1 month ago
ማቲያስ እንዴት ነው?
#ethiopia | ለረጅም ጊዜ በጉዳት ምክንያት ከሜዳ ርቆ የቆየው የቀያይ ሰይጣኖቹ የጥንካሬ ምንጭ ማቲያስ ዴሊት፣ በመጨረሻም ወደ ካሪንግተን የልምምድ ማዕከል ተመልሷል።
ክለቡ ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት፣ ተጨዋቹ የግል ልምምዶችን እና የማገገሚያ እንቅስቃሴዎችን በከፍተኛ ጥንካሬ መጀመሩ ታውቋል።
አሁን ላይ ዴሊት ከክለቡ የህክምና ቡድን ጋር በቅርበት በመሆን የማገገሚያ ሂደቱን እየተከታተለ ይገኛል። ዋነኛው ትኩረቱም የተሟላ የአካል ብቃት ደረጃ ላይ ደርሶ በቶሎ ወደ ዋናው ቡድን ስብስብ መቀላቀል እና ለቡድኑ የሚጠበቀውን ግልጋሎት መስጠት ነው።
የተከላካዩ ወደ ልምምድ መመለስ ለኤሪክ ቴን ሀግ ስብስብ ትልቅ መነቃቃትን እንደሚፈጥር ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#manchesterunited #matthijsdeligt #mufc #epl #footballnews #deligt #oldtrafford #leadtheplot #sportsnews
#ethiopia | ለረጅም ጊዜ በጉዳት ምክንያት ከሜዳ ርቆ የቆየው የቀያይ ሰይጣኖቹ የጥንካሬ ምንጭ ማቲያስ ዴሊት፣ በመጨረሻም ወደ ካሪንግተን የልምምድ ማዕከል ተመልሷል።
ክለቡ ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት፣ ተጨዋቹ የግል ልምምዶችን እና የማገገሚያ እንቅስቃሴዎችን በከፍተኛ ጥንካሬ መጀመሩ ታውቋል።
አሁን ላይ ዴሊት ከክለቡ የህክምና ቡድን ጋር በቅርበት በመሆን የማገገሚያ ሂደቱን እየተከታተለ ይገኛል። ዋነኛው ትኩረቱም የተሟላ የአካል ብቃት ደረጃ ላይ ደርሶ በቶሎ ወደ ዋናው ቡድን ስብስብ መቀላቀል እና ለቡድኑ የሚጠበቀውን ግልጋሎት መስጠት ነው።
የተከላካዩ ወደ ልምምድ መመለስ ለኤሪክ ቴን ሀግ ስብስብ ትልቅ መነቃቃትን እንደሚፈጥር ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#manchesterunited #matthijsdeligt #mufc #epl #footballnews #deligt #oldtrafford #leadtheplot #sportsnews
2 months ago
የኢትዮጵያ የርምጃ አትሌቶች ብራዚል ገቡ
#ethiopia | በደቡብ አሜሪካ ምድር የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ለማውለብለብ የጀግኖቹ ጉዞ ተጀምሯል!
በብራዚል በሚካሄደው የዓለም አትሌቲክስ የእርምጃ ውድድር ላይ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዛሬ ጠዋት ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተነስቷል። ቡድኑ በፌዴሬሽኑ አመራሮች ደማቅ ሽኝት ተደርጎለታል።
ኢትዮጵያን የሚወክሉ ጀግኖች፦
አትሌት ምስጋና ዋቁማ
በፓሪስ ኦሎምፒክ ድንቅ ብቃት ያሳየውና በ20 ኪ.ሜ የሚወዳደረው።
አትሌት ህይወት አምባው
የአፍሪካ ወጣቶች ኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት (በ10 ኪ.ሜ ሴቶች)።
አትሌት አቡዱሰላም አቡዱልወሀብ፦ በድሬደዋና በአዲስ አበባ የወጣቶች ሻምፒዮና አሸናፊ (በ10 ኪ.ሜ ወንዶች)።
ውድድሩ መጪው እሁድ በብራዚል የሚካሄድ ሲሆን፣ አትሌቶቻችን በድል ተመልሰው ሀገራዊ ኩራት እንደሚሆኑ ይጠበቃል።
ለመላው የልዑካን ቡድን መልካም ዕድል እንመኛለን!
#getu #ethiopianathletics #racewalking #worldathletics #brazil2026 #misganawakuma #teamethiopia #sportsnews #addisababa #አትሌቲክስ #እርምጃ #ኢትዮጵያ #ብራዚል #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | በደቡብ አሜሪካ ምድር የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ለማውለብለብ የጀግኖቹ ጉዞ ተጀምሯል!
በብራዚል በሚካሄደው የዓለም አትሌቲክስ የእርምጃ ውድድር ላይ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዛሬ ጠዋት ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተነስቷል። ቡድኑ በፌዴሬሽኑ አመራሮች ደማቅ ሽኝት ተደርጎለታል።
ኢትዮጵያን የሚወክሉ ጀግኖች፦
አትሌት ምስጋና ዋቁማ
በፓሪስ ኦሎምፒክ ድንቅ ብቃት ያሳየውና በ20 ኪ.ሜ የሚወዳደረው።
አትሌት ህይወት አምባው
የአፍሪካ ወጣቶች ኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት (በ10 ኪ.ሜ ሴቶች)።
አትሌት አቡዱሰላም አቡዱልወሀብ፦ በድሬደዋና በአዲስ አበባ የወጣቶች ሻምፒዮና አሸናፊ (በ10 ኪ.ሜ ወንዶች)።
ውድድሩ መጪው እሁድ በብራዚል የሚካሄድ ሲሆን፣ አትሌቶቻችን በድል ተመልሰው ሀገራዊ ኩራት እንደሚሆኑ ይጠበቃል።
ለመላው የልዑካን ቡድን መልካም ዕድል እንመኛለን!
#getu #ethiopianathletics #racewalking #worldathletics #brazil2026 #misganawakuma #teamethiopia #sportsnews #addisababa #አትሌቲክስ #እርምጃ #ኢትዮጵያ #ብራዚል #ጌጡተመስገን #getutemesgen
2 months ago
ስመጥሮቹ የእግርኳስ ከዋክብት ከ "ሌጎ" ማስታወቂያ ስንት ተከፈላቸው?
