቦች (ማክዶናልድ፣ ኮካ ኮላ) እና ታዋቂ ዩኒቨርሲቲዎች ይጠቀሳሉ።
ለደቡብ ኮሪያ "ሃሊዩ" ወይም የኮሪያ ማዕበል። ይህም የኬ-ፖፕ ሙዚቃ፣ የኮሪያ ፊልሞችና ድራማዎች እንዲሁም የውበት ምርቶች፤ ለብሪታንያ የእንግሊዝኛ ቋንቋ፣ ቢቢሲ እና የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ገሩ መንገዳቸው ነው።
ሳዑዲ ዓረቢያ እና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች እንደ ማንችስተር ሲቲ እና ኒውካስል ዩናይትድ የእግር ኳስ ክለቦችን በመግዛት እንዲሁም የዓለም ዋንጫዎችን በማዘጋጀትና እንደ ሮናልዶ ታዋቂ ተጫዋቾችን ወደ ሀገራቸው በማምጣት የዓለምን ትኩረት በመሳብ የሀገራቸውን ገጽታ እያደሱ ይገኛሉ።
ኢትዮጵያም ምድረ ቀደምት፣ የጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ምልክት የአድዋ ድል፣ የፓን-አፍሪካኒዝም ማዕከል መሆኗ፣ የቡና መገኛነቷ፣ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎቿን በማስተዋወቅ የራሷን የዲጂታል ለስላሳ ኃይል እየገነባች ትገኛለች።
በዚህም በቱሪዝም ዘርፍ ላይ ፈጣን የኢኮኖሚ መነቃቃትን ይፈጥራል።
ኢትዮጵያ ይህንን ወርቃማ የዲጂታል ዲፕሎማሲ ዕድል በመጠቀም፣ የቱሪዝምና የኢኮኖሚ ምሰሶዎቿን ለማጠናከር በጥበብና በስልታዊ መሪነት ልትራመድበት ይጠበቃል።
ዲጂታሉ ዓለም በሮችን ከፍቷል፤ የኢትዮጵያን መልኮች በአዲሱ ነጋሪት ማስተጋባት የዛሬ ስራ ነው ።
በኃይለኢየሱስ መኮንን
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዓለም ማህበራዊ ጉዷንም፣ ገዷንም በድሯ ሸምና የሰው ልጅ የደረሰበትን ታላላቅ አብዮቶች ታስመለክተን ይዛለች ።
ይህ የዲጂታሉ ዘመን፣ አዲስ መስኮት ነው።
የዓለምን ታሪክ ሰፊ ንዋይ፣ ብዙ የሰው ኃይል እና ጊዜ በልቶ የመንገር ሩጫ በዚህ የመስኮት አቋራጭ በግለሰቦች ስልክና ካሜራ መዳፍ ላይ እየወደቀ ነው።
የማህበራዊ ትስስር ሜዳው ከትናንት ዛሬ፣ ከዛሬም ነገ ትተው ቢሄዱ ቆሞ አይጠብቅም። በዐይን ጥቅሻ ፈትለክ ነው። ለውጡ ፈጣን፣ ተለዋዋጭነቱ ነቅተው እንደ ቴኒስ ዳኛ ወዲህ ወዲያ አንገትዎን የሚነቀንቅ ሆኗል።
ወደ ምድረ ቀደምት ኢትዮጵያ የካሜራ ሌንሳቸውንና በሚሊየን የሚከተሏቸውን ዐይን ይዘው የሚመጡ የመስኮቱ ዘዋሪዎች ለኢትዮጵያ አዲስ ነጋሪት የሚጎስሙ ናቸው።
በሚሊየን የሚቆጠሩ ተከታዮቻቸው በየሰከንዱ ለሚለቀቁ ይዘቶች ሲሉ ዐይንና ጆሯቸውን በእነዚህ የዘዋሪዎች ዳና ላይ አድርገዋል።
ምክንያቱም ዓለም የዲጂታል ዝመና አብዮቷ ላይ ወደ ፊት እንጂ የኋልዮች ዳራዋን ለመመልከት አፍታም የላትም፤ ተከታዮቻቸውም ጊዜ የለቸውም። አጭር፣ ፈጣን፣ አዲስ ይናፍቃሉ።
የአሜሪካው ታዋቂ የቀጥታ ስርጭት አቅራቢ አይሾው ስፒድ፣ እንዲሁም ከ19 ሚሊየን በላይ የቲክቶክ ተከታዮች ያሉት የዲጂታል ዜና አቅራቢው ዲላን ፔጅ ወደ አዲስ አበባ መምጣት ኢትዮጵያ በአፍሪካ የዲጂታል ዲፕሎማሲና የቱሪዝም ስበት ማዕከል እየሆነች መምጣቷን የሚያሳይ ትልቅ የጂኦፖለቲካዊና የማኅበራዊ ሚዲያ ለውጥ ማሳያ ነው።
