12 days ago
ከግማሽ ክፍለ ዘመን ( ከ 50 ዓመታት ) በላይ በታማኝነት ያገለገሉት መልአከ ገነት ቆሞስ አባ ተስፋ ማርያም ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
#rthiopia | በቦሬ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንደ ጽኑ ዋርካ በመሆን ለሃምሳ ዓመታት ያህል ያለመታከትና በታላቅ ፍቅር ሕዝበ ክርስቲያንን ሲያገለግሉ የኖሩት ታላቁ አባት መልአከ ገነት ቆሞስ አባ ተስፋ ማርያም ሕይወታቸው አልፏል።
አባታችን ለምዕመናን የእምነት ምሰሶ እና የትሕትና ትልቅ አርአያ ነበሩ።
በቅዱስ ሥፍራው ያሳለፏቸው ረጅም ዘመናት ለሥልጣን ወይም ለምድራዊ ዝና ሳይሆን ለእውነተኛ መንፈሳዊ አገልግሎት የተሰጡ ነበሩ።
ማንኛውንም ዓይነት ፈተናና የሕይወት መከራ ሳይበግራቸው እምነታቸውን ጠብቀው ሐዋርያዊ ሩጫቸውን በድል አጠናቀዋል።
አባታችን በ1977 ዓ.ም መልአከ ገነት የሚለውን የማዕረግ ስም ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ኃይማኖት በብፁዕ አቡነ በርተሎሚዎስ አቅራቢነት አግኝተዋል።
ታላቁ አባት በቀድሞው የሲዳሞ ክፍለ ሀገር ውስጥ በይርጋዓለም፣ በጀምጀም፣ በሻኪሶ፣ በነጌሌ ቦረና፣ በዲላ፣ በይርጋጨፌ፣ በአለታ ወንዶ፣ በቦሬ ቅድስት ማርያም እና በይርባ ሙዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሳይቀሩ ቅዱስ ወንጌልን በመስበክና የሰንበት ትምህርት ቤቶችን በማደራጀት ከልጅነት እስከ እውቀት የደከሙ ታላቅ ሐዋርያ ነበሩ።
ለቤተ ክርስቲያን ካበረከቷቸውና ሁልጊዜም በታሪክ ከሚታወሱት ተግባሮቻቸው መካከል
አንደኛው ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ያሳዩት ጽናትና ታማኝነት ሲሆን፣ ቅዱስ ስፍራውን ሳይለቁ በቅድስና መኖር የሚቻለው በእግዚአብሔር ጸጋ መሆኑን በተግባር አሳይተዋል።
ሁለተኛው ዕድሜያቸው ቢገፋም መንፈሳቸው እየታደሰ ለምዕመናን መጽናናትና ለአገልግሎት ራሳቸውን አሳልፈው መስጠታቸው ነው።
ሦስተኛው ደግሞ ያከናወኑት መንፈሳዊ ተጋድሎ ሁሉ ያለ ምንም ምድራዊ ጥቅም፣ በቅንነትና በንጹሕ ልብ የተመራ መሆኑ ነው።
በአሁኑ ወቅት አባታችን ከዚህ ዓለም ድካምና መከራ አርፈው ወደማያልፈው የቅዱሳን ማረፊያ ተሻግረዋል።
ምንም እንኳ የአካል መለያየታቸው፣ ያሳደገን፣ የመከረንና ያስተማረን ጣፋጭ ምክራቸውን ማጣታችን ልብን የሚነካ ቢሆንም፣ የሠሩት መልካም ሥራ ግን ሁልጊዜም ሕያው ሆኖ ይኖራል።
ያገለገሏት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንና ሕዝበ ክርስቲያኑ የአባታችንን ጸሎትና በረከት እንዲያገኙ እየተመኘን፣ ለእናት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን፣ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለመላው የቦሬ ከተማና የገጠር ሕዝብ መጽናናትን እንመኛለን።
#church #ethiopianorthodox #christianity #memorial #bore #sidamo #orthodox #faith #clergy #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#rthiopia | በቦሬ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንደ ጽኑ ዋርካ በመሆን ለሃምሳ ዓመታት ያህል ያለመታከትና በታላቅ ፍቅር ሕዝበ ክርስቲያንን ሲያገለግሉ የኖሩት ታላቁ አባት መልአከ ገነት ቆሞስ አባ ተስፋ ማርያም ሕይወታቸው አልፏል።
አባታችን ለምዕመናን የእምነት ምሰሶ እና የትሕትና ትልቅ አርአያ ነበሩ።
በቅዱስ ሥፍራው ያሳለፏቸው ረጅም ዘመናት ለሥልጣን ወይም ለምድራዊ ዝና ሳይሆን ለእውነተኛ መንፈሳዊ አገልግሎት የተሰጡ ነበሩ።
