15 days ago
ታዋቂዋ ማራቶን አትሌት ፋጡማ ሮባ እና ጋዜጠኛ ካሳሁን ፈይሳ ከዓመታት በኋላ በደስታ ተገናኙ
#ethiopia | የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ካስጠሩ ስመ ጥር የስፖርት ባልባለቶች መካከል አንዷ የሆነችው አትሌት ፋጡማ ሮባ እና ጋዜጠኛ ካሳሁን ፈይሳ ከረጅም ዓመታት በኋላ በድጋሚ ተገናኝተዋል።
አትሌት ፋጡማ ሮባ በታሪካዊው የአትላንታ ኦሎምፒክ በሴቶች ማራቶን ውድድር ለኢትዮጵያ ከአርባ ዓመታት በኋላ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኘች ታላቅ ባለውለታ ናት።
በወቅቱ ይህንን ታላቅ ድል ተቀዳጅታ ወደ ሀገሯ ስትመለስ በነበረው ከፍተኛ የደስታ ድባብ ውስጥ ጋዜጠኛ ካሳሁን ፈይሳ ለኢትዮጵያ ሬድዮ ፕሮግራም የሚሆን አጭር ቃለ መጠይቅ አድርጎላት እንደነበር ይታወሳል።
ያኔ በወጣትነት ዘመናቸው በስራ አጋጣሚ ተገናኝተው የተነሱትን የማይረሳ ትዝታ የያዘ ፎቶግራፍ በማስታወስ፣ ከአያሌ ዓመታት በኋላ አሁን ላይ በድጋሚ በመገናኘታቸው ለተባረከው ዕድሜና ለአምላክ ምስጋና በማቅረብ ለታዋቂዋ አትሌት መልካም ጤንነትና ረጅም ዕድሜ ተመኝቷል።
ጋዜጠኛ ካሳሁን ፈይሳ በኦንታሪዮ፣ ቶሮንቶ ካናዳ 🇨🇦 ነዋሪ ነው።
#sport #marathon #atlanta1996 #olympics #athletics #history #legend #ethiopianathletes #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ካስጠሩ ስመ ጥር የስፖርት ባልባለቶች መካከል አንዷ የሆነችው አትሌት ፋጡማ ሮባ እና ጋዜጠኛ ካሳሁን ፈይሳ ከረጅም ዓመታት በኋላ በድጋሚ ተገናኝተዋል።
አትሌት ፋጡማ ሮባ በታሪካዊው የአትላንታ ኦሎምፒክ በሴቶች ማራቶን ውድድር ለኢትዮጵያ ከአርባ ዓመታት በኋላ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኘች ታላቅ ባለውለታ ናት።
በወቅቱ ይህንን ታላቅ ድል ተቀዳጅታ ወደ ሀገሯ ስትመለስ በነበረው ከፍተኛ የደስታ ድባብ ውስጥ ጋዜጠኛ ካሳሁን ፈይሳ ለኢትዮጵያ ሬድዮ ፕሮግራም የሚሆን አጭር ቃለ መጠይቅ አድርጎላት እንደነበር ይታወሳል።
ያኔ በወጣትነት ዘመናቸው በስራ አጋጣሚ ተገናኝተው የተነሱትን የማይረሳ ትዝታ የያዘ ፎቶግራፍ በማስታወስ፣ ከአያሌ ዓመታት በኋላ አሁን ላይ በድጋሚ በመገናኘታቸው ለተባረከው ዕድሜና ለአምላክ ምስጋና በማቅረብ ለታዋቂዋ አትሌት መልካም ጤንነትና ረጅም ዕድሜ ተመኝቷል።
ጋዜጠኛ ካሳሁን ፈይሳ በኦንታሪዮ፣ ቶሮንቶ ካናዳ 🇨🇦 ነዋሪ ነው።
#sport #marathon #atlanta1996 #olympics #athletics #history #legend #ethiopianathletes #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 month ago
ኢትዮጵያን ወደ ዓለም አቀፍ ማዕከልነት...
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ በአፍሪካ አቪዬሽን ያላትን ታሪካዊ ቀዳሚነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግርና የኢኮኖሚ አቅሟን የሚቀይር አዲስ የታሪክ ምዕራፍ እየጻፈች ትገኛለች።
በ12 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር ወጪ እየተገነባ የሚገኘው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ የንግድና የጉዞ ካርታ ላይ ቀዳሚ ተመራጭ የሚያደርግ ስትራቴጂያዊ የኢኮኖሚ ሞተር ነው።
ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያ በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ ያላትን የመሪነት ሚና ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ የአቪየሽን ዘርፍም ትልቅ ተስፋ የሚሆን ነው።
በአሁኑ ወቅት የቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በዓመት ማስተናገድ የሚችለው 25 ሚሊየን መንገደኞች ሲሆን፥ አዲሱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የመጀመሪያ ምዕራፍ ሲጠናቀቅ 60 ሚሊየን መንገደኞችን ማስተናገድ ይችላል፡፡
ሁለተኛው ምዕራፍ ሲጠናቀቅ ደግሞ 110 ሚሊየን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ይኖረዋል።
በዓመት ከ106 ሚሊየን በላይ መንገደኞችን ከሚያስተናግደው የአትላንታው ሀርትስፊልድ ጃክሰን እንዲሁም ከ95 ሚሊየን በላይ መንገደኞችን ከሚያስተናግደው የዱባይ አውሮፕላን ማረፊያዎች ተርታ በመሰለፍ ኢትዮጵያን የዓለማችን ዋነኛ የመገናኛ ማዕከል ያደርጋታል።
አውሮፕላን ማረፊያው በዝቅተኛ የባህር ጠለል ከፍታ ላይ የሚገነባ በመሆኑ አውሮፕላኖች ከፍተኛ የነዳጅና የጭነት ክብደት ይዘው በቀላሉ እንዲነሱ በማስቻል የኢትዮጵያን የንግድ እንቅስቃሴ ወደፊት በማራመድ ለኢኮኖሚው ከፍተኛ መነቃቃትን ይፈጥራል።
ከዚህ ባሻገር ፕሮጀክቱ የንግድ ማዕከላትን፣ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎችንና የሎጂስቲክስ ማዕከላትን ያካተተ በመሆኑ ለዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል በመፍጠርና የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ ያደርጋል።
በተጨማሪም የአካባቢ ጥበቃን ከግምት ያስገባና አረንጓዴ ቴክኖሎጂን የሚጠቀም በመሆኑ ለዘላቂ ልማት ትልቅ ማሳያ ተደርጎ ይወሰዳል።
የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ለፕሮጀክቱ ግንባታ 92 የኤሌክትሪክ ገልባጭ መኪኖችን በቅርቡ ስራ ማስጀመሩ ለዚህ ማሳያ የሚሆን ነው።
በአጠቃላይ የቢሾፍቱ ሜጋ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያ የአህጉሪቱ መግቢያ በመሆን በዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ካርታ ላይ ያላትን ተፅዕኖ ፈጣሪነት ወደ አዲስ ከፍታ የሚያሸጋግር ግዙፍ ርምጃ ነው።
በሶስና አለማየሁ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ በአፍሪካ አቪዬሽን ያላትን ታሪካዊ ቀዳሚነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግርና የኢኮኖሚ አቅሟን የሚቀይር አዲስ የታሪክ ምዕራፍ እየጻፈች ትገኛለች።
በ12 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር ወጪ እየተገነባ የሚገኘው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ የንግድና የጉዞ ካርታ ላይ ቀዳሚ ተመራጭ የሚያደርግ ስትራቴጂያዊ የኢኮኖሚ ሞተር ነው።
ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያ በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ ያላትን የመሪነት ሚና ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ የአቪየሽን ዘርፍም ትልቅ ተስፋ የሚሆን ነው።
በአሁኑ ወቅት የቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በዓመት ማስተናገድ የሚችለው 25 ሚሊየን መንገደኞች ሲሆን፥ አዲሱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የመጀመሪያ ምዕራፍ ሲጠናቀቅ 60 ሚሊየን መንገደኞችን ማስተናገድ ይችላል፡፡
ሁለተኛው ምዕራፍ ሲጠናቀቅ ደግሞ 110 ሚሊየን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ይኖረዋል።
በዓመት ከ106 ሚሊየን በላይ መንገደኞችን ከሚያስተናግደው የአትላንታው ሀርትስፊልድ ጃክሰን እንዲሁም ከ95 ሚሊየን በላይ መንገደኞችን ከሚያስተናግደው የዱባይ አውሮፕላን ማረፊያዎች ተርታ በመሰለፍ ኢትዮጵያን የዓለማችን ዋነኛ የመገናኛ ማዕከል ያደርጋታል።
አውሮፕላን ማረፊያው በዝቅተኛ የባህር ጠለል ከፍታ ላይ የሚገነባ በመሆኑ አውሮፕላኖች ከፍተኛ የነዳጅና የጭነት ክብደት ይዘው በቀላሉ እንዲነሱ በማስቻል የኢትዮጵያን የንግድ እንቅስቃሴ ወደፊት በማራመድ ለኢኮኖሚው ከፍተኛ መነቃቃትን ይፈጥራል።
ከዚህ ባሻገር ፕሮጀክቱ የንግድ ማዕከላትን፣ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎችንና የሎጂስቲክስ ማዕከላትን ያካተተ በመሆኑ ለዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል በመፍጠርና የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ ያደርጋል።
በተጨማሪም የአካባቢ ጥበቃን ከግምት ያስገባና አረንጓዴ ቴክኖሎጂን የሚጠቀም በመሆኑ ለዘላቂ ልማት ትልቅ ማሳያ ተደርጎ ይወሰዳል።
የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ለፕሮጀክቱ ግንባታ 92 የኤሌክትሪክ ገልባጭ መኪኖችን በቅርቡ ስራ ማስጀመሩ ለዚህ ማሳያ የሚሆን ነው።
በአጠቃላይ የቢሾፍቱ ሜጋ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያ የአህጉሪቱ መግቢያ በመሆን በዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ካርታ ላይ ያላትን ተፅዕኖ ፈጣሪነት ወደ አዲስ ከፍታ የሚያሸጋግር ግዙፍ ርምጃ ነው።
በሶስና አለማየሁ
1 month ago
የሲኤንኤን (CNN) መስራች ቴድ ተርነር አረፉ
#ethiopia | የዓለማችንን የዜና አቀራረብ እና የሚዲያ አጠቃቀም የቀየሩት ዝነኛው ባለሀብት ቴድ ተርነር በ87 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ተቋማቸው ሲኤንኤን (CNN) አረጋግጧል።
በፈረንጆቹ 1980 የመጀመሪያውን የ24 ሰዓት የዜና ጣቢያ በመመስረት የሚታወቁት ተርነር፣ በወቅቱ የማይታሰብ የነበረውን የ"ቀጥታ ስርጭት" የዜና ጥበብ ለዓለም በማስተዋወቅ የሚዲያ ታሪክን የለወጡ ታላቅ ሰው ነበሩ።
ዜና በየሰዓቱ እና በየደቂቃው ለዓለም መድረስ እንዳለበት በማመን የመጀመሪያውን የ24 ሰዓት የዜና ኔትወርክ መስርተዋል።
ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) 1 ቢሊዮን ዶላር በመለገስ በሰብአዊ መብት እና በአካባቢ ጥበቃ ላይ ከፍተኛ አሻራ አሳርፈዋል።
ከተለያዩ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች በተጨማሪ በስፖርቱ ዓለምም እንደ አትላንታ ብሬቭስ ያሉ ተቋማት ባለቤት በመሆን ስማቸው ገዝፎ የሚነሳ ሰው ነበሩ።
ቴድ ተርነር በቢዝነስና በሚዲያ ዓለም ካሳዩት ብቃት ባሻገር፣ በግልጽ የመናገር ስልታቸውና በፈጠራ የታጀበ አመራራቸው በብዙዎች ዘንድ ዘላቂ ክብርን አትርፎላቸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#tedturner #cnn #mediaicon #legacy #breakingnews #restinpeace #ethiopia #የሚዲያ_ታሪክ
#ethiopia | የዓለማችንን የዜና አቀራረብ እና የሚዲያ አጠቃቀም የቀየሩት ዝነኛው ባለሀብት ቴድ ተርነር በ87 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ተቋማቸው ሲኤንኤን (CNN) አረጋግጧል።
በፈረንጆቹ 1980 የመጀመሪያውን የ24 ሰዓት የዜና ጣቢያ በመመስረት የሚታወቁት ተርነር፣ በወቅቱ የማይታሰብ የነበረውን የ"ቀጥታ ስርጭት" የዜና ጥበብ ለዓለም በማስተዋወቅ የሚዲያ ታሪክን የለወጡ ታላቅ ሰው ነበሩ።
ዜና በየሰዓቱ እና በየደቂቃው ለዓለም መድረስ እንዳለበት በማመን የመጀመሪያውን የ24 ሰዓት የዜና ኔትወርክ መስርተዋል።
ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) 1 ቢሊዮን ዶላር በመለገስ በሰብአዊ መብት እና በአካባቢ ጥበቃ ላይ ከፍተኛ አሻራ አሳርፈዋል።
ከተለያዩ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች በተጨማሪ በስፖርቱ ዓለምም እንደ አትላንታ ብሬቭስ ያሉ ተቋማት ባለቤት በመሆን ስማቸው ገዝፎ የሚነሳ ሰው ነበሩ።
ቴድ ተርነር በቢዝነስና በሚዲያ ዓለም ካሳዩት ብቃት ባሻገር፣ በግልጽ የመናገር ስልታቸውና በፈጠራ የታጀበ አመራራቸው በብዙዎች ዘንድ ዘላቂ ክብርን አትርፎላቸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#tedturner #cnn #mediaicon #legacy #breakingnews #restinpeace #ethiopia #የሚዲያ_ታሪክ
2 months ago
የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለአፍሪካ የአቪየሽን ዘርፍ ትልቅ ተስፋ ነው - ሲኤንኤን
#ethiopia | ኢትዮጵያ የአፍሪካን የበረራ መስመር እንደሚቀይር ተስፋ የተጣለበትን ግዙፍ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ እየገነባች መሆኗን ሲኤንኤን አስነብቧል፡፡
የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የመጀመሪያ ምዕራፍ በፈረንጆቹ 2030 ሲጠናቀቅ በዓመት 60 ሚሊየን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ያለው ነው፡፡
ፕሮጀክቱ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ ይህ አቅሙ ወደ 110 ሚሊየን መንገደኞች ከፍ እንደሚል የጠቀሰው ዘገባው፥ በዚህም በዓለማችን በርካታ መንገደኞችን በማስተናገድ ቀዳሚ ከሆነው አትላንታ አውሮፕላን ማረፊያ እንደሚበልጥ አመልክቷል፡፡
በአሁኑ ወቅት መንገደኞች በአፍሪካ ውስጥ የአውሮፕላን ጉዞ ለማድረግ ከአህጉሪቱ ውጪ እንደ ዱባይ፣ ፓሪስ እና ለንደን የመሳሰሉ ከተሞችን ትራንዚት ለማድረግ እንደሚገደዱ ሲኤንኤን በዘገባው ጠቅሷል፡፡
ነገር ግን በ12 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር ባሳለፍነው ጥር ወር ግንባታው የተጀመረው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ይህንን ችግር በማስቀረት ለአህጉሪቱ አዲስ የበረራ መስመር እንደሚያበጅ ተስፋ ተጥሎበታል ብሏል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአውሮፕላን ማረፊያውን ግንባታ ባስጀመሩበት ወቅት፥ ፕሮጀክቱ በአፍሪካ ታሪክ ግዙፍ የአቪየሽን መሰረተ ልማት ነው ማለታቸውን ዘገባው አስታውሷል፡፡
በአፍሪካ ቀዳሚ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የፕሮጀክቱን 30 በመቶ ወጪ እንደሚሸፍን የአየር መንገዱን ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው ተናግረዋል፡፡
አውሮፕላን ማረፊያው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓለም ፈጣን እድገት እያስመዘገቡ ካሉ የአቪዬሽን ገበያዎች አንዱ የሆነውን የአፍሪካን ሰማይ ለማገናኘት የሚደረገውን ውድድር እንዲመራ ያስችለዋል።
በተጨማሪም በዓመት 3 ነጥብ 73 ሚሊየን ቶን ጭነት የማስተናገድ አቅም የሚኖረው ሲሆን፥ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናን በመደገፍ የአህጉሪቱን ጥቅም ላይ ያልዋለ የካርጎ አቅም ለመጠቀም የሚያስችል መሆኑን ዘገባው አመልክቷል።
የአፍሪካ አየር መንገዶች በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የጭነት አገልግሎት እያስተናገዱ ሲሆን፥ ይህም በዓመት ከ15 እስከ 16 በመቶ ጭማሪ እንዳለው ጠቁሟል፡፡
ፕሮጀክቱን በገንዘብ በመደገፍ ረገድ በተለይም እንደ አሜሪካ፣ ቻይና እና ጣሊያን ያሉ ሀገራት በሂደቱ እየተሳተፉ ሲሆን፥ በዚህም ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴዎች መኖራቸውን ሲኤንኤን በዘገባው አመልክቷል፡፡
via #fmc
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ethiopia | ኢትዮጵያ የአፍሪካን የበረራ መስመር እንደሚቀይር ተስፋ የተጣለበትን ግዙፍ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ እየገነባች መሆኗን ሲኤንኤን አስነብቧል፡፡
የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የመጀመሪያ ምዕራፍ በፈረንጆቹ 2030 ሲጠናቀቅ በዓመት 60 ሚሊየን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ያለው ነው፡፡
ፕሮጀክቱ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ ይህ አቅሙ ወደ 110 ሚሊየን መንገደኞች ከፍ እንደሚል የጠቀሰው ዘገባው፥ በዚህም በዓለማችን በርካታ መንገደኞችን በማስተናገድ ቀዳሚ ከሆነው አትላንታ አውሮፕላን ማረፊያ እንደሚበልጥ አመልክቷል፡፡
በአሁኑ ወቅት መንገደኞች በአፍሪካ ውስጥ የአውሮፕላን ጉዞ ለማድረግ ከአህጉሪቱ ውጪ እንደ ዱባይ፣ ፓሪስ እና ለንደን የመሳሰሉ ከተሞችን ትራንዚት ለማድረግ እንደሚገደዱ ሲኤንኤን በዘገባው ጠቅሷል፡፡
ነገር ግን በ12 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር ባሳለፍነው ጥር ወር ግንባታው የተጀመረው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ይህንን ችግር በማስቀረት ለአህጉሪቱ አዲስ የበረራ መስመር እንደሚያበጅ ተስፋ ተጥሎበታል ብሏል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአውሮፕላን ማረፊያውን ግንባታ ባስጀመሩበት ወቅት፥ ፕሮጀክቱ በአፍሪካ ታሪክ ግዙፍ የአቪየሽን መሰረተ ልማት ነው ማለታቸውን ዘገባው አስታውሷል፡፡
በአፍሪካ ቀዳሚ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የፕሮጀክቱን 30 በመቶ ወጪ እንደሚሸፍን የአየር መንገዱን ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው ተናግረዋል፡፡
አውሮፕላን ማረፊያው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዓለም ፈጣን እድገት እያስመዘገቡ ካሉ የአቪዬሽን ገበያዎች አንዱ የሆነውን የአፍሪካን ሰማይ ለማገናኘት የሚደረገውን ውድድር እንዲመራ ያስችለዋል።
በተጨማሪም በዓመት 3 ነጥብ 73 ሚሊየን ቶን ጭነት የማስተናገድ አቅም የሚኖረው ሲሆን፥ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናን በመደገፍ የአህጉሪቱን ጥቅም ላይ ያልዋለ የካርጎ አቅም ለመጠቀም የሚያስችል መሆኑን ዘገባው አመልክቷል።
የአፍሪካ አየር መንገዶች በአሁኑ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የጭነት አገልግሎት እያስተናገዱ ሲሆን፥ ይህም በዓመት ከ15 እስከ 16 በመቶ ጭማሪ እንዳለው ጠቁሟል፡፡
ፕሮጀክቱን በገንዘብ በመደገፍ ረገድ በተለይም እንደ አሜሪካ፣ ቻይና እና ጣሊያን ያሉ ሀገራት በሂደቱ እየተሳተፉ ሲሆን፥ በዚህም ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴዎች መኖራቸውን ሲኤንኤን በዘገባው አመልክቷል፡፡
via #fmc
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
3 months ago
ትራምፕ ስለ ኢራን የዓለም ዋንጫ ተሳትፎ ደንታ እንደሌላቸው ገለጹ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ ኢራን በዚህ ዓመት በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ በሚስተናገደው የዓለም ዋንጫ ላይ ስላላት ተሳትፎ ግድ እንደማይላቸው ገለጹ።
ትራምፕ ለፖሊቲኮ በሰጡት ቃል፣ "ኢራን የተሸነፈች ሀገር ናት፤ በትርፍራፊ ነው የሚኖሩት" በማለት ተሳትፎዋ እንደማያሳስባቸው ተናግረዋል።
በዚህ ሳምንት በአትላንታ በተካሄደው የፊፋ የቅድመ ዝግጅት ስብሰባ ላይ ሳይገኝ የቀረው ብቸኛ ሀገር ኢራን ብቻ መሆኑ፣ ቡድኑ በውድድሩ ላይ ስለመካፈሉ ጥርጣሬን ፈጥሯል።
ይህ የሆነው በመካከለኛው ምስራቅ ባለው ከፍተኛ ቀውስ ምክንያት ነው። ኢራን በምድብ ሰባት ከቤልጂየም፣ ግብፅ እና ኒውዚላንድ ጋር የተመደበች ሲሆን፣ ጨዋታዎቿንም በሎስ አንጀለስ እና በሲያትል ከተሞች ለማድረግ ቀጠሮ ተይዞላቸዋል።
ሆኖም ሀገሪቱ በወቅታዊ ፖለቲካዊ ውጥረት ምክንያት በውድድሩ ላይ መገኘቷ አሁንም አጠራጣሪ ሆኗል።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ ኢራን በዚህ ዓመት በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ በሚስተናገደው የዓለም ዋንጫ ላይ ስላላት ተሳትፎ ግድ እንደማይላቸው ገለጹ።
ትራምፕ ለፖሊቲኮ በሰጡት ቃል፣ "ኢራን የተሸነፈች ሀገር ናት፤ በትርፍራፊ ነው የሚኖሩት" በማለት ተሳትፎዋ እንደማያሳስባቸው ተናግረዋል።
በዚህ ሳምንት በአትላንታ በተካሄደው የፊፋ የቅድመ ዝግጅት ስብሰባ ላይ ሳይገኝ የቀረው ብቸኛ ሀገር ኢራን ብቻ መሆኑ፣ ቡድኑ በውድድሩ ላይ ስለመካፈሉ ጥርጣሬን ፈጥሯል።
ይህ የሆነው በመካከለኛው ምስራቅ ባለው ከፍተኛ ቀውስ ምክንያት ነው። ኢራን በምድብ ሰባት ከቤልጂየም፣ ግብፅ እና ኒውዚላንድ ጋር የተመደበች ሲሆን፣ ጨዋታዎቿንም በሎስ አንጀለስ እና በሲያትል ከተሞች ለማድረግ ቀጠሮ ተይዞላቸዋል።
ሆኖም ሀገሪቱ በወቅታዊ ፖለቲካዊ ውጥረት ምክንያት በውድድሩ ላይ መገኘቷ አሁንም አጠራጣሪ ሆኗል።
4 months ago
አድዋ በአትላንታ 🇪🇹🇺🇸
130ኛው የድል በዓል በ"ስቶን ማውንቴን" ደመቀ
#ethiopia | በአሜሪካ አትላንታ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን 130ኛውን የዓድዋ የድል በዓል "የድል እንጂ የነፃነት ቀን የለንም!" በሚል መሪ ቃል በታላቅ ድምቀት አክብረዋል።
በ"ጉዞ ዓድዋ በአትላንታ ማህበር" አዘጋጅነት በስቶን ማውንቴን ፓርክ በተደረገው በዚህ ስምንተኛ ዙር የእግር ጉዞ፣ በርካታ ኢትዮጵያውያን በጠዋት በመሰባሰብ የጋራ ታሪካቸውን ዘክረዋል።
የትውልድ ቅብብል፦
አሜሪካ ተወልደው ያደጉ ሕፃናት የታሪኩ ባለቤት እንዲሆኑ "ለልጆች በልጆች" በሚል መርህ ታሪካቸውን እንዲማሩና እንዲደምቁበት ተደርጓል።
ታሪካዊ ስያሜዎች፦
በጉዞው ወቅት ወርኢሉ፣ አምባላጌ፣ መቀሌ እና ዓድዋ ተብለው የተሰየሙ ቦታዎች ተዘጋጅተው ታሪካቸው ለተሳታፊው ቀርቧል።
የአንድነት ድምቀት፦
ዕድሜ፣ ዘር፣ ጾታና ሃይማኖት ሳይለይ ሁሉም ተሳታፊ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ በሚመስል "ሁዲ" (Hoodie) ደምቆ ታሪኩን በጋራ አክብሯል።
የምኒልክ የግብር አዳራሽ፦
በጉዞው ማጠናቀቂያ ላይ በ"ምኒልክ የግብር አዳራሽ" ሁሉም ተሳታፊ የማዕዱ ተቋዳሽ እንዲሆን ተደርጓል።
🙏 የምስጋና ጥሪ
ይህ ታላቅና የተሳካ ፕሮግራም እንዲካሄድ ድጋፍ ላደረጉ ድርጅቶች፣ ግለሰቦች፣ የሚዲያ ባለሙያዎች እና ለረጅም ጊዜ የደከሙ የጉዞ ዓድዋ አስተባባሪዎች ማህበሩ ልባዊ ምስጋናውን አቅርቧል።
#አድዋ130 #ጉዞዓድዋ #አትላንታ #ኢትዮጵያ #የድልበዓል #ስቶንማውንቴን #adwa130 #guzoadwa #atlanta #ethiopia #stonemountain #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
130ኛው የድል በዓል በ"ስቶን ማውንቴን" ደመቀ
#ethiopia | በአሜሪካ አትላንታ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን 130ኛውን የዓድዋ የድል በዓል "የድል እንጂ የነፃነት ቀን የለንም!" በሚል መሪ ቃል በታላቅ ድምቀት አክብረዋል።
በ"ጉዞ ዓድዋ በአትላንታ ማህበር" አዘጋጅነት በስቶን ማውንቴን ፓርክ በተደረገው በዚህ ስምንተኛ ዙር የእግር ጉዞ፣ በርካታ ኢትዮጵያውያን በጠዋት በመሰባሰብ የጋራ ታሪካቸውን ዘክረዋል።
የትውልድ ቅብብል፦
አሜሪካ ተወልደው ያደጉ ሕፃናት የታሪኩ ባለቤት እንዲሆኑ "ለልጆች በልጆች" በሚል መርህ ታሪካቸውን እንዲማሩና እንዲደምቁበት ተደርጓል።
ታሪካዊ ስያሜዎች፦
በጉዞው ወቅት ወርኢሉ፣ አምባላጌ፣ መቀሌ እና ዓድዋ ተብለው የተሰየሙ ቦታዎች ተዘጋጅተው ታሪካቸው ለተሳታፊው ቀርቧል።
የአንድነት ድምቀት፦
ዕድሜ፣ ዘር፣ ጾታና ሃይማኖት ሳይለይ ሁሉም ተሳታፊ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ በሚመስል "ሁዲ" (Hoodie) ደምቆ ታሪኩን በጋራ አክብሯል።
የምኒልክ የግብር አዳራሽ፦
በጉዞው ማጠናቀቂያ ላይ በ"ምኒልክ የግብር አዳራሽ" ሁሉም ተሳታፊ የማዕዱ ተቋዳሽ እንዲሆን ተደርጓል።
🙏 የምስጋና ጥሪ
ይህ ታላቅና የተሳካ ፕሮግራም እንዲካሄድ ድጋፍ ላደረጉ ድርጅቶች፣ ግለሰቦች፣ የሚዲያ ባለሙያዎች እና ለረጅም ጊዜ የደከሙ የጉዞ ዓድዋ አስተባባሪዎች ማህበሩ ልባዊ ምስጋናውን አቅርቧል።
#አድዋ130 #ጉዞዓድዋ #አትላንታ #ኢትዮጵያ #የድልበዓል #ስቶንማውንቴን #adwa130 #guzoadwa #atlanta #ethiopia #stonemountain #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
4 months ago
የማርኪንዮስ እና ክቫራትስኬሊያ ግቦች ሞናኮን ከሻምፒዮንስ ሊግ አሰናበቱ
በፓሪስ ፓርክ ደ ፕሪንስ ስታዲየም በተደረገው የሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታ ፒኤስጂ እና ሞናኮ 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት ቢለያዩም፣ ፒኤስጂ በድምር ውጤት 5 ለ 4 በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር አልፏል።
ሞናኮ በ45ኛው ደቂቃ በአክሊውች ግብ ቀዳሚ መሆን ቢችልም፣ በ58ኛው ደቂቃ ኩሊባሊ በሁለት ቢጫ ካርድ ከሜዳ መውጣቱ ጨዋታውን ቀይሮታል።
ፒኤስጂዎች የተጫዋች ብልጫቸውን በመጠቀም በማርኪንዮስ እና በክቫራትስኬሊያ አማካኝነት ሁለት ግቦችን አስቆጥረዋል።
ሞናኮ በጭማሪ ሰዓት የአቻነት ግብ ቢያስቆጥርም ፒኤስጂን ከውድድር ለማስወጣት ግን አልበቃውም።
በዚህም የፈረንሳዩ ሻምፒዮን ፒኤስጂ ከሪያል ማድሪድ እና ከአትላንታ ጋር በመሆን የ16ቱን ዙር መቀላቀሉን አረጋግጧል።
በፓሪስ ፓርክ ደ ፕሪንስ ስታዲየም በተደረገው የሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታ ፒኤስጂ እና ሞናኮ 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት ቢለያዩም፣ ፒኤስጂ በድምር ውጤት 5 ለ 4 በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር አልፏል።
ሞናኮ በ45ኛው ደቂቃ በአክሊውች ግብ ቀዳሚ መሆን ቢችልም፣ በ58ኛው ደቂቃ ኩሊባሊ በሁለት ቢጫ ካርድ ከሜዳ መውጣቱ ጨዋታውን ቀይሮታል።
ፒኤስጂዎች የተጫዋች ብልጫቸውን በመጠቀም በማርኪንዮስ እና በክቫራትስኬሊያ አማካኝነት ሁለት ግቦችን አስቆጥረዋል።
ሞናኮ በጭማሪ ሰዓት የአቻነት ግብ ቢያስቆጥርም ፒኤስጂን ከውድድር ለማስወጣት ግን አልበቃውም።
በዚህም የፈረንሳዩ ሻምፒዮን ፒኤስጂ ከሪያል ማድሪድ እና ከአትላንታ ጋር በመሆን የ16ቱን ዙር መቀላቀሉን አረጋግጧል።
5 months ago
🔥 ታላቅ የሙዚቃ ኮንሠርት በአትላንታ 🇺🇸
የሶል ሙዚቃ ንግሥት አስቴር አወቀ እና ተወዳጁ ድምፃዊ ኤፍሬም አማረ በአንድ መድረክ የሚገናኙበት ታሪካዊ ምሽት!
