በቆጂ : አትሌት ማሞ ሐጫሉ እና ማህሌት ካሳሁን የድል አክሊል ደፉ
#ethiopia | ለአምስተኛ ጊዜ መነሻና መድረሻውን በቆጂ ስታዲየም ባደረገው የ12 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር በወንዶች ዘርፍ የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ክለብ ተወካይ የሆነው ማሞ ሐጫሉ አንደኛ በመሆን አሸንፏል።
በዚሁ ምድብ አማን ቃዲ እና አልዬ ቃሲም ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን አጠናቀዋል።
በሴቶች ምድብ በተደረገው ፉክክር የአሰላ አትሌቲክስ ክለብ አትሌት ማህሌት ካሳሁን ቀዳሚነቱን ስትይዝ፤ ኪያ ፍስሃ እና ድርቤ ኢርኮ በቅደም ተከተል ሁለተኛና ሶስተኛ በመሆን ተከታትለው ገብተዋል።
የልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክስ ተከታታይ ውድድር አካል በሆነው በዚህ ዝግጅት ላይ ዕድሜያቸው ከ11 እና ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ህጻናት በሁለቱም ጾታ ያደረጉት ተሳትፎ ለውድድሩ የተለየ ድምቀት ሰጥቶት አርፍዷል።
በስፍራው ተገኝተው የክብር እንግዳ የነበሩት የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ መኪዩ ሙሐመድ፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ እንደገና አበበ ዶክተር፣ የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሮዛ ቢያ እና የበቆጂ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ ብርሃኔ ነገሰ ሲሆኑ በርካታ የአካባቢው ነዋሪዎችም ታድመውታል።
በስድስት ከተሞች ላይ የሚካሄደው የልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክስ ውድድር ቀጣይ መርሃ ግብሩን ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም በአርባምንጭ ከተማ የሚያደርግ ሲሆን የፍጻሜው ውድድር ደግሞ ሐምሌ 12 ቀን በታሪካዊቷ ሐረር ከተማ እንደሚጠናቀቅ ታውቋል።
#bekoji #athletics #ethiotelecom #greatethiopianrun #sportnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ለአምስተኛ ጊዜ መነሻና መድረሻውን በቆጂ ስታዲየም ባደረገው የ12 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር በወንዶች ዘርፍ የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ክለብ ተወካይ የሆነው ማሞ ሐጫሉ አንደኛ በመሆን አሸንፏል።
በዚሁ ምድብ አማን ቃዲ እና አልዬ ቃሲም ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን አጠናቀዋል።
በሴቶች ምድብ በተደረገው ፉክክር የአሰላ አትሌቲክስ ክለብ አትሌት ማህሌት ካሳሁን ቀዳሚነቱን ስትይዝ፤ ኪያ ፍስሃ እና ድርቤ ኢርኮ በቅደም ተከተል ሁለተኛና ሶስተኛ በመሆን ተከታትለው ገብተዋል።
የልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክስ ተከታታይ ውድድር አካል በሆነው በዚህ ዝግጅት ላይ ዕድሜያቸው ከ11 እና ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ህጻናት በሁለቱም ጾታ ያደረጉት ተሳትፎ ለውድድሩ የተለየ ድምቀት ሰጥቶት አርፍዷል።
በስፍራው ተገኝተው የክብር እንግዳ የነበሩት የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ መኪዩ ሙሐመድ፣ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ እንደገና አበበ ዶክተር፣ የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሮዛ ቢያ እና የበቆጂ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ ብርሃኔ ነገሰ ሲሆኑ በርካታ የአካባቢው ነዋሪዎችም ታድመውታል።
በስድስት ከተሞች ላይ የሚካሄደው የልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክስ ውድድር ቀጣይ መርሃ ግብሩን ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም በአርባምንጭ ከተማ የሚያደርግ ሲሆን የፍጻሜው ውድድር ደግሞ ሐምሌ 12 ቀን በታሪካዊቷ ሐረር ከተማ እንደሚጠናቀቅ ታውቋል።
#bekoji #athletics #ethiotelecom #greatethiopianrun #sportnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
6 hours ago