ማንኛውንም ዓይነት ፈተናና የሕይወት መከራ ሳይበግራቸው እምነታቸውን ጠብቀው ሐዋርያዊ ሩጫቸውን በድል አጠናቀዋል።
አባታችን በ1977 ዓ.ም መልአከ ገነት የሚለውን የማዕረግ ስም ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ኃይማኖት በብፁዕ አቡነ በርተሎሚዎስ አቅራቢነት አግኝተዋል።
ታላቁ አባት በቀድሞው የሲዳሞ ክፍለ ሀገር ውስጥ በይርጋዓለም፣ በጀምጀም፣ በሻኪሶ፣ በነጌሌ ቦረና፣ በዲላ፣ በይርጋጨፌ፣ በአለታ ወንዶ፣ በቦሬ ቅድስት ማርያም እና በይርባ ሙዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሳይቀሩ ቅዱስ ወንጌልን በመስበክና የሰንበት ትምህርት ቤቶችን በማደራጀት ከልጅነት እስከ እውቀት የደከሙ ታላቅ ሐዋርያ ነበሩ።
ለቤተ ክርስቲያን ካበረከቷቸውና ሁልጊዜም በታሪክ ከሚታወሱት ተግባሮቻቸው መካከል
አንደኛው ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ያሳዩት ጽናትና ታማኝነት ሲሆን፣ ቅዱስ ስፍራውን ሳይለቁ በቅድስና መኖር የሚቻለው በእግዚአብሔር ጸጋ መሆኑን በተግባር አሳይተዋል።
ሁለተኛው ዕድሜያቸው ቢገፋም መንፈሳቸው እየታደሰ ለምዕመናን መጽናናትና ለአገልግሎት ራሳቸውን አሳልፈው መስጠታቸው ነው።
ሦስተኛው ደግሞ ያከናወኑት መንፈሳዊ ተጋድሎ ሁሉ ያለ ምንም ምድራዊ ጥቅም፣ በቅንነትና በንጹሕ ልብ የተመራ መሆኑ ነው።
በአሁኑ ወቅት አባታችን ከዚህ ዓለም ድካምና መከራ አርፈው ወደማያልፈው የቅዱሳን ማረፊያ ተሻግረዋል።
ምንም እንኳ የአካል መለያየታቸው፣ ያሳደገን፣ የመከረንና ያስተማረን ጣፋጭ ምክራቸውን ማጣታችን ልብን የሚነካ ቢሆንም፣ የሠሩት መልካም ሥራ ግን ሁልጊዜም ሕያው ሆኖ ይኖራል።
ያገለገሏት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንና ሕዝበ ክርስቲያኑ የአባታችንን ጸሎትና በረከት እንዲያገኙ እየተመኘን፣ ለእናት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን፣ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለመላው የቦሬ ከተማና የገጠር ሕዝብ መጽናናትን እንመኛለን።
#church #ethiopianorthodox #christianity #memorial #bore #sidamo #orthodox #faith #clergy #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
5 months ago
አዳም ታደሰ
ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን ፣ መዝገበ-አእምሮ ( የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ ) ፕሮጀክቱ ለአገር የሠሩ ሰዎችን ታሪክ እየሰነደ እንደሆነ ይታወቃል። ይህ ታሪክ በዲጂታል ሚድያዎች ፣በመፅሀፍ፣በድምፅ ትረካና በሌሎችም መንገዶች እየቀረበ እንደሆነ ይታወቃል።በተለይ ጉግል ላይ ታሪካቸው ሲፈለግ የማይገኝ ሰዎች አሁን የሙያ አበርክቷቸው በቀላሉ ኢንተርኔት ላይ በግልፅ ተቀምጦ ይገኛልደ ባለፉት 4 ዓመት ከ 5 ወር ጊዜ ውስጥ የ423 ሰዎችን የሕይወትና የሥራ ታሪክ ለመሰነድ የቻልን ሲሆን 600 ገፅ ባላቸው ሁለት የተለያዩ መፅሐፎች ላይም ታሪኮቹ ዘመን ተሻጋሪ ሆነው እንዲቀመጡ አድርገናል።
ከእነዚህ ውስጥ የሚድያ ሰዎችም ይገኙበታል። አጠቃላይ 74 ከፍተኛ የሚድያ አመራሮች፣ሚኒስትሮች ፣ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የግል ሚድያ መሥራቾች፣ዋና አዘጋጆች እና መካከለኛ አመራሮች ተካተዋል። 35 ያህሉ በዋና ሥራ አስፈጻሚ ደረጃ ያሉ ሲሆን የሁሉም ታሪክ በተሟላ ደረጃ ለመሰነድ ተችሏል። የእነዚህን አመራሮች እና የሚድያ ሰዎች ታሪክ ሰንዶ ለአንባቢ ተደራሽ ማድረግ ፈታኝ ቢሆንም አሳክተነዋል። በዚህ ተግባራችንም ተጠናክረን እንቀጥላለን።