#ethiopia | ግዙፍ የመጫወቻ አምራች ኩባንያ የሆነው "ሌጎ" (LEGO) የአለም ዋንጫን በማስመልከት በሰራው እና ከፍተኛ ተመልካችን ባገኘው ማስታወቂያ ላይ ለተሳተፉት ስመጥር የእግርኳስ ከዋክብት የከፈለው የገንዘብ መጠን ይፋ ተደረገ።
በማስታወቂያው ላይ ሊዮኔል ሜሲ፣ ክርስቲያኖ ሮናልዶ፣ ኪሊያን ምባፔ እና ቪንሰስ ጁኒየር በአንድ ክፍል ውስጥ ሆነው ይታያሉ።
በተለይም ሊዮኔል ሜሲ በራሱ የኢንስታግራም ማህበራዊ ትስስር ገፅ ላይ ያጋራው ይሄው የቪዲዮ ማስታወቂያ ከ 19 ሚሊዮን በላይ 'ላይክ' (Like) በማግኘት ከፍተኛ ተቀባይነትን አግኝቷል።
ሪፖርቶች እንደሚያመለክቱት ከሆነ፣ ተቋሙ ለነዚህ ከዋክብት በድምሩ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር ክፍያን የፈፀመ ሲሆን፣ ዝርዝሩም እንደሚከተለው ቀርቧል፡
* ክርስቲያኖ ሮናልዶ፡- 3.43 ሚሊዮን ዶላር
* ሊዮኔል ሜሲ፡- 2.59 ሚሊዮን ዶላር
* ኪሊያን ምባፔ፡- 852,000 ዶላር
* ቪንሰስ ጁኒየር፡- 325,000 ዶላር
አንድ አስገራሚ እውነታ ደግሞ ማስታወቂያው በሚቀረፅበት ጊዜ አራቱም ከዋክብት በአካል በአንድ ቦታ ላይ አለመገናኘታቸው ነው። የማስታወቂያው ፕሮዳክሽን ቡድን ቪዲዮውን የበለጠ ተፈጥሯዊ እና እውነተኛ ለማስመሰል ለከዋክብቱ አምሳያ ሰዎችን (stand-ins) በመጠቀም ቀረፃውን እንዳጠናቀቀ ተገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #lego #footballstars #cristianoronaldo #lionelmessi #mbappe #viniciusjr #sportsnews #footballads #sportbusiness
#ethiopia | ግዙፍ የመጫወቻ አምራች ኩባንያ የሆነው "ሌጎ" (LEGO) የአለም ዋንጫን በማስመልከት በሰራው እና ከፍተኛ ተመልካችን ባገኘው ማስታወቂያ ላይ ለተሳተፉት ስመጥር የእግርኳስ ከዋክብት የከፈለው የገንዘብ መጠን ይፋ ተደረገ።
በማስታወቂያው ላይ ሊዮኔል ሜሲ፣ ክርስቲያኖ ሮናልዶ፣ ኪሊያን ምባፔ እና ቪንሰስ ጁኒየር በአንድ ክፍል ውስጥ ሆነው ይታያሉ።
በተለይም ሊዮኔል ሜሲ በራሱ የኢንስታግራም ማህበራዊ ትስስር ገፅ ላይ ያጋራው ይሄው የቪዲዮ ማስታወቂያ ከ 19 ሚሊዮን በላይ 'ላይክ' (Like) በማግኘት ከፍተኛ ተቀባይነትን አግኝቷል።
ሪፖርቶች እንደሚያመለክቱት ከሆነ፣ ተቋሙ ለነዚህ ከዋክብት በድምሩ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር ክፍያን የፈፀመ ሲሆን፣ ዝርዝሩም እንደሚከተለው ቀርቧል፡
* ክርስቲያኖ ሮናልዶ፡- 3.43 ሚሊዮን ዶላር
* ሊዮኔል ሜሲ፡- 2.59 ሚሊዮን ዶላር
* ኪሊያን ምባፔ፡- 852,000 ዶላር
* ቪንሰስ ጁኒየር፡- 325,000 ዶላር
አንድ አስገራሚ እውነታ ደግሞ ማስታወቂያው በሚቀረፅበት ጊዜ አራቱም ከዋክብት በአካል በአንድ ቦታ ላይ አለመገናኘታቸው ነው። የማስታወቂያው ፕሮዳክሽን ቡድን ቪዲዮውን የበለጠ ተፈጥሯዊ እና እውነተኛ ለማስመሰል ለከዋክብቱ አምሳያ ሰዎችን (stand-ins) በመጠቀም ቀረፃውን እንዳጠናቀቀ ተገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #lego #footballstars #cristianoronaldo #lionelmessi #mbappe #viniciusjr #sportsnews #footballads #sportbusiness
2 months ago
"አርሰናልን በመተቸት ምን ይገኛል?" - ጋብሬል ጄሱስ
#ethiopia | ብራዚላዊው የአርሰናል የፊት መስመር አጥቂ ጋብሬል ጄሱስ፤ ክለቡን ያለበቂ ምክንያት በሚጠሉ እና የጨዋታ ስልታቸውን በሚተቹ አካላት ላይ አስተያየቱን ሰጥቷል።
ወደ ኤምሬትስ ካመራበት ጊዜ አንስቶ በብዙዎች ዘንድ በአርሰናል ላይ ያልተገባ ጥላቻ እንዳለ መታዘቡን የገለጸው ጄሱስ፤ "እውነት ለመናገር ምክንያቱ ምን እንደሆነ እስከ አሁን አላውቅም" ሲል ግራ መጋባቱን ተናግሯል።
በተለይም አርሰናል በቆሙ ኳሶች (Set pieces) ላይ ተመስርቶ ግቦችን በማስቆጠሩ በስፋት ለሚነሱበት ትችቶች ምላሽ የሰጠው አጥቂው፤ አላማቸው ማሸነፍ ብቻ እንደሆነ አጽንኦት ሰጥቷል። "የቆመ ኳስ የሊጉን ዋንጫ የሚያመጣልን ከሆነ፣ ሰዎች ስለ እኛ የሚያወሩት ነገር ለማን ግድ ይሰጠዋል?" በማለት አቋሙን አንጸባርቋል።
በመጨረሻም በክለቡ የጨዋታ አቀራረብ ምክንያት ሁሌም ለሚተቿቸው አካላት ምላሻቸው ምን እንደሆነ ለቀረበለት ጥያቄ ጄሱስ ሲመልስ፤ "እንስቆባቸዋለን" በማለት አጭር እና የማያዳግም ምላሽ ሰጥቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #arsenal #gabrieljesus #premierleague #footballnews #gunners #sportsnews
#ethiopia | ብራዚላዊው የአርሰናል የፊት መስመር አጥቂ ጋብሬል ጄሱስ፤ ክለቡን ያለበቂ ምክንያት በሚጠሉ እና የጨዋታ ስልታቸውን በሚተቹ አካላት ላይ አስተያየቱን ሰጥቷል።
ወደ ኤምሬትስ ካመራበት ጊዜ አንስቶ በብዙዎች ዘንድ በአርሰናል ላይ ያልተገባ ጥላቻ እንዳለ መታዘቡን የገለጸው ጄሱስ፤ "እውነት ለመናገር ምክንያቱ ምን እንደሆነ እስከ አሁን አላውቅም" ሲል ግራ መጋባቱን ተናግሯል።
በተለይም አርሰናል በቆሙ ኳሶች (Set pieces) ላይ ተመስርቶ ግቦችን በማስቆጠሩ በስፋት ለሚነሱበት ትችቶች ምላሽ የሰጠው አጥቂው፤ አላማቸው ማሸነፍ ብቻ እንደሆነ አጽንኦት ሰጥቷል። "የቆመ ኳስ የሊጉን ዋንጫ የሚያመጣልን ከሆነ፣ ሰዎች ስለ እኛ የሚያወሩት ነገር ለማን ግድ ይሰጠዋል?" በማለት አቋሙን አንጸባርቋል።