ቀድሞ በኢትዮጵያ ፍቅር የወደቀው ብሪታኒያዊው የቲክቶክ ዜና አቅራቢ ዲላን ፔጅ ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታና ስለ ኢትዮጵያውያን የአንድነት መንፈስ በአዎንታ በመዘገብ መንፈሱ ከአካሉ ቀድሞ አዲስ አበባ ከደረሰ ከርሟል።
ይህ ፕሮጀክት በውጭ ዕዳ ሳይሆን በሕዝብ ቦንድና በላብ የተገነባ ነው በማለት አጉልቶ አሳይቷል።
ግድቡንም “በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት የሚቀይረው የአፍሪካ የብርሃን ተስፋ” በማለት ለዓለም ማስተዋወቁን አንረሳም።
ዲላን በርካታ ቀናትን የሚወስደውን ታላቁን ጉዞዬን፣ በቅኝ ግዛት ባልተገዛችው ሀገር ኢትዮጵያ ጀምሬያለሁ በማለት ወደ አዲስ አበባ ሲገባ ይዞት የመጣው የካሜራ ሌንስ የኢትዮጵያን ጥንታዊነት ብቻ ሳይሆን አዲሱን የቴክኖሎጂ ምዕራፍም ጭምር የገለጠ ሆኗል።
በአዲስ አበባ ቆይታው የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን በጎበኘበት ወቅት፥ ይህን በቴክኖሎጂ የተቃኘ ቦታ ሳየው ተደምሜያለሁ፤ አፍሪካ ተቀይራለች፣ አዲሱን ገፅታዋን ለዓለም የሚያሳይ ቦታ ሆኖ አግኝቼዋለሁ ብሏል።
አዲስ አበባ በቅርቡ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡና በጥምረት ከ470 ሚሊየን በላይ ተከታዮች ያሏቸው ከ200 በላይ የዲጂታል ፈጣሪዎች የተሳተፉበትን የአፍሪካ ማኅበራዊ ሚዲያ ተፅእኖ ፈጣሪዎች ጉባኤን ማስተናገዷ የይዘት ፈጣሪዎች የዲፕሎማሲ ዋና ከተማ አድርጓታል።
በጉባኤው ላይ በቀረቡ መረጃዎች መሠረት ስለ አፍሪካ የሚሰራጩ የተዛቡና አሉታዊ ትረካዎች በአህጉሪቱ ላይ በየዓመቱ እስከ 4 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር የሚደርስ የኢኮኖሚ ኪሳራ ያደርሳሉ።
ዲላን ፔጅ እና መሰል የይዘት ፈጣሪዎች ይህንን የተዛባ ምስል ለመስበር 'ሳይነገራችሁ በዓይናችሁ እዩት' በሚል መርህ እየመጡ ነው።
የዲላን ፔጅ ጉዞ ስኬታማ እንዲሆን እንደ አዶናይ ያሉ የሀገር ውስጥ ይዘት ፈጣሪዎች የተጫወቱት ሚና ከፍተኛ ነው።
የተጽእኖ ፈጣሪዎች ጉብኝት የዲጂታል ዲፕሎማሲና የሀገር ገፅታ ግንባታ ወሳኝ ተግባር ሲሆን፥ የወቅቱ የሀያላን ሀገራት ፉክክር ገር ኃይል መሆኑን ላጤነ ዲፕሎማሲው ይገለጥለታል።
ገር ዲፕሎማሲ ሰዎችን ሳያስገድዱ፣ ወደውና ፈቅደው አንተ የምትፈልገውን ነገር እንዲያደርጉ የማድረግ ብቃት መሆኑን የጽንሰ ሀሳቡ ፈጣሪ አሜሪካዊው ጆሴፍ ናይ ያስረዳሉ።
ለጆሴፍ ምስጋና ይግባውና ሀገራት ከጦር መሳሪያ እሽቅድምድሞሽ ወደ ለስላሳው አቀራረብ ፊታቸውን እንዲያዞሩ አድርጓል።
ከአሜሪካ ገር መንገዶች መካከል ሆሊውድ፣ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ብራንዶች (አፕል, ጎግል, ማይክሮሶፍት)፣ ምግቦች (ማክዶናልድ፣ ኮካ ኮላ) እና ታዋቂ ዩኒቨርሲቲዎች ይጠቀሳሉ።
ለደቡብ ኮሪያ "ሃሊዩ" ወይም የኮሪያ ማዕበል። ይህም የኬ-ፖፕ ሙዚቃ፣ የኮሪያ ፊልሞችና ድራማዎች እንዲሁም የውበት ምርቶች፤ ለብሪታንያ የእንግሊዝኛ ቋንቋ፣ ቢቢሲ እና የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ገሩ መንገዳቸው ነው።
