8 days ago
አዲስ አበባ ባለፉት 5 ዓመታት የልማት አብዮት አካሂዳለች - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መዲናችን አዲስ አበባ ባለፉት 5 ዓመታት የልማት አብዮት አካሂዳለች አሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ።
ከንቲባዋ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ በባለፉት 10 ቀናት ብቻ 11 ፕሮጀክቶችን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል ብለዋል።
ለአብነትም ፦
1. በኢንዱስትሪ እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ፤ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። ይህ ፓርክ ከ20 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጥር ነው።
2. የማህበራዊ ልማት (የመኖሪያ ቤቶች)፤ ሶስቱ የበጎነት መንደሮችን በአዲስ ከተማ፣ በኮልፌ ቀራንዮ እና የካ ክፍለ ከተሞች የተገነቡ የመኖርያ ቤቶች ለሀገር ባለውለታዎች፣ ለአቅመ ደካማዎች እና ለአካል ጉዳተኞች የማስተላለፍ ስራ ተሰርቷል፡፡
3. የመዝናኛ እና የህዝብ ፓርኮች ፤በአዲስ ከተማ (አስኮ አዲስ ሰፈር) በ30 ሺህ ካሬ ሜትር እና በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ18 ሄክታር ቦታ ላይ የተገነቡ የወንዝ ዳርቻ እና የህዝብ መዝናኛ ፓርኮች ተመርቀዋል። እነዚህ ማዕከላት ህፃናትን፣ ወጣቶችን እና አረጋውያንን ያካተቱ፣ ማህበረሰቡ በጋራ የሚጠቀምባቸው ናቸው።
4. የኑሮ ውድነትን ለማቃለል የግብይት ማዕከላትን የማስፋት ስራ አካል የሆነው 7ኛው የለሚ ሁለገብ የገበያ ማዕከል፣ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል።
5. ዘመናዊ የገበያና የትራንስፖርት ማዕከል፤ አይነቱ የመጀመሪያ የሆነው የአድዋ የገበያ ማዕከል እና ዘመናዊ የትራንስፖርት ተርሚናል ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል። የዚህ ማዕከል ሱቆች እና ካፍቴሪያዎች ለፒያሳ ልማት ተነሺዎች በዕጣ ተላልፈዋል።
6. በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ3 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባውን ፣ 16 ሱቆችን እና 18 ሼዶችን የያዘ የተቀናጀ የከተማ ግብርና ማዕከል አገልግሎት ክፍት ተደርጓል ።
7. የስፖርት እና የወጣቶች ማዕከል፡ በቦሌ ክፍለ ከተማ የሚገኘው የለሚ ኮሚኒቲ ስታዲየም፣ 5 ስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ 95 የህፃናት መጫወቻዎች፣ 6 የህፃናት ማቆያ (Daycare) ማዕከላት፣ ካፍቴሪያዎች እና አምፊ ቲያትሮችን ጨምሮ ለወጣቶች ተጠቃሚነት የሚያገለግሉ መሠረተ ልማቶችን አሟልቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
8. በልደታ ክ/ከተማ ለትውልድ ግንባታ መሰረት የሚጥሉ ሁለት ት/ቤቶች እና ሶስት የህፃናት ማቆያ ማእከል ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ተደረገዋል ።
9. የተስፋ ብርሀን የምገባ ማዕከላት ተጠቃሚዎች ለነበሩ 400 ነዋሪዎቻችን መነሻ ካፒታልና የመስሪያ ቁሳቁስ በማሟሟላት ከተረጂነት ወደ የስራ እድል ተጠቃሚነት እንዲሸጋገሩ ተደርጓል።
10. 7ኛውን የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት በላፍቶ ክፍለ ከተማ ተመርቋል።
11. ዘመናዊ የጤና አገልግሎት ፤ በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የሆነው፣ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂ የተደገፈው እና እጅግ ዘመናዊ የሆነው የላፍቶ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለምርቃት በቅቷል።
አንዳንዶች እነዚህ ፕሮጀክቶች ለምርጫ ተብሎ እንደተከናወነ ያነሳሉ ያሉት ከንቲባዋ፤ ነገር ግን እውነታው ቀድሞ ያልተሰራ ለምርጫም ሊደርስ አይችልም፤ ተሰርቶም ለምርጫ ከዋለ ዋናው ህዝቡና ሀገር ተጠቃሚ ይሁን እንጂ ችግር የለውም ብለዋል፡፡
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መዲናችን አዲስ አበባ ባለፉት 5 ዓመታት የልማት አብዮት አካሂዳለች አሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ።
ከንቲባዋ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ በባለፉት 10 ቀናት ብቻ 11 ፕሮጀክቶችን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል ብለዋል።
ለአብነትም ፦
1. በኢንዱስትሪ እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ፤ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። ይህ ፓርክ ከ20 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጥር ነው።
2. የማህበራዊ ልማት (የመኖሪያ ቤቶች)፤ ሶስቱ የበጎነት መንደሮችን በአዲስ ከተማ፣ በኮልፌ ቀራንዮ እና የካ ክፍለ ከተሞች የተገነቡ የመኖርያ ቤቶች ለሀገር ባለውለታዎች፣ ለአቅመ ደካማዎች እና ለአካል ጉዳተኞች የማስተላለፍ ስራ ተሰርቷል፡፡
3. የመዝናኛ እና የህዝብ ፓርኮች ፤በአዲስ ከተማ (አስኮ አዲስ ሰፈር) በ30 ሺህ ካሬ ሜትር እና በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ18 ሄክታር ቦታ ላይ የተገነቡ የወንዝ ዳርቻ እና የህዝብ መዝናኛ ፓርኮች ተመርቀዋል። እነዚህ ማዕከላት ህፃናትን፣ ወጣቶችን እና አረጋውያንን ያካተቱ፣ ማህበረሰቡ በጋራ የሚጠቀምባቸው ናቸው።
4. የኑሮ ውድነትን ለማቃለል የግብይት ማዕከላትን የማስፋት ስራ አካል የሆነው 7ኛው የለሚ ሁለገብ የገበያ ማዕከል፣ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል።
5. ዘመናዊ የገበያና የትራንስፖርት ማዕከል፤ አይነቱ የመጀመሪያ የሆነው የአድዋ የገበያ ማዕከል እና ዘመናዊ የትራንስፖርት ተርሚናል ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል። የዚህ ማዕከል ሱቆች እና ካፍቴሪያዎች ለፒያሳ ልማት ተነሺዎች በዕጣ ተላልፈዋል።
6. በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ3 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባውን ፣ 16 ሱቆችን እና 18 ሼዶችን የያዘ የተቀናጀ የከተማ ግብርና ማዕከል አገልግሎት ክፍት ተደርጓል ።
7. የስፖርት እና የወጣቶች ማዕከል፡ በቦሌ ክፍለ ከተማ የሚገኘው የለሚ ኮሚኒቲ ስታዲየም፣ 5 ስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ 95 የህፃናት መጫወቻዎች፣ 6 የህፃናት ማቆያ (Daycare) ማዕከላት፣ ካፍቴሪያዎች እና አምፊ ቲያትሮችን ጨምሮ ለወጣቶች ተጠቃሚነት የሚያገለግሉ መሠረተ ልማቶችን አሟልቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
8. በልደታ ክ/ከተማ ለትውልድ ግንባታ መሰረት የሚጥሉ ሁለት ት/ቤቶች እና ሶስት የህፃናት ማቆያ ማእከል ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ተደረገዋል ።
9. የተስፋ ብርሀን የምገባ ማዕከላት ተጠቃሚዎች ለነበሩ 400 ነዋሪዎቻችን መነሻ ካፒታልና የመስሪያ ቁሳቁስ በማሟሟላት ከተረጂነት ወደ የስራ እድል ተጠቃሚነት እንዲሸጋገሩ ተደርጓል።
10. 7ኛውን የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት በላፍቶ ክፍለ ከተማ ተመርቋል።
11. ዘመናዊ የጤና አገልግሎት ፤ በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የሆነው፣ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂ የተደገፈው እና እጅግ ዘመናዊ የሆነው የላፍቶ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለምርቃት በቅቷል።
አንዳንዶች እነዚህ ፕሮጀክቶች ለምርጫ ተብሎ እንደተከናወነ ያነሳሉ ያሉት ከንቲባዋ፤ ነገር ግን እውነታው ቀድሞ ያልተሰራ ለምርጫም ሊደርስ አይችልም፤ ተሰርቶም ለምርጫ ከዋለ ዋናው ህዝቡና ሀገር ተጠቃሚ ይሁን እንጂ ችግር የለውም ብለዋል፡፡
12 days ago
የማዕድን ዘርፍ እና አዲስ የኢኮኖሚ ምዕራፍ
******************
(የዕለቱ መልዕክት)
በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ትንሳኤ ውስጥ ለዓመታት ተኝቶ የነበረው የማዕድን ሀብታችን አሁን ለሀገር ኢኮኖሚ ትከሻውን እየሰጠ ይገኛል። ከባህላዊ የግብርና አጥር ወጥተን አገራችንን ወደ አፍሪካ የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማሸጋገር በሚደረገው ጥረት ኢትዮጵያ ያሏትን የሀብት ክምችት በዕውቀትና በቴክኖሎጂ አቀነባብራ መጠቀም ጀምራለች። በዚህም የከርሰ ምድርና ገጸ ምድር ሀብቷን ወደ ብሔራዊ ምርታማነት የመቀየር አዲስ ምዕራፍ ከፍታለች።
የማምረቻው ዘርፍ እንደ ወንዝ ውሃ የኢኮኖሚውን አቅጣጫ የሚቀይር ከሆነ ማዕድን ደግሞ የዚያ ወንዝ ምንጭ ነው። አገራችንን የኢንዱስትሪ ፋና ለማድረግ የጀመርነው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፣ የማዕድን ዘርፉን ከምድር ውስጥ አውጥቶ ወደ ፋብሪካዎች ግብዓትነት የመቀየር ግዴታ አለበት።
የኢንዱስትሪ ፓርኮቻችን እያሳዩት ባለው አቅም የማዕድን ዘርፉን በቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ጥገኝነታችንን መቀነስ የምንችለው አሁን ነው። በገዛ መሬታችን ያለውን ሀብት በጥራትና በክህሎት ተጠቅመን የውጭ ገበያን በዋጋና በጥራት መፎካከር የሚችል አቅም መገንባትም አለብን።
ከውጥን ወደ እውነታ እየተሸጋገርን ባለበት በዚህ ወቅት የማዕድን ልማታችን ከጥሬ ዕቃ ሽያጭ አልፎ እሴት በተጨመረባቸው ምርቶች መደገፍ አለበት። የወርቅ፣ የኦፓል፣ የታንታለም እና የሌሎች ማዕድናት ፍሰት ለሀገር ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት መሆን የሚችለው፣ የማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች በፓርኮቻችን ውስጥ ሲጠናከሩ ብቻ ነው።
የኢኮኖሚ ነፃነት ማለት በውጭ ምንዛሪ መግዛት ሳይሆን በእጅ ያለን ሀብት በአገር አቅም አምርቶ ለዓለም ማቅረብ ነው። ይህ ጉዞ በሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል ጥያቄ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ የሉዓላዊነትና የብልጽግና መለኪያ ነው።
የማዕድን ዘርፉን ወደ ኢንዱስትሪ ማቀናጀት ማለት የአገርን የቴክኖሎጂ አቅም መፈተን ማለት ነው። ዘመናዊ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለዓለም አቀፍ ደረጃ ያላቸው ማዕድናት ማቀነባበሪያ ማዕከላት ሲሆኑ ኢትዮጵያ ከጥሬ ዕቃ ላኪነት ወደ ምርት አምራችነት ትሸጋገራለች።
ይህ ሽግግር በተለይም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን፣ የፀሐይ ኃይል መሣሪያዎችን እና የሕክምና መሣሪያዎችን ለማምረት ወሳኝ የሆኑ ማዕድናትን በአገር ውስጥ መጠቀምን ይጠይቃል።
"ውኃ ካልጠራ አይጠጣም፣ ሰው ካልተማረ አይጠቅም" እንደተባለው የምንፈልገውን የኢንዱስትሪ ለውጥ የምናመጣው በትምህርት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በዘርፉ በሰለጠነ የሰው ኃይል ብቻ ነው።
የኢትዮጵያ ትንሳኤ በወረቀት ላይ የተጻፈ ራዕይ ሳይሆን በየፋብሪካው መጋዘን የሚከማች ምርት፣ በየኢንዱስትሪ ፓርኩ የሚሰማ የቴክኖሎጂ ምት እና በምድር የተገኙ ማዕድናት በኢትዮጵያዊ ክህሎት ሲቀረጹ የሚታይ እውነት ነው።
በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪ ፓርኮቻችን እየሳቡት ያለው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት፣ የማዕድን ዘርፉን እንደ ታላቅ የኢኮኖሚ ምንጭ ለመጠቀም ያለንን አቅም ያሳያል። የልዩ ኢኮኖሚ ዞን አዋጁም ለዚህ ዘርፍ የሚሰጠው የግብርና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች፣ ባለሀብቶች ወደ ማዕድን ልማት እንዲገቡ ትልቅ ማበረታቻ ሆኗል።
የማዕድን ሀብታችንን በዘመናዊ አሠራር ፈትሸን፣ የኢንዱስትሪው ዘርፍ እንዲያንሰራራ ማድረጉ የጊዜው ትልቁ አገራዊ ጥሪ ነው።
ኢትዮጵያ በምርቷ ትከበራለች፤ በምድሯ የተከማቸው ሀብትም ለቀጣዩ ትውልድ የብልጽግና ፋና ሆኖ ይደምቃል። ይህ የኢንዱስትሪ አብዮት የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ከፍ የሚያደርግ፣ የኢኮኖሚ መዋቅራችንን ለዘመናት የሚያጸና የትንሳኤ ብሥራት ነው።
በየደረጃው ያለው የማዕድን ምርታችን ሲጎለብት ኢትዮጵያ የራሷን የኢንዱስትሪ ሉዓላዊነት ታውጃለች። ነገ የምናያት ኢትዮጵያ በምርቷ የምትኩራራ፣ በሀብቷ የምትበለጽግ እና ለአፍሪካ የብልጽግና ፋና የምትሆን አገር ናት።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #ebcdotstream #ethiopia #ebc #ማዕድን #ኢኮኖሚ
******************
(የዕለቱ መልዕክት)
በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ትንሳኤ ውስጥ ለዓመታት ተኝቶ የነበረው የማዕድን ሀብታችን አሁን ለሀገር ኢኮኖሚ ትከሻውን እየሰጠ ይገኛል። ከባህላዊ የግብርና አጥር ወጥተን አገራችንን ወደ አፍሪካ የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማሸጋገር በሚደረገው ጥረት ኢትዮጵያ ያሏትን የሀብት ክምችት በዕውቀትና በቴክኖሎጂ አቀነባብራ መጠቀም ጀምራለች። በዚህም የከርሰ ምድርና ገጸ ምድር ሀብቷን ወደ ብሔራዊ ምርታማነት የመቀየር አዲስ ምዕራፍ ከፍታለች።
የማምረቻው ዘርፍ እንደ ወንዝ ውሃ የኢኮኖሚውን አቅጣጫ የሚቀይር ከሆነ ማዕድን ደግሞ የዚያ ወንዝ ምንጭ ነው። አገራችንን የኢንዱስትሪ ፋና ለማድረግ የጀመርነው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፣ የማዕድን ዘርፉን ከምድር ውስጥ አውጥቶ ወደ ፋብሪካዎች ግብዓትነት የመቀየር ግዴታ አለበት።
የኢንዱስትሪ ፓርኮቻችን እያሳዩት ባለው አቅም የማዕድን ዘርፉን በቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ጥገኝነታችንን መቀነስ የምንችለው አሁን ነው። በገዛ መሬታችን ያለውን ሀብት በጥራትና በክህሎት ተጠቅመን የውጭ ገበያን በዋጋና በጥራት መፎካከር የሚችል አቅም መገንባትም አለብን።
ከውጥን ወደ እውነታ እየተሸጋገርን ባለበት በዚህ ወቅት የማዕድን ልማታችን ከጥሬ ዕቃ ሽያጭ አልፎ እሴት በተጨመረባቸው ምርቶች መደገፍ አለበት። የወርቅ፣ የኦፓል፣ የታንታለም እና የሌሎች ማዕድናት ፍሰት ለሀገር ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት መሆን የሚችለው፣ የማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች በፓርኮቻችን ውስጥ ሲጠናከሩ ብቻ ነው።
የኢኮኖሚ ነፃነት ማለት በውጭ ምንዛሪ መግዛት ሳይሆን በእጅ ያለን ሀብት በአገር አቅም አምርቶ ለዓለም ማቅረብ ነው። ይህ ጉዞ በሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል ጥያቄ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ የሉዓላዊነትና የብልጽግና መለኪያ ነው።
የማዕድን ዘርፉን ወደ ኢንዱስትሪ ማቀናጀት ማለት የአገርን የቴክኖሎጂ አቅም መፈተን ማለት ነው። ዘመናዊ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለዓለም አቀፍ ደረጃ ያላቸው ማዕድናት ማቀነባበሪያ ማዕከላት ሲሆኑ ኢትዮጵያ ከጥሬ ዕቃ ላኪነት ወደ ምርት አምራችነት ትሸጋገራለች።
ይህ ሽግግር በተለይም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን፣ የፀሐይ ኃይል መሣሪያዎችን እና የሕክምና መሣሪያዎችን ለማምረት ወሳኝ የሆኑ ማዕድናትን በአገር ውስጥ መጠቀምን ይጠይቃል።
"ውኃ ካልጠራ አይጠጣም፣ ሰው ካልተማረ አይጠቅም" እንደተባለው የምንፈልገውን የኢንዱስትሪ ለውጥ የምናመጣው በትምህርት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በዘርፉ በሰለጠነ የሰው ኃይል ብቻ ነው።
የኢትዮጵያ ትንሳኤ በወረቀት ላይ የተጻፈ ራዕይ ሳይሆን በየፋብሪካው መጋዘን የሚከማች ምርት፣ በየኢንዱስትሪ ፓርኩ የሚሰማ የቴክኖሎጂ ምት እና በምድር የተገኙ ማዕድናት በኢትዮጵያዊ ክህሎት ሲቀረጹ የሚታይ እውነት ነው።
በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪ ፓርኮቻችን እየሳቡት ያለው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት፣ የማዕድን ዘርፉን እንደ ታላቅ የኢኮኖሚ ምንጭ ለመጠቀም ያለንን አቅም ያሳያል። የልዩ ኢኮኖሚ ዞን አዋጁም ለዚህ ዘርፍ የሚሰጠው የግብርና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች፣ ባለሀብቶች ወደ ማዕድን ልማት እንዲገቡ ትልቅ ማበረታቻ ሆኗል።
የማዕድን ሀብታችንን በዘመናዊ አሠራር ፈትሸን፣ የኢንዱስትሪው ዘርፍ እንዲያንሰራራ ማድረጉ የጊዜው ትልቁ አገራዊ ጥሪ ነው።
ኢትዮጵያ በምርቷ ትከበራለች፤ በምድሯ የተከማቸው ሀብትም ለቀጣዩ ትውልድ የብልጽግና ፋና ሆኖ ይደምቃል። ይህ የኢንዱስትሪ አብዮት የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ከፍ የሚያደርግ፣ የኢኮኖሚ መዋቅራችንን ለዘመናት የሚያጸና የትንሳኤ ብሥራት ነው።
በየደረጃው ያለው የማዕድን ምርታችን ሲጎለብት ኢትዮጵያ የራሷን የኢንዱስትሪ ሉዓላዊነት ታውጃለች። ነገ የምናያት ኢትዮጵያ በምርቷ የምትኩራራ፣ በሀብቷ የምትበለጽግ እና ለአፍሪካ የብልጽግና ፋና የምትሆን አገር ናት።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #ebcdotstream #ethiopia #ebc #ማዕድን #ኢኮኖሚ
15 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) —የቀድሞው የኩባ መሪ ራውል ካስትሮ እና ሌሎች አምስት ግለሰቦች በፍሎሪዳ በሚገኝ የአሜሪካ የህግ አስከባሪ ክስ እንደተመሰረተባቸው ዛሬ ረቡዕ ይፋ የተደረጉ የፍርድ ቤት ሰነዶች አመለከቱ።
በ94 ዓመቱ ራውል ካስትሮ ላይ የቀረበው ይህ አዲስ የፌደራል ወንጀል ክስ፣ የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በኩባ መንግስት ላይ እያካሄደ ያለውን የጫና ዘመቻ ከፍ ወዳለ እና ወደተባባሰ ደረጃ ያሸጋገረው መሆኑ ተገልጿል።
ተከሳሹ ራውል ካስትሮ የሟቹ የኩባ አብዮት መሪ ፊደል ካስትሮ ወንድም ሲሆኑ፣ አሁንም ድረስ በሀገሪቱ ውስጥ እጅግ ከፍተኛ ተጽዕኖ እና ስልጣን ካላቸው ቁልፍ የፖለቲካ ሰዎች መካከል በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው።
በ94 ዓመቱ ራውል ካስትሮ ላይ የቀረበው ይህ አዲስ የፌደራል ወንጀል ክስ፣ የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በኩባ መንግስት ላይ እያካሄደ ያለውን የጫና ዘመቻ ከፍ ወዳለ እና ወደተባባሰ ደረጃ ያሸጋገረው መሆኑ ተገልጿል።
ተከሳሹ ራውል ካስትሮ የሟቹ የኩባ አብዮት መሪ ፊደል ካስትሮ ወንድም ሲሆኑ፣ አሁንም ድረስ በሀገሪቱ ውስጥ እጅግ ከፍተኛ ተጽዕኖ እና ስልጣን ካላቸው ቁልፍ የፖለቲካ ሰዎች መካከል በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው።
16 days ago
የመደመር አንቀጽ
የመደመር መንግሥት የውስጥ የኢኮኖሚ ሽግግርን በታቀደ መልኩ የሚመራ ብቻ ሳይሆን ከባቢያዊና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታን ይተነትናል። ራሱን ለመለወጥና ከእነዚህ ሁኔታዎች ጋር ራሱን ለማላመድ አስቀድሞ ይዘጋጃል። ዓለም ከአንዱ የኢኮኖሚ አብዮት ወለ ሌው እየዘለለ ከተለምዷዊው አሰራር ወጥቶ ወደ ዲጂታል ተሸጋግሯል። ከዚያም አልፎ አልፎ እንደ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ዓይነት ጨዋታ ቀያሪ ዐቅም ያላቸው ቴክኖሎጂዎችን እየታጠቀ ነው።
ከዚያም አልፎ እንደ ሰው ሠራሽ አስተውሎት ዓይነት ጨዋታ ቀያሪ ዐቅም ያላቸው ይሄንን ለውጥ በቶሎ የተላመዱ ሀገራትን ዛሬ የበለጸጉ ብለን እንጠራቸዋለን። ምክንያቱም ለውጥ የሚላመዱትን ያከብራል፤ የማይላመዱትን ደግሞ ይሰብራል። የነገው የበለጸጉ ሀገራት ዝርዝር ማለት፣ የሚቀጥሉትን አብዮቶች መላመድ የቻሉና ራሳቸውን በለውጡ ውስጥ ያሸጋገሩ ሀገራት ዝርዝር ነው።
የመደመር መንግስት
ገፅ 133
Ethiopian Broadcasting Corporation #digitalethiopia #የመረጃ_ሉዓላዊነት #data #ኢትዮጵያ
የመደመር መንግሥት የውስጥ የኢኮኖሚ ሽግግርን በታቀደ መልኩ የሚመራ ብቻ ሳይሆን ከባቢያዊና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታን ይተነትናል። ራሱን ለመለወጥና ከእነዚህ ሁኔታዎች ጋር ራሱን ለማላመድ አስቀድሞ ይዘጋጃል። ዓለም ከአንዱ የኢኮኖሚ አብዮት ወለ ሌው እየዘለለ ከተለምዷዊው አሰራር ወጥቶ ወደ ዲጂታል ተሸጋግሯል። ከዚያም አልፎ አልፎ እንደ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ዓይነት ጨዋታ ቀያሪ ዐቅም ያላቸው ቴክኖሎጂዎችን እየታጠቀ ነው።
ከዚያም አልፎ እንደ ሰው ሠራሽ አስተውሎት ዓይነት ጨዋታ ቀያሪ ዐቅም ያላቸው ይሄንን ለውጥ በቶሎ የተላመዱ ሀገራትን ዛሬ የበለጸጉ ብለን እንጠራቸዋለን። ምክንያቱም ለውጥ የሚላመዱትን ያከብራል፤ የማይላመዱትን ደግሞ ይሰብራል። የነገው የበለጸጉ ሀገራት ዝርዝር ማለት፣ የሚቀጥሉትን አብዮቶች መላመድ የቻሉና ራሳቸውን በለውጡ ውስጥ ያሸጋገሩ ሀገራት ዝርዝር ነው።
የመደመር መንግስት
ገፅ 133
Ethiopian Broadcasting Corporation #digitalethiopia #የመረጃ_ሉዓላዊነት #data #ኢትዮጵያ
16 days ago
የኢራን የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ቀጥታ የስናይፐር እና የክላሽንኮቭ ስልጠና ማስተላለፍ ጀመሩ!