በዚህ ፅሑፍ የሙያ ታሪኩ የሚሰነድለት ባለሙያ ጋዜጠኛ አዳም ታደሠ ነው። አዳም በሚድያ ሥራ 17 ዓመት ያገለገለ ሲሆን ከሪፖርተር እስከ ዳይሬክተር ደረጃ ማደግ የቻለ ነው። በፋና ሚድያ ኮርፖሬሽን እያገለገለ የሚገኘው አዳም በጤና እና በአለምአቀፍ ትንታኔ ሰጭነቱ በአድማጭ ተመልካቾች ከበሬታን አትርፏል። የመዝገበ አእምሮ ( የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ ) የኤዲቶሪያል አባላት በወሰኑት ውሳኔ መሠረት የአዳም ታደሠን የሙያ ታሪክ ለማቅረብ ችለናል። ባለ ታሪኩ አዳም የሰጠውን ማረጋገጫ እና ፈቃደኝነት በመያዝ የሕይወት ታሪኩን ቤርሳቤህ ጌቴ እንደሚከተለው አጠናክራዋለች።
ትውልድ ፣ ልጅነት ትምህርት
የዚህ ባለታሪክ ህይወት የሚጀምረው በታሪካዊቷና የብዙ ባህል መገናኛ በሆነችው የሐረር ከተማ ነው። አዳም ታደሰ ዳኛ ከነበሩት አባቱ አቶ ታደሰ ወንድምአገኘሁ እና ከእናቱ ወይዘሮ የኔነሽ ተፈራ በመጋቢት 17 1970 ዓ.ም ሐረር ላይ ተወለደ። በቤተሰቡ ውስጥ ከታላቅ እህቱ የኋላሸት ታደሰ ጋር ያደገ ሲሆን፣ የልጅነት ጊዜው በሐረር፣ ፈዲስ፣ ዓለማያ፣ ጂጂጋና ድሬደዋ ልዩ ልዩ ትዝታዎች የታጀበ ነበር። ትምህርትን ገና በለጋ እድሜው የጀመረ ሲሆን፣ ቤታቸው እንደ ቤተ-መጻሕፍት (ላይብረሪ) መሆኑና አባቱም ለትምህርት ትልቅ ቦታ መስጠታቸው ለዕውቀት ፍቅር እንዲኖረው አድርጎታል። እንደ ዘመኑ የሐረር ሕጻን በቤተክርስቲያንም በመድረሳም አልፏል፡፡ የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን በፈዲስ አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትሏል።
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ከሐረር እስከ መራቤቴ
አዳም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በጂግጂጋ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤትና በመርሐቤቴ አርበኞች ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ተምሯል፡፡ ከሐረርጌ ወጥቶ የማያውቀው አዳም የ11ኛና 12ኛ ክፍል ትምህርቱን ለመከታተል ከተወለደበትና ከለመደው አካባቢ ለቅቆ ፈፅሞ ወደማያውቀው ቦታ መሄድ የስነልቦና ዝግጅት ለማድረግ ቀላል ባይሆንለትም መራቤቴ ለእርሱ ትምህርት ቤት ብቻ አልነበረችም፤ ማንነቱ የተቀየረባት ልዩ ስፍራ እንጂ።
በሐረር ከተማ ያደገው ወጣት መራቤቴ ሲደርስ ራሱን ለባህሉና ለሕዝቡ ሙሉ በሙሉ አሳልፎ ሰጠ። የአካባቢው ማህበረሰብ ጠንካራነት፣ እንግዳ ተቀባይነትና ትውፊታዊ የአኗኗር ዘይቤ የሐረር ማንነቱን ቀስ በቀስ እንዲረሳው አደረገው። በአነጋገር፣ በአመለካከትና በአቋም ሙሉ በሙሉ "መሬ" (የመራቤቴ ሰው) ሆኖ ወጣ። የሁለት ዓመት ቆይታው በእምነቱም ጠንካራ እንዲሆንና ጽናትን እንዲማር በምሥራቃዊ ማንነቱ ላይ ማእከላዊነትን እንዲደርብ አድርጎታል፡፡ ታሪኩ የተከሰተው ከ30 ዓመታት በፊት ቢሆንም፣ የመራቤቴ ፍቅር ግን ዛሬም በውስጡ አለ። አሁንም ድረስ በሕይወቱ "ምርጥ" የሚላቸውን ጓደኞቹን ያገኘው ከዚያው ከመራቤቴ ቆይታው እንደሆነ በፍቅር ይገልጻል።
ወደ ዩኒቨርስቲ
ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲገባ በልጅነቱ ያልመው የነበረው ጋዜጠኛ ወይም መምህር መሆን ቢሆንም፣ የዩኒቨርሲቲ ምደባው ግን ያልጠበቀው ሆነ። በጎንደር የሕክምና ሳይንስ ኮሌጅ የሜዲካል ላቦራቶሪ ቴክኖሎጂ (Medical Laboratory Technology) ተማሪ ሆኖ ተመደበ። ምንም እንኳን የሕክምናው ዘርፍ የእርሱ የመጀመሪያ ምርጫ ባይሆንም፣ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ በነበረው ቆይታ የሕክምና ሳይንስን ብቻ ሳይሆን፣ እንደነ ሊቀ ሊቃውንት መንክር ካሉ አራት ዐይና የቤተክርስቲያን ሊቃውንትም ዘንድ መንፈሳዊ እውቀትንም በመቅሰም ማንነቱን ይበልጥ አበለጸገ። በነባር ማንነቱ ላይ ሰሜናዊነትን ደርቦ ሌሎች ምርጥ የሕይወት ዘመን ጓደኞችንም አፍርቶ ከጎንደር ሕክምና ኮሌጅ ተመረቀ፡፡ አዳም ሐረር ወለደችኝ፣ መሬ አሳደገችኝ፣ ጎንደር ፈጸመችኝ ማለትን ያዘወትራል፡፡ ሶስቱም ስፍራዎች አሁን ያለኝን ማንነት ያተሙ የሕይወቴ አልፋና ኦሜጋ ናቸው ይላል፡፡