በመጨረሻም በክለቡ የጨዋታ አቀራረብ ምክንያት ሁሌም ለሚተቿቸው አካላት ምላሻቸው ምን እንደሆነ ለቀረበለት ጥያቄ ጄሱስ ሲመልስ፤ "እንስቆባቸዋለን" በማለት አጭር እና የማያዳግም ምላሽ ሰጥቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #arsenal #gabrieljesus #premierleague #footballnews #gunners #sportsnews
Sponsored by
Surafel
2 months ago
የቮሊቦል ባለውለታው ኢንስትራክተር አለማየሁ ሸዋታጠቅ መታሰቢያ ውድድር ተጠናቀቀ
#ethiopia | በኢትዮጵያ ቮሊቦል ስፖርት ታሪክ ውስጥ ጉልህ አሻራ ያሳረፉትና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ150 በላይ በሚሆኑ ሀገራት የአሰልጣኝነት ስልጠና የሰጡት የሲኒየር ኢንተርናሽናል ኢንስትራክተር አለማየሁ ሸዋታጠቅ መታሰቢያ ውድድር ዛሬ በደማቅ ሁኔታ ተጠናቋል።
ኢንስትራክተር አለማየሁ ሸዋታጠቅ ከዚህ ዓለም በሞት ከተለዩ ሦስት ዓመታት የሞላቸው ሲሆን፣ ይህንን የቀድሞ ውጤታማ ስፖርተኛና የዘርፉ ባለውለታ ለመዘከር ሲካሄድ የሰነበተው ውድድር ላለፈው አንድ ሳምንት በበርካታ ክለቦች መካከል ሲካሄድ ቆይቷል።
በኢትዮጵያ ቮሊቦል ፌዴሬሽን አዘጋጅነት ከመጋቢት 5 እሰከ መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ሲደረግ የነበረው ይህ ውድድር በዛሬው የፍጻሜ ጨዋታ በወንዶች መቻል ስፖርት ክለብ እንዲሁም በሴቶች ብሔራዊ አልኮል ስፖርት ክለብ የዋንጫ አሸናፊ መሆናቸውን
አረጋግጠዋል።
በመዝጊያ መርሐግብር ላይ በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ወይዘሮ አበባ አማረ ፣ በባህልና ስፖርት የስፖርት ማህበራት መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳንኤል ዳኜ ፣ የመከላከያ መቻል ስፖርት ክለብ ስራ አስፈፃሚ ብርጋዲየር ጄኔራል ኑሩ ሙዘይን ፣የሲኒየር ኢንተርናሽናል ኢንስትራክተር አለማየሁ ሸዋታጠቅ ባለቤት ወይዘሮ ትዝታ አባተ ጫኔ እና የኢትዮጵያ ቮሊቦል ፌዴሬሽን አመራሮች በመገኘት ለአሸናፊዎች የዋንጫና የሜዳሊያ ሽልማት አበርክተዋል።
የዕለቱ የክብር እንግዶች ለኮከብ ተጫዋቾችና አሰልጣኞች ልዩ እውቅና የሰጡ ሲሆን፣ ውድድሩ የኢንስትራክተሩን ሙያዊ ተጋድሎ ከማስታወስ ባለፈ በክለቦች መካከል ያለውን የተቀናጀ ስፖርታዊ መንፈስ ይበልጥ እንዲጎለብት ማድረጉ ተገልጿል።
በተለይም በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር እና በቮሊቦል ፌዴሬሽን በኩል የተገኙት ከፍተኛ አመራሮች በዓለም አቀፍ ደረጃ ሀገራቸውን ያስጠሩ ባለሙያዎችን እንዲህ ባለ ደማቅ መድረክ መዘከር ለቀጣዩ ትውልድ ትልቅ መነሳሳትን እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
ጌጡ ተመስገን (Getu Temesgen
#getutemesgen #ethiopianvolleyball #instructoralemayehu #volleyballethiopia #sportsnews #addisababa #ethiopia #mechal #nationalalcohol
#ethiopia | በኢትዮጵያ ቮሊቦል ስፖርት ታሪክ ውስጥ ጉልህ አሻራ ያሳረፉትና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ150 በላይ በሚሆኑ ሀገራት የአሰልጣኝነት ስልጠና የሰጡት የሲኒየር ኢንተርናሽናል ኢንስትራክተር አለማየሁ ሸዋታጠቅ መታሰቢያ ውድድር ዛሬ በደማቅ ሁኔታ ተጠናቋል።
ኢንስትራክተር አለማየሁ ሸዋታጠቅ ከዚህ ዓለም በሞት ከተለዩ ሦስት ዓመታት የሞላቸው ሲሆን፣ ይህንን የቀድሞ ውጤታማ ስፖርተኛና የዘርፉ ባለውለታ ለመዘከር ሲካሄድ የሰነበተው ውድድር ላለፈው አንድ ሳምንት በበርካታ ክለቦች መካከል ሲካሄድ ቆይቷል።
በኢትዮጵያ ቮሊቦል ፌዴሬሽን አዘጋጅነት ከመጋቢት 5 እሰከ መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ሲደረግ የነበረው ይህ ውድድር በዛሬው የፍጻሜ ጨዋታ በወንዶች መቻል ስፖርት ክለብ እንዲሁም በሴቶች ብሔራዊ አልኮል ስፖርት ክለብ የዋንጫ አሸናፊ መሆናቸውን
አረጋግጠዋል።
በመዝጊያ መርሐግብር ላይ በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የስፖርት ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ወይዘሮ አበባ አማረ ፣ በባህልና ስፖርት የስፖርት ማህበራት መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳንኤል ዳኜ ፣ የመከላከያ መቻል ስፖርት ክለብ ስራ አስፈፃሚ ብርጋዲየር ጄኔራል ኑሩ ሙዘይን ፣የሲኒየር ኢንተርናሽናል ኢንስትራክተር አለማየሁ ሸዋታጠቅ ባለቤት ወይዘሮ ትዝታ አባተ ጫኔ እና የኢትዮጵያ ቮሊቦል ፌዴሬሽን አመራሮች በመገኘት ለአሸናፊዎች የዋንጫና የሜዳሊያ ሽልማት አበርክተዋል።
የዕለቱ የክብር እንግዶች ለኮከብ ተጫዋቾችና አሰልጣኞች ልዩ እውቅና የሰጡ ሲሆን፣ ውድድሩ የኢንስትራክተሩን ሙያዊ ተጋድሎ ከማስታወስ ባለፈ በክለቦች መካከል ያለውን የተቀናጀ ስፖርታዊ መንፈስ ይበልጥ እንዲጎለብት ማድረጉ ተገልጿል።
በተለይም በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር እና በቮሊቦል ፌዴሬሽን በኩል የተገኙት ከፍተኛ አመራሮች በዓለም አቀፍ ደረጃ ሀገራቸውን ያስጠሩ ባለሙያዎችን እንዲህ ባለ ደማቅ መድረክ መዘከር ለቀጣዩ ትውልድ ትልቅ መነሳሳትን እንደሚፈጥር ገልጸዋል።
ጌጡ ተመስገን (Getu Temesgen
#getutemesgen #ethiopianvolleyball #instructoralemayehu #volleyballethiopia #sportsnews #addisababa #ethiopia #mechal #nationalalcohol