#ethiopia | በኢራን፣ በአሜሪካ እና በእስራኤል መካከል ያለው ወታደራዊ ፍጥጫ እና ውጥረት እጅግ አስፈሪ ደረጃ ላይ በደረሰበት በዚህ ወቅት፣ የኢራን ብሔራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች (IRIB) ታሪክ ከየቀኑ የዜና እወጃ ወጥተው የቀጥታ የስልጠና መድረክ መሆናቸውን ዓለም በደነገጠ ስሜት እየተከታተለው ይገኛል።
የጣቢያዎቹ የዜና አቅራቢዎችና ጋዜጠኞች ራሳቸው የጦር መሣሪያዎችን በአደባባይ በመያዝ እና የቀጥታ ተኩስ ልምምድ በማድረግ ላይ ናቸው።
በእነዚህ የቀጥታ የቴሌቪዥን ሥርጭቶች ላይ በስፋት ጥቅም ላይ እየዋለ የሚገኘው የምሥራቅ ጀርመን ስሪት የሆነው እና በ7.62×39 ሚሊሜትር ጥይት የሚተኩሰው ‘MPi-KMS’ የተባለው የክላሽንኮቭ (AK-47) የጦር መሣሪያ ዓይነት ነው።
የቴሌቪዥን አቅራቢዎቹ የጦር መሣሪያውን እንዴት መፍታት፣ መግጠም፣ ጥይት መክተት እና ኢላማን መምታት እንደሚቻል ከእስላማዊ አብዮት ጥበቃ ጦር (IRGC) መኮንኖች ጋር በመሆን ለሕዝብ ቀጥታ ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ።
ኢራን ይህንን ያልተለመደ የቴሌቪዥን ስርጭት “ሕይወትን ለኢራን መስዋዕት ማድረግ” (Sacrifice Life For Iran) ከሚለው አገር አቀፍ የዝግጁነት ዘመቻ ጋር ያገናኘችው ሲሆን፣ እስካሁን ድረስ ከ31 ሚሊዮን በላይ ዜጎች በፈቃደኝነት ለዚህ የክተት ጥሪ መመዝገባቸውን የመንግስት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ከዚህም በተጨማሪ በቴህራን እና በኬርማንሻህ ከተሞች የሚገኙ ታዳጊ ወጣቶች በአደባባዮች እና በመስጊዶች በተዘጋጁ ወታደራዊ ድንኳኖች ውስጥ የጦር መሣሪያ አያያዝ፣ የውጊያ ስልቶች እና የአገር መከላከያ ስልጠናዎችን እየወሰዱ ይገኛሉ።
የኢራን ብሔራዊ ቴሌቪዥን ከፍተኛ ባለሥልጣን የሆኑት ሞህሴን ባርመህኒ የሀገሪቱ ሚዲያዎች ሙሉ በሙሉ “የጦርነት አቋም” (Wartime Posture) መያዝ እንዳለባቸው በይፋ ያወጁ ሲሆን፣ በአንድ የቀጥታ ስርጭት ፕሮግራም ላይ የቴሌቪዥን አቅራቢው ክላሽንኮቭ መሣሪያውን ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬትስ (UAE) ባንዲራ አነጣጥሮ ሲተኩስ የታየበት ትዕይንት በባህረ ሰላጤው ሀገራት ዘንድ ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ቁጣንና ውግዘትን አስከትሏል ሲል መናኸሪያ ኤፍ ኤም ዘግቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #iran #war #television
#usarmy #peace
#ethiopia | በኢራን፣ በአሜሪካ እና በእስራኤል መካከል ያለው ወታደራዊ ፍጥጫ እና ውጥረት እጅግ አስፈሪ ደረጃ ላይ በደረሰበት በዚህ ወቅት፣ የኢራን ብሔራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች (IRIB) ታሪክ ከየቀኑ የዜና እወጃ ወጥተው የቀጥታ የስልጠና መድረክ መሆናቸውን ዓለም በደነገጠ ስሜት እየተከታተለው ይገኛል።
የጣቢያዎቹ የዜና አቅራቢዎችና ጋዜጠኞች ራሳቸው የጦር መሣሪያዎችን በአደባባይ በመያዝ እና የቀጥታ ተኩስ ልምምድ በማድረግ ላይ ናቸው።
በእነዚህ የቀጥታ የቴሌቪዥን ሥርጭቶች ላይ በስፋት ጥቅም ላይ እየዋለ የሚገኘው የምሥራቅ ጀርመን ስሪት የሆነው እና በ7.62×39 ሚሊሜትር ጥይት የሚተኩሰው ‘MPi-KMS’ የተባለው የክላሽንኮቭ (AK-47) የጦር መሣሪያ ዓይነት ነው።
የቴሌቪዥን አቅራቢዎቹ የጦር መሣሪያውን እንዴት መፍታት፣ መግጠም፣ ጥይት መክተት እና ኢላማን መምታት እንደሚቻል ከእስላማዊ አብዮት ጥበቃ ጦር (IRGC) መኮንኖች ጋር በመሆን ለሕዝብ ቀጥታ ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ።
ኢራን ይህንን ያልተለመደ የቴሌቪዥን ስርጭት “ሕይወትን ለኢራን መስዋዕት ማድረግ” (Sacrifice Life For Iran) ከሚለው አገር አቀፍ የዝግጁነት ዘመቻ ጋር ያገናኘችው ሲሆን፣ እስካሁን ድረስ ከ31 ሚሊዮን በላይ ዜጎች በፈቃደኝነት ለዚህ የክተት ጥሪ መመዝገባቸውን የመንግስት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ከዚህም በተጨማሪ በቴህራን እና በኬርማንሻህ ከተሞች የሚገኙ ታዳጊ ወጣቶች በአደባባዮች እና በመስጊዶች በተዘጋጁ ወታደራዊ ድንኳኖች ውስጥ የጦር መሣሪያ አያያዝ፣ የውጊያ ስልቶች እና የአገር መከላከያ ስልጠናዎችን እየወሰዱ ይገኛሉ።
የኢራን ብሔራዊ ቴሌቪዥን ከፍተኛ ባለሥልጣን የሆኑት ሞህሴን ባርመህኒ የሀገሪቱ ሚዲያዎች ሙሉ በሙሉ “የጦርነት አቋም” (Wartime Posture) መያዝ እንዳለባቸው በይፋ ያወጁ ሲሆን፣ በአንድ የቀጥታ ስርጭት ፕሮግራም ላይ የቴሌቪዥን አቅራቢው ክላሽንኮቭ መሣሪያውን ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬትስ (UAE) ባንዲራ አነጣጥሮ ሲተኩስ የታየበት ትዕይንት በባህረ ሰላጤው ሀገራት ዘንድ ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ቁጣንና ውግዘትን አስከትሏል ሲል መናኸሪያ ኤፍ ኤም ዘግቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #iran #war #television
#usarmy #peace
16 days ago
አሉታዊ ትርክቶችን የተሻገረው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የአምስቱ ምሰሶዎች ስኬት
*************************
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መንግሥት በሚያከናውናቸው መጠነ ሰፊ የልማት ሥራዎች ላይ አልፎ አልፎ "ብልጭልጭ ጉዳዮች ላይ ብቻ ያተኮረ" የሚል ትችት ይሰማል።
ይሁን እንጂ መንግሥት ተግባራዊ እያደረገው ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ብዝኃ-ዘርፍን መሠረት ያደረገ እና ሁሉንም ቁልፍ የኢኮኖሚ ሞተሮች በእኩል ደረጃ በማልማት ላይ የተመሠረተ ስትራቴጂ ነው።
ይህ የኢኮኖሚ ማሻሻያ አንዱን ዘርፍ ብቻ ነጥሎ የሚያለማ ሳይሆን ግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝም እና ዲጂታል ኢኮኖሚን በእኩል ደረጃ የሚያንቀሳቅስ መሆኑ በተግባር እየታየ ይገኛል።
ይህ መዋቅራዊ ማሻሻያ የሀገራችንን የኢኮኖሚ ሥርዓት ከፍጆታ ወደ ምርት፣ ከአስመጪነት ወደ ላኪነት እና ከመንግሥት-መር ወደ ግል ዘርፍ መሪነት የሚያሻግር ጠንካራ መሠረት እየጣለ ይገኛል።
በግብርናው ዘርፍ የተመዘገበው ታሪካዊው የስንዴ አብዮት ኢትዮጵያን ወደ ላኪነት እያሸጋገረ ሲሆን፣ በ2018 በጀት ዓመት ሀገራዊ የስንዴ ምርት አቅም 305 ሚሊዮን ኩንታል መድረሱ ይህንኑ ያረጋግጣል።
በሌላ በኩል፣ “ኢትዮጵያ ታምርት” በተሰኘው ሀገራዊ ንቅናቄ አማካኝነት የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪው ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት 58 በመቶ የተኪ ምርት ድርሻ ላይ ደርሷል።
የዚህ ማሳያ የሚሆነው በ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄው ምርት አቁመው የነበሩ 993 ፋብሪካዎች ዳግም ወደ ምርት መግባታቸው ነው።
ቀደም ሲል ትኩረት ሳይሰጣቸው የቆዩት የኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቶች አሁን እሴት ተጨምሮባቸው የኢኮኖሚው አዲስ የጀርባ አጥንት መሆን ችለዋል።
በማዕድን ዘርፉ በተወሰዱት የሕግ እና አሠራር ማሻሻያዎች የድንጋይ ከሰል የሀገር ውስጥ ገበያ ድርሻ በ2010 ከነበረበት 17 በመቶ በ2017 ወደ 75 በመቶ ማደግ ችሏል። ወርቅም የውጭ ምንዛሬን በማስገኘት ከቡና ልቆ የተገኘው በዚሁ ማሻሻያ ነው።
በቱሪዝም ዘርፍም የ“ገበታ” ፕሮጀክቶች አዳዲስ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎችን በመፍጠርና የቱሪስት ገበያውን በማስፋት ለውጥ እያመጡ ይገኛሉ።
በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ 9 ወራት ብቻ 1.2 ሚሊዮን የውጭ ቱሪስቶችን በመሳብ ከ2.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱ የብዝኃ ዘርፍ ኢኮኖሚ ፖሊሲው ውጤማነት ማረጋገጫ ነው።
በቴክኖሎጂውና በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ረገድ “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025” ስትራቴጂ በስኬት ተጠናቅቆ ቦታውን ለ“ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” ስትራቴጂ አስረክቧል።
የዲጂታል ኢትዮጵያ እንቅስቃሴ የፋይናንስ ተደራሽነትን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ፣ እስከ መጋቢት 2018 ድረስ የተከፈቱ ዲጂታል አካውንቶችን ቁጥር 257.8 ሚሊዮን ማድረስ ተችሏል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ለሀገራዊ ኢኮኖሚው የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።
የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትም እንደ “መላ” ያሉ የሀገር ውስጥ ቋንቋዎችን የሚረዱ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ሥርዓቶችን በማልማት ኢትዮጵያን በአፍሪካ መሪ አድርጓታል።
ሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) በጤናው ዘርፍም እያመጣው ያለው እመርታ በአፍሪካ ሕብረት ጭምር ማረጋገጫ የተሰጠው እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሕብረቱ ሹመት ያገኙበት ነው።
በአጠቃላይ በእነዚህ አምስቱ ምሰሶዎች የተገኙ ስኬቶች ሀገራችን ከዚህ ቀደም ይገጥማት የነበረውን የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት ለመቅረፍ ትልቅ አቅም ፈጥረዋል።
የሥራ አጥነት ችግርን ከመቅረፍ አኳያ፣ እነዚህ ንቅናቄዎች በ2018 በሦስተኛው መቶ ቀናት ውስጥ ብቻ ከ96 ሺህ በላይ አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር ለዜጎች ተጠቃሚነት የላቀ ሚና ተጫውተዋል።
ባለፉት 8 ዓመታት ኢኮኖሚው በአማካይ በ7.5 በመቶ ያደገ ሲሆን፣ በ2018 ደግሞ የ10.2 በመቶ ድርብ አሀዝ ዕድገት እንደሚመዘገብ ይጠበቃል።
ይህ ሁሉ ሀገራችን በትክክለኛው የለውጥ እና የዘላቂ ብልጽግና ጎዳና ላይ መሆኗን በተጨባጭ የሚያስረግጥ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #economy #homegrowneconomicreform #ebc
*************************
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መንግሥት በሚያከናውናቸው መጠነ ሰፊ የልማት ሥራዎች ላይ አልፎ አልፎ "ብልጭልጭ ጉዳዮች ላይ ብቻ ያተኮረ" የሚል ትችት ይሰማል።
ይሁን እንጂ መንግሥት ተግባራዊ እያደረገው ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ብዝኃ-ዘርፍን መሠረት ያደረገ እና ሁሉንም ቁልፍ የኢኮኖሚ ሞተሮች በእኩል ደረጃ በማልማት ላይ የተመሠረተ ስትራቴጂ ነው።
ይህ የኢኮኖሚ ማሻሻያ አንዱን ዘርፍ ብቻ ነጥሎ የሚያለማ ሳይሆን ግብርና፣ ማኑፋክቸሪንግ፣ ማዕድን፣ ቱሪዝም እና ዲጂታል ኢኮኖሚን በእኩል ደረጃ የሚያንቀሳቅስ መሆኑ በተግባር እየታየ ይገኛል።
ይህ መዋቅራዊ ማሻሻያ የሀገራችንን የኢኮኖሚ ሥርዓት ከፍጆታ ወደ ምርት፣ ከአስመጪነት ወደ ላኪነት እና ከመንግሥት-መር ወደ ግል ዘርፍ መሪነት የሚያሻግር ጠንካራ መሠረት እየጣለ ይገኛል።
በግብርናው ዘርፍ የተመዘገበው ታሪካዊው የስንዴ አብዮት ኢትዮጵያን ወደ ላኪነት እያሸጋገረ ሲሆን፣ በ2018 በጀት ዓመት ሀገራዊ የስንዴ ምርት አቅም 305 ሚሊዮን ኩንታል መድረሱ ይህንኑ ያረጋግጣል።
በሌላ በኩል፣ “ኢትዮጵያ ታምርት” በተሰኘው ሀገራዊ ንቅናቄ አማካኝነት የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪው ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት 58 በመቶ የተኪ ምርት ድርሻ ላይ ደርሷል።
የዚህ ማሳያ የሚሆነው በ“ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄው ምርት አቁመው የነበሩ 993 ፋብሪካዎች ዳግም ወደ ምርት መግባታቸው ነው።
ቀደም ሲል ትኩረት ሳይሰጣቸው የቆዩት የኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቶች አሁን እሴት ተጨምሮባቸው የኢኮኖሚው አዲስ የጀርባ አጥንት መሆን ችለዋል።
በማዕድን ዘርፉ በተወሰዱት የሕግ እና አሠራር ማሻሻያዎች የድንጋይ ከሰል የሀገር ውስጥ ገበያ ድርሻ በ2010 ከነበረበት 17 በመቶ በ2017 ወደ 75 በመቶ ማደግ ችሏል። ወርቅም የውጭ ምንዛሬን በማስገኘት ከቡና ልቆ የተገኘው በዚሁ ማሻሻያ ነው።
በቱሪዝም ዘርፍም የ“ገበታ” ፕሮጀክቶች አዳዲስ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎችን በመፍጠርና የቱሪስት ገበያውን በማስፋት ለውጥ እያመጡ ይገኛሉ።
በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ 9 ወራት ብቻ 1.2 ሚሊዮን የውጭ ቱሪስቶችን በመሳብ ከ2.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱ የብዝኃ ዘርፍ ኢኮኖሚ ፖሊሲው ውጤማነት ማረጋገጫ ነው።
በቴክኖሎጂውና በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ረገድ “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025” ስትራቴጂ በስኬት ተጠናቅቆ ቦታውን ለ“ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030” ስትራቴጂ አስረክቧል።
የዲጂታል ኢትዮጵያ እንቅስቃሴ የፋይናንስ ተደራሽነትን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ፣ እስከ መጋቢት 2018 ድረስ የተከፈቱ ዲጂታል አካውንቶችን ቁጥር 257.8 ሚሊዮን ማድረስ ተችሏል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ለሀገራዊ ኢኮኖሚው የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።
የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትም እንደ “መላ” ያሉ የሀገር ውስጥ ቋንቋዎችን የሚረዱ የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ሥርዓቶችን በማልማት ኢትዮጵያን በአፍሪካ መሪ አድርጓታል።
ሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) በጤናው ዘርፍም እያመጣው ያለው እመርታ በአፍሪካ ሕብረት ጭምር ማረጋገጫ የተሰጠው እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሕብረቱ ሹመት ያገኙበት ነው።
በአጠቃላይ በእነዚህ አምስቱ ምሰሶዎች የተገኙ ስኬቶች ሀገራችን ከዚህ ቀደም ይገጥማት የነበረውን የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት ለመቅረፍ ትልቅ አቅም ፈጥረዋል።
የሥራ አጥነት ችግርን ከመቅረፍ አኳያ፣ እነዚህ ንቅናቄዎች በ2018 በሦስተኛው መቶ ቀናት ውስጥ ብቻ ከ96 ሺህ በላይ አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር ለዜጎች ተጠቃሚነት የላቀ ሚና ተጫውተዋል።
ባለፉት 8 ዓመታት ኢኮኖሚው በአማካይ በ7.5 በመቶ ያደገ ሲሆን፣ በ2018 ደግሞ የ10.2 በመቶ ድርብ አሀዝ ዕድገት እንደሚመዘገብ ይጠበቃል።
ይህ ሁሉ ሀገራችን በትክክለኛው የለውጥ እና የዘላቂ ብልጽግና ጎዳና ላይ መሆኗን በተጨባጭ የሚያስረግጥ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #economy #homegrowneconomicreform #ebc
16 days ago
ሰላም! እንዴት አመሻችሁ?
----------------------------
የአረንጓዴ አብዮት….