ሳዑዲ ዓረቢያ እና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች እንደ ማንችስተር ሲቲ እና ኒውካስል ዩናይትድ የእግር ኳስ ክለቦችን በመግዛት እንዲሁም የዓለም ዋንጫዎችን በማዘጋጀትና እንደ ሮናልዶ ታዋቂ ተጫዋቾችን ወደ ሀገራቸው በማምጣት የዓለምን ትኩረት በመሳብ የሀገራቸውን ገጽታ እያደሱ ይገኛሉ።
ኢትዮጵያም ምድረ ቀደምት፣ የጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ምልክት የአድዋ ድል፣ የፓን-አፍሪካኒዝም ማዕከል መሆኗ፣ የቡና መገኛነቷ፣ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎቿን በማስተዋወቅ የራሷን የዲጂታል ለስላሳ ኃይል እየገነባች ትገኛለች።
በዚህም በቱሪዝም ዘርፍ ላይ ፈጣን የኢኮኖሚ መነቃቃትን ይፈጥራል።
ኢትዮጵያ ይህንን ወርቃማ የዲጂታል ዲፕሎማሲ ዕድል በመጠቀም፣ የቱሪዝምና የኢኮኖሚ ምሰሶዎቿን ለማጠናከር በጥበብና በስልታዊ መሪነት ልትራመድበት ይጠበቃል።
ዲጂታሉ ዓለም በሮችን ከፍቷል፤ የኢትዮጵያን መልኮች በአዲሱ ነጋሪት ማስተጋባት የዛሬ ስራ ነው ።
በኃይለኢየሱስ መኮንን
29 days ago
ከግማሽ ክፍለ ዘመን ( ከ 50 ዓመታት ) በላይ በታማኝነት ያገለገሉት መልአከ ገነት ቆሞስ አባ ተስፋ ማርያም ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
#rthiopia | በቦሬ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንደ ጽኑ ዋርካ በመሆን ለሃምሳ ዓመታት ያህል ያለመታከትና በታላቅ ፍቅር ሕዝበ ክርስቲያንን ሲያገለግሉ የኖሩት ታላቁ አባት መልአከ ገነት ቆሞስ አባ ተስፋ ማርያም ሕይወታቸው አልፏል።
አባታችን ለምዕመናን የእምነት ምሰሶ እና የትሕትና ትልቅ አርአያ ነበሩ።
በቅዱስ ሥፍራው ያሳለፏቸው ረጅም ዘመናት ለሥልጣን ወይም ለምድራዊ ዝና ሳይሆን ለእውነተኛ መንፈሳዊ አገልግሎት የተሰጡ ነበሩ።
ማንኛውንም ዓይነት ፈተናና የሕይወት መከራ ሳይበግራቸው እምነታቸውን ጠብቀው ሐዋርያዊ ሩጫቸውን በድል አጠናቀዋል።
አባታችን በ1977 ዓ.ም መልአከ ገነት የሚለውን የማዕረግ ስም ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ኃይማኖት በብፁዕ አቡነ በርተሎሚዎስ አቅራቢነት አግኝተዋል።
ታላቁ አባት በቀድሞው የሲዳሞ ክፍለ ሀገር ውስጥ በይርጋዓለም፣ በጀምጀም፣ በሻኪሶ፣ በነጌሌ ቦረና፣ በዲላ፣ በይርጋጨፌ፣ በአለታ ወንዶ፣ በቦሬ ቅድስት ማርያም እና በይርባ ሙዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሳይቀሩ ቅዱስ ወንጌልን በመስበክና የሰንበት ትምህርት ቤቶችን በማደራጀት ከልጅነት እስከ እውቀት የደከሙ ታላቅ ሐዋርያ ነበሩ።
ለቤተ ክርስቲያን ካበረከቷቸውና ሁልጊዜም በታሪክ ከሚታወሱት ተግባሮቻቸው መካከል
