5 days ago
ኩባንያችን 8ኛውን ዙር የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በይፋ አስጀመረ!
ኩባንያችን የአረንጓዴ ኦፕሬተርነት ጉዞውን በማጠናከር፣ ዛሬ በሀገር አቀፍ ደረጃ “ለአረንጓዴ ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል 250 ሺህ ችግኞችን በስኬት ተክሏል፡፡ በዚህም በአዲስ አበባ እንጦጦ (ቁስቋም ማዞሪያ) እንዲሁም በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ ከተሞች አረንጓዴ አሻራችንን አሳርፈናል፡፡
በመርሃ-ግብሩ ላይ ዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፤ ይህ ተግባር ኩባንያችን በዘላቂነት ስትራቴጂው (Sustainability Strategy) የሚያከናውናቸው ተግባራት አካል ሲሆን፣ ባለፉት ሰባት ዓመታት ከተተከሉ ከ4.6 ሚሊዮን በላይ ችግኞች 82.7% እንዲጸድቁ መደረጉን አብራርተዋል።
በተጨማሪም በታዳሽ የኃይል ኢንቨስትመንቶች፣ በፀሐይ ኃይል የሚሠሩ የኔትወርክ መሠረተ-ልማቶች እና ኃይል ቆጣቢ አረንጓዴ የዳታ ማዕከላት አማካኝነት የካርቦን ልቀት ቅነሳን ማሳካት ተችሏል። በተመሳሳይ በገነባናቸው ከ9 በላይ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ መሙያ ጣቢያዎች ከ481 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎችን በማስተናገድ፣ ከ15.4 ሚሊዮን ኪሎግራም በላይ የካርቦን ልቀትን መከላከል ተችሏል፤ ይህም ከ76 ሺህ በላይ ዛፎችን ከመትከል ጋር እኩል ፋይዳ አለው።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ በመርሃ-ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮ ቴሌኮም ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን ለመንከባከብ ትኩረት የሚሰጥ ተቋም መሆኑን ገልጸው፣ ከዚህ ቀደም የተተከሉ ችግኞች ወደ ጫካነት መቀየራቸውን በመጥቀስ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
በ8ኛው ዙር መርሃ-ግብር ለተከላና እንክብካቤ ሥራዎች ከ2,000 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጠር ሲሆን፣ ባለፉት ሰባት ዓመታት ውስጥ በአጠቃላይ ከ24.8 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል፡፡
በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ በንቃት ለተሳተፋችሁ የኩባንያችን ቤተሰቦች፣ አጋሮቻችን እና የመትከያ ቦታ ላመቻቻችሁ የመንግስት አካላት ምስጋና እናቀርባለን፡፡
ለበለጠ፡ https://bit.ly/4xhlXxF
#digitalethiopia #digitalafrica #gsma #itu #worldbank #oecd #g6countries
ኩባንያችን የአረንጓዴ ኦፕሬተርነት ጉዞውን በማጠናከር፣ ዛሬ በሀገር አቀፍ ደረጃ “ለአረንጓዴ ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል 250 ሺህ ችግኞችን በስኬት ተክሏል፡፡ በዚህም በአዲስ አበባ እንጦጦ (ቁስቋም ማዞሪያ) እንዲሁም በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ ከተሞች አረንጓዴ አሻራችንን አሳርፈናል፡፡
በመርሃ-ግብሩ ላይ ዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፤ ይህ ተግባር ኩባንያችን በዘላቂነት ስትራቴጂው (Sustainability Strategy) የሚያከናውናቸው ተግባራት አካል ሲሆን፣ ባለፉት ሰባት ዓመታት ከተተከሉ ከ4.6 ሚሊዮን በላይ ችግኞች 82.7% እንዲጸድቁ መደረጉን አብራርተዋል።
በተጨማሪም በታዳሽ የኃይል ኢንቨስትመንቶች፣ በፀሐይ ኃይል የሚሠሩ የኔትወርክ መሠረተ-ልማቶች እና ኃይል ቆጣቢ አረንጓዴ የዳታ ማዕከላት አማካኝነት የካርቦን ልቀት ቅነሳን ማሳካት ተችሏል። በተመሳሳይ በገነባናቸው ከ9 በላይ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ መሙያ ጣቢያዎች ከ481 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎችን በማስተናገድ፣ ከ15.4 ሚሊዮን ኪሎግራም በላይ የካርቦን ልቀትን መከላከል ተችሏል፤ ይህም ከ76 ሺህ በላይ ዛፎችን ከመትከል ጋር እኩል ፋይዳ አለው።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ በመርሃ-ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮ ቴሌኮም ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን ለመንከባከብ ትኩረት የሚሰጥ ተቋም መሆኑን ገልጸው፣ ከዚህ ቀደም የተተከሉ ችግኞች ወደ ጫካነት መቀየራቸውን በመጥቀስ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
በ8ኛው ዙር መርሃ-ግብር ለተከላና እንክብካቤ ሥራዎች ከ2,000 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጠር ሲሆን፣ ባለፉት ሰባት ዓመታት ውስጥ በአጠቃላይ ከ24.8 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል፡፡
በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ በንቃት ለተሳተፋችሁ የኩባንያችን ቤተሰቦች፣ አጋሮቻችን እና የመትከያ ቦታ ላመቻቻችሁ የመንግስት አካላት ምስጋና እናቀርባለን፡፡
ለበለጠ፡ https://bit.ly/4xhlXxF
#digitalethiopia #digitalafrica #gsma #itu #worldbank #oecd #g6countries
5 days ago
ኩባንያችን 8ኛውን ዙር የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በይፋ አስጀመረ!
ኩባንያችን የአረንጓዴ ኦፕሬተርነት ጉዞውን በማጠናከር፣ ዛሬ በሀገር አቀፍ ደረጃ “ለአረንጓዴ ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል 250 ሺህ ችግኞችን በስኬት ተክሏል፡፡ በዚህም በአዲስ አበባ እንጦጦ (ቁስቋም ማዞሪያ) እንዲሁም በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ ከተሞች አረንጓዴ አሻራችንን አሳርፈናል፡፡
በመርሃ-ግብሩ ላይ ዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፤ ይህ ተግባር ኩባንያችን በዘላቂነት ስትራቴጂው (Sustainability Strategy) የሚያከናውናቸው ተግባራት አካል ሲሆን፣ ባለፉት ሰባት ዓመታት ከተተከሉ ከ4.6 ሚሊዮን በላይ ችግኞች 82.7% እንዲጸድቁ መደረጉን አብራርተዋል።
በተጨማሪም በታዳሽ የኃይል ኢንቨስትመንቶች፣ በፀሐይ ኃይል የሚሠሩ የኔትወርክ መሠረተ-ልማቶች እና ኃይል ቆጣቢ አረንጓዴ የዳታ ማዕከላት አማካኝነት የካርቦን ልቀት ቅነሳን ማሳካት ተችሏል። በተመሳሳይ በገነባናቸው ከ9 በላይ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ መሙያ ጣቢያዎች ከ481 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎችን በማስተናገድ፣ ከ15.4 ሚሊዮን ኪሎግራም በላይ የካርቦን ልቀትን መከላከል ተችሏል፤ ይህም ከ76 ሺህ በላይ ዛፎችን ከመትከል ጋር እኩል ፋይዳ አለው።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ በመርሃ-ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮ ቴሌኮም ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን ለመንከባከብ ትኩረት የሚሰጥ ተቋም መሆኑን ገልጸው፣ ከዚህ ቀደም የተተከሉ ችግኞች ወደ ጫካነት መቀየራቸውን በመጥቀስ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
በ8ኛው ዙር መርሃ-ግብር ለተከላና እንክብካቤ ሥራዎች ከ2,000 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጠር ሲሆን፣ ባለፉት ሰባት ዓመታት ውስጥ በአጠቃላይ ከ24.8 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል፡፡
በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ በንቃት ለተሳተፋችሁ የኩባንያችን ቤተሰቦች፣ አጋሮቻችን እና የመትከያ ቦታ ላመቻቻችሁ የመንግስት አካላት ምስጋና እናቀርባለን፡፡
ለበለጠ፡ https://bit.ly/4xhlXxF
#digitalethiopia #digitalafrica #gsma #itu #worldbank #oecd #g6countries
ኩባንያችን የአረንጓዴ ኦፕሬተርነት ጉዞውን በማጠናከር፣ ዛሬ በሀገር አቀፍ ደረጃ “ለአረንጓዴ ኢትዮጵያ” በሚል መሪ ቃል 250 ሺህ ችግኞችን በስኬት ተክሏል፡፡ በዚህም በአዲስ አበባ እንጦጦ (ቁስቋም ማዞሪያ) እንዲሁም በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ ከተሞች አረንጓዴ አሻራችንን አሳርፈናል፡፡
በመርሃ-ግብሩ ላይ ዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ፍሬሕይወት ታምሩ እንደገለጹት፤ ይህ ተግባር ኩባንያችን በዘላቂነት ስትራቴጂው (Sustainability Strategy) የሚያከናውናቸው ተግባራት አካል ሲሆን፣ ባለፉት ሰባት ዓመታት ከተተከሉ ከ4.6 ሚሊዮን በላይ ችግኞች 82.7% እንዲጸድቁ መደረጉን አብራርተዋል።
በተጨማሪም በታዳሽ የኃይል ኢንቨስትመንቶች፣ በፀሐይ ኃይል የሚሠሩ የኔትወርክ መሠረተ-ልማቶች እና ኃይል ቆጣቢ አረንጓዴ የዳታ ማዕከላት አማካኝነት የካርቦን ልቀት ቅነሳን ማሳካት ተችሏል። በተመሳሳይ በገነባናቸው ከ9 በላይ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ መሙያ ጣቢያዎች ከ481 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎችን በማስተናገድ፣ ከ15.4 ሚሊዮን ኪሎግራም በላይ የካርቦን ልቀትን መከላከል ተችሏል፤ ይህም ከ76 ሺህ በላይ ዛፎችን ከመትከል ጋር እኩል ፋይዳ አለው።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ በመርሃ-ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኢትዮ ቴሌኮም ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን ለመንከባከብ ትኩረት የሚሰጥ ተቋም መሆኑን ገልጸው፣ ከዚህ ቀደም የተተከሉ ችግኞች ወደ ጫካነት መቀየራቸውን በመጥቀስ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
በ8ኛው ዙር መርሃ-ግብር ለተከላና እንክብካቤ ሥራዎች ከ2,000 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጠር ሲሆን፣ ባለፉት ሰባት ዓመታት ውስጥ በአጠቃላይ ከ24.8 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል፡፡
በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ በንቃት ለተሳተፋችሁ የኩባንያችን ቤተሰቦች፣ አጋሮቻችን እና የመትከያ ቦታ ላመቻቻችሁ የመንግስት አካላት ምስጋና እናቀርባለን፡፡
ለበለጠ፡ https://bit.ly/4xhlXxF
#digitalethiopia #digitalafrica #gsma #itu #worldbank #oecd #g6countries
8 days ago
የእንጦጦ ሐመረ ኖኅ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት አንድነት ገዳም የሚያስገነባውን ሕንፃ
የፕሮጀክቱ ዓላማ
(Project Overview)
የገዳሙ አበው መነኮሳት እና ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ማረፊያ ቤት።
2. ሕንፃው በውስጡ የሚያካታታቸው
(Building Facilities)
* የአበው መነኮሳት እና ሊቃውንት ማረፊያ
* ክርስትና መጠመቂያ ቤት
* ሙዚየም
* የተለያዩ አዳራሾች
* ለቢሮ አገልግሎት የሚሆኑ ክፍሎች
3. የባንክ ሂሳብ ቁጥሮችና መዋጮ ማድረጊያ
(Donation Accounts)
ሀ) የገዳሙ አካውንት
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፡ 1000003517504
አባይ ባንክ፡ 9841111014325318
አጭር ቁጥር፡ 1612
ለ) የልማት ኮሚቴ አካውንት
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፡ 1000003780779
አባይ ባንክ፡ 9841011002322017
አጭር ቁጥር፡ 1216
4. ወቅታዊ ሁኔታ
(Current Status)
በስተቀኝ በኩል በሚታዩት ፎቶዎች ላይ እንደሚታየው ሕንፃው አሁን ያለበት የስትራክቸርና የሲቪል ግንባታ ደረጃ ("አሁን ያለበት ደረጃ") ይታያል።
እናታችን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሁላችሁንም በበረከቷ ትጎብኛችሁ፤ አሜን!
የፕሮጀክቱ ዓላማ
(Project Overview)
የገዳሙ አበው መነኮሳት እና ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ማረፊያ ቤት።
2. ሕንፃው በውስጡ የሚያካታታቸው
(Building Facilities)
* የአበው መነኮሳት እና ሊቃውንት ማረፊያ
* ክርስትና መጠመቂያ ቤት
* ሙዚየም
* የተለያዩ አዳራሾች
* ለቢሮ አገልግሎት የሚሆኑ ክፍሎች
3. የባንክ ሂሳብ ቁጥሮችና መዋጮ ማድረጊያ
(Donation Accounts)
ሀ) የገዳሙ አካውንት
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፡ 1000003517504
አባይ ባንክ፡ 9841111014325318
አጭር ቁጥር፡ 1612
ለ) የልማት ኮሚቴ አካውንት
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፡ 1000003780779
አባይ ባንክ፡ 9841011002322017
አጭር ቁጥር፡ 1216
4. ወቅታዊ ሁኔታ
(Current Status)
በስተቀኝ በኩል በሚታዩት ፎቶዎች ላይ እንደሚታየው ሕንፃው አሁን ያለበት የስትራክቸርና የሲቪል ግንባታ ደረጃ ("አሁን ያለበት ደረጃ") ይታያል።
እናታችን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሁላችሁንም በበረከቷ ትጎብኛችሁ፤ አሜን!
13 days ago
ቱሪዝም፦ የመደመር እሳቤ የተፈጥሮ ጸጋዎቻችንን ወደ ኢኮኖሚ ሞተርነት የለወጠበት ተጨባጭ ማሳያ
***************************
ኢትዮጵያ እጅግ አስደናቂ የታሪክ፣ የተፈጥሮ፣ የመልክዓ ምድር እና እምቅ የባህል ሀብት ያላት ሀገር ብትሆንም፣ እነዚህን ጸጋዎች አቀናጅቶ እና አልምቶ ለመጠቀም የሚያስችል ሥልታዊ ዕቅድ እና ቁርጠኝነት ባለመኖሩ ለዘመናት ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ተጨባጭ አስተዋጽኦ ሳያበረክቱ ቆይተዋል።
ነገር ግን ባለፉት ስምንት ዓመታት ውስጥ በሀገራችን ተግባራዊ የተደረጉት ዘርፈ ብዙ ማሻሻያዎች ይህንን የአስተሳሰብ አጥር በመስበር፣ የሀገራችንን እውነተኛ አቅም ወደ መግለጥ ተሸጋግረዋል።
ይህ ስኬት የመጣው የመንግሥትን፣ የግሉን ዘርፍ፣ የማኅበረሰቡን እና የተፈጥሮን አቅም በአንድ የጋራ ሕልም ዙሪያ አስተባብሮ ከሚመራው የመደመር ፍልስፍና ነው። ዜጎች ሀገራቸውን እንዲያውቁ፣ እንዲወዱ እና እንዲኮሩባት የተደረገው ብሔራዊ ጥሪ ቱሪዝምን ከተለመደው የታሪክ ጥበቃ አልፎ ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ሞተርነት አሸጋግሮታል።
በቱሪዝም ዘርፍ የታየው ይህ ሥር ነቀል ለውጥ የመጣው ታዲያ ፈጣን እና ፈጠራ በተሞላበት የፕሮጀክት አመራር የተመራ ሥልታዊ ለውጥ ነው። ይህ ጉዞ በ2011 ዓ.ም አዲስ አበባን ለማስዋብ ከተጀመረው እና እንጦጦ እንዲሁም ሸገር ፓርኮችን እውን ካደረገው "ገበታ ለሸገር" መርሐ ግብር ጅማሮውን አድርጓል።
የዚህ ፕሮጀክት መሳካት በ2012 ዓ.ም ልማቱን ወደ ክልሎች በማስፋፋት በጎርጎራ፣ ወንጪ እና ኮይሻ የተፈጥሮ መዳረሻዎችን በከፍተኛ ጥራት ያለማውን "ገበታ ለሀገር" ፕሮጀክትን ወልዷል።
በአሁኑ ወቅት ደግሞ ስምንት አዳዲስ መዳረሻዎችን በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለማው "ገበታ ለትውልድ" መርሐ ግብር ሀገራዊ የቱሪዝም ገጽታን በመሠረታዊነት እየቀየረ ይገኛል።
የእነዚህን ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ መዳረሻዎች አስተዳደር ለኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ለተመረጡ ባለሀብቶች መሰጠቱ ደግሞ ዓለም አቀፍ ጎብኚዎችን ለመሳብ ሥልታዊ ድልድይ ሆኗል።
በእነዚህ መርሐ ግብሮች የተገነቡት ፕሮጀክቶች የመደመር እሳቤን በተግባር የሚያሳዩ ተጨባጭ የልማት ዕንቁዎች ናቸው።
በደቡብ ኢትዮጵያ የተመረቀው የአርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት የኮንፈረንስ ቱሪዝምን ከአዲስ አበባ ውጪ በማስፋፋት እና ከአባያ እንዲሁም ጫሞ ሐይቆች ተፈጥሯዊ ውበት ጋር በመዋሃድ ለአካባቢው ኢኮኖሚ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል።
በተመሳሳይ በአማራ ክልል የተገነባው የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት 13.3 ሔክታር ላይ ያረፈ ዘመናዊ መገልገያዎችን እና የሔሊኮፕተር ማረፊያን ያካተተ ሲሆን፣ የሰሜኑን የሀገራችን የቱሪስት መስመር የሚያስተሳስር ወሳኝ ማዕከል ሆኗል።
በአፋር ክልል የተገነባው የኒዒን ሌ ፓልም ስፕሪንግ ሎጅ ከአዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ጋር ባለው ቅርበት የተፈጥሮ ፍል ውኃን እና ሐይቅን በማቀናጀት የቱሪዝም አቅምን እያጎላ ይገኛል።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የተገነባው ደንቢ ኢኮ ሎጅ በበካ የቡና እርሻ አጠገብ ሙሉ በሙሉ ከአካባቢው የተገኙ የተፈጥሮ ቁሳቁሶችን በመጠቀም የተገነባ የዘላቂ የአካባቢ ጥበቃ ሞዴል ነው። በዚሁ ክልል የሚገኘው የሀላላ ኬላ ሪዞርትም በጊቤ ሦስት ሰው ሠራሽ ሐይቅ ዳርቻ የተገነባ ሌላው አስደናቂ ማሳያ ነው።
እነዚህ ታላላቅ የቱሪዝም መዳረሻዎች በማክሮ ኢኮኖሚክስ ዕይታ የቱሪዝምን ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ በከፍተኛ ደረጃ የሚያባዙ ናቸው። ፕሮጀክቶቹ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ቁሳቁሶች እና በኢትዮጵያውያን አቅም መገንባታቸው በአካባቢው ማኅበረሰብ ውስጥ የሚፈጠረውን የግብይት ዝውውር በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል።
ይህ ስትራቴጂ ኢትዮጵያ በ2018 በጀት ዓመት የ10.2 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ ከያዘችው ግብ ጋር በቀጥታ የሚጣጣም ሲሆን፣ ዘንድሮ ከቱሪዝም ዘርፍ ከ5.2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱ የዚህ የመደመር ቀመር ተግባራዊ ስኬት ነው።
የገበታ መርሐ ግብሮች ከተለመደው የቢሮክራሲ አሠራር ወጥተው በፈጠራ የታገዘ የፕሮጀክት አመራርን በማሳየት፣ የኢትዮጵያን የተዳፈነ ጸጋ ወደ ተግባራዊ ሀብት በመቀየር ለቀጣዩ ትውልድ የበለጸገች ሀገርን ለማስረከብ የተጀመረው ጉዞ ስኬታማ ማሳያዎች ናቸው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #tourism #medemer #gebetainitiatives #economicgrowth #landoforigins
***************************
ኢትዮጵያ እጅግ አስደናቂ የታሪክ፣ የተፈጥሮ፣ የመልክዓ ምድር እና እምቅ የባህል ሀብት ያላት ሀገር ብትሆንም፣ እነዚህን ጸጋዎች አቀናጅቶ እና አልምቶ ለመጠቀም የሚያስችል ሥልታዊ ዕቅድ እና ቁርጠኝነት ባለመኖሩ ለዘመናት ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ተጨባጭ አስተዋጽኦ ሳያበረክቱ ቆይተዋል።
ነገር ግን ባለፉት ስምንት ዓመታት ውስጥ በሀገራችን ተግባራዊ የተደረጉት ዘርፈ ብዙ ማሻሻያዎች ይህንን የአስተሳሰብ አጥር በመስበር፣ የሀገራችንን እውነተኛ አቅም ወደ መግለጥ ተሸጋግረዋል።
ይህ ስኬት የመጣው የመንግሥትን፣ የግሉን ዘርፍ፣ የማኅበረሰቡን እና የተፈጥሮን አቅም በአንድ የጋራ ሕልም ዙሪያ አስተባብሮ ከሚመራው የመደመር ፍልስፍና ነው። ዜጎች ሀገራቸውን እንዲያውቁ፣ እንዲወዱ እና እንዲኮሩባት የተደረገው ብሔራዊ ጥሪ ቱሪዝምን ከተለመደው የታሪክ ጥበቃ አልፎ ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ሞተርነት አሸጋግሮታል።
በቱሪዝም ዘርፍ የታየው ይህ ሥር ነቀል ለውጥ የመጣው ታዲያ ፈጣን እና ፈጠራ በተሞላበት የፕሮጀክት አመራር የተመራ ሥልታዊ ለውጥ ነው። ይህ ጉዞ በ2011 ዓ.ም አዲስ አበባን ለማስዋብ ከተጀመረው እና እንጦጦ እንዲሁም ሸገር ፓርኮችን እውን ካደረገው "ገበታ ለሸገር" መርሐ ግብር ጅማሮውን አድርጓል።
የዚህ ፕሮጀክት መሳካት በ2012 ዓ.ም ልማቱን ወደ ክልሎች በማስፋፋት በጎርጎራ፣ ወንጪ እና ኮይሻ የተፈጥሮ መዳረሻዎችን በከፍተኛ ጥራት ያለማውን "ገበታ ለሀገር" ፕሮጀክትን ወልዷል።
በአሁኑ ወቅት ደግሞ ስምንት አዳዲስ መዳረሻዎችን በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለማው "ገበታ ለትውልድ" መርሐ ግብር ሀገራዊ የቱሪዝም ገጽታን በመሠረታዊነት እየቀየረ ይገኛል።
የእነዚህን ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ መዳረሻዎች አስተዳደር ለኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ለተመረጡ ባለሀብቶች መሰጠቱ ደግሞ ዓለም አቀፍ ጎብኚዎችን ለመሳብ ሥልታዊ ድልድይ ሆኗል።
በእነዚህ መርሐ ግብሮች የተገነቡት ፕሮጀክቶች የመደመር እሳቤን በተግባር የሚያሳዩ ተጨባጭ የልማት ዕንቁዎች ናቸው።