3 months ago
ኢራን የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎቿን ከአሜሪካ ወደ ሜክሲኮ ለማዛወር ከፊፋ ጋር እየተደራደረች ነው
#ethiopia | በፖለቲካዊ ውጥረትና በደህንነት ስጋት ምክንያት የኢራን እግር ኳስ ማህበር የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎቹን በአሜሪካ ምትክ በሜክሲኮ ለማከናወን ጥያቄ ማቅረቡ ተሰማ። የኢራን እግር ኳስ ማህበር ፕሬዝዳንት መህዲ ታጅ እንደገለጹት፣ የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ለኢራን ብሔራዊ ቡድን በቂ የደህንነት ዋስትና ለመስጠት ፈቃደኛ ባለመሆኑ ቡድኑ ወደ አሜሪካ የመጓዝ ዕቅድ የለውም።
ፕሬዝዳንቱ በኤክስ (X) ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ "ትራምፕ ለቡድናችን ደህንነት ማረጋገጫ ባልሰጡበት ሁኔታ ወደ አሜሪካ መጓዝ አንችልም" ያሉ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ጨዋታዎቹን ወደ ሜክሲኮ ለማዛወር ከዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) ጋር ንግግር እየተደረገ መሆኑን ይፋ አድርገዋል።
ይህ ውሳኔ የተሰማው የኢራን ስፖርት ሚኒስትር አሜሪካና እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት ከሰነዘሩ በኋላ በውድድሩ ላይ መሳተፍ አጠራጣሪ መሆኑን በገለጹ ማግስት ነው።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በበኩላቸው ኢራን መሳተፍ እንደምትችል ቢገልጹም፣ "ለራሳቸው ደህንነት ሲሉ ባይመጡ ይሻላል" የሚል ይዘት ያለው ማስጠንቀቂያ መስጠታቸው ይታወሳል።
እንደ መጀመሪያው መርሃ ግብር ኢራን ሁለት የምድብ ጨዋታዎቿን በሎስ አንጀለስ፣ ቀሪውን አንድ ጨዋታ ደግሞ በሲያትል ለማከናወን ተመድባ ነበር። አሁን በቀረበው ጥያቄ ላይ ፊፋ የሚሰጠው ምላሽ በጉጉት እየተጠበቀ ይገኛል::
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #worldcup2026 #fifa #iranfootball #mexico2026 #sportsnews #breakingnews #footballpolitics
#ethiopia | በፖለቲካዊ ውጥረትና በደህንነት ስጋት ምክንያት የኢራን እግር ኳስ ማህበር የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎቹን በአሜሪካ ምትክ በሜክሲኮ ለማከናወን ጥያቄ ማቅረቡ ተሰማ። የኢራን እግር ኳስ ማህበር ፕሬዝዳንት መህዲ ታጅ እንደገለጹት፣ የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ለኢራን ብሔራዊ ቡድን በቂ የደህንነት ዋስትና ለመስጠት ፈቃደኛ ባለመሆኑ ቡድኑ ወደ አሜሪካ የመጓዝ ዕቅድ የለውም።
ፕሬዝዳንቱ በኤክስ (X) ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ "ትራምፕ ለቡድናችን ደህንነት ማረጋገጫ ባልሰጡበት ሁኔታ ወደ አሜሪካ መጓዝ አንችልም" ያሉ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ጨዋታዎቹን ወደ ሜክሲኮ ለማዛወር ከዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) ጋር ንግግር እየተደረገ መሆኑን ይፋ አድርገዋል።
ይህ ውሳኔ የተሰማው የኢራን ስፖርት ሚኒስትር አሜሪካና እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት ከሰነዘሩ በኋላ በውድድሩ ላይ መሳተፍ አጠራጣሪ መሆኑን በገለጹ ማግስት ነው።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በበኩላቸው ኢራን መሳተፍ እንደምትችል ቢገልጹም፣ "ለራሳቸው ደህንነት ሲሉ ባይመጡ ይሻላል" የሚል ይዘት ያለው ማስጠንቀቂያ መስጠታቸው ይታወሳል።
እንደ መጀመሪያው መርሃ ግብር ኢራን ሁለት የምድብ ጨዋታዎቿን በሎስ አንጀለስ፣ ቀሪውን አንድ ጨዋታ ደግሞ በሲያትል ለማከናወን ተመድባ ነበር። አሁን በቀረበው ጥያቄ ላይ ፊፋ የሚሰጠው ምላሽ በጉጉት እየተጠበቀ ይገኛል::
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #worldcup2026 #fifa #iranfootball #mexico2026 #sportsnews #breakingnews #footballpolitics
3 months ago
የዛሬው የደመቀ የእግር ኳስ ምሽት! ⚽️
#ethiopia | በአገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ መድረክ ተጠባቂ የሆኑ ታላላቅ ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ ተብሎ ይጠበቃል። የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ፍልሚያዎች ከሰዓት በጉጉት ሲጠበቁ፣ ምሽቱን ደግሞ የአውሮፓ ሀያላን ክለቦች እርስ በእርስ የሚፋለሙበት ልዩ መርሃ ግብር ተዘጋጅቷል።
የዛሬ ተጠባቂ ጨዋታዎች ዝርዝር፦
በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ
* 10:00 | አዳማ ከተማ ከ አርባምንጭ ከተማ
* 10:00 | ሀዋሳ ከተማ ከ መቐለ 70 እንደርታ
በዓለም አቀፍ መድረክ
* 2:45 | ጋላታሳራይ ከ ሊቨርፑል
* 5:00 | አታላንታ ከ ባየር ሙኒክ
* 5:00 | አትሌቲኮ ማድሪድ ከ ቶተንሀም
* 5:00 | ኒውካስል ዩናይትድ ከ ባርሴሎና
ለኳስ አፍቃሪያን ድንቅ ምሽት ይሁንላችሁ!
