1 month ago
ልክ እንደ ሕዳሴ ግድብ ሁሉ ሀገርን ከስር መሠረቱ የሚቀይሩት አዳዲስ ታላላቅ የልማት ምዕራፎች የጉባ ብሥራቶች ኢትዮጵያን ወደ የትኛው ከፍታ ያሽጋግራታል? ታላቁ የሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ የልማት ጉዟችን ማብቂያ ሳይሆን ይልቁንም የኢትዮጵያ አዲስ ታሪክ መጀመሪያ መሆኑን በተግባር እያሳየ ይገኛል። #ebcdotstream #gerdcompletion #renaissancedam #sovereigntyinaction #megaprojects
2 months ago
ከተግባር ከፍታ ወደ ብሔራዊ ጽናት - የኢትዮጵያ የሜጋ ፕሮጀክቶች የስኬት ዐሻራ
****************
(የዕለቱ መልእክት)
ኢትዮጵያ ታሪክን በንግግር እና በምኞት ሳይሆን፣ በተግባር እና በግዙፍ ፕሮጀክቶች የምትቀይርበት ልዩ የዕድገት ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
“አፍ ተናግሮ እግር ሲያፍር፣ ልብ አዝኖ ዐይን ሲያለቅስ” እንደሚሉት ሳይሆን፣ ዛሬ በሀገራችን እየታየ ያለው የቃል እና የተግባር መገጣጠም ነው።
“ከነገሩ ጽናቱ” እንዲሉ በተግባር ከፍታ የተመሰከረላቸው ግዙፍ የልማት አውታሮች የብሔራዊ ጽናታችን ማማ ሆነው በግልጽ እየታዩ ነው።
ለዚህም በቢሾፍቱ እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ በኢንቨስትመንት መጠኑ እና በሥራው ግዝፈት በአፍሪካ ታሪክ ብቸኛው ፕሮጀክት መሆኑ ቀዳሚ ማሳያ ነው።
“አውቆ የተነገረ ከልብ ይደርሳል” እንደሚባለው በአዲስ አበባ ከተማ ታቅደው በአጭር ጊዜ የተጠናቀቁት እንደ ወዳጅነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ የወንዝ ዳር ልማቶች፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የዓድዋ ድል መታሰቢያ ያሉ ታላላቅ ፕሮጀክቶች መሬት ላይ የወረዱ እውነታዎች እንጂ የሩቅ ሕልሞች አይደሉም።
ከዚህም ባሻገር ሌሊት እና ቀን የተሠራው እና እየተሠራ ያለው የኮሪደር ልማት የመንግሥትን የፕሮጀክት ፈጻሚነት አቅም ቁልጭ አድርጎ ያመላከተ ሲሆን፣ ይህ ስኬት መንግሥት ላለፉት ዓታት በትኩረት ሲተገብራቸው የቆያቸው የልማት አፈጻጸሞች ቀጣይ ማሳያ ነው።
ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ መዘግየቶችን በመስበር እንደ ስኳር ፕሮጀክቶች ያሉ ግዙፍ ተቋማትን ማጠናቀቅ መቻሉ የመንግሥት ቁርጠኝነት በተግባር የታየበት ነው። ከሁሉም በላይ ደግሞ የኢትዮጵያውያን ዳግማዊ ዓድዋ የሆነው የታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ እና በቅርቡ የተበሰሩት የጉባ ብሥራቶች፣ ሀገራችን የማይቻሉ የሚመስሉ ታላላቅ ሕልሞችን የመፈጸም አቅም እንዳላት ለዓለም የመሰከሩበት ታሪካዊ ምዕራፍ ናቸው።
በአፈጻጸም ሂደት ላይ የሚያጋጥሙ ማነቆዎችን መንግሥት በግልጽ ለሕዝብ የሚያሳውቅ ከሆነ፣ ሕዝቡ ውሳኔዎችን የመረዳት እና የመቀበል ዝንባሌው ይጨምራል። “እውነት እና ንጋት እያደር ይጠራል” እንዲሉ ግልጽነት መተማመንን ይፈጥራል።
በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ (እንደ ወንጪ፣ ኮይሻ፣ ጎርጎራ) ፕሮጀክቶች ላይ ከሕዝብ የተሰበሰበው ሀብት እንዴት ወደ ተጨባጭ ልማት እንደተለወጠ ደረጃ በደረጃ ለሕዝቡ ይፋ መሆኑ ግልጽነትን አጠናክሯል። የመደመር እሳቤም ዋና ምሰሶ ይኸው ነው - ሀገርን በጋራ መገንባት።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቢሾፍቱ እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግዝፈት እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም አስመልክተው ሲናገሩ፤ "ይህንን ያህል ማሽን የሚንቀሳቀስበት ሥራ እንደ ሀገር መርተን አናውቅም፤ የመጀመሪያችን ነው። ሥርዓት ቢኖረን፣ በየቀኑ ሥራዎቻችንን ማየት ብንችል፣ አብዛኛው ፕሮጀክት በተጀመረለት ጊዜ እና ጥራት አልቆ የሕዝብን እርካታ ሊያረጋግጥ ይችላል" ብለዋል።