በደቡብ ኢትዮጵያ የተመረቀው የአርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት የኮንፈረንስ ቱሪዝምን ከአዲስ አበባ ውጪ በማስፋፋት እና ከአባያ እንዲሁም ጫሞ ሐይቆች ተፈጥሯዊ ውበት ጋር በመዋሃድ ለአካባቢው ኢኮኖሚ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል።
በተመሳሳይ በአማራ ክልል የተገነባው የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት 13.3 ሔክታር ላይ ያረፈ ዘመናዊ መገልገያዎችን እና የሔሊኮፕተር ማረፊያን ያካተተ ሲሆን፣ የሰሜኑን የሀገራችን የቱሪስት መስመር የሚያስተሳስር ወሳኝ ማዕከል ሆኗል።
በአፋር ክልል የተገነባው የኒዒን ሌ ፓልም ስፕሪንግ ሎጅ ከአዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ጋር ባለው ቅርበት የተፈጥሮ ፍል ውኃን እና ሐይቅን በማቀናጀት የቱሪዝም አቅምን እያጎላ ይገኛል።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የተገነባው ደንቢ ኢኮ ሎጅ በበካ የቡና እርሻ አጠገብ ሙሉ በሙሉ ከአካባቢው የተገኙ የተፈጥሮ ቁሳቁሶችን በመጠቀም የተገነባ የዘላቂ የአካባቢ ጥበቃ ሞዴል ነው። በዚሁ ክልል የሚገኘው የሀላላ ኬላ ሪዞርትም በጊቤ ሦስት ሰው ሠራሽ ሐይቅ ዳርቻ የተገነባ ሌላው አስደናቂ ማሳያ ነው።
እነዚህ ታላላቅ የቱሪዝም መዳረሻዎች በማክሮ ኢኮኖሚክስ ዕይታ የቱሪዝምን ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ በከፍተኛ ደረጃ የሚያባዙ ናቸው። ፕሮጀክቶቹ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ቁሳቁሶች እና በኢትዮጵያውያን አቅም መገንባታቸው በአካባቢው ማኅበረሰብ ውስጥ የሚፈጠረውን የግብይት ዝውውር በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል።
ይህ ስትራቴጂ ኢትዮጵያ በ2018 በጀት ዓመት የ10.2 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ ከያዘችው ግብ ጋር በቀጥታ የሚጣጣም ሲሆን፣ ዘንድሮ ከቱሪዝም ዘርፍ ከ5.2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱ የዚህ የመደመር ቀመር ተግባራዊ ስኬት ነው።
የገበታ መርሐ ግብሮች ከተለመደው የቢሮክራሲ አሠራር ወጥተው በፈጠራ የታገዘ የፕሮጀክት አመራርን በማሳየት፣ የኢትዮጵያን የተዳፈነ ጸጋ ወደ ተግባራዊ ሀብት በመቀየር ለቀጣዩ ትውልድ የበለጸገች ሀገርን ለማስረከብ የተጀመረው ጉዞ ስኬታማ ማሳያዎች ናቸው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #tourism #medemer #gebetainitiatives #economicgrowth #landoforigins
Sponsored by
Surafel
20 days ago
የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ አዲስ ዕይታና ዕድሎች
**********************
ኢትዮጵያ በታሪክ፣ በባህልና በተፈጥሮ ሀብት የታደለች፣ የበርካታ የዓለም ቅርሶች ባለቤት የሆነች ሀገር ናት። ይሁን እንጂ ይህን እምቅ አቅም ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ጥቅም ከመቀየር አንጻር ዘርፉ ለብዙ ዓመታት በርካታ ተግዳሮቶች ሲገጥሙት ቆይቷል።
በአሁኑ ወቅት ግን፣ የመደመር መንግሥት በሰጠው ልዩ ትኩረት የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ አሮጌውን አካሄድ በመቀየር፣ በአዳዲስ ስትራቴጂዎችና ሜጋ ፕሮጀክቶች የታገዘ አዲስ የዕድገት ምዕራፍ ላይ ይገኛል።
ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ቱሪዝም በአብዛኛው የታሪክና የሃይማኖት ቅርሶችን ብቻ ማዕከል ያደረገ ነበር። አሁን ላይ ይህ አካሄድ ተቀይሮ የቱሪስት መዳረሻዎች ብዝኃነትን እንዲያካትቱ ተደርጓል።
በአዲስ አበባ በ“ገበታ ለሸገር” ፕሮጀክት የተገነቡት እንደ አንድነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የወዳጅነት አደባባይ ያሉ ፕሮጀክቶች ዋና ከተማዋን የቱሪስት ማረፊያና መስኅብ አድርገዋታል።
አንዲሁም በገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች የተገነቡት የቱሪዝም መስኅቦች የሀገራችን የተፈጥሮ ውበት እና ሥነ-ምህዳር ለዓለም አቀፍ ጎብኝዎች በአዲስ መልክ እያስተዋወቁ ይገኛሉ።
በሌላ በኩል የቱሪዝም ዕድገት ያለ አስተማማኝ መሠረተ-ልማት ሊታሰብ የማይችል ሲሆን፣ በዚህ ረገድ የተሠሩ ሥራዎችም ለዘርፉ መነቃቃት ትልቅ አስተዋጽዖ አበርክተዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዳዲስ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎችን በመጨመር እና የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ-ልማቶችን በሀገር ውስጥ በማስፋፋት ተጓዦችን ከዓለም ዙሪያ በቀላሉ የማገናኘት ሚናውን እየተወጣ ይገኛል።
በተጨማሪም የኢ-ቪዛ አሰጣጥ መዘርጋት እና የኦንላይን የክፍያ ሥርዓቶች መዘመን የጎብኝዎችን እንግልት በመቀነስ የጉዞ ሂደቱን ቀላልና ፈጣን በማድረግ ሀገራችን ከዘርፉ ተጠቃሚ እንድትሆን እያስቻላት ነው።
የቱሪዝም ዕድገት ስትራቴጂ ትኩረት የነዋሪውን ማኅበረሰብ ሕይወት መለወጥ ላይ ነው። በአዳዲስ መዳረሻዎች አካባቢ የሚኖሩ ማኅበረሰቦች በዕደ-ጥበብ፣ በቅርስ ጥበቃ፣ በሎጅና በእንግዳ ተቀባይነት ዘርፍ ቀጥተኛ ተጠቃሚ እየሆኑ ነው። ይህም ቅርሶችና ተፈጥሯዊ ሀብቶችን በባለቤትነት ስሜት እንዲጠበቁ አድርጓቸዋል።
የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ ካለበት "የማይነካ እምቅ አቅም" ተሻግሮ ወደ ተግባራዊ የኢኮኖሚ ምሰሶነት እየተቀየረ ይገኛል። አዳዲስ መዳረሻዎችን ማልማት፣ ጥራትን ማሻሻል እና ዲጂታል ስትራቴጂዎችን በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ፣ ቱሪዝም ለሀገራችን የውጭ ምንዛሪ ግኝትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ቀዳሚው አንቀሳቃሽ ኃይል መሆኑ አይቀሬ ነው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopianbroadcastingcorporation #tourismethiopia #landoforigins #visitethiopia
**********************
ኢትዮጵያ በታሪክ፣ በባህልና በተፈጥሮ ሀብት የታደለች፣ የበርካታ የዓለም ቅርሶች ባለቤት የሆነች ሀገር ናት። ይሁን እንጂ ይህን እምቅ አቅም ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ጥቅም ከመቀየር አንጻር ዘርፉ ለብዙ ዓመታት በርካታ ተግዳሮቶች ሲገጥሙት ቆይቷል።
በአሁኑ ወቅት ግን፣ የመደመር መንግሥት በሰጠው ልዩ ትኩረት የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ አሮጌውን አካሄድ በመቀየር፣ በአዳዲስ ስትራቴጂዎችና ሜጋ ፕሮጀክቶች የታገዘ አዲስ የዕድገት ምዕራፍ ላይ ይገኛል።
ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ቱሪዝም በአብዛኛው የታሪክና የሃይማኖት ቅርሶችን ብቻ ማዕከል ያደረገ ነበር። አሁን ላይ ይህ አካሄድ ተቀይሮ የቱሪስት መዳረሻዎች ብዝኃነትን እንዲያካትቱ ተደርጓል።
በአዲስ አበባ በ“ገበታ ለሸገር” ፕሮጀክት የተገነቡት እንደ አንድነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የወዳጅነት አደባባይ ያሉ ፕሮጀክቶች ዋና ከተማዋን የቱሪስት ማረፊያና መስኅብ አድርገዋታል።
አንዲሁም በገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች የተገነቡት የቱሪዝም መስኅቦች የሀገራችን የተፈጥሮ ውበት እና ሥነ-ምህዳር ለዓለም አቀፍ ጎብኝዎች በአዲስ መልክ እያስተዋወቁ ይገኛሉ።
በሌላ በኩል የቱሪዝም ዕድገት ያለ አስተማማኝ መሠረተ-ልማት ሊታሰብ የማይችል ሲሆን፣ በዚህ ረገድ የተሠሩ ሥራዎችም ለዘርፉ መነቃቃት ትልቅ አስተዋጽዖ አበርክተዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዳዲስ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎችን በመጨመር እና የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ-ልማቶችን በሀገር ውስጥ በማስፋፋት ተጓዦችን ከዓለም ዙሪያ በቀላሉ የማገናኘት ሚናውን እየተወጣ ይገኛል።
በተጨማሪም የኢ-ቪዛ አሰጣጥ መዘርጋት እና የኦንላይን የክፍያ ሥርዓቶች መዘመን የጎብኝዎችን እንግልት በመቀነስ የጉዞ ሂደቱን ቀላልና ፈጣን በማድረግ ሀገራችን ከዘርፉ ተጠቃሚ እንድትሆን እያስቻላት ነው።
የቱሪዝም ዕድገት ስትራቴጂ ትኩረት የነዋሪውን ማኅበረሰብ ሕይወት መለወጥ ላይ ነው። በአዳዲስ መዳረሻዎች አካባቢ የሚኖሩ ማኅበረሰቦች በዕደ-ጥበብ፣ በቅርስ ጥበቃ፣ በሎጅና በእንግዳ ተቀባይነት ዘርፍ ቀጥተኛ ተጠቃሚ እየሆኑ ነው። ይህም ቅርሶችና ተፈጥሯዊ ሀብቶችን በባለቤትነት ስሜት እንዲጠበቁ አድርጓቸዋል።
የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ ካለበት "የማይነካ እምቅ አቅም" ተሻግሮ ወደ ተግባራዊ የኢኮኖሚ ምሰሶነት እየተቀየረ ይገኛል። አዳዲስ መዳረሻዎችን ማልማት፣ ጥራትን ማሻሻል እና ዲጂታል ስትራቴጂዎችን በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ፣ ቱሪዝም ለሀገራችን የውጭ ምንዛሪ ግኝትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ቀዳሚው አንቀሳቃሽ ኃይል መሆኑ አይቀሬ ነው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopianbroadcastingcorporation #tourismethiopia #landoforigins #visitethiopia
21 days ago
ኢትዮጵያ የአፍሪካን አዲስ የቱሪዝም ካርታ በጥበብ እየሳለች ነው
******************
"ኢትዮጵያ ታሪክ ብቻ ናት" የሚለው የቆየ አስተሳሰብ ከጊዜ ጋር በከፍተኛ ፍጥነት እየተቀየረ ይገኛል። ዛሬ ኢትዮጵያ የሺህ ዓመታት ጥንታዊ ቅርሶቿን ከዘመናዊ የቱሪዝም ልማቶች ጋር በስምምነት እያጣመረች፣ ለዓለም አቀፍ ጎብኚዎች አዲስና ተመራጭ የጉዞ መስመር እየሆነች ነው።
ኢትዮጵያ ታሪክን፣ ተፈጥሮን፣ ባህልን እና ዘመናዊ መሠረተ-ልማትን በአንድ ወጥ የጉዞ ተሞክሮ ውስጥ አጣምራ የምታቀርብበት አዲስ ምዕራፍ ተከፍቷል።
ዛሬ ኢትዮጵያ የቱሪዝም ታሪኳን ብቻ አትተርክም፤ ይልቁንም አዲስ የቱሪዝም ታሪክ በተግባር እየጻፈች ትገኛለች። ለምሳሌ ያህል፣ በቅርቡ ተገንብተው ለፍሬ የበቁት የ"ገበታ ለሀገር" እና "ገበታ ለትውልድ" ታላላቅ ፕሮጀክቶች፣ የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት፣ ዘመናዊ መናፈሻዎች፣ ሰፋፊ የእግረኛ መንገዶች እና አረንጓዴ ስፍራዎች ኢትዮጵያን ከባህላዊ መዳረሻነት ወደ ዘመናዊ የጉዞ ልምድ እየቀየሯት ይገኛሉ።
በጎርጎራ የጣና ሐይቅ ዳርቻ ላይ የተገነቡት ዘመናዊ የመስተንግዶ ማዕከላት፣ በወንጪ የተራራ ሐይቅን የሚያቅፉት አስደናቂ የእይታ መድረኮች፣ እንዲሁም በሀላላ ኬላ የተፈጥሮንና የታሪክን ውበት የሚያሳዩት መዝናኛዎች የሀገሪቱን የቱሪዝም ገጽታ በአዲስ መልክ የሳሉት ትልልቅ ስኬቶች ናቸው። ከዚህ በተጨማሪም የአንድነት ፓርክ፣ የወዳጅነት ፓርክ፣ የእንጦጦ ተፈጥሮ ፓርክ፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የአዲስ አበባ አዳዲስ አረንጓዴ መናፈሻዎች የከተማ ቱሪዝምን ወደ ላቀ የደረጃ ማማ አሸጋግረውታል።
ነገር ግን ሀገራችን የዘመናዊ ቱሪዝም ልማትን በከፍተኛ ደረጃ ስታስፋፋ የትናንት ታሪኳንና ማንነቷን ከቶም አልዘነጋችም። እንደ ላሊበላ ውቅር አብያተ-ክርስቲያናት፣ የአክሱም ሐውልቶች፣ የፋሲል ግቢ፣ የሰሜንና የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርኮች፣ እሳተ-ገሞራማው የዳናኪል ምድር እና የአንትሮፖሎጂ መገኛ የሆነው የኦሞ ሸለቆ ያሉ ዓለም አቀፍ ቅርሶች ከአዳዲሶቹ መዳረሻዎች ጋር ተደምረው ለጎብኚዎች ልዩና ድንቅ የጉዞ ተሞክሮ እየፈጠሩ ይገኛሉ።
ዓለም ዛሬ መዝናናትንና መጎብኘትን ብቻ ሳይሆን፣ የማይረሳ ሕያው ተሞክሮን አጥብቆ በሚሻበት በዚህ ዘመን፤ ኢትዮጵያ ያንን ፍላጎት በተፈጥሮ፣ በታሪክ፣ በሕዝቦቿ ሞቅ ያለ ፈገግታና በዘመናዊ ልማቶቿ በአንድ ላይ አሟልታ ታቀርባለች። ዛሬ ጎብኚዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ የምትጋብዝበት ምክንያት ትናንቷ ብቻ አይደለም፤ ብሩህ የሆነው ነገዋም ጭምር ነው። በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ታሪኳን በአግባቡ ጠብቃ፣ የወደፊቱን የአፍሪካ የቱሪዝም ካርታ በበላይነት እየሳለች ያለች ታላቅ ሀገር መሆኗን በተግባር እያረጋገጠች ትገኛለች።
በልዩ እሸቱ
#ebc #ethiopia #tourism #landoforigins #visitethiopia
******************
"ኢትዮጵያ ታሪክ ብቻ ናት" የሚለው የቆየ አስተሳሰብ ከጊዜ ጋር በከፍተኛ ፍጥነት እየተቀየረ ይገኛል። ዛሬ ኢትዮጵያ የሺህ ዓመታት ጥንታዊ ቅርሶቿን ከዘመናዊ የቱሪዝም ልማቶች ጋር በስምምነት እያጣመረች፣ ለዓለም አቀፍ ጎብኚዎች አዲስና ተመራጭ የጉዞ መስመር እየሆነች ነው።
ኢትዮጵያ ታሪክን፣ ተፈጥሮን፣ ባህልን እና ዘመናዊ መሠረተ-ልማትን በአንድ ወጥ የጉዞ ተሞክሮ ውስጥ አጣምራ የምታቀርብበት አዲስ ምዕራፍ ተከፍቷል።
ዛሬ ኢትዮጵያ የቱሪዝም ታሪኳን ብቻ አትተርክም፤ ይልቁንም አዲስ የቱሪዝም ታሪክ በተግባር እየጻፈች ትገኛለች። ለምሳሌ ያህል፣ በቅርቡ ተገንብተው ለፍሬ የበቁት የ"ገበታ ለሀገር" እና "ገበታ ለትውልድ" ታላላቅ ፕሮጀክቶች፣ የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት፣ ዘመናዊ መናፈሻዎች፣ ሰፋፊ የእግረኛ መንገዶች እና አረንጓዴ ስፍራዎች ኢትዮጵያን ከባህላዊ መዳረሻነት ወደ ዘመናዊ የጉዞ ልምድ እየቀየሯት ይገኛሉ።
በጎርጎራ የጣና ሐይቅ ዳርቻ ላይ የተገነቡት ዘመናዊ የመስተንግዶ ማዕከላት፣ በወንጪ የተራራ ሐይቅን የሚያቅፉት አስደናቂ የእይታ መድረኮች፣ እንዲሁም በሀላላ ኬላ የተፈጥሮንና የታሪክን ውበት የሚያሳዩት መዝናኛዎች የሀገሪቱን የቱሪዝም ገጽታ በአዲስ መልክ የሳሉት ትልልቅ ስኬቶች ናቸው። ከዚህ በተጨማሪም የአንድነት ፓርክ፣ የወዳጅነት ፓርክ፣ የእንጦጦ ተፈጥሮ ፓርክ፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የአዲስ አበባ አዳዲስ አረንጓዴ መናፈሻዎች የከተማ ቱሪዝምን ወደ ላቀ የደረጃ ማማ አሸጋግረውታል።
ነገር ግን ሀገራችን የዘመናዊ ቱሪዝም ልማትን በከፍተኛ ደረጃ ስታስፋፋ የትናንት ታሪኳንና ማንነቷን ከቶም አልዘነጋችም። እንደ ላሊበላ ውቅር አብያተ-ክርስቲያናት፣ የአክሱም ሐውልቶች፣ የፋሲል ግቢ፣ የሰሜንና የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርኮች፣ እሳተ-ገሞራማው የዳናኪል ምድር እና የአንትሮፖሎጂ መገኛ የሆነው የኦሞ ሸለቆ ያሉ ዓለም አቀፍ ቅርሶች ከአዳዲሶቹ መዳረሻዎች ጋር ተደምረው ለጎብኚዎች ልዩና ድንቅ የጉዞ ተሞክሮ እየፈጠሩ ይገኛሉ።
ዓለም ዛሬ መዝናናትንና መጎብኘትን ብቻ ሳይሆን፣ የማይረሳ ሕያው ተሞክሮን አጥብቆ በሚሻበት በዚህ ዘመን፤ ኢትዮጵያ ያንን ፍላጎት በተፈጥሮ፣ በታሪክ፣ በሕዝቦቿ ሞቅ ያለ ፈገግታና በዘመናዊ ልማቶቿ በአንድ ላይ አሟልታ ታቀርባለች። ዛሬ ጎብኚዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ የምትጋብዝበት ምክንያት ትናንቷ ብቻ አይደለም፤ ብሩህ የሆነው ነገዋም ጭምር ነው። በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ታሪኳን በአግባቡ ጠብቃ፣ የወደፊቱን የአፍሪካ የቱሪዝም ካርታ በበላይነት እየሳለች ያለች ታላቅ ሀገር መሆኗን በተግባር እያረጋገጠች ትገኛለች።
በልዩ እሸቱ
#ebc #ethiopia #tourism #landoforigins #visitethiopia
23 days ago
አሐዱ ባንክ 4ኛ ዓመቱን በእንጦጦ የችግኝ ተከላ እና በበጎ አድራጎት ሥራዎች እያከበረ ይገኛል
#ethiopia | አሐዱ ባንክ ወደ ስራ የገባበትን አራተኛ ዓመት የምስረታ በዓል ምክንያት በማድረግ በጉለሌ ክፍለ ከተማ እንጦጦ ተራራ ላይ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሄደ።
ዛሬ ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም የባንኩ ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት በእንጦጦ ተራራ የአፈር መሸርሸርን ለመከላከልና ብዝሃ ሕይወትን ለመጠበቅ የሚያግዙ ከ600 በላይ አገር በቀል ችግኞች ተተክለዋል።
የአሐዱ ባንክ የማርኬቲንግ እና ኮሚኒኬሽንስ ዳይሬክተር አቶ አብይ መልካ ለዝግጅት ክፍላችን እንደገለጹት፣ በዛሬው እለት ከ600 በላይ የሚሆኑና ለአካባቢው ሥነ-ምህዳር ዘላቂ ጠቀሜታ ያላቸው ሀገር በቀል ችግኞች ተተክለዋል ብለዋል።
ተለይተው ከተተከሉት ዝርያዎች መካከል እንደ ኮሶ፣ ብርብራ፣ ዋንዛ፣ ዝግባ እና ቀረሮ ያሉ እፅዋት የሚገኙበት ሲሆን፣ ይህም ቀደም ሲል በቦታው ላይ በስፋት ይስተዋል የነበረውንና ከፍተኛ የውሃ ፍጆታ የሚጠይቀውን የባህር ዛፍ ተክል በሀገር በቀል ዛፎች ለመተካት ያለመ ነው።
አቶ አብይ አክለውም፣ ባንኩ ችግኞቹን ከመትከል ባለፈ በየሦስት ወሩ ክትትልና እንክብካቤ እንደሚያደርግላቸውና ይህንንም ሥራ ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለአደራ ተቋም ጋር በመተባበር በኃላፊነት እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
የአሐዱ ባንክ የኩባንያ ሴክሬተሪ እና የዳይሬክተሮች ቦርድ ጽሕፈት ቤት ተወካይ የሆኑት አቶ ቢኒያም አህመድ በበኩላቸው ለዝግጅት ክፍላችን እንደገለጹት፣ ይህ የአካባቢ ጥበቃ እንቅስቃሴ ባንኩ በአምስት ዓመት ስትራቴጂያዊ ዕቅዱ ውስጥ ካካተታቸውና ትኩረት ከሰጣቸው መርሆዎች ጋር ቀጥተኛ ትስስር አለው ብለዋል።
አቶ ቢኒያም እንደገለጹት፣ የችግኝ ተከላው በአንድ ጀንበር ዘመቻ ብቻ የሚያበቃ ሳይሆን፣ ባንኩ በቋሚነት ከተረከበው ቦታ በተጨማሪ በአገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ108 በላይ በሚሆኑ ቅርንጫፎችም ጭምር በየአካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ ተግባራዊ የሚደረግና የባንኩን መሠረታዊ እሴት የሚያንጸባርቅ ዘላቂ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።
ባንኩ ከአካባቢ ጥበቃ በተጨማሪ ዘርፈ ብዙ በሆኑ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች ላይ በንቃት እየተሳተፈ ይገኛል። የማርኬቲንግ ዳይሬክተሩ አቶ አብይ እንደገለጹት፣ ባንኩ በየዓመቱ እንደ መቄዶንያ፣ ጌርጌሴኖን እና የሰበታ ደናግላን ገዳም ላሉ ተቋማት የሚሰጠውን ድጋፍ አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የ204 የሚሆኑ አቅመ-ደካማ ሕፃናትን የትምህርትና የመኖሪያ ወጪዎች በየወሩ በመሸፈን እያሳደገ ይገኛል።
ከዚህም ባሻገር የፊታችን ቅዳሜ ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም የአሐዱ ባንክ ሠራተኞቹ እና ደንበኞች በተደጋጋሚ የሚሳተፉበት የደም ልገሳ መርሃ ግብር ዘንድሮሞ በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
በአራት ዓመታት የአገልግሎት ዘመኑ ፈጣን ዕድገት እያሳየ የመጣው አሐዱ ባንክ፣ በበጀት ዓመቱ 1.15 ቢሊዮን ብር ያልተጣራ ትርፍ ማስመዝገቡንና በቀጣይም ከኢትዮጵያ ካፒታል ማርኬት ባለሥልጣን ፈቃድ ሲያገኝ ወደ ሰፊ የአክሲዮን ሽያጭ እንቅስቃሴ በመግባት ደንበኞቹንና ባለአክሲዮኖቹን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ ዝግጅት እያጠናቀቀ መሆኑ ይታወሳል።
ጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#greenlegacy #greeninitiative
#indigenoustrees #entotomountain
#gullele #addisababa #ethiopia
#ahadubank #ahadubank4thanniversary
#ethiopia | አሐዱ ባንክ ወደ ስራ የገባበትን አራተኛ ዓመት የምስረታ በዓል ምክንያት በማድረግ በጉለሌ ክፍለ ከተማ እንጦጦ ተራራ ላይ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሄደ።
ዛሬ ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም የባንኩ ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት በእንጦጦ ተራራ የአፈር መሸርሸርን ለመከላከልና ብዝሃ ሕይወትን ለመጠበቅ የሚያግዙ ከ600 በላይ አገር በቀል ችግኞች ተተክለዋል።
የአሐዱ ባንክ የማርኬቲንግ እና ኮሚኒኬሽንስ ዳይሬክተር አቶ አብይ መልካ ለዝግጅት ክፍላችን እንደገለጹት፣ በዛሬው እለት ከ600 በላይ የሚሆኑና ለአካባቢው ሥነ-ምህዳር ዘላቂ ጠቀሜታ ያላቸው ሀገር በቀል ችግኞች ተተክለዋል ብለዋል።
ተለይተው ከተተከሉት ዝርያዎች መካከል እንደ ኮሶ፣ ብርብራ፣ ዋንዛ፣ ዝግባ እና ቀረሮ ያሉ እፅዋት የሚገኙበት ሲሆን፣ ይህም ቀደም ሲል በቦታው ላይ በስፋት ይስተዋል የነበረውንና ከፍተኛ የውሃ ፍጆታ የሚጠይቀውን የባህር ዛፍ ተክል በሀገር በቀል ዛፎች ለመተካት ያለመ ነው።
አቶ አብይ አክለውም፣ ባንኩ ችግኞቹን ከመትከል ባለፈ በየሦስት ወሩ ክትትልና እንክብካቤ እንደሚያደርግላቸውና ይህንንም ሥራ ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለአደራ ተቋም ጋር በመተባበር በኃላፊነት እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