የጤና ባለሙያው አዳም
ሕይወት ከምረቃ በኋላ ለአዳም ፍጹም ያለጠበቀው ስፍራ አውሎታል፤ ወቅቱ የኢትዮ ኤርትራ (በተለምዶ የባድመው) ጦርነት የጀመረበት ወቅት ነበርና አዳም እንደ ጤና ባለሙያነቱ ወደ ጦር ግንባር ዘምቷል፡፡ በቡሬ ግንባር በአዋሽ አርባ ሜካናይዝድ ማሰልጠኛ ውስጥ አገልግሏል፡፡ ለሁለት ዓመታት ብቻ ብሎ መከላከያን የተቀላቀለው አዳም የሠራዊቱ ጀግንነት፣ የሐገር ፍቅር ስሜትና ዲሲፕሊን ገዝቶኝ እዚያው ቀረሁ ይላል፡፡ አዋሽ አርባ ለ5 ዓመታት ያህል፣ በኋላም አዲስ አበባ ማዕከላዊ እዝ 3 ዓመታት ያህል ለሠራዊቱ ህክምናን ሰጥቷል፡፡ በሕይወቱ ከፈጸማቸውም ከሚፈጽማቸውም ሥራዎቹ ሁሉ እጅግ ከፍተኛ ኩራት የሚሰማው መከላከያ ሠራዊትን ያገለገለበትን ግዜ ነው፡፡ የአፋሯ አዋሽ አርባ ሌሎች የሕይወት ዘመን ጓደኞቹንም ያፈራባት ከተማ ናት፡፡ ብዙ ቦታዎችን መርገጡን እንደ እድለኛነት የሚቆጥረው አዳም ከሁሉም ባህል ተቀላቅዬ የተሠራሁ ምርጥ ኢትዮጲያዊ ነኝ ይላል፡፡
የጥንት የጋዜጠኝነት ፍቅሩ በባድመው ጦርነት ግዜ ብቸኛ የመረጃ ምንጩ በነበረው ሬድዮ ፍቅር ተነሳስቶ ጦርነቱ አብቅቶ ሰላም ሲሰፍን ጋዜጠኝነትን እማራለሁ ብሎ እንዲወስን አድርጎታል፡፡ በተለይም ሬድዮ ፋናና የኢትዮጵያ ሬዲዮ ምርጥ የበረሃ ጓደኞቹ ነበሩ፡፡ አዳም በዚያው በመከላከያ ኮሌጅና በሌሎችም ዩኒቨርሲቲዎች የሕክምና ትምህርቱን እንዲቀጥል አድል ቢመቻችለትም፤ ከሕክምናውም ከውትድርናውም አሰናብቱኝ ብሎ ጓዙን ጠቅሎ እንደገና የዩኒቨርሲቲ ትምህርቱን ለመማር አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ገባ፡፡
ፋና የመግባት ህልም እና ከመከላከያ መውጣት
በመከላከያ ውስጥ በነበረው የሥራ ዲሲፕሊንና ብቃት ይወዱት የነበሩት አለቆቹ በሕክምናው እንዲቀጥል ቢለምኑትም እኔ ጋዜጠኛ ነው የምሆነው ትምህርቴን ስጨርስም ፋና እገባለሁ በማለት ተሰናተ፡፡ ቤተሰቡና ጓደኞቹም እንዴት ሕክምናን የመሰለ ሙያ ትተህ ትወጣለህ ቢሉትም፣ ንስሀ አባቱ ሳይቀሩ ይሄ የሰይጣን ፈተና ይሆናልና ጸበል ተጠመቅ ቢሉትም ጋዜጠኝነት የጠራችው አዳም ግን ሁሉን ይቅርታ ጠይቆ ስድስት ኪሎ ፖለቲካ ሳይንስንና ሊትሬቸርን መርጦ ለ5 ዓመታት ያህል ተምሮ በኢትዮጵያ ሚሊኒየም 2000ዓ.ም ዲግሪውን በከፍተኛ ማእረግ ጨርሶ ተመረቀ፡፡
የፋና ቆይታ እና የተማራቸው ተጨማሪ ትምህርቶችእንደ ነፍሴ ነው የምወደው የሚለውን ሬድዮ ጣቢያ ፋናንም በዓመቱ ጥር 2001ዓ.ም ላይ ተቀላቀለ፡፡ ፋናም የቀድሞ ሙያውን ሕክምናን፣ የአሁኑ ሙያውን ፖለቲካ ሳይንስን ታሳቢ በማድረግ የጤና ፕሮግራሞችና የአፍሪካ ፖለቲካ ፕሮግራሞችን እንዲያዘጋጅ መደበው፡፡ ከእነዚህ በተጨማሪም ሌሎች ፕሮግራሞችንም በትጋት ይሰራ ነበር፡፡ ፍኖተ ጤና፣ መድሀኒት፣ የአፍሪካ ማህደር፣ ዓለም በፋና እና ሌሎች ዝግጅቶችም ላይ በስፋት ሠርቷል፡፡ በተለይ ለዜና ልዩ ፍቅር ያለው አዳም 90 ደቂቃ በተሰኘው የፋና ልዩ መለያ በሆነው የዜና ፕሮግራም ላይ ከ12 ዓመታት በላይ እየሰራ ነው፡፡
ሰው መማር ካቆመ ይሞታል የሚል እምነት ያለው አዳም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዲግሪውን በዓለም አቀፍ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ (International Relations and Diplomacy) ሲማር፣ የጤና ትምህርቱን እንዳይረሳውም ከጅማ ዩኒቨርሲቲ በጤና ተግባቦትና ባህርያዊ ሳይንስ (Health Education and Behavioral Science) በመጀመሪያ ዲግሪ (BSc) ተመርቋል፡፡