በናሆም ሪከርድስ፣ ቤኒ ኢንተርተይመንት እና ይቻላል ኢንተርቴይመንት ለአዲሱ ዓመት የተዘጋጀ ልዩ የሙዚቃ ድግስ እንዳያመልጥዎ!
📅 ቀን: ቅዳሜ፣ January 18, 2026
📍 ቦታ: Bliss Nightclub (Stone Mountain, GA)
🎫 ትኬት ለማግኘት:
በኦንላይን ወይም በአካል ከሚከተሉት ቦታዎች መግዛት ይችላሉ፡
1️⃣ የሺ ፉድ ማርት
(Yeshi Food Mart) - Clarkston
2️⃣ ባላገሩ ፉድ ማርት
(Balageru Food Mart) - Clarkston
3️⃣ መርካቶ ማርኬት
(Merkato Market) - Atlanta
ወይም በኦንላይን ለማግኘት በፖስተሩ ላይ ያለውን QR Code ስካን ያድርጉ!
📞 ለበለጠ መረጃ:
+1 202-262-8134
+1 202-993-3251
ቦታው ሳይሞላ ቀድመው ይያዙ! 💃🕺
የሶል ሙዚቃ ንግሥት አስቴር አወቀ እና ተወዳጁ ድምፃዊ ኤፍሬም አማረ በአንድ መድረክ የሚገናኙበት ታሪካዊ ምሽት!
በናሆም ሪከርድስ፣ ቤኒ ኢንተርተይመንት እና ይቻላል ኢንተርቴይመንት ለአዲሱ ዓመት የተዘጋጀ ልዩ የሙዚቃ ድግስ እንዳያመልጥዎ!
📅 ቀን: ቅዳሜ፣ January 18, 2026
📍 ቦታ: Bliss Nightclub (Stone Mountain, GA)
🎫 ትኬት ለማግኘት:
በኦንላይን ወይም በአካል ከሚከተሉት ቦታዎች መግዛት ይችላሉ፡
1️⃣ የሺ ፉድ ማርት
(Yeshi Food Mart) - Clarkston
2️⃣ ባላገሩ ፉድ ማርት
(Balageru Food Mart) - Clarkston
3️⃣ መርካቶ ማርኬት
(Merkato Market) - Atlanta
ወይም በኦንላይን ለማግኘት በፖስተሩ ላይ ያለውን QR Code ስካን ያድርጉ!
📞 ለበለጠ መረጃ:
+1 202-262-8134
+1 202-993-3251
ቦታው ሳይሞላ ቀድመው ይያዙ! 💃🕺
5 months ago
🔥 ታላቅ የሙዚቃ ኮንሠርት በአትላንታ 🇺🇸
የሶል ሙዚቃ ንግሥት አስቴር አወቀ እና ተወዳጁ ድምፃዊ ኤፍሬም አማረ በአንድ መድረክ የሚገናኙበት ታሪካዊ ምሽት!
በናሆም ሪከርድስ፣ ቤኒ ኢንተርተይመንት እና ይቻላል ኢንተርቴይመንት ለአዲሱ ዓመት የተዘጋጀ ልዩ የሙዚቃ ድግስ እንዳያመልጥዎ!
📅 ቀን: እሁድ፣ January 18, 2026
📍 ቦታ: Bliss Nightclub (Stone Mountain, GA)
🎫 ትኬት ለማግኘት:
በኦንላይን ወይም በአካል ከሚከተሉት ቦታዎች መግዛት ይችላሉ፡
1️⃣ የሺ ፉድ ማርት
(Yeshi Food Mart) - Clarkston
2️⃣ ባላገሩ ፉድ ማርት
(Balageru Food Mart) - Clarkston
3️⃣ መርካቶ ማርኬት
(Merkato Market) - Atlanta
ወይም በኦንላይን ለማግኘት በፖስተሩ ላይ ያለውን QR Code ስካን ያድርጉ!
📞 ለበለጠ መረጃ:
+1 202-262-8134
+1 202-993-3251
ቦታው ሳይሞላ ቀድመው ይያዙ! 💃🕺
የሶል ሙዚቃ ንግሥት አስቴር አወቀ እና ተወዳጁ ድምፃዊ ኤፍሬም አማረ በአንድ መድረክ የሚገናኙበት ታሪካዊ ምሽት!
በናሆም ሪከርድስ፣ ቤኒ ኢንተርተይመንት እና ይቻላል ኢንተርቴይመንት ለአዲሱ ዓመት የተዘጋጀ ልዩ የሙዚቃ ድግስ እንዳያመልጥዎ!
📅 ቀን: እሁድ፣ January 18, 2026
📍 ቦታ: Bliss Nightclub (Stone Mountain, GA)
🎫 ትኬት ለማግኘት:
በኦንላይን ወይም በአካል ከሚከተሉት ቦታዎች መግዛት ይችላሉ፡
1️⃣ የሺ ፉድ ማርት
(Yeshi Food Mart) - Clarkston
2️⃣ ባላገሩ ፉድ ማርት
(Balageru Food Mart) - Clarkston
3️⃣ መርካቶ ማርኬት
(Merkato Market) - Atlanta
ወይም በኦንላይን ለማግኘት በፖስተሩ ላይ ያለውን QR Code ስካን ያድርጉ!
📞 ለበለጠ መረጃ:
+1 202-262-8134
+1 202-993-3251
ቦታው ሳይሞላ ቀድመው ይያዙ! 💃🕺
5 months ago
✈️ጉዞ ወደ አሜሪካ ፍሎሪዳ ታላሃስ ከተማ ✈️
♦️በዓለም አገር አቋራጭ ሻምፒዮና ላይ የሚሳተፈው
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ቡድን የኮኔክሽን ችግሮቹ ተፈተው ምሽት 4:00 ወደ አትላንታ ✈️ ይበራሉ ✈️
♦️ከአታላንታ ወደ ታላሃስ በአውቶቡስ ከ4 ሠዓት በላይ የሚጓዙ ይሆናል
♦️በ8ኪ.ሜ ወጣት ወንዶችና በ6ኪ.ሜ ወጣት ሴቶች በግል ከመሳተፍ በዘለለ ውጤት አይጠበቅበትም
♦️በግል አሸናፊ ለሚሆን 30ሺ፣በቡድን 20ሺ ዶላር ለሽልማት ተመድቧል
ለዓመታት ሽርጉድ ስትል የቆየችው የአሜሪካ ፍሎሪዳዋ ታላሃስ ከተማ የፊታችን ጃንዋሪ 10 46ኛውን የአለም አገር አቋራጭ ሻምፒዮና በልዩ ድምቀት ታስተናግዳለች።
በ1984 ኒውዮርክ፣በ1992 ቦስተን የአለም አገር አቋራጭ ውድድርን ካስተናገደች ከ30 ዓመታት በኃላ የማስተናገድ ዕድል ያገኘችው አሜሪካ ከ60 በላይ ሀገራት የተውጣጡ 500 አትሌቶች የሚሳተፉበትን የአንድ ቀን ውድድር ለማስተናገድ ሽርጉዷን አጠናቃ የእንግዶቿን መምጣት በመጠባበቅ ላይ ትገኛለች።
በውድድሩ ለአሸናፊነት ግምት ከተሠጣቸው ሀገሮች አንዷ የሆነችው ኬንያ የልዑካን ቡድናን ከፋፍላ ወደ ፍሎሪዳ የሸኘች ሲሆን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድንም ለ47 ቀናት በቀነኒሳ ሆቴል ሱሉልታ ሲያደረገው የነበረው ዝግጅትን አጠናቆ ትናንት(ዓርብ)የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር የሆኑት ክቡር አቶ መኪዩ መሀመድ በተገኙበት የክብር ሽኝት የተደረገለት ሲሆን ዛሬ ምሽት 4:00 ወደ ውድድሩ ስፍራ የሚጓዝ ይሆናል።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በቂ የዝግጅት ጊዜ(47 ቀን)በመስጠት፣ከረዥም ዓመት በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከአዲስ አበባ ከተማ ውጪ በሱሉልታ ቀነኒሳ ሪዞርት ሆቴል እንዲዘጋጁ በማድረግና በደማቅ የክብር አሸኛኘት ማድረጉ ብዙዎች ፌዴሬሽኑን እንዲያመሠግኑ አስገድዷል።
የአሜሪካ ኤምባሲ የቪዛ ማመልከቻ ጥያቄያቸው ተቀባይነት በማጣቱ ምክንያት በቪዛ ችግር ሲታመስ የቆየው የአትሌቲክስ ቡድን አባላቱ በአሁን ሠዓት በቦሌ ኢንተርናሽናል አውሮፕላን ማረፊያ ለጉዞ አስፈሊጊ የሆነውን የኢሚግሬሽን ፕሮሰስ እያከናወኑ ሲሆን ምሽት 4:30 ከአዲስ አበባ በቀጥታ አታላንታ እንደሚበሩ የፌዴሬሽኑ ታማኝ የመረጃ ምንጮቻችን ገልፀውልናል።
የኢትዮጵያ የአትሌቲክስ ቡድን ከጉዞ ጋር በተለይ ከ flight ✈️ ኮኔክሽን ጋር በተያያዘ ችግር ገጥሞት በተለይ ከአታላንታ ወደ ታላሃስ በረራ ባለመገኘቱ ቡድኑን በሶስት ግሩፕ ከፋፍሎ የመውሠድ ዕቅድ ታቅዶ የነበረ ሲሆን በመጨረሻ ከአየር መንገዱ ጋር በተደረገ ንግግር ቡድኑ ተበታትኖ ከመሄድ በአንድነት ቢሄዱና አታላንታ ላይ ኮኔክሽን ፍላይት ባይኖርም በአውቶቡስ መሄድ እንችላለን የሚለው ሃሳብ ገዥ አግኝቶ ሁሉም የቡድኑ አባላት ከአዲስ አበባ አታላንታ ከአታላንታ የውድድሩ ስፍራ ወደ ሆነችው ታላሃስ Apalachee Regional Park በተዘጋጀላቸው ደረጃውን የጠበቀ አውቶብስ ከ4:30-6:00 የሚፈጅ የመኪና ጉዞ በማድረግ ወደተዘጋጀላቸው ደብል ትሪ ሆቴል እንደሚያመሩ ተረጋግጧል።
በሶስት ግሩፕ ተከፋፍሎ ሁሉም አንድ ላይ የመጓዛቸው ውሳኔ ብዙዎችን ያስደሠተ ሲሆን ከ4:00 እስከ 6:00 የፈጀ የአውቶቡስ ጉዞ ማድረጋቸው የድካም ስሜትን ያመጣል የሚል ስጋትን ከወዲሁ በብዙዎች እንዲፈጠር አድርጓል።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከአትሌቶችና ከአሠልጣኞች በተጨማሪ ለአንድ ቀን ውድድር ሁለት የቡድን መሪ እንዲሁም ሁለት ጊዜ ቪዛ በተከለከሉት የፅ/ቤት ኃላፊው አመንሲሳ ከበደ(ዶ/ር) ምትክ ቡድኑን እንዲያግዝ በሚል ከስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው ፕሬዝዳንቱ ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን በመጨረሻ ሠዓት በጉዞው የተካተተ ሲሆን ሌሎቹ ዛሬ ምሽት ፕሬዝዳንቱ ደግሞ በነገው ዕለት ወደ ፍሎሪዳ ታላሃስ እንደሚያመሩ ታውቋል።
ከዚሁ ከአሜሪካው ታላሃስ ዜና ሳንወጣ በአሁን ሠዓት አሜሪካ የሚገኘው የአገር አቋራጩ ጀግና አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ቡድኑን በአካል ተገኝቶ እንዲያበረታታ ጥረት እየተደረገ ሲሆን የቡድኑ አባል እንዲሆንና አትሌቶቹን እንዲያበረታታ አስፈላጊው ፕሮሠስ እንደተደረገለትም ወደስፍራው ከሚጓዙ ታማኝ የመረጃ ምንጮቻችን ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል።
በ46ኛው የአለም አገር አቋራጭ ውድድር ላይ የምትሳተፈው ሀገራችን በ10ኪ.ሜ አዋቂ ወንዶች 6፣ በ10ኪ.ሜ አዋቂ ሴቶች 6፣ በ8ኪ.ሜ ወጣት ወንዶች 6፣ በ6ኪ.ሜ ወጣት ሴቶች 3፣ በድብልቅ ሪሌ የሚወዳደሩ ሲሆን፤በድብልቅ ሪሌ በ8ኪ.ሜ ወጣት ወንዶችና በ6ኪ.ሜ ወጣት ሴቶች በግል ከመሳተፍ በዘለለ ውጤት አይጠበቅበትም፤ከላይ እንደተጠቀሠው በወንድና በሴት የመወዳደር ዕድል ቢኖርም ከመሳተፍ በዘለለ ውጤቱ የሚመዘገብ እንደማይሆን ተረጋግጧል።
በውድድሩ አሸናፊ ለሚሆኑ አትሌቶች አወዳዳሪው አካል የገንዘብ ሽልማት የመደበ ሲሆን በግልም፣በቡድንምጨአሸናፊ በመሆን የሜዳልያ ባለቤት ለሚሆኑ በግል ለወርቅ 30ሺ፣ለብር 15ሺ፣ለነሐስ 10ሺ፣4ኛ ለሚወጣ 7ሺ፣ለ5ኛ 5ሺ፣ለ6ኛ 3ሺ የገንዘብ ሽልማት የሚያገኙ ሲሆን በቡድን አሸናፊ ለሚሆኑ ደግሞ ለወርቅ 20ሺ፣ለብር 16ሺ፣ለነሐስ 12ሺ፣4ኛ ለሚወጣ 10ሺ፣ለ5ኛ 8ሺ፣ለ6ኛ 7ሺ የአሜሪካን ዶላር የገንዘብ ሽልማት እንደሚበረከት ታውቋል።
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
♦️በዓለም አገር አቋራጭ ሻምፒዮና ላይ የሚሳተፈው
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ቡድን የኮኔክሽን ችግሮቹ ተፈተው ምሽት 4:00 ወደ አትላንታ ✈️ ይበራሉ ✈️
♦️ከአታላንታ ወደ ታላሃስ በአውቶቡስ ከ4 ሠዓት በላይ የሚጓዙ ይሆናል
♦️በ8ኪ.ሜ ወጣት ወንዶችና በ6ኪ.ሜ ወጣት ሴቶች በግል ከመሳተፍ በዘለለ ውጤት አይጠበቅበትም
♦️በግል አሸናፊ ለሚሆን 30ሺ፣በቡድን 20ሺ ዶላር ለሽልማት ተመድቧል
ለዓመታት ሽርጉድ ስትል የቆየችው የአሜሪካ ፍሎሪዳዋ ታላሃስ ከተማ የፊታችን ጃንዋሪ 10 46ኛውን የአለም አገር አቋራጭ ሻምፒዮና በልዩ ድምቀት ታስተናግዳለች።
በ1984 ኒውዮርክ፣በ1992 ቦስተን የአለም አገር አቋራጭ ውድድርን ካስተናገደች ከ30 ዓመታት በኃላ የማስተናገድ ዕድል ያገኘችው አሜሪካ ከ60 በላይ ሀገራት የተውጣጡ 500 አትሌቶች የሚሳተፉበትን የአንድ ቀን ውድድር ለማስተናገድ ሽርጉዷን አጠናቃ የእንግዶቿን መምጣት በመጠባበቅ ላይ ትገኛለች።
በውድድሩ ለአሸናፊነት ግምት ከተሠጣቸው ሀገሮች አንዷ የሆነችው ኬንያ የልዑካን ቡድናን ከፋፍላ ወደ ፍሎሪዳ የሸኘች ሲሆን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድንም ለ47 ቀናት በቀነኒሳ ሆቴል ሱሉልታ ሲያደረገው የነበረው ዝግጅትን አጠናቆ ትናንት(ዓርብ)የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር የሆኑት ክቡር አቶ መኪዩ መሀመድ በተገኙበት የክብር ሽኝት የተደረገለት ሲሆን ዛሬ ምሽት 4:00 ወደ ውድድሩ ስፍራ የሚጓዝ ይሆናል።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በቂ የዝግጅት ጊዜ(47 ቀን)በመስጠት፣ከረዥም ዓመት በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከአዲስ አበባ ከተማ ውጪ በሱሉልታ ቀነኒሳ ሪዞርት ሆቴል እንዲዘጋጁ በማድረግና በደማቅ የክብር አሸኛኘት ማድረጉ ብዙዎች ፌዴሬሽኑን እንዲያመሠግኑ አስገድዷል።
የአሜሪካ ኤምባሲ የቪዛ ማመልከቻ ጥያቄያቸው ተቀባይነት በማጣቱ ምክንያት በቪዛ ችግር ሲታመስ የቆየው የአትሌቲክስ ቡድን አባላቱ በአሁን ሠዓት በቦሌ ኢንተርናሽናል አውሮፕላን ማረፊያ ለጉዞ አስፈሊጊ የሆነውን የኢሚግሬሽን ፕሮሰስ እያከናወኑ ሲሆን ምሽት 4:30 ከአዲስ አበባ በቀጥታ አታላንታ እንደሚበሩ የፌዴሬሽኑ ታማኝ የመረጃ ምንጮቻችን ገልፀውልናል።
የኢትዮጵያ የአትሌቲክስ ቡድን ከጉዞ ጋር በተለይ ከ flight ✈️ ኮኔክሽን ጋር በተያያዘ ችግር ገጥሞት በተለይ ከአታላንታ ወደ ታላሃስ በረራ ባለመገኘቱ ቡድኑን በሶስት ግሩፕ ከፋፍሎ የመውሠድ ዕቅድ ታቅዶ የነበረ ሲሆን በመጨረሻ ከአየር መንገዱ ጋር በተደረገ ንግግር ቡድኑ ተበታትኖ ከመሄድ በአንድነት ቢሄዱና አታላንታ ላይ ኮኔክሽን ፍላይት ባይኖርም በአውቶቡስ መሄድ እንችላለን የሚለው ሃሳብ ገዥ አግኝቶ ሁሉም የቡድኑ አባላት ከአዲስ አበባ አታላንታ ከአታላንታ የውድድሩ ስፍራ ወደ ሆነችው ታላሃስ Apalachee Regional Park በተዘጋጀላቸው ደረጃውን የጠበቀ አውቶብስ ከ4:30-6:00 የሚፈጅ የመኪና ጉዞ በማድረግ ወደተዘጋጀላቸው ደብል ትሪ ሆቴል እንደሚያመሩ ተረጋግጧል።
በሶስት ግሩፕ ተከፋፍሎ ሁሉም አንድ ላይ የመጓዛቸው ውሳኔ ብዙዎችን ያስደሠተ ሲሆን ከ4:00 እስከ 6:00 የፈጀ የአውቶቡስ ጉዞ ማድረጋቸው የድካም ስሜትን ያመጣል የሚል ስጋትን ከወዲሁ በብዙዎች እንዲፈጠር አድርጓል።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከአትሌቶችና ከአሠልጣኞች በተጨማሪ ለአንድ ቀን ውድድር ሁለት የቡድን መሪ እንዲሁም ሁለት ጊዜ ቪዛ በተከለከሉት የፅ/ቤት ኃላፊው አመንሲሳ ከበደ(ዶ/ር) ምትክ ቡድኑን እንዲያግዝ በሚል ከስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው ፕሬዝዳንቱ ኮማንደር አትሌት ስለሺ ስህን በመጨረሻ ሠዓት በጉዞው የተካተተ ሲሆን ሌሎቹ ዛሬ ምሽት ፕሬዝዳንቱ ደግሞ በነገው ዕለት ወደ ፍሎሪዳ ታላሃስ እንደሚያመሩ ታውቋል።
ከዚሁ ከአሜሪካው ታላሃስ ዜና ሳንወጣ በአሁን ሠዓት አሜሪካ የሚገኘው የአገር አቋራጩ ጀግና አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ቡድኑን በአካል ተገኝቶ እንዲያበረታታ ጥረት እየተደረገ ሲሆን የቡድኑ አባል እንዲሆንና አትሌቶቹን እንዲያበረታታ አስፈላጊው ፕሮሠስ እንደተደረገለትም ወደስፍራው ከሚጓዙ ታማኝ የመረጃ ምንጮቻችን ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል።
በ46ኛው የአለም አገር አቋራጭ ውድድር ላይ የምትሳተፈው ሀገራችን በ10ኪ.ሜ አዋቂ ወንዶች 6፣ በ10ኪ.ሜ አዋቂ ሴቶች 6፣ በ8ኪ.ሜ ወጣት ወንዶች 6፣ በ6ኪ.ሜ ወጣት ሴቶች 3፣ በድብልቅ ሪሌ የሚወዳደሩ ሲሆን፤በድብልቅ ሪሌ በ8ኪ.ሜ ወጣት ወንዶችና በ6ኪ.ሜ ወጣት ሴቶች በግል ከመሳተፍ በዘለለ ውጤት አይጠበቅበትም፤ከላይ እንደተጠቀሠው በወንድና በሴት የመወዳደር ዕድል ቢኖርም ከመሳተፍ በዘለለ ውጤቱ የሚመዘገብ እንደማይሆን ተረጋግጧል።
በውድድሩ አሸናፊ ለሚሆኑ አትሌቶች አወዳዳሪው አካል የገንዘብ ሽልማት የመደበ ሲሆን በግልም፣በቡድንምጨአሸናፊ በመሆን የሜዳልያ ባለቤት ለሚሆኑ በግል ለወርቅ 30ሺ፣ለብር 15ሺ፣ለነሐስ 10ሺ፣4ኛ ለሚወጣ 7ሺ፣ለ5ኛ 5ሺ፣ለ6ኛ 3ሺ የገንዘብ ሽልማት የሚያገኙ ሲሆን በቡድን አሸናፊ ለሚሆኑ ደግሞ ለወርቅ 20ሺ፣ለብር 16ሺ፣ለነሐስ 12ሺ፣4ኛ ለሚወጣ 10ሺ፣ለ5ኛ 8ሺ፣ለ6ኛ 7ሺ የአሜሪካን ዶላር የገንዘብ ሽልማት እንደሚበረከት ታውቋል።