የአሐዱ ባንክ የኩባንያ ሴክሬተሪ እና የዳይሬክተሮች ቦርድ ጽሕፈት ቤት ተወካይ የሆኑት አቶ ቢኒያም አህመድ በበኩላቸው ለዝግጅት ክፍላችን እንደገለጹት፣ ይህ የአካባቢ ጥበቃ እንቅስቃሴ ባንኩ በአምስት ዓመት ስትራቴጂያዊ ዕቅዱ ውስጥ ካካተታቸውና ትኩረት ከሰጣቸው መርሆዎች ጋር ቀጥተኛ ትስስር አለው ብለዋል።
አቶ ቢኒያም እንደገለጹት፣ የችግኝ ተከላው በአንድ ጀንበር ዘመቻ ብቻ የሚያበቃ ሳይሆን፣ ባንኩ በቋሚነት ከተረከበው ቦታ በተጨማሪ በአገር አቀፍ ደረጃ ባሉት ከ108 በላይ በሚሆኑ ቅርንጫፎችም ጭምር በየአካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ ተግባራዊ የሚደረግና የባንኩን መሠረታዊ እሴት የሚያንጸባርቅ ዘላቂ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።
ባንኩ ከአካባቢ ጥበቃ በተጨማሪ ዘርፈ ብዙ በሆኑ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች ላይ በንቃት እየተሳተፈ ይገኛል። የማርኬቲንግ ዳይሬክተሩ አቶ አብይ እንደገለጹት፣ ባንኩ በየዓመቱ እንደ መቄዶንያ፣ ጌርጌሴኖን እና የሰበታ ደናግላን ገዳም ላሉ ተቋማት የሚሰጠውን ድጋፍ አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የ204 የሚሆኑ አቅመ-ደካማ ሕፃናትን የትምህርትና የመኖሪያ ወጪዎች በየወሩ በመሸፈን እያሳደገ ይገኛል።
ከዚህም ባሻገር የፊታችን ቅዳሜ ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም የአሐዱ ባንክ ሠራተኞቹ እና ደንበኞች በተደጋጋሚ የሚሳተፉበት የደም ልገሳ መርሃ ግብር ዘንድሮሞ በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
በአራት ዓመታት የአገልግሎት ዘመኑ ፈጣን ዕድገት እያሳየ የመጣው አሐዱ ባንክ፣ በበጀት ዓመቱ 1.15 ቢሊዮን ብር ያልተጣራ ትርፍ ማስመዝገቡንና በቀጣይም ከኢትዮጵያ ካፒታል ማርኬት ባለሥልጣን ፈቃድ ሲያገኝ ወደ ሰፊ የአክሲዮን ሽያጭ እንቅስቃሴ በመግባት ደንበኞቹንና ባለአክሲዮኖቹን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ ዝግጅት እያጠናቀቀ መሆኑ ይታወሳል።
ጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#greenlegacy #greeninitiative
#indigenoustrees #entotomountain
#gullele #addisababa #ethiopia
#ahadubank #ahadubank4thanniversary
1 month ago
የቱሪዝም ዘርፍ ትንሳኤ እና አዳዲስ መዳረሻዎች
የዛሬ አምስት ዓመት መንግሥት ሲመሠርት፣ ሀገር ለመምራት በምርጫ የህዝብ ድምጽ ያገኘው ፓርቲ በቱሪዝም ዘርፍ ለማሳካት ቃል የገባቸው በርካታ ጉዳዮች ነበሩ፡፡
እነዚህም በሀገሪቱ የነበሩ የቱሪስት መዳረሻዎችን ማዘመን፣ አዳዲስ ሰው ሰራሽ የቱሪስት መስህቦችን መገንባት፣ የሀገር ገፅታን ማሻሻል እና ከዘርፉ የሚገኘውን የውጭ ምንዛሪ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ የሚሉ ታላላቅ ቃሎች ነበሩ፡፡
በዝርዝር ስናይ፡-
1. የገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ሜጋ ፕሮጀክቶች፡-
የተገባ ቃል፦ ከባህላዊ እና ታሪካዊ ቅርሶች በተጨማሪ አዳዲስና ዘመናዊ የተፈጥሮ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በመላ ሀገሪቱ በከፍተኛ ጥራት መገንባት።
አፈጻጸም፦
የገበታዎች ስኬት፦ ይህ ዘርፍ መንግሥት ባለፉት አምስት ዓመታት እጅግ አስደናቂ እና ፈጣን አፈጻጸም ካሳየባቸው መርሃ ግብሮች መካከል አንዱ ነው። መንግሥት በአዲስ አበባ በገበታ ለሸገር ፕሮጀክቶች አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግቧል፡፡ ቀጥሎ በገበታ ለሀገር መዳረሻ ፕሮጀክቶች ሀገር ተጨማሪ ሀብቶችን በዘርፉ አፍርታለች፡፡
የገበታ ለሸገርና የገበታ ለሀገር ስኬትን ተከትሎ የተጀመረው የገበታ ለትውልድ መርሃ ግብር በርካታ ታሪካዊ ስፍራዎችን ወደ ዘመናዊ ሪዞርት እና መዝናኛነት በመቀየር አዲስ የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች ፍሰት መፍጠር ችሏል።
2. የአዲስ አበባ ከተማ ገፅታ ግንባታ :-
የተገባ ቃል፦ ዋና ከተማዋን አዲስ አበባን ለአፍሪካ እና ለዓለም አቀፍ ጎብኚዎች ምቹ፣ ውብ እና ማራኪ የቱሪዝም ማዕከል ማድረግ።
አፈጻጸም፦
የኮሪደር ልማት እና አዳዲስ መስህቦች፦ ባለፉት አምስት ዓመታት በአዲስ አበባ የተከናወኑት ታላላቅ የኮሪደር ልማት ሥራዎች፣ የሳይንስ ሙዚየም፣ የአብርሆት ቤተ መጻሕፍት፣ የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ የእንጦጦ ፓርክ፣ የወዳጅነት እና የአንድነት ፓርኮች ግንባታ የከተማዋን ገፅታ ሙሉ በሙሉ ቀይረውታል።
የኮንፈረንስ ቱሪዝም ማደግ፦ እነዚህ አዳዲስ መሠረተ ልማቶች ከተማዋ የዓለም አቀፍ ስብሰባዎችን፣ ኤክስፖዎችን እና የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤዎችን በከፍተኛ የደኅንነትና የውበት ደረጃ እንድታስተናግድ በማድረግ ረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ አበርክተዋል።
3. የቪዛ ሥርዓትን ማዘመን እና የሀገር ውስጥ ቱሪዝም፡-
የተገባ ቃል፦ የውጭ ቱሪስቶች ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡበትን የቪዛ አሰጣጥ ሥርዓት ማቅለል እና የሀገር ውስጥ የቱሪዝም ባህልን ማሳደግ።
አፈጻጸም ፦
የኢ-ቪዛ መስፋፋት፦ የኢሚግሬሽን ሥርዓቱን በማዘመን የውጭ ዜጎች በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ በኦንላይን ቪዛ የሚያገኙበት ሥርዓት ይበልጥ ተጠናክሯል።
የሀገር ውስጥ ቱሪዝም መነቃቃት፦ ቀደም ሲል ቱሪዝም በውጭ ዜጎች ላይ ብቻ ተደግፎ የነበረ ቢሆንም፣ ባለፉት አምስት ዓመታት በተሰሩት ሰፊ ሥራዎች የሀገር ውስጥ ተወላጆች፣ ተማሪዎች እና ድርጅቶች አዳዲስ ፓርኮችንና መዳረሻዎችን የመጎብኘት ባህላቸው በከፍተኛ ደረጃ አድጓል።
በአጠቃላይ ባለፉት አምስት የመደመር መንግሥት ዓመታት መንግሥት በቱሪዝም ዘርፍ በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ታላቅ እና ስኬታማ አፈጻጸም አስመዝግቧል።
የዛሬ አምስት ዓመት መንግሥት ሲመሠርት፣ ሀገር ለመምራት በምርጫ የህዝብ ድምጽ ያገኘው ፓርቲ በቱሪዝም ዘርፍ ለማሳካት ቃል የገባቸው በርካታ ጉዳዮች ነበሩ፡፡
እነዚህም በሀገሪቱ የነበሩ የቱሪስት መዳረሻዎችን ማዘመን፣ አዳዲስ ሰው ሰራሽ የቱሪስት መስህቦችን መገንባት፣ የሀገር ገፅታን ማሻሻል እና ከዘርፉ የሚገኘውን የውጭ ምንዛሪ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ የሚሉ ታላላቅ ቃሎች ነበሩ፡፡
በዝርዝር ስናይ፡-
1. የገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ሜጋ ፕሮጀክቶች፡-
የተገባ ቃል፦ ከባህላዊ እና ታሪካዊ ቅርሶች በተጨማሪ አዳዲስና ዘመናዊ የተፈጥሮ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በመላ ሀገሪቱ በከፍተኛ ጥራት መገንባት።
አፈጻጸም፦
የገበታዎች ስኬት፦ ይህ ዘርፍ መንግሥት ባለፉት አምስት ዓመታት እጅግ አስደናቂ እና ፈጣን አፈጻጸም ካሳየባቸው መርሃ ግብሮች መካከል አንዱ ነው። መንግሥት በአዲስ አበባ በገበታ ለሸገር ፕሮጀክቶች አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግቧል፡፡ ቀጥሎ በገበታ ለሀገር መዳረሻ ፕሮጀክቶች ሀገር ተጨማሪ ሀብቶችን በዘርፉ አፍርታለች፡፡
የገበታ ለሸገርና የገበታ ለሀገር ስኬትን ተከትሎ የተጀመረው የገበታ ለትውልድ መርሃ ግብር በርካታ ታሪካዊ ስፍራዎችን ወደ ዘመናዊ ሪዞርት እና መዝናኛነት በመቀየር አዲስ የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች ፍሰት መፍጠር ችሏል።
2. የአዲስ አበባ ከተማ ገፅታ ግንባታ :-
የተገባ ቃል፦ ዋና ከተማዋን አዲስ አበባን ለአፍሪካ እና ለዓለም አቀፍ ጎብኚዎች ምቹ፣ ውብ እና ማራኪ የቱሪዝም ማዕከል ማድረግ።
አፈጻጸም፦
የኮሪደር ልማት እና አዳዲስ መስህቦች፦ ባለፉት አምስት ዓመታት በአዲስ አበባ የተከናወኑት ታላላቅ የኮሪደር ልማት ሥራዎች፣ የሳይንስ ሙዚየም፣ የአብርሆት ቤተ መጻሕፍት፣ የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ የእንጦጦ ፓርክ፣ የወዳጅነት እና የአንድነት ፓርኮች ግንባታ የከተማዋን ገፅታ ሙሉ በሙሉ ቀይረውታል።
የኮንፈረንስ ቱሪዝም ማደግ፦ እነዚህ አዳዲስ መሠረተ ልማቶች ከተማዋ የዓለም አቀፍ ስብሰባዎችን፣ ኤክስፖዎችን እና የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤዎችን በከፍተኛ የደኅንነትና የውበት ደረጃ እንድታስተናግድ በማድረግ ረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ አበርክተዋል።
3. የቪዛ ሥርዓትን ማዘመን እና የሀገር ውስጥ ቱሪዝም፡-
የተገባ ቃል፦ የውጭ ቱሪስቶች ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡበትን የቪዛ አሰጣጥ ሥርዓት ማቅለል እና የሀገር ውስጥ የቱሪዝም ባህልን ማሳደግ።
አፈጻጸም ፦
የኢ-ቪዛ መስፋፋት፦ የኢሚግሬሽን ሥርዓቱን በማዘመን የውጭ ዜጎች በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ በኦንላይን ቪዛ የሚያገኙበት ሥርዓት ይበልጥ ተጠናክሯል።
የሀገር ውስጥ ቱሪዝም መነቃቃት፦ ቀደም ሲል ቱሪዝም በውጭ ዜጎች ላይ ብቻ ተደግፎ የነበረ ቢሆንም፣ ባለፉት አምስት ዓመታት በተሰሩት ሰፊ ሥራዎች የሀገር ውስጥ ተወላጆች፣ ተማሪዎች እና ድርጅቶች አዳዲስ ፓርኮችንና መዳረሻዎችን የመጎብኘት ባህላቸው በከፍተኛ ደረጃ አድጓል።
በአጠቃላይ ባለፉት አምስት የመደመር መንግሥት ዓመታት መንግሥት በቱሪዝም ዘርፍ በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ታላቅ እና ስኬታማ አፈጻጸም አስመዝግቧል።
1 month ago
ሰላም፤ እንደምን አደራችሁ?
የመደመር መንግሥት በአምስቱ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች ሲመዘን
የመደመር መንግሥት ወደ ሥልጣን ሲመጣ የኢትዮጵያን የምጣኔ ሀብት መዋቅር ካረጀውና በአንድ ዘርፍ ላይ ብቻ ከተደገፈው የግብርና ምህዳር በማውጣት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስትራቴጂን ቀረጸ።
በዚህ ስትራቴጂ ውስጥ አምስት ቁልፍ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች፡ ግብርና፣ ቱሪዝም፣ ማዕድን፣ አይሲቲ እና አምራች ኢንዱስትሪ ተለይተው ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቷቸዋል።
መንግሥት በነዚህ ዘርፎች የገባውን ቃል እና ባለፉት አምስት ዓመታት የታየውን አፈጻጸም በአጭር በአጭሩ ለማየት እንሞክር፡፡
1. ግብርና፡-
ቃል የተገባው፡ የግብርናውን ዘርፍ ማዘመን፣ የምግብ ዋስትናን (ራስን መቻል) ማረጋገጥ እና ኢትዮጵያን ከእህል አስመጪነት ወደ ላኪነት ማሸጋገር።
አፈጻጸም ፦ ግብርናው በመደመር መንግሥት ስር ትልቅ የመዋቅር ለውጥ ያሳየበት ዘርፍ ነው። በተለይም በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተመዘገበው ውጤት ሀገሪቱን ወደ ስንዴ ላኪነት ያሸጋገረ ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኗል።
2. ቱሪዝም ፡-
ቃል የተገባው፦ የቱሪስት መስህቦቻችንን አቧራ አራግፈን አሻራ እናኖራለን በሚል መርህ፣ ዘርፉን የሀገር ገጽታ መገንቢያና የውጭ ምንዛሬ ማግኛ ምሰሶ ማድረግ።
አፈጻጸም ፦ ዘርፉ ከፍተኛ መነቃቃት የታየበት ነው። በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች አማካኝነት እንደ እንጦጦ፣ አንድነት ፓርክ፣ ጎርጎራ፣ ወንጪ እና በቅርቡ የተመረቀው የአርባምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት ያሉን ጨምሮ አዳዲስና ዘመናዊ መዳረሻዎች ተገንብተዋል።
3. ማዕድን ፡-
ቃል የተገባው፦ የሀገሪቱን የማዕድን ሀብት በአግባቡ ማልማት፣ ህገ-ወጥ የማዕድን ዝውውርን መቆጣጠር እና ዘርፉን የብሔራዊ ኢኮኖሚ ሉዓላዊነት ምሰሶ ማድረግ።
አፈጻጸም ፦ መንግሥት የድንጋይ ከሰል ምርትን በማሳደግ የውጭ ምንዛሪን ለማዳን የጀመረው ስራ እና የወርቅ ግዢ አሰራርን በማዘመን የሀገር ውስጥ ገበያ ድርሻን ከፍ ለማድረግ ያደረገው ጥረት የሚጠቀስ ነው።
4. አይሲቲ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ:-
ቃል የተገባው፦ የቴሌኮም ገበያውን ለግሉ ዘርፍ ክፍት ማድረግ፣ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን መተግበር እና የቢሮክራሲ አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ ማድረግ።
አፈጻጸም ፦ የመደመር መንግሥት በትልቅ ቁርጠኝነት ካሳካቸው ጉዳዮች አንዱ የኢትዮ ቴሌኮም ሞኖፖሊን ሰብሮ ሳፋሪኮምን ወደ ገበያ ማስገባት እና የዲጂታል ክፍያ ስርዓትን ማስፋፋት ነው። የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ እና የቴሌብር/ባንኪንግ መተግበሪያዎች የዜጎችን የዕለት ተዕለት ሕይወትና የንግድ እንቅስቃሴ አቅልለዋል።
5. አምራች ኢንዱስትሪ:-
ቃል የተገባው፦ የሀገር ውስጥ አምራችነትን ማሳደግ፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን መተካት እና ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር።
አፈጻጸም ፦ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተከፈተው ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አማካኝነት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ የመተካት አቅም 58 በመቶ ደርሷል።
በአጠቃላይ ባለፉት አምስት ዓመታት
በአምስቱ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች በመደመር መንግሥት መሪነት የተመዘገቡት ስኬቶች መንግሥት ገቢር-ነበብ እና ተግባር ተኮር መሆኑን ያሳዩ ናቸው።
የመደመር መንግሥት በአምስቱ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች ሲመዘን
የመደመር መንግሥት ወደ ሥልጣን ሲመጣ የኢትዮጵያን የምጣኔ ሀብት መዋቅር ካረጀውና በአንድ ዘርፍ ላይ ብቻ ከተደገፈው የግብርና ምህዳር በማውጣት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስትራቴጂን ቀረጸ።
በዚህ ስትራቴጂ ውስጥ አምስት ቁልፍ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች፡ ግብርና፣ ቱሪዝም፣ ማዕድን፣ አይሲቲ እና አምራች ኢንዱስትሪ ተለይተው ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቷቸዋል።
መንግሥት በነዚህ ዘርፎች የገባውን ቃል እና ባለፉት አምስት ዓመታት የታየውን አፈጻጸም በአጭር በአጭሩ ለማየት እንሞክር፡፡
1. ግብርና፡-
ቃል የተገባው፡ የግብርናውን ዘርፍ ማዘመን፣ የምግብ ዋስትናን (ራስን መቻል) ማረጋገጥ እና ኢትዮጵያን ከእህል አስመጪነት ወደ ላኪነት ማሸጋገር።
አፈጻጸም ፦ ግብርናው በመደመር መንግሥት ስር ትልቅ የመዋቅር ለውጥ ያሳየበት ዘርፍ ነው። በተለይም በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተመዘገበው ውጤት ሀገሪቱን ወደ ስንዴ ላኪነት ያሸጋገረ ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኗል።
2. ቱሪዝም ፡-
ቃል የተገባው፦ የቱሪስት መስህቦቻችንን አቧራ አራግፈን አሻራ እናኖራለን በሚል መርህ፣ ዘርፉን የሀገር ገጽታ መገንቢያና የውጭ ምንዛሬ ማግኛ ምሰሶ ማድረግ።
አፈጻጸም ፦ ዘርፉ ከፍተኛ መነቃቃት የታየበት ነው። በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች አማካኝነት እንደ እንጦጦ፣ አንድነት ፓርክ፣ ጎርጎራ፣ ወንጪ እና በቅርቡ የተመረቀው የአርባምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት ያሉን ጨምሮ አዳዲስና ዘመናዊ መዳረሻዎች ተገንብተዋል።
3. ማዕድን ፡-
ቃል የተገባው፦ የሀገሪቱን የማዕድን ሀብት በአግባቡ ማልማት፣ ህገ-ወጥ የማዕድን ዝውውርን መቆጣጠር እና ዘርፉን የብሔራዊ ኢኮኖሚ ሉዓላዊነት ምሰሶ ማድረግ።
አፈጻጸም ፦ መንግሥት የድንጋይ ከሰል ምርትን በማሳደግ የውጭ ምንዛሪን ለማዳን የጀመረው ስራ እና የወርቅ ግዢ አሰራርን በማዘመን የሀገር ውስጥ ገበያ ድርሻን ከፍ ለማድረግ ያደረገው ጥረት የሚጠቀስ ነው።
4. አይሲቲ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ:-
ቃል የተገባው፦ የቴሌኮም ገበያውን ለግሉ ዘርፍ ክፍት ማድረግ፣ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን መተግበር እና የቢሮክራሲ አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ ማድረግ።
አፈጻጸም ፦ የመደመር መንግሥት በትልቅ ቁርጠኝነት ካሳካቸው ጉዳዮች አንዱ የኢትዮ ቴሌኮም ሞኖፖሊን ሰብሮ ሳፋሪኮምን ወደ ገበያ ማስገባት እና የዲጂታል ክፍያ ስርዓትን ማስፋፋት ነው። የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ እና የቴሌብር/ባንኪንግ መተግበሪያዎች የዜጎችን የዕለት ተዕለት ሕይወትና የንግድ እንቅስቃሴ አቅልለዋል።
5. አምራች ኢንዱስትሪ:-
ቃል የተገባው፦ የሀገር ውስጥ አምራችነትን ማሳደግ፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን መተካት እና ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር።
አፈጻጸም ፦ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተከፈተው ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አማካኝነት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ የመተካት አቅም 58 በመቶ ደርሷል።
በአጠቃላይ ባለፉት አምስት ዓመታት
በአምስቱ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች በመደመር መንግሥት መሪነት የተመዘገቡት ስኬቶች መንግሥት ገቢር-ነበብ እና ተግባር ተኮር መሆኑን ያሳዩ ናቸው።
1 month ago
እንደገና የተወለደው ቀበና…
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተገኙበት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል፡፡
በ87 ነጥብ 6 ሔክታር መሬት ያረፈው እና 10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው ፕሮጀክቱ የወንዝ መከላከያ ግንቦችን፣ ዘመናዊ ድልድዮችን እና ሰፊ አረንጓዴ ሥፍራዎችን ይዟል።
ይህ ቀበናን ውብ ገጽታ ያለበሰው እና የትውልድ ዐሻራ ያረፈበት ፕሮጀክት ነዋሪዎቿን አስደስቷል።
የቀበና ነዋሪዎቹ አቶ አለማየሁ፣ አቶ አወቀ እና ወ/ሮ መሰሉ ስለ ቀበና ልማት ድሮና ዘንድሮን እያነሱ ከፋና ፖድካስት ጋር ቆይታ አድርገዋል፡፡
አቶ አወቀ÷ የነዋሪው ቁጥር እየጨመረ ሲመጣ ንጹህ የነበረው የቀበና ወንዝ እየተበከለ እና የመጸዳጃ ቤት ፍሳሽ እየተለቀቀበት ቀድሞ የነበረውን ውበትና ገፅታውን እንዳጣ ያስታውሳሉ፡፡ በዚህ ምክንያት ለነዋሪው የማይመች እና ጤናን የሚነሳ ሆነ ይላሉ፡፡
ቀበና አካባቢ ተወልደው ላለፉት 49 ዓመታት የኖሩት ወ/ሮ መሰሉ በበኩላቸው÷ የቀበና የቀድሞ ገፅታ በጫካ የተሸፈነ መሆኑን ይናገራሉ። በቀበና ወንዝ ቅዳሜ እና እሑድ ልጆች ጊዜያቸውን በዋና እና ሌሎች ጨዋታዎች የሚያሳልፉበት እንደነበር ያስታውሳሉ።
በሒደትም ቦታው መበከሉንና ለመዋኘት ቀርቶ ለማየት ደስ ወደማይል ገጽታ መቀየሩን ነው የሚያስረዱት፡፡
ሌላው የቀበና ነዋሪ አቶ አለማየሁ በ1959 ዓ.ም ነው በቀበና የተወለዱት፡፡ ስለአከባቢውም ብዙ ትዝታ አላቸው፡፡ መንገዱ አስቸጋሪ ስለነበር እና በአንድ ወቅት አዳልጧቸው ቀበና ወንዝ ውስጥ በመግባታቸው ከስራ እንደቀሩ ያስታውሳሉ፡፡ አሁን ያ ሁሉ ተለውጦ እንዲህ ተውቦ በማየታቸው "ራሴን እንደ እድለኛ እቆጥረዋለሁ" ይላሉ፡፡
"ቀደምት ሰዎች እኔ ያየሁትን ቢያዩ" ሲሉ ቁጭታቸውን የገለፁት ነዋሪው በተወለዱበት ቦታ ላይ በአሁኑ ወቅት ውብ የህጻናት መጫወቻ መሰራቱን በማየታቸው እንደተደሰቱ ተናግረዋል። አቶ አለማየሁ በዚህ ምክንያት "አባቴ እዛ ቦታ ላይ ሐውልት እንደተሰራለት እቆጥረዋለሁ" ሲሉም የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል፡፡
ወ/ሮ መሰሉ በተሰራው ልማት የቀበና ገጽታ ተለውጦ በማየታቸው መደሰታቸውን ገልጸው÷ ልጆች እና ወጣቶች ምቹና ጤናማ በሆነ አካባቢ እንዲያድጉ ያስችላል ብለዋል፡፡
በልማቱ ቀበና ውበት መላበሷ እንዳስደሰታቸው የሚናገሩት አቶ አወቀ÷ የአካባቢው ማሕበረሰብ ከልማቱ ተጠቃሚ በመሆኑ ሊጠብቀውና ሊንከባከበው ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል፡፡
ቀበና ድምጻዊ ጸሀዬ ዮሐንስ የተወለደባት፣ የቦረቀባት፣ የዋኘባትና ያዜመላት መሆኗን የገለጹት አቶ አወቀ÷ "ጸሐዬ ቀበና ላይ የሙዚቃ ድግስ አዘጋጅቶ ቀበናን ቀበና ማሰኘት አለበት" ነው ያሉት፡፡
በቴዎድሮስ ሳህለ
የቀበና ነዋሪዎች ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረጉትን ቆይታ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ https://youtube.com/watch?...
