2 months ago
አዲስ አበባ ፡ የኤምኤምኤ እና የቦክስ ስፖርት ውድድር ሊካሄድ ነው
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ ከዚህ ቀደም ከተደረጉት የንክኪ ስፖርት ሁነቶች ሁሉ እጅግ ግዙፍ የሆነው የኢትዮ ፋይት ናይት የውድድር መድረክ ይፋ ሆኗል::
ዝግጅቱ የአዲስ አበባ ኪክ ቦክስ ፌዴሬሽን፣ የአዲስ አበባ ቦክስ ፌዴሬሽን እና የአዲስ አበባ ወጣቶች ስፖርት ቢሮ በጋራ በመተባበር ያዘጋጁት ሲሆን ነሀሴ 23 ቀን 2018 ዓ.ም (Aug 29/2026) በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቤንሽን ሴንተር በደመቀ ሁኔታ ይካሄዳል::
በዚህ ልዩ ስፖርታዊ ፌስቲቫል ላይ በድብልቅ ማርሻል አርት (MMA) ዘርፍ ዓለም አቀፍ እውቅና ያላቸው የውጭ ሀገር ተወዳዳሪዎች የሚሳተፉ ሲሆን ሀገራችንን ወክለው ደግሞ ቢኒያም ሽብሬ፣ ክብሮም ንጉሴ እና አገረሰላም አርባን ጨምሮ በርካታ ስፖርተኞች ወደ መድረኩ ይወርዳሉ::
በጠቅላላው ከ6 እስከ 8 የሚደርሱ ብርቱ ፍልሚያዎች የሚስተናገዱ ሲሆን ተወዳዳሪዎቹ የተመረጡት በውድድር ታሪካቸው፣ በዓለም አቀፍ ልምዳቸው፣ በአካል ብቃት ጥንካሬያቸው እና ማራኪ ትዕይንት ማሳየት በሚችሉበት ብቃታቸው ላይ ተመስርቶ ነው::
አትሌቶቹ በፌዴሬሽኑ ህግ መሰረት አስፈላጊውን የህክምና ምርመራ፣ የክብደት ልኬትና የፈቃድ አሰጣጥ ሂደቶችን ያጠናቀቁ ሲሆን ዝርዝር የክብደት መጠናቸውና ዜግነታቸው በቅርቡ ይፋ ይደረጋል::
ይህንን ታሪካዊ ፍልሚያ ለመታደም ከ8,000 እስከ 10,000 የሚደርሱ የስፖርት አፍቃሪዎች በአዳራሹ ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል::
አዘጋጆቹ የአፍሪካንና የሀገራችንን ስፖርታዊ አቅም ለዓለም የሚያስተዋውቅ፣ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀና ፍጹም ሙያዊ ብቃት የተላበሰ ዝግጅት ለማቅረብ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሳቸውን ገልጸዋል::
የውድድሩ ዋነኛ ዓላማ የንክኪ ስፖርቶችን ከማሳደግ ባለፈ ለሀገር ውስጥ አትሌቶች ሙያዊ መድረክ መፍጠር፣ ወጣቶችን ማነሳሳት፣ ስፖርታዊ ቱሪዝምን በአዲስ አበባና በኢትዮጵያ ማስፋፋት እንዲሁም ሀገራችንን የዓለም አቀፍ ውድድሮች ማዕከል ማድረግ ነው::
ዝግጅቱ የሚስተናገድበት አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቤንሽን ሴንተር (AICC) ዘመናዊ የዲጂታል ምስልና የድምፅ መገልገያ መሳሪያዎች የተሟሉለት በመሆኑ ለታዳሚው ምቹ መዝናኛን ለመፍጠር ተመራጭ አድርጎታል::
ገራሚ ኢቨንትስ የዝግጅቱን አጠቃላይ የፕሮዳክሽን ስራ በማስተናገድ ከባለቤቶቹ ጋር በጋራ የሚሰራ ሲሆን ለአትሌቶች ስልጠና፣ ለደህንነት፣ ለቦታ ዝግጅትና ለሎጂስቲክስ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ፈሷል::
ይህንን ውድድር በኢትዮጵያና በአፍሪካ ደረጃ ተከታታይነት ባለው መልኩ ለማዘጋጀት የታቀደ በመሆኑ፣ የዝግጅቱን ጥራት ይበልጥ ለማሳደግ ሀገር በቀልና ዓለም አቀፍ ተቋማት በስፖንሰርሺፕ፣ በሚዲያ ሽፋን፣ በዲጂታል ግብይትና በቪአይፒ ተሳትፎ ላይ አብረው እንዲሰሩ ጥሪ ቀርቧል::
የመግቢያ ትኬት ዋጋንና የስርጭት ሽፋንን በተመለከተ ከሚዲያ አጋሮች ጋር ውይይት እየተደረገ ሲሆን የቴሌቪዥንና የዲጂታል ቀጥታ ስርጭት መረጃዎች በቅርቡ ይፋ የሚደረጉ ይሆናል::