አንደኛው ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ያሳዩት ጽናትና ታማኝነት ሲሆን፣ ቅዱስ ስፍራውን ሳይለቁ በቅድስና መኖር የሚቻለው በእግዚአብሔር ጸጋ መሆኑን በተግባር አሳይተዋል።
ሁለተኛው ዕድሜያቸው ቢገፋም መንፈሳቸው እየታደሰ ለምዕመናን መጽናናትና ለአገልግሎት ራሳቸውን አሳልፈው መስጠታቸው ነው።
ሦስተኛው ደግሞ ያከናወኑት መንፈሳዊ ተጋድሎ ሁሉ ያለ ምንም ምድራዊ ጥቅም፣ በቅንነትና በንጹሕ ልብ የተመራ መሆኑ ነው።
በአሁኑ ወቅት አባታችን ከዚህ ዓለም ድካምና መከራ አርፈው ወደማያልፈው የቅዱሳን ማረፊያ ተሻግረዋል።
ምንም እንኳ የአካል መለያየታቸው፣ ያሳደገን፣ የመከረንና ያስተማረን ጣፋጭ ምክራቸውን ማጣታችን ልብን የሚነካ ቢሆንም፣ የሠሩት መልካም ሥራ ግን ሁልጊዜም ሕያው ሆኖ ይኖራል።
ያገለገሏት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንና ሕዝበ ክርስቲያኑ የአባታችንን ጸሎትና በረከት እንዲያገኙ እየተመኘን፣ ለእናት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን፣ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለመላው የቦሬ ከተማና የገጠር ሕዝብ መጽናናትን እንመኛለን።
#church #ethiopianorthodox #christianity #memorial #bore #sidamo #orthodox #faith #clergy #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#rthiopia | በቦሬ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንደ ጽኑ ዋርካ በመሆን ለሃምሳ ዓመታት ያህል ያለመታከትና በታላቅ ፍቅር ሕዝበ ክርስቲያንን ሲያገለግሉ የኖሩት ታላቁ አባት መልአከ ገነት ቆሞስ አባ ተስፋ ማርያም ሕይወታቸው አልፏል።
አባታችን ለምዕመናን የእምነት ምሰሶ እና የትሕትና ትልቅ አርአያ ነበሩ።
በቅዱስ ሥፍራው ያሳለፏቸው ረጅም ዘመናት ለሥልጣን ወይም ለምድራዊ ዝና ሳይሆን ለእውነተኛ መንፈሳዊ አገልግሎት የተሰጡ ነበሩ።
ማንኛውንም ዓይነት ፈተናና የሕይወት መከራ ሳይበግራቸው እምነታቸውን ጠብቀው ሐዋርያዊ ሩጫቸውን በድል አጠናቀዋል።
አባታችን በ1977 ዓ.ም መልአከ ገነት የሚለውን የማዕረግ ስም ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ኃይማኖት በብፁዕ አቡነ በርተሎሚዎስ አቅራቢነት አግኝተዋል።
ታላቁ አባት በቀድሞው የሲዳሞ ክፍለ ሀገር ውስጥ በይርጋዓለም፣ በጀምጀም፣ በሻኪሶ፣ በነጌሌ ቦረና፣ በዲላ፣ በይርጋጨፌ፣ በአለታ ወንዶ፣ በቦሬ ቅድስት ማርያም እና በይርባ ሙዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሳይቀሩ ቅዱስ ወንጌልን በመስበክና የሰንበት ትምህርት ቤቶችን በማደራጀት ከልጅነት እስከ እውቀት የደከሙ ታላቅ ሐዋርያ ነበሩ።
ለቤተ ክርስቲያን ካበረከቷቸውና ሁልጊዜም በታሪክ ከሚታወሱት ተግባሮቻቸው መካከል
አንደኛው ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ያሳዩት ጽናትና ታማኝነት ሲሆን፣ ቅዱስ ስፍራውን ሳይለቁ በቅድስና መኖር የሚቻለው በእግዚአብሔር ጸጋ መሆኑን በተግባር አሳይተዋል።