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተገኙበት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል፡፡
በ87 ነጥብ 6 ሔክታር መሬት ያረፈው እና 10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው ፕሮጀክቱ የወንዝ መከላከያ ግንቦችን፣ ዘመናዊ ድልድዮችን እና ሰፊ አረንጓዴ ሥፍራዎችን ይዟል።
ይህ ቀበናን ውብ ገጽታ ያለበሰው እና የትውልድ ዐሻራ ያረፈበት ፕሮጀክት ነዋሪዎቿን አስደስቷል።
የቀበና ነዋሪዎቹ አቶ አለማየሁ፣ አቶ አወቀ እና ወ/ሮ መሰሉ ስለ ቀበና ልማት ድሮና ዘንድሮን እያነሱ ከፋና ፖድካስት ጋር ቆይታ አድርገዋል፡፡
አቶ አወቀ÷ የነዋሪው ቁጥር እየጨመረ ሲመጣ ንጹህ የነበረው የቀበና ወንዝ እየተበከለ እና የመጸዳጃ ቤት ፍሳሽ እየተለቀቀበት ቀድሞ የነበረውን ውበትና ገፅታውን እንዳጣ ያስታውሳሉ፡፡ በዚህ ምክንያት ለነዋሪው የማይመች እና ጤናን የሚነሳ ሆነ ይላሉ፡፡
ቀበና አካባቢ ተወልደው ላለፉት 49 ዓመታት የኖሩት ወ/ሮ መሰሉ በበኩላቸው÷ የቀበና የቀድሞ ገፅታ በጫካ የተሸፈነ መሆኑን ይናገራሉ። በቀበና ወንዝ ቅዳሜ እና እሑድ ልጆች ጊዜያቸውን በዋና እና ሌሎች ጨዋታዎች የሚያሳልፉበት እንደነበር ያስታውሳሉ።
በሒደትም ቦታው መበከሉንና ለመዋኘት ቀርቶ ለማየት ደስ ወደማይል ገጽታ መቀየሩን ነው የሚያስረዱት፡፡
ሌላው የቀበና ነዋሪ አቶ አለማየሁ በ1959 ዓ.ም ነው በቀበና የተወለዱት፡፡ ስለአከባቢውም ብዙ ትዝታ አላቸው፡፡ መንገዱ አስቸጋሪ ስለነበር እና በአንድ ወቅት አዳልጧቸው ቀበና ወንዝ ውስጥ በመግባታቸው ከስራ እንደቀሩ ያስታውሳሉ፡፡ አሁን ያ ሁሉ ተለውጦ እንዲህ ተውቦ በማየታቸው "ራሴን እንደ እድለኛ እቆጥረዋለሁ" ይላሉ፡፡
"ቀደምት ሰዎች እኔ ያየሁትን ቢያዩ" ሲሉ ቁጭታቸውን የገለፁት ነዋሪው በተወለዱበት ቦታ ላይ በአሁኑ ወቅት ውብ የህጻናት መጫወቻ መሰራቱን በማየታቸው እንደተደሰቱ ተናግረዋል። አቶ አለማየሁ በዚህ ምክንያት "አባቴ እዛ ቦታ ላይ ሐውልት እንደተሰራለት እቆጥረዋለሁ" ሲሉም የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል፡፡
ወ/ሮ መሰሉ በተሰራው ልማት የቀበና ገጽታ ተለውጦ በማየታቸው መደሰታቸውን ገልጸው÷ ልጆች እና ወጣቶች ምቹና ጤናማ በሆነ አካባቢ እንዲያድጉ ያስችላል ብለዋል፡፡
በልማቱ ቀበና ውበት መላበሷ እንዳስደሰታቸው የሚናገሩት አቶ አወቀ÷ የአካባቢው ማሕበረሰብ ከልማቱ ተጠቃሚ በመሆኑ ሊጠብቀውና ሊንከባከበው ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል፡፡
ቀበና ድምጻዊ ጸሀዬ ዮሐንስ የተወለደባት፣ የቦረቀባት፣ የዋኘባትና ያዜመላት መሆኗን የገለጹት አቶ አወቀ÷ "ጸሐዬ ቀበና ላይ የሙዚቃ ድግስ አዘጋጅቶ ቀበናን ቀበና ማሰኘት አለበት" ነው ያሉት፡፡
በቴዎድሮስ ሳህለ
የቀበና ነዋሪዎች ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረጉትን ቆይታ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ https://youtube.com/watch?...
1 month ago
የአዲስ አበባ ሯጮች በአፍሪካ እምብርት ላይ በሚካሄድ ማራቶን ላይ እንዲሳተፉ ግብዣ ቀረበ
#ethiopia | በኢትዮዽያ ሩጫ ከስፖርት በላይ ነው ፤ ሩጫ የሀገር ኩራት፣ የጋራ በዓል፣ የጤና ፣ የህብረተሰብ ትስስር እና የነፍስ ደስታ ነው።
በአፍሪካ ዕምብርቷ ኡጋንዳም ተመሳሳይነት ያለውን ስሜት ለመጋራት፣ ታላቁ ሩጫ በኢትዮዽያ ከተስከር ላይት ሩዌንዞሪ ማራቶን ጋር በመተባበር ለሩጫ ወዳጆች ጥሪን አቅርቧል።
ኢትዮጵያ እና ኡጋንዳ የምስራቅ አፍሪካን ተራራማ መልክዓ ምድር ብቻ ሳይሆን፣ እያንዳንዱን የሩጫ ውድድር ወደ ታላቅ በዓል የመቀየር ተመሳሳይ ባህል አላቸው። ከአዲስ አበባ ለሚሄዱ ሯጮች በካሴሴ የሚስተዋለው የባህል ድባብ፣ ሙዚቃ እና የህዝብ አቀባበል እንደ ቤት እንዲሰማ የሚያደርግ የቅርብነት ስሜት አለው።
በሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ፣ በእንጦጦ ፓርክ ሲቢኢ ሩጫ ላይ የሚሳተፉ እና ሌሎችም የሩጫ አፍቃሪያን፣ ያንኑ የሩጫ መንፈስ በመያዝ ከሀገር ውጪ በመጓዝ ውድድሩን እንዲቀላቀሉ እንጋብዛለን።
ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. በኡጋንዳ፣ ካሴሴ ከተማ የሚካሄደው ተስከር ላይት ሩዌንዞሪ ማራቶን፣ ከአዲስ አበባ የባህር ዛፍ ጠረን ካለው ቀዝቃዛ አየር ወደ ሳቫናው ግርማ ሞገስ እና ወደ ሩዌንዞሪ ተራሮች ግርጌ የሚያደርጉት ልዩ የሩጫ ጉዞ ነው። በኢትዮጵያ የክረምቱ ዝናብና ቅዝቃዜ ሲጠነከር፣ በዩጋንዳ ካሴሴ ደግሞ ሞቅ ያለ ፀሐይና የኢኩዌተር መስመር ላይ የሚደረግ ውድድር ይጠብቅዎታል።
የተስከር ላይት ሩዌንዞሪ ማራቶን የዓለም አትሌቲክስ ሌብል (World Athletics Label Road Race) ደረጃ ያለዉ ዉድድር ነዉ። ይህም በአትሌቶች ጥራት እና በአደረጃጀት በዓለም ላይ ካሉ ምርጥ 200 ውድድሮች አንዱ ያደርገዋል። በውድድሩ ከማራቶን በተጨማሪ በ5 ኪ.ሜ.፣ 10 ኪ.ሜ.፣ እና 21 ኪ.ሜ . (ግማሽ ማራቶን) መሳተፍ ይችላሉ።
የሩጫው መስመር በዩኔስኮ የዓለም ቅርስ በሆነው የንግስት ኤልሳቤጥ ብሔራዊ ፓርክ ይጀምራል። በከበሮና በሙዚቃ በምትደምቀው የካሴሴ ከተማ መንገዶች አድርጎ፣ በበረዶ በተሸፈኑት የሩዌንዞሪ ተራሮች ግርጌ በሚገኘው አስደናቂው የኪሌምቤ ሸለቆ ይዘልቃል። ማጠናቀቂያው ላይ ሲደርሱ፣ ከኋላዎ የተዘረጋው ግዙፍ የተራራ ሰንሰለት ለእርስዎ የሚሰጠው ስሜት ምን ያህል ድንቅ እንደሆነ በራስዎ ይመሰክራሉ።
እንዴት መመዝገብ ይቻላል?
ይህንን ታላቅ የሩጫ በዓል ለመቀላቀል እና በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ፣ አሁኑኑ ከዚህ በታች በተቀመጠው ድረ-ገጽ አማካኝነት በመግባት መመዝገብ ይችላሉ።
www.rwenzorimarathon.com/r...
#ethiopia | በኢትዮዽያ ሩጫ ከስፖርት በላይ ነው ፤ ሩጫ የሀገር ኩራት፣ የጋራ በዓል፣ የጤና ፣ የህብረተሰብ ትስስር እና የነፍስ ደስታ ነው።
በአፍሪካ ዕምብርቷ ኡጋንዳም ተመሳሳይነት ያለውን ስሜት ለመጋራት፣ ታላቁ ሩጫ በኢትዮዽያ ከተስከር ላይት ሩዌንዞሪ ማራቶን ጋር በመተባበር ለሩጫ ወዳጆች ጥሪን አቅርቧል።
ኢትዮጵያ እና ኡጋንዳ የምስራቅ አፍሪካን ተራራማ መልክዓ ምድር ብቻ ሳይሆን፣ እያንዳንዱን የሩጫ ውድድር ወደ ታላቅ በዓል የመቀየር ተመሳሳይ ባህል አላቸው። ከአዲስ አበባ ለሚሄዱ ሯጮች በካሴሴ የሚስተዋለው የባህል ድባብ፣ ሙዚቃ እና የህዝብ አቀባበል እንደ ቤት እንዲሰማ የሚያደርግ የቅርብነት ስሜት አለው።
በሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ፣ በእንጦጦ ፓርክ ሲቢኢ ሩጫ ላይ የሚሳተፉ እና ሌሎችም የሩጫ አፍቃሪያን፣ ያንኑ የሩጫ መንፈስ በመያዝ ከሀገር ውጪ በመጓዝ ውድድሩን እንዲቀላቀሉ እንጋብዛለን።
ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. በኡጋንዳ፣ ካሴሴ ከተማ የሚካሄደው ተስከር ላይት ሩዌንዞሪ ማራቶን፣ ከአዲስ አበባ የባህር ዛፍ ጠረን ካለው ቀዝቃዛ አየር ወደ ሳቫናው ግርማ ሞገስ እና ወደ ሩዌንዞሪ ተራሮች ግርጌ የሚያደርጉት ልዩ የሩጫ ጉዞ ነው። በኢትዮጵያ የክረምቱ ዝናብና ቅዝቃዜ ሲጠነከር፣ በዩጋንዳ ካሴሴ ደግሞ ሞቅ ያለ ፀሐይና የኢኩዌተር መስመር ላይ የሚደረግ ውድድር ይጠብቅዎታል።
የተስከር ላይት ሩዌንዞሪ ማራቶን የዓለም አትሌቲክስ ሌብል (World Athletics Label Road Race) ደረጃ ያለዉ ዉድድር ነዉ። ይህም በአትሌቶች ጥራት እና በአደረጃጀት በዓለም ላይ ካሉ ምርጥ 200 ውድድሮች አንዱ ያደርገዋል። በውድድሩ ከማራቶን በተጨማሪ በ5 ኪ.ሜ.፣ 10 ኪ.ሜ.፣ እና 21 ኪ.ሜ . (ግማሽ ማራቶን) መሳተፍ ይችላሉ።
የሩጫው መስመር በዩኔስኮ የዓለም ቅርስ በሆነው የንግስት ኤልሳቤጥ ብሔራዊ ፓርክ ይጀምራል። በከበሮና በሙዚቃ በምትደምቀው የካሴሴ ከተማ መንገዶች አድርጎ፣ በበረዶ በተሸፈኑት የሩዌንዞሪ ተራሮች ግርጌ በሚገኘው አስደናቂው የኪሌምቤ ሸለቆ ይዘልቃል። ማጠናቀቂያው ላይ ሲደርሱ፣ ከኋላዎ የተዘረጋው ግዙፍ የተራራ ሰንሰለት ለእርስዎ የሚሰጠው ስሜት ምን ያህል ድንቅ እንደሆነ በራስዎ ይመሰክራሉ።
እንዴት መመዝገብ ይቻላል?
ይህንን ታላቅ የሩጫ በዓል ለመቀላቀል እና በውድድሩ ላይ ለመሳተፍ፣ አሁኑኑ ከዚህ በታች በተቀመጠው ድረ-ገጽ አማካኝነት በመግባት መመዝገብ ይችላሉ።
www.rwenzorimarathon.com/r...
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ቀደም ሲል በባህር ዛፍ ደን ብቻ ይታወቅ የነበረው ታሪካዊው የእንጦጦ ተራራ፣ ዛሬ ለገበያ ከፍተኛ እሴት ያለው እና ለሥነ-ምግብ ጠቃሚ የሆነው እንጆሪ በስፋት የሚመረትበት ስፍራ መሆኑ በተግባር ተረጋግጧል።
➡https://youtu.be/5UyyrcjM8...