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
6 months ago
በሰሜን አሜሪካ አትላንታ በየአመቱ በምሳሌ ግብረሰናይ ድርጅት የሚከናወነው 'ምሳሌ አዋርድ ' የ2025 የሽልማት ስነ ስርአቱ በዘመናት መካከል ሳይሰለች የዘለቀውን ድምፃዊ ፀሐዬ ዮሃንስ በዘመን ተሻጋሪ ዘርፍ የአመቱ ተሸላሚ አድርጎታል።
Sponsored by
Surafel
6 months ago
" በሙያዬ ምሳሌ ሆኜ ከተገኘሁ የነ ጥላሁንና ማህሙድ ልፋት ከንቱ አልቀረም ማለት ነው"
ተወዳጁ ድምፃዊ ፀሐዬ ዮሐንስ
#ethiopia | በሰሜን አሜሪካ አትላንታ በየአመቱ በምሳሌ ግብረሰናይ ድርጅት የሚከናወነው 'ምሳሌ አዋርድ ' የ2025 የሽልማት ስነ ስርአቱን በከፍተኛ ድምቀት አከናውኗል ።
በ12 የሽልማት ዘርፎች ለአገራቸውና ለህዝባቸው የሚታይ አርአያነት ያለው ስራ የሰሩ ታላላቅ ሰዎች የተሸለሙ ሲሆን ከነዚህም መካከል ከመጀመሪያዎቹ የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ፕሮፌሰሮች አንዱ የሆኑት እና በከፍተኛ ምርምርና ውጤታቸው አለም አቀፍ ሽልማቶችን የተቀዳጁት ፕሮፌሰር መሰለ ገደቡ አንዱ ናቸው። ፕሮፌሰር መሠለ ባስተማሯቸው ዶክተሮች ታጅበው የክብር ካባ ሲጎናፀፉ ለኔ ትልቁ ክብር ይህ ነው ብለዋል።
በሰሜን አሜሪካ ተፅዕኖአቸው እየጎሉ ከመጡ ሚዲያዎች መካከል የሆነው፣ የኛ ሰው በአሜሪካ ጨምሮ ለዜጎችና ለሀበሻ የንግ ተቋማት ማንሰራራት የጠቀሙ ዘገባዎችን በመስራት የሚታወቀው ቸቤ ሚዲያ በኪነጥበብ፣ ስፖርትና ሚዲያ ዘርፍ የአመቱ የምሳሌ ተሸላሚ ሆኗል።
የተቋሙ መስራች ኤርሚያስ አባተ (ቸቤ) በስልክ ከመቅረፅ ጀምሮ አሁን የተደራጀ ሚዲያ እስከመሆን ብዙ ዋጋ እንደከፈለ ገልፆ አብረው የሚሰሩ አጋሮቹ፣ ተከታዮቹና ስፖንሰሮቹ ለውጤታማ ጉዟቸው ሚናቸው የጎላ መሆኑን ገልፆል።
አትላንታዎች የዘመናዊ ሙዚቃ ባለውለታ፣ በዘመናት መካከል ሳይሰለች የዘለቀውን ድምፃዊ ፀሐዬ ዮሃንስ በዘመን ተሻጋሪ ዘርፍ የአመቱ ተሸላሚ አድርገውታል።
የክብር ካባውንም በአንጋፋው ድምፃዊ ተሾመ አሰግድ እጅ ደርቧል።
ፀሀዬ ከሽልማቱ በኋላ በእድገቱ እናትና አባቱ ምሳሌዎቹ መሆናቸውን ገልፆ በሙያዬ ለምሳሌነት ከበቃሁ የነ ጥላሁን ገሰሰ እና መሀሙድ አህመድ ልፋት ከንቱ አልቀረም ማለት ነው ብሏል።
የመጀመሪያ ሙዚቃው 'ማንበብና መፃፍ' ዘመን ተሻጋሪ ስራው 'ከሷ ጋር እያለሁ' ሀገሩን ያወደሰበት ስራዎቹን በመድረኩ በሚያስደንቅ ሁኔታ አቅርቧል ።
የምሳሌ ግብረሰናይ ድርጅት ፕሬዝዳንት አቶ ዳግም መንበረ ምሳሌ በቀጣይ ተግባራቶች እያደገ እንደሚመጣ ገልፀው ለስኬቱ የተባበሯቸውን ሁሉ አመስግነዋል።
ካስትሮ - ከአትላንታ 🇺🇸
ተወዳጁ ድምፃዊ ፀሐዬ ዮሐንስ
#ethiopia | በሰሜን አሜሪካ አትላንታ በየአመቱ በምሳሌ ግብረሰናይ ድርጅት የሚከናወነው 'ምሳሌ አዋርድ ' የ2025 የሽልማት ስነ ስርአቱን በከፍተኛ ድምቀት አከናውኗል ።
በ12 የሽልማት ዘርፎች ለአገራቸውና ለህዝባቸው የሚታይ አርአያነት ያለው ስራ የሰሩ ታላላቅ ሰዎች የተሸለሙ ሲሆን ከነዚህም መካከል ከመጀመሪያዎቹ የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ፕሮፌሰሮች አንዱ የሆኑት እና በከፍተኛ ምርምርና ውጤታቸው አለም አቀፍ ሽልማቶችን የተቀዳጁት ፕሮፌሰር መሰለ ገደቡ አንዱ ናቸው። ፕሮፌሰር መሠለ ባስተማሯቸው ዶክተሮች ታጅበው የክብር ካባ ሲጎናፀፉ ለኔ ትልቁ ክብር ይህ ነው ብለዋል።
በሰሜን አሜሪካ ተፅዕኖአቸው እየጎሉ ከመጡ ሚዲያዎች መካከል የሆነው፣ የኛ ሰው በአሜሪካ ጨምሮ ለዜጎችና ለሀበሻ የንግ ተቋማት ማንሰራራት የጠቀሙ ዘገባዎችን በመስራት የሚታወቀው ቸቤ ሚዲያ በኪነጥበብ፣ ስፖርትና ሚዲያ ዘርፍ የአመቱ የምሳሌ ተሸላሚ ሆኗል።
የተቋሙ መስራች ኤርሚያስ አባተ (ቸቤ) በስልክ ከመቅረፅ ጀምሮ አሁን የተደራጀ ሚዲያ እስከመሆን ብዙ ዋጋ እንደከፈለ ገልፆ አብረው የሚሰሩ አጋሮቹ፣ ተከታዮቹና ስፖንሰሮቹ ለውጤታማ ጉዟቸው ሚናቸው የጎላ መሆኑን ገልፆል።
አትላንታዎች የዘመናዊ ሙዚቃ ባለውለታ፣ በዘመናት መካከል ሳይሰለች የዘለቀውን ድምፃዊ ፀሐዬ ዮሃንስ በዘመን ተሻጋሪ ዘርፍ የአመቱ ተሸላሚ አድርገውታል።
የክብር ካባውንም በአንጋፋው ድምፃዊ ተሾመ አሰግድ እጅ ደርቧል።
ፀሀዬ ከሽልማቱ በኋላ በእድገቱ እናትና አባቱ ምሳሌዎቹ መሆናቸውን ገልፆ በሙያዬ ለምሳሌነት ከበቃሁ የነ ጥላሁን ገሰሰ እና መሀሙድ አህመድ ልፋት ከንቱ አልቀረም ማለት ነው ብሏል።
የመጀመሪያ ሙዚቃው 'ማንበብና መፃፍ' ዘመን ተሻጋሪ ስራው 'ከሷ ጋር እያለሁ' ሀገሩን ያወደሰበት ስራዎቹን በመድረኩ በሚያስደንቅ ሁኔታ አቅርቧል ።
የምሳሌ ግብረሰናይ ድርጅት ፕሬዝዳንት አቶ ዳግም መንበረ ምሳሌ በቀጣይ ተግባራቶች እያደገ እንደሚመጣ ገልፀው ለስኬቱ የተባበሯቸውን ሁሉ አመስግነዋል።
ካስትሮ - ከአትላንታ 🇺🇸
6 months ago
በአሜሪካ መወለድ ብቻውን አንድ ሺህ ዶላር ያስገኛል
ለአሜሪካ ህጻናት የተከፈተው ''ትራምፕ አካውንት"
ከመጪው የፈረንጆቹ ሐምሌ ወር 2026 የአሜሪካ የነጻነት ቀን ጀምሮ፣ ለሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት በአሜሪካ የሚወለዱ ህጻናት ''ትራምፕ አካውንት" በተሰኘ የባንክ ሂሳብ፣አንድ ሺህ ዶላር ይበረከትላቸዋል።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ፊርማቸውን በማኖር ባስጀመሩት በዚህ መርሐ ግብር መሰረት፣ በመገባደድ ላይ ባለው የፈረንጆቹ 2025 የተወለደች አንዲት ህጻን በመጪው ሐምሌ አንድ ሺህ የአሜሪካ ዶላር የያዘ የባንክ ደብተር ይኖራታል።
በመርሐ ግብሩ መሰረት፣ለእዚች ልጅ፣ወላጆቿ፣ ቤተሰቦቿ ወይንም ሌሎች መሥሪያ ቤቶች በባንክ ቁጥሯ፣በዓመት እስከ አምስት ሺህ ዶላር ድረስ ሊቆጥቡላት ይችላሉ። በዚህ ስሌትም፣ ይህች ልጅ 18 ዓመት ሲሆናት፣ 170 ሺህ ዶላር ይኖራታል፡፡
''ይሄ የትራምፕ አካውንት፣ከ18 አመት በታች ያሉ ህጻናትን ይመለከታል። አካውንቱ በገንዘብ ግምጃ ቤት የግብር ክፍል የሚከናወን ሲሆን፤ በዚህ ዓመት 2025 ከጥር አንድ ቀን ጀምሮ፣ አሜሪካ ውስጥ ለተወለዱ ወይም የአሜሪካ ዜግነት ላላቸው ህጻናት አንድ ሺ ዶላር የሚሰጥ ነው። ይህ አንድ ሺህ ዶላር በባንክ ሂሳብ ቁጥራቸው የሚገባ ነው። እስከ 2028 ድረስ የሚቀጥል ነው፤በትራምፕ ዘመን ማለት ነው።" ሲሉ በአትላንታ ጆርጂያ የታክስ ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ አስገዶም ተመልሶ ለዶቸ ቬለ አብራርተዋል፡፡
አቶ አስገዶም እንደሚሉት፣ልጆቹ 18 ዓመት እስኪሞላቸው ድረስ፣ይህንን ገንዘብ ከባንክ ሂሳባቸው ማውጣት አይችሉም። ''18 ዓመት እስኪሞላቸው፣አይነካም፤ማውጣት አይችሉም። እና እያደገ እያደገ ይሄዳል።18 ዓመት ሲሞላቸው፣በቂ ገንዘብ ይኖራቸዋል የሚል እሳቤ ነው።'' ብለዋል፡፡
seledadotio
seledadotio
ለአሜሪካ ህጻናት የተከፈተው ''ትራምፕ አካውንት"
ከመጪው የፈረንጆቹ ሐምሌ ወር 2026 የአሜሪካ የነጻነት ቀን ጀምሮ፣ ለሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት በአሜሪካ የሚወለዱ ህጻናት ''ትራምፕ አካውንት" በተሰኘ የባንክ ሂሳብ፣አንድ ሺህ ዶላር ይበረከትላቸዋል።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ፊርማቸውን በማኖር ባስጀመሩት በዚህ መርሐ ግብር መሰረት፣ በመገባደድ ላይ ባለው የፈረንጆቹ 2025 የተወለደች አንዲት ህጻን በመጪው ሐምሌ አንድ ሺህ የአሜሪካ ዶላር የያዘ የባንክ ደብተር ይኖራታል።
በመርሐ ግብሩ መሰረት፣ለእዚች ልጅ፣ወላጆቿ፣ ቤተሰቦቿ ወይንም ሌሎች መሥሪያ ቤቶች በባንክ ቁጥሯ፣በዓመት እስከ አምስት ሺህ ዶላር ድረስ ሊቆጥቡላት ይችላሉ። በዚህ ስሌትም፣ ይህች ልጅ 18 ዓመት ሲሆናት፣ 170 ሺህ ዶላር ይኖራታል፡፡
''ይሄ የትራምፕ አካውንት፣ከ18 አመት በታች ያሉ ህጻናትን ይመለከታል። አካውንቱ በገንዘብ ግምጃ ቤት የግብር ክፍል የሚከናወን ሲሆን፤ በዚህ ዓመት 2025 ከጥር አንድ ቀን ጀምሮ፣ አሜሪካ ውስጥ ለተወለዱ ወይም የአሜሪካ ዜግነት ላላቸው ህጻናት አንድ ሺ ዶላር የሚሰጥ ነው። ይህ አንድ ሺህ ዶላር በባንክ ሂሳብ ቁጥራቸው የሚገባ ነው። እስከ 2028 ድረስ የሚቀጥል ነው፤በትራምፕ ዘመን ማለት ነው።" ሲሉ በአትላንታ ጆርጂያ የታክስ ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ አስገዶም ተመልሶ ለዶቸ ቬለ አብራርተዋል፡፡
አቶ አስገዶም እንደሚሉት፣ልጆቹ 18 ዓመት እስኪሞላቸው ድረስ፣ይህንን ገንዘብ ከባንክ ሂሳባቸው ማውጣት አይችሉም። ''18 ዓመት እስኪሞላቸው፣አይነካም፤ማውጣት አይችሉም። እና እያደገ እያደገ ይሄዳል።18 ዓመት ሲሞላቸው፣በቂ ገንዘብ ይኖራቸዋል የሚል እሳቤ ነው።'' ብለዋል፡፡
seledadotio
seledadotio
7 months ago
በአሜሪካ ቨርጂኒያ ስቴት የAlexandria city Nov 30 የወንድወሰን ከበደ ቀን ተብሎ ተሰይሟል
ጋዜጠኛና መድረክ መሪ ወንድወሰን ከበደ በአሜሪካ ዕውቅና ተቀብሏል
ከዕዝራ እጅጉ(ተወዳጅ ሚድያ)
#ethiopia | በአሜሪካ ቨርጂኒያ ስቴት የAlexandria city Nov 30 የወንድወሰን ከበደ ቀን ተብሎ ተሰይሟል ። ወንድወሰን ከበደ በሚድያ ሥራ ላበረከተው አስተዋፅኦ ነው ክፍለ ግዛቱ ይህን ትልቅ ክብር የሰጠው። ወንድወሰን ከበደ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ከተወዳጅ ሚድያ ጋር ባደረገው ቆይታ ይህ ትልቅ ዕውቅና መሆኑን ተናግሯል። የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ መዝገበ አእምሮ ቅፅ ሁለት( ከ6ወር በፊት የታተመው) የወንድወሰንን ታሪክ የሰነደ ሲሆን እኛም ዕውቅናውን አስመልክቶ የሙያ ታሪኩን እንደሚከተለው እናቀርብላችኋለን ።
እንኳን ለዚህ ክብር አበቃህ ወንዴ!!!!
ትውልድ ልጅነትና ትምህርት
ወንድወሰን ከበደ በ1964 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ ሩፋኤል ነው የተወለደው ከአንድ ዓመቱ ጀምሮ እስከ አራተኛ ክፍል ድረስ ቀጨኔ መድኃኔዓለም መዳረሻ በችሎት ሰፈር ነው ያደገው፡፡
ከጀማሪ ክፍል እስከ አራተኛ ክፍል በቤተልሔም ትምህርት ቤት ተከታትሏል፡፡ ከዚያም ቤተሰቡ ወደ አዲሱ ቄራ ከገቡ በኋላ ከ5ኛ እስከ 7ኛ ክፍል ፊት አውራሪ ላቀ አድገህ /ጎፋ/ ትምህርት ቤት ሲማር 8ኛ ክፍል ነፃነት ጮራ ትምህርት ቤት ተምሯል፡፡
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ያጠናቀቀው በንፋስ ስልክ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ነው፡፡
የከፍተኛ ደረጃ ትምህርቱ በቴክኒክ ላይ ያተኮረ ሲሆን ከአዲስ ቴክኒክ ኮሌጅ በጄኔራል መካኒክስ በዲፕሎማ ተመርቋል፣ ከኦ፡አይ፡ሲ፡ኢ ኢንተርናሽናል በከተማ ማስተር ፕላንና በፕላቢንግ ኢንስታሌሽን በሠርተፍኬት ሲመረቅ፣ በአውቶ መካኒክስ ርቀት ትምህርት ቤት ሠርተፍኬት አግኝቷል፡፡
ወደ ሥራ ዓለም
መደበኛ የሥራ ሕይወቱን በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል በሚዘጋጁ የንግድ ትርዒቶች፣ ባዛሮችና ፌስቲቫሎች መድረክ በመምራት፣ በማዘጋጀት፣ በማማከርና በማስተባበር፣ የጀመረ ሲሆን፣ ከዚያም ጎን ለጎን በሬዲዮ ፋና በስፖርት ጋዜጠኝነትና በዜና አንባቢነት ተቀጥሮ ለሰባት ዓመታት አገልግሏል፡፡
በስፖርት ጋዜጠኝነት ከዓለም አቀፍ ኦሊምፒክ ኮሚቴ /IOC/ ያዘጋጀውን ሥልጠና ወስዶ ሠርተፍኬት ተቀብሏል፡፡
በርካታ የጋዜጠኝነትና የኮሙዩኒኬሽን ሥልጠናዎችን በሚገባ ተከታትሎ ሠርተፍኬቶችን አግኝቷል፡፡
"ጉራማይሌ" የተሰኘ አጫጭር ድራማዎችና የባህል ሙዚቃዎችን የያዘ ቪዲዮ ፕሮዲዩስ አድርጓል፡፡
WBK የተሰኘ የማስታወቂያ ድርጅት አቋቁሞ በርካታ የቴሌቪዥንና የሬዲዮ ማስታወቂያዎችንና የድርጅቶች ዶክመንተሪ ሠርቷል፡፡
እጅግ በርካታ አገር አቀፍና ዓለም አቀፍ መድረኮችን በኤግዚቢሽን ማዕከል፣ በመስቀል አደባባይና በሐዋሳ ከተማና በተለያዩ ሥፍራዎች መርቷል፡፡
የፀጋዬ እሸቱ የሙዚቃ ወዳጆች ማኅበር በሚል ለትርፍ ያልተቋቋመ ማኅበር መሥርቶ ከሁለት ሺሕ መነሻ አድርጎ እስከ አሥር ሺሕ በሚጠጉ ወላጅ አልባ ሕፃናትንና ደካማ ወገኖችን አሰባስቦ ለበዓላት በመመገብ፣ የተማሪዎችን የትምህርት ወጪና ራሳቸውን የሚችሉበትን መንገድ አመቻችቷል፡፡
የኪነ ጥበብ ዝንባሌ
በልጅነቱ ዓለም አቀፍ ሬዲዮ (ብሥራተ ወንጌል) ለገዳዲ ኢትዮጵያና የኢትዮጵያ ሬዲዮ ፕሮግራሞችንና ዜናዎችን ይከታተል የነበረ ሲሆን የሃይስኩል ተማሪ ሳለ በሚኒሚዲያ ውስጥ አገልግሏል፣ ከዚያም ለሬዲዮኖች መጣጥፎችን በመላክ ተሳትፎ ያደርግ ነበር፡፡
ወንድወሰን ከበደ ባለትዳርና ሁለት የሃይስኩል ተማሪ ልጆች ያለው ሲሆን ነዋሪነቱ በሰሜን አሜሪካ በሜሪላንድ ግዛት ነው፡፡
ወንድወሰን ከበደ ኑሮውን በአሜካን አገር ካደረገ ሃያ ዓመት ሆኖታል፡፡ በዋሽንግተን ዲሲ፣ በቨርጂኒያ፣ በሜሪላንድ፣ በሲያትል፣ በሎስአንጀለስ፣ በአትላንታ፣ በዳላስ፣ በዴንቨር፣ በተካሄዱ ትልልቅ መድረኮችን በመምራት፣ በማዘጋጀትና በማስተባበር ሠርቷል፡፡ አሁንም በመሥራት ላይ ይገኛል፡፡
በሰሜን አሜሪካ ብቸኛ የስፖርት ሬዲዮ በመክፈት ልዩ ሬዲዮ በሚል ለአምስት ዓመታት አገልግሏል፡፡
ኢትዮጵያ ናሽናል ብሮድካስቲንግ ሰርቪስ /ENBS/ የቴሌቪዥን ፕሮግራም ከሌሎች ባልደረቦች ጋር በማቋቋም በአሜሪካን የቴሌቪዥን ቻናል WHUT ያስተላልፍ ነበር፡፡
ሰንደቅ ሚዲያ የተሰኘ ከአንድ ባልደረባው በማቋቋም ለሁለት ዓመታትም ሠርቷል፡፡ በENT ሚዲያ ላይም ለተወሰኑ ወራቶች አገልግሏል፡፡
ከ ስድስት ወር በፊትም መድረክ ሲመራ ያሰባሰባቸውን ምስሎች በመፅሀፍ ፅፎ አስመርቋል ።
መጽሐፍ
- በቅርቡ የኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ከ1980ዎቹ እስከ 1990ዎቹ የሚል በበርካታ ምስሎችና ታሪኮች የተዘጋጀ መጽሐፍ ለአንባቢ ያበረክታል፡፡
- ግለ ታሪኩ በተመለከተ ቀጣይ የሚኖረው መጽሐፍ ነው፡፡
በቅርቡ
- ትዳር በአሜሪካ የተሰኘ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ
- ከባልደረቦቹ ጋር እየተቋቋም ባለ አዲስ ሚዲያ በልዩ አቀራረብ ይመጣል፡፡
- 1980ዎቹ/1990ዎቹ የኢትዮጵያ ሙዚቃ በተመለከተ ልዩ ተከታታይ የቪዲዮ ቅንብር በማዘጋጀት ላይ ይገኛል፡፡
ጋዜጠኛና መድረክ መሪ ወንድወሰን ከበደ በአሜሪካ ዕውቅና ተቀብሏል
ከዕዝራ እጅጉ(ተወዳጅ ሚድያ)
#ethiopia | በአሜሪካ ቨርጂኒያ ስቴት የAlexandria city Nov 30 የወንድወሰን ከበደ ቀን ተብሎ ተሰይሟል ። ወንድወሰን ከበደ በሚድያ ሥራ ላበረከተው አስተዋፅኦ ነው ክፍለ ግዛቱ ይህን ትልቅ ክብር የሰጠው። ወንድወሰን ከበደ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ከተወዳጅ ሚድያ ጋር ባደረገው ቆይታ ይህ ትልቅ ዕውቅና መሆኑን ተናግሯል። የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ መዝገበ አእምሮ ቅፅ ሁለት( ከ6ወር በፊት የታተመው) የወንድወሰንን ታሪክ የሰነደ ሲሆን እኛም ዕውቅናውን አስመልክቶ የሙያ ታሪኩን እንደሚከተለው እናቀርብላችኋለን ።
እንኳን ለዚህ ክብር አበቃህ ወንዴ!!!!