ሁለተኛው ዕድሜያቸው ቢገፋም መንፈሳቸው እየታደሰ ለምዕመናን መጽናናትና ለአገልግሎት ራሳቸውን አሳልፈው መስጠታቸው ነው።
ሦስተኛው ደግሞ ያከናወኑት መንፈሳዊ ተጋድሎ ሁሉ ያለ ምንም ምድራዊ ጥቅም፣ በቅንነትና በንጹሕ ልብ የተመራ መሆኑ ነው።
በአሁኑ ወቅት አባታችን ከዚህ ዓለም ድካምና መከራ አርፈው ወደማያልፈው የቅዱሳን ማረፊያ ተሻግረዋል።
ምንም እንኳ የአካል መለያየታቸው፣ ያሳደገን፣ የመከረንና ያስተማረን ጣፋጭ ምክራቸውን ማጣታችን ልብን የሚነካ ቢሆንም፣ የሠሩት መልካም ሥራ ግን ሁልጊዜም ሕያው ሆኖ ይኖራል።
ያገለገሏት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንና ሕዝበ ክርስቲያኑ የአባታችንን ጸሎትና በረከት እንዲያገኙ እየተመኘን፣ ለእናት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን፣ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለመላው የቦሬ ከተማና የገጠር ሕዝብ መጽናናትን እንመኛለን።
#church #ethiopianorthodox #christianity #memorial #bore #sidamo #orthodox #faith #clergy #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 month ago
24ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ በሚደረጉ ውድድሮች ፍፃሜውን ያገኛል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 24ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ በሚደረጉ ውድድሮች ይጠናቀቃል።
በውድድሩ የመጨረሻ ቀን ላይ ኢትዮጵያን የወከሉ አትሌቶች የሚካፈሉባቸው 8 የፍፃሜ ውድድሮች ምሽት ላይ ይደረጋሉ።
በዚህም አመሻሽ 12:30 ላይ በከፍታ ዝላይ አትሌት ገመዶ አባተ እንዲሁም አመሻሽ 12:40 አትሌት ኦታጌ ኦባንግ በወንዶች የጦር ውርወራ ላይ ኢትዮጵያን ወክለው ይወዳደራሉ።
ምሽት 1 ሰዓት ላይ ደግሞ በ3 ሺህ ሜትር የሴቶች መሰናክል ሩጫ ላይ አትሌት ወሰኔ አሰፋ እና አትሌት አልማዝ ዮሐንስ የሚሳተፉ ሲሆን÷ ምሽት 1:20 ላይ ደግሞ በ400 ሜትር የሴቶች መሰናክል አትሌት ደራርቱ እኖታ፣ አትሌት እመቤት ተከተል እና አትሌት ባንቻየሁ ተሰማ ኢትዮጵያን ይወክላሉ።
እንዲሁም ምሽት 1:50 ላይ የ1 ሺህ 500 ሜትር የሴቶች ሩጫ አትሌት አዳኑ ኔንቆ፣ አትሌት ማህተቤ ፍቃዱ እና አትሌት ደስታ ታደለ ተሳታፊ ናቸው።
ምሽት 2 ሰዓት ላይ የ1 ሺህ 500 ሜትር ወንዶች ሩጫ አትሌት እንዳሻው ረታና አትሌት አሸናፊ ኢማና ሲካፈሉት÷ ምሽት 2:20 ላይ ደግሞ በ5 ሺህ ሜትር የወንዶች ሩጫ አትሌት ሙቢን ሀጂ፣ አትሌት ጀምበሩ ሲሳይ እና አትሌት ገብሩ አብረሃ ተፋላሚ ናቸው።
በመጨረሻም ምሽት 3 ሰዓት በ400 ሜትር የሴቶች ሩጫ አትሌት ገነት አየለ፣ አትሌት ምስጋና ኃይሉ፣ አትሌት ትዕግስት አያና እና አትሌት አጃይባ አልዪ ይወዳደራሉ።
በውድድሩ ኢትዮጵያ እስካሁን 11 ሜዳሊያዎች አስመዝግባለች።