#ethiopia #ebc #pmabiyahmed #strawberry #entoto
1 month ago
የሚያስደንቅ ውበት የተጎናጸፈው የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ ዳርቻ ልማት…
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ውበትና ድምቀት የሚያስደንቅ ነው አሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች።
የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትናንትናው ዕለት በይፋ ተመርቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ ባዘጋጀው የምስጋና መርሐ-ግብር ላይ የተሳተፉ የከተማዋ ነዋሪዎች ፕሮጀክቱን ጎብኝተዋል።
አስተያየታቸውን የሰጡ ነዋሪዎች ልማቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ለውጥ ማምጣቱንና ለከተማዋ ውበት ተጨማሪ ድምቀት መፍጠሩን ገልጸዋል።
አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል ፈዲሉ ኢብራሂም÷ የቀበና ወንዝ ለረጅም ዘመናት በቆሻሻ መጣያነቱና በማይመች ሁኔታው ይታወቅ እንደነበር አስታውሰዋል።
በአሁኑ ወቅት የተከናወነው አስደናቂ የልማት ስራ ግን አካባቢውን በሚያስደንቅ ሁኔታ የቀየረው ሲሆን ይህም ትልቅ ደስታና እርካታ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
ቀደም ሲል ስሙ በክፉ ይነሳ የነበረው ይህ አካባቢ አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ ወደ ውብ መልክዓ ምድርነት መቀየሩ እንዳስደነቃት የተናገረችው ደግሞ እስራኤል አሸናፊ ናት።
በአሁኑ ወቅት ስፍራው ለህጻናትና ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ምቹ መጫወቻና የመዝናኛ ሆኖ መዘጋጀቱ እንዳስደሰታትም ተናግራለች።
ወጣት ዳንኤል በበኩሉ÷ የቀበና ወንዝ ዳርቻ ቀደም ሲል አስቀያሚና ለጤና ጠንቅ የነበረ ስፍራ መሆኑን አስታውሶ ይህን ስፍራ ውብ ያደረጉ አመራሮች ትልቅ ምስጋና ይገባቸዋል ብሏል።
ሌላው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ከድር ጃርሶ በአጭር ጊዜ ውስጥ በአካባቢው ላይ የታየው ለውጥ እጅግ አስደናቂ እይታ መፍጠሩን ለኢዜአ ገልጸዋል፡፡
ይህ ስፍራ ቀደም ሲል በቆሻሻ ተሸፍኖ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ግን በሐይቅ እና በአረንጓዴ ሥፍራ የተዋበ መሆኑንና አካባቢው ለኑሮ ምቹና ማራኪ ሆኖ መገንባቱን የጠቀሱት ደግሞ መቅደስ በቀለ ናቸው።
አካባቢውን ለረጅም ዓመታት የሚያውቁት አቶ አብደላ ኑሪ÷ ቀደም ሲል ስፍራው እጅግ ምቾት የማይሰጥና የሚያሳቅቅ ነበር፤በአሁኑ ወቅት የታየው ውበትና ልማት እጅግ አስገራሚ ነው፤ ተግባሩ ለመንግሥት ትልቅ ምስጋና የሚያሰጥ ነው ብለዋል።
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ውበትና ድምቀት የሚያስደንቅ ነው አሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች።
የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትናንትናው ዕለት በይፋ ተመርቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ ባዘጋጀው የምስጋና መርሐ-ግብር ላይ የተሳተፉ የከተማዋ ነዋሪዎች ፕሮጀክቱን ጎብኝተዋል።
አስተያየታቸውን የሰጡ ነዋሪዎች ልማቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ለውጥ ማምጣቱንና ለከተማዋ ውበት ተጨማሪ ድምቀት መፍጠሩን ገልጸዋል።
አስተያየታቸውን ከሰጡት መካከል ፈዲሉ ኢብራሂም÷ የቀበና ወንዝ ለረጅም ዘመናት በቆሻሻ መጣያነቱና በማይመች ሁኔታው ይታወቅ እንደነበር አስታውሰዋል።
በአሁኑ ወቅት የተከናወነው አስደናቂ የልማት ስራ ግን አካባቢውን በሚያስደንቅ ሁኔታ የቀየረው ሲሆን ይህም ትልቅ ደስታና እርካታ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
ቀደም ሲል ስሙ በክፉ ይነሳ የነበረው ይህ አካባቢ አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ ወደ ውብ መልክዓ ምድርነት መቀየሩ እንዳስደነቃት የተናገረችው ደግሞ እስራኤል አሸናፊ ናት።
በአሁኑ ወቅት ስፍራው ለህጻናትና ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ምቹ መጫወቻና የመዝናኛ ሆኖ መዘጋጀቱ እንዳስደሰታትም ተናግራለች።
ወጣት ዳንኤል በበኩሉ÷ የቀበና ወንዝ ዳርቻ ቀደም ሲል አስቀያሚና ለጤና ጠንቅ የነበረ ስፍራ መሆኑን አስታውሶ ይህን ስፍራ ውብ ያደረጉ አመራሮች ትልቅ ምስጋና ይገባቸዋል ብሏል።
ሌላው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ከድር ጃርሶ በአጭር ጊዜ ውስጥ በአካባቢው ላይ የታየው ለውጥ እጅግ አስደናቂ እይታ መፍጠሩን ለኢዜአ ገልጸዋል፡፡
ይህ ስፍራ ቀደም ሲል በቆሻሻ ተሸፍኖ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ግን በሐይቅ እና በአረንጓዴ ሥፍራ የተዋበ መሆኑንና አካባቢው ለኑሮ ምቹና ማራኪ ሆኖ መገንባቱን የጠቀሱት ደግሞ መቅደስ በቀለ ናቸው።
አካባቢውን ለረጅም ዓመታት የሚያውቁት አቶ አብደላ ኑሪ÷ ቀደም ሲል ስፍራው እጅግ ምቾት የማይሰጥና የሚያሳቅቅ ነበር፤በአሁኑ ወቅት የታየው ውበትና ልማት እጅግ አስገራሚ ነው፤ ተግባሩ ለመንግሥት ትልቅ ምስጋና የሚያሰጥ ነው ብለዋል።
1 month ago
ዜጎች የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን በተገለጠ ልቦና ሊመለከቱ ይገባል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
********************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትን በዛሬው ዕለት መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምረቃው ወቅት እንደተናገሩት፤ የወደፊቱን ውበት አስቀድሞ በአእምሮ መሳል መቻል ለስራ ስኬታማነት ቁልፍ መንገድ መሆኑን አንስተዋል።
"መደመር" ማለት የዕውቀት፣ የፋይናንስ፣ የጉልበትና የአመራር ብቃትን በአንድነት ማዋሃድ መሆኑን ያብራሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ዜጎች ተባብረውና ተደጋግፈው ከተነሱ ከቀበና የላቁ አስደናቂ ተአምራትን መሥራት እንደሚችሉ በተግባር መመስከሩን ገልጸዋል።
ይህ ግዙፍ ልማት የአዲስ አበባን ስልጣኔ ከፍ የሚያደርግና ከተማዋን ለአየር ንብረት መዛባት የማይበገሩ እንዲሁም ለነዋሪዎቿ እጅግ ምቹ ከሚያደርጉ ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች አንዱ ነው ብለዋል።
አክለውም "ለዋና ከተማዋ ነዋሪዎች ዝቅጠት፣ መቆሸሽና በሌሎች አገራት ስልጣኔ መቅናት አይገባቸውም" ሲሉ ተናግረዋል።
ይህ የአረንጓዴ ልማት ሲጀመር በርካቶች አይሳካላችሁም የሚል ድምፅ አሰምተው ነበር ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ኢትዮጵያውያን ግን ጥንታዊ የማንነት ጥባቸውንና ጽናታቸውን ተጠቅመው በተግባር በማሳየት ለተቺዎች የማይናወጥ ምላሽ መስጠታቸውን አረጋግጠዋል።
አዲስ አበባ ያላትን እምቅ ተፈጥሯዊ ለግስና በተደራጀ ዕይታ ማውጣት ባለመቻላችን ለዘመናት ማራኪ ገጽታዋ ተደብቆ መቆየቱን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ ማኅበረሰቡ እነዚህን አገራዊ ስኬቶች በተገለጠ ልቦና እንዲመለከትና ለቀጣይ የጋራ ድሎች እንዲዘጋጅም ጥሪ አስተላልፈዋል።
#ethiopianbroadcastingcorporation #pmabiy #addisababa #entotokebena #riverside #urbantransformation
********************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትን በዛሬው ዕለት መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምረቃው ወቅት እንደተናገሩት፤ የወደፊቱን ውበት አስቀድሞ በአእምሮ መሳል መቻል ለስራ ስኬታማነት ቁልፍ መንገድ መሆኑን አንስተዋል።
"መደመር" ማለት የዕውቀት፣ የፋይናንስ፣ የጉልበትና የአመራር ብቃትን በአንድነት ማዋሃድ መሆኑን ያብራሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ዜጎች ተባብረውና ተደጋግፈው ከተነሱ ከቀበና የላቁ አስደናቂ ተአምራትን መሥራት እንደሚችሉ በተግባር መመስከሩን ገልጸዋል።
ይህ ግዙፍ ልማት የአዲስ አበባን ስልጣኔ ከፍ የሚያደርግና ከተማዋን ለአየር ንብረት መዛባት የማይበገሩ እንዲሁም ለነዋሪዎቿ እጅግ ምቹ ከሚያደርጉ ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች አንዱ ነው ብለዋል።
አክለውም "ለዋና ከተማዋ ነዋሪዎች ዝቅጠት፣ መቆሸሽና በሌሎች አገራት ስልጣኔ መቅናት አይገባቸውም" ሲሉ ተናግረዋል።
ይህ የአረንጓዴ ልማት ሲጀመር በርካቶች አይሳካላችሁም የሚል ድምፅ አሰምተው ነበር ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ኢትዮጵያውያን ግን ጥንታዊ የማንነት ጥባቸውንና ጽናታቸውን ተጠቅመው በተግባር በማሳየት ለተቺዎች የማይናወጥ ምላሽ መስጠታቸውን አረጋግጠዋል።
አዲስ አበባ ያላትን እምቅ ተፈጥሯዊ ለግስና በተደራጀ ዕይታ ማውጣት ባለመቻላችን ለዘመናት ማራኪ ገጽታዋ ተደብቆ መቆየቱን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ ማኅበረሰቡ እነዚህን አገራዊ ስኬቶች በተገለጠ ልቦና እንዲመለከትና ለቀጣይ የጋራ ድሎች እንዲዘጋጅም ጥሪ አስተላልፈዋል።
#ethiopianbroadcastingcorporation #pmabiy #addisababa #entotokebena #riverside #urbantransformation
1 month ago
የሸገር ወንዞች ሲፈውሱ፡- ከብክለት ወደ ሕዝብ መዝናኛነት
********************
አዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ያስመዘገበችው ግዙፍ የከተማ ገጽታ ለውጥ ከመሠረተ ልማት ዝርጋታ ባሻገር የከተማዋን ነዋሪዎች አኗኗር፣ ማኅበራዊ መስተጋብርና የኢኮኖሚ አቅጣጫ የቀየረ ጥልቅ ስትራቴጂካዊ ሽግግር ነው።
ለረጅም ዘመናት አዲስ አበባ በከፍተኛ የሕዝብ ቁጥር ማደግ፣ በኮንክሪት ሕንጻዎች መበራከትና በአረንጓዴ ሥፍራዎች መመናመን ትታወቅ የነበረች ቢሆንም በቅርቡ የተከናወኑት የተቀናጁ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት ሥራዎች ግን ከተማዋን ወደ አዲስ የዕድገትና የውበት ምዕራፍ አሸጋግረዋታል።
ይህ ዘመናዊ ለውጥ በተለይም ቀደም ሲል የብክለት፣ የቸልተኝነትና የከተማዋ የጀርባ ገጽታ መገለጫ የነበሩትን የውሃ አካላትና ተፋሰሶች ወደ ሕያው፣ ማራኪና ሥነ-ምህዳራዊ ጠቀሜታ ወደላቸው የሕዝብ መጠቀሚያዎች በመለወጥ ረገድ ያተመዘገበው ስኬት የከተማዋን ታሪክና ገጽታ ሙሉ በሙሉ ቀይሮታል።
ይህ ዓይነቱ ትራንስፎርሜሽን የከተማዋን ነዋሪዎች የኑሮ ጥራት ከማሻሻሉም በላይ አዲስ አበባ በዓለም አቀፍና በአህጉራዊ መድረኮች ያላትን የላቀ አቋምና የቱሪስት መዳረሻነት በከፍተኛ ደረጃ እያሳደገው ይገኛል።
ለዚህም በዋና ማሳያነት የሚጠቀሰው ከእንጦጦ ጋራ ተነስቶ እስከ ቀበና የሚዘልቀው የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ነው። ይህ ሰፊ ኮሪደር ቀደም ሲል ለደህንነት አስጊና በቆሻሻ መጣያነት ያገለግል የነበረ አካባቢን ወደ ዘመናዊ የሕዝብ መዝናኛ፣ የእግር ጉዞ መንገዶችና የአረንጓዴ ልማት ማዕከልነት እንዴት መቀየር እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ታላቅ ስኬት ነው።
በእንጦጦ እና በቀበና ተፋሰስ መካከል በተገነቡት ዘመናዊ የሕዝብ መጠቀሚያ ሥፍራዎች ውስጥ የሚገኙት ውብ የእግር ጉዞ መስመሮች፣ የተፈጥሮን ሚዛን የጠበቁ የአትክልትና የዛፍ ዝርያዎች እንዲሁም ለዕረፍትና ለንባብ የተዘጋጁ ምቹ መቀመጫዎች ተፈጥሮንና ዘመናዊነትን በአንድ ጥላ ሥር ያቀናጁ ናቸው።
ነዋሪዎችና ጎብኚዎች ከከተማዋ የዕለት ተዕለት ጫጫታና ውጥረት ወጥተው ንጹህ አየር የሚተነፍሱበት አካላዊና አዕምሯዊ ጤንነታቸውን የሚያድሱበት ሰላማዊ ምኅዳር ተፈጥሯል።
ይህ መሠረተ ልማት በከተማ ፕላን ውስጥ ለሰዎች ቅድሚያ የመስጠትን መርህ ያረጋገጠ ከመሆኑም በላይ ወንዞች የከተማዋ የጀርባ አጥንትና የውበት መገለጫ መሆን እንደሚችሉ ያስመሰከረ አብነት ነው።
የዚህ የገጽታ መቀየር ዘላቂ ፋይዳ በዋናነት በሦስት ታላላቅ ዘርፎች ጎልቶ ይታያል። የመጀመሪያውና ግዙፉ ተጽዕኖ በቱሪዝም ዘርፍ ላይ የታየው አስደናቂ መነቃቃት ነው። አዲስ አበባ ቀደም ሲል የዓለም አቀፍ ስብሰባዎችና የትራንዚት መንገደኞች ጊዜያዊ ማረፊያ ብቻ ሆና የምትታወቅበትን የቆየ ገጽታ በመቀየር አሁን ላይ ጎብኚዎች ቀናትን አሳልፈው የሚዝናኑባትና የሚጎበኟት እውነተኛ የመዳረሻ ከተማ እየሆነች ነው።
የወንዝ ዳርቻዎቹ ውበት፣ ማራኪ የውሃ ፏፏቴዎችና በምሽት በደማቅና ውብ መብራቶች የሚዋቡት ፓርኮች ለምሽት ቱሪዝም አዲስ በር ከፍተዋል። ይህም የፎቶግራፍ አፍቃሪዎችንና ማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎችን የሚስቡ በርካታ ማራኪ ቦታዎችን በመፍጠር የከተማዋን ዓለም አቀፍ ገጽታ በከፍተኛ ደረጃ ገንብቶታል።
ሁለተኛው ከኢኮኖሚ ዕድገትና ከሥራ ዕድል ፈጠራ ጋር የተያያዘ ነው። በእነዚህ የተገነቡ የሕዝብ መጠቀሚያዎች ዙሪያ የሚንቀሳቀሱ አነስተኛና መካከለኛ የንግድ ተቋማት፣ ባህላዊ የምግብና የመጠጥ አቅራቢዎች እንዲሁም የዕደ-ጥበብ ውጤቶች መሸጫዎች ለበርካታ ዜጎች ዘላቂ የገቢ ምንጭና የሥራ ዕድል መፍጠር ችለዋል። ይህ ሁኔታ የከተማዋን የምጣኔ ሀብት እንቅስቃሴ በማነቃቃት የቱሪዝም ኢኮኖሚው በቀጥታ ወደ ማኅበረሰቡ እንዲደርስ አድርጓል።
ሶስተኛውና ትልቁ ስኬት የአካባቢ ጥበቃና የስነ-ምህዳር ሚዛንን ከመጠበቅ አንጻር የተመዘገበው ዘላቂ ውጤት ነው። ወንዞችን ከኢንዱስትሪና ከቤት ውስጥ ብክለት መታደግ መቻሉ፣ በዳርቻዎቻቸው ላይ የተተከሉ አረንጓዴ ተክሎችና ዛፎች የከተማዋን የካርቦን ልቀትን ለመቀነስና ብዝሃ ሕይወትን መልሶ ለማደስ ያላቸው ሚና ወደር የለውም።
በአጠቃላይ ሲታይ በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የተመዘገበው የወንዝ ዳርቻ ልማትና የውበት ስራ ከተማዋን ይበልጥ ለኑሮ ተስማሚ፣ ለዐይን ማራኪና በኢኮኖሚ ረገድ እራሷን የቻለች ማዕከል እያደረጋት ይገኛል።
ይህ ዓይነቱ የተቀናጀ የልማት አካሄድ አዲስ አበባ በአፍሪካ አህጉር ያላትን ተወዳዳሪነት ይበልጥ የሚያጠናክር ከመሆኑም በላይ ለቀጣይ ትውልድ የሚሻገር ታላቅ የታሪክና የውበት ዐሻራ ነው።
በበረከት ሽመልስ
#addisababa #riversidedevelopment #greenlegacy #tourismethiopia #ethiopianbroadcastingcorporation
********************
አዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ያስመዘገበችው ግዙፍ የከተማ ገጽታ ለውጥ ከመሠረተ ልማት ዝርጋታ ባሻገር የከተማዋን ነዋሪዎች አኗኗር፣ ማኅበራዊ መስተጋብርና የኢኮኖሚ አቅጣጫ የቀየረ ጥልቅ ስትራቴጂካዊ ሽግግር ነው።
ለረጅም ዘመናት አዲስ አበባ በከፍተኛ የሕዝብ ቁጥር ማደግ፣ በኮንክሪት ሕንጻዎች መበራከትና በአረንጓዴ ሥፍራዎች መመናመን ትታወቅ የነበረች ቢሆንም በቅርቡ የተከናወኑት የተቀናጁ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት ሥራዎች ግን ከተማዋን ወደ አዲስ የዕድገትና የውበት ምዕራፍ አሸጋግረዋታል።
ይህ ዘመናዊ ለውጥ በተለይም ቀደም ሲል የብክለት፣ የቸልተኝነትና የከተማዋ የጀርባ ገጽታ መገለጫ የነበሩትን የውሃ አካላትና ተፋሰሶች ወደ ሕያው፣ ማራኪና ሥነ-ምህዳራዊ ጠቀሜታ ወደላቸው የሕዝብ መጠቀሚያዎች በመለወጥ ረገድ ያተመዘገበው ስኬት የከተማዋን ታሪክና ገጽታ ሙሉ በሙሉ ቀይሮታል።
ይህ ዓይነቱ ትራንስፎርሜሽን የከተማዋን ነዋሪዎች የኑሮ ጥራት ከማሻሻሉም በላይ አዲስ አበባ በዓለም አቀፍና በአህጉራዊ መድረኮች ያላትን የላቀ አቋምና የቱሪስት መዳረሻነት በከፍተኛ ደረጃ እያሳደገው ይገኛል።
ለዚህም በዋና ማሳያነት የሚጠቀሰው ከእንጦጦ ጋራ ተነስቶ እስከ ቀበና የሚዘልቀው የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ነው። ይህ ሰፊ ኮሪደር ቀደም ሲል ለደህንነት አስጊና በቆሻሻ መጣያነት ያገለግል የነበረ አካባቢን ወደ ዘመናዊ የሕዝብ መዝናኛ፣ የእግር ጉዞ መንገዶችና የአረንጓዴ ልማት ማዕከልነት እንዴት መቀየር እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ታላቅ ስኬት ነው።
በእንጦጦ እና በቀበና ተፋሰስ መካከል በተገነቡት ዘመናዊ የሕዝብ መጠቀሚያ ሥፍራዎች ውስጥ የሚገኙት ውብ የእግር ጉዞ መስመሮች፣ የተፈጥሮን ሚዛን የጠበቁ የአትክልትና የዛፍ ዝርያዎች እንዲሁም ለዕረፍትና ለንባብ የተዘጋጁ ምቹ መቀመጫዎች ተፈጥሮንና ዘመናዊነትን በአንድ ጥላ ሥር ያቀናጁ ናቸው።
ነዋሪዎችና ጎብኚዎች ከከተማዋ የዕለት ተዕለት ጫጫታና ውጥረት ወጥተው ንጹህ አየር የሚተነፍሱበት አካላዊና አዕምሯዊ ጤንነታቸውን የሚያድሱበት ሰላማዊ ምኅዳር ተፈጥሯል።
ይህ መሠረተ ልማት በከተማ ፕላን ውስጥ ለሰዎች ቅድሚያ የመስጠትን መርህ ያረጋገጠ ከመሆኑም በላይ ወንዞች የከተማዋ የጀርባ አጥንትና የውበት መገለጫ መሆን እንደሚችሉ ያስመሰከረ አብነት ነው።
የዚህ የገጽታ መቀየር ዘላቂ ፋይዳ በዋናነት በሦስት ታላላቅ ዘርፎች ጎልቶ ይታያል። የመጀመሪያውና ግዙፉ ተጽዕኖ በቱሪዝም ዘርፍ ላይ የታየው አስደናቂ መነቃቃት ነው። አዲስ አበባ ቀደም ሲል የዓለም አቀፍ ስብሰባዎችና የትራንዚት መንገደኞች ጊዜያዊ ማረፊያ ብቻ ሆና የምትታወቅበትን የቆየ ገጽታ በመቀየር አሁን ላይ ጎብኚዎች ቀናትን አሳልፈው የሚዝናኑባትና የሚጎበኟት እውነተኛ የመዳረሻ ከተማ እየሆነች ነው።
የወንዝ ዳርቻዎቹ ውበት፣ ማራኪ የውሃ ፏፏቴዎችና በምሽት በደማቅና ውብ መብራቶች የሚዋቡት ፓርኮች ለምሽት ቱሪዝም አዲስ በር ከፍተዋል። ይህም የፎቶግራፍ አፍቃሪዎችንና ማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎችን የሚስቡ በርካታ ማራኪ ቦታዎችን በመፍጠር የከተማዋን ዓለም አቀፍ ገጽታ በከፍተኛ ደረጃ ገንብቶታል።
ሁለተኛው ከኢኮኖሚ ዕድገትና ከሥራ ዕድል ፈጠራ ጋር የተያያዘ ነው። በእነዚህ የተገነቡ የሕዝብ መጠቀሚያዎች ዙሪያ የሚንቀሳቀሱ አነስተኛና መካከለኛ የንግድ ተቋማት፣ ባህላዊ የምግብና የመጠጥ አቅራቢዎች እንዲሁም የዕደ-ጥበብ ውጤቶች መሸጫዎች ለበርካታ ዜጎች ዘላቂ የገቢ ምንጭና የሥራ ዕድል መፍጠር ችለዋል። ይህ ሁኔታ የከተማዋን የምጣኔ ሀብት እንቅስቃሴ በማነቃቃት የቱሪዝም ኢኮኖሚው በቀጥታ ወደ ማኅበረሰቡ እንዲደርስ አድርጓል።