#mma #boxing #ethiofightnight #sportstourism #aicc #ethiopianathletes #geramievents #sports #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ ከዚህ ቀደም ከተደረጉት የንክኪ ስፖርት ሁነቶች ሁሉ እጅግ ግዙፍ የሆነው የኢትዮ ፋይት ናይት የውድድር መድረክ ይፋ ሆኗል::
ዝግጅቱ የአዲስ አበባ ኪክ ቦክስ ፌዴሬሽን፣ የአዲስ አበባ ቦክስ ፌዴሬሽን እና የአዲስ አበባ ወጣቶች ስፖርት ቢሮ በጋራ በመተባበር ያዘጋጁት ሲሆን ነሀሴ 23 ቀን 2018 ዓ.ም (Aug 29/2026) በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቤንሽን ሴንተር በደመቀ ሁኔታ ይካሄዳል::
በዚህ ልዩ ስፖርታዊ ፌስቲቫል ላይ በድብልቅ ማርሻል አርት (MMA) ዘርፍ ዓለም አቀፍ እውቅና ያላቸው የውጭ ሀገር ተወዳዳሪዎች የሚሳተፉ ሲሆን ሀገራችንን ወክለው ደግሞ ቢኒያም ሽብሬ፣ ክብሮም ንጉሴ እና አገረሰላም አርባን ጨምሮ በርካታ ስፖርተኞች ወደ መድረኩ ይወርዳሉ::
በጠቅላላው ከ6 እስከ 8 የሚደርሱ ብርቱ ፍልሚያዎች የሚስተናገዱ ሲሆን ተወዳዳሪዎቹ የተመረጡት በውድድር ታሪካቸው፣ በዓለም አቀፍ ልምዳቸው፣ በአካል ብቃት ጥንካሬያቸው እና ማራኪ ትዕይንት ማሳየት በሚችሉበት ብቃታቸው ላይ ተመስርቶ ነው::
አትሌቶቹ በፌዴሬሽኑ ህግ መሰረት አስፈላጊውን የህክምና ምርመራ፣ የክብደት ልኬትና የፈቃድ አሰጣጥ ሂደቶችን ያጠናቀቁ ሲሆን ዝርዝር የክብደት መጠናቸውና ዜግነታቸው በቅርቡ ይፋ ይደረጋል::
ይህንን ታሪካዊ ፍልሚያ ለመታደም ከ8,000 እስከ 10,000 የሚደርሱ የስፖርት አፍቃሪዎች በአዳራሹ ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል::
አዘጋጆቹ የአፍሪካንና የሀገራችንን ስፖርታዊ አቅም ለዓለም የሚያስተዋውቅ፣ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀና ፍጹም ሙያዊ ብቃት የተላበሰ ዝግጅት ለማቅረብ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሳቸውን ገልጸዋል::
የውድድሩ ዋነኛ ዓላማ የንክኪ ስፖርቶችን ከማሳደግ ባለፈ ለሀገር ውስጥ አትሌቶች ሙያዊ መድረክ መፍጠር፣ ወጣቶችን ማነሳሳት፣ ስፖርታዊ ቱሪዝምን በአዲስ አበባና በኢትዮጵያ ማስፋፋት እንዲሁም ሀገራችንን የዓለም አቀፍ ውድድሮች ማዕከል ማድረግ ነው::
ዝግጅቱ የሚስተናገድበት አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቤንሽን ሴንተር (AICC) ዘመናዊ የዲጂታል ምስልና የድምፅ መገልገያ መሳሪያዎች የተሟሉለት በመሆኑ ለታዳሚው ምቹ መዝናኛን ለመፍጠር ተመራጭ አድርጎታል::
ገራሚ ኢቨንትስ የዝግጅቱን አጠቃላይ የፕሮዳክሽን ስራ በማስተናገድ ከባለቤቶቹ ጋር በጋራ የሚሰራ ሲሆን ለአትሌቶች ስልጠና፣ ለደህንነት፣ ለቦታ ዝግጅትና ለሎጂስቲክስ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ፈሷል::
ይህንን ውድድር በኢትዮጵያና በአፍሪካ ደረጃ ተከታታይነት ባለው መልኩ ለማዘጋጀት የታቀደ በመሆኑ፣ የዝግጅቱን ጥራት ይበልጥ ለማሳደግ ሀገር በቀልና ዓለም አቀፍ ተቋማት በስፖንሰርሺፕ፣ በሚዲያ ሽፋን፣ በዲጂታል ግብይትና በቪአይፒ ተሳትፎ ላይ አብረው እንዲሰሩ ጥሪ ቀርቧል::