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiopianpremierleague #football #matchday #liverpool #barcelona #bayernmunich #sportsnews #አዳማ #ሀዋሳ #የዛሬጨዋታዎች
#ethiopia | በአገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ መድረክ ተጠባቂ የሆኑ ታላላቅ ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ ተብሎ ይጠበቃል። የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ፍልሚያዎች ከሰዓት በጉጉት ሲጠበቁ፣ ምሽቱን ደግሞ የአውሮፓ ሀያላን ክለቦች እርስ በእርስ የሚፋለሙበት ልዩ መርሃ ግብር ተዘጋጅቷል።
የዛሬ ተጠባቂ ጨዋታዎች ዝርዝር፦
በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ
* 10:00 | አዳማ ከተማ ከ አርባምንጭ ከተማ
* 10:00 | ሀዋሳ ከተማ ከ መቐለ 70 እንደርታ
በዓለም አቀፍ መድረክ
* 2:45 | ጋላታሳራይ ከ ሊቨርፑል
* 5:00 | አታላንታ ከ ባየር ሙኒክ
* 5:00 | አትሌቲኮ ማድሪድ ከ ቶተንሀም
* 5:00 | ኒውካስል ዩናይትድ ከ ባርሴሎና
ለኳስ አፍቃሪያን ድንቅ ምሽት ይሁንላችሁ!
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiopianpremierleague #football #matchday #liverpool #barcelona #bayernmunich #sportsnews #አዳማ #ሀዋሳ #የዛሬጨዋታዎች
3 months ago
ዩናይትድ በካዝናው በኩል ድል እየተቀዳጀ ነው
#ethiopia | ማንችስተር ዩናይትድ በሜዳ ላይ ውጤቱ ላይ መዋዥቅ ቢታይበትም፣ በካዝናው በኩል ግን ብርቅዬ የሆነ ስኬት እያገኘ መሆኑን ይፋ አድርጓል። ክለቡ ባወጣው የሁለተኛው ሩብ ዓመት የፋይናንስ ሪፖርት፣ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር አስገራሚ የትርፍ ጭማሪ ማሳየቱን አስታውቋል።
የቁጥሮቹ ይናገራሉ፦ ካለፈው ዓመት እስከ ዛሬ
የክለቡ የፋይናንስ ጉዞ በቁጥር ሲሰላ እንዲህ ይመስላል፦
* የሩብ ዓመቱ ትርፍ፦ በዚህ ሩብ ዓመት 19.6 ሚሊዮን ፓውንድ ትርፍ ተመዝግቧል። ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት (3.1 ሚሊዮን ፓውንድ) ጋር ሲነፃፀር እጅግ ግዙፍ ጭማሪ ነው
* የስድስት ወራት ድምር፦ ክለቡ በመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ያስመዘገበው ጠቅላላ ትርፍ ወደ 32.2 ሚሊዮን ፓውንድ ከፍ ብሏል።
* ከኪሳራ ወደ ትርፍ፦ የሚገርመው ግን፣ ባለፈው ዓመት በዚህ ወቅት ክለቡ 3.9 ሚሊዮን ፓውንድ ኪሳራ ላይ ነበር። በአንድ ዓመት ውስጥ እንዲህ ተገልብጦ ትርፍ ላይ መገኘቱ የክለቡን ጥንካሬ ያሳያል።
"የቁጠባው መርሐግብር ፍሬ እያፈራ ነው" — ኦማር ቤራዳ
የክለቡ የበላይ ኃላፊ ኦማር ቤራዳ እንደገለጹት፣ ይህ ውጤት እንዲሁ በአጋጣሚ የመጣ አይደለም። ክለቡ ከሜዳ ውጪ የወሰዳቸው "የወጪ ቅነሳ እርምጃዎች" እና መዋቅራዊ ለውጦች ውጤት ማምጣት መጀመራቸውን ገልጸዋል።
እንደ ቤራዳ እምነት፣ ይህ የፋይናንስ ጥንካሬ በቀጣይ በሜዳ ላይ ለሚኖረው ውጤትም መሰረት ይሆናል። ዩናይትድ አላስፈላጊ ወጪዎችን በመቀነስና የገቢ ምንጮቹን በማጠናከር ወደ ቀድሞ ግርማ ሞገሱ ለመመለስ በዝግጅት ላይ መሆኑን ሪፖርቱ ይጠቁማል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #manutd #mufc #manchesterunited #finance #sportsnews #ኦማር_ቤራዳ #ማንችስተር_ዩናይትድ #ትርፍ
#ethiopia | ማንችስተር ዩናይትድ በሜዳ ላይ ውጤቱ ላይ መዋዥቅ ቢታይበትም፣ በካዝናው በኩል ግን ብርቅዬ የሆነ ስኬት እያገኘ መሆኑን ይፋ አድርጓል። ክለቡ ባወጣው የሁለተኛው ሩብ ዓመት የፋይናንስ ሪፖርት፣ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር አስገራሚ የትርፍ ጭማሪ ማሳየቱን አስታውቋል።
የቁጥሮቹ ይናገራሉ፦ ካለፈው ዓመት እስከ ዛሬ
የክለቡ የፋይናንስ ጉዞ በቁጥር ሲሰላ እንዲህ ይመስላል፦
* የሩብ ዓመቱ ትርፍ፦ በዚህ ሩብ ዓመት 19.6 ሚሊዮን ፓውንድ ትርፍ ተመዝግቧል። ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት (3.1 ሚሊዮን ፓውንድ) ጋር ሲነፃፀር እጅግ ግዙፍ ጭማሪ ነው
* የስድስት ወራት ድምር፦ ክለቡ በመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ያስመዘገበው ጠቅላላ ትርፍ ወደ 32.2 ሚሊዮን ፓውንድ ከፍ ብሏል።
* ከኪሳራ ወደ ትርፍ፦ የሚገርመው ግን፣ ባለፈው ዓመት በዚህ ወቅት ክለቡ 3.9 ሚሊዮን ፓውንድ ኪሳራ ላይ ነበር። በአንድ ዓመት ውስጥ እንዲህ ተገልብጦ ትርፍ ላይ መገኘቱ የክለቡን ጥንካሬ ያሳያል።
"የቁጠባው መርሐግብር ፍሬ እያፈራ ነው" — ኦማር ቤራዳ
የክለቡ የበላይ ኃላፊ ኦማር ቤራዳ እንደገለጹት፣ ይህ ውጤት እንዲሁ በአጋጣሚ የመጣ አይደለም። ክለቡ ከሜዳ ውጪ የወሰዳቸው "የወጪ ቅነሳ እርምጃዎች" እና መዋቅራዊ ለውጦች ውጤት ማምጣት መጀመራቸውን ገልጸዋል።
እንደ ቤራዳ እምነት፣ ይህ የፋይናንስ ጥንካሬ በቀጣይ በሜዳ ላይ ለሚኖረው ውጤትም መሰረት ይሆናል። ዩናይትድ አላስፈላጊ ወጪዎችን በመቀነስና የገቢ ምንጮቹን በማጠናከር ወደ ቀድሞ ግርማ ሞገሱ ለመመለስ በዝግጅት ላይ መሆኑን ሪፖርቱ ይጠቁማል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #manutd #mufc #manchesterunited #finance #sportsnews #ኦማር_ቤራዳ #ማንችስተር_ዩናይትድ #ትርፍ
Sponsored by
Surafel
4 months ago
የ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ወደ 2028 ሊራዘም ይችላል? ኬንያ የጸጥታ ስጋት እንዳለባት ገለጸች
#ethiopia | በጋራ አዘጋጅነት የተረከቡት የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት (ኬንያ፣ ዩጋንዳ እና ታንዛኒያ) ታሪክ ለመስራት እየተዘጋጁ ቢሆንም፣ ውድድሩ የአንድ ዓመት መራዘም ሊገጥመው እንደሚችል ፍንጮች እየታዩ ነው።
ለምን ሊራዘም ይችላል?