ትውልድ ልጅነትና ትምህርት
ወንድወሰን ከበደ በ1964 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ ሩፋኤል ነው የተወለደው ከአንድ ዓመቱ ጀምሮ እስከ አራተኛ ክፍል ድረስ ቀጨኔ መድኃኔዓለም መዳረሻ በችሎት ሰፈር ነው ያደገው፡፡
ከጀማሪ ክፍል እስከ አራተኛ ክፍል በቤተልሔም ትምህርት ቤት ተከታትሏል፡፡ ከዚያም ቤተሰቡ ወደ አዲሱ ቄራ ከገቡ በኋላ ከ5ኛ እስከ 7ኛ ክፍል ፊት አውራሪ ላቀ አድገህ /ጎፋ/ ትምህርት ቤት ሲማር 8ኛ ክፍል ነፃነት ጮራ ትምህርት ቤት ተምሯል፡፡
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ያጠናቀቀው በንፋስ ስልክ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ነው፡፡
የከፍተኛ ደረጃ ትምህርቱ በቴክኒክ ላይ ያተኮረ ሲሆን ከአዲስ ቴክኒክ ኮሌጅ በጄኔራል መካኒክስ በዲፕሎማ ተመርቋል፣ ከኦ፡አይ፡ሲ፡ኢ ኢንተርናሽናል በከተማ ማስተር ፕላንና በፕላቢንግ ኢንስታሌሽን በሠርተፍኬት ሲመረቅ፣ በአውቶ መካኒክስ ርቀት ትምህርት ቤት ሠርተፍኬት አግኝቷል፡፡
ወደ ሥራ ዓለም
መደበኛ የሥራ ሕይወቱን በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል በሚዘጋጁ የንግድ ትርዒቶች፣ ባዛሮችና ፌስቲቫሎች መድረክ በመምራት፣ በማዘጋጀት፣ በማማከርና በማስተባበር፣ የጀመረ ሲሆን፣ ከዚያም ጎን ለጎን በሬዲዮ ፋና በስፖርት ጋዜጠኝነትና በዜና አንባቢነት ተቀጥሮ ለሰባት ዓመታት አገልግሏል፡፡
በስፖርት ጋዜጠኝነት ከዓለም አቀፍ ኦሊምፒክ ኮሚቴ /IOC/ ያዘጋጀውን ሥልጠና ወስዶ ሠርተፍኬት ተቀብሏል፡፡
በርካታ የጋዜጠኝነትና የኮሙዩኒኬሽን ሥልጠናዎችን በሚገባ ተከታትሎ ሠርተፍኬቶችን አግኝቷል፡፡
"ጉራማይሌ" የተሰኘ አጫጭር ድራማዎችና የባህል ሙዚቃዎችን የያዘ ቪዲዮ ፕሮዲዩስ አድርጓል፡፡
WBK የተሰኘ የማስታወቂያ ድርጅት አቋቁሞ በርካታ የቴሌቪዥንና የሬዲዮ ማስታወቂያዎችንና የድርጅቶች ዶክመንተሪ ሠርቷል፡፡
እጅግ በርካታ አገር አቀፍና ዓለም አቀፍ መድረኮችን በኤግዚቢሽን ማዕከል፣ በመስቀል አደባባይና በሐዋሳ ከተማና በተለያዩ ሥፍራዎች መርቷል፡፡
የፀጋዬ እሸቱ የሙዚቃ ወዳጆች ማኅበር በሚል ለትርፍ ያልተቋቋመ ማኅበር መሥርቶ ከሁለት ሺሕ መነሻ አድርጎ እስከ አሥር ሺሕ በሚጠጉ ወላጅ አልባ ሕፃናትንና ደካማ ወገኖችን አሰባስቦ ለበዓላት በመመገብ፣ የተማሪዎችን የትምህርት ወጪና ራሳቸውን የሚችሉበትን መንገድ አመቻችቷል፡፡
የኪነ ጥበብ ዝንባሌ
በልጅነቱ ዓለም አቀፍ ሬዲዮ (ብሥራተ ወንጌል) ለገዳዲ ኢትዮጵያና የኢትዮጵያ ሬዲዮ ፕሮግራሞችንና ዜናዎችን ይከታተል የነበረ ሲሆን የሃይስኩል ተማሪ ሳለ በሚኒሚዲያ ውስጥ አገልግሏል፣ ከዚያም ለሬዲዮኖች መጣጥፎችን በመላክ ተሳትፎ ያደርግ ነበር፡፡
ወንድወሰን ከበደ ባለትዳርና ሁለት የሃይስኩል ተማሪ ልጆች ያለው ሲሆን ነዋሪነቱ በሰሜን አሜሪካ በሜሪላንድ ግዛት ነው፡፡
ወንድወሰን ከበደ ኑሮውን በአሜካን አገር ካደረገ ሃያ ዓመት ሆኖታል፡፡ በዋሽንግተን ዲሲ፣ በቨርጂኒያ፣ በሜሪላንድ፣ በሲያትል፣ በሎስአንጀለስ፣ በአትላንታ፣ በዳላስ፣ በዴንቨር፣ በተካሄዱ ትልልቅ መድረኮችን በመምራት፣ በማዘጋጀትና በማስተባበር ሠርቷል፡፡ አሁንም በመሥራት ላይ ይገኛል፡፡
በሰሜን አሜሪካ ብቸኛ የስፖርት ሬዲዮ በመክፈት ልዩ ሬዲዮ በሚል ለአምስት ዓመታት አገልግሏል፡፡
ኢትዮጵያ ናሽናል ብሮድካስቲንግ ሰርቪስ /ENBS/ የቴሌቪዥን ፕሮግራም ከሌሎች ባልደረቦች ጋር በማቋቋም በአሜሪካን የቴሌቪዥን ቻናል WHUT ያስተላልፍ ነበር፡፡
ሰንደቅ ሚዲያ የተሰኘ ከአንድ ባልደረባው በማቋቋም ለሁለት ዓመታትም ሠርቷል፡፡ በENT ሚዲያ ላይም ለተወሰኑ ወራቶች አገልግሏል፡፡
ከ ስድስት ወር በፊትም መድረክ ሲመራ ያሰባሰባቸውን ምስሎች በመፅሀፍ ፅፎ አስመርቋል ።
መጽሐፍ
- በቅርቡ የኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ከ1980ዎቹ እስከ 1990ዎቹ የሚል በበርካታ ምስሎችና ታሪኮች የተዘጋጀ መጽሐፍ ለአንባቢ ያበረክታል፡፡
- ግለ ታሪኩ በተመለከተ ቀጣይ የሚኖረው መጽሐፍ ነው፡፡
በቅርቡ
- ትዳር በአሜሪካ የተሰኘ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ
- ከባልደረቦቹ ጋር እየተቋቋም ባለ አዲስ ሚዲያ በልዩ አቀራረብ ይመጣል፡፡
- 1980ዎቹ/1990ዎቹ የኢትዮጵያ ሙዚቃ በተመለከተ ልዩ ተከታታይ የቪዲዮ ቅንብር በማዘጋጀት ላይ ይገኛል፡፡
7 months ago
የአቶ መርዕድ በቀለ ጸሎተ ፍትሀት በቦሌ መድኃኔዓለም ካቴድራል
#ethiopia | አንጋፋው የሚድያ ሰው አቶ መርዕድ በቀለ ባለፈው ሳምንት ህዳር 6 ቀን 2018ዓ.ም በአትላንታ የቀብር ሥነ ሥርዓታቸው መፈፀሙ ይታወቃል።
አዲስ አበባ ለሚገኙ የሀዘኑ ተካፋዮች ደግሞ ቅዳሜ ህዳር 13 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ሰዓት በቦሌ መድኃኔዓለም ካቴድራል ጸሎተ ፍትሀት ይደረጋል።
በመሆኑም፣በዚሁ ዕለት በፀሎት ፍትሐት ሥነሥርዓቱ ላይ በመገኘት ቤተሰቡን ማፅናናት እንደሚቻል እንገልፃለን ።
#ethiopia | አንጋፋው የሚድያ ሰው አቶ መርዕድ በቀለ ባለፈው ሳምንት ህዳር 6 ቀን 2018ዓ.ም በአትላንታ የቀብር ሥነ ሥርዓታቸው መፈፀሙ ይታወቃል።
አዲስ አበባ ለሚገኙ የሀዘኑ ተካፋዮች ደግሞ ቅዳሜ ህዳር 13 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ሰዓት በቦሌ መድኃኔዓለም ካቴድራል ጸሎተ ፍትሀት ይደረጋል።
በመሆኑም፣በዚሁ ዕለት በፀሎት ፍትሐት ሥነሥርዓቱ ላይ በመገኘት ቤተሰቡን ማፅናናት እንደሚቻል እንገልፃለን ።
7 months ago
ስመ ጥሩ የሚድያ ሰው መርዕድ በቀለ በአትላንታ አረፈ
. በደርግ ጊዜ የማስታወቂያ ምክትል ሚኒስትር ነበር
ከዕዝራ እጅጉ (ተወዳጅ ሚድያ)
#ታሪክ በኢትዮጵያን ሄራልድ፣በየዛሬይቱ ኢትዮጵያ ጋዜጦች፣እንዲሁም በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በመምሪያ ኃላፊነት ያገለገለው አቶ መርዕድ በቀለ ትናንት ህዳር 4 2018 በአትላንታ ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል።
የደርግ ዘመን ማብቂያ ላይ የማስታወቂያ ምክትል ሚኒስትር የነበረው የሚድያ ሰው አቶ መርዕድ በሥነ ፅሁፍ ችሎታው የተመሠከረለት ነበር። የሕይወት ታሪኩ የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ "መዝገበ አእምሮ ቅፅ ሁለት ላይ የሰፈረለት አቶ መርዕድ በቀለ በ2016 በተደረገው የክብር ሽልማት የህይወት ዘመን ተሸላሚዎች ከእጩዎቹ አንዱ ነበር።
አቶ መርዕድ ተወዳጅ ሚድያ የሚያከናውናቸውን የስነዳ ሥራዎች የሚደግፍ ፣ የሚያበረታታ የቅርብ ሰው ሲሆን በህልፈቱም የተሰማንን ሀዘን እንገልጻለን። የካቲት 26 2018 ሲመጣ 80 ዓመቱን ይይዝ የነበረው አቶ መርዕድ ከሰዎች ጋር በቀላሉ የሚግባባ እና የፅሑፍ ሥራንም በጥንቃቄ የሚያከናውን ነበር። እኛም የህይወት ታሪኩን እንደሚከተለው እናቀርባለን።
ትውልድ እና ልጅነት
መርዕድ በቀለ በ1938 ዓ.ም. የካቲት 26 ቀን አዲስ አበባ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ተወለደ። አባቱ አቶ በቀለ ወ/ኪዳን የአብነት ትምህርት ቤት ገብቶ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት እንዲማር ፍላጎቱ ቢኖራቸውም፣ እናቱ ወ/ሮ ጽጌ ወርቅ ተክለ ጻዲቅ ግን ልጃቸው ከአጠገባቸው እንዳይርቅ በማሰብ በቤት ውስጥ መምህር ቀጥረው ፊደል ከቆጠረ በኋላ በአካባቢው በነበረው የየኔታ ትምህርት ቤት ገባ።
ትምህርት
በኋላም በአምኃ ደስታ የአንደኛ፣ በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት ደግሞ የኹለተኛ ደረጃ ትምህርቱን አጠናቀቀ። አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ገብቶ በውጭ ቋንቋዎች እና ሥነጽሑፍ በእንግሊዘኛ ቋንቋ በ1965 ዓ.ም. ተመረቀ።
ወደ ሥራ ዓለም
በዚያው ዓመት ነበር በቀድሞው ልዩ ካቢኔ ቢሮ በታላቁ ቤተመንግሥት ውስጥ የተቀጠረው። ልዩ ካቢኔ በነበረበት ወቅትም ዋና ሥራው ከተለያዩ የዓለም ዜና ምንጮች (Reuters, AFP, BBC… ወዘተ) ከሚሠራጩ ዜናዎች ውስጥ የተመረጡትን እየተረጎመ በአለቃው በኩል ለንጉሡ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ማቅረብ ነበር። ሆኖም በዚህ ሥራ ከሦስት ሳምንት በላይ አልዘለለም።
በወቅቱ የማስታወቂያ ሚኒስቴር ለኢትዮጵያን ሄራልድ እንግሊዘኛ ጋዜጣ የሪፖርተር ቅጥር ያወጣውን ፈተና አልፎ፥ የማታ ኤዲተር ሆኖ ሥራ ጀመረ። ብዙም ሳይቆይ ወደ ቀን ተዘዋወረ።
የህትመት ሚድያ
መርዕድ በ1967 ዓ.ም. ባገኘው የትምህርት ዕድል ወደ ሞስኮ አቅንቶ ነበር። በዚያም ለአንድ ዓመት ስለ ሶሻሊዝም ፅንሰ ሐሳብ ካጠና በኋላ ወደ አገሩ ተመልሶ በዚያው በኢትዮጵያን ሄራልድ በአዘጋጅነት ለተወሰኑ ዓመታት አገልግሏል። ቀጥሎም ወደ “የዛሬይቱ ኢትዮጵያ” ጋዜጣ በዋና አዘጋጅነት ዕድገት አግኝቶ እንዲሠራ ተደረገ። ብዙም ሳይቆይ ወደ አዲስ ዘመን ዕለታዊ ጋዜጣ በዕድገት ተዛውሮ በምክትል ዋና አዘጅነት ለኹለት ዓመታት ከሠራ በኋላ ዋና አዘጋጅ ሆኖ እንዲሠራ ተመደበ።
ከኢዜአ እስከ ምክትል ሚኒስትር
በሥራው ባሕርይ የተነሣ መርዕድ በተደጋጋሚ ‘‘ለጥያቄ ትፈለጋለህ’’ እየተባለ ወደ ደርግ ጽሕፈት ቤት ይጠራ ነበር። እንደ እኤአ 1975/76 ሁለት የደኅንነት ሰዎች ከመሥሪያ ቤቱ መጥተው ወደ ማዕከላዊ እስር ቤት ወሰዱት። ሁኔታው ነገሩ ለሕይወቱ እንደሚያሰጋው በመገንዘብ ከቦታው እንዲዛወር አለቃው የነበረውን ደራሲ በዓሉ ግርማን ደጋግሞ ይጠይቅ፣ ይወተውትም ጀመር። ውትወታው ተቀባይነት አግኝቶ በዕድገት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ሐላፊ ሆኖ ተዛወረ፡፡ እዚያ ለአንድ ዓመት እንደቆየ፥ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት መምሪያ ሐላፊ ሆኖ እንዲሠራ ተመደበ። ለኹለት ዓመታት ካገለገለ በኋላ፥ ከሀገር እስከወጣበት ጊዜ ድረስ የማስታወቂያ ምክትል ሚኒስትር ሆኖ አገልግሏል።
አበርክቶ
መርዕድ በሥራ ላይ በነበረበት ጊዜ በተለያዩ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ ስብሰባዎች ላይ ኢትዮጵያን በመወከል፣ አንዳንዴም በልኡካን ቡድን አባልነት ታድሟል። እ.ኤ.አ በ1990/91 መንግሥት ከሻዕቢያ ጋር የሰላም ውይይት በመጀመሪያ በአትላንታ ጆርጂያ በካርተር ማዕከል፣ ቀጥሎ ኹለተኛና ሦስተኛ ዙሮች በዋሽንግተንና በኬንያ ናይሮቢ በተካኼደበት ጊዜ የልኡካኑ ቃል አቀባይ ብቻ ሳይሆን የጋዜጠኞችን ቡድን በመምራት ተሳትፏል።
ከአለቆቹ ጋር በመነጋገር በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የCNN ሥርጭት አገልግሎት እንዲጀመር ያደረገውም እርሱ ነው። አዲስ ዘመን ዋና አዘጋጅ በነበረበት ጊዜ ታደሰ ውቤ ያዘጋጀው በነበረው የፍትሕ ዓምድ አማካኝነት በጊዜው አብዮታዊ ዘመቻ ኮሚቴ (አዘኮ) በሚባል ‘‘ተቋም’’ በየክፍለ ሀገሩ የታሰሩ ንጹሐን ዜጎች እንዲፈቱ አስችሏል።
በወቅቱ የግብፅ ፕሬዚዳንት አንዋር ሳዳት ወደ ሥልጣን የመጡበትን 10ኛ ዓመት በዓል ላይ ለመታደም ከሌሎች ባልደረቦች ጋር ወደ ካይሮ ያቀና ሲኾን፥ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት መምሪያ ሐላፊ በነበረበት ጊዜም የአፍሪካ ዜና አገልግሎት PANA በአዲስ አበባ ሲቋቋም፣ በኋላም በሴኔጋል ዳካር ጽሕፈት ቤቱ በተደረገ ስብሰባ ተካፍሏል።
የመጀመሪያው ‘‘Council of minister of information of non-aligned countries (COMINACI)’’ ጉባኤ በህንድ ኒውዴልሂ ሲካኼድ ኢትዮጵያን በመወከል በስብሰባው ላይ ተካፍሏል። ይኸው ጉባኤ በኢንዶኒዥያ ጃካርታ ሲካኼድ የልኡካን ቡድኑ አባል በመሆን ታድሟል።
ከዚህ ባሻገር የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ወደ ቀለም በተሸጋገረበት ወቅት፥ ሕዝቡ በየቤቱ ባለቀለም ሥርጭቱን የሚመለከትበት ቴሌቪዥን ኢትዮጵያ አልነበራትም። እናም በመንግሥት አስቸኳይ ትእዛዝ ርዳታ ለመጠየቅ በዶ/ር ፈለቀ ገድለ ጊዮርጊስ በተመራው የልኡካ ቡድን አባል በመሆን ወደ ጃፓን ቶክዮ በመሄድ ከማሩቤኒ ኩባንያ በመቶዎች የሚቆጠሩ ባለቀለም ቴሌቪዥኖች በርዳታ አግኝተው ተመልሰዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ከሱዳን ዜና አገልግሎት (SUNA)፣ ከጀርመን ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክና ከሌሎች አገሮች የዜና አገልግሎት ተቋሞች ጋር የኹለትዮሽ ስምምነት ተፈራርሟል።
መርዕድ ካገኛቸው ሽልማቶች መካከል ኢትዮጵያን ሄራልድ በነበረበት ጊዜ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካኼደው መርሐ ግብር ‘‘የዓመቱ ምርጥ ጋዜጠኛ’’ በመባል የምስክር ወረቀት አግኝቷል። በአዲስ ዘመን ዋና አዘጋጅ ሳለም ዋና መሥሪያ ቤቱ ቬንዙዌላ ካራካስ ከሚገኝ ‘‘ኢንተርናሽናል ጎልድ ሜርኩሪ’’ ከተባለ ተቋም ተሸልሟል።
መርዕድ ወደ ስደት
መርዕድ በቀለ በግንቦት ወር 1983 ዓ.ም. ሕወሐት አዲስ አበባ ሊገባ አንድ ቀን ሲቀረው ነበር፥ በድሬዳዋ አድርጎ ዲክል በምትባል አነስተኛ የጅቡቲ የጠረፍ ከተማ የደረሰው። የጅቡቲ የደኅንነት ሰዎች እርሱንና ከርሱ ጋር የነበሩትን ሌሎች ሦስት ኢትዮጵያውያን አሰሯቸው። ዲክል ከአንድ ዓመት ከአራት ወራት የስደት ኑሮ በኋላ እ.ኤ.አ በ1992 ወደ አሜሪካ በማቅናት ከባለቤቱ እና ከአዳጊ ልጆቹ ጋር ተገናኝቶ ኹለተኛውን የስደት ኑሮ ምዕራፍ “ሀ” ብሎ ጀመረ።
በ1996 እኤአ በአትላንታ በተካኼደው 26ኛ የኦሎምፒክ ውድድር ወቅት የኢትዮጵያ መንግሥት መርዕድ በቀለ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ቡድን ባልደረባ (envoy) እንዲሆን አልስማማም በማለቱ፥ የዓለም አቀፉ አዘጋጅ ኮሚቴ የኡጋንዳ ኦሎምፒክ ቡድን ባልደረባ እንዲሆን ወሰነ። በዚኽ ሁኔታ መርዕድ በሙሉ የኦሎምፒክ ውድድር ላይ ከመታደሙ ባሻገር፥ በወቅቱ ኹለት የኡጋንዳ ቦክሰኞች ውድድራቸውን በማካኼድ ላይ እንዳሉ በወንጀል በመታሰራቸው በግሉ ዋስ በመሆን ከእስር እንዲፈቱና ውድድራቸውን እንዲጨርሱ ረድቷቸዋል።
እኤአ 2019/20 የዓለማችን ከፍተኛ ሥጋት የነበረው የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ወረርሽኝ በአገራችንም በተከሠተ ጊዜ ሥርጭቱን ለመግታትና ወገኖችን ለመርዳት በኢትዮጵያ መንግሥት የቀረበውን የድጋፍ ጥሪ ተቀብሎ በአበረከተው በጎ አስተዋፅኦ ከአምባሳደር ፍጹም አረጋ የምስጋና የምስክር ወረቀት ተሰጥቶታል፡፡
መርዕድ በጆርጂያ
መርዕድ በጆርጅያ ‘‘Department of juvenile justice’’ በሚባል መንግሥታዊ መሥሪያ ቤት ውስጥ በአይ. ቲ. ክፍል ለ13 ዓመታት አገልግሏል። ከዚህ በኋላ በአትላንታ ትልቁ የታክሲ ኩባንያ ‘የሎው ካብ’ yellow cub የአትላንታው ቅርንጫፍ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆኖ ጡረታ እስከወጣበት እስከ 2020 ዓ.ም. በርካታ ኢትዮጵያውያንን የዩጋንዳ፣ የኬንያ፣ የሱዳንና የበርታ አረብ ሀገር ዜጎችን አገልግሏል።
ከዚህ ሌላ በአትላንታ መጀመሪያ አካባቢ ወርሃዊ ጋዜጣ ማሳተም ጀምሮ ነበር። ሆኖም ከጥቂት ዕትሞች በኋላ በተለያየ ምክንያት ሊቀጥል ባለመቻሉ ኅትመቱ ቆሟል።
እ.ኤ.አ በ1994 የማኅደረ አንድነት የሲቪክ ማኅበር በተቋቋመ በዓመቱ የሬዲዮ ፕሮግራም ሲከፈት ከሌሎች ባልደረቦቹ ጋር በመሆን የሬዲዮ ፕሮግራሙን ይዘት፣ ፖሊሲና የመሳሰሉትን በመጻፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል።
መርዕድ የኢትዮጵያና የአሜሪካ ግንኙነት ይበልጥ እንዲጠናከርና የአሜሪካ ምክር ቤት ኢትዮጵያን የሚጎዳ ሕግ እንዳያወጣ የሚታገለው፥ በኢትዮጵያውያን የተቋቋመው የመጀመሪያው የlobyalot ድርጅት ‘‘American Ethiopian Public Affair Committee’’ የአትላንታ ቅርንጫፍ ሊቀመንበር ሆኖ በማገልገል ላይ ነው።
አቶ መርዕድ በቀለ ለ49 ዓመታት የትዳር አጋሩ ከሆነችው ከወይዘሮ ኤፍራት እንደሻው፤ኤፍራት ቤሉል መርዕድ እና ዮናታን መርዕድ የተባሉትን ልጆቻቸውን አፍርተዋል፡፡ ሶፍያ ካሊዬሮ ደግሞ የልጅ ልጃቸው ናት፡፡ ለቤተሰቡ መፅናናት ይሁን።
. በደርግ ጊዜ የማስታወቂያ ምክትል ሚኒስትር ነበር
ከዕዝራ እጅጉ (ተወዳጅ ሚድያ)
#ታሪክ በኢትዮጵያን ሄራልድ፣በየዛሬይቱ ኢትዮጵያ ጋዜጦች፣እንዲሁም በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በመምሪያ ኃላፊነት ያገለገለው አቶ መርዕድ በቀለ ትናንት ህዳር 4 2018 በአትላንታ ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል።
የደርግ ዘመን ማብቂያ ላይ የማስታወቂያ ምክትል ሚኒስትር የነበረው የሚድያ ሰው አቶ መርዕድ በሥነ ፅሁፍ ችሎታው የተመሠከረለት ነበር። የሕይወት ታሪኩ የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ "መዝገበ አእምሮ ቅፅ ሁለት ላይ የሰፈረለት አቶ መርዕድ በቀለ በ2016 በተደረገው የክብር ሽልማት የህይወት ዘመን ተሸላሚዎች ከእጩዎቹ አንዱ ነበር።
አቶ መርዕድ ተወዳጅ ሚድያ የሚያከናውናቸውን የስነዳ ሥራዎች የሚደግፍ ፣ የሚያበረታታ የቅርብ ሰው ሲሆን በህልፈቱም የተሰማንን ሀዘን እንገልጻለን። የካቲት 26 2018 ሲመጣ 80 ዓመቱን ይይዝ የነበረው አቶ መርዕድ ከሰዎች ጋር በቀላሉ የሚግባባ እና የፅሑፍ ሥራንም በጥንቃቄ የሚያከናውን ነበር። እኛም የህይወት ታሪኩን እንደሚከተለው እናቀርባለን።
ትውልድ እና ልጅነት
መርዕድ በቀለ በ1938 ዓ.ም. የካቲት 26 ቀን አዲስ አበባ ቀጨኔ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ተወለደ። አባቱ አቶ በቀለ ወ/ኪዳን የአብነት ትምህርት ቤት ገብቶ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት እንዲማር ፍላጎቱ ቢኖራቸውም፣ እናቱ ወ/ሮ ጽጌ ወርቅ ተክለ ጻዲቅ ግን ልጃቸው ከአጠገባቸው እንዳይርቅ በማሰብ በቤት ውስጥ መምህር ቀጥረው ፊደል ከቆጠረ በኋላ በአካባቢው በነበረው የየኔታ ትምህርት ቤት ገባ።
ትምህርት
በኋላም በአምኃ ደስታ የአንደኛ፣ በዳግማዊ ምኒልክ ትምህርት ቤት ደግሞ የኹለተኛ ደረጃ ትምህርቱን አጠናቀቀ። አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ገብቶ በውጭ ቋንቋዎች እና ሥነጽሑፍ በእንግሊዘኛ ቋንቋ በ1965 ዓ.ም. ተመረቀ።
ወደ ሥራ ዓለም
በዚያው ዓመት ነበር በቀድሞው ልዩ ካቢኔ ቢሮ በታላቁ ቤተመንግሥት ውስጥ የተቀጠረው። ልዩ ካቢኔ በነበረበት ወቅትም ዋና ሥራው ከተለያዩ የዓለም ዜና ምንጮች (Reuters, AFP, BBC… ወዘተ) ከሚሠራጩ ዜናዎች ውስጥ የተመረጡትን እየተረጎመ በአለቃው በኩል ለንጉሡ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ማቅረብ ነበር። ሆኖም በዚህ ሥራ ከሦስት ሳምንት በላይ አልዘለለም።