በወርቅነህ ጋሻሁን
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 24ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ በሚደረጉ ውድድሮች ይጠናቀቃል።
በውድድሩ የመጨረሻ ቀን ላይ ኢትዮጵያን የወከሉ አትሌቶች የሚካፈሉባቸው 8 የፍፃሜ ውድድሮች ምሽት ላይ ይደረጋሉ።
በዚህም አመሻሽ 12:30 ላይ በከፍታ ዝላይ አትሌት ገመዶ አባተ እንዲሁም አመሻሽ 12:40 አትሌት ኦታጌ ኦባንግ በወንዶች የጦር ውርወራ ላይ ኢትዮጵያን ወክለው ይወዳደራሉ።
ምሽት 1 ሰዓት ላይ ደግሞ በ3 ሺህ ሜትር የሴቶች መሰናክል ሩጫ ላይ አትሌት ወሰኔ አሰፋ እና አትሌት አልማዝ ዮሐንስ የሚሳተፉ ሲሆን÷ ምሽት 1:20 ላይ ደግሞ በ400 ሜትር የሴቶች መሰናክል አትሌት ደራርቱ እኖታ፣ አትሌት እመቤት ተከተል እና አትሌት ባንቻየሁ ተሰማ ኢትዮጵያን ይወክላሉ።
እንዲሁም ምሽት 1:50 ላይ የ1 ሺህ 500 ሜትር የሴቶች ሩጫ አትሌት አዳኑ ኔንቆ፣ አትሌት ማህተቤ ፍቃዱ እና አትሌት ደስታ ታደለ ተሳታፊ ናቸው።
ምሽት 2 ሰዓት ላይ የ1 ሺህ 500 ሜትር ወንዶች ሩጫ አትሌት እንዳሻው ረታና አትሌት አሸናፊ ኢማና ሲካፈሉት÷ ምሽት 2:20 ላይ ደግሞ በ5 ሺህ ሜትር የወንዶች ሩጫ አትሌት ሙቢን ሀጂ፣ አትሌት ጀምበሩ ሲሳይ እና አትሌት ገብሩ አብረሃ ተፋላሚ ናቸው።
በመጨረሻም ምሽት 3 ሰዓት በ400 ሜትር የሴቶች ሩጫ አትሌት ገነት አየለ፣ አትሌት ምስጋና ኃይሉ፣ አትሌት ትዕግስት አያና እና አትሌት አጃይባ አልዪ ይወዳደራሉ።
በውድድሩ ኢትዮጵያ እስካሁን 11 ሜዳሊያዎች አስመዝግባለች።
በወርቅነህ ጋሻሁን
1 month ago
የኢትዮጵያ አየር መንገድ 80ኛ ዓመቱን በታላቅ የጎዳና ላይ ሩጫ አከበረ
#fastmereja I የኢትዮጵያ አየር መንገድ የተመሰረተበትን 80ኛ ዓመት በዓል አስመልክቶ ያዘጋጀው የ8 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ዛሬ ግንቦት 9 ቀን 2018 ዓ.ም በልዩ ድምቀት ተካሄደ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፣ ተቋሙ በታሪኩ መጀመሪያ በ1938 ዓ.ም ስራ ሲጀምር በጥቂት አነስተኛ አውሮፕላኖች ብቻ በረራ ያደርግ እንደነበር አስታውሰው፣ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ባደረገው ያልተቋረጠ እድገት በአሁኑ ወቅት የዓለምን ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ያካተቱ የተለያዩ የቦይንግ፣ የኤርባስ እና የሌሎች አውሮፕላኖች ባለቤት መሆን መቻሉን አብራርተዋል። አየር መንገዱ በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ145 በላይ መዳረሻዎች እንዳሉት የገለጹት ዋና ስራ አስፈጻሚው፣ በተለይም በካርጎ፣ በአቪዬሽን አካዳሚ ማሰልጠኛ እና በሌሎችም የዘርፉ አገልግሎቶች አርዓያ የሚሆን ተግባር እያከናወነ ይገኛል ብለዋል። ይህ መዋቅራዊ ጥንካሬውና ስትራቴጂካዊ ዕድገቱ አየር መንገዱን ተመራጭና ቀዳሚ እንዲሆን እንዳስቻለውም አመልክተዋል።