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያውያንን ከዳር እስከ ዳር ለተመሳሳይ ሀገራዊ ዓላማ ያሰለፈ ታላቅ ሀገራዊ አብዮት ነው፡፡
ይህ ታላቅ የተፈጥሮ ሀብት የልማት እቅድ በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ትኩረት እና አድናቆት ያገኘ የአካባቢ ጥበቃ ሞዴል ለመሆን በቅቷል።
ፕሮግራሙ በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል፣ የደን ሽፋንን ለማሳደግ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ውሏል፡፡
በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረ ይህ ብሔራዊ የችግኝ ተከላ ፕሮግራም፣ ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ እስከ አሁን ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች እንዲተከሉ ምክንያት ሆኗል።
በዘመቻው በተከናወኑ ተከታታይ ስራዎች የሀገሪቱ የደን ሽፋን በከፍተኛ ሁኔታ አድጎ 23.6 በመቶ ደርሷል።
በዚህ ዓመት የሁለተኛው ምዕራፍ ማብቂያ በአጠቃላይ 50 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል የታለመ ሲሆን፣ ይህም በየዓመቱ በአማካይ 7.5 ቢሊዮን ችግኞች ይተከላሉ እንደ ማለት ነው።
ሐምሌ 2017 ዓ.ም በተደረገ የአንድ ቀን ታላቅ የችግኝ ተከላ ዘመቻ ብቻ ከ714 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በአንድ ጀምበር በመትከል አዲስ የዓለም ክብረ ወሰን ተመዝግቧል።
በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ ከማልበስ ባለፈ ለኢኮኖሚ እመርታ ትልቅ ትኩረት ተሰጥቷል። በመርሃ ግብሩ የተተከሉት ችግኞችም ያለምክንያት አልተተከሉም፡፡
ከ56 በመቶ በላይ የሚሆነው የጥምር ደን እርሻ ሲሆን፣ ለአርሶ አደሩ ተጨማሪ ገቢና የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡ እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ እና ፓፓያ ያሉ የፍራፍሬ ችግኞች እንዲሁም ለመኖ የሚያገለግሉ ዕፅዋትን ያካተተ ነው።
ሌላኛውና ሁለተኛው አይነት ለአፈር ጥበቃ፣ ለውሃ አካላት መነቃቃት እና ለአካባቢ ጥበቃ የሚውሉ የሀገር በቀል የእፅዋት ዝርያዎች ናቸው።
ሦስተኛው እና በምክንያት የተተከሉት የችግኝ አይነቶች ለከተማ ውበት የሚውሉት ያጠቃልላል፡፡ እነዚህም የከተማ የአየር ንብረትን ለማስተካከል እና ለጽዳትና ውበት የተተከሉ ዛፎች ናቸው።
ችግኝ በመትከላችን የውሃ አካላትን ማዳን ችለናል፡፡ ከሀገራችን ተርፈንም የበረሃማነትን መስፋፋት ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ ለመግታት፣ ቀጣናዊ አጋርነቷን በመፍጠር አህጉራዊ ትስስርን ማሳደግ ችለናል፡፡
በዚሁ በርትተን ከቀጠልን የሀገራችን የደን ሽፋን አሁን ካለው በላይ በማሳደግ ከዓለም አቀፍ የካርበን ሽያጭ ልማት የምናገኘው ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እያደገ ይመጣል።
ይህንንም ለማሳካት አሁን ያለውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከአበው ብሂል ጋር ማስተሳሰር ያሻናል፡፡
በእኛ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ችግኝ መትከልና መንከባከብ ትልቅ ስፍራ ይሰጠዋል፡፡
አብያተ ክርስቲያናት እና ገዳማት ዙሪያን ብንመለከት ከጥንት ጀምሮ በዛፍ የመሸፈን ባህል አለን፡፡
ገዳ ስርዓት ለዛፍ ትልቅ ስፍራ ይሰጣል፡፡ ያለ አግባብ ዛፍ የቆረጠ ሰው መቀጮው ከባድ ነው፡፡
በሀገራችን ዛፍ ከጥላነት ያለፈ ትርጉም አለው፡፡ በህይወት እያለን ጥላ ከለላ፣ በዘላቂ ማረፊያም በጥንት እንደ ምልክት ይተከል ነበር፡፡
ዛፍን ለሽምግልና እና ለባህላዊ ስነ-ስርዓቶች መጠቀም የተለመደ ነው። ቤተሰብ ለቀጣይ ልጆቻቸው መሬት ሲያወርሱ ዛፍ ተክለው የማስረከብ የቆየ ልማድ አላቸው።
በመሆኑም መልካም ባህላችንን ከአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ጋር በመደመር የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ህልማችንን እናሳካለን፡፡
----------------------------
የአረንጓዴ አብዮት….
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያውያንን ከዳር እስከ ዳር ለተመሳሳይ ሀገራዊ ዓላማ ያሰለፈ ታላቅ ሀገራዊ አብዮት ነው፡፡
ይህ ታላቅ የተፈጥሮ ሀብት የልማት እቅድ በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ትኩረት እና አድናቆት ያገኘ የአካባቢ ጥበቃ ሞዴል ለመሆን በቅቷል።
ፕሮግራሙ በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል፣ የደን ሽፋንን ለማሳደግ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ውሏል፡፡
በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረ ይህ ብሔራዊ የችግኝ ተከላ ፕሮግራም፣ ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ እስከ አሁን ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች እንዲተከሉ ምክንያት ሆኗል።
በዘመቻው በተከናወኑ ተከታታይ ስራዎች የሀገሪቱ የደን ሽፋን በከፍተኛ ሁኔታ አድጎ 23.6 በመቶ ደርሷል።
በዚህ ዓመት የሁለተኛው ምዕራፍ ማብቂያ በአጠቃላይ 50 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል የታለመ ሲሆን፣ ይህም በየዓመቱ በአማካይ 7.5 ቢሊዮን ችግኞች ይተከላሉ እንደ ማለት ነው።
ሐምሌ 2017 ዓ.ም በተደረገ የአንድ ቀን ታላቅ የችግኝ ተከላ ዘመቻ ብቻ ከ714 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በአንድ ጀምበር በመትከል አዲስ የዓለም ክብረ ወሰን ተመዝግቧል።
በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ ከማልበስ ባለፈ ለኢኮኖሚ እመርታ ትልቅ ትኩረት ተሰጥቷል። በመርሃ ግብሩ የተተከሉት ችግኞችም ያለምክንያት አልተተከሉም፡፡
ከ56 በመቶ በላይ የሚሆነው የጥምር ደን እርሻ ሲሆን፣ ለአርሶ አደሩ ተጨማሪ ገቢና የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡ እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ እና ፓፓያ ያሉ የፍራፍሬ ችግኞች እንዲሁም ለመኖ የሚያገለግሉ ዕፅዋትን ያካተተ ነው።
ሌላኛውና ሁለተኛው አይነት ለአፈር ጥበቃ፣ ለውሃ አካላት መነቃቃት እና ለአካባቢ ጥበቃ የሚውሉ የሀገር በቀል የእፅዋት ዝርያዎች ናቸው።
ሦስተኛው እና በምክንያት የተተከሉት የችግኝ አይነቶች ለከተማ ውበት የሚውሉት ያጠቃልላል፡፡ እነዚህም የከተማ የአየር ንብረትን ለማስተካከል እና ለጽዳትና ውበት የተተከሉ ዛፎች ናቸው።
ችግኝ በመትከላችን የውሃ አካላትን ማዳን ችለናል፡፡ ከሀገራችን ተርፈንም የበረሃማነትን መስፋፋት ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ ለመግታት፣ ቀጣናዊ አጋርነቷን በመፍጠር አህጉራዊ ትስስርን ማሳደግ ችለናል፡፡
በዚሁ በርትተን ከቀጠልን የሀገራችን የደን ሽፋን አሁን ካለው በላይ በማሳደግ ከዓለም አቀፍ የካርበን ሽያጭ ልማት የምናገኘው ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እያደገ ይመጣል።
ይህንንም ለማሳካት አሁን ያለውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከአበው ብሂል ጋር ማስተሳሰር ያሻናል፡፡
በእኛ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ችግኝ መትከልና መንከባከብ ትልቅ ስፍራ ይሰጠዋል፡፡
አብያተ ክርስቲያናት እና ገዳማት ዙሪያን ብንመለከት ከጥንት ጀምሮ በዛፍ የመሸፈን ባህል አለን፡፡
ገዳ ስርዓት ለዛፍ ትልቅ ስፍራ ይሰጣል፡፡ ያለ አግባብ ዛፍ የቆረጠ ሰው መቀጮው ከባድ ነው፡፡
በሀገራችን ዛፍ ከጥላነት ያለፈ ትርጉም አለው፡፡ በህይወት እያለን ጥላ ከለላ፣ በዘላቂ ማረፊያም በጥንት እንደ ምልክት ይተከል ነበር፡፡
ዛፍን ለሽምግልና እና ለባህላዊ ስነ-ስርዓቶች መጠቀም የተለመደ ነው። ቤተሰብ ለቀጣይ ልጆቻቸው መሬት ሲያወርሱ ዛፍ ተክለው የማስረከብ የቆየ ልማድ አላቸው።
በመሆኑም መልካም ባህላችንን ከአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ጋር በመደመር የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ህልማችንን እናሳካለን፡፡
Sponsored by
Surafel
17 days ago
18 days ago
ድንቁ ሔኖክ
#ethiopia | የሔኖክ የመጀመርያ ፊልም "ትራፊኳ.." የተሰኘው ፊልም ነበር። ከሜሮን ጌትነት ጋር ነበር አብረው የሰሩት። እዛ ፊልም ላይ የተመለከትነው የሔኖክ Acting የመጀመርያ ፊልሙ ሁላ አይመስልም ነበር። ይህ ማለት ከዛሬ 12 እና 13 አመት በፊት ነው።
ከዛ በኋላ በርካታ ፊልሞች ላይ በትወና ተሳትፏል። በሂደት ደግሞ ፊልሞችን እና የሙዚቃ ቪዲዮዎችንም ጭምር ዳይሬክት ማድረግ ጀመረ። ከታሪኩ [ ባባ ] ጋር እና ከማንዴላ ጋር የሰራው አንድ ፊልም አለ - በጣም የሚመቸኝ። እነ አለምሰገድ ተስፋዬን፣ ሙሉአለም ጌታቸው፣ ማንዴላን ካነሳን ሔኖክንም በእነሱ ምድብ ልናካትተው የምንችል ምርጥ የፊልም ተዋናይ ነው። ትናንትና በ Seifu on EBS ላይ ቀርቦ እሱ ራሱ እንደተናገረው ከሆነ የሔኖክ ወንድሙ ህይወት በ 2 ይከፈላል። የመጀመርያው ፈረጃ የተሰኘውን አዲሱን ፊልም መስራት ከመጀመሩ በፊት ያለው ህይወቱ ነው - ቀጥሎ ደግሞ ከፈረጃ በኋላ ያለው ህይወት።
ሔኖክ አዲስ ለሚሰራው ፊልም ብዙ ዋጋ ከፍሏል። የሚታዩም - የማይታዩም ብዙ መስእዋትነቶች ተከፍለዋል። ለዚህ ፊልም Character ብሎ ከሰውነቱ ላይ 41 ኪሎ ቀንሷል። የፊልሙ ገፀባህሪ የሰውነት አቋም ስላስገደደው።
ሔኖክ "ፈረጃ.." ፊልምን ሲሰራ 4 ነገሮችን ነው አብሮ የሚሰራው። የፊልሙ መሪ ተዋናይ ነው ፤ ደራሲ ነው ፤ ዳይሬክተር ነው ፤ Executive Producer ነው። ይህንን ፊልም እውን ለማድረግ ደግሞ 6 አመታት ያህል ፈጅቶበታል። ሌላ ስራ ሳይሰራ - ሙሉ ትኩረቱን "ፈረጃ.." ላይ ብቻ አድርጎ።
በገንዘብም ቢሆን - ብዙ አውጥቶበታል። መኪናውን እስከመሸጥ ድረስ ደርሷል። ፊልሙ በአጠቃላይ የፈጀው 7.5 ሚሊየን ብር ነው።
ከህዝብ [ ከ 1,200 ሰዎች ] የተዋጣው ገንዘብ ግን 3 ሚሊየን ብር ብቻ ነበር። እውነት ለመናገር ሔኖክ ያሰበው ሀሳብ በጣም ገራሚ ሀሳብ ነው።
"ህዝብ አምስት - አምስት ብር አዋጥቶ ፊልም እንስራ ከዛ በኋላ በዚህ ፊልም ሽያጭ ደግሞ ሌላ ፊልም ይሰራል ፤ ህዝቡን የማስቸግረው አንድ ጊዜ ብቻ ነው።
ሁለተኛው ፊልም ከመጀመርያው ገቢ ነው የሚሰራው። ሶስተኛው ፊልም ደግሞ ከሁለተኛው ፊልም ገቢ። እንደዚህ እያልኩ - 50 ፊልሞችን የመስራት እቅድ አለኝ.." ብሏል። በጣም እኮ ፀዴ ሀሳብ ነው።
ሔኖክ ያመጣው "ህዝብ አምስት - አምስት ብር አዋጥቶ ፊልም መስራት.." የሚለው ሀሳብ በአለም አቀፍ ደረጃ Crowd funding የሚባለው እና ብዙ ትልልቅ ስራዎች የሚሰሩበት መንገድ ነው።
በሀገራችን ይሄንን ተጠቅሞ የፊልም ኢንዱስትሪውን Self-sustaining [ ራሱን በራሱ የሚደግፍ ኢንዱስትሪ ] ለማድረግ ማሰቡ ትልቅ አብዮት ነው። ይህ ሀሳብ ፊልምን ከባለሀብቶች ጥገኝነት አውጥቶ የህዝብ ንብረት የሚያደርግ ግሩም ሀሳብ ነው።
ህዝቡ 5 ብር ሲያዋጣ ዝም ብሎ ተመልካች ሳይሆን የፊልሙ ባለቤት እና ደጋፊ ይሆናል ማለት ነው። እኛ ሀገር ለአንድ የጥበብ ስራ 6 አመት ሙሉ ተግቶ መስራት እብደት ሊመስል ይችላል ፤ ነገር ግን እውነተኛ ጥበብ የሚወለደው እንዲህ አይነት ትጋት ውስጥ ነው።
ሔኖክ ለጥበብ የከፈለውን መስዋዕትነት [ ገንዘቡን፣ አካሉን እና ጊዜውን ] የምንክሰው እኛ ተመልካቾች ይሄንን ራእይ ስንደግፍና ሀሳቡን ስንገዛ ብቻ ነው።
በተለይ በኢትዮጵያ የፊልም ኢንዱስትሪ ውስጥ ለገፀ-ባህሪ [ Character ] ተብሎ 41 ኪሎ መቀነስ እና መኪና እስከመሸጥ ድረስ መድረስ - የኪነጥበብን ፍቅርና ቁርጠኝነትን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።
በፍራኦል ሀበሻ
#ethiopia | የሔኖክ የመጀመርያ ፊልም "ትራፊኳ.." የተሰኘው ፊልም ነበር። ከሜሮን ጌትነት ጋር ነበር አብረው የሰሩት። እዛ ፊልም ላይ የተመለከትነው የሔኖክ Acting የመጀመርያ ፊልሙ ሁላ አይመስልም ነበር። ይህ ማለት ከዛሬ 12 እና 13 አመት በፊት ነው።
ከዛ በኋላ በርካታ ፊልሞች ላይ በትወና ተሳትፏል። በሂደት ደግሞ ፊልሞችን እና የሙዚቃ ቪዲዮዎችንም ጭምር ዳይሬክት ማድረግ ጀመረ። ከታሪኩ [ ባባ ] ጋር እና ከማንዴላ ጋር የሰራው አንድ ፊልም አለ - በጣም የሚመቸኝ። እነ አለምሰገድ ተስፋዬን፣ ሙሉአለም ጌታቸው፣ ማንዴላን ካነሳን ሔኖክንም በእነሱ ምድብ ልናካትተው የምንችል ምርጥ የፊልም ተዋናይ ነው። ትናንትና በ Seifu on EBS ላይ ቀርቦ እሱ ራሱ እንደተናገረው ከሆነ የሔኖክ ወንድሙ ህይወት በ 2 ይከፈላል። የመጀመርያው ፈረጃ የተሰኘውን አዲሱን ፊልም መስራት ከመጀመሩ በፊት ያለው ህይወቱ ነው - ቀጥሎ ደግሞ ከፈረጃ በኋላ ያለው ህይወት።
ሔኖክ አዲስ ለሚሰራው ፊልም ብዙ ዋጋ ከፍሏል። የሚታዩም - የማይታዩም ብዙ መስእዋትነቶች ተከፍለዋል። ለዚህ ፊልም Character ብሎ ከሰውነቱ ላይ 41 ኪሎ ቀንሷል። የፊልሙ ገፀባህሪ የሰውነት አቋም ስላስገደደው።
ሔኖክ "ፈረጃ.." ፊልምን ሲሰራ 4 ነገሮችን ነው አብሮ የሚሰራው። የፊልሙ መሪ ተዋናይ ነው ፤ ደራሲ ነው ፤ ዳይሬክተር ነው ፤ Executive Producer ነው። ይህንን ፊልም እውን ለማድረግ ደግሞ 6 አመታት ያህል ፈጅቶበታል። ሌላ ስራ ሳይሰራ - ሙሉ ትኩረቱን "ፈረጃ.." ላይ ብቻ አድርጎ።
በገንዘብም ቢሆን - ብዙ አውጥቶበታል። መኪናውን እስከመሸጥ ድረስ ደርሷል። ፊልሙ በአጠቃላይ የፈጀው 7.5 ሚሊየን ብር ነው።
ከህዝብ [ ከ 1,200 ሰዎች ] የተዋጣው ገንዘብ ግን 3 ሚሊየን ብር ብቻ ነበር። እውነት ለመናገር ሔኖክ ያሰበው ሀሳብ በጣም ገራሚ ሀሳብ ነው።
"ህዝብ አምስት - አምስት ብር አዋጥቶ ፊልም እንስራ ከዛ በኋላ በዚህ ፊልም ሽያጭ ደግሞ ሌላ ፊልም ይሰራል ፤ ህዝቡን የማስቸግረው አንድ ጊዜ ብቻ ነው።
ሁለተኛው ፊልም ከመጀመርያው ገቢ ነው የሚሰራው። ሶስተኛው ፊልም ደግሞ ከሁለተኛው ፊልም ገቢ። እንደዚህ እያልኩ - 50 ፊልሞችን የመስራት እቅድ አለኝ.." ብሏል። በጣም እኮ ፀዴ ሀሳብ ነው።
ሔኖክ ያመጣው "ህዝብ አምስት - አምስት ብር አዋጥቶ ፊልም መስራት.." የሚለው ሀሳብ በአለም አቀፍ ደረጃ Crowd funding የሚባለው እና ብዙ ትልልቅ ስራዎች የሚሰሩበት መንገድ ነው።
በሀገራችን ይሄንን ተጠቅሞ የፊልም ኢንዱስትሪውን Self-sustaining [ ራሱን በራሱ የሚደግፍ ኢንዱስትሪ ] ለማድረግ ማሰቡ ትልቅ አብዮት ነው። ይህ ሀሳብ ፊልምን ከባለሀብቶች ጥገኝነት አውጥቶ የህዝብ ንብረት የሚያደርግ ግሩም ሀሳብ ነው።
ህዝቡ 5 ብር ሲያዋጣ ዝም ብሎ ተመልካች ሳይሆን የፊልሙ ባለቤት እና ደጋፊ ይሆናል ማለት ነው። እኛ ሀገር ለአንድ የጥበብ ስራ 6 አመት ሙሉ ተግቶ መስራት እብደት ሊመስል ይችላል ፤ ነገር ግን እውነተኛ ጥበብ የሚወለደው እንዲህ አይነት ትጋት ውስጥ ነው።
ሔኖክ ለጥበብ የከፈለውን መስዋዕትነት [ ገንዘቡን፣ አካሉን እና ጊዜውን ] የምንክሰው እኛ ተመልካቾች ይሄንን ራእይ ስንደግፍና ሀሳቡን ስንገዛ ብቻ ነው።
በተለይ በኢትዮጵያ የፊልም ኢንዱስትሪ ውስጥ ለገፀ-ባህሪ [ Character ] ተብሎ 41 ኪሎ መቀነስ እና መኪና እስከመሸጥ ድረስ መድረስ - የኪነጥበብን ፍቅርና ቁርጠኝነትን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።
በፍራኦል ሀበሻ
23 days ago
“አዲሲቱ አዲስ”
የጥናታዊ ፅሑፍና የውይይት መድረክ ተካሄደ
የአዲስ አበባ ከተማን ዕድገት የቃኘና የከተሞችን አመሠራረት ያሳየ ምሁራዊ የጥናታዊ ፅሑፍ አቅርቦትና የውይይት መድረክ በዛሬው ዕለት በአድዋ ሙዚየም አዳራሽ ተካሂዷል።
ናሽናል ሚድያ አክሲዮን ማህበር (ኤን ቢ ሲ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን) ባዘጋጀው በዚህ መድረክ የአዲስ አበባን እድገትና ውበት የተመለከቱ የጥናት ወረቀቶች ቀርበዋል።የጥያቄና መልስ፣የአስተያየትና የውይይት መርሀ -ግብርም ተካሂዷል።
የናሽናል ሚዲያ አክስዮን ማህበር ም/ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘካርያስ ብርሃኑ የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል።አቶ ዘካርያስ እንዳሉት ኤን ቢ ሲ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ተመልካችን የሚመጥኑ፣በጥናትና ምርምር የተደገፉ ርዕሰ ጉዳዮችን አየር ላይ እያዋለ መሆኑን ገልፀው በአድዋ ሙዚየም የተካሄደው ሲምፖዚየምም የዚሁ አካል መሆኑን ገልፀዋል።
የከተማነት ጉዞ ከትናንት እስከ ዛሬ እሳቤውና አፈፃፀሙ፣ ስኬትና ተግዳሮቶቹ ምን እንደሆነ በጥልቀት መስማትና መረዳት፣መጠየቅና መወያየት፣ ከምንም በላይ ደግሞ በከተማ ማደስ የታየው አስደናቂ የለውጥ አመራርና የሥራ አፈጻጸም በሌሎች የህይወትና የኑሮ ለውጥ ሥራዎች እውን የሚሆንበትን ምስጢር አውቆ ለመተግበር እንደዚህ ዓይነት መድረክ በጣም አስፈላጊና ወሳኝ እንደሆነ አቶ ዘካርያስ ብርሃኑ ገልጸዋል።
ፖለቲከኞች እና አስተዳዳሪዎቹ ከሚነግሩት ባሻገር የዘርፉ ምሁራንና ተመራማሪዎች ፣ባለድርሻ አካላትና ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በአንድ መድረክ ታድመው ለተሻለ የጋራ ውጤት በጋራ እንዲመክሩና እንዲወያዩ በማለም መድረኩ የተዘጋጀ መሆኑንም ኃላፊው ጨምረው ገልጸዋል።