በወቅቱ የማስታወቂያ ሚኒስቴር ለኢትዮጵያን ሄራልድ እንግሊዘኛ ጋዜጣ የሪፖርተር ቅጥር ያወጣውን ፈተና አልፎ፥ የማታ ኤዲተር ሆኖ ሥራ ጀመረ። ብዙም ሳይቆይ ወደ ቀን ተዘዋወረ።
የህትመት ሚድያ
መርዕድ በ1967 ዓ.ም. ባገኘው የትምህርት ዕድል ወደ ሞስኮ አቅንቶ ነበር። በዚያም ለአንድ ዓመት ስለ ሶሻሊዝም ፅንሰ ሐሳብ ካጠና በኋላ ወደ አገሩ ተመልሶ በዚያው በኢትዮጵያን ሄራልድ በአዘጋጅነት ለተወሰኑ ዓመታት አገልግሏል። ቀጥሎም ወደ “የዛሬይቱ ኢትዮጵያ” ጋዜጣ በዋና አዘጋጅነት ዕድገት አግኝቶ እንዲሠራ ተደረገ። ብዙም ሳይቆይ ወደ አዲስ ዘመን ዕለታዊ ጋዜጣ በዕድገት ተዛውሮ በምክትል ዋና አዘጅነት ለኹለት ዓመታት ከሠራ በኋላ ዋና አዘጋጅ ሆኖ እንዲሠራ ተመደበ።
ከኢዜአ እስከ ምክትል ሚኒስትር
በሥራው ባሕርይ የተነሣ መርዕድ በተደጋጋሚ ‘‘ለጥያቄ ትፈለጋለህ’’ እየተባለ ወደ ደርግ ጽሕፈት ቤት ይጠራ ነበር። እንደ እኤአ 1975/76 ሁለት የደኅንነት ሰዎች ከመሥሪያ ቤቱ መጥተው ወደ ማዕከላዊ እስር ቤት ወሰዱት። ሁኔታው ነገሩ ለሕይወቱ እንደሚያሰጋው በመገንዘብ ከቦታው እንዲዛወር አለቃው የነበረውን ደራሲ በዓሉ ግርማን ደጋግሞ ይጠይቅ፣ ይወተውትም ጀመር። ውትወታው ተቀባይነት አግኝቶ በዕድገት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ሐላፊ ሆኖ ተዛወረ፡፡ እዚያ ለአንድ ዓመት እንደቆየ፥ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት መምሪያ ሐላፊ ሆኖ እንዲሠራ ተመደበ። ለኹለት ዓመታት ካገለገለ በኋላ፥ ከሀገር እስከወጣበት ጊዜ ድረስ የማስታወቂያ ምክትል ሚኒስትር ሆኖ አገልግሏል።
አበርክቶ
መርዕድ በሥራ ላይ በነበረበት ጊዜ በተለያዩ ዓለም አቀፍና አህጉራዊ ስብሰባዎች ላይ ኢትዮጵያን በመወከል፣ አንዳንዴም በልኡካን ቡድን አባልነት ታድሟል። እ.ኤ.አ በ1990/91 መንግሥት ከሻዕቢያ ጋር የሰላም ውይይት በመጀመሪያ በአትላንታ ጆርጂያ በካርተር ማዕከል፣ ቀጥሎ ኹለተኛና ሦስተኛ ዙሮች በዋሽንግተንና በኬንያ ናይሮቢ በተካኼደበት ጊዜ የልኡካኑ ቃል አቀባይ ብቻ ሳይሆን የጋዜጠኞችን ቡድን በመምራት ተሳትፏል።
ከአለቆቹ ጋር በመነጋገር በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የCNN ሥርጭት አገልግሎት እንዲጀመር ያደረገውም እርሱ ነው። አዲስ ዘመን ዋና አዘጋጅ በነበረበት ጊዜ ታደሰ ውቤ ያዘጋጀው በነበረው የፍትሕ ዓምድ አማካኝነት በጊዜው አብዮታዊ ዘመቻ ኮሚቴ (አዘኮ) በሚባል ‘‘ተቋም’’ በየክፍለ ሀገሩ የታሰሩ ንጹሐን ዜጎች እንዲፈቱ አስችሏል።
በወቅቱ የግብፅ ፕሬዚዳንት አንዋር ሳዳት ወደ ሥልጣን የመጡበትን 10ኛ ዓመት በዓል ላይ ለመታደም ከሌሎች ባልደረቦች ጋር ወደ ካይሮ ያቀና ሲኾን፥ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት መምሪያ ሐላፊ በነበረበት ጊዜም የአፍሪካ ዜና አገልግሎት PANA በአዲስ አበባ ሲቋቋም፣ በኋላም በሴኔጋል ዳካር ጽሕፈት ቤቱ በተደረገ ስብሰባ ተካፍሏል።
የመጀመሪያው ‘‘Council of minister of information of non-aligned countries (COMINACI)’’ ጉባኤ በህንድ ኒውዴልሂ ሲካኼድ ኢትዮጵያን በመወከል በስብሰባው ላይ ተካፍሏል። ይኸው ጉባኤ በኢንዶኒዥያ ጃካርታ ሲካኼድ የልኡካን ቡድኑ አባል በመሆን ታድሟል።
ከዚህ ባሻገር የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ወደ ቀለም በተሸጋገረበት ወቅት፥ ሕዝቡ በየቤቱ ባለቀለም ሥርጭቱን የሚመለከትበት ቴሌቪዥን ኢትዮጵያ አልነበራትም። እናም በመንግሥት አስቸኳይ ትእዛዝ ርዳታ ለመጠየቅ በዶ/ር ፈለቀ ገድለ ጊዮርጊስ በተመራው የልኡካ ቡድን አባል በመሆን ወደ ጃፓን ቶክዮ በመሄድ ከማሩቤኒ ኩባንያ በመቶዎች የሚቆጠሩ ባለቀለም ቴሌቪዥኖች በርዳታ አግኝተው ተመልሰዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ከሱዳን ዜና አገልግሎት (SUNA)፣ ከጀርመን ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክና ከሌሎች አገሮች የዜና አገልግሎት ተቋሞች ጋር የኹለትዮሽ ስምምነት ተፈራርሟል።
መርዕድ ካገኛቸው ሽልማቶች መካከል ኢትዮጵያን ሄራልድ በነበረበት ጊዜ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካኼደው መርሐ ግብር ‘‘የዓመቱ ምርጥ ጋዜጠኛ’’ በመባል የምስክር ወረቀት አግኝቷል። በአዲስ ዘመን ዋና አዘጋጅ ሳለም ዋና መሥሪያ ቤቱ ቬንዙዌላ ካራካስ ከሚገኝ ‘‘ኢንተርናሽናል ጎልድ ሜርኩሪ’’ ከተባለ ተቋም ተሸልሟል።
መርዕድ ወደ ስደት
መርዕድ በቀለ በግንቦት ወር 1983 ዓ.ም. ሕወሐት አዲስ አበባ ሊገባ አንድ ቀን ሲቀረው ነበር፥ በድሬዳዋ አድርጎ ዲክል በምትባል አነስተኛ የጅቡቲ የጠረፍ ከተማ የደረሰው። የጅቡቲ የደኅንነት ሰዎች እርሱንና ከርሱ ጋር የነበሩትን ሌሎች ሦስት ኢትዮጵያውያን አሰሯቸው። ዲክል ከአንድ ዓመት ከአራት ወራት የስደት ኑሮ በኋላ እ.ኤ.አ በ1992 ወደ አሜሪካ በማቅናት ከባለቤቱ እና ከአዳጊ ልጆቹ ጋር ተገናኝቶ ኹለተኛውን የስደት ኑሮ ምዕራፍ “ሀ” ብሎ ጀመረ።
በ1996 እኤአ በአትላንታ በተካኼደው 26ኛ የኦሎምፒክ ውድድር ወቅት የኢትዮጵያ መንግሥት መርዕድ በቀለ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ቡድን ባልደረባ (envoy) እንዲሆን አልስማማም በማለቱ፥ የዓለም አቀፉ አዘጋጅ ኮሚቴ የኡጋንዳ ኦሎምፒክ ቡድን ባልደረባ እንዲሆን ወሰነ። በዚኽ ሁኔታ መርዕድ በሙሉ የኦሎምፒክ ውድድር ላይ ከመታደሙ ባሻገር፥ በወቅቱ ኹለት የኡጋንዳ ቦክሰኞች ውድድራቸውን በማካኼድ ላይ እንዳሉ በወንጀል በመታሰራቸው በግሉ ዋስ በመሆን ከእስር እንዲፈቱና ውድድራቸውን እንዲጨርሱ ረድቷቸዋል።
እኤአ 2019/20 የዓለማችን ከፍተኛ ሥጋት የነበረው የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ 19) ወረርሽኝ በአገራችንም በተከሠተ ጊዜ ሥርጭቱን ለመግታትና ወገኖችን ለመርዳት በኢትዮጵያ መንግሥት የቀረበውን የድጋፍ ጥሪ ተቀብሎ በአበረከተው በጎ አስተዋፅኦ ከአምባሳደር ፍጹም አረጋ የምስጋና የምስክር ወረቀት ተሰጥቶታል፡፡
መርዕድ በጆርጂያ
መርዕድ በጆርጅያ ‘‘Department of juvenile justice’’ በሚባል መንግሥታዊ መሥሪያ ቤት ውስጥ በአይ. ቲ. ክፍል ለ13 ዓመታት አገልግሏል። ከዚህ በኋላ በአትላንታ ትልቁ የታክሲ ኩባንያ ‘የሎው ካብ’ yellow cub የአትላንታው ቅርንጫፍ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆኖ ጡረታ እስከወጣበት እስከ 2020 ዓ.ም. በርካታ ኢትዮጵያውያንን የዩጋንዳ፣ የኬንያ፣ የሱዳንና የበርታ አረብ ሀገር ዜጎችን አገልግሏል።
ከዚህ ሌላ በአትላንታ መጀመሪያ አካባቢ ወርሃዊ ጋዜጣ ማሳተም ጀምሮ ነበር። ሆኖም ከጥቂት ዕትሞች በኋላ በተለያየ ምክንያት ሊቀጥል ባለመቻሉ ኅትመቱ ቆሟል።
እ.ኤ.አ በ1994 የማኅደረ አንድነት የሲቪክ ማኅበር በተቋቋመ በዓመቱ የሬዲዮ ፕሮግራም ሲከፈት ከሌሎች ባልደረቦቹ ጋር በመሆን የሬዲዮ ፕሮግራሙን ይዘት፣ ፖሊሲና የመሳሰሉትን በመጻፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቷል።
መርዕድ የኢትዮጵያና የአሜሪካ ግንኙነት ይበልጥ እንዲጠናከርና የአሜሪካ ምክር ቤት ኢትዮጵያን የሚጎዳ ሕግ እንዳያወጣ የሚታገለው፥ በኢትዮጵያውያን የተቋቋመው የመጀመሪያው የlobyalot ድርጅት ‘‘American Ethiopian Public Affair Committee’’ የአትላንታ ቅርንጫፍ ሊቀመንበር ሆኖ በማገልገል ላይ ነው።
አቶ መርዕድ በቀለ ለ49 ዓመታት የትዳር አጋሩ ከሆነችው ከወይዘሮ ኤፍራት እንደሻው፤ኤፍራት ቤሉል መርዕድ እና ዮናታን መርዕድ የተባሉትን ልጆቻቸውን አፍርተዋል፡፡ ሶፍያ ካሊዬሮ ደግሞ የልጅ ልጃቸው ናት፡፡ ለቤተሰቡ መፅናናት ይሁን።
Sponsored by
Surafel
7 months ago
አሜሪካ ያወጣችው መመሪያ ተጽዕኖ አይፈጥርብኝም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቡድን፣ የአሜሪካ የፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር (FAA) ያወጣው አዲስ መመሪያ ወደ አሜሪካ እና ከአሜሪካ በሚያደርጋቸው ዓለም አቀፍ በረራዎች ላይ ተጽዕኖ እንደማይፈጥር አስታውቋል።
አየር መንገዱ ትናንት ጥቅምት 28 ባወጣው መግለጫ፣ አፍሪካንና አሜሪካን የሚያገናኙ ሁሉም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራዎች በታቀደላቸው መርሃ ግብር መሰረት እንደሚከናወኑ አረጋግጧል።
ይሁን እንጂ፣ ሌላ አየር መንገዶችን በመጠቀም ከአሜሪካ ከተሞች ወይም ከሌሎች መዳረሻዎች የሚመጡ ተሳፋሪዎች በመመሪያው ምክንያት "የበረራ ሰዓት ማስተካከያ” ወይም “ተጨማሪ የማረጋገጫ ሂደቶች” ሊገጥማቸው ይችላል ሲል አስገንዝቧል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዚህ ምድብ ውስጥ ለሚገኙ ተጓዦች "ለጉዟቸው ተጨማሪ ጊዜ እንዲሰጡ እና ከመነሳታቸው በፊት የግንኙነት ዝርዝሮችን ከየአየር መንገዶቻቸው እንዲያረጋግጡ" መክሯል።
አየር መንገዱ አክሎም፣ የአሜሪካ መግቢያ በሆኑት ዋሽንግተን ደለስ (IAD)፣ ኒው ዮርክ JFK (JFK)፣ ኒዋርክ (EWR)፣ ቺካጎ (ORD) እና አትላንታ (ATL) በኩል የሚጓዙ መንገደኞች የሚመለከታቸውን አየር መንገዶች እንዲያጣሩ እና ለግንኙነቶች ተጨማሪ ጊዜ እንዲያቅዱ አሳስቧል።
መግለጫው፣ "የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አሜሪካ፣ አፍሪካ እና ሌሎች ቦታዎች ለሚጓዙ ሁሉም ደንበኞቹ አስተማማኝ፣ ምቹና እንከን የለሽ አገልግሎት ለመስጠት ቁርጠኛ ነው" ብሏል።
seledadotio
seledadotio
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቡድን፣ የአሜሪካ የፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር (FAA) ያወጣው አዲስ መመሪያ ወደ አሜሪካ እና ከአሜሪካ በሚያደርጋቸው ዓለም አቀፍ በረራዎች ላይ ተጽዕኖ እንደማይፈጥር አስታውቋል።
አየር መንገዱ ትናንት ጥቅምት 28 ባወጣው መግለጫ፣ አፍሪካንና አሜሪካን የሚያገናኙ ሁሉም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራዎች በታቀደላቸው መርሃ ግብር መሰረት እንደሚከናወኑ አረጋግጧል።
ይሁን እንጂ፣ ሌላ አየር መንገዶችን በመጠቀም ከአሜሪካ ከተሞች ወይም ከሌሎች መዳረሻዎች የሚመጡ ተሳፋሪዎች በመመሪያው ምክንያት "የበረራ ሰዓት ማስተካከያ” ወይም “ተጨማሪ የማረጋገጫ ሂደቶች” ሊገጥማቸው ይችላል ሲል አስገንዝቧል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዚህ ምድብ ውስጥ ለሚገኙ ተጓዦች "ለጉዟቸው ተጨማሪ ጊዜ እንዲሰጡ እና ከመነሳታቸው በፊት የግንኙነት ዝርዝሮችን ከየአየር መንገዶቻቸው እንዲያረጋግጡ" መክሯል።
አየር መንገዱ አክሎም፣ የአሜሪካ መግቢያ በሆኑት ዋሽንግተን ደለስ (IAD)፣ ኒው ዮርክ JFK (JFK)፣ ኒዋርክ (EWR)፣ ቺካጎ (ORD) እና አትላንታ (ATL) በኩል የሚጓዙ መንገደኞች የሚመለከታቸውን አየር መንገዶች እንዲያጣሩ እና ለግንኙነቶች ተጨማሪ ጊዜ እንዲያቅዱ አሳስቧል።
መግለጫው፣ "የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አሜሪካ፣ አፍሪካ እና ሌሎች ቦታዎች ለሚጓዙ ሁሉም ደንበኞቹ አስተማማኝ፣ ምቹና እንከን የለሽ አገልግሎት ለመስጠት ቁርጠኛ ነው" ብሏል።
seledadotio
seledadotio
7 months ago
የሶማሊያ የባሕር ላይ ወንበዴዎች ከ2024 ወዲህ እጅግ ከባድ የተባለውን ጥቃት ፈፀሙ
#ethiopia | ወንበዴዎቹ በማልታ ባንዲራ ስር ቤንዚን ጭኖ ይጓዝ የነበረ የነዳጅ መርከብን ከሶማሊያ የባሕር ዳርቻ አጠገብ በኃይል መውረራቸው ተገልጿል። በመርከቧ ውስጥ የነበሩ 24 ሠራተኞች በደህንነት ክፍል ውስጥ በመደበቅ ሁኔታውን ተቆጣጥረው እንደቆዩ የተለያዩ ምንጮች ዘግበዋል።
🛳 ሄላስ አፍሮዳይት የተባለችው እና በግሪኩ ላስኮ ማሪን ማኔጅመንት ኩባንያ የምትተዳደረው መርከቧ፤ ከህንድ ሲካ ወደ ደቡብ አፍሪካ ደርባን በመጓዝ ላይ ነበረች።
ጥቃት ፈፃሚዎቹ መርከቧ ላይ ከመውጣታቸው በፊት በቁጥጥራቸው ሥር ከነበረች አነስተኛ የኢራን የሸራ መርከብ ባንቀሳቀሱት ፈጣን ጀልባ በአውቶማቲክ መሳሪያዎች እና በሮኬት ማስወንጨፊያ ተኩስ እንደከፈቱ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
🗺 ክስተቱ የተፈፀመው ከሶማሊያዋ ሆብዮ በግምት 550 የባሕር ማይል ርቀት ላይ እና በተለምዶ ከፍተኛ ስጋት ካለባቸው አካባቢዎች እጅግ በራቀ ቦታ ነው። በመርከቧ ላይ የታጠቁ ጠባቂዎች አልነበሩም ተብሏል።
ዓለም አቀፍ ምላሽ፦
በምላሹም በአፍሪካ ቀንድ የባሕር ውንብድናን የሚዋጋው የአውሮፓ ኅብረት አትላንታ ኦፕሬሽንየባሕር ኃይል፤ ምላሽ ለመስጠት በአቅራቢያው ያለ መርከብ አሠማርቷል። በተጨማሪም የጃፓን አውሮፕላን በአካባቢው የቅኝት በረራ አካሂዷል። #spuntik
#ethiopia | ወንበዴዎቹ በማልታ ባንዲራ ስር ቤንዚን ጭኖ ይጓዝ የነበረ የነዳጅ መርከብን ከሶማሊያ የባሕር ዳርቻ አጠገብ በኃይል መውረራቸው ተገልጿል። በመርከቧ ውስጥ የነበሩ 24 ሠራተኞች በደህንነት ክፍል ውስጥ በመደበቅ ሁኔታውን ተቆጣጥረው እንደቆዩ የተለያዩ ምንጮች ዘግበዋል።
🛳 ሄላስ አፍሮዳይት የተባለችው እና በግሪኩ ላስኮ ማሪን ማኔጅመንት ኩባንያ የምትተዳደረው መርከቧ፤ ከህንድ ሲካ ወደ ደቡብ አፍሪካ ደርባን በመጓዝ ላይ ነበረች።
ጥቃት ፈፃሚዎቹ መርከቧ ላይ ከመውጣታቸው በፊት በቁጥጥራቸው ሥር ከነበረች አነስተኛ የኢራን የሸራ መርከብ ባንቀሳቀሱት ፈጣን ጀልባ በአውቶማቲክ መሳሪያዎች እና በሮኬት ማስወንጨፊያ ተኩስ እንደከፈቱ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
🗺 ክስተቱ የተፈፀመው ከሶማሊያዋ ሆብዮ በግምት 550 የባሕር ማይል ርቀት ላይ እና በተለምዶ ከፍተኛ ስጋት ካለባቸው አካባቢዎች እጅግ በራቀ ቦታ ነው። በመርከቧ ላይ የታጠቁ ጠባቂዎች አልነበሩም ተብሏል።
ዓለም አቀፍ ምላሽ፦
በምላሹም በአፍሪካ ቀንድ የባሕር ውንብድናን የሚዋጋው የአውሮፓ ኅብረት አትላንታ ኦፕሬሽንየባሕር ኃይል፤ ምላሽ ለመስጠት በአቅራቢያው ያለ መርከብ አሠማርቷል። በተጨማሪም የጃፓን አውሮፕላን በአካባቢው የቅኝት በረራ አካሂዷል። #spuntik
8 months ago
እንሰሳ እንኳ ሲሞት ቆዳውን ትቶ ይሞታል ፣ እኛ ለትውልድ ምን ትተን እንሄድ ይሆን ?
#ethiopia | የእጅ አሻራችን ስለ እኛ እውነቱን ያናገራል ፡፡ አይዋሸም፡፡ የእግር አሻራችን ሰለ እኛ እውነቱን ይናገራል ፡፡ አይዋሸም፡፡የእናቴ እጆችን ስመለከተው አንዳንዱ ቆስላል፤ አንዳንዱ ጠቁራል ፡፡ አንዳንዱ ሻካራ ሆናል፡፡ብዙ ጊዜ ባዝሊን ትቀባዋለች፡፡ ይህ የእናቴ እጅ አሻራ ስለ እናቴ የሚናገረው ነገር አለ፡፡ የእናቴ የጠቆሩ እጆች፤ የተጠበሱ እጆች፤ የድሙ እጆች፤ የቆስሉ እጆች፤ ስለ እናቴ እውነቱን ይናገራሉ፡፡
ይህም እናቴ ታታሪ ስራተኛ መሆናን ይናገራል፡፡ ጎበዝ ስራተኛ መሆናን ይናገራል፤ብርቱ ስራተኛ መሆናን ይናገራሉ፡፡የእናቴ ጠባሳ እጅ ስለ እናቴ ትጉነት ነው የሚናገረው፡፡
የእጅ አሻራችን ስለ እኛ እውነቱን ያናገራል
የእኛ እጅ ስለ እኛ ምን ይናገራል? የእናንተ እጅ ስለ እናንተ ምን ይናገራል? የአንተ እጅ ስለ አንተ ምን ይናገራል? የአንቺ እጅ ስለ አንቺ ምን ይናገራል?
እጃችን መጥፎም ሆነ መልካም ማድረግ ይችላል
እጃችሁ ማንን ነካበት? ማንን እረዳበት? እጃችሁ ማንን ወጋበት? እጃችሁ ማንን አከመበት? እጃችሁ ለማን ተቆረሰበት? እጃችሁ ማንን መረቀበት? እጃችሁ ምን አይነት ድልድይ ሰራ? እጃችሁ ምን አፈረሰ? እጃችሁ ማንን ሰብረ? እጃችሁ ማን ላይ ምን አለ?
እጃችንን ሁል ጊዜ ሌሎችን ለመረዳት እናድረገው፡፡ እጃችንን ሁል ጊዜ ሌሎችን ለማቅፍ እናድርገው፡፡ እጃችንን ሁል ጊዜ ሌሎችን ለማበራታት እናድርገው፡፡ እጃችንን ሁል ጊዜ ሌሎችን ለመደገፍ እናድርገው፤ እጃችንን ሁል ጊዜ ሰውን ለማገዝ እንጠቀምበት፡፡ እጃችንን ሁል ጊዜ ሰውን ለመግደል አንጠቀምበት፡፡ እጃችንን ሁል ጊዜ ሰውን ለመስበር አንጠቀምበት፡፡የእየሱስ እጅ ስለ እየሱሱ ይናጋራለ፡፡ የእየሱስ የቆሰለው እጆች ስለ እየሱስ እውነቱን ይናጋራሉ፡፡
አንድ ወቅት ቅዱስ አውግስጢኖስን በፍትወትና በዝሙት ህይወቱ የሚያውቁት አንድ ቀን አገኘትና የባለፈውን ማንነቱን እያነሱ ሊወግሩት ና ሊያሸማቅቁት ሲሞክሩ" ያ ሰው አሁን እኔ አይደልሁም" አላቸው፡፡ በእርግጥ ይህ የሄሮድስ ሀሳብ ና መንፈስ ለሁለት ዓመት የቤተ ልሔም ሕፃናትም አልራራም፡፡
አንዳንድ እንሰሳ እንኳ ሲሞት ቆዳውን ትቶ ይሞታል ፣ እኛ ለትውልድ ምን ትተን እንሄድ ይሆን?
ክፋት? ምቀኝነት? ጥላቻ?
Yonas Zewde
ከ አገረ አሜሪካ አትላንታ ጆርጂያ መርሰር ዩኒቨርሲቲ 🇺🇸
#ethiopia | የእጅ አሻራችን ስለ እኛ እውነቱን ያናገራል ፡፡ አይዋሸም፡፡ የእግር አሻራችን ሰለ እኛ እውነቱን ይናገራል ፡፡ አይዋሸም፡፡የእናቴ እጆችን ስመለከተው አንዳንዱ ቆስላል፤ አንዳንዱ ጠቁራል ፡፡ አንዳንዱ ሻካራ ሆናል፡፡ብዙ ጊዜ ባዝሊን ትቀባዋለች፡፡ ይህ የእናቴ እጅ አሻራ ስለ እናቴ የሚናገረው ነገር አለ፡፡ የእናቴ የጠቆሩ እጆች፤ የተጠበሱ እጆች፤ የድሙ እጆች፤ የቆስሉ እጆች፤ ስለ እናቴ እውነቱን ይናገራሉ፡፡
ይህም እናቴ ታታሪ ስራተኛ መሆናን ይናገራል፡፡ ጎበዝ ስራተኛ መሆናን ይናገራል፤ብርቱ ስራተኛ መሆናን ይናገራሉ፡፡የእናቴ ጠባሳ እጅ ስለ እናቴ ትጉነት ነው የሚናገረው፡፡
የእጅ አሻራችን ስለ እኛ እውነቱን ያናገራል
የእኛ እጅ ስለ እኛ ምን ይናገራል? የእናንተ እጅ ስለ እናንተ ምን ይናገራል? የአንተ እጅ ስለ አንተ ምን ይናገራል? የአንቺ እጅ ስለ አንቺ ምን ይናገራል?
እጃችን መጥፎም ሆነ መልካም ማድረግ ይችላል
እጃችሁ ማንን ነካበት? ማንን እረዳበት? እጃችሁ ማንን ወጋበት? እጃችሁ ማንን አከመበት? እጃችሁ ለማን ተቆረሰበት? እጃችሁ ማንን መረቀበት? እጃችሁ ምን አይነት ድልድይ ሰራ? እጃችሁ ምን አፈረሰ? እጃችሁ ማንን ሰብረ? እጃችሁ ማን ላይ ምን አለ?
እጃችንን ሁል ጊዜ ሌሎችን ለመረዳት እናድረገው፡፡ እጃችንን ሁል ጊዜ ሌሎችን ለማቅፍ እናድርገው፡፡ እጃችንን ሁል ጊዜ ሌሎችን ለማበራታት እናድርገው፡፡ እጃችንን ሁል ጊዜ ሌሎችን ለመደገፍ እናድርገው፤ እጃችንን ሁል ጊዜ ሰውን ለማገዝ እንጠቀምበት፡፡ እጃችንን ሁል ጊዜ ሰውን ለመግደል አንጠቀምበት፡፡ እጃችንን ሁል ጊዜ ሰውን ለመስበር አንጠቀምበት፡፡የእየሱስ እጅ ስለ እየሱሱ ይናጋራለ፡፡ የእየሱስ የቆሰለው እጆች ስለ እየሱስ እውነቱን ይናጋራሉ፡፡
አንድ ወቅት ቅዱስ አውግስጢኖስን በፍትወትና በዝሙት ህይወቱ የሚያውቁት አንድ ቀን አገኘትና የባለፈውን ማንነቱን እያነሱ ሊወግሩት ና ሊያሸማቅቁት ሲሞክሩ" ያ ሰው አሁን እኔ አይደልሁም" አላቸው፡፡ በእርግጥ ይህ የሄሮድስ ሀሳብ ና መንፈስ ለሁለት ዓመት የቤተ ልሔም ሕፃናትም አልራራም፡፡
አንዳንድ እንሰሳ እንኳ ሲሞት ቆዳውን ትቶ ይሞታል ፣ እኛ ለትውልድ ምን ትተን እንሄድ ይሆን?
ክፋት? ምቀኝነት? ጥላቻ?