ሶስተኛውና ትልቁ ስኬት የአካባቢ ጥበቃና የስነ-ምህዳር ሚዛንን ከመጠበቅ አንጻር የተመዘገበው ዘላቂ ውጤት ነው። ወንዞችን ከኢንዱስትሪና ከቤት ውስጥ ብክለት መታደግ መቻሉ፣ በዳርቻዎቻቸው ላይ የተተከሉ አረንጓዴ ተክሎችና ዛፎች የከተማዋን የካርቦን ልቀትን ለመቀነስና ብዝሃ ሕይወትን መልሶ ለማደስ ያላቸው ሚና ወደር የለውም።
በአጠቃላይ ሲታይ በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የተመዘገበው የወንዝ ዳርቻ ልማትና የውበት ስራ ከተማዋን ይበልጥ ለኑሮ ተስማሚ፣ ለዐይን ማራኪና በኢኮኖሚ ረገድ እራሷን የቻለች ማዕከል እያደረጋት ይገኛል።
ይህ ዓይነቱ የተቀናጀ የልማት አካሄድ አዲስ አበባ በአፍሪካ አህጉር ያላትን ተወዳዳሪነት ይበልጥ የሚያጠናክር ከመሆኑም በላይ ለቀጣይ ትውልድ የሚሻገር ታላቅ የታሪክና የውበት ዐሻራ ነው።
በበረከት ሽመልስ
#addisababa #riversidedevelopment #greenlegacy #tourismethiopia #ethiopianbroadcastingcorporation
1 month ago
እንጦጦ እስከ ቀበና የወንዝ ዳርቻ ሲገለጥ
Entoto to Kebena Riverside Unveiled
የእንጦጦ–ቀበና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ተመረቀ
#ethiopia | የአዲስ አበባን ስነ-ምህዳር፣ ቱሪዝምና ኢኮኖሚ ለማጠናከር የታለመ ግዙፍ ፕሮጀክት
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ የተመረቀው የእንጦጦ–ቀበና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት፣ የአዲስ አበባን የከተማ ገጽታ ከማሻሻል ባለፈ የስነ-ምህዳር ጥበቃ፣ የመሰረተ ልማት ማሻሻያ እና የኢኮኖሚ ዕድሎችን ለማስፋፋት የታለመ ትልቅ ፕሮጀክት ነው።
ፕሮጀክቱ የወንዝ ተፋሰስን በማልማትና ከተማዋን ለነዋሪዎች እና ለጎብኚዎች የተሻለች ለማድረግ የሚያግዙ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን አካትቷል።
የፕሮጀክቱ ዋና ዋና ክፍሎች
የወንዝ ልማት
- 1 ትልቅ ግድብ
- 16 አነስተኛ ግድቦች
- 3 ቼክ ዳሞች
- 20.2 ኪሎ ሜትር የድጋፍ ግንብ
የወንዝ ዳርቻ ጥበቃ
- 36.9 ኪሎ ሜትር የአፈርና የስነ-ምህዳር ጥበቃ ሥራዎች፣ የኮንሶ ጋቢዮን እና እርከን ሥራዎችን ጨምሮ።
አረንጓዴ ልማት
- 59.7 ሄክታር አረንጓዴ ሽፋን
- 50,330 ዛፎች ተተክለዋል
የተቀናጀ መሰረተ ልማት
- 21 የእግረኛ ድልድዮች
- 33.2 ኪሎ ሜትር የውስጥ መንገዶች
- የፍሳሽ መስመር
- 695 ተሽከርካሪዎችን የሚያስተናግዱ 7 የመኪና ማቆሚያ ስፍራዎች ናቸው።
Entoto to Kebena Riverside Unveiled
የእንጦጦ–ቀበና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ተመረቀ
#ethiopia | የአዲስ አበባን ስነ-ምህዳር፣ ቱሪዝምና ኢኮኖሚ ለማጠናከር የታለመ ግዙፍ ፕሮጀክት
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ የተመረቀው የእንጦጦ–ቀበና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት፣ የአዲስ አበባን የከተማ ገጽታ ከማሻሻል ባለፈ የስነ-ምህዳር ጥበቃ፣ የመሰረተ ልማት ማሻሻያ እና የኢኮኖሚ ዕድሎችን ለማስፋፋት የታለመ ትልቅ ፕሮጀክት ነው።
ፕሮጀክቱ የወንዝ ተፋሰስን በማልማትና ከተማዋን ለነዋሪዎች እና ለጎብኚዎች የተሻለች ለማድረግ የሚያግዙ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን አካትቷል።
የፕሮጀክቱ ዋና ዋና ክፍሎች
የወንዝ ልማት
- 1 ትልቅ ግድብ
- 16 አነስተኛ ግድቦች
- 3 ቼክ ዳሞች
- 20.2 ኪሎ ሜትር የድጋፍ ግንብ
የወንዝ ዳርቻ ጥበቃ
- 36.9 ኪሎ ሜትር የአፈርና የስነ-ምህዳር ጥበቃ ሥራዎች፣ የኮንሶ ጋቢዮን እና እርከን ሥራዎችን ጨምሮ።
አረንጓዴ ልማት
- 59.7 ሄክታር አረንጓዴ ሽፋን
- 50,330 ዛፎች ተተክለዋል
የተቀናጀ መሰረተ ልማት
- 21 የእግረኛ ድልድዮች
- 33.2 ኪሎ ሜትር የውስጥ መንገዶች
- የፍሳሽ መስመር
- 695 ተሽከርካሪዎችን የሚያስተናግዱ 7 የመኪና ማቆሚያ ስፍራዎች ናቸው።
1 month ago
Sponsored by
Surafel
1 month ago
1 month ago
አዲስ አበባ የነዋሪዎቿን ጥያቄዎችና መሰረታዊ ፍላጎቶች በተጨባጭ እየመለሰች ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የነዋሪዎች ጥያቄ እና መሰረታዊ ፍላጎት በተጨባጭ እየተመለሰ ነው አሉ፡፡
የእንጦጦ-ቀበና የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት እንዲሁም የቀበና ግድብ ፕሮጀክት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።
ከንቲባ አዳነች በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት÷ አዲስ አበባ ለሕዝባችን ቅድሚያ የሚሰጣቸውንና ከተማዋ የሚመጥናትን ታላላቅ የልማት ሥራዎች በላቀ ብቃትና ትጋት እያከናወነች ትገኛለች ብለዋል።
ዛሬ ለከተማችን ድምቀት፣ ተጨማሪ ጌጥ እና የውበት ፀዳል ያላበሰውን የወንዝ ዳርቻ እና የግድብ ልማት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በተሰጠን የስራ መመሪያ መሰረት በጥራትና በፍጥነት አጠናቀን ለሕዝብ አቅርበናል ነው ያሉት።
ፕሮጀክቱ አዲስ አበባ በዓለም አቀፍ ደረጃ ምርጧ የቱሪስት መዳረሻ ብቻ ሳትሆን የውበት ማማ የሚያደርጋት ድንቅ ሥራ ነው ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡
ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ 87 ነጥብ 6 ሔክታር መሬት እንደሚሸፍን ጠቁመው ÷ 10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ርዝመት እንዳለው ገልጸዋል፡፡
በውስጡም የጋራ አገልግሎት መስጫዎችን እና የሕዝብ መገልገያዎችን አሟልቶ መያዙን ነው የገለጹት፡፡
ፕሮጀክቱ በታለመለት የጊዜ እና የጥራት ደረጃ እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ከንቲባ አዳነች ምስጋና አቅርበዋል፡፡
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የነዋሪዎች ጥያቄ እና መሰረታዊ ፍላጎት በተጨባጭ እየተመለሰ ነው አሉ፡፡
የእንጦጦ-ቀበና የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት እንዲሁም የቀበና ግድብ ፕሮጀክት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዛሬው ዕለት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።
ከንቲባ አዳነች በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት÷ አዲስ አበባ ለሕዝባችን ቅድሚያ የሚሰጣቸውንና ከተማዋ የሚመጥናትን ታላላቅ የልማት ሥራዎች በላቀ ብቃትና ትጋት እያከናወነች ትገኛለች ብለዋል።
ዛሬ ለከተማችን ድምቀት፣ ተጨማሪ ጌጥ እና የውበት ፀዳል ያላበሰውን የወንዝ ዳርቻ እና የግድብ ልማት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በተሰጠን የስራ መመሪያ መሰረት በጥራትና በፍጥነት አጠናቀን ለሕዝብ አቅርበናል ነው ያሉት።
ፕሮጀክቱ አዲስ አበባ በዓለም አቀፍ ደረጃ ምርጧ የቱሪስት መዳረሻ ብቻ ሳትሆን የውበት ማማ የሚያደርጋት ድንቅ ሥራ ነው ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡
ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ 87 ነጥብ 6 ሔክታር መሬት እንደሚሸፍን ጠቁመው ÷ 10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ርዝመት እንዳለው ገልጸዋል፡፡
በውስጡም የጋራ አገልግሎት መስጫዎችን እና የሕዝብ መገልገያዎችን አሟልቶ መያዙን ነው የገለጹት፡፡
ፕሮጀክቱ በታለመለት የጊዜ እና የጥራት ደረጃ እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ከንቲባ አዳነች ምስጋና አቅርበዋል፡፡
1 month ago
የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ ተመርቋል
****************************
87.6 ሄክታር መሬት የሚሸፍነውን እና 10.5 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለውን የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትን ዛሬ በይፋ መርቀናል።
ይህ ሰፊ መሰረተ ልማት የወንዝ መከላከያ ግንቦችን፣ ዘመናዊ ድልድዮችን እና ሰፊ አረንጓዴ ስፍራዎችን በጋራ የያዘ ነው።
ፕሮጀክቱ የግንባታ ስኬት ብቻ ሳይሆን፣ መዲናችንን የአየር ንብረት ለውጥን የምትቋቋምና ለነዋሪዎቿ ምቹ የሆነች፣ ዓለም አቀፍ የቱሪዝም እና የኢኮኖሚ ማዕከል ለማድረግ የጀመርነውን ስልታዊ ሽግግር የሚያፋጥን ታላቅ አጋጣሚ ነው።
የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን
1 month ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትን መረቁ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክትን በዛሬው ዕለት መርቀዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት÷ ይህ ሰፊ መሰረተ ልማት የወንዝ መከላከያ ግንቦችን፣ ዘመናዊ ድልድዮችን እና ሰፊ አረንጓዴ ስፍራዎችን በጋራ የያዘ ነው ብለዋል።
በዛሬው ዕለት የተመረቀው ፕሮጀክት 87 ነጥብ 6 ሄክታር መሬት የሚሸፍን ሲሆን ÷ 10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ርዝመት እንዳለው አመልክተዋል፡፡
ፕሮጀክቱ የግንባታ ስኬት ብቻ ሳይሆን መዲናዋን የአየር ንብረት ለውጥን የምትቋቋምና ለነዋሪዎቿ ምቹ የሆነች፣ ዓለም አቀፍ የቱሪዝም እና የኢኮኖሚ ማዕከል ለማድረግ የጀመርነውን ስልታዊ ሽግግር የሚያፋጥን ታላቅ አጋጣሚ ነው ብለዋል።
የተሰጠንን ሕዝባዊ አደራ በታማኝነት፣ በጽኑ ትጋት እና በቅንነት በመፈጸም የዜጎቻችንን የኑሮ ጥራት ለማሻሻልና መሠረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጀመርነውን ጉዞ አበክረን እንቀጥላለን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ከተግባር ከፍታ ወደ ብሔራዊ ጽናት - የኢትዮጵያ የሜጋ ፕሮጀክቶች የስኬት ዐሻራ
****************
(የዕለቱ መልእክት)
ኢትዮጵያ ታሪክን በንግግር እና በምኞት ሳይሆን፣ በተግባር እና በግዙፍ ፕሮጀክቶች የምትቀይርበት ልዩ የዕድገት ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
“አፍ ተናግሮ እግር ሲያፍር፣ ልብ አዝኖ ዐይን ሲያለቅስ” እንደሚሉት ሳይሆን፣ ዛሬ በሀገራችን እየታየ ያለው የቃል እና የተግባር መገጣጠም ነው።
“ከነገሩ ጽናቱ” እንዲሉ በተግባር ከፍታ የተመሰከረላቸው ግዙፍ የልማት አውታሮች የብሔራዊ ጽናታችን ማማ ሆነው በግልጽ እየታዩ ነው።
ለዚህም በቢሾፍቱ እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ በኢንቨስትመንት መጠኑ እና በሥራው ግዝፈት በአፍሪካ ታሪክ ብቸኛው ፕሮጀክት መሆኑ ቀዳሚ ማሳያ ነው።
“አውቆ የተነገረ ከልብ ይደርሳል” እንደሚባለው በአዲስ አበባ ከተማ ታቅደው በአጭር ጊዜ የተጠናቀቁት እንደ ወዳጅነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ የወንዝ ዳር ልማቶች፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የዓድዋ ድል መታሰቢያ ያሉ ታላላቅ ፕሮጀክቶች መሬት ላይ የወረዱ እውነታዎች እንጂ የሩቅ ሕልሞች አይደሉም።
ከዚህም ባሻገር ሌሊት እና ቀን የተሠራው እና እየተሠራ ያለው የኮሪደር ልማት የመንግሥትን የፕሮጀክት ፈጻሚነት አቅም ቁልጭ አድርጎ ያመላከተ ሲሆን፣ ይህ ስኬት መንግሥት ላለፉት ዓታት በትኩረት ሲተገብራቸው የቆያቸው የልማት አፈጻጸሞች ቀጣይ ማሳያ ነው።
ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ መዘግየቶችን በመስበር እንደ ስኳር ፕሮጀክቶች ያሉ ግዙፍ ተቋማትን ማጠናቀቅ መቻሉ የመንግሥት ቁርጠኝነት በተግባር የታየበት ነው። ከሁሉም በላይ ደግሞ የኢትዮጵያውያን ዳግማዊ ዓድዋ የሆነው የታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ እና በቅርቡ የተበሰሩት የጉባ ብሥራቶች፣ ሀገራችን የማይቻሉ የሚመስሉ ታላላቅ ሕልሞችን የመፈጸም አቅም እንዳላት ለዓለም የመሰከሩበት ታሪካዊ ምዕራፍ ናቸው።
በአፈጻጸም ሂደት ላይ የሚያጋጥሙ ማነቆዎችን መንግሥት በግልጽ ለሕዝብ የሚያሳውቅ ከሆነ፣ ሕዝቡ ውሳኔዎችን የመረዳት እና የመቀበል ዝንባሌው ይጨምራል። “እውነት እና ንጋት እያደር ይጠራል” እንዲሉ ግልጽነት መተማመንን ይፈጥራል።
በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ (እንደ ወንጪ፣ ኮይሻ፣ ጎርጎራ) ፕሮጀክቶች ላይ ከሕዝብ የተሰበሰበው ሀብት እንዴት ወደ ተጨባጭ ልማት እንደተለወጠ ደረጃ በደረጃ ለሕዝቡ ይፋ መሆኑ ግልጽነትን አጠናክሯል። የመደመር እሳቤም ዋና ምሰሶ ይኸው ነው - ሀገርን በጋራ መገንባት።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቢሾፍቱ እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግዝፈት እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም አስመልክተው ሲናገሩ፤ "ይህንን ያህል ማሽን የሚንቀሳቀስበት ሥራ እንደ ሀገር መርተን አናውቅም፤ የመጀመሪያችን ነው። ሥርዓት ቢኖረን፣ በየቀኑ ሥራዎቻችንን ማየት ብንችል፣ አብዛኛው ፕሮጀክት በተጀመረለት ጊዜ እና ጥራት አልቆ የሕዝብን እርካታ ሊያረጋግጥ ይችላል" ብለዋል።
ይህ ተከታታይነት እና ወጥነት ያለው የፕሮጀክቶች አፈጻጸም በቁስ አካል ደረጃ ከሚታዩ ውጤቶች ባሻገር፣ በሀገራችን የአስተዳደር ሥነ ልቦና ላይ ታላቅ የባህል ለውጥ ፈጥሯል። የዘገምተኛነት እና የቢሮክራሲ ሰንሰለትን ሙሉ በሙሉ በመበጠስ፣ አሁን ላይ ሌሊት እና ቀን ሳይለዩ የማያቋርጥ ሥራ የመሥራት፣ የቀጠሮ ትክክለኛነት እና ፈጣን ውሳኔ የመስጠት አዲስ ሀገራዊ የፈጠነ ሥራ ባህል ተተክሏል።
የሜጋ ፕሮጀክቶች መሳካት ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸው በላይ የኅብረተሰቡን ሥነ ልቦና የማነጽ እና የጋራ ማንነትን የማንቃት ታላቅ አቅም አላቸው። ለረጅም ዘመናት በአንዳንዶች ዘንድ ይንጸባረቅ የነበረውን የተሸናፊነት እና የዝቅተኝነት ሥነ ልቦና ሙሉ በሙሉ በመስበር፣ “እኛም እንችላለን” የሚል የጽኑ እምነት እና የሀገራዊ ኩራት ስሜት በትውልዱ ልብ ውስጥ እንዲቀረጽ አድርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሥራው ላይ ለሚታዩት ተግዳሮቶች እና የጥርጣሬ ሐሳቦች በሰጡት ምላሽ፤ "ብዙዎች ‘አትችሉም፣ ገንዘቡም አይገኝም፣ ሥራውን መምራት አይሆንላችሁም’ የሚል እሳቤ ሲያራግቡ ይሰማል። እኛ ደግሞ ‘እንችላለን፤ ይገባናል፤ የሚመጥነን ትልቅ ነገር ነው’ እያልን ነው። ማን እንደሚያሸንፍ ጊዜው ሲደርስ እናያለን" በማለት የሀገራችንን ጽኑ አቋም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያውያን በራሳቸው ተነሣሽነት እና ብርታት በተደጋጋሚ ታሪክ እየሠሩ መሆናቸውን በተግባር አሳይተዋል።
በመሆኑም መላው ሕዝብ በተባበረ ክንድ ድህነትን ለመስበር፣ የጠለሸ ማንነትን ለመቀየር እና የበለጸገች ሀገር ለትውልድ ለማውረስ “ሳይደክሙ አይታለፍም የኑሮ አቀበት” እንዲሉ በሥራ እና በልፋት ብቻ መረባረብ ይኖርበታል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ebc #ethiopia #megaprojects #pmabiyahmed
****************
(የዕለቱ መልእክት)
ኢትዮጵያ ታሪክን በንግግር እና በምኞት ሳይሆን፣ በተግባር እና በግዙፍ ፕሮጀክቶች የምትቀይርበት ልዩ የዕድገት ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
“አፍ ተናግሮ እግር ሲያፍር፣ ልብ አዝኖ ዐይን ሲያለቅስ” እንደሚሉት ሳይሆን፣ ዛሬ በሀገራችን እየታየ ያለው የቃል እና የተግባር መገጣጠም ነው።
“ከነገሩ ጽናቱ” እንዲሉ በተግባር ከፍታ የተመሰከረላቸው ግዙፍ የልማት አውታሮች የብሔራዊ ጽናታችን ማማ ሆነው በግልጽ እየታዩ ነው።
ለዚህም በቢሾፍቱ እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ በኢንቨስትመንት መጠኑ እና በሥራው ግዝፈት በአፍሪካ ታሪክ ብቸኛው ፕሮጀክት መሆኑ ቀዳሚ ማሳያ ነው።
“አውቆ የተነገረ ከልብ ይደርሳል” እንደሚባለው በአዲስ አበባ ከተማ ታቅደው በአጭር ጊዜ የተጠናቀቁት እንደ ወዳጅነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ የወንዝ ዳር ልማቶች፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የዓድዋ ድል መታሰቢያ ያሉ ታላላቅ ፕሮጀክቶች መሬት ላይ የወረዱ እውነታዎች እንጂ የሩቅ ሕልሞች አይደሉም።
ከዚህም ባሻገር ሌሊት እና ቀን የተሠራው እና እየተሠራ ያለው የኮሪደር ልማት የመንግሥትን የፕሮጀክት ፈጻሚነት አቅም ቁልጭ አድርጎ ያመላከተ ሲሆን፣ ይህ ስኬት መንግሥት ላለፉት ዓታት በትኩረት ሲተገብራቸው የቆያቸው የልማት አፈጻጸሞች ቀጣይ ማሳያ ነው።
ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ መዘግየቶችን በመስበር እንደ ስኳር ፕሮጀክቶች ያሉ ግዙፍ ተቋማትን ማጠናቀቅ መቻሉ የመንግሥት ቁርጠኝነት በተግባር የታየበት ነው። ከሁሉም በላይ ደግሞ የኢትዮጵያውያን ዳግማዊ ዓድዋ የሆነው የታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ እና በቅርቡ የተበሰሩት የጉባ ብሥራቶች፣ ሀገራችን የማይቻሉ የሚመስሉ ታላላቅ ሕልሞችን የመፈጸም አቅም እንዳላት ለዓለም የመሰከሩበት ታሪካዊ ምዕራፍ ናቸው።
በአፈጻጸም ሂደት ላይ የሚያጋጥሙ ማነቆዎችን መንግሥት በግልጽ ለሕዝብ የሚያሳውቅ ከሆነ፣ ሕዝቡ ውሳኔዎችን የመረዳት እና የመቀበል ዝንባሌው ይጨምራል። “እውነት እና ንጋት እያደር ይጠራል” እንዲሉ ግልጽነት መተማመንን ይፈጥራል።
በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ (እንደ ወንጪ፣ ኮይሻ፣ ጎርጎራ) ፕሮጀክቶች ላይ ከሕዝብ የተሰበሰበው ሀብት እንዴት ወደ ተጨባጭ ልማት እንደተለወጠ ደረጃ በደረጃ ለሕዝቡ ይፋ መሆኑ ግልጽነትን አጠናክሯል። የመደመር እሳቤም ዋና ምሰሶ ይኸው ነው - ሀገርን በጋራ መገንባት።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቢሾፍቱ እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግዝፈት እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም አስመልክተው ሲናገሩ፤ "ይህንን ያህል ማሽን የሚንቀሳቀስበት ሥራ እንደ ሀገር መርተን አናውቅም፤ የመጀመሪያችን ነው። ሥርዓት ቢኖረን፣ በየቀኑ ሥራዎቻችንን ማየት ብንችል፣ አብዛኛው ፕሮጀክት በተጀመረለት ጊዜ እና ጥራት አልቆ የሕዝብን እርካታ ሊያረጋግጥ ይችላል" ብለዋል።