በዕለቱ፣ አርኪቴክት ዳዊት በንቲ "ከተሞችና የአዲስ አበባ ዘመናዊ ጉዞ" በሚል ርዕስ ጥናታዊ ፅሑፍ አቅርበዋል።
አርክቴክት ዳዊት በንቲ " ከተሞችና የአዲስ አበባ ጉዞ" በሚል ርዕስ ባቀረቡት የጥናት ወረቀት በዓለም ላይ የከተሞች አመሠራረት ላይ ታሪካዊ ዳራዎችን አንስተዋል።
እንደ አርክቴክት ዳዊት ስለ ከተማ እድገት ስናነሳ የመካከለኛው ዘመን ከተሞች፣የህዳሴ ዘመን ከተሞች እንደነበሩ ጠቅሰው ከ1800 አንስቶ በኢንዱስትሪ አብዮት የከተማ ተሀድሶ ይደረግ እንደነበር አንስተዋል።
የአዲስ አበባ ዘመናዊ ጉዞ በብዙ የዕድገት ደረጃዎች ማለፉን የጥናት አቅራቢው ገልፀው ይህም ታሪክ በሙዚየም ተቀምጦ አዲሱ ትውልድ ሊያውቀው ይገባል ብለዋል።
"የከተማ ትራንስፎርሜሽን እሳቤዎች፣ ትግበራ እና እንድምታዎች በአዲስ አበባ" በሚል ርዕስ ጥናት ያቀረቡት እሸትአየሁ ክንፉ( ዶ/ር ኢንጂነር) አዲስ አበባ ከንጉሡ ዘመን አንስቶ እድሳት እየተደረገላት መምጣቷን ገልፀዋል። አዲስ አበባ በቀደሙት ዘመናት ለማዘመን ነባራዊ ሁኔታዋ ባይመችም በጊዜው የመጡት መንግሥታት እንደ አቅማቸው ከተማዋን ለመቀየር መሞከራቸውን የጥናት አቅራቢው ገልፀዋል።
ከ2010 ዓ.ም በኃላ የከተሞች ጉዳይ እንደ ትልቅ ጉዳይ ተቆጥሮና ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶበት ሰፊ የማዘመን ሥራ መሠራቱን፣ይህም በቁርጠኛ አመራር የመጣ መሆኑን ጥናት አቅራቢው ገልፀዋል።
በዕለቱ የታደሙ ባለድርሻ አካላት እና ከልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተጋበዙ እንግዶችም ለጥናት አቅራቢዎቹ አስተያየት እና ጥያቄዎችን ሰንዝረዋል።
በሲንፖዝየሙ የታደሙት የአዲስ አበባ ከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ ከርዕሰ ጉዳዩ ጋር በተያያዘ ሰፊ ማብራሪያና ገጠመኞቻቸውን ተናግረዋል።
የሲምፖዚየሙ አወያይ እና የኤን ቢ ሲ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ብሩክ ከበደ በርዕሰ ጉዳዩ ዙሪያ እንደ ሚዲያ የተሰራውን እና ሊሰራ የሚገባውን ጉዳይ አብራርተዋል። የከተማዋን ሥር ነቀል እድገትና ተያይዘው የመጡ ቱሩፋቶች የምንረዳበትንና ከህዝብ ጋር የምናገናኝበትን የመገናኛ ዘዴ (communication)በተመለከተም ሰፊ ሞያዊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
"ኢዲሲቱ አዲስ" በተሰኝ ዐቢይ ርዕስ ዛሬ የተካሄደው ሲንፖዝየም ሙሉ መርሃግብር በኤን ቢ ሲ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በቅርቡ ለህዝብ እንደሚሰራጭ ታውቋል።
የዚህን ስምፖዚየም የሚድያ ማስተባበር ያከናወነው ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን (ዕዝራ እጅጉ) እንደሆነ ታውቋል።
የጥናታዊ ፅሑፍና የውይይት መድረክ ተካሄደ
የአዲስ አበባ ከተማን ዕድገት የቃኘና የከተሞችን አመሠራረት ያሳየ ምሁራዊ የጥናታዊ ፅሑፍ አቅርቦትና የውይይት መድረክ በዛሬው ዕለት በአድዋ ሙዚየም አዳራሽ ተካሂዷል።
ናሽናል ሚድያ አክሲዮን ማህበር (ኤን ቢ ሲ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን) ባዘጋጀው በዚህ መድረክ የአዲስ አበባን እድገትና ውበት የተመለከቱ የጥናት ወረቀቶች ቀርበዋል።የጥያቄና መልስ፣የአስተያየትና የውይይት መርሀ -ግብርም ተካሂዷል።
የናሽናል ሚዲያ አክስዮን ማህበር ም/ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘካርያስ ብርሃኑ የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል።አቶ ዘካርያስ እንዳሉት ኤን ቢ ሲ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ተመልካችን የሚመጥኑ፣በጥናትና ምርምር የተደገፉ ርዕሰ ጉዳዮችን አየር ላይ እያዋለ መሆኑን ገልፀው በአድዋ ሙዚየም የተካሄደው ሲምፖዚየምም የዚሁ አካል መሆኑን ገልፀዋል።
የከተማነት ጉዞ ከትናንት እስከ ዛሬ እሳቤውና አፈፃፀሙ፣ ስኬትና ተግዳሮቶቹ ምን እንደሆነ በጥልቀት መስማትና መረዳት፣መጠየቅና መወያየት፣ ከምንም በላይ ደግሞ በከተማ ማደስ የታየው አስደናቂ የለውጥ አመራርና የሥራ አፈጻጸም በሌሎች የህይወትና የኑሮ ለውጥ ሥራዎች እውን የሚሆንበትን ምስጢር አውቆ ለመተግበር እንደዚህ ዓይነት መድረክ በጣም አስፈላጊና ወሳኝ እንደሆነ አቶ ዘካርያስ ብርሃኑ ገልጸዋል።
ፖለቲከኞች እና አስተዳዳሪዎቹ ከሚነግሩት ባሻገር የዘርፉ ምሁራንና ተመራማሪዎች ፣ባለድርሻ አካላትና ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በአንድ መድረክ ታድመው ለተሻለ የጋራ ውጤት በጋራ እንዲመክሩና እንዲወያዩ በማለም መድረኩ የተዘጋጀ መሆኑንም ኃላፊው ጨምረው ገልጸዋል።
በዕለቱ፣ አርኪቴክት ዳዊት በንቲ "ከተሞችና የአዲስ አበባ ዘመናዊ ጉዞ" በሚል ርዕስ ጥናታዊ ፅሑፍ አቅርበዋል።
አርክቴክት ዳዊት በንቲ " ከተሞችና የአዲስ አበባ ጉዞ" በሚል ርዕስ ባቀረቡት የጥናት ወረቀት በዓለም ላይ የከተሞች አመሠራረት ላይ ታሪካዊ ዳራዎችን አንስተዋል።
እንደ አርክቴክት ዳዊት ስለ ከተማ እድገት ስናነሳ የመካከለኛው ዘመን ከተሞች፣የህዳሴ ዘመን ከተሞች እንደነበሩ ጠቅሰው ከ1800 አንስቶ በኢንዱስትሪ አብዮት የከተማ ተሀድሶ ይደረግ እንደነበር አንስተዋል።
የአዲስ አበባ ዘመናዊ ጉዞ በብዙ የዕድገት ደረጃዎች ማለፉን የጥናት አቅራቢው ገልፀው ይህም ታሪክ በሙዚየም ተቀምጦ አዲሱ ትውልድ ሊያውቀው ይገባል ብለዋል።
"የከተማ ትራንስፎርሜሽን እሳቤዎች፣ ትግበራ እና እንድምታዎች በአዲስ አበባ" በሚል ርዕስ ጥናት ያቀረቡት እሸትአየሁ ክንፉ( ዶ/ር ኢንጂነር) አዲስ አበባ ከንጉሡ ዘመን አንስቶ እድሳት እየተደረገላት መምጣቷን ገልፀዋል። አዲስ አበባ በቀደሙት ዘመናት ለማዘመን ነባራዊ ሁኔታዋ ባይመችም በጊዜው የመጡት መንግሥታት እንደ አቅማቸው ከተማዋን ለመቀየር መሞከራቸውን የጥናት አቅራቢው ገልፀዋል።
ከ2010 ዓ.ም በኃላ የከተሞች ጉዳይ እንደ ትልቅ ጉዳይ ተቆጥሮና ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶበት ሰፊ የማዘመን ሥራ መሠራቱን፣ይህም በቁርጠኛ አመራር የመጣ መሆኑን ጥናት አቅራቢው ገልፀዋል።
በዕለቱ የታደሙ ባለድርሻ አካላት እና ከልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተጋበዙ እንግዶችም ለጥናት አቅራቢዎቹ አስተያየት እና ጥያቄዎችን ሰንዝረዋል።
በሲንፖዝየሙ የታደሙት የአዲስ አበባ ከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ ከርዕሰ ጉዳዩ ጋር በተያያዘ ሰፊ ማብራሪያና ገጠመኞቻቸውን ተናግረዋል።
የሲምፖዚየሙ አወያይ እና የኤን ቢ ሲ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ብሩክ ከበደ በርዕሰ ጉዳዩ ዙሪያ እንደ ሚዲያ የተሰራውን እና ሊሰራ የሚገባውን ጉዳይ አብራርተዋል። የከተማዋን ሥር ነቀል እድገትና ተያይዘው የመጡ ቱሩፋቶች የምንረዳበትንና ከህዝብ ጋር የምናገናኝበትን የመገናኛ ዘዴ (communication)በተመለከተም ሰፊ ሞያዊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
"ኢዲሲቱ አዲስ" በተሰኝ ዐቢይ ርዕስ ዛሬ የተካሄደው ሲንፖዝየም ሙሉ መርሃግብር በኤን ቢ ሲ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በቅርቡ ለህዝብ እንደሚሰራጭ ታውቋል።
የዚህን ስምፖዚየም የሚድያ ማስተባበር ያከናወነው ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን (ዕዝራ እጅጉ) እንደሆነ ታውቋል።
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጀማል አህመድ ይፋ የተደረገው አዲሱ ፕሮጀክት፣ ለረጅም ጊዜ በህዝብ ዘንድ ሲያስነሳ የነበረውን ወቀሳ ለመቅረፍ ያለመ ነው። ኩባንያው የባህር ዳሩን ታሪካዊ ጣና ሆቴል ከገዛ በኋላ ግንባታ ሳይጀመርበት መቆየቱን ተከትሎ ሲቀርብበት የነበረውን ትችት በማስቀረት፣ ሆቴሉን ወደ አለም አቀፍ ደረጃ ለማሳደግ ዛሬ በይፋ ስራ መጀመሩን አብስሯል።
አቶ ጀማል በንግግራቸው እንዳብራሩት፣ይህ ግንባታ የአለቃቸውን (የሼክ መሀመድ ሁሴን አል አሙዲን) ራዕይ ለማሳካት እና የመንግስትን የቱሪዝም ልማት ምሰሶ ለመደገፍ ታቅዶ የተጀመረ ነው። ፕሮጀክቱ በአገር በቀል ኢንጂነሮች እና በማርዮት ዓለም አቀፍ ሆቴል ቴክኒካል ድጋፍ የሚገነባ ሲሆን፣ በ18 ወራት ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃ ቃል ተገብቷል።
ዋና ስራ አስፈፃሚው አያይዘውም፣ ከዚህ ቀደም አንድ ባለስልጣንን "ጀማል አንተ እርሻ)ላይ ጎበዝ ነህ፣ ሆቴል ግን አትችልበትም" ብለው ላነሱባቸው ወዳጃዊ ትችት፣ ጡረታ ከመውጣታቸው በፊት በሆቴል ዘርፍም ስኬታማ መሆናቸውን በተግባር እንደሚያሳዩ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ከሼክ መሀመድ በፊት ከሂልተን ውጭ አለም አቀፍ ሆቴል እንዳልነበራት ያስታወሱት አቶ ጀማል፣ ሸራተን አዲስ ሲገነባ "እብደት ነው" ይባል እንደነበር በማስታወስ አሁንም ሚድሮክ በቱሪዝሙ ዘርፍ ትልቅ አብዮት እያመጣ መሆኑን ጠቁመዋል።
ሚድሮክ ከዚህ ፕሮጀክት ባሻገር በሆቴል እና ቱሪዝም ዘርፍ ግዙፍ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ ይገኛል። አቶ ጀማል እንዳስታወቁት፣ ኩባንያቸው አስር የማርዮት ሆቴሎችን ለመገንባት ስምምነት የተፈራረመ ሲሆን፣ እነዚህንም ሆቴሎች በፍራንቻይዝ ለማስተዳደር "ዘ ፈርስት ግሩፕ" የተሰኘ ትልቅ ዓለም አቀፍ ኩባንያ ጋር ውል አስሯል።
በተጨማሪም የዌስቲን ሆቴል ግንባታ በዘንድሮው ወይም በሚቀጥለው የፈረንጆች አመት መባቻ ተጠናቆ ይመረቃል ተብሎ ይጠበቃል። ቀድመው የተጀመሩት የጅማ እና የሀዋሳ ፕሮጀክቶችም በፍጥነት እየተሰሩ መሆኑን የገለጹት ዋና ስራ አስፈፃሚው፣ የባህር ዳሩ አቫንቲ ሆቴልም ወደ "ፕሮቲያ ባይ ማርዮት" ለመቀየር በቅርቡ ስራ እንደሚጀመር ያላቸውን ተስፋ አጋርተዋል።
አቶ ጀማል በንግግራቸው እንዳብራሩት፣ይህ ግንባታ የአለቃቸውን (የሼክ መሀመድ ሁሴን አል አሙዲን) ራዕይ ለማሳካት እና የመንግስትን የቱሪዝም ልማት ምሰሶ ለመደገፍ ታቅዶ የተጀመረ ነው። ፕሮጀክቱ በአገር በቀል ኢንጂነሮች እና በማርዮት ዓለም አቀፍ ሆቴል ቴክኒካል ድጋፍ የሚገነባ ሲሆን፣ በ18 ወራት ውስጥ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቃ ቃል ተገብቷል።
ዋና ስራ አስፈፃሚው አያይዘውም፣ ከዚህ ቀደም አንድ ባለስልጣንን "ጀማል አንተ እርሻ)ላይ ጎበዝ ነህ፣ ሆቴል ግን አትችልበትም" ብለው ላነሱባቸው ወዳጃዊ ትችት፣ ጡረታ ከመውጣታቸው በፊት በሆቴል ዘርፍም ስኬታማ መሆናቸውን በተግባር እንደሚያሳዩ አረጋግጠዋል። ኢትዮጵያ ከሼክ መሀመድ በፊት ከሂልተን ውጭ አለም አቀፍ ሆቴል እንዳልነበራት ያስታወሱት አቶ ጀማል፣ ሸራተን አዲስ ሲገነባ "እብደት ነው" ይባል እንደነበር በማስታወስ አሁንም ሚድሮክ በቱሪዝሙ ዘርፍ ትልቅ አብዮት እያመጣ መሆኑን ጠቁመዋል።
ሚድሮክ ከዚህ ፕሮጀክት ባሻገር በሆቴል እና ቱሪዝም ዘርፍ ግዙፍ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ ይገኛል። አቶ ጀማል እንዳስታወቁት፣ ኩባንያቸው አስር የማርዮት ሆቴሎችን ለመገንባት ስምምነት የተፈራረመ ሲሆን፣ እነዚህንም ሆቴሎች በፍራንቻይዝ ለማስተዳደር "ዘ ፈርስት ግሩፕ" የተሰኘ ትልቅ ዓለም አቀፍ ኩባንያ ጋር ውል አስሯል።
በተጨማሪም የዌስቲን ሆቴል ግንባታ በዘንድሮው ወይም በሚቀጥለው የፈረንጆች አመት መባቻ ተጠናቆ ይመረቃል ተብሎ ይጠበቃል። ቀድመው የተጀመሩት የጅማ እና የሀዋሳ ፕሮጀክቶችም በፍጥነት እየተሰሩ መሆኑን የገለጹት ዋና ስራ አስፈፃሚው፣ የባህር ዳሩ አቫንቲ ሆቴልም ወደ "ፕሮቲያ ባይ ማርዮት" ለመቀየር በቅርቡ ስራ እንደሚጀመር ያላቸውን ተስፋ አጋርተዋል።
1 month ago
ገበታ ለሀገር ! ገበታ ለጣና!
ባህርዳር የግዙፉን የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት የምረቃ ስነስርአት እያስተናገደች ነው!
______________________________
ዛሬ ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በውቧ ባህር ዳር ከተማ የግዙፉ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት መመረቅ ተበስሯል።
በደቡባዊ የጣና ሐይቅ ዳርቻ፤ በባህር ዳር ከተማ የተገነባው የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ለጣና የቀረበ የጎርጎራን ብርሃን በሌላኛው ዳርቻ ያስቀጠለ ግዙፍ ኢንቨስትመንት ነው።
ይህ ውጥን ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ የጎርጎራን ታላቅ ስራ ሙሉ ለማድረግ በሌላኛው የጣና አቅጣጫ፥ በውቧ ባህር ዳር የሚተሳሰሩ ሁለት የአንድ ሐይቅ ዳርቻ ገናና ህልሞችን ለማሳካት በገበታ ለሃገር ያለሙት ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ ቀደምቷን የዐፄ ሱስኒዮስ መናገሻ ጎርጎራን ከዘመናት ጨለማ በኋላ ታላቅ ብርሃን እንድትጎናፀፍ ያደረጉበትን እጅግ ድንቅ አሻራ ተከትሎ ዳግም በዐፄ ሱስኒዮስ ልጅ በፋሲለደስ መናገሻ ጎንደር አዲስ ነገር አሳዩ።
በመከራ ውስጥ የኖረውን የጎንደር አብያተ መንግሥታት ግብረ ሕንፃ እንደ አዲስ ነፍስ የዘራበትን የቅርስ ጥገና እና ልማት ዕውን አደረጉ። ይህ የቅርስ ጥገናና ልማት የዓለም ቅርሱን ታሪክ ወደ ላቀ ስኬት ያሻገረ የዘላቂ ቱሪዝም ትልቅ አቅም ነው።
የቀጠናውን መፃኢ ዕድል ነገውን ያስናፍቃል ያስባለው ሌላው ፕሮጀክት በጎንደር ከተማ የሚገኘው የመገጭ የመጠጥ፣ የመስኖ እና ሁለንተናዊ ልማት አቅም የሆነው ግድብ ነው። ግድቡ የውሃ እጥረት ላለባት ጎንደር ከቱሪዝም ልማት አኳያ ለውሃ ቱሪዝምና መዝናኛ ኢንቨስትመንት አዲስ ዕድል ይዞ እየመጣ ነው።
የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት በገበታ ለሀገር እንደለማው ሁሉ ይህ ራዕይ እንዲዘልቅና እንዲስፋፋ ገበታ ለሀገር በግል ኢንቨስትመንትም እንዲቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት የመሪነት ሚና ሀሳባቸውን በመግዛት የቤአኢካ እና የእህት ኩባንያዎቹ መሥራች አቶ ካሳሁን ምስጋናው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርትን በገበታ ለሀገር ማዕቀፍ ውስጥ 4.5 ቢሊዮን ብር ወጭ አድርገው በሁለት አመት ከስድስት ወር ግዜ ውስጥ እውን አድርገዋል።
ከዚህ ሪዞርት እና ከሌሎች ገናና ውጥኖች ዕውን መሆን ጀርባ የተጣለበትን ኃላፊነት በብቃት በመወጣት ረገድ ከሀገር ልማት ጎን የቆመው የቤአኢካ ንግድና ኢንቨስትመንት ሚና የላቀ ነው።
በተለይም የድርጅቱ መሥራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሀገር ወዳዱ አቶ ካሳሁን ምስጋናው በጎርጎራ ኢኮ ቱሪዝም ግንባታ በኮንትራክተርነት በታሰበው ጊዜ፣ በታለመው ጥራት እና በሚያኮራ ኃላፊነትን የመወጣት ስኬት አጠናቀዋል።
በተመሳሳይ እንደ ሀገርም ባልተለመደ ሁኔታ በሀገር ልጅ ብቃት እና ኃላፊነትን የመወጣት ተግባር ምስጋና የቀረበለትን የጎንደር አብያተ መንግሥታት ግብረ ሕንፃ የቅርስ ጥገናና ልማት ስራ ሌላው ስለ ሀገር የተወጡት ኃላፊነት ነው።
በዚሁ 'በጎንደር እስከ ምፅአት' በሚል ሲፌዝበት የኖረውን የመገጭ ፕሮጀክት በጠቅላይ ሚኒስትሩ በተሰጠ ከባድ የቁጭት አደራ እና ኃላፊነት ተረክበው የግንባታ ሂደቱን በሚያስደንቅ ፍጥነት አሳክተው በመጠናቀቂያው ምዕራፍ ሊገኝ ችሏል።
አሁን ደግሞ በሀገር በቀሉ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ትልቅ ቦታ የተሰጠው የቱሪዝም ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ውጥንን ለፍሬ ያበቁት አቶ ካሳሁን ምስጋናው በሌሎች ኢንቨስትመንቶቻቸው ካሳኩት ልምድ በመነሳት መንግስት ትልቅ ትኩረት የሰጠውን የቱሪዝም ኢንዱስትሪ በግሉ ዘርፍ ለማልማት፣ ከመገንባት ልምድና አቅማቸው በተጨማሪ ሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕን አቋቁመዋል።
አቶ ካሳሁን እነኚህ ፕሮጀክቶች ስኬታማ ሆነው ሀገር እና ህዝብ የጣሉባቸውን ኃላፊነቶች እንዲወጡ በማስቻል ረገድ የፌዴራል ፣ የክልል አንዲሁም የከተማ አስተዳደሮች ትልቁን ሚና እንደተጫዎቱ አፅንዎት ሰጥተው ገልጸዋል።
በተለይም የክልሉ መንግስት የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይን የቱሪዝም አብዮት ራዕይ ተቀብሎ ድርጅታቸው እና እሳቸው የተጣለባቸውን አደራ በአግባቡ እንዲወጡ ላደረገው ከፍተኛ ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በቀጣይ የማስፋፊያ ስራዎቹ ተጨማሪ አያሌ እቅዶችን የያዘው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ከጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት ጋር በመቀናጀት በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ ስር ይተዳደራል።
ሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርትን እና ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርትን በመያዝ ስራ የጀመረ፤ በቀጣይ ለማስተዳደር በሚረከባቸውም እራሱ በሚገነባቸውም የሆስፒታሊቲ ተቋማት የላቀ፣ ዘመናዊና ተወዳዳሪ አገልግሎትን ለመስጠት 'ልባችን ኢትዮጵያ ደረጃችን ዓለም አቀፍ!' በሚል ፍልስፍና ኢንቨስትመንቱን የተቀላቀለ ሀገር በቀል ተቋም ነው።
በገበታ ለሃገር ማእቀፍ ውስጥ በግል ኢንቨትመንት የታነጸው የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ምርቃት ተበስሯል።
ባህርዳር የግዙፉን የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት የምረቃ ስነስርአት እያስተናገደች ነው!