ዋናው ምክንያት የኬንያ ሀገራዊ ምርጫ ነው። እ.ኤ.አ በ2027 ኬንያ ጠቅላይ ምርጫ የምታካሂድ በመሆኑ፣ የሀገሪቱ የጸጥታ ሁኔታ ለትልቅ ስፖርታዊ ውድድር አስተማማኝ ላይሆን ይችላል የሚል ስጋት ተፈጥሯል።
የኬንያ የአዘጋጅ ኮሚቴ ሊቀመንበር ኒኮላስ ሙሶንዬ በጉዳዩ ላይ ሲናገሩ፦
> "በምርጫ ወቅት የደህንነት ሁኔታው አስተማማኝ ስለማይሆን፣ ውድድሩ ወደ 2028 ቢራዘም ለኬንያ መልካም ነው" ብለዋል።
>
የካፍ (CAF) ምላሽ ምን ሊሆን ይችላል?
የአፍሪካ እግርኳስ ኮንፌዴሬሽን (CAF) ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ዛሬ በታንዛኒያ ዳሬሰላም በሚያደርገው ስብሰባ በዚህ አጀንዳ ላይ በጥልቅ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል። ካፍ የኬንያን ጥያቄ ተቀብሎ ውድድሩን ያራዝመዋል ወይንስ ሌሎች አማራጮችን ይፈልጋል? የሚለው ጉዳይ የብዙዎችን ትኩረት ስቧል።
ውድድሩ የሚራዘም ከሆነ በዩጋንዳ እና ታንዛኒያ ዝግጅት ላይም የራሱ የሆነ ጫና ማሳረፉ አይቀሬ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #afcon2027 #caf #kenya #tanzania #uganda #africanfootball #sportsnews #pamojabid #የአፍሪካዋንጫ #ኬንያ
#ethiopia | በጋራ አዘጋጅነት የተረከቡት የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት (ኬንያ፣ ዩጋንዳ እና ታንዛኒያ) ታሪክ ለመስራት እየተዘጋጁ ቢሆንም፣ ውድድሩ የአንድ ዓመት መራዘም ሊገጥመው እንደሚችል ፍንጮች እየታዩ ነው።
ለምን ሊራዘም ይችላል?
ዋናው ምክንያት የኬንያ ሀገራዊ ምርጫ ነው። እ.ኤ.አ በ2027 ኬንያ ጠቅላይ ምርጫ የምታካሂድ በመሆኑ፣ የሀገሪቱ የጸጥታ ሁኔታ ለትልቅ ስፖርታዊ ውድድር አስተማማኝ ላይሆን ይችላል የሚል ስጋት ተፈጥሯል።
የኬንያ የአዘጋጅ ኮሚቴ ሊቀመንበር ኒኮላስ ሙሶንዬ በጉዳዩ ላይ ሲናገሩ፦
> "በምርጫ ወቅት የደህንነት ሁኔታው አስተማማኝ ስለማይሆን፣ ውድድሩ ወደ 2028 ቢራዘም ለኬንያ መልካም ነው" ብለዋል።
>
የካፍ (CAF) ምላሽ ምን ሊሆን ይችላል?
የአፍሪካ እግርኳስ ኮንፌዴሬሽን (CAF) ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ዛሬ በታንዛኒያ ዳሬሰላም በሚያደርገው ስብሰባ በዚህ አጀንዳ ላይ በጥልቅ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል። ካፍ የኬንያን ጥያቄ ተቀብሎ ውድድሩን ያራዝመዋል ወይንስ ሌሎች አማራጮችን ይፈልጋል? የሚለው ጉዳይ የብዙዎችን ትኩረት ስቧል።
ውድድሩ የሚራዘም ከሆነ በዩጋንዳ እና ታንዛኒያ ዝግጅት ላይም የራሱ የሆነ ጫና ማሳረፉ አይቀሬ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #afcon2027 #caf #kenya #tanzania #uganda #africanfootball #sportsnews #pamojabid #የአፍሪካዋንጫ #ኬንያ
4 months ago
🎾 ኖቫክ ጆኮቪች ለ11ኛ ጊዜ ለአውስትራሊያ ኦፕን ፍፃሜ ደረሰ! 🔥
#ethiopia | "የ38 ዓመቱ ጆኮቪች የአምናውን ሻምፒዮን ያኒክ ሲነርን 3-2 በመርታት ተአምሩን ቀጥሏል"
ሰርቢያዊው የቴኒስ ኮከብ ኖቫክ ጆኮቪች፤ በአውስትራሊያ ኦፕን የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ የአምናውን ሻምፒዮን ጣሊያናዊውን ያኒክ ሲነርን በድምር ውጤት 3 ለ 2 በሆነ ጠባብ ውጤት በማሸነፍ ለፍፃሜ አልፏል።
የድሉ ትርጉም:
✅ ይህ ለጆኮቪች 11ኛው የአውስትራሊያ ኦፕን ፍፃሜ ነው።
✅ በ38 ዓመት እድሜው አሁንም በከፍተኛ ብቃት ላይ እንደሚገኝ አስመስክሯል።
የእሁዱ ታላቅ ፍልሚያ:
በፍፃሜው ጨዋታ ጆኮቪች ከወቅቱ የዓለም ቁጥር አንድ ስፔናዊው ካርሎስ አልካራዝ ጋር እሁድ ይፋጠጣሉ።
ልምድ ወይስ ወጣትነት? እሁድ ማን የሚያሸንፍ ይመስላችኋል?