Yonas Zewde
ከ አገረ አሜሪካ አትላንታ ጆርጂያ መርሰር ዩኒቨርሲቲ 🇺🇸
9 months ago
የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎች ደህንነት በራቃቸው ከተሞች እንደማይካሄዱ ዶናልድ ትራምፕ አስታወቁ
#ethiopia | የአሜሪካው ዶናልድ ትራምፕ የ2026 ዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ጨዋታዎችን ደህንነት የራቃቸው ናቸው ብለው ከሚያስቧቸው ከተሞች እንደሚቀይሩ ተናግረዋል።
በሚቀጥለው ዓመት ክረምት ላይ 48 ቡድኖች የሚጋጠሙበትን የዓለም ዋንጫ 11 የአሜሪካ ከተሞች ለማስተናገድ ተዘጋጅተዋል።
የ2026 የዓለም ዋንጫን ካናዳ እና ሜክሲኮ አሜሪካ በጋራ እንደሚያሰናዱም ይታወቃል፡፡
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኦቫል ኦፊስ ለተገኙ ጋዜጠኞች "ይህ ለዓለም ዋንጫ መልካም ነው፤እኔ ደህንነቱ የተጠበቀ አይደለም ብዬ ካሰብኩ ወደ ሌላ ከተማ እናዞረዋለን" ሲሉ ተናግረዋል።
የዓለም ዋንጫን የሚያስተናግዱት 11 ከተሞች አትላንታ፣ ቦስተን፣ ዳላስ፣ ሂውስተን፣ ካንሳስ ሲቲ፣ ሎስ አንጀለስ፣ ማያሚ፣ ኒው ዮፕሬዚዳንትርክ/ኒው ጀርሲ፣ ፊላደልፊያ፣ ሳንፍራንሲስኮ እና ሲያትል ናቸው።
ትራምፕ ጥያቄ የቀረበላቸው በዲሞክራቶች በሚመሩት ሲያትል እና ሳን ፍራንሲስኮ ስለሚካሄዱ ጨዋታዎች ነበር።
ሁለቱም ከተሞች ስድስት ጨዋታዎችን እንደሚያዘጋጁ የወጣው ድልድል ያሳያል።
ትራምፕ በተደጋጋሚ በአሜሪካ የተለያዩ ግዛቶች የሚታዩ ወንጀሎችን መቅረፍ የአጀንዳቸው ማዕከል መሆኑን ይናገራሉ።
መረጃው የቢቢሲ ስፖርት ነው፡፡
#hagerie #sport #gtmc
#ethiopia | የአሜሪካው ዶናልድ ትራምፕ የ2026 ዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ጨዋታዎችን ደህንነት የራቃቸው ናቸው ብለው ከሚያስቧቸው ከተሞች እንደሚቀይሩ ተናግረዋል።
በሚቀጥለው ዓመት ክረምት ላይ 48 ቡድኖች የሚጋጠሙበትን የዓለም ዋንጫ 11 የአሜሪካ ከተሞች ለማስተናገድ ተዘጋጅተዋል።
የ2026 የዓለም ዋንጫን ካናዳ እና ሜክሲኮ አሜሪካ በጋራ እንደሚያሰናዱም ይታወቃል፡፡
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኦቫል ኦፊስ ለተገኙ ጋዜጠኞች "ይህ ለዓለም ዋንጫ መልካም ነው፤እኔ ደህንነቱ የተጠበቀ አይደለም ብዬ ካሰብኩ ወደ ሌላ ከተማ እናዞረዋለን" ሲሉ ተናግረዋል።
የዓለም ዋንጫን የሚያስተናግዱት 11 ከተሞች አትላንታ፣ ቦስተን፣ ዳላስ፣ ሂውስተን፣ ካንሳስ ሲቲ፣ ሎስ አንጀለስ፣ ማያሚ፣ ኒው ዮፕሬዚዳንትርክ/ኒው ጀርሲ፣ ፊላደልፊያ፣ ሳንፍራንሲስኮ እና ሲያትል ናቸው።
ትራምፕ ጥያቄ የቀረበላቸው በዲሞክራቶች በሚመሩት ሲያትል እና ሳን ፍራንሲስኮ ስለሚካሄዱ ጨዋታዎች ነበር።
ሁለቱም ከተሞች ስድስት ጨዋታዎችን እንደሚያዘጋጁ የወጣው ድልድል ያሳያል።
ትራምፕ በተደጋጋሚ በአሜሪካ የተለያዩ ግዛቶች የሚታዩ ወንጀሎችን መቅረፍ የአጀንዳቸው ማዕከል መሆኑን ይናገራሉ።
መረጃው የቢቢሲ ስፖርት ነው፡፡
#hagerie #sport #gtmc
9 months ago
ትራምፕ የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎች 'ደህንነት በራቃቸው ከተሞች እንደማይካሄዱ' አስታወቁ
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የ2026 ዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ጨዋታዎችን ደህንነት የራቃቸው ናቸው ብለው ከሚያስቧቸው ከተሞች እንደሚቀይሩ ተናገሩ።
በሚቀጥለው ዓመት ክረምት ላይ 48 ቡድኖች የሚጋጠሙበትን የዓለም ዋንጫ 11 የአሜሪካ ከተሞች ለማስተናገድ ተዘጋጅተዋል።
የ2026 የዓለም ዋንጫን ካናዳ እና ሜክሲኮ አሜሪካ በጋራ ያሰናዳሉ።
ውድድሩን የማዘጋጀት እና አስተናጋጅ ከተሞችን የመምረጥ ኃላፊነት ያለበት ፊፋ በዚህ ውሳኔ ምክንያት የሎጂስቲክስ ችግሮች ሊገጥሙት እንደሚችል ይጠበቃል።
ትራምፕ ይህንን ለውጥ ለማድረግ ሥልጣን ይኑራቸው አይኑራቸው ግልጽ ባይሆንም ከፕሬዚዳነት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ጋር ግን የቅርብ ወዳጅ ናቸው። የዓለም ዋንጫን የሚያስተናግዱት 11 ከተሞች አትላንታ፣ ቦስተን፣ ዳላስ፣ ሂውስተን፣ ካንሳስ ሲቲ፣ ሎስ አንጀለስ፣ ማያሚ፣ ኒው ዮርክ/ኒው ጀርሲ፣ ፊላደልፊያ፣ ሳንፍራንሲስኮ እና ሲያትል ናቸው።
ትራምፕ ጥያቄ የቀረበላቸው በዲሞክራቶች በሚመሩት ሲያትል እና ሳን ፍራንሲስኮ ስለሚካሄዱ ጨዋታዎች ነበር።
ሁለቱም ከተሞች ስድስት ጨዋታዎችን እንደሚያዘጋጁ የወጣው ድልድል ያሳያል።
በሚቀጥለው ዓመት ስምንት ጨዋታዎችን እንዲሁም የ2028 ኦሊምፒክ የምታስተናግደው እና የዲሞክራቶች ጠንካራ ግዛት የሆነችው ሎስ አንጀለስንም ጠቅሰዋል።
"ማንኛውም ከተማ ለዓለም ዋንጫ፣ ወይንም ለኦሊምፒክ ትንሽም ቢሆን አደገኛ እንደሆነ ካሰብን፣ ጨዋታዎች በተለያዩ ከተሞች ስለሚደረጉ በተለይ ለዓለም ዋንጫ፣ እዚያ እንዲካሄድ አንፈቅድም። ወደ ሌላ አካባቢ እንቀይረዋለን" ብለዋል።
ትራምፕ በተደጋጋሚ በአሜሪካ የተለያዩ ግዛቶች የሚታዩ ወንጀሎችን መቅረፍ የአጀንዳቸው ማዕከል መሆኑን ይናገራሉ።
ምንም እንኳ እአአ ከ2023 ጀምሮ ወንጀል እየቀነሰ መምጣቱን መረጃዎች ቢያሳዩም ባለፈው ወር የብሔራዊ ዘብ አባላትን እና የፌደራል ኃይሎችን በዋሺንግተን ዲሲ አሰማርተዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ወደ ሜንፊስ እና ቺካጎ ወታደሮችን ለመላክ እቅድ እንዳላቸው ተናግረዋል።
ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር 2000 የብሔራዊ ዘብ አባላትን በሎስ አንጀለስ የሚገኙ ሰነድ አልባ ስደተኞችን እና የተቃውሞ ሠልፎችን ለመቆጣጠር አሰማርተዋል።
የዓለም ዋንጫ የምድብ ድልድል እአአ ዴሴምበር 5 በዋሺንግተን ዲሲ ይወጣል።
ጨዋታው እአአ በ2026 ከሰኔ 11 እስከ ሐምሌ 19 ድረስ ይካሄዳል።
ትራምፕ ስለዓለም ዋንጫ ሲናገሩ ይህ የመጀመርያቸው አይደለም።
በግንቦት ወር ሩሲያ በዓለም ዋንጫ መሳተፏ ከዩክሬን ጋር የምታደርገውን ጦርነት ለማቆም "እንደ ማበረታቻ" ያገለግላል ብለው ነበር።
ይህ ንግግራቸው የተሰማው ሩሲያ ዩክሬንን ከወረረች በኋላ ፊፋ እና የአውሮፓ እግር ኳስ ማኅበር የእግር ኳስ ብሔራዊ ቡድኗን ከየትኛውም የዓለም አቀፍ ውድድሮች ካገዱ በኋላ ነው።
በመጋቢት ወር ደግሞ ዋንጫውን በጥምረት በሚያዘጋጁት አሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ መካከል ያለው ፖለቲካዊ ውጥረት ለውድድሩ ጥሩ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
BBC
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የ2026 ዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ጨዋታዎችን ደህንነት የራቃቸው ናቸው ብለው ከሚያስቧቸው ከተሞች እንደሚቀይሩ ተናገሩ።
በሚቀጥለው ዓመት ክረምት ላይ 48 ቡድኖች የሚጋጠሙበትን የዓለም ዋንጫ 11 የአሜሪካ ከተሞች ለማስተናገድ ተዘጋጅተዋል።
የ2026 የዓለም ዋንጫን ካናዳ እና ሜክሲኮ አሜሪካ በጋራ ያሰናዳሉ።
ውድድሩን የማዘጋጀት እና አስተናጋጅ ከተሞችን የመምረጥ ኃላፊነት ያለበት ፊፋ በዚህ ውሳኔ ምክንያት የሎጂስቲክስ ችግሮች ሊገጥሙት እንደሚችል ይጠበቃል።
ትራምፕ ይህንን ለውጥ ለማድረግ ሥልጣን ይኑራቸው አይኑራቸው ግልጽ ባይሆንም ከፕሬዚዳነት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ጋር ግን የቅርብ ወዳጅ ናቸው። የዓለም ዋንጫን የሚያስተናግዱት 11 ከተሞች አትላንታ፣ ቦስተን፣ ዳላስ፣ ሂውስተን፣ ካንሳስ ሲቲ፣ ሎስ አንጀለስ፣ ማያሚ፣ ኒው ዮርክ/ኒው ጀርሲ፣ ፊላደልፊያ፣ ሳንፍራንሲስኮ እና ሲያትል ናቸው።
ትራምፕ ጥያቄ የቀረበላቸው በዲሞክራቶች በሚመሩት ሲያትል እና ሳን ፍራንሲስኮ ስለሚካሄዱ ጨዋታዎች ነበር።
ሁለቱም ከተሞች ስድስት ጨዋታዎችን እንደሚያዘጋጁ የወጣው ድልድል ያሳያል።
በሚቀጥለው ዓመት ስምንት ጨዋታዎችን እንዲሁም የ2028 ኦሊምፒክ የምታስተናግደው እና የዲሞክራቶች ጠንካራ ግዛት የሆነችው ሎስ አንጀለስንም ጠቅሰዋል።
"ማንኛውም ከተማ ለዓለም ዋንጫ፣ ወይንም ለኦሊምፒክ ትንሽም ቢሆን አደገኛ እንደሆነ ካሰብን፣ ጨዋታዎች በተለያዩ ከተሞች ስለሚደረጉ በተለይ ለዓለም ዋንጫ፣ እዚያ እንዲካሄድ አንፈቅድም። ወደ ሌላ አካባቢ እንቀይረዋለን" ብለዋል።
ትራምፕ በተደጋጋሚ በአሜሪካ የተለያዩ ግዛቶች የሚታዩ ወንጀሎችን መቅረፍ የአጀንዳቸው ማዕከል መሆኑን ይናገራሉ።
ምንም እንኳ እአአ ከ2023 ጀምሮ ወንጀል እየቀነሰ መምጣቱን መረጃዎች ቢያሳዩም ባለፈው ወር የብሔራዊ ዘብ አባላትን እና የፌደራል ኃይሎችን በዋሺንግተን ዲሲ አሰማርተዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ወደ ሜንፊስ እና ቺካጎ ወታደሮችን ለመላክ እቅድ እንዳላቸው ተናግረዋል።
ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር 2000 የብሔራዊ ዘብ አባላትን በሎስ አንጀለስ የሚገኙ ሰነድ አልባ ስደተኞችን እና የተቃውሞ ሠልፎችን ለመቆጣጠር አሰማርተዋል።
የዓለም ዋንጫ የምድብ ድልድል እአአ ዴሴምበር 5 በዋሺንግተን ዲሲ ይወጣል።
ጨዋታው እአአ በ2026 ከሰኔ 11 እስከ ሐምሌ 19 ድረስ ይካሄዳል።
ትራምፕ ስለዓለም ዋንጫ ሲናገሩ ይህ የመጀመርያቸው አይደለም።
በግንቦት ወር ሩሲያ በዓለም ዋንጫ መሳተፏ ከዩክሬን ጋር የምታደርገውን ጦርነት ለማቆም "እንደ ማበረታቻ" ያገለግላል ብለው ነበር።
ይህ ንግግራቸው የተሰማው ሩሲያ ዩክሬንን ከወረረች በኋላ ፊፋ እና የአውሮፓ እግር ኳስ ማኅበር የእግር ኳስ ብሔራዊ ቡድኗን ከየትኛውም የዓለም አቀፍ ውድድሮች ካገዱ በኋላ ነው።
በመጋቢት ወር ደግሞ ዋንጫውን በጥምረት በሚያዘጋጁት አሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ መካከል ያለው ፖለቲካዊ ውጥረት ለውድድሩ ጥሩ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
BBC
9 months ago
የተባባሪ ፕሮፌሰር በዛብህ ወልዴ ሃታኡ የመታሰቢያ ሀውልት ተመረቀ
ተባባሪ ፕሮፌሰር በዛብህ ወልዴ ሃትኡ(ዶ/ር) ከሐምሌ 23/1952 – ነሃሴ 19/2014 ዓ.ም
#ethiopia | ተባባሪ ፕሮፌሰር በዛብህ ወልዴ በቀድሞው ባሌ ክፍለ ሀገር ልዩ ስሙ ጊኒር በሚባል አካባቢ ሐምሌ 23/1952 ዓ.ም ተወለዱ፡፡
በትምህርቱ ዘርፍ የነበራቸው አበርክቶ ትምህርታቸውን በጅማ መምህራን ማሰልጠኛ ተቋም፣ በኮተቤ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጅ ፤በቡልጋሪያ አገር በሶፊያ ሰውነት ማጎልመሻ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፤በፖላንድ አገር በሚገኘው ዋርሶ የሰውነት ማጎልመሻ ማእከል ተከታትለው በከፍተኛ ማዕረግ ተመርቀዋል ።
በኮተቤ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጅና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት፣ በምርምር ስራዎችና በማህበረሰብ አገልግሎት የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል፤ ከመጀመሪያ ደረጃ እስከ ሶስተኛ ዲግሪ መርሀ-ግብሮች በመምህርነት አገልግለዋል፤
በአገር ውስጥና ከአገር ውጪ በሚገኙ የተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በተጋበዥ መምህርነት፣ ተማሪዎችን በማማከርና የምርምር ስራዎችን በማቅረብ አገልግለዋል፤
በስፖርቱ ዘርፍ ነበራቸው አበርክቶ ከ20 አመት በላይ በአትሌቲክሱ ላይ :-
በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በዋና ፀኃፊነት፣በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በዋና ፀኃፊነት፣ በሥራ አስፈጻሚ ኮ/አባልነት፣ በአቃቢ ነዋይነት አገልግለዋል።
በአትላንታና በሲድኒ ኦሎምፒክ በዝግጅትና በአመራር፤በኤድመንተን ዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በአመራርነት፤ በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በፕሬዚዳንትነት፣በአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በፕሬዜዳንትነት
በቴክኒክና በህክምና ኮሚቴ ሰብሳቢነት ፣በአቃቤ ነዋይነት እስከ ህልፈተ ህይወታቸው ድረስ ደከመኝ፣ ሰለቸኝ ሳይሉ አትሌቲክሱን ያገለገሉ የኢትዮጵያ ባለውለታ በመሆናቸው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሙሉ ወጪዉን በመሸፈን የመታሰቢያ ሐውልት በስማቸው አሰርቶላቸዋል።
ሐዉልቱም ዛሬ ጠዋት ጳጉሜ 2/2017 ዓ.ም በመንበረ ፀባኦት ቤተክርስቲያን ወዳጅ ዘመዶቹ ፣የፌዴሬሽኑ አመራሮች፣አንጋፋ አትሌቶች ፣የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ አመራሮች ፣የሙያ አጋሮቹ እንዲሁም የቀድሞ ተማሪዎቹ በተገኙበት ተመርቀዋል።
ተባባሪ ፕሮፌሰር በዛብህ ወልዴ ለኢትዮጵያ ስፖርት ላደረከዉ አስተዋፅኦ ሁሌም እናመሰግንሀለን። ❤🙏
ተባባሪ ፕሮፌሰር በዛብህ ወልዴ ሃትኡ(ዶ/ር) ከሐምሌ 23/1952 – ነሃሴ 19/2014 ዓ.ም
#ethiopia | ተባባሪ ፕሮፌሰር በዛብህ ወልዴ በቀድሞው ባሌ ክፍለ ሀገር ልዩ ስሙ ጊኒር በሚባል አካባቢ ሐምሌ 23/1952 ዓ.ም ተወለዱ፡፡
በትምህርቱ ዘርፍ የነበራቸው አበርክቶ ትምህርታቸውን በጅማ መምህራን ማሰልጠኛ ተቋም፣ በኮተቤ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጅ ፤በቡልጋሪያ አገር በሶፊያ ሰውነት ማጎልመሻ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፤በፖላንድ አገር በሚገኘው ዋርሶ የሰውነት ማጎልመሻ ማእከል ተከታትለው በከፍተኛ ማዕረግ ተመርቀዋል ።
በኮተቤ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጅና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት፣ በምርምር ስራዎችና በማህበረሰብ አገልግሎት የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል፤ ከመጀመሪያ ደረጃ እስከ ሶስተኛ ዲግሪ መርሀ-ግብሮች በመምህርነት አገልግለዋል፤
በአገር ውስጥና ከአገር ውጪ በሚገኙ የተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በተጋበዥ መምህርነት፣ ተማሪዎችን በማማከርና የምርምር ስራዎችን በማቅረብ አገልግለዋል፤
በስፖርቱ ዘርፍ ነበራቸው አበርክቶ ከ20 አመት በላይ በአትሌቲክሱ ላይ :-
በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በዋና ፀኃፊነት፣በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በዋና ፀኃፊነት፣ በሥራ አስፈጻሚ ኮ/አባልነት፣ በአቃቢ ነዋይነት አገልግለዋል።
በአትላንታና በሲድኒ ኦሎምፒክ በዝግጅትና በአመራር፤በኤድመንተን ዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በአመራርነት፤ በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በፕሬዚዳንትነት፣በአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በፕሬዜዳንትነት
በቴክኒክና በህክምና ኮሚቴ ሰብሳቢነት ፣በአቃቤ ነዋይነት እስከ ህልፈተ ህይወታቸው ድረስ ደከመኝ፣ ሰለቸኝ ሳይሉ አትሌቲክሱን ያገለገሉ የኢትዮጵያ ባለውለታ በመሆናቸው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሙሉ ወጪዉን በመሸፈን የመታሰቢያ ሐውልት በስማቸው አሰርቶላቸዋል።
ሐዉልቱም ዛሬ ጠዋት ጳጉሜ 2/2017 ዓ.ም በመንበረ ፀባኦት ቤተክርስቲያን ወዳጅ ዘመዶቹ ፣የፌዴሬሽኑ አመራሮች፣አንጋፋ አትሌቶች ፣የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ አመራሮች ፣የሙያ አጋሮቹ እንዲሁም የቀድሞ ተማሪዎቹ በተገኙበት ተመርቀዋል።
ተባባሪ ፕሮፌሰር በዛብህ ወልዴ ለኢትዮጵያ ስፖርት ላደረከዉ አስተዋፅኦ ሁሌም እናመሰግንሀለን። ❤🙏
9 months ago
ህገወጥ ስደተኞችን ለመያዝ በአሜሪካ ፋብሪካ ላይ በተደረገ ወረራ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰራተኞች ታሰሩ
በጆርጂያ በሚገኘው የሃዩንዳይ መኪና ማምረቻ ፋብሪካ ላይ በተካሄደ ወረራ የአሜሪካ የኢሚግሬሽን ባለስልጣናት 475 የሚጠጉ ሰዎችን በቁጥጥር ስር ያዋሉ ሲሆን አብዛኛዎቹም የኮሪያ ዜጎች ናቸው።
ይህ ወረራ ዶናልድ ትራምፕ ለሁለተኛ ጊዜ ስልጣን ከያዙ በኋላ በማንኛውም የስራ ቦታ ላይ ከተካሄዱት ወረራዎች ሁሉ ትልቁ ተብሏል።
ደቡብ ኮሪያ በዘመቻው ላይ "ስጋትና ቁጣዋን" የገለፀች ሲሆን የአሜሪካ መንግስት የዜጎቿን መብት እንዲያከብር አሳስባለች።
የዩኤስ የሀገር ውስጥ ደህንነት ዲፓርትመንት ለቢቢሲ እንደተናገረው ወኪሎቹ በህገ ወጥ መንገድ የስራ እድሎችን እና ሌሎች ከባድ የፌዴራል ወንጀሎችን በመከልከል ወንጀል ምርመራ አድርገዋል።
“ይህ የኢሚግሬሽን ዘመቻ አልነበረም ወኪሎቻችን ወደ አካባቢው ገብተው ከበው ሰዎችን አውጥተው በአውቶቡስ ያጓጉዙ” ሲሉ በአትላንታ የሀገር ውስጥ ደህንነት ምርመራዎች ሃላፊ የሆኑት ልዩ ወኪል ስቲቭ ሽራንክ አርብ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል።
በዘመቻው ከተያዙት መካከል ብዙዎቹ ከላቲን አሜሪካ አገሮች ጋር ግንኙነት ቢኖራቸውም የሌሎች ሀገራት ሰዎችም ታስረዋል።
በጆርጂያ በሚገኘው የሃዩንዳይ መኪና ማምረቻ ፋብሪካ ላይ በተካሄደ ወረራ የአሜሪካ የኢሚግሬሽን ባለስልጣናት 475 የሚጠጉ ሰዎችን በቁጥጥር ስር ያዋሉ ሲሆን አብዛኛዎቹም የኮሪያ ዜጎች ናቸው።
ይህ ወረራ ዶናልድ ትራምፕ ለሁለተኛ ጊዜ ስልጣን ከያዙ በኋላ በማንኛውም የስራ ቦታ ላይ ከተካሄዱት ወረራዎች ሁሉ ትልቁ ተብሏል።
ደቡብ ኮሪያ በዘመቻው ላይ "ስጋትና ቁጣዋን" የገለፀች ሲሆን የአሜሪካ መንግስት የዜጎቿን መብት እንዲያከብር አሳስባለች።
የዩኤስ የሀገር ውስጥ ደህንነት ዲፓርትመንት ለቢቢሲ እንደተናገረው ወኪሎቹ በህገ ወጥ መንገድ የስራ እድሎችን እና ሌሎች ከባድ የፌዴራል ወንጀሎችን በመከልከል ወንጀል ምርመራ አድርገዋል።
“ይህ የኢሚግሬሽን ዘመቻ አልነበረም ወኪሎቻችን ወደ አካባቢው ገብተው ከበው ሰዎችን አውጥተው በአውቶቡስ ያጓጉዙ” ሲሉ በአትላንታ የሀገር ውስጥ ደህንነት ምርመራዎች ሃላፊ የሆኑት ልዩ ወኪል ስቲቭ ሽራንክ አርብ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል።
በዘመቻው ከተያዙት መካከል ብዙዎቹ ከላቲን አሜሪካ አገሮች ጋር ግንኙነት ቢኖራቸውም የሌሎች ሀገራት ሰዎችም ታስረዋል።
Sponsored by
Surafel
10 months ago
የካሊፎርንያው ዝርፊያ !
በዶ/ር ወዳጄነህ መሐረነ
በአሜሪካ እያደረኩ ያለሁት ጉዞ (tour) የተዘጋጀው በ ድሮፕስ ኦፍ ሆፕ (Drops of Hope) በተባለ ድርጅት ነው። የዚህ ድርጅት መስራቾች ደግሞ ስምረት ቢውቲ (ኦስተን) እና ኤደን አባተ (አትላንታ) ናቸው።
ጉዞው በሲያትል ጀምሮ ፓርትላንድ፣ ሎስ አንጀለስ፣ ላስቬጋስ፣ ዴንቨር፣ ዳላስ፣ ሚኖሶታ፣ በተባሉ ከተሞች ተደርጎ ቤይ ኤርያ ኦክላንድ ካሊፎርንያ ደረሰ። በዚህም ከተማ በጣም ውጤታማ ፕሮግራም አድርገን ከጨረስን በኋላ በመጨረሻው ቀን ምሽት ጋባዦቻችን አንድ የታወቀ የኢትዬጵያ ሬስቶራንት ወሰዱን።
እኔና አብረውኝ የሚሰሩ ወዳጆቼ ብዙ ከተማዎች እንደምናደርገው ኦክላንድም መኪና ተከራይተን ነበር። ከራት ግብዣው ስንወጣ የመኪናችን መስታዎት ተሰብሮ አገኘነው። መኪናው ውስጥ የነበረ አንድ ሻንጣ ተወስዷል። በሻንጣው ውስጥ የስራ ባልደረቦቼ ጥቂት ልብሶች ነበሩ።
እኔ በግሌ ምንም አልጠፋብኝም። ዶክመንትም፣ ገንዘብም፣ ንብረትም አልጠፋብኝም። የመኪናውንም መስታዎት አሰርተን መልሰናል።
ዘረፋውን ያደረሱብን ሰዎች ማን እንደሆኑ አላውቅም። በከተማው ያሉ በሌብነት ላይ የተሰማሩ ግለሰቦች ይመስሉኛል። ዘሀበሻም ያቀረበው ዘገባ ትክክል ነበር።
በጣም ላሰባችሁልኝ ወዳጆቼ፣ ወገኖቼ ከልብ የሆነ ምስጋናዬን አቀርባለሁ። አጋጣሚው እናንተ ለእኔ ያላችሁን ፍቅርና ርህራሄ እንዳይ ረድቶኛል።
ከዚህ በኋላ የፊታችን እሁድ በአትላንታ በሳምንቱም በአሌክሳንድርያ ቨርጂንያ ፕሬግራሞቹ ተደርገው ሲያበቁ ወደ አዲስ አበባ እመለሳለሁ።