______________________________
ዛሬ ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በውቧ ባህር ዳር ከተማ የግዙፉ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት መመረቅ ተበስሯል።
በደቡባዊ የጣና ሐይቅ ዳርቻ፤ በባህር ዳር ከተማ የተገነባው የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ለጣና የቀረበ የጎርጎራን ብርሃን በሌላኛው ዳርቻ ያስቀጠለ ግዙፍ ኢንቨስትመንት ነው።
ይህ ውጥን ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ የጎርጎራን ታላቅ ስራ ሙሉ ለማድረግ በሌላኛው የጣና አቅጣጫ፥ በውቧ ባህር ዳር የሚተሳሰሩ ሁለት የአንድ ሐይቅ ዳርቻ ገናና ህልሞችን ለማሳካት በገበታ ለሃገር ያለሙት ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ ቀደምቷን የዐፄ ሱስኒዮስ መናገሻ ጎርጎራን ከዘመናት ጨለማ በኋላ ታላቅ ብርሃን እንድትጎናፀፍ ያደረጉበትን እጅግ ድንቅ አሻራ ተከትሎ ዳግም በዐፄ ሱስኒዮስ ልጅ በፋሲለደስ መናገሻ ጎንደር አዲስ ነገር አሳዩ።
በመከራ ውስጥ የኖረውን የጎንደር አብያተ መንግሥታት ግብረ ሕንፃ እንደ አዲስ ነፍስ የዘራበትን የቅርስ ጥገና እና ልማት ዕውን አደረጉ። ይህ የቅርስ ጥገናና ልማት የዓለም ቅርሱን ታሪክ ወደ ላቀ ስኬት ያሻገረ የዘላቂ ቱሪዝም ትልቅ አቅም ነው።
የቀጠናውን መፃኢ ዕድል ነገውን ያስናፍቃል ያስባለው ሌላው ፕሮጀክት በጎንደር ከተማ የሚገኘው የመገጭ የመጠጥ፣ የመስኖ እና ሁለንተናዊ ልማት አቅም የሆነው ግድብ ነው። ግድቡ የውሃ እጥረት ላለባት ጎንደር ከቱሪዝም ልማት አኳያ ለውሃ ቱሪዝምና መዝናኛ ኢንቨስትመንት አዲስ ዕድል ይዞ እየመጣ ነው።
የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት በገበታ ለሀገር እንደለማው ሁሉ ይህ ራዕይ እንዲዘልቅና እንዲስፋፋ ገበታ ለሀገር በግል ኢንቨስትመንትም እንዲቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት የመሪነት ሚና ሀሳባቸውን በመግዛት የቤአኢካ እና የእህት ኩባንያዎቹ መሥራች አቶ ካሳሁን ምስጋናው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርትን በገበታ ለሀገር ማዕቀፍ ውስጥ 4.5 ቢሊዮን ብር ወጭ አድርገው በሁለት አመት ከስድስት ወር ግዜ ውስጥ እውን አድርገዋል።
ከዚህ ሪዞርት እና ከሌሎች ገናና ውጥኖች ዕውን መሆን ጀርባ የተጣለበትን ኃላፊነት በብቃት በመወጣት ረገድ ከሀገር ልማት ጎን የቆመው የቤአኢካ ንግድና ኢንቨስትመንት ሚና የላቀ ነው።
በተለይም የድርጅቱ መሥራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሀገር ወዳዱ አቶ ካሳሁን ምስጋናው በጎርጎራ ኢኮ ቱሪዝም ግንባታ በኮንትራክተርነት በታሰበው ጊዜ፣ በታለመው ጥራት እና በሚያኮራ ኃላፊነትን የመወጣት ስኬት አጠናቀዋል።
በተመሳሳይ እንደ ሀገርም ባልተለመደ ሁኔታ በሀገር ልጅ ብቃት እና ኃላፊነትን የመወጣት ተግባር ምስጋና የቀረበለትን የጎንደር አብያተ መንግሥታት ግብረ ሕንፃ የቅርስ ጥገናና ልማት ስራ ሌላው ስለ ሀገር የተወጡት ኃላፊነት ነው።
በዚሁ 'በጎንደር እስከ ምፅአት' በሚል ሲፌዝበት የኖረውን የመገጭ ፕሮጀክት በጠቅላይ ሚኒስትሩ በተሰጠ ከባድ የቁጭት አደራ እና ኃላፊነት ተረክበው የግንባታ ሂደቱን በሚያስደንቅ ፍጥነት አሳክተው በመጠናቀቂያው ምዕራፍ ሊገኝ ችሏል።
አሁን ደግሞ በሀገር በቀሉ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ትልቅ ቦታ የተሰጠው የቱሪዝም ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ውጥንን ለፍሬ ያበቁት አቶ ካሳሁን ምስጋናው በሌሎች ኢንቨስትመንቶቻቸው ካሳኩት ልምድ በመነሳት መንግስት ትልቅ ትኩረት የሰጠውን የቱሪዝም ኢንዱስትሪ በግሉ ዘርፍ ለማልማት፣ ከመገንባት ልምድና አቅማቸው በተጨማሪ ሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕን አቋቁመዋል።
አቶ ካሳሁን እነኚህ ፕሮጀክቶች ስኬታማ ሆነው ሀገር እና ህዝብ የጣሉባቸውን ኃላፊነቶች እንዲወጡ በማስቻል ረገድ የፌዴራል ፣ የክልል አንዲሁም የከተማ አስተዳደሮች ትልቁን ሚና እንደተጫዎቱ አፅንዎት ሰጥተው ገልጸዋል።
በተለይም የክልሉ መንግስት የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይን የቱሪዝም አብዮት ራዕይ ተቀብሎ ድርጅታቸው እና እሳቸው የተጣለባቸውን አደራ በአግባቡ እንዲወጡ ላደረገው ከፍተኛ ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በቀጣይ የማስፋፊያ ስራዎቹ ተጨማሪ አያሌ እቅዶችን የያዘው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ከጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት ጋር በመቀናጀት በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ ስር ይተዳደራል።
ሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርትን እና ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርትን በመያዝ ስራ የጀመረ፤ በቀጣይ ለማስተዳደር በሚረከባቸውም እራሱ በሚገነባቸውም የሆስፒታሊቲ ተቋማት የላቀ፣ ዘመናዊና ተወዳዳሪ አገልግሎትን ለመስጠት 'ልባችን ኢትዮጵያ ደረጃችን ዓለም አቀፍ!' በሚል ፍልስፍና ኢንቨስትመንቱን የተቀላቀለ ሀገር በቀል ተቋም ነው።
በገበታ ለሃገር ማእቀፍ ውስጥ በግል ኢንቨትመንት የታነጸው የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ምርቃት ተበስሯል።
Sponsored by
Surafel
1 month ago
በሸገር ከተማ በሶስት አመት የተከናወኑ የልማት ስራዎች ተጎበኙ!
በትላንትናው እለት ከ50 በላይ ማህበራዊ ሚዲያ ተፅእኖ ፈጣሪዎች እና ጋዜጠኞች በተገኙበት ነው ጉብኝቱ የተከናወነው!
ከንቲባው ይህን የተናገሩት ከማህበራዊ ሚዲያ ተፅእኖ ፈጣሪዎች እና ከጋዜጠኞች ጋር በተገናኙ በኃላ ነው።
በትላንትናው እለት ከ50 በላይ ማህበራዊ ሚዲያ ተፅእኖ ፈጣሪዎች እና ጋዜጠኞች በተገኙበት የሸገር ከተማ አስተዳደር ምስረታውን ተከትሎ ባለፉት ሦስት ዓመታት ያከናወናቸውን ግዙፍ የልማት ስኬቶች በይፋ አስተዋውቋል።
የጉብኝት መርሃ ግብሩን በንግግር የከፈቱት በኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት ማዕረግ የሸገር ከተማ ከንቲባ አቶ ተሾመ አዱኛ (PhD) “ከተማዋ በትምህርት፣ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ እና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ታይቶ የማይታወቅ እመርታ ታይቷል። ይኸውም 3ቱን አመት እንደ 30 አመት በመስራታችን ነው” ሲሉ ተደምጠዋል።
“የሚታረስ መሬት ከ60 ሺህ ሄክታር ወደ 81 ሺህ ሄክታር አድጓል። ለምርት ሂደት የሚውሉ 19 ሺህ ሼዶች ተገንብተዋል ብሏል።
ባለፉት ሦስት ዓመታት ውስጥ ብቻ ከ330 በላይ ትምህርት ቤቶች የተገነቡ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የተማሪዎች ቁጥር ከ420 ሺህ በላይ ደርሷል።
ከተማዋን የንግድና የቴክኖሎጂ ኮሪደር ለማድረግ በተነደፈው ዕቅድ 2 ሺህ የሚጠጉ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ወደ ሥራ ገብተዋል። ከእነዚህም መካከል ዓለም አቀፍ የመኪና መሸጫ ማዕከል አንዱ ነው።
የካዳስተር ሥርዓትን ተግባራዊ በማድረግ ለ170 ሺህ ነዋሪዎች የይዞታ ማረጋገጫ ሰነድ (ካርታ) ተሰጥቷል።
ሸገር ከተማ በ2022 እ.ኤ.አ (2015 ዓ.ም) የተመሰረተች ሲሆን፣ በ160,892 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈችና በ12 ክፍለ ከተማ የተዋቀረች ናት። በአሁኑ ወቅት ከ3.2 ሚሊዮን በላይ ህዝብ የሚኖርባት ሲሆን፣ ኮዬ ፈጬ "የሸገር ኮከብ ከተማ" ተብላ ተሰይማለች።
አሁን በአጠቃላይ እንቁላል በሲኖትራክ ወደተለያዩ ክልል ከተሞች እየተጫኑ ነው” ሲሉ በጥናት ላይ የተመረኮዘ ፅሁፍ አቅርበዋል።
ሸገር ከተማ በ2022 እ.ኤ.አ (2015 ዓ.ም) የተመሰረተች ሲሆን፣ በ160,892 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈችና በ12 ክፍለ ከተማ የተዋቀረች ናት። በአሁኑ ወቅት ከ3.2 ሚሊዮን በላይ ህዝብ የሚኖርባት ሲሆን፣ ኮዬ ፈጬ "የሸገር ኮከብ ከተማ" ተብላ ተሰይማለች።
እነዚህን ከተሞች በውስጧ የያዘችው ሸገር ከፍተኛ ሆስፒታሎችን፣ ዩኒቨርሲቲዎችን፣ የሆቴል ኢንቨስትመንቶችንና የግብርና ልማቶችን አስጎብኝታለች።
በዛሬው እለትም
ሸገር ከተማ በ2022 እ.ኤ.አ (2015 ዓ.ም) የተመሰረተች ሲሆን፣ በ160,892 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈችና በ12 ክፍለ ከተማ የተዋቀረች ናት። በአሁኑ ወቅት ከ3.2 ሚሊዮን በላይ ህዝብ የሚኖርባት ሲሆን፣ ኮዬ ፈጬ "የሸገር ኮከብ ከተማ" ተብላ ተሰይማለች።
ከንቲባው አክለውም የተመዘገቡት ውጤቶች በዘፈቀደ ሳይሆን በተቀናጀ ፕላን የተመሩ መሆናቸውን ጠቁመው፣ "በሦስት ዓመት ውስጥ እንደ 30 ዓመት ሠርተናል" ሲሉ የሥራውን ስፋት ገልጸዋል። የሚዲያ ባለሙያዎች እና የማህበራዊ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች በተለያዩ የልማት ቀጠናዎች የመስክ ምልከታ አድርጓል።
በተጨማሪም "ለመምረጥ እሮጣለሁ፣ ሰላሜን እጠብቃለሁ!" በሚል መሪ ቃል በዛሬው እለት በፉሪ ክፍለ ከተማ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎችና የሲቪክ ማህበራትን ያሳተፈ ታላቅ የመንገድ ላይ ሩጫ ተካሂዷል።
በዕለቱ የተገኙት የሸገር ከተማ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክት፣ ሸገር የቀጣይነትና የዘመናዊነት ተምሳሌት፣ የኢኮኖሚ አብዮት ማዕከል ናት። ባለፉት 3 ዓመታት የትምህርት ተቋማት ቁጥር ከ958 ወደ 1,315 አድጓል። 7ኛው አገራዊ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የሁላችንም ሚና ወሳኝ ነው።
በውድድሩ ለአሸናፊዎች የዋንጫና የገንዘብ ሽልማት የተበረከተ ሲሆን፣ የከተማዋ ከፍተኛ አመራሮችና የሲቪክ ማህበራት ተወካዮችም በጋራ በሩጫው ተሳታፊ ሆነዋል።
በትላንትናው እለት ከ50 በላይ ማህበራዊ ሚዲያ ተፅእኖ ፈጣሪዎች እና ጋዜጠኞች በተገኙበት ነው ጉብኝቱ የተከናወነው!
ከንቲባው ይህን የተናገሩት ከማህበራዊ ሚዲያ ተፅእኖ ፈጣሪዎች እና ከጋዜጠኞች ጋር በተገናኙ በኃላ ነው።
በትላንትናው እለት ከ50 በላይ ማህበራዊ ሚዲያ ተፅእኖ ፈጣሪዎች እና ጋዜጠኞች በተገኙበት የሸገር ከተማ አስተዳደር ምስረታውን ተከትሎ ባለፉት ሦስት ዓመታት ያከናወናቸውን ግዙፍ የልማት ስኬቶች በይፋ አስተዋውቋል።
የጉብኝት መርሃ ግብሩን በንግግር የከፈቱት በኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት ማዕረግ የሸገር ከተማ ከንቲባ አቶ ተሾመ አዱኛ (PhD) “ከተማዋ በትምህርት፣ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ እና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ታይቶ የማይታወቅ እመርታ ታይቷል። ይኸውም 3ቱን አመት እንደ 30 አመት በመስራታችን ነው” ሲሉ ተደምጠዋል።
“የሚታረስ መሬት ከ60 ሺህ ሄክታር ወደ 81 ሺህ ሄክታር አድጓል። ለምርት ሂደት የሚውሉ 19 ሺህ ሼዶች ተገንብተዋል ብሏል።
ባለፉት ሦስት ዓመታት ውስጥ ብቻ ከ330 በላይ ትምህርት ቤቶች የተገነቡ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የተማሪዎች ቁጥር ከ420 ሺህ በላይ ደርሷል።
ከተማዋን የንግድና የቴክኖሎጂ ኮሪደር ለማድረግ በተነደፈው ዕቅድ 2 ሺህ የሚጠጉ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ወደ ሥራ ገብተዋል። ከእነዚህም መካከል ዓለም አቀፍ የመኪና መሸጫ ማዕከል አንዱ ነው።
የካዳስተር ሥርዓትን ተግባራዊ በማድረግ ለ170 ሺህ ነዋሪዎች የይዞታ ማረጋገጫ ሰነድ (ካርታ) ተሰጥቷል።
ሸገር ከተማ በ2022 እ.ኤ.አ (2015 ዓ.ም) የተመሰረተች ሲሆን፣ በ160,892 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈችና በ12 ክፍለ ከተማ የተዋቀረች ናት። በአሁኑ ወቅት ከ3.2 ሚሊዮን በላይ ህዝብ የሚኖርባት ሲሆን፣ ኮዬ ፈጬ "የሸገር ኮከብ ከተማ" ተብላ ተሰይማለች።
አሁን በአጠቃላይ እንቁላል በሲኖትራክ ወደተለያዩ ክልል ከተሞች እየተጫኑ ነው” ሲሉ በጥናት ላይ የተመረኮዘ ፅሁፍ አቅርበዋል።
ሸገር ከተማ በ2022 እ.ኤ.አ (2015 ዓ.ም) የተመሰረተች ሲሆን፣ በ160,892 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈችና በ12 ክፍለ ከተማ የተዋቀረች ናት። በአሁኑ ወቅት ከ3.2 ሚሊዮን በላይ ህዝብ የሚኖርባት ሲሆን፣ ኮዬ ፈጬ "የሸገር ኮከብ ከተማ" ተብላ ተሰይማለች።
እነዚህን ከተሞች በውስጧ የያዘችው ሸገር ከፍተኛ ሆስፒታሎችን፣ ዩኒቨርሲቲዎችን፣ የሆቴል ኢንቨስትመንቶችንና የግብርና ልማቶችን አስጎብኝታለች።
በዛሬው እለትም
ሸገር ከተማ በ2022 እ.ኤ.አ (2015 ዓ.ም) የተመሰረተች ሲሆን፣ በ160,892 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈችና በ12 ክፍለ ከተማ የተዋቀረች ናት። በአሁኑ ወቅት ከ3.2 ሚሊዮን በላይ ህዝብ የሚኖርባት ሲሆን፣ ኮዬ ፈጬ "የሸገር ኮከብ ከተማ" ተብላ ተሰይማለች።
ከንቲባው አክለውም የተመዘገቡት ውጤቶች በዘፈቀደ ሳይሆን በተቀናጀ ፕላን የተመሩ መሆናቸውን ጠቁመው፣ "በሦስት ዓመት ውስጥ እንደ 30 ዓመት ሠርተናል" ሲሉ የሥራውን ስፋት ገልጸዋል። የሚዲያ ባለሙያዎች እና የማህበራዊ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች በተለያዩ የልማት ቀጠናዎች የመስክ ምልከታ አድርጓል።
በተጨማሪም "ለመምረጥ እሮጣለሁ፣ ሰላሜን እጠብቃለሁ!" በሚል መሪ ቃል በዛሬው እለት በፉሪ ክፍለ ከተማ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎችና የሲቪክ ማህበራትን ያሳተፈ ታላቅ የመንገድ ላይ ሩጫ ተካሂዷል።
በዕለቱ የተገኙት የሸገር ከተማ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር) ባስተላለፉት መልዕክት፣ ሸገር የቀጣይነትና የዘመናዊነት ተምሳሌት፣ የኢኮኖሚ አብዮት ማዕከል ናት። ባለፉት 3 ዓመታት የትምህርት ተቋማት ቁጥር ከ958 ወደ 1,315 አድጓል። 7ኛው አገራዊ ምርጫ ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የሁላችንም ሚና ወሳኝ ነው።
በውድድሩ ለአሸናፊዎች የዋንጫና የገንዘብ ሽልማት የተበረከተ ሲሆን፣ የከተማዋ ከፍተኛ አመራሮችና የሲቪክ ማህበራት ተወካዮችም በጋራ በሩጫው ተሳታፊ ሆነዋል።
1 month ago
የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ አዲስ ኢንዱስትሪያዊ የሥራ ባህል እየገነባ ነው - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ ከቴክኒካዊ ብቃት ባሻገር አዲስ ኢንዱስትሪያዊ ሰብዕና እና የሥራ ባህል እየገነባ ነው አለ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት።
አገልግሎቱ የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ አስመልክቶ ባወጣው መረጃ፤ በኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማሩ ዜጎች ዓለም አቀፍ የጥራት ቁጥጥር ስታንዳርዶችን፣ ጥብቅ የጊዜ አጠቃቀምንና ስልታዊ የአመራር ክህሎትን በመላበስ ላይ ናቸው ብሏል።
ከታችኛው የሥራ እርከን ተነስተው በዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ውስጥ እስከ ከፍተኛ የውሳኔ ሰጪነት ደረጃ የደረሱ ወጣቶች፣ ኢትዮጵያ ለዓለም ገበያ የምታቀርበው "ምርጥ ምርት" የሰው ሀብቷ መሆኑን እያስመሰከሩ ነው ሲልም ገልጿል።
