Logo
YenetaTube
የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም እድሳት ተጠናቆ ወደ ውድድር ሊመለስ መሆኑ ተገለጸ

የባሕር ዳር ዓለም ከባህር ዳር ከተማ ስታዲየም በቅርቡ ወደ ስፖርታዊ ውድድሮች እንደሚመለስ የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው አስታወቁ።

ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ይህንን የገለጹት በከተማዋ በደመቀ ሁኔታ በተካሄደው የ1ኛው የኢትዮጵያ 10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር መዝጊያ ስነስርዓት ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ነው።

የስታዲየሙን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ጎሹ እንዳላማው የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም የእድሳት ሥራ በአሁኑ ወቅት እየተጠናቀቀ መሆኑን ጠቁመው፣ ስታዲየሙ በቅርቡ ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ ውድድሮችን ማስተናገድ በሚችልበት ቁመና ላይ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል።

ከተማዋ ያሏትን ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎችና አዳዲስ እየተገነቡ ያሉ መስተንግዶዎችን ያነሱት ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ይህ መሰረተልማት ስታዲየሙንና ባህር ዳርን ሁሉ የተሟላላት ዘመናዊ የቱሪዝምና የስፖርት ከተማ እንደሚያደርጋት ገልጸዋል።

በሌላ በኩል በከተማዋ የተካሄደውን የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር አስመልክቶ ባደረጉት ንግግር ውድድሩ የባሕር ዳር ከተማ አስተማማኝ የሰላም ከተማ መሆኗን በተግባር ያረጋገጠበት መድረክ መሆኑን አስገንዝበዋል።

ውድድሩ በባሕር ዳር እንዲካሄድ ውሳኔ ላስተላለፉና በቦታው ተገኝተው ለታደሙት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮችም የከተማ አስተዳደሩን ምስጋና አቅርበዋል።
#አሐዱ

9 hours ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.