ምስጋናና ክብር ለልዑል እግዚአብሔር ይሁን! ምህረቱ ለዘላለም ነውና! 🙏
በዶ/ር ወዳጄነህ መሐረነ
በአሜሪካ እያደረኩ ያለሁት ጉዞ (tour) የተዘጋጀው በ ድሮፕስ ኦፍ ሆፕ (Drops of Hope) በተባለ ድርጅት ነው። የዚህ ድርጅት መስራቾች ደግሞ ስምረት ቢውቲ (ኦስተን) እና ኤደን አባተ (አትላንታ) ናቸው።
ጉዞው በሲያትል ጀምሮ ፓርትላንድ፣ ሎስ አንጀለስ፣ ላስቬጋስ፣ ዴንቨር፣ ዳላስ፣ ሚኖሶታ፣ በተባሉ ከተሞች ተደርጎ ቤይ ኤርያ ኦክላንድ ካሊፎርንያ ደረሰ። በዚህም ከተማ በጣም ውጤታማ ፕሮግራም አድርገን ከጨረስን በኋላ በመጨረሻው ቀን ምሽት ጋባዦቻችን አንድ የታወቀ የኢትዬጵያ ሬስቶራንት ወሰዱን።
እኔና አብረውኝ የሚሰሩ ወዳጆቼ ብዙ ከተማዎች እንደምናደርገው ኦክላንድም መኪና ተከራይተን ነበር። ከራት ግብዣው ስንወጣ የመኪናችን መስታዎት ተሰብሮ አገኘነው። መኪናው ውስጥ የነበረ አንድ ሻንጣ ተወስዷል። በሻንጣው ውስጥ የስራ ባልደረቦቼ ጥቂት ልብሶች ነበሩ።
እኔ በግሌ ምንም አልጠፋብኝም። ዶክመንትም፣ ገንዘብም፣ ንብረትም አልጠፋብኝም። የመኪናውንም መስታዎት አሰርተን መልሰናል።
ዘረፋውን ያደረሱብን ሰዎች ማን እንደሆኑ አላውቅም። በከተማው ያሉ በሌብነት ላይ የተሰማሩ ግለሰቦች ይመስሉኛል። ዘሀበሻም ያቀረበው ዘገባ ትክክል ነበር።
በጣም ላሰባችሁልኝ ወዳጆቼ፣ ወገኖቼ ከልብ የሆነ ምስጋናዬን አቀርባለሁ። አጋጣሚው እናንተ ለእኔ ያላችሁን ፍቅርና ርህራሄ እንዳይ ረድቶኛል።
ከዚህ በኋላ የፊታችን እሁድ በአትላንታ በሳምንቱም በአሌክሳንድርያ ቨርጂንያ ፕሬግራሞቹ ተደርገው ሲያበቁ ወደ አዲስ አበባ እመለሳለሁ።
ምስጋናና ክብር ለልዑል እግዚአብሔር ይሁን! ምህረቱ ለዘላለም ነውና! 🙏
10 months ago
አንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።
ተዋናይ ፣ኮሜዲያን፣ አዘጋጅ ሆኖ ለረዥም ዓመታት አገልግሏል፡፡ በመድረክ ፣ በሬዲዩ፣ በቴሌቪዥን፣ በፊልም ስራ እና በጋዜጠኝነት ሙያ ሠርቷል ። በአፍሪካ የመድረክ ሙያተኞች ማህበር በሊቀመንበርነት መርቷል ፣ በአትላንታ ጆርጂያ በበረከተው የሙያው ሥራ ኖቬምበር 24 ቀን በስሙ ተሰይሞለታል። (ጋሽ ደቤ) በኢትዮጵያ ውስጥ አሁን በህይወት ካሉት አርቲስቶች ግንባር ቀደሙና አንጋፋው ነው።
መጀመሪያ በቴያትር የታዩት በመንግስቱ ለማ በተጻፈው ያላቻ ጋብቻ ሲሆን ከዚያ በአንዳንድ እንግሊዝኛ ትርኢት (The game of chess, ‘Waiting for Godot’) እንዲሁም በራዲዮም ሆነ በቴሌቪዥን ተጫወቱ።
አርቲስት ደበበ እሸቱ (ጋሽ ደቤ) ለታሪክ የሚተላለፉ ህያው ስራዎች ሰርቷል እስቲ ጋሽ ደቤ ከሰራቸው ስራዎች ውስጥ በጥቂቱ እንያቸው፤ በሃገር ውስጥ ካለው ታዋቂነትና ለሙያው ካደረገው አስተዋጽኦ ለመጠቀስ ያህል ፡-
በቤተኪነጥበባት ወቴአትር፡-
ያላቻ ጋብቻ ተዋናይ
ሮሚዎባ ዡልየት ተዋናይ
ጠልፎ በኪሴ ተዋናይም አዘጋጂም
ዳንዴው ጨቡዴ ››
ዘ ጌም ኦፍ ቼዝ (በእንግሊዝኛ) ተዋናይ
ኦቴሎ (በአንግሊዝኛ) ተዋናይም አዘጋጂም
አዳ ኦክ አራክል (በእንግሊዝኛ)ከሎ.ጸ.ገ.መ ተዋናይ
በቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ(ብሔራዊ) ቴአትር፡-
የበጋ ሌሊት ራዕይ ተዋናይ
አንድ ዓመት ከአንድ ቀን ተዋናይ
እናት ዓለም ጠኑ ተዋናይ
ኪንግ ሊር ተዋናይ
ዋናው ተቆጣጣሪ ተዋናይ
ጠያቂ ተዋናይ አዘጋጅ
በቀይካባ ስውር ደባ አዘጋጅ
ተሓድሶ አዘጋጅ
የአዘውንቶች ክበብ አዘጋጅ ተዋናይ
በሃገር ፍቅር ቴአትር፡-
ጠልፎ በኪሴ አዘጋጅ/ተዋናይ
የወፍ ጎጆ ተዋናይ
ኪንግ ሊር ተዋናይ
የቬኒሱ ነጋዴ ተዋናይ
ናትናኤል ጠቢቡ ተዋናይ
ድብልቅልቅ ተርጓሚ/ ተዋናይ
ማዕበል ተርጓሚ አዘጋጅ
በፊልም በሃገርና በዓለም አቀፍ፡-
ዘ ሴይለር ፍሮም ጂብራልታር
ሻፍት ኢን አፍሪካ
ጉማ
ዚ አፍሪካን ስፓይ
ዜልዳ
አፍሪካ
ዘግሬቭ ዲገር
ዘ ግሬት ሪቤሊየን
እነዚህ ለምሳሌ ያህል የቀረቡ እንጂ የደበበ ስራዎች በርካቶች ናቸው፡፡ ከመድረክና ፊልም ስራዎቹ ባሻገር ተማሪዎችም አሰልጥኗል፡፡ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህን በብሔራዊ ቴአትር የተዋንያን ስልጠና ማዕከል ሲያቋቁሙ ከመምሃራኖቹ መሃልና በግምባር ቀደምትነት የሚጠቀሰው መምህር ደበበ ሲሆን ለተማሪዎቹም መማርያ እንዲሆን የተረጎመው የስታንስላቭስኪ የተዋናይ ሀሁ ለበርካታዎች የሙያ ተማሪዎች የሙያቸው ፊደል መቁጠርያ ሆኖ ይገ ኛል፡፡
በትርጉም በኩልም ደበበ ከቴአትር፡-
ያልታመመው በሽተኛ
ድብልቅልቅ
ጎርፉ
ከመጽሐፍ ደሞ
የዳዊት ወልደጊዮርጊስን
የደም እንባ
የራሱን ወጥ ሥራ በተመለከተ
የእምነቴ ፈተና
ሊጠቀሱ የሚችሉ ናቸው
ደበበ ለአፍሪካ ጥበብ ያለውን አመለካከትና ግንዛቤ ከቅኝ ገዢዎች ትርጓሜ ለማውጣትና ሶስተኛው ዓለም ኋላ ቀር ሲባልም በኤኮኖሚና በቴክኒዮሎጂ እንደሆነ፤ ይህም የሆነው ነጩ የአፍሪካን የዋህነት፤ እንግዳ ተቀባይነትና ሩህሩህነት መንጠላጠያ በማድረግ ቅኝ አድርገው ህሊናውን ስለዘጉበትና ስላሰሩት መሆኑን፤በባህል በኩል ግን ጨርሶ ሊደርሱበት የማይችሉትና ሊያጠፉትም ያደረጉት ሙከራ ዋጋ ቢስ ሆኖ እንደቀረ የሚያስረዳ ጥናታዊ ጽሁፍ በማቅረብ ተቀባይነትን አግኝቶ ድል ያደረገና፤ ቀደም ሲል የጀመረውን ትግል አጠናክሮ በመቀጠል በ1985 ዓ/ም እንደ አውሮፓውያን ቆጣጠር በርሊን ላይ በተካሄደው የዩኔስኮ የባህል(አይ ቲ አይ) ኢንተርናሽናል ቴአትር ኢትዮጵያን ወክሎ በመገኘት በአፍሪካ ውስጥ የመጀመርያው ፕሮፌሽናል ቴአትር ቤት የሃገር ፍቅር ቴአትር መሆኑን በማስረጃ አስደግፎ ተቀባይነትን አገኘ፡፡
በዚሁ ዓመት የዩኔስኮ የባሕል ክፍል አይ ቲ አይ የአፍሪካ ተጠሪ ሆኖ በመመረጥ፤ በዚያው ዘመን ዝምባብዌ ላይ በሚካሄደው ቴአትር ለልማትና ዕድገት ወርክሾፕ ላይ በመሪነት እንዲገኝ በዩኔስኮ ተወክሎ በመሄድ ወርክሾፑን በአጥጋቢ ችሎታውና የአመራር ብቃቱ ከመፈጸሙም ባሻገር ለብዙ ጊዜ ተሞክሮ ሲወድቅ ሲነሳ የነበረውን የአፍሪካ የመድረክ ባለሙያዎች ማሕበርን አስተባብሮ በማቋቋም የማሕበሩም መስራች ፕሬዜዳንት ሆኖ ለ12 ዓመታት መርቷል፡፡ አሁንም መስራች ፕሬዛዳንት በመባል ይጠራል፡:
ደበበ በችሎታውና በብቃቱ በማስተባበር ችሎታው ዩኔስኮ ዓለም አቀፍ የቴአትር ኢንሳይክሎፒዲያን ለማዘጋጀት ሲወስን ደበበንም አፍሪካን በመወከል የኤዲቶርያል ቦርድ አባል አድርጎ መድቦት ሥራውን በሚገባ ተወጥቷል፡፡
ደበበ ቴአትር ለልማትና ለእድገት በሚል የሚታወቀውን የቴአትር ዲሲፕሊን ስልጠና ለበርካታ ሃገራት ባለሙያዎች ያስተማረ ሲሆን በርካታ ወርክሾፖችም በየሃገራቱ እየተጋበዘ መርቷል፡፡ ይሀን ዘዴ ካዋቀሩትም አምስት አፍሪካዊ ባለሙያዎች አንዱ ደበበ ነው፡፡
ወርክሾፕ የሰጠባቸው ቦታዎች፤ ታንዛኒያ፤ኡጋንዳ፤ኬንያ፤ማላዊ፤ኮንጎ ብራዛቪል፤አይቮሪ ኮስት፤ ካሜሩን፤ ናይጄርያ፤አይርላንድ፤ብራዚል፤ሰሜን አሜሪካ፤እንግሊዝ፤ ኩባ፤ በርሊን፤ካናዳ ይገኙበታል፡፡
ደበበ ላለፉት ከ40 በላይ ዓመታት በቴአትር ጥበብ ውስጥ ኖሮ በ1995 በተካሄደው ሃገራዊ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ውስጥ ‹‹ቀስተደመና›› የፖለቲካ ፓርቲን ተቀላቅሎ፤ በኋላም ቅንጅት ሲፈጠር የምክር ቤት አባልና የሕዝብ ግንኙነት በመሆን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደረገ ቅንጅትን ለድል ያበቃ፤ የሬዲዮና የቴሌቪዥን ዝግጅቶቹ ገዢውን ፓርቲ ያንበረከኩና ቅንጅትና ያገዘፉ ነበሩ፡፡በዚህም ከሌሎች አመራሮች ጋር ለአንድ ዓመት ከአስር ወራት ለእስር ተዳርጓል፡፡ እንዲሁም በ2002 በድጋሚ ለአንድ አመት ታስሮ ተፈቷል፡፡
ደበበ በሃገሩ ለመሸለም ባይበቃም በዓለም አቀፍ ደረጃ ግን ለሽልማቶች የበቃ ባለሙያ ነው፡፡ ለዚሁ የሙያ አስተዋጽኦ ክፍተኛው ክብሩ በአትላንታ ጆርጂያ ኖቬምበር 24 የደበበ እሸቱ ቀን ተብሎ እንዲሰየም የከተማው ምክር ቤት ማጽደቁ ነው፡፡
ጋሽ ደቤ ጋደኛም ሚስትም ከሆነችው ከአልማዝ ደጀኔ ጋር 4 ልጆች እና 6 የልጅ ልጆች አሉት።
ነፍስ ይማር
viaጌጡ ተመስገን
ተዋናይ ፣ኮሜዲያን፣ አዘጋጅ ሆኖ ለረዥም ዓመታት አገልግሏል፡፡ በመድረክ ፣ በሬዲዩ፣ በቴሌቪዥን፣ በፊልም ስራ እና በጋዜጠኝነት ሙያ ሠርቷል ። በአፍሪካ የመድረክ ሙያተኞች ማህበር በሊቀመንበርነት መርቷል ፣ በአትላንታ ጆርጂያ በበረከተው የሙያው ሥራ ኖቬምበር 24 ቀን በስሙ ተሰይሞለታል። (ጋሽ ደቤ) በኢትዮጵያ ውስጥ አሁን በህይወት ካሉት አርቲስቶች ግንባር ቀደሙና አንጋፋው ነው።
መጀመሪያ በቴያትር የታዩት በመንግስቱ ለማ በተጻፈው ያላቻ ጋብቻ ሲሆን ከዚያ በአንዳንድ እንግሊዝኛ ትርኢት (The game of chess, ‘Waiting for Godot’) እንዲሁም በራዲዮም ሆነ በቴሌቪዥን ተጫወቱ።
አርቲስት ደበበ እሸቱ (ጋሽ ደቤ) ለታሪክ የሚተላለፉ ህያው ስራዎች ሰርቷል እስቲ ጋሽ ደቤ ከሰራቸው ስራዎች ውስጥ በጥቂቱ እንያቸው፤ በሃገር ውስጥ ካለው ታዋቂነትና ለሙያው ካደረገው አስተዋጽኦ ለመጠቀስ ያህል ፡-
በቤተኪነጥበባት ወቴአትር፡-
ያላቻ ጋብቻ ተዋናይ
ሮሚዎባ ዡልየት ተዋናይ
ጠልፎ በኪሴ ተዋናይም አዘጋጂም
ዳንዴው ጨቡዴ ››
ዘ ጌም ኦፍ ቼዝ (በእንግሊዝኛ) ተዋናይ
ኦቴሎ (በአንግሊዝኛ) ተዋናይም አዘጋጂም
አዳ ኦክ አራክል (በእንግሊዝኛ)ከሎ.ጸ.ገ.መ ተዋናይ
በቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ(ብሔራዊ) ቴአትር፡-
የበጋ ሌሊት ራዕይ ተዋናይ
አንድ ዓመት ከአንድ ቀን ተዋናይ
እናት ዓለም ጠኑ ተዋናይ
ኪንግ ሊር ተዋናይ
ዋናው ተቆጣጣሪ ተዋናይ
ጠያቂ ተዋናይ አዘጋጅ
በቀይካባ ስውር ደባ አዘጋጅ
ተሓድሶ አዘጋጅ
የአዘውንቶች ክበብ አዘጋጅ ተዋናይ
በሃገር ፍቅር ቴአትር፡-
ጠልፎ በኪሴ አዘጋጅ/ተዋናይ
የወፍ ጎጆ ተዋናይ
ኪንግ ሊር ተዋናይ
የቬኒሱ ነጋዴ ተዋናይ
ናትናኤል ጠቢቡ ተዋናይ
ድብልቅልቅ ተርጓሚ/ ተዋናይ
ማዕበል ተርጓሚ አዘጋጅ
በፊልም በሃገርና በዓለም አቀፍ፡-
ዘ ሴይለር ፍሮም ጂብራልታር
ሻፍት ኢን አፍሪካ
ጉማ
ዚ አፍሪካን ስፓይ
ዜልዳ
አፍሪካ
ዘግሬቭ ዲገር
ዘ ግሬት ሪቤሊየን
እነዚህ ለምሳሌ ያህል የቀረቡ እንጂ የደበበ ስራዎች በርካቶች ናቸው፡፡ ከመድረክና ፊልም ስራዎቹ ባሻገር ተማሪዎችም አሰልጥኗል፡፡ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህን በብሔራዊ ቴአትር የተዋንያን ስልጠና ማዕከል ሲያቋቁሙ ከመምሃራኖቹ መሃልና በግምባር ቀደምትነት የሚጠቀሰው መምህር ደበበ ሲሆን ለተማሪዎቹም መማርያ እንዲሆን የተረጎመው የስታንስላቭስኪ የተዋናይ ሀሁ ለበርካታዎች የሙያ ተማሪዎች የሙያቸው ፊደል መቁጠርያ ሆኖ ይገ ኛል፡፡
በትርጉም በኩልም ደበበ ከቴአትር፡-
ያልታመመው በሽተኛ
ድብልቅልቅ
ጎርፉ
ከመጽሐፍ ደሞ
የዳዊት ወልደጊዮርጊስን
የደም እንባ
የራሱን ወጥ ሥራ በተመለከተ
የእምነቴ ፈተና
ሊጠቀሱ የሚችሉ ናቸው
ደበበ ለአፍሪካ ጥበብ ያለውን አመለካከትና ግንዛቤ ከቅኝ ገዢዎች ትርጓሜ ለማውጣትና ሶስተኛው ዓለም ኋላ ቀር ሲባልም በኤኮኖሚና በቴክኒዮሎጂ እንደሆነ፤ ይህም የሆነው ነጩ የአፍሪካን የዋህነት፤ እንግዳ ተቀባይነትና ሩህሩህነት መንጠላጠያ በማድረግ ቅኝ አድርገው ህሊናውን ስለዘጉበትና ስላሰሩት መሆኑን፤በባህል በኩል ግን ጨርሶ ሊደርሱበት የማይችሉትና ሊያጠፉትም ያደረጉት ሙከራ ዋጋ ቢስ ሆኖ እንደቀረ የሚያስረዳ ጥናታዊ ጽሁፍ በማቅረብ ተቀባይነትን አግኝቶ ድል ያደረገና፤ ቀደም ሲል የጀመረውን ትግል አጠናክሮ በመቀጠል በ1985 ዓ/ም እንደ አውሮፓውያን ቆጣጠር በርሊን ላይ በተካሄደው የዩኔስኮ የባህል(አይ ቲ አይ) ኢንተርናሽናል ቴአትር ኢትዮጵያን ወክሎ በመገኘት በአፍሪካ ውስጥ የመጀመርያው ፕሮፌሽናል ቴአትር ቤት የሃገር ፍቅር ቴአትር መሆኑን በማስረጃ አስደግፎ ተቀባይነትን አገኘ፡፡
በዚሁ ዓመት የዩኔስኮ የባሕል ክፍል አይ ቲ አይ የአፍሪካ ተጠሪ ሆኖ በመመረጥ፤ በዚያው ዘመን ዝምባብዌ ላይ በሚካሄደው ቴአትር ለልማትና ዕድገት ወርክሾፕ ላይ በመሪነት እንዲገኝ በዩኔስኮ ተወክሎ በመሄድ ወርክሾፑን በአጥጋቢ ችሎታውና የአመራር ብቃቱ ከመፈጸሙም ባሻገር ለብዙ ጊዜ ተሞክሮ ሲወድቅ ሲነሳ የነበረውን የአፍሪካ የመድረክ ባለሙያዎች ማሕበርን አስተባብሮ በማቋቋም የማሕበሩም መስራች ፕሬዜዳንት ሆኖ ለ12 ዓመታት መርቷል፡፡ አሁንም መስራች ፕሬዛዳንት በመባል ይጠራል፡:
ደበበ በችሎታውና በብቃቱ በማስተባበር ችሎታው ዩኔስኮ ዓለም አቀፍ የቴአትር ኢንሳይክሎፒዲያን ለማዘጋጀት ሲወስን ደበበንም አፍሪካን በመወከል የኤዲቶርያል ቦርድ አባል አድርጎ መድቦት ሥራውን በሚገባ ተወጥቷል፡፡
ደበበ ቴአትር ለልማትና ለእድገት በሚል የሚታወቀውን የቴአትር ዲሲፕሊን ስልጠና ለበርካታ ሃገራት ባለሙያዎች ያስተማረ ሲሆን በርካታ ወርክሾፖችም በየሃገራቱ እየተጋበዘ መርቷል፡፡ ይሀን ዘዴ ካዋቀሩትም አምስት አፍሪካዊ ባለሙያዎች አንዱ ደበበ ነው፡፡
ወርክሾፕ የሰጠባቸው ቦታዎች፤ ታንዛኒያ፤ኡጋንዳ፤ኬንያ፤ማላዊ፤ኮንጎ ብራዛቪል፤አይቮሪ ኮስት፤ ካሜሩን፤ ናይጄርያ፤አይርላንድ፤ብራዚል፤ሰሜን አሜሪካ፤እንግሊዝ፤ ኩባ፤ በርሊን፤ካናዳ ይገኙበታል፡፡
ደበበ ላለፉት ከ40 በላይ ዓመታት በቴአትር ጥበብ ውስጥ ኖሮ በ1995 በተካሄደው ሃገራዊ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ውስጥ ‹‹ቀስተደመና›› የፖለቲካ ፓርቲን ተቀላቅሎ፤ በኋላም ቅንጅት ሲፈጠር የምክር ቤት አባልና የሕዝብ ግንኙነት በመሆን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደረገ ቅንጅትን ለድል ያበቃ፤ የሬዲዮና የቴሌቪዥን ዝግጅቶቹ ገዢውን ፓርቲ ያንበረከኩና ቅንጅትና ያገዘፉ ነበሩ፡፡በዚህም ከሌሎች አመራሮች ጋር ለአንድ ዓመት ከአስር ወራት ለእስር ተዳርጓል፡፡ እንዲሁም በ2002 በድጋሚ ለአንድ አመት ታስሮ ተፈቷል፡፡
ደበበ በሃገሩ ለመሸለም ባይበቃም በዓለም አቀፍ ደረጃ ግን ለሽልማቶች የበቃ ባለሙያ ነው፡፡ ለዚሁ የሙያ አስተዋጽኦ ክፍተኛው ክብሩ በአትላንታ ጆርጂያ ኖቬምበር 24 የደበበ እሸቱ ቀን ተብሎ እንዲሰየም የከተማው ምክር ቤት ማጽደቁ ነው፡፡
ጋሽ ደቤ ጋደኛም ሚስትም ከሆነችው ከአልማዝ ደጀኔ ጋር 4 ልጆች እና 6 የልጅ ልጆች አሉት።
ነፍስ ይማር
viaጌጡ ተመስገን
10 months ago
የኪነ ጥበቡ ዋርካ አርፈዋል
#ethiopia | አንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።
በሕክምና በተለያዩ ሆስፒታሎች ይከታተሉ ነበር።
***
ጋሽ ደቤ !
ተዋናይ ፣ኮሜዲያን፣ አዘጋጅ ሆኖ ለረዥም ዓመታት አገልግሏል፡፡ በመድረክ ፣ በሬዲዩ፣ በቴሌቪዥን፣ በፊልም ስራ እና በጋዜጠኝነት ሙያ ሠርቷል ። በአፍሪካ የመድረክ ሙያተኞች ማህበር በሊቀመንበርነት መርቷል ፣ በአትላንታ ጆርጂያ በበረከተው የሙያው ሥራ ኖቬምበር 24 ቀን በስሙ ተሰይሞለታል። (ጋሽ ደቤ) በኢትዮጵያ ውስጥ አሁን በህይወት ካሉት አርቲስቶች ግንባር ቀደሙና አንጋፋው ነው።
መጀመሪያ በቴያትር የታዩት በመንግስቱ ለማ በተጻፈው ያላቻ ጋብቻ ሲሆን ከዚያ በአንዳንድ እንግሊዝኛ ትርኢት (The game of chess, ‘Waiting for Godot’) እንዲሁም በራዲዮም ሆነ በቴሌቪዥን ተጫወቱ።
አርቲስት ደበበ እሸቱ (ጋሽ ደቤ) ለታሪክ የሚተላለፉ ህያው ስራዎች ሰርቷል እስቲ ጋሽ ደቤ ከሰራቸው ስራዎች ውስጥ በጥቂቱ እንያቸው፤ በሃገር ውስጥ ካለው ታዋቂነትና ለሙያው ካደረገው አስተዋጽኦ ለመጠቀስ ያህል ፡-
በቤተኪነጥበባት ወቴአትር፡-
ያላቻ ጋብቻ ተዋናይ
ሮሚዎባ ዡልየት ተዋናይ
ጠልፎ በኪሴ ተዋናይም አዘጋጂም
ዳንዴው ጨቡዴ ››
ዘ ጌም ኦፍ ቼዝ (በእንግሊዝኛ) ተዋናይ
ኦቴሎ (በአንግሊዝኛ) ተዋናይም አዘጋጂም
አዳ ኦክ አራክል (በእንግሊዝኛ)ከሎ.ጸ.ገ.መ ተዋናይ
በቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ(ብሔራዊ) ቴአትር፡-
የበጋ ሌሊት ራዕይ ተዋናይ
አንድ ዓመት ከአንድ ቀን ተዋናይ
እናት ዓለም ጠኑ ተዋናይ
ኪንግ ሊር ተዋናይ
ዋናው ተቆጣጣሪ ተዋናይ
ጠያቂ ተዋናይ አዘጋጅ
በቀይካባ ስውር ደባ አዘጋጅ
ተሓድሶ አዘጋጅ
የአዘውንቶች ክበብ አዘጋጅ ተዋናይ
በሃገር ፍቅር ቴአትር፡-
ጠልፎ በኪሴ አዘጋጅ/ተዋናይ
የወፍ ጎጆ ተዋናይ
ኪንግ ሊር ተዋናይ
የቬኒሱ ነጋዴ ተዋናይ
ናትናኤል ጠቢቡ ተዋናይ
ድብልቅልቅ ተርጓሚ/ ተዋናይ
ማዕበል ተርጓሚ አዘጋጅ
በፊልም በሃገርና በዓለም አቀፍ፡-
ዘ ሴይለር ፍሮም ጂብራልታር
ሻፍት ኢን አፍሪካ
ጉማ
ዚ አፍሪካን ስፓይ
ዜልዳ
አፍሪካ
ዘግሬቭ ዲገር
ዘ ግሬት ሪቤሊየን
እነዚህ ለምሳሌ ያህል የቀረቡ እንጂ የደበበ ስራዎች በርካቶች ናቸው፡፡ ከመድረክና ፊልም ስራዎቹ ባሻገር ተማሪዎችም አሰልጥኗል፡፡ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህን በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር የተዋንያን ስልጠና ማዕከል ሲያቋቁሙ ከመምህራኖቹ መሃልና በግምባር ቀደምትነት የሚጠቀሰው መምህር ደበበ ሲሆን ለተማሪዎቹም መማርያ እንዲሆን የተረጎመው የስታንስላቭስኪ የተዋናይ ሀሁ ለበርካታዎች የሙያ ተማሪዎች የሙያቸው ፊደል መቁጠርያ ሆኖ ይገኛል፡፡
በትርጉም በኩልም ደበበ ከቴአትር፡-
ያልታመመው በሽተኛ
ድብልቅልቅ
ጎርፉ
ከመጽሐፍ ደሞ
የዳዊት ወልደጊዮርጊስን
የደም እንባ
የራሱን ወጥ ሥራ በተመለከተ
የእምነቴ ፈተና
ሊጠቀሱ የሚችሉ ናቸው
ደበበ ለአፍሪካ ጥበብ ያለውን አመለካከትና ግንዛቤ ከቅኝ ገዢዎች ትርጓሜ ለማውጣትና ሦስተኛው ዓለም ኋላ ቀር ሲባልም በኤኮኖሚና በቴክኒዮሎጂ እንደሆነ፤ ይህም የሆነው ነጩ የአፍሪካን የዋህነት፤ እንግዳ ተቀባይነትና ሩህሩህነት መንጠላጠያ በማድረግ ቅኝ አድርገው ህሊናውን ስለዘጉበትና ስላሰሩት መሆኑን፤ በባህል በኩል ግን ጨርሶ ሊደርሱበት የማይችሉትና ሊያጠፉትም ያደረጉት ሙከራ ዋጋ ቢስ ሆኖ እንደቀረ የሚያስረዳ ጥናታዊ ጽሁፍ በማቅረብ ተቀባይነትን አግኝቶ ድል ያደረገና፤ ቀደም ሲል የጀመረውን ትግል አጠናክሮ በመቀጠል በ1985 ዓ.ም እንደ አውሮፓውያን ቆጣጠር በርሊን ላይ በተካሄደው የዩኔስኮ የባህል(አይ ቲ አይ) ኢንተርናሽናል ቴአትር ኢትዮጵያን ወክሎ በመገኘት በአፍሪካ ውስጥ የመጀመርያው ፕሮፌሽናል ቴአትር ቤት የሃገር ፍቅር ቴአትር መሆኑን በማስረጃ አስደግፎ ተቀባይነትን አገኝቷል፡፡
በዚሁ ዓመት የዩኔስኮ የባሕል ክፍል አይ ቲ አይ የአፍሪካ ተጠሪ ሆኖ በመመረጥ፤ በዚያው ዘመን ዝምባብዌ ላይ በሚካሄደው ቴአትር ለልማትና ዕድገት ወርክሾፕ ላይ በመሪነት እንዲገኝ በዩኔስኮ ተወክሎ በመሄድ ወርክሾፑን በአጥጋቢ ችሎታውና የአመራር ብቃቱ ከመፈጸሙም ባሻገር ለብዙ ጊዜ ተሞክሮ ሲወድቅ ሲነሳ የነበረውን የአፍሪካ የመድረክ ባለሙያዎች ማሕበርን አስተባብሮ በማቋቋም የማሕበሩም መስራች ፕሬዜዳንት ሆኖ ለ12 ዓመታት መርቷል፡፡ አሁንም መሥራች ፕሬዚዳንት በመባል ይጠራል፡:
ደበበ በችሎታውና በብቃቱ በማስተባበር ችሎታው ዩኔስኮ ዓለም አቀፍ የቴአትር ኢንሳይክሎፒዲያን ለማዘጋጀት ሲወስን ደበበንም አፍሪካን በመወከል የኤዲቶርያል ቦርድ አባል አድርጎ መድቦት ሥራውን በሚገባ ተወጥቷል፡፡
ደበበ ቴአትር ለልማትና ለእድገት በሚል የሚታወቀውን የቴአትር ዲሲፕሊን ስልጠና ለበርካታ ሃገራት ባለሙያዎች ያስተማረ ሲሆን በርካታ ወርክሾፖችም በየሃገራቱ እየተጋበዘ መርቷል፡፡ ይህን ዘዴ ካዋቀሩትም አምስት አፍሪካዊ ባለሙያዎች አንዱ ደበበ ነው፡፡
ወርክሾፕ የሰጠባቸው ቦታዎች፤ ታንዛኒያ፤ ኡጋንዳ፤ ኬንያ፤ማላዊ፤ ኮንጎ ብራዛቪል፤ አይቮሪ ኮስት፤ ካሜሩን፤ ናይጄርያ፤ አይርላንድ፤ ብራዚል፤ ሰሜን አሜሪካ፤ እንግሊዝ፤ ኩባ፤ በርሊን፤ ካናዳ ይገኙበታል፡፡
ደበበ ላለፉት ከ40 በላይ ዓመታት በቴአትር ጥበብ ውስጥ ኖሮ በ1995 በተካሄደው ሃገራዊ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ውስጥ ‹‹ቀስተደመና›› የፖለቲካ ፓርቲን ተቀላቅሎ፤ በኋላም ቅንጅት ሲፈጠር የምክር ቤት አባልና የሕዝብ ግንኙነት በመሆን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደረገ ቅንጅትን ለድል ያበቃ፤ የሬዲዮና የቴሌቪዥን ዝግጅቶቹ ቅንጅትን ያገዘፉ ነበሩ፡፡በዚህም ከሌሎች አመራሮች ጋር ለአንድ ዓመት ከአስር ወራት ለእስር ተዳርጓል፡፡ እንዲሁም በ2002 በድጋሚ ለአንድ አመት ታስሮ ተፈቷል፡፡
ደበበ በሃገሩ ለመሸለም ባይበቃም በዓለም አቀፍ ደረጃ ግን ለሽልማቶች የበቃ ባለሙያ ነው፡፡ ለዚሁ የሙያ አስተዋጽኦ ክፍተኛው ክብሩ በአትላንታ ጆርጂያ ኖቬምበር 24 የደበበ እሸቱ ቀን ተብሎ እንዲሰየም የከተማው ምክር ቤት ማጽደቁ ነው፡፡
ጋሽ ደቤ ጋደኛም፤ ሚስትም ከሆነችው ከአልማዝ ደጀኔ ጋር 4 ልጆች እና 6 የልጅ ልጆች አሉት።
ነፍስ ይማር
#ethiopia | አንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።
በሕክምና በተለያዩ ሆስፒታሎች ይከታተሉ ነበር።
***
ጋሽ ደቤ !