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#australianopen2026 #djokovic #alcaraz #tennis #grandslam #final #sportsnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
#ethiopia | "የ38 ዓመቱ ጆኮቪች የአምናውን ሻምፒዮን ያኒክ ሲነርን 3-2 በመርታት ተአምሩን ቀጥሏል"
ሰርቢያዊው የቴኒስ ኮከብ ኖቫክ ጆኮቪች፤ በአውስትራሊያ ኦፕን የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ የአምናውን ሻምፒዮን ጣሊያናዊውን ያኒክ ሲነርን በድምር ውጤት 3 ለ 2 በሆነ ጠባብ ውጤት በማሸነፍ ለፍፃሜ አልፏል።
የድሉ ትርጉም:
✅ ይህ ለጆኮቪች 11ኛው የአውስትራሊያ ኦፕን ፍፃሜ ነው።
✅ በ38 ዓመት እድሜው አሁንም በከፍተኛ ብቃት ላይ እንደሚገኝ አስመስክሯል።
የእሁዱ ታላቅ ፍልሚያ:
በፍፃሜው ጨዋታ ጆኮቪች ከወቅቱ የዓለም ቁጥር አንድ ስፔናዊው ካርሎስ አልካራዝ ጋር እሁድ ይፋጠጣሉ።
ልምድ ወይስ ወጣትነት? እሁድ ማን የሚያሸንፍ ይመስላችኋል?
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#australianopen2026 #djokovic #alcaraz #tennis #grandslam #final #sportsnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
4 months ago
🏆 የ2030 ዓለም ዋንጫ ፍፃሜ፦ ስፔን ወይስ ሞሮኮ? ፍጥጫው በርትቷል!
#ethiopia | የ2030 ዓለም ዋንጫን በጋራ የሚያዘጋጁት ሀገራት በፍፃሜው ጨዋታ ቦታ ላይ መስማማት አልቻሉም። የስፔን እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ራፋኤል ሉዛን ጨዋታው በስፔን እንደሚካሄድ በልበ ሙሉነት ተናግረዋል።
"ፍፃሜው ስፔን ውስጥ ይደረጋል!"
ፕሬዝዳንት ሉዛን ስፔን ውድድሩን የማዘጋጀት ብቃቷን ያረጋገጠች ሀገር መሆኗን ገልጸው፣ ሞሮኮን ግን በጠንካራ ቃላት ተችተዋል። ፕሬዝዳንቱ በቅርቡ በሞሮኮ በተካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ የታዩ ክስተቶችን በማንሳት፣ "የዓለም እግር ኳስን ገጽታ ያበላሹ ነገሮችን ተመልክተናል" ሲሉ የሞሮኮን ብቃት ጥያቄ ውስጥ ከትተዋል።
የስታዲየሞች ክፍፍል፦
ለ2030 ዓለም ዋንጫ የተመደቡት ስታዲየሞች ብዛትም የስፔንን የበላይነት ያሳያል ተብሏል፦
* ስፔን፦ በ11 ስታዲየሞች (አብዛኛውን ጨዋታ ታስተናግዳለች)
* ሞሮኮ፦ በ6 ስታዲየሞች
* ፖርቹጋል፦ በ3 ስታዲየሞች
ሞሮኮ በበኩሏ ለፍፃሜው ጨዋታ የሚሆን እጅግ ግዙፍ እና ዘመናዊ ስታዲየም እየገነባች መሆኗ የሚታወቅ ሲሆን፣ ይህ የፕሬዝዳንቱ ንግግር በሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ እና ስፖርታዊ ግንኙነት ላይ ምን ዓይነት ተጽዕኖ እንደሚፈጥር በጉጉት የሚጠበቅ ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#worldcup2030 #spain #morocco #portugal #fifa #footballnews #rafaelluzan #worldcupfinal #ethiopia #sportsnews
#ethiopia | የ2030 ዓለም ዋንጫን በጋራ የሚያዘጋጁት ሀገራት በፍፃሜው ጨዋታ ቦታ ላይ መስማማት አልቻሉም። የስፔን እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ራፋኤል ሉዛን ጨዋታው በስፔን እንደሚካሄድ በልበ ሙሉነት ተናግረዋል።
"ፍፃሜው ስፔን ውስጥ ይደረጋል!"
ፕሬዝዳንት ሉዛን ስፔን ውድድሩን የማዘጋጀት ብቃቷን ያረጋገጠች ሀገር መሆኗን ገልጸው፣ ሞሮኮን ግን በጠንካራ ቃላት ተችተዋል። ፕሬዝዳንቱ በቅርቡ በሞሮኮ በተካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ላይ የታዩ ክስተቶችን በማንሳት፣ "የዓለም እግር ኳስን ገጽታ ያበላሹ ነገሮችን ተመልክተናል" ሲሉ የሞሮኮን ብቃት ጥያቄ ውስጥ ከትተዋል።
የስታዲየሞች ክፍፍል፦
ለ2030 ዓለም ዋንጫ የተመደቡት ስታዲየሞች ብዛትም የስፔንን የበላይነት ያሳያል ተብሏል፦
* ስፔን፦ በ11 ስታዲየሞች (አብዛኛውን ጨዋታ ታስተናግዳለች)
* ሞሮኮ፦ በ6 ስታዲየሞች
* ፖርቹጋል፦ በ3 ስታዲየሞች
ሞሮኮ በበኩሏ ለፍፃሜው ጨዋታ የሚሆን እጅግ ግዙፍ እና ዘመናዊ ስታዲየም እየገነባች መሆኗ የሚታወቅ ሲሆን፣ ይህ የፕሬዝዳንቱ ንግግር በሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ እና ስፖርታዊ ግንኙነት ላይ ምን ዓይነት ተጽዕኖ እንደሚፈጥር በጉጉት የሚጠበቅ ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#worldcup2030 #spain #morocco #portugal #fifa #footballnews #rafaelluzan #worldcupfinal #ethiopia #sportsnews
4 months ago
🇰🇼 የኩዌት እግር ኳስ ፌዴሬሽን የማንችስተር ዩናይትድ እና የኢንተር ሚያሚን ጥያቄ "ለአሁኑ አይሆንም" አለ!
#ethiopia | ታላቁ የእንግሊዝ ክለብ ማንችስተር ዩናይትድ እና የሊዮኔል ሜሲው ኢንተር ሚያሚ በኩዌት የወዳጅነት ጨዋታ ለማድረግ ፍላጎት ቢያሳዩም፣ ጥያቄያቸው በፌዴሬሽኑ በኩል አፋጣኝ ምላሽ አላገኘም።
ምን ተፈጠረ?