ይህ ተከታታይነት እና ወጥነት ያለው የፕሮጀክቶች አፈጻጸም በቁስ አካል ደረጃ ከሚታዩ ውጤቶች ባሻገር፣ በሀገራችን የአስተዳደር ሥነ ልቦና ላይ ታላቅ የባህል ለውጥ ፈጥሯል። የዘገምተኛነት እና የቢሮክራሲ ሰንሰለትን ሙሉ በሙሉ በመበጠስ፣ አሁን ላይ ሌሊት እና ቀን ሳይለዩ የማያቋርጥ ሥራ የመሥራት፣ የቀጠሮ ትክክለኛነት እና ፈጣን ውሳኔ የመስጠት አዲስ ሀገራዊ የፈጠነ ሥራ ባህል ተተክሏል።
የሜጋ ፕሮጀክቶች መሳካት ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸው በላይ የኅብረተሰቡን ሥነ ልቦና የማነጽ እና የጋራ ማንነትን የማንቃት ታላቅ አቅም አላቸው። ለረጅም ዘመናት በአንዳንዶች ዘንድ ይንጸባረቅ የነበረውን የተሸናፊነት እና የዝቅተኝነት ሥነ ልቦና ሙሉ በሙሉ በመስበር፣ “እኛም እንችላለን” የሚል የጽኑ እምነት እና የሀገራዊ ኩራት ስሜት በትውልዱ ልብ ውስጥ እንዲቀረጽ አድርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሥራው ላይ ለሚታዩት ተግዳሮቶች እና የጥርጣሬ ሐሳቦች በሰጡት ምላሽ፤ "ብዙዎች ‘አትችሉም፣ ገንዘቡም አይገኝም፣ ሥራውን መምራት አይሆንላችሁም’ የሚል እሳቤ ሲያራግቡ ይሰማል። እኛ ደግሞ ‘እንችላለን፤ ይገባናል፤ የሚመጥነን ትልቅ ነገር ነው’ እያልን ነው። ማን እንደሚያሸንፍ ጊዜው ሲደርስ እናያለን" በማለት የሀገራችንን ጽኑ አቋም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያውያን በራሳቸው ተነሣሽነት እና ብርታት በተደጋጋሚ ታሪክ እየሠሩ መሆናቸውን በተግባር አሳይተዋል።
በመሆኑም መላው ሕዝብ በተባበረ ክንድ ድህነትን ለመስበር፣ የጠለሸ ማንነትን ለመቀየር እና የበለጸገች ሀገር ለትውልድ ለማውረስ “ሳይደክሙ አይታለፍም የኑሮ አቀበት” እንዲሉ በሥራ እና በልፋት ብቻ መረባረብ ይኖርበታል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ebc #ethiopia #megaprojects #pmabiyahmed
****************
(የዕለቱ መልእክት)
ኢትዮጵያ ታሪክን በንግግር እና በምኞት ሳይሆን፣ በተግባር እና በግዙፍ ፕሮጀክቶች የምትቀይርበት ልዩ የዕድገት ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
“አፍ ተናግሮ እግር ሲያፍር፣ ልብ አዝኖ ዐይን ሲያለቅስ” እንደሚሉት ሳይሆን፣ ዛሬ በሀገራችን እየታየ ያለው የቃል እና የተግባር መገጣጠም ነው።
“ከነገሩ ጽናቱ” እንዲሉ በተግባር ከፍታ የተመሰከረላቸው ግዙፍ የልማት አውታሮች የብሔራዊ ጽናታችን ማማ ሆነው በግልጽ እየታዩ ነው።
ለዚህም በቢሾፍቱ እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ በኢንቨስትመንት መጠኑ እና በሥራው ግዝፈት በአፍሪካ ታሪክ ብቸኛው ፕሮጀክት መሆኑ ቀዳሚ ማሳያ ነው።
“አውቆ የተነገረ ከልብ ይደርሳል” እንደሚባለው በአዲስ አበባ ከተማ ታቅደው በአጭር ጊዜ የተጠናቀቁት እንደ ወዳጅነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ የወንዝ ዳር ልማቶች፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የዓድዋ ድል መታሰቢያ ያሉ ታላላቅ ፕሮጀክቶች መሬት ላይ የወረዱ እውነታዎች እንጂ የሩቅ ሕልሞች አይደሉም።
ከዚህም ባሻገር ሌሊት እና ቀን የተሠራው እና እየተሠራ ያለው የኮሪደር ልማት የመንግሥትን የፕሮጀክት ፈጻሚነት አቅም ቁልጭ አድርጎ ያመላከተ ሲሆን፣ ይህ ስኬት መንግሥት ላለፉት ዓታት በትኩረት ሲተገብራቸው የቆያቸው የልማት አፈጻጸሞች ቀጣይ ማሳያ ነው።
ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ መዘግየቶችን በመስበር እንደ ስኳር ፕሮጀክቶች ያሉ ግዙፍ ተቋማትን ማጠናቀቅ መቻሉ የመንግሥት ቁርጠኝነት በተግባር የታየበት ነው። ከሁሉም በላይ ደግሞ የኢትዮጵያውያን ዳግማዊ ዓድዋ የሆነው የታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ እና በቅርቡ የተበሰሩት የጉባ ብሥራቶች፣ ሀገራችን የማይቻሉ የሚመስሉ ታላላቅ ሕልሞችን የመፈጸም አቅም እንዳላት ለዓለም የመሰከሩበት ታሪካዊ ምዕራፍ ናቸው።
በአፈጻጸም ሂደት ላይ የሚያጋጥሙ ማነቆዎችን መንግሥት በግልጽ ለሕዝብ የሚያሳውቅ ከሆነ፣ ሕዝቡ ውሳኔዎችን የመረዳት እና የመቀበል ዝንባሌው ይጨምራል። “እውነት እና ንጋት እያደር ይጠራል” እንዲሉ ግልጽነት መተማመንን ይፈጥራል።
በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ (እንደ ወንጪ፣ ኮይሻ፣ ጎርጎራ) ፕሮጀክቶች ላይ ከሕዝብ የተሰበሰበው ሀብት እንዴት ወደ ተጨባጭ ልማት እንደተለወጠ ደረጃ በደረጃ ለሕዝቡ ይፋ መሆኑ ግልጽነትን አጠናክሯል። የመደመር እሳቤም ዋና ምሰሶ ይኸው ነው - ሀገርን በጋራ መገንባት።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቢሾፍቱ እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግዝፈት እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም አስመልክተው ሲናገሩ፤ "ይህንን ያህል ማሽን የሚንቀሳቀስበት ሥራ እንደ ሀገር መርተን አናውቅም፤ የመጀመሪያችን ነው። ሥርዓት ቢኖረን፣ በየቀኑ ሥራዎቻችንን ማየት ብንችል፣ አብዛኛው ፕሮጀክት በተጀመረለት ጊዜ እና ጥራት አልቆ የሕዝብን እርካታ ሊያረጋግጥ ይችላል" ብለዋል።
ይህ ተከታታይነት እና ወጥነት ያለው የፕሮጀክቶች አፈጻጸም በቁስ አካል ደረጃ ከሚታዩ ውጤቶች ባሻገር፣ በሀገራችን የአስተዳደር ሥነ ልቦና ላይ ታላቅ የባህል ለውጥ ፈጥሯል። የዘገምተኛነት እና የቢሮክራሲ ሰንሰለትን ሙሉ በሙሉ በመበጠስ፣ አሁን ላይ ሌሊት እና ቀን ሳይለዩ የማያቋርጥ ሥራ የመሥራት፣ የቀጠሮ ትክክለኛነት እና ፈጣን ውሳኔ የመስጠት አዲስ ሀገራዊ የፈጠነ ሥራ ባህል ተተክሏል።
የሜጋ ፕሮጀክቶች መሳካት ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸው በላይ የኅብረተሰቡን ሥነ ልቦና የማነጽ እና የጋራ ማንነትን የማንቃት ታላቅ አቅም አላቸው። ለረጅም ዘመናት በአንዳንዶች ዘንድ ይንጸባረቅ የነበረውን የተሸናፊነት እና የዝቅተኝነት ሥነ ልቦና ሙሉ በሙሉ በመስበር፣ “እኛም እንችላለን” የሚል የጽኑ እምነት እና የሀገራዊ ኩራት ስሜት በትውልዱ ልብ ውስጥ እንዲቀረጽ አድርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሥራው ላይ ለሚታዩት ተግዳሮቶች እና የጥርጣሬ ሐሳቦች በሰጡት ምላሽ፤ "ብዙዎች ‘አትችሉም፣ ገንዘቡም አይገኝም፣ ሥራውን መምራት አይሆንላችሁም’ የሚል እሳቤ ሲያራግቡ ይሰማል። እኛ ደግሞ ‘እንችላለን፤ ይገባናል፤ የሚመጥነን ትልቅ ነገር ነው’ እያልን ነው። ማን እንደሚያሸንፍ ጊዜው ሲደርስ እናያለን" በማለት የሀገራችንን ጽኑ አቋም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያውያን በራሳቸው ተነሣሽነት እና ብርታት በተደጋጋሚ ታሪክ እየሠሩ መሆናቸውን በተግባር አሳይተዋል።
በመሆኑም መላው ሕዝብ በተባበረ ክንድ ድህነትን ለመስበር፣ የጠለሸ ማንነትን ለመቀየር እና የበለጸገች ሀገር ለትውልድ ለማውረስ “ሳይደክሙ አይታለፍም የኑሮ አቀበት” እንዲሉ በሥራ እና በልፋት ብቻ መረባረብ ይኖርበታል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ebc #ethiopia #megaprojects #pmabiyahmed
Comments