ተዋናይ ፣ኮሜዲያን፣ አዘጋጅ ሆኖ ለረዥም ዓመታት አገልግሏል፡፡ በመድረክ ፣ በሬዲዩ፣ በቴሌቪዥን፣ በፊልም ስራ እና በጋዜጠኝነት ሙያ ሠርቷል ። በአፍሪካ የመድረክ ሙያተኞች ማህበር በሊቀመንበርነት መርቷል ፣ በአትላንታ ጆርጂያ በበረከተው የሙያው ሥራ ኖቬምበር 24 ቀን በስሙ ተሰይሞለታል። (ጋሽ ደቤ) በኢትዮጵያ ውስጥ አሁን በህይወት ካሉት አርቲስቶች ግንባር ቀደሙና አንጋፋው ነው።
መጀመሪያ በቴያትር የታዩት በመንግስቱ ለማ በተጻፈው ያላቻ ጋብቻ ሲሆን ከዚያ በአንዳንድ እንግሊዝኛ ትርኢት (The game of chess, ‘Waiting for Godot’) እንዲሁም በራዲዮም ሆነ በቴሌቪዥን ተጫወቱ።
አርቲስት ደበበ እሸቱ (ጋሽ ደቤ) ለታሪክ የሚተላለፉ ህያው ስራዎች ሰርቷል እስቲ ጋሽ ደቤ ከሰራቸው ስራዎች ውስጥ በጥቂቱ እንያቸው፤ በሃገር ውስጥ ካለው ታዋቂነትና ለሙያው ካደረገው አስተዋጽኦ ለመጠቀስ ያህል ፡-
በቤተኪነጥበባት ወቴአትር፡-
ያላቻ ጋብቻ ተዋናይ
ሮሚዎባ ዡልየት ተዋናይ
ጠልፎ በኪሴ ተዋናይም አዘጋጂም
ዳንዴው ጨቡዴ ››
ዘ ጌም ኦፍ ቼዝ (በእንግሊዝኛ) ተዋናይ
ኦቴሎ (በአንግሊዝኛ) ተዋናይም አዘጋጂም
አዳ ኦክ አራክል (በእንግሊዝኛ)ከሎ.ጸ.ገ.መ ተዋናይ
በቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ(ብሔራዊ) ቴአትር፡-
የበጋ ሌሊት ራዕይ ተዋናይ
አንድ ዓመት ከአንድ ቀን ተዋናይ
እናት ዓለም ጠኑ ተዋናይ
ኪንግ ሊር ተዋናይ
ዋናው ተቆጣጣሪ ተዋናይ
ጠያቂ ተዋናይ አዘጋጅ
በቀይካባ ስውር ደባ አዘጋጅ
ተሓድሶ አዘጋጅ
የአዘውንቶች ክበብ አዘጋጅ ተዋናይ
በሃገር ፍቅር ቴአትር፡-
ጠልፎ በኪሴ አዘጋጅ/ተዋናይ
የወፍ ጎጆ ተዋናይ
ኪንግ ሊር ተዋናይ
የቬኒሱ ነጋዴ ተዋናይ
ናትናኤል ጠቢቡ ተዋናይ
ድብልቅልቅ ተርጓሚ/ ተዋናይ
ማዕበል ተርጓሚ አዘጋጅ
በፊልም በሃገርና በዓለም አቀፍ፡-
ዘ ሴይለር ፍሮም ጂብራልታር
ሻፍት ኢን አፍሪካ
ጉማ
ዚ አፍሪካን ስፓይ
ዜልዳ
አፍሪካ
ዘግሬቭ ዲገር
ዘ ግሬት ሪቤሊየን
እነዚህ ለምሳሌ ያህል የቀረቡ እንጂ የደበበ ስራዎች በርካቶች ናቸው፡፡ ከመድረክና ፊልም ስራዎቹ ባሻገር ተማሪዎችም አሰልጥኗል፡፡ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህን በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር የተዋንያን ስልጠና ማዕከል ሲያቋቁሙ ከመምህራኖቹ መሃልና በግምባር ቀደምትነት የሚጠቀሰው መምህር ደበበ ሲሆን ለተማሪዎቹም መማርያ እንዲሆን የተረጎመው የስታንስላቭስኪ የተዋናይ ሀሁ ለበርካታዎች የሙያ ተማሪዎች የሙያቸው ፊደል መቁጠርያ ሆኖ ይገኛል፡፡
በትርጉም በኩልም ደበበ ከቴአትር፡-
ያልታመመው በሽተኛ
ድብልቅልቅ
ጎርፉ
ከመጽሐፍ ደሞ
የዳዊት ወልደጊዮርጊስን
የደም እንባ
የራሱን ወጥ ሥራ በተመለከተ
የእምነቴ ፈተና
ሊጠቀሱ የሚችሉ ናቸው
ደበበ ለአፍሪካ ጥበብ ያለውን አመለካከትና ግንዛቤ ከቅኝ ገዢዎች ትርጓሜ ለማውጣትና ሦስተኛው ዓለም ኋላ ቀር ሲባልም በኤኮኖሚና በቴክኒዮሎጂ እንደሆነ፤ ይህም የሆነው ነጩ የአፍሪካን የዋህነት፤ እንግዳ ተቀባይነትና ሩህሩህነት መንጠላጠያ በማድረግ ቅኝ አድርገው ህሊናውን ስለዘጉበትና ስላሰሩት መሆኑን፤ በባህል በኩል ግን ጨርሶ ሊደርሱበት የማይችሉትና ሊያጠፉትም ያደረጉት ሙከራ ዋጋ ቢስ ሆኖ እንደቀረ የሚያስረዳ ጥናታዊ ጽሁፍ በማቅረብ ተቀባይነትን አግኝቶ ድል ያደረገና፤ ቀደም ሲል የጀመረውን ትግል አጠናክሮ በመቀጠል በ1985 ዓ.ም እንደ አውሮፓውያን ቆጣጠር በርሊን ላይ በተካሄደው የዩኔስኮ የባህል(አይ ቲ አይ) ኢንተርናሽናል ቴአትር ኢትዮጵያን ወክሎ በመገኘት በአፍሪካ ውስጥ የመጀመርያው ፕሮፌሽናል ቴአትር ቤት የሃገር ፍቅር ቴአትር መሆኑን በማስረጃ አስደግፎ ተቀባይነትን አገኝቷል፡፡
በዚሁ ዓመት የዩኔስኮ የባሕል ክፍል አይ ቲ አይ የአፍሪካ ተጠሪ ሆኖ በመመረጥ፤ በዚያው ዘመን ዝምባብዌ ላይ በሚካሄደው ቴአትር ለልማትና ዕድገት ወርክሾፕ ላይ በመሪነት እንዲገኝ በዩኔስኮ ተወክሎ በመሄድ ወርክሾፑን በአጥጋቢ ችሎታውና የአመራር ብቃቱ ከመፈጸሙም ባሻገር ለብዙ ጊዜ ተሞክሮ ሲወድቅ ሲነሳ የነበረውን የአፍሪካ የመድረክ ባለሙያዎች ማሕበርን አስተባብሮ በማቋቋም የማሕበሩም መስራች ፕሬዜዳንት ሆኖ ለ12 ዓመታት መርቷል፡፡ አሁንም መሥራች ፕሬዚዳንት በመባል ይጠራል፡:
ደበበ በችሎታውና በብቃቱ በማስተባበር ችሎታው ዩኔስኮ ዓለም አቀፍ የቴአትር ኢንሳይክሎፒዲያን ለማዘጋጀት ሲወስን ደበበንም አፍሪካን በመወከል የኤዲቶርያል ቦርድ አባል አድርጎ መድቦት ሥራውን በሚገባ ተወጥቷል፡፡
ደበበ ቴአትር ለልማትና ለእድገት በሚል የሚታወቀውን የቴአትር ዲሲፕሊን ስልጠና ለበርካታ ሃገራት ባለሙያዎች ያስተማረ ሲሆን በርካታ ወርክሾፖችም በየሃገራቱ እየተጋበዘ መርቷል፡፡ ይህን ዘዴ ካዋቀሩትም አምስት አፍሪካዊ ባለሙያዎች አንዱ ደበበ ነው፡፡
ወርክሾፕ የሰጠባቸው ቦታዎች፤ ታንዛኒያ፤ ኡጋንዳ፤ ኬንያ፤ማላዊ፤ ኮንጎ ብራዛቪል፤ አይቮሪ ኮስት፤ ካሜሩን፤ ናይጄርያ፤ አይርላንድ፤ ብራዚል፤ ሰሜን አሜሪካ፤ እንግሊዝ፤ ኩባ፤ በርሊን፤ ካናዳ ይገኙበታል፡፡
ደበበ ላለፉት ከ40 በላይ ዓመታት በቴአትር ጥበብ ውስጥ ኖሮ በ1995 በተካሄደው ሃገራዊ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ውስጥ ‹‹ቀስተደመና›› የፖለቲካ ፓርቲን ተቀላቅሎ፤ በኋላም ቅንጅት ሲፈጠር የምክር ቤት አባልና የሕዝብ ግንኙነት በመሆን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደረገ ቅንጅትን ለድል ያበቃ፤ የሬዲዮና የቴሌቪዥን ዝግጅቶቹ ቅንጅትን ያገዘፉ ነበሩ፡፡በዚህም ከሌሎች አመራሮች ጋር ለአንድ ዓመት ከአስር ወራት ለእስር ተዳርጓል፡፡ እንዲሁም በ2002 በድጋሚ ለአንድ አመት ታስሮ ተፈቷል፡፡
ደበበ በሃገሩ ለመሸለም ባይበቃም በዓለም አቀፍ ደረጃ ግን ለሽልማቶች የበቃ ባለሙያ ነው፡፡ ለዚሁ የሙያ አስተዋጽኦ ክፍተኛው ክብሩ በአትላንታ ጆርጂያ ኖቬምበር 24 የደበበ እሸቱ ቀን ተብሎ እንዲሰየም የከተማው ምክር ቤት ማጽደቁ ነው፡፡
ጋሽ ደቤ ጋደኛም፤ ሚስትም ከሆነችው ከአልማዝ ደጀኔ ጋር 4 ልጆች እና 6 የልጅ ልጆች አሉት።
ነፍስ ይማር
Sponsored by
Surafel
10 months ago
📌 ላልተዘመረለት ጀግና የኢ/አ/ፌ ሀዉልት አቆመለት!!
#ethiopia | ተባባሪ ፕሮፌሰር በዛብህ ወልዴ ሃታኡ (ዶ/ር)፤ ከሐምሌ 23/1952 – ነሃሴ 19/2014 ዓ.ም
👉 ተባባሪ ፕሮፌሰር በዛብህ ወልዴ በቀድሞው ባሌ ክፍለ ሀገር ልዩ ስሙ ጊኒር በሚባል አካባቢ ሐምሌ 23/1952 ዓ.ም ተወለዱ፡፡
የእስፖርት ሳይንሱ አባት ዶ/ር በዛብህ ወልዴ ሰብእናው፥ ሙያው እና ሕይወቱ በአንድ ቃል ይገለጽ ቢባል ያ ቃል "ፈውስ" ነው።
እጁ የአካል ሰብራትን ሲጠግን ንግግሩ መንፈስን ከድቀት ይታደጋል።
ሁሉንም ሰው እንደየመልኩና እንደየ አመሉ በፍቅርና ከልብ በመነጨ ፈገግታ መቀበሉ፤ ለኹሉም የሚዳረስ የጊዜ በረከት የታደለ መሆኑ ወዳጆቹን ዘወትር እንዳስደነቀ ይኖራል።
ረጅም ቁመናው ብዙዎችን ለማስጠለል ለሚችለው ጠባዩ ጥሩ ምሳሌ ይሆናል።
ዕድልና አጋጣሚ አግኝተን ባወቅነው ፤በቀረብነው ፥ ባወጋነው ዘንድ የማይረሳ የሰው አብነት ነው።
ቸሩ እግዚአብሔር ነፍሱን ከደጋጎች ጎራ እንዲያሳርፍ እንጸልያለን።
በትምህርቱ ዘርፍ የነበራቸው አበርክቶ
***
➡️ ትምህርታቸውን በጅማ መምህራን ማሰልጠኛ ተቋም፣ በኮተቤ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጅ ፤በቡልጋሪያ አገር በሶፊያ ሰውነት ማጎልመሻ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፤በፖላንድ አገር በሚገኘው ዋርሶ የሰውነት ማጎልመሻ ማእከል ተከታትለው በከፍተኛ ማዕረግ ተመርቀዋል ።
➡️ በኮተቤ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጅና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት፣ በምርምር ስራዎችና በማህበረሰብ አገልግሎት የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል፤
➡️ ከመጀመሪያ ደረጃ እስከ ሶስተኛ ዲግሪ መርሀ-ግብሮች በመምህርነት አገልግለዋል፤
➡️ በአገር ውስጥና ከአገር ውጪ በሚገኙ የተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በተጋበዥ መምህርነት፣ ተማሪዎችን በማማከርና የምርምር ስራዎችን በማቅረብ አገልግለዋል፤
በስፖርቱ ዘርፍ ነበራቸው አበርክቶ
***
በኢትዮጵያ ስፖርት ታሪክ ‹‹የአትሌቲክስ አባት›› ተብለው ከሚታወቁ የዘርፉ ምሁራንና ባለሙያዎች መካከል በግንባር ቀደምትነት የሚጠሩ አንጋፋና ባለውለታ ነበሩ፡፡
ከ20 አመት በላይ በአትሌቲክሱ ላይ እጅግ ደማቅ አሻራቸውን ያሳረፉ ሲሆን ከብዙው በጥቂቱ ለመጥቀስ:-
➡️ በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በዋና ፀኃፊነት፣
➡️ በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በዋና ፀኃፊነት፣ በሥራ አስፈጻሚ ኮ/አባልነት፣ በአቃቢ ነዋይነት አገልግለዋል።
➡️ በአትላንታና በሲድኒ ኦሎምፒክ በዝግጅትና በአመራር፤
➡️ በኤድመንተን ዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በአመራርነት፤
➡️ በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በፕሬዚዳንትነት፣
➡️ በአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
በፕሬዜዳንትነት እንዲሁም
➡️ በቴክኒክና በህክምና ኮሚቴ ሰብሳቢነት ፣በአቃቤ ነዋይነት እስከ ህልፈተ ህይወታቸው ድረስ ደከመኝ፣ ሰለቸኝ ሳይሉ አትሌቲክሱን ያገለገሉ የኢትዮጵያ ባለውለታ በመሆናቸው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሙሉ ወጪዉን በመሸፈን የመታሰቢያ ሐውልት በስማቸው አሰርቶላቸዋል።
ሐዉልቱም የፊታችን ጳጉሜ 2 በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ⛪ ቤተክርስቲያን ወዳጅ ዘመዶቹ ፣የሙያ አጋሮቹ እንዲሁም የቀድሞ ተማሪዎቹ በተገኙበት የሚመረቅ ይሆናል።
ተባባሪ ፕሮፌሰር በዛብህ ወልዴ ለኢትዮጵያ እስፖርት ላደረከዉ አስተዋፅኦ ሁሌም እናመሰግንሀለን ።🙏🙏🙏🙏🙏
ተባባሪ ፕሮፌሰር በዛብህ ወልዴ ሃታኡ ነሃሴ 19/2014 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፡፡
በተስፋዬ አብዲሳ (ቻይና አብዲ)
#ethiopia | ተባባሪ ፕሮፌሰር በዛብህ ወልዴ ሃታኡ (ዶ/ር)፤ ከሐምሌ 23/1952 – ነሃሴ 19/2014 ዓ.ም
👉 ተባባሪ ፕሮፌሰር በዛብህ ወልዴ በቀድሞው ባሌ ክፍለ ሀገር ልዩ ስሙ ጊኒር በሚባል አካባቢ ሐምሌ 23/1952 ዓ.ም ተወለዱ፡፡
የእስፖርት ሳይንሱ አባት ዶ/ር በዛብህ ወልዴ ሰብእናው፥ ሙያው እና ሕይወቱ በአንድ ቃል ይገለጽ ቢባል ያ ቃል "ፈውስ" ነው።
እጁ የአካል ሰብራትን ሲጠግን ንግግሩ መንፈስን ከድቀት ይታደጋል።
ሁሉንም ሰው እንደየመልኩና እንደየ አመሉ በፍቅርና ከልብ በመነጨ ፈገግታ መቀበሉ፤ ለኹሉም የሚዳረስ የጊዜ በረከት የታደለ መሆኑ ወዳጆቹን ዘወትር እንዳስደነቀ ይኖራል።
ረጅም ቁመናው ብዙዎችን ለማስጠለል ለሚችለው ጠባዩ ጥሩ ምሳሌ ይሆናል።
ዕድልና አጋጣሚ አግኝተን ባወቅነው ፤በቀረብነው ፥ ባወጋነው ዘንድ የማይረሳ የሰው አብነት ነው።
ቸሩ እግዚአብሔር ነፍሱን ከደጋጎች ጎራ እንዲያሳርፍ እንጸልያለን።
በትምህርቱ ዘርፍ የነበራቸው አበርክቶ
***
➡️ ትምህርታቸውን በጅማ መምህራን ማሰልጠኛ ተቋም፣ በኮተቤ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጅ ፤በቡልጋሪያ አገር በሶፊያ ሰውነት ማጎልመሻ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፤በፖላንድ አገር በሚገኘው ዋርሶ የሰውነት ማጎልመሻ ማእከል ተከታትለው በከፍተኛ ማዕረግ ተመርቀዋል ።
➡️ በኮተቤ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጅና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት፣ በምርምር ስራዎችና በማህበረሰብ አገልግሎት የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል፤
➡️ ከመጀመሪያ ደረጃ እስከ ሶስተኛ ዲግሪ መርሀ-ግብሮች በመምህርነት አገልግለዋል፤
➡️ በአገር ውስጥና ከአገር ውጪ በሚገኙ የተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በተጋበዥ መምህርነት፣ ተማሪዎችን በማማከርና የምርምር ስራዎችን በማቅረብ አገልግለዋል፤
በስፖርቱ ዘርፍ ነበራቸው አበርክቶ
***
በኢትዮጵያ ስፖርት ታሪክ ‹‹የአትሌቲክስ አባት›› ተብለው ከሚታወቁ የዘርፉ ምሁራንና ባለሙያዎች መካከል በግንባር ቀደምትነት የሚጠሩ አንጋፋና ባለውለታ ነበሩ፡፡
ከ20 አመት በላይ በአትሌቲክሱ ላይ እጅግ ደማቅ አሻራቸውን ያሳረፉ ሲሆን ከብዙው በጥቂቱ ለመጥቀስ:-
➡️ በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በዋና ፀኃፊነት፣
➡️ በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በዋና ፀኃፊነት፣ በሥራ አስፈጻሚ ኮ/አባልነት፣ በአቃቢ ነዋይነት አገልግለዋል።
➡️ በአትላንታና በሲድኒ ኦሎምፒክ በዝግጅትና በአመራር፤
➡️ በኤድመንተን ዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በአመራርነት፤
➡️ በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በፕሬዚዳንትነት፣
➡️ በአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
በፕሬዜዳንትነት እንዲሁም
➡️ በቴክኒክና በህክምና ኮሚቴ ሰብሳቢነት ፣በአቃቤ ነዋይነት እስከ ህልፈተ ህይወታቸው ድረስ ደከመኝ፣ ሰለቸኝ ሳይሉ አትሌቲክሱን ያገለገሉ የኢትዮጵያ ባለውለታ በመሆናቸው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሙሉ ወጪዉን በመሸፈን የመታሰቢያ ሐውልት በስማቸው አሰርቶላቸዋል።
ሐዉልቱም የፊታችን ጳጉሜ 2 በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ⛪ ቤተክርስቲያን ወዳጅ ዘመዶቹ ፣የሙያ አጋሮቹ እንዲሁም የቀድሞ ተማሪዎቹ በተገኙበት የሚመረቅ ይሆናል።
ተባባሪ ፕሮፌሰር በዛብህ ወልዴ ለኢትዮጵያ እስፖርት ላደረከዉ አስተዋፅኦ ሁሌም እናመሰግንሀለን ።🙏🙏🙏🙏🙏
ተባባሪ ፕሮፌሰር በዛብህ ወልዴ ሃታኡ ነሃሴ 19/2014 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፡፡
በተስፋዬ አብዲሳ (ቻይና አብዲ)
11 months ago
የአንጋፋው አቃቤ እምነት ዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌ የሦስት አስርት ዓመታት የአገልግሎት አበርክቶ እውቅና መስጫ መርሃ ግብር በአትላንታ ከተማ ተካሄደ
#ethiopia | በዚህ ጁላይ 27/2025 በአትላንታ ርኆቦት የኢትዮጵያውያን ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን በተካሄደ መርሃ ግብር ላይ በከተማዋ የሚገኙ እና ከተለያዩ የአሜሪካ ግዛቶች የመጡ የዶ/ር ተሰፋዬ አገልግሎት ተጠቃሚዎች፣ የቤተ ክርስቲያናት መጋቢያን እና መሪዎች፣ እንዲሁም ቤተሰቦቹ እና ወዳጆቹ በመገኘት ለአገልጋዩ አክብሮታቸውን የገለጹ ሲሆን ደጋፊ በማጣት እየተዳከመ የመጣውን የእቅበተ እምነት አገልግሎቱን በጽናት እንዲቀጥልም አበረታተውታል፡፡
በተካሄደው የእውቅና እና የምስጋና ፕሮግራም ላይም ከአዲስ አበባ እነ ጋሽ ንጉሤ ቡልቻን የመሳሰሉ አንጋፋ አገልጋዮች እንዲሁም በዶ/ር ተስፋዬ አገልግሎት ከተለያዩ የስህተት ትምህርት አስተማሪ ቤተ እምነቶች ወጥተው በወንጌል አማኝ ቤተ ክርስቲያናት የሚያገለግሉ አገልጋዮች እና አማኞች ስለ ዶ/ር ተስፋዬ እና የሚሰጠው አገልግሎት ጠቀሜታ የቪዲዮ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ መገኘት የቻሉ የተለያዩ ቤተ ክርስቲያናት መጋቢያን እና አገልጋዮችም የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በከፋ ሁኔታ እየተስፋፋ የመጣውን የተለያዩ የኑፋቄ አስተምህሮዎችን የሚያጋልጡ እና ቤተክርስቲያንን በዚህ ዙሪያ ተዘጋጅታ እንድትቆም በማስታጠቅ አገልግሎት የተሰማሩ እንደ ዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌ ያሉ አገልጋዮችን መደገፍ አማራጭ የሌለው አደራዋ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በዕለቱ የእግዚአብሔር ቃል ስብከት እና የዝማሬ አምልኮ የተከናወነ ሲሆን በቅርቡ በዶ/ር ተስፋዬ ተጽፎ በሚመራው ተስፋ ዐቃብያነ ክርስትና ማኅበር አማካኝነት የታተመው “የሐዋሪያት ቤተ ክርስቲያን” ኑፋቄ መጽሐፍ ጠቀሜታ ዳሰሳ ቀርቧል፡፡
በመርሃ ግብሩ ፍጻሜ ላይም በዕለቱ የተገኙ የመርሃ ግብሩ ታዳሚያን እና ለዚህ አገልግሎት ቀናዒ የሆኑ የእውነተኛው ወንጌል ቤተሰቦች የዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌ አገልግሎት ደጋፊ በመሆን ከጎኑ እንዲቆሙ እና ድጋፍ በማጣት ተስፋ ቆርጦ አገልግሎቱን እንዳያቆም በቋሚ ደጋፊነት ከጎኑ እንዲሰለፉ በፕሮግራሙ አዘጋጆች ጥሪ ቀርቧል፡፡
ይህንኑ በቀላሉ ለማከናወን እንዲቻልም የተሻሻለው የአገልግሎቱ ድረ ገጽ እና በቋሚነት የአገልግሎቱ ደጋፍ አድራጊ እና ተጠቃሚ ደንበኝነት መመዝገቢያ መተግበሪያ ተዋውቋል፡፡ ዶ/ር ተስፋዬ እስከዛሬ በታማኝነት ዋጋ በመክፈል ስለሰጠው ያላቀ አገልግሎትም የእውቅና ስጦታ በመርሃ ግብሩ አዘጋጆች አማካኝነት ተበርክቶለታል፡፡
በዕለቱ መርሃ ግብር ማጠቃለያ ላይም የዕቅበተ እምነት አገልግሎትን ለመስጠት ከሦስት አስርት ዓመታት በላይ በጽናት ዋጋ የከፈለው ዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌ አገልግሎቱ እጅግ አንገብጋቢ ሆኖ ሳለ ደጋፊ በማጣቱ የሚሰማውን ሃዘኔታ በመግለጽ በዚህ ዕለት በበጎ ፈቃደኝነት እና በራሳቸው ተነሳሽነት ይህንኑ መርሃ ግብር ላዘጋጁ ወገኖች የላቀ ምስጋናውን አቅርቧል፡፡
ከዚሁ ጋር በማያያዝም ለዓመታት የአገልግሎቱ ደጋፊዎች የሆኑትን በተለይም ልዩ ልዩ ሥራዎችን በመሥራት እርሱ የሙሉ ግዜ አገልግሎት ያለክፍያ እንዲሠራ ያስቻለችውን ባለቤቱ ሰምራዊት ኤርሚያስን እናቷን አስቴር መንግሥቴን እና በቋሚነት ድጋፍ ያደረጉለት አብያተ ክርስቲያናት እና ግለሰብ የአገልግሎቱ አጋሮችን አመስግኖ የመታሰቢያ የምስክር ወረቀት በማኅበሩ ስም ተበርክቶላቸዋል፡፡
እኛም የወንጌል ቤተሰቦች ሁሉhi ከዚሁ እግዚአብሔር ለኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ስጦታ አድርጎ ከሰጠው ወንድም ጎን እንዲቆሙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
#ethiopia | በዚህ ጁላይ 27/2025 በአትላንታ ርኆቦት የኢትዮጵያውያን ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን በተካሄደ መርሃ ግብር ላይ በከተማዋ የሚገኙ እና ከተለያዩ የአሜሪካ ግዛቶች የመጡ የዶ/ር ተሰፋዬ አገልግሎት ተጠቃሚዎች፣ የቤተ ክርስቲያናት መጋቢያን እና መሪዎች፣ እንዲሁም ቤተሰቦቹ እና ወዳጆቹ በመገኘት ለአገልጋዩ አክብሮታቸውን የገለጹ ሲሆን ደጋፊ በማጣት እየተዳከመ የመጣውን የእቅበተ እምነት አገልግሎቱን በጽናት እንዲቀጥልም አበረታተውታል፡፡
በተካሄደው የእውቅና እና የምስጋና ፕሮግራም ላይም ከአዲስ አበባ እነ ጋሽ ንጉሤ ቡልቻን የመሳሰሉ አንጋፋ አገልጋዮች እንዲሁም በዶ/ር ተስፋዬ አገልግሎት ከተለያዩ የስህተት ትምህርት አስተማሪ ቤተ እምነቶች ወጥተው በወንጌል አማኝ ቤተ ክርስቲያናት የሚያገለግሉ አገልጋዮች እና አማኞች ስለ ዶ/ር ተስፋዬ እና የሚሰጠው አገልግሎት ጠቀሜታ የቪዲዮ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ መገኘት የቻሉ የተለያዩ ቤተ ክርስቲያናት መጋቢያን እና አገልጋዮችም የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በከፋ ሁኔታ እየተስፋፋ የመጣውን የተለያዩ የኑፋቄ አስተምህሮዎችን የሚያጋልጡ እና ቤተክርስቲያንን በዚህ ዙሪያ ተዘጋጅታ እንድትቆም በማስታጠቅ አገልግሎት የተሰማሩ እንደ ዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌ ያሉ አገልጋዮችን መደገፍ አማራጭ የሌለው አደራዋ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በዕለቱ የእግዚአብሔር ቃል ስብከት እና የዝማሬ አምልኮ የተከናወነ ሲሆን በቅርቡ በዶ/ር ተስፋዬ ተጽፎ በሚመራው ተስፋ ዐቃብያነ ክርስትና ማኅበር አማካኝነት የታተመው “የሐዋሪያት ቤተ ክርስቲያን” ኑፋቄ መጽሐፍ ጠቀሜታ ዳሰሳ ቀርቧል፡፡
በመርሃ ግብሩ ፍጻሜ ላይም በዕለቱ የተገኙ የመርሃ ግብሩ ታዳሚያን እና ለዚህ አገልግሎት ቀናዒ የሆኑ የእውነተኛው ወንጌል ቤተሰቦች የዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌ አገልግሎት ደጋፊ በመሆን ከጎኑ እንዲቆሙ እና ድጋፍ በማጣት ተስፋ ቆርጦ አገልግሎቱን እንዳያቆም በቋሚ ደጋፊነት ከጎኑ እንዲሰለፉ በፕሮግራሙ አዘጋጆች ጥሪ ቀርቧል፡፡
ይህንኑ በቀላሉ ለማከናወን እንዲቻልም የተሻሻለው የአገልግሎቱ ድረ ገጽ እና በቋሚነት የአገልግሎቱ ደጋፍ አድራጊ እና ተጠቃሚ ደንበኝነት መመዝገቢያ መተግበሪያ ተዋውቋል፡፡ ዶ/ር ተስፋዬ እስከዛሬ በታማኝነት ዋጋ በመክፈል ስለሰጠው ያላቀ አገልግሎትም የእውቅና ስጦታ በመርሃ ግብሩ አዘጋጆች አማካኝነት ተበርክቶለታል፡፡
በዕለቱ መርሃ ግብር ማጠቃለያ ላይም የዕቅበተ እምነት አገልግሎትን ለመስጠት ከሦስት አስርት ዓመታት በላይ በጽናት ዋጋ የከፈለው ዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌ አገልግሎቱ እጅግ አንገብጋቢ ሆኖ ሳለ ደጋፊ በማጣቱ የሚሰማውን ሃዘኔታ በመግለጽ በዚህ ዕለት በበጎ ፈቃደኝነት እና በራሳቸው ተነሳሽነት ይህንኑ መርሃ ግብር ላዘጋጁ ወገኖች የላቀ ምስጋናውን አቅርቧል፡፡
ከዚሁ ጋር በማያያዝም ለዓመታት የአገልግሎቱ ደጋፊዎች የሆኑትን በተለይም ልዩ ልዩ ሥራዎችን በመሥራት እርሱ የሙሉ ግዜ አገልግሎት ያለክፍያ እንዲሠራ ያስቻለችውን ባለቤቱ ሰምራዊት ኤርሚያስን እናቷን አስቴር መንግሥቴን እና በቋሚነት ድጋፍ ያደረጉለት አብያተ ክርስቲያናት እና ግለሰብ የአገልግሎቱ አጋሮችን አመስግኖ የመታሰቢያ የምስክር ወረቀት በማኅበሩ ስም ተበርክቶላቸዋል፡፡
እኛም የወንጌል ቤተሰቦች ሁሉhi ከዚሁ እግዚአብሔር ለኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ስጦታ አድርጎ ከሰጠው ወንድም ጎን እንዲቆሙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
Comments