የሰው ልጅ ሥጋ ብቻ አይደለም ነፍስና መንፈስም ነው የሚለው አዳም ለመንፈሳዊ ሕይወቴ ይጠቅመኛል በማለትም ወደ ነገረ መለኮት ትምህርትም ጎራ ብሏል፡፡ ከቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ በከፍተኛ ማእረግ የነገረ መለኮት (Theology) ትምህርቱን አጠናቋል፤ በዚህም ብቻ ያልረካው አዳም አሜሪካ አገር ከሚገኘው የአጎራ ዩኒቨርሲቲም (Agora University) በነገረ መለኮት/ነገረ ክርስቶስ (Christology) ሁለተኛ ዲግሪውን ሰርቷል፡፡ በቅርቡም በአገር ውስጥ ወይም በውጪ አገር የሶስተኛ ዲግሪውን (Phd) ለመማር እየተዘጋጀ ነው፡፡
በጤና ተግባቦትና የማይተላለፉ በሽታዎች ስርጭት ላይ (Health Communication and Non Communicable Diseases) ላይ ከሰራው የመጀመሪያ ዲግሪ መመረቂያ ጽሁፉ ጀምሮ፣ የውሀ ፖለቲካ (Hydro Politics of Ethiopian Rivers) ፣ መከራና ስደት በሃይማኖት ውስጥ (Suffering and Persecution in Christianity) እንዲሁም ፖለቲካና ነገረ መለኮትን ያዛመደበት (Political Theology in Christianity) የሰራቸው የጥናት ጽሁፎቹ ናቸው፡፡
90 ደቂቃና አዳም የሚነፋፈቁ ጓደኛሞች ናቸው፡፡ በበዙ ትምህርቶች፣ በልምድና በዘወትር ንባብ የዳበረው አዳም የሚያወራው የማያልቅበት የሚያውቀውን ለማስረዳት የማይቦዝን ጋዜጠኛ ነው፡፡ አዳም ታደሰ በፋና ውስጥ በቆየባቸው 17 ዓመታት ውስጥ ከሪፖርተርነት እስከ ዳይሬክተርነት ደርሷል፡፡ የሚዲያ አመራርነትን ሲገልፀው "በመንግስት ፍላጎት፣ በሕዝብ ጥያቄና በጋዜጠኝነት ነፃነት መካከል ሆኖ ሚዛን መጠበቅ መቻል ነው" ይላል፡፡
አዳም ታደሰ በሙያዊ ጉዞው ውስጥም በርካታ የጋዜጠኝነት፣ የፖለቲካ ኮሙኒኬሽንና የአመራር ጥበብ ስልጠናዎችን በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ወስዷል። ከጋዜጠኝነቱ እኩል የሚወደውን መምህርነት በፋና ሥልጠና ማእከል እየተገበረው ሲሆን በሌሎች ተቋማት ግብዣም በኮሚኒኬሽን፣ በሚዲያ፣ በጋዜጠኝነት በጤና፣ በፖለቲካ፣ በአመራርነት በርካታ ስልጠናዎችን እየሰጠ ነው፡፡
ወደ ትዳር ዓለም
"ትምህርት ለትዳር አዘግይቶኛል የሚለው አዳም ከባለቤቱ ከአበራሽ ጥበበ ጋር 12 ዓመታትን በትዳር አሳልፏል፡፡ የ11 ዓመት ሴት ልጅ አባት የሆነው አዳም ልጁ ሐረርን እንድታስታውሰው ድሮ በሚዘፍነው የአሊ ቢራ ዲንቡሼ ገላ ሙዚቃ የተነሳ ድንቡሼ ሲላት መርሐቤቴና ጎንደር ከሄደ በኋላ በሚዘምረው ትንሣኤከ ለእለ አመነ መዝሙር የተነሳ ትንሣኤ ብሏታል፡፡
በቀሪ ዘመኑ ሁሉ ከጋዜጠኝነት መውጣት የማይፈልገው አዳም ሁለት ህልሞች አሉት። የራሱን የሬድዮ ጣቢያ ማቋቋምና ማሠልጠኛ ማዕከል መክፈት፡፡ አዳም አንድ መርህ አለው "ክርስቶስ ዳግመኛ ሲመጣ ትምህርት ስማር እንዲያገኘኝ እፈልጋለሁ" ይላል፡፡
ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን ፣ መዝገበ-አእምሮ ( የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ ) ፕሮጀክቱ ለአገር የሠሩ ሰዎችን ታሪክ እየሰነደ እንደሆነ ይታወቃል። ይህ ታሪክ በዲጂታል ሚድያዎች ፣በመፅሀፍ፣በድምፅ ትረካና በሌሎችም መንገዶች እየቀረበ እንደሆነ ይታወቃል።በተለይ ጉግል ላይ ታሪካቸው ሲፈለግ የማይገኝ ሰዎች አሁን የሙያ አበርክቷቸው በቀላሉ ኢንተርኔት ላይ በግልፅ ተቀምጦ ይገኛልደ ባለፉት 4 ዓመት ከ 5 ወር ጊዜ ውስጥ የ423 ሰዎችን የሕይወትና የሥራ ታሪክ ለመሰነድ የቻልን ሲሆን 600 ገፅ ባላቸው ሁለት የተለያዩ መፅሐፎች ላይም ታሪኮቹ ዘመን ተሻጋሪ ሆነው እንዲቀመጡ አድርገናል።