አየር መንገዱ የ80 ዓመት ታሪካዊ የስኬት ጉዞውን የዛሬው የጎዳና ላይ ሩጫን ጨምሮ በፓናል ውይይቶች፣ በአውደ-ርዕዮች እና በተለያዩ ማህበራዊ ዝግጅቶች በታላቅ ድምቀት እያከበረ እንደሚገኝ ተገልጿል። በሩጫ መርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኮማንደር ስለሺ ስህንን ጨምሮ የአየር መንገዱ የስራ ሀላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
መነሻውን ከሣር ቤት በማድረግ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ማጠናቀቂያውን ያደረገው በዚህ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ላይ አትሌቶች፣ የአየር መንገዱ ሰራተኞች፣ የስፖርት ቤተሰቡ እና ከተለያዩ ተቋማት የተወጣጡ ሰራተኞች ተሳትፏል።
#fastmereja I የኢትዮጵያ አየር መንገድ የተመሰረተበትን 80ኛ ዓመት በዓል አስመልክቶ ያዘጋጀው የ8 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ዛሬ ግንቦት 9 ቀን 2018 ዓ.ም በልዩ ድምቀት ተካሄደ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፣ ተቋሙ በታሪኩ መጀመሪያ በ1938 ዓ.ም ስራ ሲጀምር በጥቂት አነስተኛ አውሮፕላኖች ብቻ በረራ ያደርግ እንደነበር አስታውሰው፣ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ባደረገው ያልተቋረጠ እድገት በአሁኑ ወቅት የዓለምን ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ያካተቱ የተለያዩ የቦይንግ፣ የኤርባስ እና የሌሎች አውሮፕላኖች ባለቤት መሆን መቻሉን አብራርተዋል። አየር መንገዱ በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ145 በላይ መዳረሻዎች እንዳሉት የገለጹት ዋና ስራ አስፈጻሚው፣ በተለይም በካርጎ፣ በአቪዬሽን አካዳሚ ማሰልጠኛ እና በሌሎችም የዘርፉ አገልግሎቶች አርዓያ የሚሆን ተግባር እያከናወነ ይገኛል ብለዋል። ይህ መዋቅራዊ ጥንካሬውና ስትራቴጂካዊ ዕድገቱ አየር መንገዱን ተመራጭና ቀዳሚ እንዲሆን እንዳስቻለውም አመልክተዋል።
አየር መንገዱ የ80 ዓመት ታሪካዊ የስኬት ጉዞውን የዛሬው የጎዳና ላይ ሩጫን ጨምሮ በፓናል ውይይቶች፣ በአውደ-ርዕዮች እና በተለያዩ ማህበራዊ ዝግጅቶች በታላቅ ድምቀት እያከበረ እንደሚገኝ ተገልጿል። በሩጫ መርሃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኮማንደር ስለሺ ስህንን ጨምሮ የአየር መንገዱ የስራ ሀላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
መነሻውን ከሣር ቤት በማድረግ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ማጠናቀቂያውን ያደረገው በዚህ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ላይ አትሌቶች፣ የአየር መንገዱ ሰራተኞች፣ የስፖርት ቤተሰቡ እና ከተለያዩ ተቋማት የተወጣጡ ሰራተኞች ተሳትፏል።