የኩዌት እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት እንደገለጹት፣ ማንችስተር ዩናይትድ ከ16 ቀናት በኋላ በሀገሪቱ ጨዋታ ለማድረግ ጥያቄ አቅርቦ ነበር። በተመሳሳይ የሜጀር ሊግ ሶከሩ ኢንተር ሚያሚም ተመሳሳይ ፍላጎት እንዳለው አሳውቋል።
ጥያቄው ውድቅ የተደረገበት ምክንያት፦
* የጊዜ እጥረት፦ ፕሬዝዳንቱ እንደገለጹት ጨዋታዎቹን ለማዘጋጀት የተሰጠው ጊዜ በጣም አጭር በመሆኑ አስፈላጊውን ዝግጅት ለማድረግ አይቻልም።
* ደህንነትና ዝግጅት፦ እንዲህ ያሉ ግዙፍ ክለቦችን ለማስተናገድ ሰፊ የደህንነት እና የሎጂስቲክስ ዝግጅት ስለሚያስፈልግ "አይቻልም" የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
ተስፋው አልተቆረጠም!
ይሁን እንጂ ፕሬዝዳንቱ አክለው እንደገለጹት፣
ጨዋታዎቹን በሌላ አመቺ ጊዜ ለማካሄድ ከሁለቱም ክለቦች ጋር ስምምነት ላይ ደርሰዋል። ይህም ማለት በቅርብ ወራት ውስጥ ቀያይ ሰይጣኖቹን እና ሜሲን በኩዌት የመመልከት እድሉ ሰፊ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#manchesterunited #intermiami #kuwaitfootball #mufc #messi #transfernews #footballupdates #ethiopia #sportsnews
#ethiopia | ታላቁ የእንግሊዝ ክለብ ማንችስተር ዩናይትድ እና የሊዮኔል ሜሲው ኢንተር ሚያሚ በኩዌት የወዳጅነት ጨዋታ ለማድረግ ፍላጎት ቢያሳዩም፣ ጥያቄያቸው በፌዴሬሽኑ በኩል አፋጣኝ ምላሽ አላገኘም።
ምን ተፈጠረ?
የኩዌት እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት እንደገለጹት፣ ማንችስተር ዩናይትድ ከ16 ቀናት በኋላ በሀገሪቱ ጨዋታ ለማድረግ ጥያቄ አቅርቦ ነበር። በተመሳሳይ የሜጀር ሊግ ሶከሩ ኢንተር ሚያሚም ተመሳሳይ ፍላጎት እንዳለው አሳውቋል።
ጥያቄው ውድቅ የተደረገበት ምክንያት፦
* የጊዜ እጥረት፦ ፕሬዝዳንቱ እንደገለጹት ጨዋታዎቹን ለማዘጋጀት የተሰጠው ጊዜ በጣም አጭር በመሆኑ አስፈላጊውን ዝግጅት ለማድረግ አይቻልም።
* ደህንነትና ዝግጅት፦ እንዲህ ያሉ ግዙፍ ክለቦችን ለማስተናገድ ሰፊ የደህንነት እና የሎጂስቲክስ ዝግጅት ስለሚያስፈልግ "አይቻልም" የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
ተስፋው አልተቆረጠም!
ይሁን እንጂ ፕሬዝዳንቱ አክለው እንደገለጹት፣
ጨዋታዎቹን በሌላ አመቺ ጊዜ ለማካሄድ ከሁለቱም ክለቦች ጋር ስምምነት ላይ ደርሰዋል። ይህም ማለት በቅርብ ወራት ውስጥ ቀያይ ሰይጣኖቹን እና ሜሲን በኩዌት የመመልከት እድሉ ሰፊ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#manchesterunited #intermiami #kuwaitfootball #mufc #messi #transfernews #footballupdates #ethiopia #sportsnews
4 months ago
🔴 "ቀይ ለበሶቹ ማሸነፍ አቅቷቸዋል፤ ለ5 ተከታታይ ጨዋታዎች ከድል ርቀዋል!"
#ethiopia | በ23ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ከሜዳው ውጭ ወደ ቪታሊቲ ስታዲየም ያቀናው ሊቨርፑል፤ እጅግ አሳዛኝ በሆነ ሁኔታ በቦርንማውዝ 3-2 ተሸንፏል።
የጨዋታው ድራማ:
ሊቨርፑል በቨርጂል ቫን ዳይክ እና በዶሚኒክ ሶቦዝላይ ግቦች አማካኝነት ነጥብ ተጋርቶ ለመውጣት ተቃርቦ የነበረ ቢሆንም፤ ቦርንማውዞች በኢቫኒልሰን እና አሌክስ ጂሚኔዝ ከመመራታቸው በተጨማሪ፤ በባከነ ሰዓት በአድሊ አማካኝነት የማሸነፊያዋን ግብ በማስቆጠር 3 ነጥቡን ጠቅልለው ወስደዋል።
የሊቨርፑል ቀውስ:
📉 በውድድር ዓመቱ ለ7ኛ ጊዜ ተሸንፈዋል።
📉 በሊጉ ብቻ ለ5 ተከታታይ ጊዜ ማሸነፍ ተስኗቸዋል።
የሊቨርፑል ችግር መከላከሉ ላይ ነው ወይስ አሰልጣኙ ጋር? ሀሳባችሁን ስጡን!
#liverpoolfc #bournemouth #premierleague #epl #lfc #football #ethiopia #sportsnews
#ethiopia | በ23ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ከሜዳው ውጭ ወደ ቪታሊቲ ስታዲየም ያቀናው ሊቨርፑል፤ እጅግ አሳዛኝ በሆነ ሁኔታ በቦርንማውዝ 3-2 ተሸንፏል።
የጨዋታው ድራማ:
ሊቨርፑል በቨርጂል ቫን ዳይክ እና በዶሚኒክ ሶቦዝላይ ግቦች አማካኝነት ነጥብ ተጋርቶ ለመውጣት ተቃርቦ የነበረ ቢሆንም፤ ቦርንማውዞች በኢቫኒልሰን እና አሌክስ ጂሚኔዝ ከመመራታቸው በተጨማሪ፤ በባከነ ሰዓት በአድሊ አማካኝነት የማሸነፊያዋን ግብ በማስቆጠር 3 ነጥቡን ጠቅልለው ወስደዋል።
የሊቨርፑል ቀውስ:
📉 በውድድር ዓመቱ ለ7ኛ ጊዜ ተሸንፈዋል።
📉 በሊጉ ብቻ ለ5 ተከታታይ ጊዜ ማሸነፍ ተስኗቸዋል።
የሊቨርፑል ችግር መከላከሉ ላይ ነው ወይስ አሰልጣኙ ጋር? ሀሳባችሁን ስጡን!
#liverpoolfc #bournemouth #premierleague #epl #lfc #football #ethiopia #sportsnews
Sponsored by
Surafel