ከእነዚህ ውስጥ የሚድያ ሰዎችም ይገኙበታል። አጠቃላይ 74 ከፍተኛ የሚድያ አመራሮች፣ሚኒስትሮች ፣ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የግል ሚድያ መሥራቾች፣ዋና አዘጋጆች እና መካከለኛ አመራሮች ተካተዋል። 35 ያህሉ በዋና ሥራ አስፈጻሚ ደረጃ ያሉ ሲሆን የሁሉም ታሪክ በተሟላ ደረጃ ለመሰነድ ተችሏል። የእነዚህን አመራሮች እና የሚድያ ሰዎች ታሪክ ሰንዶ ለአንባቢ ተደራሽ ማድረግ ፈታኝ ቢሆንም አሳክተነዋል። በዚህ ተግባራችንም ተጠናክረን እንቀጥላለን።
በዚህ ፅሑፍ የሙያ ታሪኩ የሚሰነድለት ባለሙያ ጋዜጠኛ አዳም ታደሠ ነው። አዳም በሚድያ ሥራ 17 ዓመት ያገለገለ ሲሆን ከሪፖርተር እስከ ዳይሬክተር ደረጃ ማደግ የቻለ ነው። በፋና ሚድያ ኮርፖሬሽን እያገለገለ የሚገኘው አዳም በጤና እና በአለምአቀፍ ትንታኔ ሰጭነቱ በአድማጭ ተመልካቾች ከበሬታን አትርፏል። የመዝገበ አእምሮ ( የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ ) የኤዲቶሪያል አባላት በወሰኑት ውሳኔ መሠረት የአዳም ታደሠን የሙያ ታሪክ ለማቅረብ ችለናል። ባለ ታሪኩ አዳም የሰጠውን ማረጋገጫ እና ፈቃደኝነት በመያዝ የሕይወት ታሪኩን ቤርሳቤህ ጌቴ እንደሚከተለው አጠናክራዋለች።
ትውልድ ፣ ልጅነት ትምህርት
የዚህ ባለታሪክ ህይወት የሚጀምረው በታሪካዊቷና የብዙ ባህል መገናኛ በሆነችው የሐረር ከተማ ነው። አዳም ታደሰ ዳኛ ከነበሩት አባቱ አቶ ታደሰ ወንድምአገኘሁ እና ከእናቱ ወይዘሮ የኔነሽ ተፈራ በመጋቢት 17 1970 ዓ.ም ሐረር ላይ ተወለደ። በቤተሰቡ ውስጥ ከታላቅ እህቱ የኋላሸት ታደሰ ጋር ያደገ ሲሆን፣ የልጅነት ጊዜው በሐረር፣ ፈዲስ፣ ዓለማያ፣ ጂጂጋና ድሬደዋ ልዩ ልዩ ትዝታዎች የታጀበ ነበር። ትምህርትን ገና በለጋ እድሜው የጀመረ ሲሆን፣ ቤታቸው እንደ ቤተ-መጻሕፍት (ላይብረሪ) መሆኑና አባቱም ለትምህርት ትልቅ ቦታ መስጠታቸው ለዕውቀት ፍቅር እንዲኖረው አድርጎታል። እንደ ዘመኑ የሐረር ሕጻን በቤተክርስቲያንም በመድረሳም አልፏል፡፡ የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን በፈዲስ አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትሏል።
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ከሐረር እስከ መራቤቴ
አዳም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በጂግጂጋ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤትና በመርሐቤቴ አርበኞች ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ተምሯል፡፡ ከሐረርጌ ወጥቶ የማያውቀው አዳም የ11ኛና 12ኛ ክፍል ትምህርቱን ለመከታተል ከተወለደበትና ከለመደው አካባቢ ለቅቆ ፈፅሞ ወደማያውቀው ቦታ መሄድ የስነልቦና ዝግጅት ለማድረግ ቀላል ባይሆንለትም መራቤቴ ለእርሱ ትምህርት ቤት ብቻ አልነበረችም፤ ማንነቱ የተቀየረባት ልዩ ስፍራ እንጂ።
በሐረር ከተማ ያደገው ወጣት መራቤቴ ሲደርስ ራሱን ለባህሉና ለሕዝቡ ሙሉ በሙሉ አሳልፎ ሰጠ። የአካባቢው ማህበረሰብ ጠንካራነት፣ እንግዳ ተቀባይነትና ትውፊታዊ የአኗኗር ዘይቤ የሐረር ማንነቱን ቀስ በቀስ እንዲረሳው አደረገው። በአነጋገር፣ በአመለካከትና በአቋም ሙሉ በሙሉ "መሬ" (የመራቤቴ ሰው) ሆኖ ወጣ። የሁለት ዓመት ቆይታው በእምነቱም ጠንካራ እንዲሆንና ጽናትን እንዲማር በምሥራቃዊ ማንነቱ ላይ ማእከላዊነትን እንዲደርብ አድርጎታል፡፡ ታሪኩ የተከሰተው ከ30 ዓመታት በፊት ቢሆንም፣ የመራቤቴ ፍቅር ግን ዛሬም በውስጡ አለ። አሁንም ድረስ በሕይወቱ "ምርጥ" የሚላቸውን ጓደኞቹን ያገኘው ከዚያው ከመራቤቴ ቆይታው እንደሆነ በፍቅር ይገልጻል።