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ‘በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ምርትን ከማሳደግና የውጭ ምንዛሬን ከመታደግ ባሻገር ዕውቀትንና ክህሎትን ለዓለም የምናበረክትበት አዲስ የኢንዱስትሪ ምዕራፍ ተጀምሯል!’ በሚል ያወጣው መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው “ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ፤ 830 ፋብሪካዎችን ዳግም ወደ ስራ በማስገባት፣ 4.85 ቢሊየን ዶላር ገቢ ምርትን በመተካት እና 433 ሚሊየን ዶላር ከኤክስፖርት በማስገኘት አስደናቂ የኢንዱስትሪ ሽግግር ውጤት አስመዝግቧል። ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ መንግሥት የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ሀገራዊ ንቅናቄ ሲጀምር፣ ግቡ ምርትን ማሳደግና የውጭ ምንዛሬን መታደግ ብቻ አልነበረም።
ከእነዚህ ኢኮኖሚያዊ ስሌቶች ባሻገር፣ ትልቁና ስትራቴጂካዊው ስኬታችን የተመዘገበው ኢትዮጵያን የዕውቀትና የክህሎት ምንጭ በሚያደርገው የሰው ሀብት ልማት ላይ ነው። ዛሬ ላይ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የፋብሪካዎች ስብስብ መሆኑ ቀርቶ፣ የነገዋን ኢትዮጵያ የሚገነቡ ብቁ ባለሙያዎችና መሪዎች የሚፈሩበት ታላቅ የተግባር ትምህርት ቤት መሆን ችሏል። ይህ ሽግግር ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተወዳዳሪነት ከጥሬ ዕቃ ላኪነት ወደ ቴክኖሎጂ ላኪነትና ክህሎት አቅራቢነት ከፍ የሚያደርግ ለነገዋ ኢትዮጵያዊ መሠረት የሚጥል የታሪካችን እጥፋት ነው።
በታላላቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች፣ በኢንዱስትሪ ፓርኮችና በግዙፍ ፋብሪካዎች ውስጥ የታየው ተጨባጭ ለውጥ የመንግሥትን የፖሊሲ ጥንካሬ በተግባር የሚያረጋግጥ ነው። ከዚህ ቀደም በከፍተኛ ክፍያ በሚመጡ የውጭ ሀገር ዜጎች ብቻ ይተዳደሩ የነበሩ ውስብስብ የቴክኖሎጂ ሲስተሞች፣ ዘመናዊ የምርት መስመሮችና የሶፍትዌር መሠረተ-ልማቶች ዛሬ ላይ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ወጣት መሐንዲሶችና ቴክኒሻኖች እየተመሩ ይገኛሉ። ይህ ስኬታማ የዕውቀት ሽግግር፣ መንግሥት ጥራት ያለው ፖሊሲ የመቅረጽ ብቻ ሳይሆን ፖሊሲን በተጨባጭ ወደ ተግባር የመለወጥና የማስፈጸም አቅም እንዳለው ትልቅ ማሳያ ነው።
በዘረፉ የተሠማሩ ኢትዮጵያውያን ወጣቶችም የተፈጠረላቸውን ምቹ ዐውድ ተጠቀመው ቴክኖሎጂን የመቀበል ብቻ ሳይሆን፣ የመግራትና የማላመድ ብቃታቸውን በተግባር በማሳየት፣ ሀገራችን ለዘመናት የነበረባትን የቴክኖሎጂ ጥገኝነት በፈጠራ አቅማቸው እያስቀሩና አዳዲስ የሥራ ባሕልና የታሪክ ምዕራፍ እየጻፉ ይገኛሉ።
የ "ኢትዮጵያ ታምርት"ንቅናቄ ከቴክኒካዊ ብቃት ባሻገር፣ አዲስ ኢንዱስትሪያዊ ሰብዕና እና የሥራ ባህል እየገነባ ነው ። በዘርፉ የተሰማሩ ዜጎች ዓለም አቀፍ የጥራት ቁጥጥር ስታንዳርዶችን፣ ጥብቅ የጊዜ አጠቃቀምንና ስልታዊ የአመራር ክህሎትን በመላበስ ላይ ናቸው። ከታችኛው የሥራ እርከን ተነስተው በዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ውስጥ እስከ ከፍተኛ የውሳኔ ሰጪነት ደረጃ የደረሱ ወጣቶቻች፣ ኢትዮጵያ ለዓለም ገበያ የምታቀርበው "ምርጥ ምርት" የሰው ሀብቷ መሆኑን እያስመሰከሩ ነው።
መንግሥት የኢንዱስትሪ ሽግግሩን ትክክለኛ ፍሬ የሚለካው በወጪ ንግድ ስሌቶች ብቻ ሳይሆን በቴክኖሎጂ የደረጀና በዕውቀት የበለጸገ አምራች ዜጋ መፈጠሩ ነው። በመሆኑም ይህን የክህሎት አብዮት ይበልጥ በማፋጠንና ዘርፉን የቴክኖሎጂ ምንጭ በማድረግ፣ የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች በቁርጠኝነት ይቀጥላሉ።
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ ከቴክኒካዊ ብቃት ባሻገር አዲስ ኢንዱስትሪያዊ ሰብዕና እና የሥራ ባህል እየገነባ ነው አለ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት።
አገልግሎቱ የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄ አስመልክቶ ባወጣው መረጃ፤ በኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማሩ ዜጎች ዓለም አቀፍ የጥራት ቁጥጥር ስታንዳርዶችን፣ ጥብቅ የጊዜ አጠቃቀምንና ስልታዊ የአመራር ክህሎትን በመላበስ ላይ ናቸው ብሏል።
ከታችኛው የሥራ እርከን ተነስተው በዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ውስጥ እስከ ከፍተኛ የውሳኔ ሰጪነት ደረጃ የደረሱ ወጣቶች፣ ኢትዮጵያ ለዓለም ገበያ የምታቀርበው "ምርጥ ምርት" የሰው ሀብቷ መሆኑን እያስመሰከሩ ነው ሲልም ገልጿል።
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ‘በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ምርትን ከማሳደግና የውጭ ምንዛሬን ከመታደግ ባሻገር ዕውቀትንና ክህሎትን ለዓለም የምናበረክትበት አዲስ የኢንዱስትሪ ምዕራፍ ተጀምሯል!’ በሚል ያወጣው መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመረው “ኢትዮጵያ ታምርት” ንቅናቄ፤ 830 ፋብሪካዎችን ዳግም ወደ ስራ በማስገባት፣ 4.85 ቢሊየን ዶላር ገቢ ምርትን በመተካት እና 433 ሚሊየን ዶላር ከኤክስፖርት በማስገኘት አስደናቂ የኢንዱስትሪ ሽግግር ውጤት አስመዝግቧል። ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ መንግሥት የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ሀገራዊ ንቅናቄ ሲጀምር፣ ግቡ ምርትን ማሳደግና የውጭ ምንዛሬን መታደግ ብቻ አልነበረም።
ከእነዚህ ኢኮኖሚያዊ ስሌቶች ባሻገር፣ ትልቁና ስትራቴጂካዊው ስኬታችን የተመዘገበው ኢትዮጵያን የዕውቀትና የክህሎት ምንጭ በሚያደርገው የሰው ሀብት ልማት ላይ ነው። ዛሬ ላይ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የፋብሪካዎች ስብስብ መሆኑ ቀርቶ፣ የነገዋን ኢትዮጵያ የሚገነቡ ብቁ ባለሙያዎችና መሪዎች የሚፈሩበት ታላቅ የተግባር ትምህርት ቤት መሆን ችሏል። ይህ ሽግግር ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተወዳዳሪነት ከጥሬ ዕቃ ላኪነት ወደ ቴክኖሎጂ ላኪነትና ክህሎት አቅራቢነት ከፍ የሚያደርግ ለነገዋ ኢትዮጵያዊ መሠረት የሚጥል የታሪካችን እጥፋት ነው።
በታላላቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች፣ በኢንዱስትሪ ፓርኮችና በግዙፍ ፋብሪካዎች ውስጥ የታየው ተጨባጭ ለውጥ የመንግሥትን የፖሊሲ ጥንካሬ በተግባር የሚያረጋግጥ ነው። ከዚህ ቀደም በከፍተኛ ክፍያ በሚመጡ የውጭ ሀገር ዜጎች ብቻ ይተዳደሩ የነበሩ ውስብስብ የቴክኖሎጂ ሲስተሞች፣ ዘመናዊ የምርት መስመሮችና የሶፍትዌር መሠረተ-ልማቶች ዛሬ ላይ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ወጣት መሐንዲሶችና ቴክኒሻኖች እየተመሩ ይገኛሉ። ይህ ስኬታማ የዕውቀት ሽግግር፣ መንግሥት ጥራት ያለው ፖሊሲ የመቅረጽ ብቻ ሳይሆን ፖሊሲን በተጨባጭ ወደ ተግባር የመለወጥና የማስፈጸም አቅም እንዳለው ትልቅ ማሳያ ነው።
በዘረፉ የተሠማሩ ኢትዮጵያውያን ወጣቶችም የተፈጠረላቸውን ምቹ ዐውድ ተጠቀመው ቴክኖሎጂን የመቀበል ብቻ ሳይሆን፣ የመግራትና የማላመድ ብቃታቸውን በተግባር በማሳየት፣ ሀገራችን ለዘመናት የነበረባትን የቴክኖሎጂ ጥገኝነት በፈጠራ አቅማቸው እያስቀሩና አዳዲስ የሥራ ባሕልና የታሪክ ምዕራፍ እየጻፉ ይገኛሉ።
የ "ኢትዮጵያ ታምርት"ንቅናቄ ከቴክኒካዊ ብቃት ባሻገር፣ አዲስ ኢንዱስትሪያዊ ሰብዕና እና የሥራ ባህል እየገነባ ነው ። በዘርፉ የተሰማሩ ዜጎች ዓለም አቀፍ የጥራት ቁጥጥር ስታንዳርዶችን፣ ጥብቅ የጊዜ አጠቃቀምንና ስልታዊ የአመራር ክህሎትን በመላበስ ላይ ናቸው። ከታችኛው የሥራ እርከን ተነስተው በዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ውስጥ እስከ ከፍተኛ የውሳኔ ሰጪነት ደረጃ የደረሱ ወጣቶቻች፣ ኢትዮጵያ ለዓለም ገበያ የምታቀርበው "ምርጥ ምርት" የሰው ሀብቷ መሆኑን እያስመሰከሩ ነው።
መንግሥት የኢንዱስትሪ ሽግግሩን ትክክለኛ ፍሬ የሚለካው በወጪ ንግድ ስሌቶች ብቻ ሳይሆን በቴክኖሎጂ የደረጀና በዕውቀት የበለጸገ አምራች ዜጋ መፈጠሩ ነው። በመሆኑም ይህን የክህሎት አብዮት ይበልጥ በማፋጠንና ዘርፉን የቴክኖሎጂ ምንጭ በማድረግ፣ የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች በቁርጠኝነት ይቀጥላሉ።
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
1 month ago
በኦርዌል "1984" እና የኢትዮጵያ ፖለቲካ ምንና ምን ናቸው?
(ቃልኪዳን ኃይሉ)
ጆርጅ ኦርዌል ማነው?
#ethiopia | ጆርጅ ኦርዌል (ትክክለኛ ስሙ ኤሪክ አርተር ብሌየር) እ.ኤ.አ. በ1903 ሕንድ ውስጥ ተወለደ። ጆርጅ ኦርዌክ በሕይወቱ ለጽሑፎቹ ትልቅ ግብዓት የሆኑ ሦስት ዋና ዋና ምዕራፎች ነበሩት፦ እነሱም የፖሊስነት ተሞክሮ፣ በአውሮፓ የነበረው የድህነት ኑሮ እና የስፔን የእርስ በርስ ጦርነት፡ በፋሺዝም ላይ ለመዋጋት ወደ ስፔን ሄዶ በጦርነቱ መሳተፉ አስተሳሰቡን እና መጻሕፍቱን በዚያ ልምድና ተሞክሮው ላይ እንዲያጠነጥን አድርጎታል።
ኦርዌል በተለይ በሁለት ዝነኛ መጻሕፍቱ ይበልጥ ይታወቃል፦Animal Farm (የእንስሳት እርሻ) እና 1984 ነው።
Animal Farm የራሺያን አብዮት መነሻ በማድረግ የተጻፈ ተምሳሌታዊ (Allegory) ድርሰት ነው። "ሁሉም እንስሳት እኩል ናቸው፤ ነገር ግን አንዳንዶቹ ከሌሎቹ ይበልጥ እኩል ናቸው" የሚለው ዝነኛ ጥቅሱ ሥልጣን እንዴት አብዮተኞችን ወደ ጨቋኝነታቸው እንደሚቀይር ያሳያል።
ሌላው 1984 ይህ ደግሞ የግለሰብ ነፃነት ሙሉ በሙሉ በጠፋበት ዓለም ውስጥ የሚኖርን ሰው ሕይወት የሚተነብይ የ"ዳይስቶፒያ" (Dystopia) ልብ-ወለድ ነው።
የመከራከሪያ ነጥቦቹ (Core Ideas)
ኦርዌል በሥራዎቹ ውስጥ ሦስት መሠረታዊ ነገሮችን በጽኑ ይቃወማል፦
1.የእውነት መጥፋት (The Erosion of Truth)፦ ኦርዌል በጣም የሚፈራው "እውነት" የሚባል ነገር ጠፍቶ፣ ገዢዎች የሚሉትን ብቻ ሕዝቡ እንዲያምን የሚደረግበትን ሥርዓት ነው። "በሁለንተናዊ የማታለል ዘመን እውነትን መናገር አብዮታዊ ተግባር ነው" የሚል እምነት ነበረው።
2.የቋንቋ መበላሸት (Corruption of Language)፦ ፖለቲከኞች መጥፎ ተግባራቸውን ለመሸፈን ቋንቋን እንደሚጠቀሙ ይከራከራል። ለምሳሌ "ሰላም ማስከበር" የሚለው ቃል ጦርነትን ለመሸፈን፣ "ማስተካከል" የሚለው ቃል ደግሞ ግድያን ለመሸፈን ጥቅም ላይ ሊውል እንደሚችል ያሳያል።
3. የግለሰብ ነፃነት (Individual Autonomy)፦ ሥልጣን የሰውን ልጅ አካል ብቻ ሳይሆን አእምሮውንና ትውስታውን ጭምር እንዲቆጣጠር ኦርዌል አይፈልግም።
"ኦርዌሊያን" (Orwellian) የሚለው ቃል
በአሁኑ ጊዜ ይህ ቃል በዓለም አቀፍ ደረጃ እንደ ቅጽል ጥቅም ላይ ይውላል። አንድን ሁኔታ "ኦርዌሊያን" ስንለው፣ ያ ሁኔታ መንግሥት የሰዎችን የግል ሕይወት የሚቆጣጠርበት፣ መረጃን የሚያዛባበትና ዜጎችን በውሸት ፕሮፓጋንዳ የሚያደነዝዝበት መሆኑን ለመግለጽ ነው።
1984 Vs ኢትይጵያ
"1984" እስካሁን ድረስ ጸንቶ የቆየው እንደ ተራ የአምባገነንነት ማስጠንቀቂያ ሳይሆን፣ ሥልጣን ከተራ የተግባር ቁጥጥር ባለፈ የአረዳድ (Perception) የበላይነትን ለመያዝ በሚሻበት ጊዜ እንዴት እንደሚሠራ የሚያሳይ ጥቁር ትንታኔ በመሆኑ ነው።
በጥልቅ ሲታይ፣ ሥርዓቱ በእውቀት ቁጥጥር (Epistemic Control)፣ በቋንቋ ምህንድስና እና በሥነ-ልቦናዊ ተገዥነት ላይ የተገነባ መሆኑን እንረዳለን።
1. ሥልጣን እንደ እውነት የማምረቻ መሣሪያ
የኦርዌል ዋነኛ መከራከሪያ ፍጹም ፖለቲካዊ ሥልጣን የሚገኘው እውነታን የመተርጎም አቅም ላይ ነው የሚል ነው። "ፓርቲው" ነባራዊ እውነታዎች ለፖለቲካዊ ፍላጎት ተገዥ መሆን አለባቸው ብሎ መሟገቱ እንዲሁ ለንግግር ያህል የመጣ ሳይሆን መዋቅራዊ መርህ ነው። የሚጋጩ እውነታዎችን በግዴታ አምኖ መቀበል (Doublethink) ዜጎችን የማላመጃ ዘዴ ሲሆን፣ በእውነትና በሥልጣን መካከል ያለውን ድንበር ያጠፋዋል።
በኢትዮጵያ ሁኔታ፡ አሁን በኢትዮጵያ የፖለቲካ ውድድር በዋነኝነት የሚካሄደው በትርክት ግንባታ (Narrative Construction) ነው።
የመንግሥት ተቋማት፣ የተቃዋሚ ንቅናቄዎች እና የሚዲያ ተዋናዮች ስለ ግጭት፣ ስለ ሪፎርም እና ስለ ቅቡልነት የተራራቁ ትርክቶችን ያቀርባሉ። እዚህ ላይ ችግሩ የፕሮፓጋንዳ መኖር ብቻ ሳይሆን፣ "ትክክለኛውን የታሪክ ስሪት" የማጽደቅ ፍልሚያ ነው። የጋራ የሆነ የእውነታ መሠረት በሌለበት ሁኔታ፣ ፖለቲካዊ ፍርድ በቀላሉ የሚለዋወጥና ለማጭበርበር የተጋለጠ ይሆናል።
2. የቋንቋ ቅነሳና ፖለቲካዊ ቅርጻ (Linguistic Compression and Framing)
"ኒውስፒክ" (Newspeak) ቋንቋ የሐሳብ መሠረት (Infrastructure) መሆኑን በሚገባ የተረዳ ስልት ነው። የቃላት ግምጃ ቤትን በዘዴ በመቀነስ፣ ፓርቲው ተቃውሞን ለማሰብ የሚያስፈልጉ የግንዛቤ መሣሪያዎችን ያጠፋል።
በኢትዮጵያ ሁኔታ፡ ምንም እንኳ አተገባበሩ እንደ መጽሐፉ የተማከለ ባይሆንም፣ ውጤቱ ግን ተመሳሳይ ነው። ከማንነት፣ ከፌዴራሊዝም፣ ከሉዓላዊነትና ከደኅንነት ጋር የተያያዙ ቃላት በጽንፍ በተራራቁ መንገዶች ጥቅም ላይ ይውላሉ።
ትንታኔዎች በታፔላዎች (Labels) ይተካሉ። ውስብስብ የሆኑ ነባራዊ ሁኔታዎች በስሜት ወደተሞሉ ምድቦች ይጠቅለላሉ። ይህ ሐሳብን ባያጠፋውም እንኳ፣ አስቀድሞ ወደ ተወሰኑ የፖለቲካ አሰላለፎች እንዲፈስ ያደርገዋል። ውጤቱም ውይይቶች ገና ሳይጀመሩ በቋንቋ አጠቃቀም ብቻ ውጤታቸው እንዲወሰን ያደርጋል።
3. የታሪክ ትርክትና የማስታወስ ፖለቲካ
ፓርቲው ያለፈውን ታሪክ በመቆጣጠር፣ ከሥርዓቱ ቁጥጥር ውጭ የሆነ ነፃ የማጣቀሻ ነጥብ እንዳይኖር ያደርጋል። ታሪክ ለወቅታዊው ሥልጣን ቅቡልነት ሲባል በየጊዜው የሚስተካከል ተለዋዋጭ ነገር ይሆናል።
በኢትዮጵያ ሁኔታ፡ በኢትዮጵያም እርስ በርሳቸው የሚጋጩ የታሪክ ትርክቶች ለወቅታዊ የፖለቲካ ጥያቄዎች ድጋፍ እንዲሆኑ ተደርገው ይቀርባሉ።
ስለ ሀገር ምስረታ፣ ስለ ማንነትና ስለ ታሪካዊ በደሎች የሚደረጉ ክርክሮች የትምህርት ዘርፍ ብቻ ሳይሆኑ የፖለቲካ መሣሪያዎች ናቸው። በታሪክ ትርጓሜ ላይ ስምምነት አለመኖሩ፣ ለጋራ ሀገራዊ ትርክት መፈጠር እንቅፋት ከመሆኑም በላይ ተጠያቂነትንና እርቅን የማምጣት ሂደትን ያወሳስበዋል።
4. ቁጥጥር፣ ራስን መገደብና የሕዝብ ውይይት
"ቴሌስክሪን" (Telescreen) የማያቋርጥ ክትትልን ያመለክታል፤ ሆኖም ዋናው ተግባሩ ግለሰቡ "እየታየሁ ነው" የሚለውን ስሜት ውስጣዊ አድርጎ ራሱን እንዲቆጣጠር ማድረግ ነው።
በኢትዮጵያ ሁኔታ፡ ክትትል በተቋማዊ፣ በዲጂታልና በማኅበራዊ መዋቅሮች አማካኝነት ይከናወናል። ምንም እንኳ ቁጥጥሩ ፍጹም ባይሆንም፣ ዜጎች የሚናገሩትን ነገር እንዲመጥኑ (Calibrate) እና ራሳዊ ቅድም ምርመራ (Self censorship) ያደርጋል።
የማኅበረሰብ አንቂዎች፣ ጋዜጠኞች፣ ተንታኞችና ተራ ዜጎች በሕግ፣ በፖለቲካዊ ተጋላጭነትና በማኅበራዊ ጫናዎች የሚወሰኑ ድንበሮችን እያጤኑ ይንቀሳቀሳሉ
(Self censorship)። ውጤቱም ፍጹም ዝምታ ሳይሆን፣ ያልተባለው ነገር ከተባለው እኩል ትርጉም የሚሰጥበት "ስልታዊ የሐሳብ ልውውጥ" (Strategic Communication) መፈጠሩ ነው።
5. ማስገደድና የውዴታ ግዴታን ማምረት (Coercion and Consent)
በመጽሐፉ ውስጥ የሚገኘው የኦብራይን (O'Brien) ገጸ-ባህሪ ዓላማው ተቃውሞን ማጥፋት ብቻ ሳይሆን፣ የሰውን እምነትና አስተሳሰብ ጭምር እንደ አዲስ መቅረጽ ነው።
በኢትዮጵያ ሁኔታ፡ የፖለቲካው ምኅዳር የተለያየና ብዙ ተዋናዮች የሚሳተፉበት በመሆኑ፣ ጫናው እንደ ኦርዌል ዓለም ወጥና ፍጹም አይደለም። ይሁን እንጂ የሕዝብን ድጋፍ በትርክት የማምረት ፍላጎት ማዕከላዊ ነው። የሚዲያ ሥነ-ምህዳሩ (መደበኛም ሆነ ማኅበራዊ) የተወሰኑ ትርክቶችን በማግነንና ሌሎችን በማዳከም ረገድ ትልቅ ሚና ይጫወታሉ።
ትግሉ አንድ ወጥ የሆነ አስተሳሰብን ከመጫን ይልቅ፣ በተሰባበረ የመረጃ አውድ ውስጥ የትርክት የበላይነትን (Narrative Dominance) የመያዝ ትግል ነው።
ማጠቃለያ
የ"1984" ፋይዳ ያለው በፅንሰ-ሐሳብ ግልጽነቱ ላይ ነው። ሥልጣን ግንዛቤን፣ ቋንቋንና ትውስታን በመቆጣጠር ራሱን እንዴት እንደሚያደላድል ነጥሎ ያሳየናል።
ኢትዮጵያ የኦርዌልን ዝግ የአምባገነንነት፣ የፖለቲካው ሜዳ ተለዋዋጭና የተለያየ ተፅዕኖ ያላቸው ኃይሎች የሚጋጩበት ነው።
ኦርዌል የለያቸው መሠረታዊ መዋቅሮች መልክ ቀይረው ይታያሉ። መረጃን መቆጣጠር፣ ቋንቋን ለፖለቲካ ዓላማ መጠቀምና ታሪክን ፖለቲካዊ ማድረግ እስካሁንም የሥልጣን ትግሉ ማዕከል ናቸው።
(ቃልኪዳን ኃይሉ)
ጆርጅ ኦርዌል ማነው?