የመግቢያ ትኬት ዋጋንና የስርጭት ሽፋንን በተመለከተ ከሚዲያ አጋሮች ጋር ውይይት እየተደረገ ሲሆን የቴሌቪዥንና የዲጂታል ቀጥታ ስርጭት መረጃዎች በቅርቡ ይፋ የሚደረጉ ይሆናል::
#mma #boxing #ethiofightnight #sportstourism #aicc #ethiopianathletes #geramievents #sports #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
ታዋቂዋ ማራቶን አትሌት ፋጡማ ሮባ እና ጋዜጠኛ ካሳሁን ፈይሳ ከዓመታት በኋላ በደስታ ተገናኙ
#ethiopia | የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ካስጠሩ ስመ ጥር የስፖርት ባልባለቶች መካከል አንዷ የሆነችው አትሌት ፋጡማ ሮባ እና ጋዜጠኛ ካሳሁን ፈይሳ ከረጅም ዓመታት በኋላ በድጋሚ ተገናኝተዋል።
አትሌት ፋጡማ ሮባ በታሪካዊው የአትላንታ ኦሎምፒክ በሴቶች ማራቶን ውድድር ለኢትዮጵያ ከአርባ ዓመታት በኋላ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኘች ታላቅ ባለውለታ ናት።
በወቅቱ ይህንን ታላቅ ድል ተቀዳጅታ ወደ ሀገሯ ስትመለስ በነበረው ከፍተኛ የደስታ ድባብ ውስጥ ጋዜጠኛ ካሳሁን ፈይሳ ለኢትዮጵያ ሬድዮ ፕሮግራም የሚሆን አጭር ቃለ መጠይቅ አድርጎላት እንደነበር ይታወሳል።
ያኔ በወጣትነት ዘመናቸው በስራ አጋጣሚ ተገናኝተው የተነሱትን የማይረሳ ትዝታ የያዘ ፎቶግራፍ በማስታወስ፣ ከአያሌ ዓመታት በኋላ አሁን ላይ በድጋሚ በመገናኘታቸው ለተባረከው ዕድሜና ለአምላክ ምስጋና በማቅረብ ለታዋቂዋ አትሌት መልካም ጤንነትና ረጅም ዕድሜ ተመኝቷል።
ጋዜጠኛ ካሳሁን ፈይሳ በኦንታሪዮ፣ ቶሮንቶ ካናዳ 🇨🇦 ነዋሪ ነው።
#sport #marathon #atlanta1996 #olympics #athletics #history #legend #ethiopianathletes #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ካስጠሩ ስመ ጥር የስፖርት ባልባለቶች መካከል አንዷ የሆነችው አትሌት ፋጡማ ሮባ እና ጋዜጠኛ ካሳሁን ፈይሳ ከረጅም ዓመታት በኋላ በድጋሚ ተገናኝተዋል።
አትሌት ፋጡማ ሮባ በታሪካዊው የአትላንታ ኦሎምፒክ በሴቶች ማራቶን ውድድር ለኢትዮጵያ ከአርባ ዓመታት በኋላ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኘች ታላቅ ባለውለታ ናት።
በወቅቱ ይህንን ታላቅ ድል ተቀዳጅታ ወደ ሀገሯ ስትመለስ በነበረው ከፍተኛ የደስታ ድባብ ውስጥ ጋዜጠኛ ካሳሁን ፈይሳ ለኢትዮጵያ ሬድዮ ፕሮግራም የሚሆን አጭር ቃለ መጠይቅ አድርጎላት እንደነበር ይታወሳል።
ያኔ በወጣትነት ዘመናቸው በስራ አጋጣሚ ተገናኝተው የተነሱትን የማይረሳ ትዝታ የያዘ ፎቶግራፍ በማስታወስ፣ ከአያሌ ዓመታት በኋላ አሁን ላይ በድጋሚ በመገናኘታቸው ለተባረከው ዕድሜና ለአምላክ ምስጋና በማቅረብ ለታዋቂዋ አትሌት መልካም ጤንነትና ረጅም ዕድሜ ተመኝቷል።
ጋዜጠኛ ካሳሁን ፈይሳ በኦንታሪዮ፣ ቶሮንቶ ካናዳ 🇨🇦 ነዋሪ ነው።
#sport #marathon #atlanta1996 #olympics #athletics #history #legend #ethiopianathletes #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 months ago
የጀግናዋ አትሌት ሻምበል ባሻ የብርጓል መለሰ የቀብር ሥነ ሥርዓት ተፈጸመ