ይህ ተከታታይነት እና ወጥነት ያለው የፕሮጀክቶች አፈጻጸም በቁስ አካል ደረጃ ከሚታዩ ውጤቶች ባሻገር፣ በሀገራችን የአስተዳደር ሥነ ልቦና ላይ ታላቅ የባህል ለውጥ ፈጥሯል። የዘገምተኛነት እና የቢሮክራሲ ሰንሰለትን ሙሉ በሙሉ በመበጠስ፣ አሁን ላይ ሌሊት እና ቀን ሳይለዩ የማያቋርጥ ሥራ የመሥራት፣ የቀጠሮ ትክክለኛነት እና ፈጣን ውሳኔ የመስጠት አዲስ ሀገራዊ የፈጠነ ሥራ ባህል ተተክሏል።
የሜጋ ፕሮጀክቶች መሳካት ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸው በላይ የኅብረተሰቡን ሥነ ልቦና የማነጽ እና የጋራ ማንነትን የማንቃት ታላቅ አቅም አላቸው። ለረጅም ዘመናት በአንዳንዶች ዘንድ ይንጸባረቅ የነበረውን የተሸናፊነት እና የዝቅተኝነት ሥነ ልቦና ሙሉ በሙሉ በመስበር፣ “እኛም እንችላለን” የሚል የጽኑ እምነት እና የሀገራዊ ኩራት ስሜት በትውልዱ ልብ ውስጥ እንዲቀረጽ አድርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሥራው ላይ ለሚታዩት ተግዳሮቶች እና የጥርጣሬ ሐሳቦች በሰጡት ምላሽ፤ "ብዙዎች ‘አትችሉም፣ ገንዘቡም አይገኝም፣ ሥራውን መምራት አይሆንላችሁም’ የሚል እሳቤ ሲያራግቡ ይሰማል። እኛ ደግሞ ‘እንችላለን፤ ይገባናል፤ የሚመጥነን ትልቅ ነገር ነው’ እያልን ነው። ማን እንደሚያሸንፍ ጊዜው ሲደርስ እናያለን" በማለት የሀገራችንን ጽኑ አቋም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያውያን በራሳቸው ተነሣሽነት እና ብርታት በተደጋጋሚ ታሪክ እየሠሩ መሆናቸውን በተግባር አሳይተዋል።
በመሆኑም መላው ሕዝብ በተባበረ ክንድ ድህነትን ለመስበር፣ የጠለሸ ማንነትን ለመቀየር እና የበለጸገች ሀገር ለትውልድ ለማውረስ “ሳይደክሙ አይታለፍም የኑሮ አቀበት” እንዲሉ በሥራ እና በልፋት ብቻ መረባረብ ይኖርበታል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ebc #ethiopia #megaprojects #pmabiyahmed
2 months ago
የ5ቱ ዓመታት ገፆች፦ መደመር ያዋለዳቸው የገበታ ፕሮጀክቶች
**************
ታሪክ በየዘመኑ የራሱን ዐሻራ ጥሎ ያልፋል። ከስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ አንስቶ ወደ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዋዜማ ስንሸጋገር የተፃፉት የአምስቱ ዓመታት ገፆች ደግሞ፣ ኢትዮጵያ ድብቅ የተፈጥሮ ውበቷንና ፀዳሏን አውጥታ ለዓለም ያሳየችባቸው የውበት አብዮት ድርሳናት ናቸው።
ለዘመናት "የ13 ወር ፀጋ" በሚለው የቱሪዝም መሪ ቃል ብቻ ስትጠራ የነበረችው ሀገራችን፣ ዛሬ ከመፈክር ባለፈ "ምድረ ቀደምት" በሚለው ከፍታዋ ልክ በተጨባጭ በዓለም አቀፍ መድረክ ደምቃ እንድትታይ ያደረጋት አስደናቂ የታሪክ እጥፋት ተፈጥሯል። የዚህ ታላቅ ሀገራዊ ትራንስፎርሜሽን የጀርባ አጥንትና ሞተር ደግሞ ከመደመር እሳቤ የተወለዱት የ"ገበታ" ፕሮጀክቶች ናቸው።
የገበታ ፕሮጀክቶች “ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ” ተራ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች አይደሉም። ይልቁንም ሃብትን አስተባብሮ ከተፈጥሮ ፀጋዎች ጋር በማዋሀድ ኢትዮጵያን ወደ ተፈጥሯዊ የቱሪዝም መስህብነት የቀየሩና ከመደመር እሳቤ የፈለቁ እውነተኛ ኢትዮጵያዊ ትርክቶች ናቸው። የመደመር ትውልድ ሀገርን ማልማት ማለት የውጭ ዕርዳታን መጠበቅ ሳይሆን፣ የራስን እምቅ አቅም፣ የተፈጥሮ ውበትና ታሪክን ወደ ኢኮኖሚያዊ እሴት መቀየር መሆኑን በተግባር አሳይቶበታል።
ይህ የገበታ ጉዞ የተጀመረው በ"ገበታ ለሸገር" ሲሆን፣ ለዘመናት በቆሻሻ ተውጠው የነበሩ የከተማ ቦታዎችንና የተተው ተራራዎችን ወደ ምድር ገነት ቀይሯቸዋል። ጫካና ገደል የነበረው የእንጦጦ ተራራ ወደ ማራኪው "እንጦጦ ፓርክ" ሲቀየር፣ የአዲስ አበባን የልብ ትርታ ያደሰው "ወዳጅነት ፓርክ" እና ታሪክን ከተፈጥሮ ጋር ያዋሀደው ግዙፉ "አንድነት ፓርክ" የዚህ ስኬት በኩር ፍሬዎች ሆነዋል።
ይህ ስኬት በመዲናዋ ብቻ አልተገታም፤ የመደመር እሳቤ "ገበታ ለሀገር" በሚል አዲስ ሀገራዊ ንቅናቄ መላዋን ኢትዮጵያ አዳረሰ። ማራኪው የ"ወንጪ" ሐይቅ ከተፈጥሮ አቀማመጡ ጋር በተዋሀደ መልኩ በዓለም አቀፍ ስታንዳርድ ለቱሪዝም ክፍት ሆነ። የጣናን ሐይቅ ሞገድ የሚያማትረው የ"ጎርጎራ" ፕሮጀክት ታሪካዊቷን ከተማ ዳግም ሲያነቃ፣ በደቡብ ምዕራብ የሚገኘው "ኮይሻ" እና የታላቁ ሸለቆ ድንቅ ስጦታ የሆነው "ሀላላ ኬላ ሎጅ" እንዲሁም በጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ የተገነባው “ጨበራ የዝሆን ዳና ሎጅ” የኢትዮጵያን የተፈጥሮ ውበትና የባህል ብዝኃነት ቁልጭ አድርገው አሳይተዋል።
በዚህ ያላቆመው የመደመር ትውልድ "ገበታ ለትውልድ" በማለት ሌላ ምዕራፍ ከፈተ። የደንዲ ሐይቅ፣ የጢስ አባይ ፏፏቴ፣ የጅማ ዞን ቦንጋ አካባቢ እና የሶፍ ኡመር ዋሻን ጨምሮ በርካታ ድንቅ የቱሪስት መዳረሻዎች በተፈጥሮ ላይ ምንም ዓይነት አሉታዊ ተፅዕኖ በማያሳድር (eco-friendly) እና ከዓለም አቀፍ ስታንዳርድ ጋር በተናበበ አኳኋን እየተገነቡ ይገኛሉ።
እነዚህ ሁሉ የገበታ ፕሮጀክቶች ስኬታማ ሊሆኑ የቻሉበት ትልቁ ምስጢር የሥራ ባህል ለውጥ ነው። ፕሮጀክቶቹ የተመሩት "ጥራትና ፍጥነት"ን ባማከለ ጽኑ መርህ ነው። ለዘመናት ሲንከባለሉና ሲጓተቱ የነበሩ የመንግሥት ፕሮጀክቶችን ልማድ በመስበር፣ የገበታ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው በጀት፣ በተቀመጠላቸው እጅግ አጭር ጊዜ እና ዓለም አቀፍ ጥራታቸውን በጠበቀ መልኩ ተጠናቅቀዋል። ፕሮጀክቶቹ ከተፈጥሮ ጋር የፈጠሩት አስደናቂ መስተጋብር ሳይነካ የአካባቢን ሥነ-ምህዳር በጠበቀ መልኩ የተከናወኑ በመሆናቸው፣ ሀገራችንን የዓለም ጎብኚዎች ተመራጭ መዳረሻ አድርገዋታል።
የገበታ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን እውነተኛ ፀዳል የገለጡ፣ የመደመር ትውልድ ሀገሩን በዓለም አቀፍ የቱሪዝም ካርታ ላይ ቀዳሚ ለማድረግ ያለውን ብቃት፣ ፍጥነትና የፈጠራ ጥበብ ያረጋገጡ ሕያው ሐውልቶች ናቸው።
ኢትዮጵያም "ምድረ ቀደምት" መሆኗን በኩራት እያወጀች፣ የተፈጥሮና የሰው ልጅ ጥበብ የተዋሀደበትን አዲሱን ገፅታዋን ለዓለም እየገለጠች ትገኛለች።
በአጠቃላይ፣ ከስድስተኛው እስከ ሰባተኛው ምርጫ የተጓዝንባቸው የአምስቱ ዓመታት ገፆች፣ የኢትዮጵያ ውበት ከግጥምና ከዘፈን ወጥቶ መሬት የነካባቸው የክብር ዘመናት ናቸው።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #tourism #ecotourism #greentourism #sustainabletourism #ebc
**************
ታሪክ በየዘመኑ የራሱን ዐሻራ ጥሎ ያልፋል። ከስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ አንስቶ ወደ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዋዜማ ስንሸጋገር የተፃፉት የአምስቱ ዓመታት ገፆች ደግሞ፣ ኢትዮጵያ ድብቅ የተፈጥሮ ውበቷንና ፀዳሏን አውጥታ ለዓለም ያሳየችባቸው የውበት አብዮት ድርሳናት ናቸው።
ለዘመናት "የ13 ወር ፀጋ" በሚለው የቱሪዝም መሪ ቃል ብቻ ስትጠራ የነበረችው ሀገራችን፣ ዛሬ ከመፈክር ባለፈ "ምድረ ቀደምት" በሚለው ከፍታዋ ልክ በተጨባጭ በዓለም አቀፍ መድረክ ደምቃ እንድትታይ ያደረጋት አስደናቂ የታሪክ እጥፋት ተፈጥሯል። የዚህ ታላቅ ሀገራዊ ትራንስፎርሜሽን የጀርባ አጥንትና ሞተር ደግሞ ከመደመር እሳቤ የተወለዱት የ"ገበታ" ፕሮጀክቶች ናቸው።
የገበታ ፕሮጀክቶች “ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ” ተራ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች አይደሉም። ይልቁንም ሃብትን አስተባብሮ ከተፈጥሮ ፀጋዎች ጋር በማዋሀድ ኢትዮጵያን ወደ ተፈጥሯዊ የቱሪዝም መስህብነት የቀየሩና ከመደመር እሳቤ የፈለቁ እውነተኛ ኢትዮጵያዊ ትርክቶች ናቸው። የመደመር ትውልድ ሀገርን ማልማት ማለት የውጭ ዕርዳታን መጠበቅ ሳይሆን፣ የራስን እምቅ አቅም፣ የተፈጥሮ ውበትና ታሪክን ወደ ኢኮኖሚያዊ እሴት መቀየር መሆኑን በተግባር አሳይቶበታል።
ይህ የገበታ ጉዞ የተጀመረው በ"ገበታ ለሸገር" ሲሆን፣ ለዘመናት በቆሻሻ ተውጠው የነበሩ የከተማ ቦታዎችንና የተተው ተራራዎችን ወደ ምድር ገነት ቀይሯቸዋል። ጫካና ገደል የነበረው የእንጦጦ ተራራ ወደ ማራኪው "እንጦጦ ፓርክ" ሲቀየር፣ የአዲስ አበባን የልብ ትርታ ያደሰው "ወዳጅነት ፓርክ" እና ታሪክን ከተፈጥሮ ጋር ያዋሀደው ግዙፉ "አንድነት ፓርክ" የዚህ ስኬት በኩር ፍሬዎች ሆነዋል።
ይህ ስኬት በመዲናዋ ብቻ አልተገታም፤ የመደመር እሳቤ "ገበታ ለሀገር" በሚል አዲስ ሀገራዊ ንቅናቄ መላዋን ኢትዮጵያ አዳረሰ። ማራኪው የ"ወንጪ" ሐይቅ ከተፈጥሮ አቀማመጡ ጋር በተዋሀደ መልኩ በዓለም አቀፍ ስታንዳርድ ለቱሪዝም ክፍት ሆነ። የጣናን ሐይቅ ሞገድ የሚያማትረው የ"ጎርጎራ" ፕሮጀክት ታሪካዊቷን ከተማ ዳግም ሲያነቃ፣ በደቡብ ምዕራብ የሚገኘው "ኮይሻ" እና የታላቁ ሸለቆ ድንቅ ስጦታ የሆነው "ሀላላ ኬላ ሎጅ" እንዲሁም በጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ የተገነባው “ጨበራ የዝሆን ዳና ሎጅ” የኢትዮጵያን የተፈጥሮ ውበትና የባህል ብዝኃነት ቁልጭ አድርገው አሳይተዋል።
በዚህ ያላቆመው የመደመር ትውልድ "ገበታ ለትውልድ" በማለት ሌላ ምዕራፍ ከፈተ። የደንዲ ሐይቅ፣ የጢስ አባይ ፏፏቴ፣ የጅማ ዞን ቦንጋ አካባቢ እና የሶፍ ኡመር ዋሻን ጨምሮ በርካታ ድንቅ የቱሪስት መዳረሻዎች በተፈጥሮ ላይ ምንም ዓይነት አሉታዊ ተፅዕኖ በማያሳድር (eco-friendly) እና ከዓለም አቀፍ ስታንዳርድ ጋር በተናበበ አኳኋን እየተገነቡ ይገኛሉ።
እነዚህ ሁሉ የገበታ ፕሮጀክቶች ስኬታማ ሊሆኑ የቻሉበት ትልቁ ምስጢር የሥራ ባህል ለውጥ ነው። ፕሮጀክቶቹ የተመሩት "ጥራትና ፍጥነት"ን ባማከለ ጽኑ መርህ ነው። ለዘመናት ሲንከባለሉና ሲጓተቱ የነበሩ የመንግሥት ፕሮጀክቶችን ልማድ በመስበር፣ የገበታ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው በጀት፣ በተቀመጠላቸው እጅግ አጭር ጊዜ እና ዓለም አቀፍ ጥራታቸውን በጠበቀ መልኩ ተጠናቅቀዋል። ፕሮጀክቶቹ ከተፈጥሮ ጋር የፈጠሩት አስደናቂ መስተጋብር ሳይነካ የአካባቢን ሥነ-ምህዳር በጠበቀ መልኩ የተከናወኑ በመሆናቸው፣ ሀገራችንን የዓለም ጎብኚዎች ተመራጭ መዳረሻ አድርገዋታል።
የገበታ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን እውነተኛ ፀዳል የገለጡ፣ የመደመር ትውልድ ሀገሩን በዓለም አቀፍ የቱሪዝም ካርታ ላይ ቀዳሚ ለማድረግ ያለውን ብቃት፣ ፍጥነትና የፈጠራ ጥበብ ያረጋገጡ ሕያው ሐውልቶች ናቸው።
ኢትዮጵያም "ምድረ ቀደምት" መሆኗን በኩራት እያወጀች፣ የተፈጥሮና የሰው ልጅ ጥበብ የተዋሀደበትን አዲሱን ገፅታዋን ለዓለም እየገለጠች ትገኛለች።
በአጠቃላይ፣ ከስድስተኛው እስከ ሰባተኛው ምርጫ የተጓዝንባቸው የአምስቱ ዓመታት ገፆች፣ የኢትዮጵያ ውበት ከግጥምና ከዘፈን ወጥቶ መሬት የነካባቸው የክብር ዘመናት ናቸው።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #tourism #ecotourism #greentourism #sustainabletourism #ebc
2 months ago
የኢትዮጵያ ቱሪዝም፦ ከአቧራ የተነሱ ጸጋዎች፣ ለዕለት ጉርስ የሆኑ ዐሻራዎች!
**************
የዕለቱ መልዕክት
ባለፉት አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ የታየው አዲስ ተነሳሽነትና ስር ነቀል መዋቅራዊ ሽግግር፣ ሀገራችን ለዘመናት በአቧራ ተሸፍነው የቆዩ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ ጸጋዎቿን ለሕዝብ ጥቅምና ለሀገር ግንባታ የምታውልበትን አዲስ ምዕራፍ ፈጥሯል።
ይህ ለውጥ ቱሪዝምን ከተራ የኢኮኖሚ ዘርፍነት ባሻገር የብሔራዊ አንድነት፣ የሰላም፣ የብዝኃነት መገናኛና የሀገር ገጽታ ግንባታ ታላቅ መሣሪያ አድርጎታል።
ለ16 ዓመታት ሳይሻሻል የቆየውን የቱርዝም ፖሊሲ በአዲስ በመተካት ዘርፉን በሚኒስቴር ደረጃ ማደራጀት፣ የዲጂታል አሰራርንና የኢ-ቪዛ ቴክኖሎጂን መተግበር እንዲሁም የስብሰባና ኤግዚቢሽን ስትራቴጂን መቅረጽ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ አድርጓታል።
እንደ “ገበታ ለሸገር”፣ “ገበታ ለሀገር” እና “ገበታ ለትውልድ” ያሉ ታላላቅ ፅንሰ-ሀሳቦች በተግባር ተተርጉመው በአጭር ጊዜ ውስጥ አዳዲስ የመስህብ ስፍራዎችን መፍጠር ችለዋል።
በአዲስ አበባ የተከናወነው ሰፊ የኮሪደር ልማትም የሀገራችን ዋና መግቢያ በር ውበትና ምቾት በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል። ፈታኝ በሆኑ ዓለም አቀፋዊና አገራዊ ሁኔታዎች ውስጥም ቢሆን እነዚህ ስልታዊ የልማት ፕሮጀክቶች የኢኮኖሚውን ትንሳኤ የሚያፋጥኑ ትልልቅ በረከቶችን ይዘውልን መጥተዋል።
የዚህ ሁሉን አቀፍ ጥረት ውጤትም ተጨባጭ ስኬት አስገኝቷል። ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ የውጭ ቱሪስቶች ቁጥር ከ781 ሺህ ወደ 1.3 ሚሊዮን ማደጉ፣ የውጭ ምንዛሪ ገቢን ከማሳደጉም በላይ ለሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ዘላቂ የሥራ ዕድል ፈጥሯል።
እንጦጦ ፓርክ፣ ሳይንስ ሙዚየም፣ ታላቁ ብሔራዊ ቤተመንግስት፣ ደንቢና ጎሪጎራ ኢኮ ሪዞርቶች፣ የሃላላ ኬላ እና የኮይሻ ፓርክ "ከቅርሱ ወደ ቁርሱ" የሚለውን መርህ በተግባር ያሳዩ ናቸው። ኢትዮጵያ በዓለም ቱሪዝም ድርጅት ልዩ ዕውቅና ማግኘቷና በአንድ ዓመት ውስጥ ሦስት አዳዲስ ቅርሶችን በዩኔስኮ ማስመዝገቧም የዚሁ ታሪካዊ ስኬት አካል ነው።
ይሁን እንጂ የተመዘገቡት ስኬቶች የዛሬ ጥንካሬዎቻችን ማሳያ እንጂ የነገው ስልታዊ ጉዟችን ማዘናጊያ አይደሉም። ሀገራችን በቀጣይ ዓመታት የውጭ ቱሪስት ፍሰቱን እስከ 7.3 ሚሊዮን ለማድረስ የሰነቀችው ግዙፍ ብሔራዊ ራዕይ ትልቅና የተቀናጀ ሥራን ይጠይቃል።
ይህንን ታላቅ ግብ ለማሳካት የመንግሥት፣ የግል ዘርፍና የኅብረተሰቡ የተቀናጀ አጋርነት ወሳኝ ነው። የመሠረተ ልማት አውታሮችን በተለይም መንገዶችን፣ አስተማማኝ ኤሌክትሪክን፣ ንጹህ ውሃንና የቴሌኮም ኔትወርኮችን በመዳረሻዎች አካባቢ ማሻሻልና ደህንነቱ የተጠበቀ ምቹ ሁኔታን መፍጠር የቀዳሚነት ደረጃ ሊሰጠው ይገባል።
በተጨማሪም የዲጂታል ቴክኖሎጂን፣ ዘመናዊ የዳታ አያያዝንና አርቲፊሻል ኢንተለጀንስን (AI) በመጠቀም አገልግሎቶችን ማዘመን፤የጎብኚዎችን ልምድ መጠቀምና የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን መደገፍና ማበረታታት ይኖርብናል።
ቱሪዝም ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለዜጎች ኑሮ መሻሻል ያለውን የማይተካ ሚና በመገንዘብ፣ የተጀመረው አገራዊ የልማት ዐሻራ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና የሀገራችን ራዕይ እውን እንዲሆን ሁላችንም በጋራ ልንረባረብ ይገባል።
በብሔራዊ ዕድገታችንና በትውልድ ገጽታ ግንባታችን ላይ የሚጋረጡ ማናቸውንም ተግዳሮቶች የምንሻገረው በጀመርነው የልማት መስመር ላይ በጽናትና በአንድነት ስንቆም ብቻ ነው።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
**************
የዕለቱ መልዕክት
ባለፉት አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ የታየው አዲስ ተነሳሽነትና ስር ነቀል መዋቅራዊ ሽግግር፣ ሀገራችን ለዘመናት በአቧራ ተሸፍነው የቆዩ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ ጸጋዎቿን ለሕዝብ ጥቅምና ለሀገር ግንባታ የምታውልበትን አዲስ ምዕራፍ ፈጥሯል።
ይህ ለውጥ ቱሪዝምን ከተራ የኢኮኖሚ ዘርፍነት ባሻገር የብሔራዊ አንድነት፣ የሰላም፣ የብዝኃነት መገናኛና የሀገር ገጽታ ግንባታ ታላቅ መሣሪያ አድርጎታል።
ለ16 ዓመታት ሳይሻሻል የቆየውን የቱርዝም ፖሊሲ በአዲስ በመተካት ዘርፉን በሚኒስቴር ደረጃ ማደራጀት፣ የዲጂታል አሰራርንና የኢ-ቪዛ ቴክኖሎጂን መተግበር እንዲሁም የስብሰባና ኤግዚቢሽን ስትራቴጂን መቅረጽ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ አድርጓታል።
እንደ “ገበታ ለሸገር”፣ “ገበታ ለሀገር” እና “ገበታ ለትውልድ” ያሉ ታላላቅ ፅንሰ-ሀሳቦች በተግባር ተተርጉመው በአጭር ጊዜ ውስጥ አዳዲስ የመስህብ ስፍራዎችን መፍጠር ችለዋል።
በአዲስ አበባ የተከናወነው ሰፊ የኮሪደር ልማትም የሀገራችን ዋና መግቢያ በር ውበትና ምቾት በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል። ፈታኝ በሆኑ ዓለም አቀፋዊና አገራዊ ሁኔታዎች ውስጥም ቢሆን እነዚህ ስልታዊ የልማት ፕሮጀክቶች የኢኮኖሚውን ትንሳኤ የሚያፋጥኑ ትልልቅ በረከቶችን ይዘውልን መጥተዋል።
የዚህ ሁሉን አቀፍ ጥረት ውጤትም ተጨባጭ ስኬት አስገኝቷል። ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ የውጭ ቱሪስቶች ቁጥር ከ781 ሺህ ወደ 1.3 ሚሊዮን ማደጉ፣ የውጭ ምንዛሪ ገቢን ከማሳደጉም በላይ ለሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ዘላቂ የሥራ ዕድል ፈጥሯል።
እንጦጦ ፓርክ፣ ሳይንስ ሙዚየም፣ ታላቁ ብሔራዊ ቤተመንግስት፣ ደንቢና ጎሪጎራ ኢኮ ሪዞርቶች፣ የሃላላ ኬላ እና የኮይሻ ፓርክ "ከቅርሱ ወደ ቁርሱ" የሚለውን መርህ በተግባር ያሳዩ ናቸው። ኢትዮጵያ በዓለም ቱሪዝም ድርጅት ልዩ ዕውቅና ማግኘቷና በአንድ ዓመት ውስጥ ሦስት አዳዲስ ቅርሶችን በዩኔስኮ ማስመዝገቧም የዚሁ ታሪካዊ ስኬት አካል ነው።
ይሁን እንጂ የተመዘገቡት ስኬቶች የዛሬ ጥንካሬዎቻችን ማሳያ እንጂ የነገው ስልታዊ ጉዟችን ማዘናጊያ አይደሉም። ሀገራችን በቀጣይ ዓመታት የውጭ ቱሪስት ፍሰቱን እስከ 7.3 ሚሊዮን ለማድረስ የሰነቀችው ግዙፍ ብሔራዊ ራዕይ ትልቅና የተቀናጀ ሥራን ይጠይቃል።
ይህንን ታላቅ ግብ ለማሳካት የመንግሥት፣ የግል ዘርፍና የኅብረተሰቡ የተቀናጀ አጋርነት ወሳኝ ነው። የመሠረተ ልማት አውታሮችን በተለይም መንገዶችን፣ አስተማማኝ ኤሌክትሪክን፣ ንጹህ ውሃንና የቴሌኮም ኔትወርኮችን በመዳረሻዎች አካባቢ ማሻሻልና ደህንነቱ የተጠበቀ ምቹ ሁኔታን መፍጠር የቀዳሚነት ደረጃ ሊሰጠው ይገባል።
በተጨማሪም የዲጂታል ቴክኖሎጂን፣ ዘመናዊ የዳታ አያያዝንና አርቲፊሻል ኢንተለጀንስን (AI) በመጠቀም አገልግሎቶችን ማዘመን፤የጎብኚዎችን ልምድ መጠቀምና የሀገር ውስጥ ቱሪዝምን መደገፍና ማበረታታት ይኖርብናል።
ቱሪዝም ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለዜጎች ኑሮ መሻሻል ያለውን የማይተካ ሚና በመገንዘብ፣ የተጀመረው አገራዊ የልማት ዐሻራ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና የሀገራችን ራዕይ እውን እንዲሆን ሁላችንም በጋራ ልንረባረብ ይገባል።