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ማሞ ለማ እና መልክናት ውዱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ8 ኪሎ ሜትር የጎዳና ሩጫ ውድድርን አሸነፉ
******************
የአፍሪካ ግዙፉና የሀገራችን ኩራት የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የተመሰረተበትን 80ኛ ዓመት አስመልክቶ ያዘጋጀው የ8 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ መነሻውን ሳር ቤት፣ መዳረሻውን ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አድርጎ ተከናውኗል።
"80 ዓመታት የዘለቀ አስተማማኝ አገልግሎት፤ ዘመን ተሻጋሪ ቅርስ" በሚል መሪ ቃል በተከናወነው የሩጫ ውድድር ላይ ታዋቂ አትሌቶች፣ በሺዎች የሚቆጠሩ የአየር መንገዱ ሰራተኞች፣ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የስፖርት ቤተሰቦች ተሳትፈዋል።
ውድድሩ "8 ኪሎ ሜትር ለ80 ዓመታት የላቀ አገልግሎት" በሚል ተምሳሌትነት የተዘጋጀ ሲሆን፣ አየር መንገዱ እ.ኤ.አ ከ1946 ጀምሮ እስከ 2026 ዓ.ም የዘለቀውን የላቀ የዓለም አቀፍ የአቪየሽን ስኬት የዘከረበት ሆኗል።
በውድድሩም በታዋቂ አትሌቶች ዘርፍ በወንዶች ማሞ ለማ ከኦሮሚያ ኮንስትራክሽን፣ በሴቶች ደግሞ መልክናት ውዱ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሸናፊ ሆነዋል።
በዮሴፍ ሹምዬ
#ethiopianairlines #flyethiopian #athlete #athletics
******************
የአፍሪካ ግዙፉና የሀገራችን ኩራት የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የተመሰረተበትን 80ኛ ዓመት አስመልክቶ ያዘጋጀው የ8 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ መነሻውን ሳር ቤት፣ መዳረሻውን ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አድርጎ ተከናውኗል።
"80 ዓመታት የዘለቀ አስተማማኝ አገልግሎት፤ ዘመን ተሻጋሪ ቅርስ" በሚል መሪ ቃል በተከናወነው የሩጫ ውድድር ላይ ታዋቂ አትሌቶች፣ በሺዎች የሚቆጠሩ የአየር መንገዱ ሰራተኞች፣ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የስፖርት ቤተሰቦች ተሳትፈዋል።
ውድድሩ "8 ኪሎ ሜትር ለ80 ዓመታት የላቀ አገልግሎት" በሚል ተምሳሌትነት የተዘጋጀ ሲሆን፣ አየር መንገዱ እ.ኤ.አ ከ1946 ጀምሮ እስከ 2026 ዓ.ም የዘለቀውን የላቀ የዓለም አቀፍ የአቪየሽን ስኬት የዘከረበት ሆኗል።
በውድድሩም በታዋቂ አትሌቶች ዘርፍ በወንዶች ማሞ ለማ ከኦሮሚያ ኮንስትራክሽን፣ በሴቶች ደግሞ መልክናት ውዱ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሸናፊ ሆነዋል።
በዮሴፍ ሹምዬ
#ethiopianairlines #flyethiopian #athlete #athletics
Comments