ወደ ዩኒቨርስቲ
ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲገባ በልጅነቱ ያልመው የነበረው ጋዜጠኛ ወይም መምህር መሆን ቢሆንም፣ የዩኒቨርሲቲ ምደባው ግን ያልጠበቀው ሆነ። በጎንደር የሕክምና ሳይንስ ኮሌጅ የሜዲካል ላቦራቶሪ ቴክኖሎጂ (Medical Laboratory Technology) ተማሪ ሆኖ ተመደበ። ምንም እንኳን የሕክምናው ዘርፍ የእርሱ የመጀመሪያ ምርጫ ባይሆንም፣ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ በነበረው ቆይታ የሕክምና ሳይንስን ብቻ ሳይሆን፣ እንደነ ሊቀ ሊቃውንት መንክር ካሉ አራት ዐይና የቤተክርስቲያን ሊቃውንትም ዘንድ መንፈሳዊ እውቀትንም በመቅሰም ማንነቱን ይበልጥ አበለጸገ። በነባር ማንነቱ ላይ ሰሜናዊነትን ደርቦ ሌሎች ምርጥ የሕይወት ዘመን ጓደኞችንም አፍርቶ ከጎንደር ሕክምና ኮሌጅ ተመረቀ፡፡ አዳም ሐረር ወለደችኝ፣ መሬ አሳደገችኝ፣ ጎንደር ፈጸመችኝ ማለትን ያዘወትራል፡፡ ሶስቱም ስፍራዎች አሁን ያለኝን ማንነት ያተሙ የሕይወቴ አልፋና ኦሜጋ ናቸው ይላል፡፡
የጤና ባለሙያው አዳም
ሕይወት ከምረቃ በኋላ ለአዳም ፍጹም ያለጠበቀው ስፍራ አውሎታል፤ ወቅቱ የኢትዮ ኤርትራ (በተለምዶ የባድመው) ጦርነት የጀመረበት ወቅት ነበርና አዳም እንደ ጤና ባለሙያነቱ ወደ ጦር ግንባር ዘምቷል፡፡ በቡሬ ግንባር በአዋሽ አርባ ሜካናይዝድ ማሰልጠኛ ውስጥ አገልግሏል፡፡ ለሁለት ዓመታት ብቻ ብሎ መከላከያን የተቀላቀለው አዳም የሠራዊቱ ጀግንነት፣ የሐገር ፍቅር ስሜትና ዲሲፕሊን ገዝቶኝ እዚያው ቀረሁ ይላል፡፡ አዋሽ አርባ ለ5 ዓመታት ያህል፣ በኋላም አዲስ አበባ ማዕከላዊ እዝ 3 ዓመታት ያህል ለሠራዊቱ ህክምናን ሰጥቷል፡፡ በሕይወቱ ከፈጸማቸውም ከሚፈጽማቸውም ሥራዎቹ ሁሉ እጅግ ከፍተኛ ኩራት የሚሰማው መከላከያ ሠራዊትን ያገለገለበትን ግዜ ነው፡፡ የአፋሯ አዋሽ አርባ ሌሎች የሕይወት ዘመን ጓደኞቹንም ያፈራባት ከተማ ናት፡፡ ብዙ ቦታዎችን መርገጡን እንደ እድለኛነት የሚቆጥረው አዳም ከሁሉም ባህል ተቀላቅዬ የተሠራሁ ምርጥ ኢትዮጲያዊ ነኝ ይላል፡፡
የጥንት የጋዜጠኝነት ፍቅሩ በባድመው ጦርነት ግዜ ብቸኛ የመረጃ ምንጩ በነበረው ሬድዮ ፍቅር ተነሳስቶ ጦርነቱ አብቅቶ ሰላም ሲሰፍን ጋዜጠኝነትን እማራለሁ ብሎ እንዲወስን አድርጎታል፡፡ በተለይም ሬድዮ ፋናና የኢትዮጵያ ሬዲዮ ምርጥ የበረሃ ጓደኞቹ ነበሩ፡፡ አዳም በዚያው በመከላከያ ኮሌጅና በሌሎችም ዩኒቨርሲቲዎች የሕክምና ትምህርቱን እንዲቀጥል አድል ቢመቻችለትም፤ ከሕክምናውም ከውትድርናውም አሰናብቱኝ ብሎ ጓዙን ጠቅሎ እንደገና የዩኒቨርሲቲ ትምህርቱን ለመማር አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ገባ፡፡
ፋና የመግባት ህልም እና ከመከላከያ መውጣት
በመከላከያ ውስጥ በነበረው የሥራ ዲሲፕሊንና ብቃት ይወዱት የነበሩት አለቆቹ በሕክምናው እንዲቀጥል ቢለምኑትም እኔ ጋዜጠኛ ነው የምሆነው ትምህርቴን ስጨርስም ፋና እገባለሁ በማለት ተሰናተ፡፡ ቤተሰቡና ጓደኞቹም እንዴት ሕክምናን የመሰለ ሙያ ትተህ ትወጣለህ ቢሉትም፣ ንስሀ አባቱ ሳይቀሩ ይሄ የሰይጣን ፈተና ይሆናልና ጸበል ተጠመቅ ቢሉትም ጋዜጠኝነት የጠራችው አዳም ግን ሁሉን ይቅርታ ጠይቆ ስድስት ኪሎ ፖለቲካ ሳይንስንና ሊትሬቸርን መርጦ ለ5 ዓመታት ያህል ተምሮ በኢትዮጵያ ሚሊኒየም 2000ዓ.ም ዲግሪውን በከፍተኛ ማእረግ ጨርሶ ተመረቀ፡፡