#ethiopia | በበርካታ ዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ ስታደርግ የቆየችው ዝነኛዋ አትሌት ሻምበል ባሻ የብርጓል መለሰ የቀብር ሥነ ሥርዓት በመንበረ ፀባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በክብር ተፈጽሟል።
በመጋቢት ወር 1982 ዓ.ም በሰሜን ወሎ መቄት ወረዳ የተወለደችው አትሌቷ ከ1999 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሩጫው ዓለም በመግባት ስኬታማ ጉዞ ስታደርግ ቆይታለች።
በ2003 ዓ.ም የመከላከያ መቻል ስፖርት ክለብን በመቀላቀል በሀገር ውስጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ በ10 ኪሎ ሜትር፣ በሀገር አቋራጭ እንዲሁም በማራቶን ውድድሮች በርካታ ድሎችን ለሀገሯና ለክለቧ አስመዝግባለች።
አትሌት የብርጓል መለሰ እ.ኤ.አ በ2015 በመላ አፍሪካ ጨዋታዎች የነሐስ ሜዳሊያ፣ በ2013 በዓለም ሀገር አቋራጭ ውድድር የብር ሜዳሊያ እንዲሁም በሂውስተን፣ በሻንጋይ፣ በፕራግ እና በሊዝበን ማራቶኖች አንደኛ በመውጣት ታላቅ ውጤት ያስመዘገበች ጀግና ነበረች።
አትሌቷ በካናዳ ለሚካሄደው የኦታዋ ማራቶን ዝግጅት እያደረገች በነበረበት ወቅት በደረሰባት ድንገተኛ የጤና እክል ግንቦት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች።
በዛሬው የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮች፣ የጦር ኃይሎች መኮንኖች፣ አትሌቶችና ቤተሰቦቿ በተገኙበት በመከላከያ የክብር ዘብ የታጀበ ሽኝት ተደርጎላታል።
አትሌት የብርጓል በትዳር አጋሯ አትሌት ወሰን ዘለቀና በሁለት ሕፃናት ልጆቿ እንዲሁም በሥራ ባልደረቦቿ ዘንድ በትሕትናዋና በአርአያነቷ የምትታወስ ታላቅ ስፖርተኛ ነበረች።
Getu Temesgen ( ጌጡ ተመስገን) ሚዲያና ኮሙኒኬሽንስ በጀግናዋ አትሌት ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን እየገለጽን ለቤተሰቦ፤ ለአድናቂዎቿ መጽናናትን እንመኛለን።
#athletics #ethiopianathletes #yebrgualmelese #sportnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በበርካታ ዓለም አቀፍ የውድድር መድረኮች የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ከፍ ስታደርግ የቆየችው ዝነኛዋ አትሌት ሻምበል ባሻ የብርጓል መለሰ የቀብር ሥነ ሥርዓት በመንበረ ፀባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በክብር ተፈጽሟል።
በመጋቢት ወር 1982 ዓ.ም በሰሜን ወሎ መቄት ወረዳ የተወለደችው አትሌቷ ከ1999 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሩጫው ዓለም በመግባት ስኬታማ ጉዞ ስታደርግ ቆይታለች።
በ2003 ዓ.ም የመከላከያ መቻል ስፖርት ክለብን በመቀላቀል በሀገር ውስጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ በ10 ኪሎ ሜትር፣ በሀገር አቋራጭ እንዲሁም በማራቶን ውድድሮች በርካታ ድሎችን ለሀገሯና ለክለቧ አስመዝግባለች።