#ethiopia | ጆርጅ ኦርዌል (ትክክለኛ ስሙ ኤሪክ አርተር ብሌየር) እ.ኤ.አ. በ1903 ሕንድ ውስጥ ተወለደ። ጆርጅ ኦርዌክ በሕይወቱ ለጽሑፎቹ ትልቅ ግብዓት የሆኑ ሦስት ዋና ዋና ምዕራፎች ነበሩት፦ እነሱም የፖሊስነት ተሞክሮ፣ በአውሮፓ የነበረው የድህነት ኑሮ እና የስፔን የእርስ በርስ ጦርነት፡ በፋሺዝም ላይ ለመዋጋት ወደ ስፔን ሄዶ በጦርነቱ መሳተፉ አስተሳሰቡን እና መጻሕፍቱን በዚያ ልምድና ተሞክሮው ላይ እንዲያጠነጥን አድርጎታል።
ኦርዌል በተለይ በሁለት ዝነኛ መጻሕፍቱ ይበልጥ ይታወቃል፦Animal Farm (የእንስሳት እርሻ) እና 1984 ነው።
Animal Farm የራሺያን አብዮት መነሻ በማድረግ የተጻፈ ተምሳሌታዊ (Allegory) ድርሰት ነው። "ሁሉም እንስሳት እኩል ናቸው፤ ነገር ግን አንዳንዶቹ ከሌሎቹ ይበልጥ እኩል ናቸው" የሚለው ዝነኛ ጥቅሱ ሥልጣን እንዴት አብዮተኞችን ወደ ጨቋኝነታቸው እንደሚቀይር ያሳያል።
ሌላው 1984 ይህ ደግሞ የግለሰብ ነፃነት ሙሉ በሙሉ በጠፋበት ዓለም ውስጥ የሚኖርን ሰው ሕይወት የሚተነብይ የ"ዳይስቶፒያ" (Dystopia) ልብ-ወለድ ነው።
የመከራከሪያ ነጥቦቹ (Core Ideas)
ኦርዌል በሥራዎቹ ውስጥ ሦስት መሠረታዊ ነገሮችን በጽኑ ይቃወማል፦
1.የእውነት መጥፋት (The Erosion of Truth)፦ ኦርዌል በጣም የሚፈራው "እውነት" የሚባል ነገር ጠፍቶ፣ ገዢዎች የሚሉትን ብቻ ሕዝቡ እንዲያምን የሚደረግበትን ሥርዓት ነው። "በሁለንተናዊ የማታለል ዘመን እውነትን መናገር አብዮታዊ ተግባር ነው" የሚል እምነት ነበረው።
2.የቋንቋ መበላሸት (Corruption of Language)፦ ፖለቲከኞች መጥፎ ተግባራቸውን ለመሸፈን ቋንቋን እንደሚጠቀሙ ይከራከራል። ለምሳሌ "ሰላም ማስከበር" የሚለው ቃል ጦርነትን ለመሸፈን፣ "ማስተካከል" የሚለው ቃል ደግሞ ግድያን ለመሸፈን ጥቅም ላይ ሊውል እንደሚችል ያሳያል።
3. የግለሰብ ነፃነት (Individual Autonomy)፦ ሥልጣን የሰውን ልጅ አካል ብቻ ሳይሆን አእምሮውንና ትውስታውን ጭምር እንዲቆጣጠር ኦርዌል አይፈልግም።
"ኦርዌሊያን" (Orwellian) የሚለው ቃል
በአሁኑ ጊዜ ይህ ቃል በዓለም አቀፍ ደረጃ እንደ ቅጽል ጥቅም ላይ ይውላል። አንድን ሁኔታ "ኦርዌሊያን" ስንለው፣ ያ ሁኔታ መንግሥት የሰዎችን የግል ሕይወት የሚቆጣጠርበት፣ መረጃን የሚያዛባበትና ዜጎችን በውሸት ፕሮፓጋንዳ የሚያደነዝዝበት መሆኑን ለመግለጽ ነው።
1984 Vs ኢትይጵያ
"1984" እስካሁን ድረስ ጸንቶ የቆየው እንደ ተራ የአምባገነንነት ማስጠንቀቂያ ሳይሆን፣ ሥልጣን ከተራ የተግባር ቁጥጥር ባለፈ የአረዳድ (Perception) የበላይነትን ለመያዝ በሚሻበት ጊዜ እንዴት እንደሚሠራ የሚያሳይ ጥቁር ትንታኔ በመሆኑ ነው።
በጥልቅ ሲታይ፣ ሥርዓቱ በእውቀት ቁጥጥር (Epistemic Control)፣ በቋንቋ ምህንድስና እና በሥነ-ልቦናዊ ተገዥነት ላይ የተገነባ መሆኑን እንረዳለን።
1. ሥልጣን እንደ እውነት የማምረቻ መሣሪያ
የኦርዌል ዋነኛ መከራከሪያ ፍጹም ፖለቲካዊ ሥልጣን የሚገኘው እውነታን የመተርጎም አቅም ላይ ነው የሚል ነው። "ፓርቲው" ነባራዊ እውነታዎች ለፖለቲካዊ ፍላጎት ተገዥ መሆን አለባቸው ብሎ መሟገቱ እንዲሁ ለንግግር ያህል የመጣ ሳይሆን መዋቅራዊ መርህ ነው። የሚጋጩ እውነታዎችን በግዴታ አምኖ መቀበል (Doublethink) ዜጎችን የማላመጃ ዘዴ ሲሆን፣ በእውነትና በሥልጣን መካከል ያለውን ድንበር ያጠፋዋል።
በኢትዮጵያ ሁኔታ፡ አሁን በኢትዮጵያ የፖለቲካ ውድድር በዋነኝነት የሚካሄደው በትርክት ግንባታ (Narrative Construction) ነው።
የመንግሥት ተቋማት፣ የተቃዋሚ ንቅናቄዎች እና የሚዲያ ተዋናዮች ስለ ግጭት፣ ስለ ሪፎርም እና ስለ ቅቡልነት የተራራቁ ትርክቶችን ያቀርባሉ። እዚህ ላይ ችግሩ የፕሮፓጋንዳ መኖር ብቻ ሳይሆን፣ "ትክክለኛውን የታሪክ ስሪት" የማጽደቅ ፍልሚያ ነው። የጋራ የሆነ የእውነታ መሠረት በሌለበት ሁኔታ፣ ፖለቲካዊ ፍርድ በቀላሉ የሚለዋወጥና ለማጭበርበር የተጋለጠ ይሆናል።
2. የቋንቋ ቅነሳና ፖለቲካዊ ቅርጻ (Linguistic Compression and Framing)
"ኒውስፒክ" (Newspeak) ቋንቋ የሐሳብ መሠረት (Infrastructure) መሆኑን በሚገባ የተረዳ ስልት ነው። የቃላት ግምጃ ቤትን በዘዴ በመቀነስ፣ ፓርቲው ተቃውሞን ለማሰብ የሚያስፈልጉ የግንዛቤ መሣሪያዎችን ያጠፋል።
በኢትዮጵያ ሁኔታ፡ ምንም እንኳ አተገባበሩ እንደ መጽሐፉ የተማከለ ባይሆንም፣ ውጤቱ ግን ተመሳሳይ ነው። ከማንነት፣ ከፌዴራሊዝም፣ ከሉዓላዊነትና ከደኅንነት ጋር የተያያዙ ቃላት በጽንፍ በተራራቁ መንገዶች ጥቅም ላይ ይውላሉ።
ትንታኔዎች በታፔላዎች (Labels) ይተካሉ። ውስብስብ የሆኑ ነባራዊ ሁኔታዎች በስሜት ወደተሞሉ ምድቦች ይጠቅለላሉ። ይህ ሐሳብን ባያጠፋውም እንኳ፣ አስቀድሞ ወደ ተወሰኑ የፖለቲካ አሰላለፎች እንዲፈስ ያደርገዋል። ውጤቱም ውይይቶች ገና ሳይጀመሩ በቋንቋ አጠቃቀም ብቻ ውጤታቸው እንዲወሰን ያደርጋል።
3. የታሪክ ትርክትና የማስታወስ ፖለቲካ
ፓርቲው ያለፈውን ታሪክ በመቆጣጠር፣ ከሥርዓቱ ቁጥጥር ውጭ የሆነ ነፃ የማጣቀሻ ነጥብ እንዳይኖር ያደርጋል። ታሪክ ለወቅታዊው ሥልጣን ቅቡልነት ሲባል በየጊዜው የሚስተካከል ተለዋዋጭ ነገር ይሆናል።
በኢትዮጵያ ሁኔታ፡ በኢትዮጵያም እርስ በርሳቸው የሚጋጩ የታሪክ ትርክቶች ለወቅታዊ የፖለቲካ ጥያቄዎች ድጋፍ እንዲሆኑ ተደርገው ይቀርባሉ።
ስለ ሀገር ምስረታ፣ ስለ ማንነትና ስለ ታሪካዊ በደሎች የሚደረጉ ክርክሮች የትምህርት ዘርፍ ብቻ ሳይሆኑ የፖለቲካ መሣሪያዎች ናቸው። በታሪክ ትርጓሜ ላይ ስምምነት አለመኖሩ፣ ለጋራ ሀገራዊ ትርክት መፈጠር እንቅፋት ከመሆኑም በላይ ተጠያቂነትንና እርቅን የማምጣት ሂደትን ያወሳስበዋል።
4. ቁጥጥር፣ ራስን መገደብና የሕዝብ ውይይት
"ቴሌስክሪን" (Telescreen) የማያቋርጥ ክትትልን ያመለክታል፤ ሆኖም ዋናው ተግባሩ ግለሰቡ "እየታየሁ ነው" የሚለውን ስሜት ውስጣዊ አድርጎ ራሱን እንዲቆጣጠር ማድረግ ነው።
በኢትዮጵያ ሁኔታ፡ ክትትል በተቋማዊ፣ በዲጂታልና በማኅበራዊ መዋቅሮች አማካኝነት ይከናወናል። ምንም እንኳ ቁጥጥሩ ፍጹም ባይሆንም፣ ዜጎች የሚናገሩትን ነገር እንዲመጥኑ (Calibrate) እና ራሳዊ ቅድም ምርመራ (Self censorship) ያደርጋል።
የማኅበረሰብ አንቂዎች፣ ጋዜጠኞች፣ ተንታኞችና ተራ ዜጎች በሕግ፣ በፖለቲካዊ ተጋላጭነትና በማኅበራዊ ጫናዎች የሚወሰኑ ድንበሮችን እያጤኑ ይንቀሳቀሳሉ
(Self censorship)። ውጤቱም ፍጹም ዝምታ ሳይሆን፣ ያልተባለው ነገር ከተባለው እኩል ትርጉም የሚሰጥበት "ስልታዊ የሐሳብ ልውውጥ" (Strategic Communication) መፈጠሩ ነው።
5. ማስገደድና የውዴታ ግዴታን ማምረት (Coercion and Consent)
በመጽሐፉ ውስጥ የሚገኘው የኦብራይን (O'Brien) ገጸ-ባህሪ ዓላማው ተቃውሞን ማጥፋት ብቻ ሳይሆን፣ የሰውን እምነትና አስተሳሰብ ጭምር እንደ አዲስ መቅረጽ ነው።
በኢትዮጵያ ሁኔታ፡ የፖለቲካው ምኅዳር የተለያየና ብዙ ተዋናዮች የሚሳተፉበት በመሆኑ፣ ጫናው እንደ ኦርዌል ዓለም ወጥና ፍጹም አይደለም። ይሁን እንጂ የሕዝብን ድጋፍ በትርክት የማምረት ፍላጎት ማዕከላዊ ነው። የሚዲያ ሥነ-ምህዳሩ (መደበኛም ሆነ ማኅበራዊ) የተወሰኑ ትርክቶችን በማግነንና ሌሎችን በማዳከም ረገድ ትልቅ ሚና ይጫወታሉ።
ትግሉ አንድ ወጥ የሆነ አስተሳሰብን ከመጫን ይልቅ፣ በተሰባበረ የመረጃ አውድ ውስጥ የትርክት የበላይነትን (Narrative Dominance) የመያዝ ትግል ነው።
ማጠቃለያ
የ"1984" ፋይዳ ያለው በፅንሰ-ሐሳብ ግልጽነቱ ላይ ነው። ሥልጣን ግንዛቤን፣ ቋንቋንና ትውስታን በመቆጣጠር ራሱን እንዴት እንደሚያደላድል ነጥሎ ያሳየናል።
ኢትዮጵያ የኦርዌልን ዝግ የአምባገነንነት፣ የፖለቲካው ሜዳ ተለዋዋጭና የተለያየ ተፅዕኖ ያላቸው ኃይሎች የሚጋጩበት ነው።
ኦርዌል የለያቸው መሠረታዊ መዋቅሮች መልክ ቀይረው ይታያሉ። መረጃን መቆጣጠር፣ ቋንቋን ለፖለቲካ ዓላማ መጠቀምና ታሪክን ፖለቲካዊ ማድረግ እስካሁንም የሥልጣን ትግሉ ማዕከል ናቸው።
1 month ago
እስራኤል እና ሊባኖስ የተኩስ አቁም ስምምነቱን ለሦስት ሳምንት አራዘሙ
እስራኤል እና ሊባኖስ የተኩስ አቁም ስምምነቱን በሦስት ሳምንታት ለማራዘም ተስማምተዋል ሲሉ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሳውቀዋል።ስምምነቱ የመጣው የእስራኤል እና የሊባኖስ ባለሥልጣናት ዋይት ሀውስ ውስጥ ያልተለመደ ስብሰባ ካደረጉ በኋላ ነው።
በጎርጎሪዮሱ የካቲት 28 ቀን፣ እስራኤል በኢራን ላይ የጋራ ጥቃት ከጀመረችበት ጊዜ ጀምሮ እስራኤል በሊባኖስ፣ በተለይም በደቡብ እና በዋና ከተማዋ ቤሩት ላይ የአየር ድብደባ ስትፈጽም ቆይታለች።እስራኤል ጥቃቱ በሊባኖስ ውስጥ የሒዝቦላህ መቀመጫ ቦታዎችን እና ምሽጎችን ዒላማ ያደረገ መሆኑን ገልፃለች።
ሒዝቦላህ በዩናይትድ ስቴትስ፤ ጀርመን እና በርካታ የሱኒ ዐረብ ሃገራት አሸባሪ ተብሎ የተፈረጀ፤ በኢራን የሚደገፍ የሊባኖስ የሺዓ ፖለቲካ ፓርቲ እና ወታደራዊ ክንፍ ነው ። በጎርጎሪዮሱ 1982 በሊባኖስ የእርስ በርስ ጦርነት (1975-1990) እና በእስራኤል የደቡብ ሊባኖስ ወረራ ወቅት ብቅ ያለ ቡድን ነው። ሒዝቦላህ የፖለቲካ እና የትጥቅ ቡድን ሲሆን፤በ1979 በኢራን የእስልምና አብዮት መሰረት በነበረው የሺዓ እስላማዊ ርዕዮተ ዓለም ደጋፊ ነው። ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮም በኢራን የእስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ድጋፍ፣ ስልጠና እና መሣሪያ ያገኛል።
ቡድኑም ለትልቋ ለጋሽ ሀገር ለኢራን ወኪል ሆና ይሰራል። የአሜሪካ መንግስት በጎርጎሪያኑ 2023 መጨረሻ ባወጣው መረጃ ኢራን ለሒዝቦላህ በየዓመቱ ወደ 700 ሚሊዮን
ዶላር (661 ሚሊዮን ዩሮ) ትሰጣለች ተብሎ ይገመታል።
DW Amharic
እስራኤል እና ሊባኖስ የተኩስ አቁም ስምምነቱን በሦስት ሳምንታት ለማራዘም ተስማምተዋል ሲሉ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሳውቀዋል።ስምምነቱ የመጣው የእስራኤል እና የሊባኖስ ባለሥልጣናት ዋይት ሀውስ ውስጥ ያልተለመደ ስብሰባ ካደረጉ በኋላ ነው።
በጎርጎሪዮሱ የካቲት 28 ቀን፣ እስራኤል በኢራን ላይ የጋራ ጥቃት ከጀመረችበት ጊዜ ጀምሮ እስራኤል በሊባኖስ፣ በተለይም በደቡብ እና በዋና ከተማዋ ቤሩት ላይ የአየር ድብደባ ስትፈጽም ቆይታለች።እስራኤል ጥቃቱ በሊባኖስ ውስጥ የሒዝቦላህ መቀመጫ ቦታዎችን እና ምሽጎችን ዒላማ ያደረገ መሆኑን ገልፃለች።
ሒዝቦላህ በዩናይትድ ስቴትስ፤ ጀርመን እና በርካታ የሱኒ ዐረብ ሃገራት አሸባሪ ተብሎ የተፈረጀ፤ በኢራን የሚደገፍ የሊባኖስ የሺዓ ፖለቲካ ፓርቲ እና ወታደራዊ ክንፍ ነው ። በጎርጎሪዮሱ 1982 በሊባኖስ የእርስ በርስ ጦርነት (1975-1990) እና በእስራኤል የደቡብ ሊባኖስ ወረራ ወቅት ብቅ ያለ ቡድን ነው። ሒዝቦላህ የፖለቲካ እና የትጥቅ ቡድን ሲሆን፤በ1979 በኢራን የእስልምና አብዮት መሰረት በነበረው የሺዓ እስላማዊ ርዕዮተ ዓለም ደጋፊ ነው። ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮም በኢራን የእስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ድጋፍ፣ ስልጠና እና መሣሪያ ያገኛል።
ቡድኑም ለትልቋ ለጋሽ ሀገር ለኢራን ወኪል ሆና ይሰራል። የአሜሪካ መንግስት በጎርጎሪያኑ 2023 መጨረሻ ባወጣው መረጃ ኢራን ለሒዝቦላህ በየዓመቱ ወደ 700 ሚሊዮን
ዶላር (661 ሚሊዮን ዩሮ) ትሰጣለች ተብሎ ይገመታል።
DW Amharic
2 months ago
የኤሌክትሪክ መኪና አብዮት፦ ቴስላ እጅግ ርካሽ እና አዲስ የሆነ "SUV" መኪና ሊያመርት ነው!
የዓለማችን ግዙፉ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ አምራች ቴስላ አሁን ካሉት ሞዴሎች በዋጋ እጅግ የሚረክስ እና አነስተኛ መጠን ያለው አዲስ የ"SUV" መኪና ለማምረት ዝግጅት መጀመሩን የሮይተርስ የዜና ምንጮች ገለጹ። ይህ "ሬድውድ" በሚል የኮድ ስም የሚጠራው አዲስ ፕሮጀክት አሁን በገበያ ላይ ካሉት ሞዴል 3 ወይም ሞዴል ዋይ የተቀየረ ሳይሆን ሙሉ በሙሉ አዲስ ዲዛይን የሚኖረው መሆኑ ታውቋል።
የመኪናው ዋጋ ከሌሎቹ የቴስላ ሞዴሎች በከፍተኛ ሁኔታ ቅናሽ የሚደረግበት ሲሆን ይህም ኩባንያው ሰፊውን የህብረተሰብ ክፍል ተደራሽ ለማድረግ የያዘው ስትራቴጂ አካል ነው። ተሽከርካሪው ከሞዴል ዋይ በርዝመቱ አጭርና ክብደቱም ቀለል ተደርጎ የሚሰራ ሲሆን ቴስላ ከሳምንታት በፊት ከመለዋወጫ አቅራቢዎች ጋር ሰፊ ውይይት መጀመሩም ተጠቁሟል።
ይህ የምርት ሂደት በዋናነት በቻይናው የሻንጋይ ፋብሪካ እንደሚጀምርና ወደ አሜሪካና አውሮፓ እንደሚስፋፋ ይጠበቃል። የቴስላ ይህ እርምጃ በአሁኑ ወቅት በአነስተኛ ዋጋ የኤሌክትሪክ መኪኖችን በብዛት እያመረቱ ካሉ የቻይና ኩባንያዎች ጋር ያለውን ፉክክር ለማጠናከር የሚረዳው ሲሆን መኪናው ለገበያ ሲበቃ በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሀገራት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ተደራሽነት በእጅጉ ሊጨምር እንደሚችል ይገመታል።
seledadotio
seledadotio
የዓለማችን ግዙፉ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ አምራች ቴስላ አሁን ካሉት ሞዴሎች በዋጋ እጅግ የሚረክስ እና አነስተኛ መጠን ያለው አዲስ የ"SUV" መኪና ለማምረት ዝግጅት መጀመሩን የሮይተርስ የዜና ምንጮች ገለጹ። ይህ "ሬድውድ" በሚል የኮድ ስም የሚጠራው አዲስ ፕሮጀክት አሁን በገበያ ላይ ካሉት ሞዴል 3 ወይም ሞዴል ዋይ የተቀየረ ሳይሆን ሙሉ በሙሉ አዲስ ዲዛይን የሚኖረው መሆኑ ታውቋል።
የመኪናው ዋጋ ከሌሎቹ የቴስላ ሞዴሎች በከፍተኛ ሁኔታ ቅናሽ የሚደረግበት ሲሆን ይህም ኩባንያው ሰፊውን የህብረተሰብ ክፍል ተደራሽ ለማድረግ የያዘው ስትራቴጂ አካል ነው። ተሽከርካሪው ከሞዴል ዋይ በርዝመቱ አጭርና ክብደቱም ቀለል ተደርጎ የሚሰራ ሲሆን ቴስላ ከሳምንታት በፊት ከመለዋወጫ አቅራቢዎች ጋር ሰፊ ውይይት መጀመሩም ተጠቁሟል።
ይህ የምርት ሂደት በዋናነት በቻይናው የሻንጋይ ፋብሪካ እንደሚጀምርና ወደ አሜሪካና አውሮፓ እንደሚስፋፋ ይጠበቃል። የቴስላ ይህ እርምጃ በአሁኑ ወቅት በአነስተኛ ዋጋ የኤሌክትሪክ መኪኖችን በብዛት እያመረቱ ካሉ የቻይና ኩባንያዎች ጋር ያለውን ፉክክር ለማጠናከር የሚረዳው ሲሆን መኪናው ለገበያ ሲበቃ በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሀገራት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ተደራሽነት በእጅጉ ሊጨምር እንደሚችል ይገመታል።
seledadotio
seledadotio
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ሆርሙዝ ዳግም ተዘጋ!