የፋና ቆይታ እና የተማራቸው ተጨማሪ ትምህርቶችእንደ ነፍሴ ነው የምወደው የሚለውን ሬድዮ ጣቢያ ፋናንም በዓመቱ ጥር 2001ዓ.ም ላይ ተቀላቀለ፡፡ ፋናም የቀድሞ ሙያውን ሕክምናን፣ የአሁኑ ሙያውን ፖለቲካ ሳይንስን ታሳቢ በማድረግ የጤና ፕሮግራሞችና የአፍሪካ ፖለቲካ ፕሮግራሞችን እንዲያዘጋጅ መደበው፡፡ ከእነዚህ በተጨማሪም ሌሎች ፕሮግራሞችንም በትጋት ይሰራ ነበር፡፡ ፍኖተ ጤና፣ መድሀኒት፣ የአፍሪካ ማህደር፣ ዓለም በፋና እና ሌሎች ዝግጅቶችም ላይ በስፋት ሠርቷል፡፡ በተለይ ለዜና ልዩ ፍቅር ያለው አዳም 90 ደቂቃ በተሰኘው የፋና ልዩ መለያ በሆነው የዜና ፕሮግራም ላይ ከ12 ዓመታት በላይ እየሰራ ነው፡፡
ሰው መማር ካቆመ ይሞታል የሚል እምነት ያለው አዳም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዲግሪውን በዓለም አቀፍ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ (International Relations and Diplomacy) ሲማር፣ የጤና ትምህርቱን እንዳይረሳውም ከጅማ ዩኒቨርሲቲ በጤና ተግባቦትና ባህርያዊ ሳይንስ (Health Education and Behavioral Science) በመጀመሪያ ዲግሪ (BSc) ተመርቋል፡፡
የሰው ልጅ ሥጋ ብቻ አይደለም ነፍስና መንፈስም ነው የሚለው አዳም ለመንፈሳዊ ሕይወቴ ይጠቅመኛል በማለትም ወደ ነገረ መለኮት ትምህርትም ጎራ ብሏል፡፡ ከቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ በከፍተኛ ማእረግ የነገረ መለኮት (Theology) ትምህርቱን አጠናቋል፤ በዚህም ብቻ ያልረካው አዳም አሜሪካ አገር ከሚገኘው የአጎራ ዩኒቨርሲቲም (Agora University) በነገረ መለኮት/ነገረ ክርስቶስ (Christology) ሁለተኛ ዲግሪውን ሰርቷል፡፡ በቅርቡም በአገር ውስጥ ወይም በውጪ አገር የሶስተኛ ዲግሪውን (Phd) ለመማር እየተዘጋጀ ነው፡፡
በጤና ተግባቦትና የማይተላለፉ በሽታዎች ስርጭት ላይ (Health Communication and Non Communicable Diseases) ላይ ከሰራው የመጀመሪያ ዲግሪ መመረቂያ ጽሁፉ ጀምሮ፣ የውሀ ፖለቲካ (Hydro Politics of Ethiopian Rivers) ፣ መከራና ስደት በሃይማኖት ውስጥ (Suffering and Persecution in Christianity) እንዲሁም ፖለቲካና ነገረ መለኮትን ያዛመደበት (Political Theology in Christianity) የሰራቸው የጥናት ጽሁፎቹ ናቸው፡፡
90 ደቂቃና አዳም የሚነፋፈቁ ጓደኛሞች ናቸው፡፡ በበዙ ትምህርቶች፣ በልምድና በዘወትር ንባብ የዳበረው አዳም የሚያወራው የማያልቅበት የሚያውቀውን ለማስረዳት የማይቦዝን ጋዜጠኛ ነው፡፡ አዳም ታደሰ በፋና ውስጥ በቆየባቸው 17 ዓመታት ውስጥ ከሪፖርተርነት እስከ ዳይሬክተርነት ደርሷል፡፡ የሚዲያ አመራርነትን ሲገልፀው "በመንግስት ፍላጎት፣ በሕዝብ ጥያቄና በጋዜጠኝነት ነፃነት መካከል ሆኖ ሚዛን መጠበቅ መቻል ነው" ይላል፡፡
አዳም ታደሰ በሙያዊ ጉዞው ውስጥም በርካታ የጋዜጠኝነት፣ የፖለቲካ ኮሙኒኬሽንና የአመራር ጥበብ ስልጠናዎችን በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ወስዷል። ከጋዜጠኝነቱ እኩል የሚወደውን መምህርነት በፋና ሥልጠና ማእከል እየተገበረው ሲሆን በሌሎች ተቋማት ግብዣም በኮሚኒኬሽን፣ በሚዲያ፣ በጋዜጠኝነት በጤና፣ በፖለቲካ፣ በአመራርነት በርካታ ስልጠናዎችን እየሰጠ ነው፡፡
ወደ ትዳር ዓለም
"ትምህርት ለትዳር አዘግይቶኛል የሚለው አዳም ከባለቤቱ ከአበራሽ ጥበበ ጋር 12 ዓመታትን በትዳር አሳልፏል፡፡ የ11 ዓመት ሴት ልጅ አባት የሆነው አዳም ልጁ ሐረርን እንድታስታውሰው ድሮ በሚዘፍነው የአሊ ቢራ ዲንቡሼ ገላ ሙዚቃ የተነሳ ድንቡሼ ሲላት መርሐቤቴና ጎንደር ከሄደ በኋላ በሚዘምረው ትንሣኤከ ለእለ አመነ መዝሙር የተነሳ ትንሣኤ ብሏታል፡፡
በቀሪ ዘመኑ ሁሉ ከጋዜጠኝነት መውጣት የማይፈልገው አዳም ሁለት ህልሞች አሉት። የራሱን የሬድዮ ጣቢያ ማቋቋምና ማሠልጠኛ ማዕከል መክፈት፡፡ አዳም አንድ መርህ አለው "ክርስቶስ ዳግመኛ ሲመጣ ትምህርት ስማር እንዲያገኘኝ እፈልጋለሁ" ይላል፡፡