አትሌት የብርጓል መለሰ እ.ኤ.አ በ2015 በመላ አፍሪካ ጨዋታዎች የነሐስ ሜዳሊያ፣ በ2013 በዓለም ሀገር አቋራጭ ውድድር የብር ሜዳሊያ እንዲሁም በሂውስተን፣ በሻንጋይ፣ በፕራግ እና በሊዝበን ማራቶኖች አንደኛ በመውጣት ታላቅ ውጤት ያስመዘገበች ጀግና ነበረች።
አትሌቷ በካናዳ ለሚካሄደው የኦታዋ ማራቶን ዝግጅት እያደረገች በነበረበት ወቅት በደረሰባት ድንገተኛ የጤና እክል ግንቦት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች።
በዛሬው የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮች፣ የጦር ኃይሎች መኮንኖች፣ አትሌቶችና ቤተሰቦቿ በተገኙበት በመከላከያ የክብር ዘብ የታጀበ ሽኝት ተደርጎላታል።
አትሌት የብርጓል በትዳር አጋሯ አትሌት ወሰን ዘለቀና በሁለት ሕፃናት ልጆቿ እንዲሁም በሥራ ባልደረቦቿ ዘንድ በትሕትናዋና በአርአያነቷ የምትታወስ ታላቅ ስፖርተኛ ነበረች።
Getu Temesgen ( ጌጡ ተመስገን) ሚዲያና ኮሙኒኬሽንስ በጀግናዋ አትሌት ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን እየገለጽን ለቤተሰቦ፤ ለአድናቂዎቿ መጽናናትን እንመኛለን።
#athletics #ethiopianathletes #yebrgualmelese #sportnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 months ago
የለንደን ማራቶን ነገ ይካሄዳል
* ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ለድል ተዘጋጅተዋል
#ethiopia | ነገ ሚያዚያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም. በዓለም አትሌቲክስ የፕላቲኒየም ደረጃ የተሰጠውና በጉጉት የሚጠበቀው የለንደን ማራቶን ይካሄዳል። የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ክብራቸውን ለማስጠበቅና አዲስ ታሪክ ለመጻፍ ወደ ለንደን አምርተዋል።
በሴቶች
ያለፈው ዓመት ሻምፒዮን እና በለንደን ማራቶን (ሴቶች ብቻ በሚሳተፉበት) የዓለም ክብረ ወሰን ባለቤት (2:15:50)! ትግስት ባደረገቻቸው ያለፉት 6 ማራቶኖች ከ2ኛ ደረጃ ዝቅ ብላ አታውቅም። ነገም ክብሯን እንደምታስጠብቅ ትልቅ ተስፋ ተጥሎባታል።
በወንዶች
የኦሎምፒክና የዓለም ሻምፒዮኑ ታምራት ቶላ ለ5ኛ ጊዜ በለንደን ይሳተፋል። ከዚህ ቀደም በተሳተፈባቸው 4ቱም ውድድሮች እስከ 6ኛ ባለው ደረጃ ማጠናቀቁ ለነገው ድል ትልቅ መተማመኛ ሆኖታል።
በ10 ሺህ ሜትር ዝነኛው ዮሚፍ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ 42 ኪሎ ሜትር (ማራቶን) የሚሮጥበት ታሪካዊ መድረክ ይሆናል። ዮሚፍ በማራቶን ምን ዓይነት አስገራሚ ውጤት ይይዝ ይሆን? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ነው።
ያለፈው ዓመት ሻምፒዮኑ ኬንያዊው ሰባስቲያን ሳዌ፣ ዩጋንዳውያኑ ጃኮብ ኪፕሊሞ እና ጆሽዋ ቼፕቴጋይ ለኢትዮጵያውያን ብርቱ ተቀናቃኝ እንደሚሆኑ ይጠበቃል።
ለንደን ማራቶን ለኢትዮጵያውያን የድል አውድማ ነው። ትግስት አሰፋ በለንደን ጎዳናዎች ላይ በድጋሚ የዓለምን ትኩረት እንደምትስብ ጥርጥር የለኝም። ዮሚፍ ቀጀልቻ ደግሞ ወደ ማራቶን ያደረገው ሽግግር ለሀገራችን አትሌቲክስ አዲስ ተስፋ ነው። ይህንን ታላቅ ውድድር በሀገሬ ቴሌቪዥን በቀጥታ መመልከት መቻላችን ደግሞ ድሉን ከቤታችን ሆነን እንድንጋራ ያደርገናል።
ድል ለኢትዮጵያ አትሌቶች!