በብሔራዊ ዕድገታችንና በትውልድ ገጽታ ግንባታችን ላይ የሚጋረጡ ማናቸውንም ተግዳሮቶች የምንሻገረው በጀመርነው የልማት መስመር ላይ በጽናትና በአንድነት ስንቆም ብቻ ነው።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
2 months ago
ነገ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን ኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅ ከጠዋቱ 4፡00 – 8፡00
👉 ፍላሚንጎ፣ ኦሎምፒያ ፣ ደንበል፣ ደንበል ጀርባ፣ ፐርፕል ካፌ ፣ ሜክሲኮ ደብረወርቅ ሕንጻ፣ ለገሐር ጀርባ ፣ ለገሐር አሸዋ ተራ ፣ ኤግዝቢሽን ሴንተር፣ ቦሌ ማተሚያ ቤት፣ ተወካዮች ምክርቤት መኖሪያ ፣ ፒኮክ መናፈሻ፣ አስቴር ቡና እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 2፡00 – 8፡30
👉 ጎፋ ኮንዶኒየም፣ ጥቃቅንና አነስተኛ፣ ጎፋ ኪደነምህረት ቤ/ክ፣ በአሚጎ ካፌ፣ መካኒሳ ቆሬ ኮንዶሚኒየም ፣ዶምቦስኮ ት/ቤት፣ሚካኤል አደባባይ፣ ከፍያለው መድሐኒት ቤት ፣ ቆሬ ኮንዶሚኒየም፣ ዩኒቲ ዩኒቨርስቲ፣ለውሃ እና አንበሳ ጋራዥ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 2፡00 – 9፡30
👉 6 ኪሎ ዩኒቨርስቲ፣ አፍንጮ በር መስጊድ፣ ደጃች ውቤ፣ ጊዮርጊስ እሳት አደጋ፣ሹፉኔ፣ ኪምቢሬ፣ ዋሰርቢ፣ 10 ኪሎ፣ እንጦጦ እና አካኮ፣ነጋ ቦንገር ዝቅ ብሎ፣ ጀሶ ፋብሪካ ፣ ብሔረፅጌ ቆዳ ፋብሪካ ፣ ፓስታና መኮረኒ፣ ቡራዩ ሪፍቲ ቫልይ ዩኒቫርሲቲ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 3፡00 – 10፡00
👉 ሰበታ ከተማ ፣ አቀበና ውሃ ማምረቻ ፣ ዲማ ሆስፒታል፣ ዋን ውሃ ፣ አባሃዋ ትሬዲንግ፣ ዋልያ ብረታ ብረት፣ ኖክ አደባባይ፣ ካፒታል ሲሚንቶ፣ ጀሞ-2 ኮንዶሚኒየም፣ የስ ውሃ ፣ዓለምገና ማርስ ብስኩት፣ ኃይሌ ጋርንት፣ ላፍቶ ኢንዱስት በከፊል፣ ናሆም አደባባይ፣ ለውሃ ሐና ቡስተር፣ ካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ፣ የሺ ሰፈር እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 2፡00 – 9፡30
👉 ሱሉልታ ከተማ በከፍል፣ ኢትዮ-ቴሌ ኮም፣ አትሌት መንደር፣ ሚዛን ሹፍኔ በከፊል፣ ጎሮ እና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ይቋረጣል።
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ የተከበራችሁ ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን እንጠይቃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
✅ ከጠዋቱ 4፡00 – 8፡00
👉 ፍላሚንጎ፣ ኦሎምፒያ ፣ ደንበል፣ ደንበል ጀርባ፣ ፐርፕል ካፌ ፣ ሜክሲኮ ደብረወርቅ ሕንጻ፣ ለገሐር ጀርባ ፣ ለገሐር አሸዋ ተራ ፣ ኤግዝቢሽን ሴንተር፣ ቦሌ ማተሚያ ቤት፣ ተወካዮች ምክርቤት መኖሪያ ፣ ፒኮክ መናፈሻ፣ አስቴር ቡና እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 2፡00 – 8፡30
👉 ጎፋ ኮንዶኒየም፣ ጥቃቅንና አነስተኛ፣ ጎፋ ኪደነምህረት ቤ/ክ፣ በአሚጎ ካፌ፣ መካኒሳ ቆሬ ኮንዶሚኒየም ፣ዶምቦስኮ ት/ቤት፣ሚካኤል አደባባይ፣ ከፍያለው መድሐኒት ቤት ፣ ቆሬ ኮንዶሚኒየም፣ ዩኒቲ ዩኒቨርስቲ፣ለውሃ እና አንበሳ ጋራዥ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 2፡00 – 9፡30
👉 6 ኪሎ ዩኒቨርስቲ፣ አፍንጮ በር መስጊድ፣ ደጃች ውቤ፣ ጊዮርጊስ እሳት አደጋ፣ሹፉኔ፣ ኪምቢሬ፣ ዋሰርቢ፣ 10 ኪሎ፣ እንጦጦ እና አካኮ፣ነጋ ቦንገር ዝቅ ብሎ፣ ጀሶ ፋብሪካ ፣ ብሔረፅጌ ቆዳ ፋብሪካ ፣ ፓስታና መኮረኒ፣ ቡራዩ ሪፍቲ ቫልይ ዩኒቫርሲቲ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 3፡00 – 10፡00
👉 ሰበታ ከተማ ፣ አቀበና ውሃ ማምረቻ ፣ ዲማ ሆስፒታል፣ ዋን ውሃ ፣ አባሃዋ ትሬዲንግ፣ ዋልያ ብረታ ብረት፣ ኖክ አደባባይ፣ ካፒታል ሲሚንቶ፣ ጀሞ-2 ኮንዶሚኒየም፣ የስ ውሃ ፣ዓለምገና ማርስ ብስኩት፣ ኃይሌ ጋርንት፣ ላፍቶ ኢንዱስት በከፊል፣ ናሆም አደባባይ፣ ለውሃ ሐና ቡስተር፣ ካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ፣ የሺ ሰፈር እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 2፡00 – 9፡30
👉 ሱሉልታ ከተማ በከፍል፣ ኢትዮ-ቴሌ ኮም፣ አትሌት መንደር፣ ሚዛን ሹፍኔ በከፊል፣ ጎሮ እና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ይቋረጣል።
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ የተከበራችሁ ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን እንጠይቃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ከእንጦጦ ማማ እስከ ሽሮሜዳ እና ቀጨኔ፤ የአዲስ አበባ ወንዞች አዲስ ገጽታ #ethiopianbrodcastingcorporethion #greencorridor #የወንዞች_ልማት #አረንጓዴ_ኮሪደር #አዲስ_አበባ #ተችሏል
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
2 months ago
በተግባር የተገለጠው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል - አዲስ አበባን የማዘመን ጉዞ ስኬት
**********************
ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "የዛሬ አምስት ዓመት አዲስ አበባ በአፍሪካ ውስጥ እጅግ ውብ ከሚባሉ ከተሞች አንዷ ትሆናለች" ሲሉ ተናግረው ነበር።
ያኔ ንግግራቸውን ከሰሙት መካከል የመዲናዋን የዛሬ ገጽታ በዐይነ ኅሊናቸው የሣሉት ጥቂቶች ነበሩ።
በወቅቱ ንግግሩ ከተራ የፖለቲካ ተስፋ በላይ ትርጉም አይኖረውም ብለው የተጠራጠሩ ቢኖሩም፣ ዛሬ ግን አዲስ አበባ በአጭር ጊዜ ውስጥ እጅግ ማራኪ፣ ጽዱ እና ዘመናዊ ዲፕሎማሲያዊ ማዕከል በመሆን ራዕዩን በተግባር አሳይታለች።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመዲናዋ ተበታትነው የሚገኙትን እምቅ አቅሞች ወይም "ያልተያያዙ ትላልቅ ዶቶችን" በማገናኘት ከተማዋን በአዲስ መልክ የመገንባት ዕቅድ እንዳላቸው አስረድተውም ነበር።
ይህ አርቆ አሳቢ የከተማ ልማት ፍልስፍና ታሪካዊ ክስተቶችን የሚያስታውስ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳስታወሱት፣ ንጉሥ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን መገንባት በጀመሩበት ወቅት "ድንጋይ መቆርቆር የስንፍና ምልክት ነው" በማለት ያሾፉባቸው ነበሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፈጣሪዎች እና አልሚዎች ሁልጊዜም በዘመናቸው ካሉ "አውርቶ አደር" ተቺዎች ጋር መጋፈጣቸው አይቀርም የሚል እሳቤ አላቸው።
ዛሬ በኮሪደር ልማቱ እየታየ ያለውም ይኸው እውነታ ነው፤ "እኛ የምንሠራው ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለነገ እና ለቀጣዩ ትውልድ ነው፤ ነገ የሚፈርስ ዳስ አንሠራም" በሚለው መርሐቸው ለትውልድ የሚሻገር ዘላቂ ሥራ እየተሠራ ይገኛል።
"የመደመር መንግሥት" መጽሐፍ ላይ እንደተብራራው፣ ከተሜነት የብልጽግና መዳረሻ እና የኢኮኖሚ ሞተር ነው።
ከተማን ማዘመን ረጃጅም ሕንፃዎችን ከመገንባት ባለፈ ሰፊ የእግረኛ እና የሳይክል መንገዶችን፣ አረንጓዴ ስፍራዎችን እና ምቹ መሠረተ ልማቶችን ማካተትን ይጠይቃል።
አዲስ አበባ ላይ በተግባር ሥራ ላይ ውሎ አዲስ አበባን ምርጥ የአፍሪካ ከተማ ያደረገው ይኸው ሰዎችን ማዕከል ያደረገው ፍልስፍና ነው።
ከዚህ ቀደም የተገነቡት አንድነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ ወዳጅነት አደባባይ እና የዓድዋ ድል መታሰቢያ የዚህ ዘመናዊ አስተሳሰብ ማሳያዎች ናቸው።
በዚህም የኮሪደር ልማቱ በግንባታው ሂደት ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም በላይ፣ የካርቦን ልቀትን በመቀነስ የነዋሪዎችን ጤና እና ደኅንነት የሚጠብቅ ንፁህ አካባቢን መፍጠር ችሏል።
እነዚህ ስልታዊ ለውጦች አዲስ አበባን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለበርካታ ሽልማቶች አብቅተዋታል።
በ2015 ዓ.ም በናይሮቢ በተካሄደው የአፍሪካ ስማርት ሲቲዎች ኢንቨስትመንት ጉባኤ ላይ 36 የአፍሪካ ከተሞችን በመብለጥ ‘የዓመቱ ምርጥ ስማርት ሲቲ' ሽልማትን አሸንፋለች።
እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ አዳራሽ (Historic Africa Hall) እድሳት ፕሮጀክት የሞደርኒዝም ጥበቃ ሽልማትን (World Monuments Fund/Knoll Modernism Prize) ተቀዳጅቷል።
ይህ ሽልማት ከተመሠረተበት እ.ኤ.አ. 2008 ጀምሮ በአፍሪካ አህጉር ሲሰጥ አዲስ አበባ የመጀመሪያዋ ነች።
እነዚህ ስኬቶች ከተማዋ እ.አ.አ በ2027 የዓለም አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (COP32) እንድታስተናግድ ትልቅ መተማመኛ ፈጥረዋል።
በአዲስ አበባ የተመዘገበው ይህ ስኬታማ የከተማ ማዘመን ልምድ በአሁኑ ወቅት ከ70 በላይ ወደሚሆኑ የሀገራችን ከተሞችም እንዲስፋፋ ተደርጓል።
ይህ አዲስ የከተማ ማሻሻያ ፍልስፍና በቱሪዝም ዘርፉ ላይም ታይቶ የማይታወቅ መነቃቃት ፈጥሯል።
በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ዘጠኝ ወራት ብቻ ከ1.5 ሚሊዮን በላይ ከሚሆኑ የውጭ ቱሪስቶች ከ2.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል።
በተባበሩት መንግሥታት የቱሪዝም ድርጅት (UN Tourism) መረጃ መሰረትም ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2025 የዓለም አቀፍ ቱሪስቶችን ፍሰት በ15 በመቶ በማሳደግ ፈጣን ዕድገት እያስመዘገቡ ካሉ የቱሪዝም መዳረሻዎች ተርታ ተሰልፋለች።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ይህን ግዙፍ ልማት ሲያከናውን ያጋጠሙትን ማኅበራዊ እና ሕጋዊ ተግዳሮቶች ሰብአዊነትን በተላበሰ መንገድ ለመፍታት ያደረገው ጥረት የልማቱን ፍትሐዊነት ያረጋግጣል።
ከተማዋን ለሕፃናት፣ ለወጣቶች እና ለአካል ጉዳተኞች ጭምር ምቹ በማድረግ የቦታ ፍትሐዊነትን ማረጋገጥ ተችሏል።
ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም የተነገረው ራዕይ ዛሬ እውን ሆኖ፣ አዲስ አበባ በምድረ አፍሪካ ውብ፣ ተመራጭ እና የሁሉንም ነዋሪዎቿን ፍላጎት ያማከለች መዲና መሆኗን በተግባር እያረጋገጠች ትገኛለች።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #addisababa #corridordevelopment #smartcity
**********************
ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "የዛሬ አምስት ዓመት አዲስ አበባ በአፍሪካ ውስጥ እጅግ ውብ ከሚባሉ ከተሞች አንዷ ትሆናለች" ሲሉ ተናግረው ነበር።
ያኔ ንግግራቸውን ከሰሙት መካከል የመዲናዋን የዛሬ ገጽታ በዐይነ ኅሊናቸው የሣሉት ጥቂቶች ነበሩ።
በወቅቱ ንግግሩ ከተራ የፖለቲካ ተስፋ በላይ ትርጉም አይኖረውም ብለው የተጠራጠሩ ቢኖሩም፣ ዛሬ ግን አዲስ አበባ በአጭር ጊዜ ውስጥ እጅግ ማራኪ፣ ጽዱ እና ዘመናዊ ዲፕሎማሲያዊ ማዕከል በመሆን ራዕዩን በተግባር አሳይታለች።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመዲናዋ ተበታትነው የሚገኙትን እምቅ አቅሞች ወይም "ያልተያያዙ ትላልቅ ዶቶችን" በማገናኘት ከተማዋን በአዲስ መልክ የመገንባት ዕቅድ እንዳላቸው አስረድተውም ነበር።
ይህ አርቆ አሳቢ የከተማ ልማት ፍልስፍና ታሪካዊ ክስተቶችን የሚያስታውስ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳስታወሱት፣ ንጉሥ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን መገንባት በጀመሩበት ወቅት "ድንጋይ መቆርቆር የስንፍና ምልክት ነው" በማለት ያሾፉባቸው ነበሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፈጣሪዎች እና አልሚዎች ሁልጊዜም በዘመናቸው ካሉ "አውርቶ አደር" ተቺዎች ጋር መጋፈጣቸው አይቀርም የሚል እሳቤ አላቸው።
ዛሬ በኮሪደር ልማቱ እየታየ ያለውም ይኸው እውነታ ነው፤ "እኛ የምንሠራው ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለነገ እና ለቀጣዩ ትውልድ ነው፤ ነገ የሚፈርስ ዳስ አንሠራም" በሚለው መርሐቸው ለትውልድ የሚሻገር ዘላቂ ሥራ እየተሠራ ይገኛል።
"የመደመር መንግሥት" መጽሐፍ ላይ እንደተብራራው፣ ከተሜነት የብልጽግና መዳረሻ እና የኢኮኖሚ ሞተር ነው።
ከተማን ማዘመን ረጃጅም ሕንፃዎችን ከመገንባት ባለፈ ሰፊ የእግረኛ እና የሳይክል መንገዶችን፣ አረንጓዴ ስፍራዎችን እና ምቹ መሠረተ ልማቶችን ማካተትን ይጠይቃል።
አዲስ አበባ ላይ በተግባር ሥራ ላይ ውሎ አዲስ አበባን ምርጥ የአፍሪካ ከተማ ያደረገው ይኸው ሰዎችን ማዕከል ያደረገው ፍልስፍና ነው።
ከዚህ ቀደም የተገነቡት አንድነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ ወዳጅነት አደባባይ እና የዓድዋ ድል መታሰቢያ የዚህ ዘመናዊ አስተሳሰብ ማሳያዎች ናቸው።
በዚህም የኮሪደር ልማቱ በግንባታው ሂደት ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም በላይ፣ የካርቦን ልቀትን በመቀነስ የነዋሪዎችን ጤና እና ደኅንነት የሚጠብቅ ንፁህ አካባቢን መፍጠር ችሏል።
እነዚህ ስልታዊ ለውጦች አዲስ አበባን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለበርካታ ሽልማቶች አብቅተዋታል።
በ2015 ዓ.ም በናይሮቢ በተካሄደው የአፍሪካ ስማርት ሲቲዎች ኢንቨስትመንት ጉባኤ ላይ 36 የአፍሪካ ከተሞችን በመብለጥ ‘የዓመቱ ምርጥ ስማርት ሲቲ' ሽልማትን አሸንፋለች።
እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ አዳራሽ (Historic Africa Hall) እድሳት ፕሮጀክት የሞደርኒዝም ጥበቃ ሽልማትን (World Monuments Fund/Knoll Modernism Prize) ተቀዳጅቷል።
ይህ ሽልማት ከተመሠረተበት እ.ኤ.አ. 2008 ጀምሮ በአፍሪካ አህጉር ሲሰጥ አዲስ አበባ የመጀመሪያዋ ነች።
እነዚህ ስኬቶች ከተማዋ እ.አ.አ በ2027 የዓለም አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (COP32) እንድታስተናግድ ትልቅ መተማመኛ ፈጥረዋል።
በአዲስ አበባ የተመዘገበው ይህ ስኬታማ የከተማ ማዘመን ልምድ በአሁኑ ወቅት ከ70 በላይ ወደሚሆኑ የሀገራችን ከተሞችም እንዲስፋፋ ተደርጓል።
ይህ አዲስ የከተማ ማሻሻያ ፍልስፍና በቱሪዝም ዘርፉ ላይም ታይቶ የማይታወቅ መነቃቃት ፈጥሯል።
በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ዘጠኝ ወራት ብቻ ከ1.5 ሚሊዮን በላይ ከሚሆኑ የውጭ ቱሪስቶች ከ2.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል።
በተባበሩት መንግሥታት የቱሪዝም ድርጅት (UN Tourism) መረጃ መሰረትም ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2025 የዓለም አቀፍ ቱሪስቶችን ፍሰት በ15 በመቶ በማሳደግ ፈጣን ዕድገት እያስመዘገቡ ካሉ የቱሪዝም መዳረሻዎች ተርታ ተሰልፋለች።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ይህን ግዙፍ ልማት ሲያከናውን ያጋጠሙትን ማኅበራዊ እና ሕጋዊ ተግዳሮቶች ሰብአዊነትን በተላበሰ መንገድ ለመፍታት ያደረገው ጥረት የልማቱን ፍትሐዊነት ያረጋግጣል።
ከተማዋን ለሕፃናት፣ ለወጣቶች እና ለአካል ጉዳተኞች ጭምር ምቹ በማድረግ የቦታ ፍትሐዊነትን ማረጋገጥ ተችሏል።
ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም የተነገረው ራዕይ ዛሬ እውን ሆኖ፣ አዲስ አበባ በምድረ አፍሪካ ውብ፣ ተመራጭ እና የሁሉንም ነዋሪዎቿን ፍላጎት ያማከለች መዲና መሆኗን በተግባር እያረጋገጠች ትገኛለች።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #addisababa #corridordevelopment #smartcity
2 months ago
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት
የአዲስ አበባ የወንዞች ዳርቻ ልማት፤ የወንዝ ዳርቻዎችን ከማስዋብ ያለፈ ፋይዳን የያዘ ፕሮጀክት ነው!
ከእንጦጦ እስከ ፒኮክ፣ እንዲሁም ከእንጦጦ እስከ ቀበና ባለው መስመር የሚከናወነው መጠነ ሰፊ የከተማ ትራንስፎርሜሽን፤ ከወንዞቹ ባሻገር እስከ 50 ሜትር የሚዘልቅ ሲሆን፤ የአረንጓዴ ኮሪደሮችን፣ የሕዝብ መሰብሰቢያ ቦታዎችን፣ የእግረኛ መንገዶችን፣ የመዝናኛ ስፍራዎችን እና የንግድ ቦታዎችን ልማት ያካተተ ሲሆን ከተማዋንም በእጅጉ የቀየረ ነው።
የፕሮጀክቱን አስፈላጊነት ልዩ የሚያደርገው ከፍ ያለ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ፋይዳው ነው። የወንዝ ዳርቻዎችን ገጽታ እና አገልግሎት ከማሻሻል ባለፈ በኮንስትራክሽን፣ በኢንጂነሪንግ፣ በመልክዓ-ምድር ውበት ግንባታ፣ በሎጂስቲክስ እና በተያያዙ ዘርፎች ለብዙ ሰዎች የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፤ ለሀገር በቀል ተቋራጮች፣ አቅራቢዎችና ንግዶችም ዕድሎችን አመቻችቷል። አብዛኛው ሥራ በሀገር ውስጥ መሐንዲሶች መቀረጹና መተግበሩ፤ የኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች በከተማ ልማት እና በመሠረተ ልማት ግንባታ ላይ ያላቸው አቅም እያደገ መምጣቱን ያሳያል።
የልማቱ ዘላቂነትም እኩል ትኩረት የሚሰጠው ነው። ቀደም ሲል መርዛማ ኬሚካሎች እና ቆሻሻዎች የሚጣሉባቸው፣ በወንዝ ዳርቻዎች በሚኖሩ ማኅበረሰቦች ላይ የጎርፍ አደጋ ይጋርጡ የነበሩት እነዚህ አካባቢዎች፣ አሁን ላይ ወደ አረንጓዴ፣ ጤናማ እና ለሕይወት ምቹ ወደሆነ የከተማ ቦታነት እየተቀየሩ ይገኛል። በተመሳሳይ ሁኔታም፤ የንግድ እና የሕዝብ መዝናኛ ቦታዎች ተቀናጅተው መገንባታቸው፤ የአካባቢ ጥበቃ እና የኢኮኖሚ ዕድገት ከዚህ ቀደም ከነበረው ያልተናበበ ስራ ተላቀው በጥናትና በጋራ ግብ ተባብሮ መስራት እንደሚችሉ ማረጋገጫ ነው።
ይህ ፈጣን የልማት ስራ አዲስ አበባን አረንጓዴ፣ ይበልጥ የተሳሰረች፣ በኢኮኖሚ ንቁ እና ሰውን ማዕከል ያደረገች ከተማ የማድረግ የወደፊት ዕጣ ፈንታዋ ላይ መሰረት የተጣለበት የረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንት ነው!
Comments