#getu #londonmarathon2026 #ethiopianathletes #tigistassefa #tamirattola #yomifkejelcha #athleticsnews #worldrecord #hagerietv #ለንደንማራቶን #ኢትዮጵያ #ትግስትአሰፋ #ታምራትቶላ #ዮሚፍቀጀልቻ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
* ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ለድል ተዘጋጅተዋል
#ethiopia | ነገ ሚያዚያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም. በዓለም አትሌቲክስ የፕላቲኒየም ደረጃ የተሰጠውና በጉጉት የሚጠበቀው የለንደን ማራቶን ይካሄዳል። የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ክብራቸውን ለማስጠበቅና አዲስ ታሪክ ለመጻፍ ወደ ለንደን አምርተዋል።
በሴቶች
ያለፈው ዓመት ሻምፒዮን እና በለንደን ማራቶን (ሴቶች ብቻ በሚሳተፉበት) የዓለም ክብረ ወሰን ባለቤት (2:15:50)! ትግስት ባደረገቻቸው ያለፉት 6 ማራቶኖች ከ2ኛ ደረጃ ዝቅ ብላ አታውቅም። ነገም ክብሯን እንደምታስጠብቅ ትልቅ ተስፋ ተጥሎባታል።
በወንዶች
የኦሎምፒክና የዓለም ሻምፒዮኑ ታምራት ቶላ ለ5ኛ ጊዜ በለንደን ይሳተፋል። ከዚህ ቀደም በተሳተፈባቸው 4ቱም ውድድሮች እስከ 6ኛ ባለው ደረጃ ማጠናቀቁ ለነገው ድል ትልቅ መተማመኛ ሆኖታል።
በ10 ሺህ ሜትር ዝነኛው ዮሚፍ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ 42 ኪሎ ሜትር (ማራቶን) የሚሮጥበት ታሪካዊ መድረክ ይሆናል። ዮሚፍ በማራቶን ምን ዓይነት አስገራሚ ውጤት ይይዝ ይሆን? የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ነው።
ያለፈው ዓመት ሻምፒዮኑ ኬንያዊው ሰባስቲያን ሳዌ፣ ዩጋንዳውያኑ ጃኮብ ኪፕሊሞ እና ጆሽዋ ቼፕቴጋይ ለኢትዮጵያውያን ብርቱ ተቀናቃኝ እንደሚሆኑ ይጠበቃል።
ለንደን ማራቶን ለኢትዮጵያውያን የድል አውድማ ነው። ትግስት አሰፋ በለንደን ጎዳናዎች ላይ በድጋሚ የዓለምን ትኩረት እንደምትስብ ጥርጥር የለኝም። ዮሚፍ ቀጀልቻ ደግሞ ወደ ማራቶን ያደረገው ሽግግር ለሀገራችን አትሌቲክስ አዲስ ተስፋ ነው። ይህንን ታላቅ ውድድር በሀገሬ ቴሌቪዥን በቀጥታ መመልከት መቻላችን ደግሞ ድሉን ከቤታችን ሆነን እንድንጋራ ያደርገናል።
ድል ለኢትዮጵያ አትሌቶች!
#getu #londonmarathon2026 #ethiopianathletes #tigistassefa #tamirattola #yomifkejelcha #athleticsnews #worldrecord #hagerietv #ለንደንማራቶን #ኢትዮጵያ #ትግስትአሰፋ #ታምራትቶላ #ዮሚፍቀጀልቻ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
Comments