የኢራን መገናኛ ብዙኃን እስራኤል የእግረኛ ጦሯ ወደ ሊባኖስ ከገባ ወዲህ ግዙፍ ያለችወን ድብደባ መፈጸሟን ተከትሎ በሆርሙዝ ወሽመጥ ነዳጅ ጫኝ መርከቦች ማለፍ ማቆማቸውን ዘገቡ።
ኢራን እና አሜሪካ በደረሱት የተኩስ አቁም ላይ በባሕር ወሽመጡ በኩል ነዳጅ ጫኝ መርከቦች እንዲያልፉ ማድረግ ቁልፍ የስምምነቱ አካል ነው።
ነገር ግን ከኢራን እስላማዊ አብዮት ዘብ ጋር ግንኙነት ያለው ፋርስ ዜና ወኪል ዛሬ ማለዳ ከቴህራን ፈቃድ አግኝተው ሁለት ነዳጅ የጫኑ መርከቦች ማለፍ ችለው የነበረ ቢሆንም ከዚያ በኋላ ግን መርከቦች እንዳያልፉ ተደርገዋል።
seledadotio
seledadotio
የኢራን መገናኛ ብዙኃን እስራኤል የእግረኛ ጦሯ ወደ ሊባኖስ ከገባ ወዲህ ግዙፍ ያለችወን ድብደባ መፈጸሟን ተከትሎ በሆርሙዝ ወሽመጥ ነዳጅ ጫኝ መርከቦች ማለፍ ማቆማቸውን ዘገቡ።
ኢራን እና አሜሪካ በደረሱት የተኩስ አቁም ላይ በባሕር ወሽመጡ በኩል ነዳጅ ጫኝ መርከቦች እንዲያልፉ ማድረግ ቁልፍ የስምምነቱ አካል ነው።
ነገር ግን ከኢራን እስላማዊ አብዮት ዘብ ጋር ግንኙነት ያለው ፋርስ ዜና ወኪል ዛሬ ማለዳ ከቴህራን ፈቃድ አግኝተው ሁለት ነዳጅ የጫኑ መርከቦች ማለፍ ችለው የነበረ ቢሆንም ከዚያ በኋላ ግን መርከቦች እንዳያልፉ ተደርገዋል።
seledadotio
seledadotio
2 months ago
ዶ/ር ቴድሮስ በጎጃም በጤና ባለሙያዎች ላይ የተፈጸመውን ግድያ አወገዙ፤ ገለልተኛ ምርመራ እንዲደረግም ጠየቁ
#fastmereja I የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም፣ በአማራ ክልል ሰሜን ሜጫ ወረዳ በሦስት የጤና ባለሙያዎች ላይ የተፈጸመውን ግድያ በጽኑ ማውገዛቸውን ገለጹ። ዋና ዳይሬክተሩ ድርጊቱን አስመልክቶ ባወጡት መግለጫ፣ በጉዳዩ ላይ ገለልተኛ አካል ምርመራ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
ዶ/ር ቴድሮስ እንዳመለከቱት፣ የጤና ባለሙያዎች በማንኛውም የግጭት ወቅት ጥበቃ ሊደረግላቸው የሚገባና ለሰዎች ሕይወት መታደግ የሚሠሩ ወገኖች ናቸው። "የጤና ባለሙያዎች በማንኛውም ጊዜ ጥበቃ ሊደረግላቸውና ለሚያስፈልጋቸው ሰው ሁሉ ሕይወት አድን ሥራዎቻቸውን ሊያከናውኑ ይገባል" ሲሉ አሳስበዋል።
ሰለባዎቹ በአብዮት ፋና የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ጣቢያና በግል ተቋም ውስጥ ይሠሩ የነበሩ ባለሙያዎች መሆናቸው ይታወቃል። ዋና ዳይሬክተሩ የዓለም ጤና ድርጅት በጉዳዩ ላይ ያለውን ጥብቅ አቋምና የገለልተኛ ምርመራ አስፈላጊነት በአጽንኦት ገልጸዋል።
#fastmereja I የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም፣ በአማራ ክልል ሰሜን ሜጫ ወረዳ በሦስት የጤና ባለሙያዎች ላይ የተፈጸመውን ግድያ በጽኑ ማውገዛቸውን ገለጹ። ዋና ዳይሬክተሩ ድርጊቱን አስመልክቶ ባወጡት መግለጫ፣ በጉዳዩ ላይ ገለልተኛ አካል ምርመራ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።
ዶ/ር ቴድሮስ እንዳመለከቱት፣ የጤና ባለሙያዎች በማንኛውም የግጭት ወቅት ጥበቃ ሊደረግላቸው የሚገባና ለሰዎች ሕይወት መታደግ የሚሠሩ ወገኖች ናቸው። "የጤና ባለሙያዎች በማንኛውም ጊዜ ጥበቃ ሊደረግላቸውና ለሚያስፈልጋቸው ሰው ሁሉ ሕይወት አድን ሥራዎቻቸውን ሊያከናውኑ ይገባል" ሲሉ አሳስበዋል።
ሰለባዎቹ በአብዮት ፋና የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ጣቢያና በግል ተቋም ውስጥ ይሠሩ የነበሩ ባለሙያዎች መሆናቸው ይታወቃል። ዋና ዳይሬክተሩ የዓለም ጤና ድርጅት በጉዳዩ ላይ ያለውን ጥብቅ አቋምና የገለልተኛ ምርመራ አስፈላጊነት በአጽንኦት ገልጸዋል።
2 months ago
#የቀብር ስነስርአት በደቡብ አፍሪካ በ16ጥይት በአሰቃቂ የተገደለው ወንዴ ዜብራ (ወንድም አገኝ አየለ😭😭😭😭😭😭
#ለሚዲያ ዲያ ተቋማት በሙሉ
#የባልደረባችንና የሙያ አጋራችን የጋዜጠኛ ሲሳይ መንግስቴ አጎት(የአክስት ልጅ) የሆነዉና ወንድማችን አብሮ አደጋችን ታታሪዉ ዲያስፖራ #ወንድሜነህ አየለ በባለፈው ሳምንት መጋቢት 17/2018 ዓ.ም. በደቡብ አፍሪካ ጁሀንስበርግ ባልታወቁ ገዳዮች በ16 ጥይት ህይወቱ በአሰቃቂ ሁኔታ አልፏል
ታታሪዉ እና የጥረትተምሳሌቱ ኢትዮጵያዊ ወጣት አቶ ወንድሜነህ አየለ የቀብር ስነስርዓት ነገ ረቡዕ በአዲስአበባ ላፍቶ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
ስለሆነም ነገ ረቡዕ ከቀኑ 9:00 ሰዓት በደብረ ትጉኃን ቅዱስ ሚካኤል ላፍቶ ስርዓተ ቀብሩ ስለሚፈፀም የሚዲያ ተቋማቶች በመገኘትና በመዘገብ ፍትህ ርትህ እንድናገኝ ድምፅ እንድትሆኑን እንጠይቃለን። ቤተሰብቹ😭😭😭😭😭😭😭😭😭
🎯መቼ
ረቡዕ መጋቢት 23/2018 ዓ.ም.ከቀኑ 9:00 ሰዓት
🎯የት
በላፍቶ ትጉኃን ቅዱስ ሚካኤል(ላፍቶ ሚካኤል በቤተክርስቲያን
*መኖሪያ ቤት ሳሪስ ቀይ አፈር ከአብዮት ፋና ት/ቤት ወረድ ብሎ
ወደላፍቶ መሸጋገሪያ ድልድይ አጠገብ
#ለሚዲያ ዲያ ተቋማት በሙሉ
#የባልደረባችንና የሙያ አጋራችን የጋዜጠኛ ሲሳይ መንግስቴ አጎት(የአክስት ልጅ) የሆነዉና ወንድማችን አብሮ አደጋችን ታታሪዉ ዲያስፖራ #ወንድሜነህ አየለ በባለፈው ሳምንት መጋቢት 17/2018 ዓ.ም. በደቡብ አፍሪካ ጁሀንስበርግ ባልታወቁ ገዳዮች በ16 ጥይት ህይወቱ በአሰቃቂ ሁኔታ አልፏል
ታታሪዉ እና የጥረትተምሳሌቱ ኢትዮጵያዊ ወጣት አቶ ወንድሜነህ አየለ የቀብር ስነስርዓት ነገ ረቡዕ በአዲስአበባ ላፍቶ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
ስለሆነም ነገ ረቡዕ ከቀኑ 9:00 ሰዓት በደብረ ትጉኃን ቅዱስ ሚካኤል ላፍቶ ስርዓተ ቀብሩ ስለሚፈፀም የሚዲያ ተቋማቶች በመገኘትና በመዘገብ ፍትህ ርትህ እንድናገኝ ድምፅ እንድትሆኑን እንጠይቃለን። ቤተሰብቹ😭😭😭😭😭😭😭😭😭
🎯መቼ
ረቡዕ መጋቢት 23/2018 ዓ.ም.ከቀኑ 9:00 ሰዓት
🎯የት
በላፍቶ ትጉኃን ቅዱስ ሚካኤል(ላፍቶ ሚካኤል በቤተክርስቲያን
*መኖሪያ ቤት ሳሪስ ቀይ አፈር ከአብዮት ፋና ት/ቤት ወረድ ብሎ
ወደላፍቶ መሸጋገሪያ ድልድይ አጠገብ
2 months ago
አዲስ አበባን የረገትጥኩ ሰሞን
(ዘላለም ጸጋዬ)
#ethiopia | ምንም እንኩዋን የተወለድኩት ከአንዲት ትንሽዬ የገጠር ከተማ ቢሆንም የልጅነት አይኔን ስገልጥ ግን የማስታውሰው የማርያምን ቤተክርስትያን፣ የመቅድስዋን የእጣን ሽታ፣የንፋስ ሽውታ የሚያስፉዋጨውን የጉዋሮዋን አርዘሊባኖስ፣የደጀ ሰላምዋን መአዛ ፣ካጠገቡም ያለውን ጭው ያለ ገደል እንዲሁም "መልእክተ ዮሀንስ ሀዋርያ ወልደ ዘብድዮስ" እያሉ መርጌታ አየለን የከበቡ የቆሎ ተማሪዎች ድምጽ እና የመሳሰለው ነው።በጥቅሉ የልጅነት አይኔን የገለጥኩት ስልጣኔ ካልጎበኘው እልም ካለ ገጠር ውስጥ ነው ...እናማ አኩፋዳዬን ጣጥዬ አዲስ አበባ የገባሁት የሶስተኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ ነበር።ነፍሱን ይማረውና አባቴ ፈለገ ዮርዲያኖስ ትምህርት ቤት ወስዶ ከተተኝ።አባቴ ቀድሞ ከተማ ገብቶ አስኩዋላት ተምሮ እቀድሞዋ ቺኮዝሎቫኪያ ድረስም ሂዶ ተምሮ ነበር የመጣው።ተያም በሁዋላ እስከ ደርግ ምክርቤት አባልነት ደርሶ ነበር።
ትምህርት የተጀመረ ሰሞን የእርሻ መመህራችን ስለ ስንዴ አበቃቀል ሲያስተምሩ ቆይተው።"ጥያቄያለው አለ?" ሲሉ ከመቅጽበት እጄን እንደ ኢራን ሚሳኤል ዘረጋሁት።እኔ በገጠር አያለሁ የማውቀው ትልቅ ስራ መምህረነት ነው።ከዛ ባለፈ ሁሉም አርሶ ነው የሚበላ።እናም ከተማ ከገባሁበት ቀን ጀምሮ ስትከነክነኝ የከረመችውን ጥያቄ እንዲህ በማለት አቀረብኩ "መምህር የስንዴ አበቃቀልን አላጣሁትም የኔ ጥያቄ ግን... እንዲያው ለመሆኑ ይሄ ሁሉ ከተሜ የት አርሶ ነው የሚበላ" ብዬ ስጠይቅ...የክፍሉ ተማሪ ሁሉ በሳቅ ፈረሰ።ያልሳቀ አንድ ሰው ቢኖር መምህሩ ብቻ ነበሩ።እንዴ ምንድነው አዳሜን ሚያስቀው ብዬ ተገረምኩ።አባቴ በሰው ላይ መሳቅ እና ማላገጥ አይገባም እንዲይ ካደረግክ ነገ ሌሎች በአንተ ላይ ያላግጡብሀል ይለኝ ነበር።በገጠርም ቢሆን ምን አልባት ነጠላችንን አፋችን ላይ ጣል አርገን በትንሹ ብናንጉዋጥጥ ነውይ በሰው ላይ ካካካክ ብለን አንስቅም።
የእርሻ ክፍለ ግዜው እንዳለቀ።መምህሩ ሲወጡ የክፍሉ ተማሪ ሁሉ እየተከተለ "ዘላለም ገበሬው" ማለት ጀመረ።ምንም አልተደናገጥኩም።ድሮም ደንቆሮ ወሬ አያጣም ብዬ ኮስተር አልኩ።የገጠር ልጅ ልበሙሉ አይደል።እህኔ እኮ የአንዱን ተማሪ የአይን መጋረጃ በዚህ አፈር ሲግፍ በከረመ እጄ ብከድንለት እኮ ሌላው አርፎ ይቀመጥ ነበር ብዬ አሰብኩ። ነገር ግን ከክላስ ስወጣ ወይም ስኔ 30 ጠብቀው ጨርቆስ ጉሊት መሃል ተሰብስበው ዱቄት እንዳያደርጉኝ ደግሞ ፈራሁ።በዛ ላይ ሰፈሩ ብዙ ግዜ በችግር ብዛት በህይወት አረቄ ሰክረው የሚደባደቡ አያጣውም ነበር።
የሆነው ሆኖ እንዲህ አልኩዋቸው...አዎ ገበሬ ነኝ።የገበሬ ምርቱ በትሳስ ነው።ታህሳስ ላይ እንገናኝ አልኩዋቸው።ቅኔ መሆኑዋ ነበር።የተሳዳቢው ተማሪ ቡድን መሪ ደግሞ አንዲት ድፍኑዋን ጨረቃ የመሰለች ዘቢብ የምትባል ቆንጅዬ ልጅ ነበረች።ቆንጆ ሰው አመሉም እንደመልኩ ሸጋ፣ልቡም እንደ እጣን ንጹህ ይመስለኝ ነበር።ገና ያኔ ነው አዬ ውበት ከንቱ ደምግባትም ብላሽ ያልኩት::ዘቢብ ግን ዛሬ የት ነሽ...እነዛ እንደ ቤተመቅደስ ጧፍ የሚያበሩ አይኖችሽ ሰላም ናቸው ወይ??? አቤት ውበታቸው አይን ያስፈነጥዝ ነበር•••
የሆነው ሆኖ በመጨረሻም ታህሳስ የመጀመርያ ሴሚስተር ውጤት ሲመጣ ከክፍሉ አንደኛ ወጣሁ።ያሁሉ ተማሪ እንደ ንጉስ ያየኝ ጀመር።እኔም ቆፍጠን ቄምጨጭ አልኩ "አለም ምንግዜም የቆራጦች ናት" ይል ነበር በዓሉ ግርማ።እናማ በክፍላችን ውስጥ እንግሊዘኛን እንደኔ የሚያነባት አልነበረም።አፌን ያዝ ከሚያደርገኝ የገጠር አማርኛ በስተቀር ምንም የሚወጣልኝ አልነበረም።ከባድ ጥያቄ በተጠየቀ ቁጠር መምህራን አይናቸውን ወደኔ ነበር የሚያቆለቁሉት።
ውሸት የሚባል አላውቅም ነበር።አሁንም ይተናነቀኛል።"እናትክን" የሚል ስድብ የሰማሁት እዛው ከትምህርት ቤታችን ፊትለፊት ከጉሊቱ መካከል ነበር።የዛን ቀን ከሰማይ እሳት እና ምስማር ቀላቅሎ የሚጥል ነበር የመሰለኝ።ያለወላጅ እናት ስላደግኩ በሱዋ ምትክ በልቤ እመቤታችን ንጽህት ድንግል ማርያም እናቴ እያልኩ ስላደግኩ እሱዋ የተሰደበች ያክል ነበር የሰቀጠጠኝ።በዛ ላይ ደግሞ "በእንተ ስሙዋ ለማርያም" ያልኩበት በስሙዋ ተማጽኜ ጎርሼ ያደርኩበት ዘመን ውልብ አለብኝ።
ምንም እንኩዋን አዲስ አበባ አቀባበሉዋ እንደ ደንባራ በቅሎ መንቃራ ቢሆንም።ኢለመንታሪ ፈለገ ዮርዳኖስ፣ ሀይስኩል 9 እና 10 አብዮት ቅርስ፣ 11 እና 12 ቦሌ ሀይስኩል፣ እንዲሁም እስከ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ድረስ አንቀባርራ አሳድጋኛለች።ከገጠር ይዤ የወጣሁት ስብእና ለዛሬው ማንነቴ እጅጉን አስተዋጽኦ አድርጉዋል።አንዳንዱም ጎጂ ባህል ነበር ለምሳሌ ሳልደርስበት የደረሰብኝን ሰው ሳልበቀል መተው ሽንፈት ይመስለኛል።እርቅም ከታሰበ ከተመጣጣኝ አጻፋ በቀል በሁዋላ እንጂ እንዲሁ አንተም ተው አንተም ተው አይሰራም።
ለማንኛውም አዲስ አበባ ቤቴ፣አሳዳጊዬ ክፉውንም፣ ደጉንም ያሳለፍኩብሽ፣ የኔ ሁሉን ቻይ ኑሪልኝ።ምንም እንኳን ባህር ብሻገርም ልቤ ግን ያለው ካንቺው ዘንድ ነው።•••የሰው ልጅ ከመኖር የሚያተርፈው ትዝታ ነው።
እኔም እነሆ ትዝታዬን አጋራኋችሁ!
መልካም ሰንበት!
(ዘላለም ጸጋዬ)
#ethiopia | ምንም እንኩዋን የተወለድኩት ከአንዲት ትንሽዬ የገጠር ከተማ ቢሆንም የልጅነት አይኔን ስገልጥ ግን የማስታውሰው የማርያምን ቤተክርስትያን፣ የመቅድስዋን የእጣን ሽታ፣የንፋስ ሽውታ የሚያስፉዋጨውን የጉዋሮዋን አርዘሊባኖስ፣የደጀ ሰላምዋን መአዛ ፣ካጠገቡም ያለውን ጭው ያለ ገደል እንዲሁም "መልእክተ ዮሀንስ ሀዋርያ ወልደ ዘብድዮስ" እያሉ መርጌታ አየለን የከበቡ የቆሎ ተማሪዎች ድምጽ እና የመሳሰለው ነው።በጥቅሉ የልጅነት አይኔን የገለጥኩት ስልጣኔ ካልጎበኘው እልም ካለ ገጠር ውስጥ ነው ...እናማ አኩፋዳዬን ጣጥዬ አዲስ አበባ የገባሁት የሶስተኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ ነበር።ነፍሱን ይማረውና አባቴ ፈለገ ዮርዲያኖስ ትምህርት ቤት ወስዶ ከተተኝ።አባቴ ቀድሞ ከተማ ገብቶ አስኩዋላት ተምሮ እቀድሞዋ ቺኮዝሎቫኪያ ድረስም ሂዶ ተምሮ ነበር የመጣው።ተያም በሁዋላ እስከ ደርግ ምክርቤት አባልነት ደርሶ ነበር።
ትምህርት የተጀመረ ሰሞን የእርሻ መመህራችን ስለ ስንዴ አበቃቀል ሲያስተምሩ ቆይተው።"ጥያቄያለው አለ?" ሲሉ ከመቅጽበት እጄን እንደ ኢራን ሚሳኤል ዘረጋሁት።እኔ በገጠር አያለሁ የማውቀው ትልቅ ስራ መምህረነት ነው።ከዛ ባለፈ ሁሉም አርሶ ነው የሚበላ።እናም ከተማ ከገባሁበት ቀን ጀምሮ ስትከነክነኝ የከረመችውን ጥያቄ እንዲህ በማለት አቀረብኩ "መምህር የስንዴ አበቃቀልን አላጣሁትም የኔ ጥያቄ ግን... እንዲያው ለመሆኑ ይሄ ሁሉ ከተሜ የት አርሶ ነው የሚበላ" ብዬ ስጠይቅ...የክፍሉ ተማሪ ሁሉ በሳቅ ፈረሰ።ያልሳቀ አንድ ሰው ቢኖር መምህሩ ብቻ ነበሩ።እንዴ ምንድነው አዳሜን ሚያስቀው ብዬ ተገረምኩ።አባቴ በሰው ላይ መሳቅ እና ማላገጥ አይገባም እንዲይ ካደረግክ ነገ ሌሎች በአንተ ላይ ያላግጡብሀል ይለኝ ነበር።በገጠርም ቢሆን ምን አልባት ነጠላችንን አፋችን ላይ ጣል አርገን በትንሹ ብናንጉዋጥጥ ነውይ በሰው ላይ ካካካክ ብለን አንስቅም።
የእርሻ ክፍለ ግዜው እንዳለቀ።መምህሩ ሲወጡ የክፍሉ ተማሪ ሁሉ እየተከተለ "ዘላለም ገበሬው" ማለት ጀመረ።ምንም አልተደናገጥኩም።ድሮም ደንቆሮ ወሬ አያጣም ብዬ ኮስተር አልኩ።የገጠር ልጅ ልበሙሉ አይደል።እህኔ እኮ የአንዱን ተማሪ የአይን መጋረጃ በዚህ አፈር ሲግፍ በከረመ እጄ ብከድንለት እኮ ሌላው አርፎ ይቀመጥ ነበር ብዬ አሰብኩ። ነገር ግን ከክላስ ስወጣ ወይም ስኔ 30 ጠብቀው ጨርቆስ ጉሊት መሃል ተሰብስበው ዱቄት እንዳያደርጉኝ ደግሞ ፈራሁ።በዛ ላይ ሰፈሩ ብዙ ግዜ በችግር ብዛት በህይወት አረቄ ሰክረው የሚደባደቡ አያጣውም ነበር።
የሆነው ሆኖ እንዲህ አልኩዋቸው...አዎ ገበሬ ነኝ።የገበሬ ምርቱ በትሳስ ነው።ታህሳስ ላይ እንገናኝ አልኩዋቸው።ቅኔ መሆኑዋ ነበር።የተሳዳቢው ተማሪ ቡድን መሪ ደግሞ አንዲት ድፍኑዋን ጨረቃ የመሰለች ዘቢብ የምትባል ቆንጅዬ ልጅ ነበረች።ቆንጆ ሰው አመሉም እንደመልኩ ሸጋ፣ልቡም እንደ እጣን ንጹህ ይመስለኝ ነበር።ገና ያኔ ነው አዬ ውበት ከንቱ ደምግባትም ብላሽ ያልኩት::ዘቢብ ግን ዛሬ የት ነሽ...እነዛ እንደ ቤተመቅደስ ጧፍ የሚያበሩ አይኖችሽ ሰላም ናቸው ወይ??? አቤት ውበታቸው አይን ያስፈነጥዝ ነበር•••
የሆነው ሆኖ በመጨረሻም ታህሳስ የመጀመርያ ሴሚስተር ውጤት ሲመጣ ከክፍሉ አንደኛ ወጣሁ።ያሁሉ ተማሪ እንደ ንጉስ ያየኝ ጀመር።እኔም ቆፍጠን ቄምጨጭ አልኩ "አለም ምንግዜም የቆራጦች ናት" ይል ነበር በዓሉ ግርማ።እናማ በክፍላችን ውስጥ እንግሊዘኛን እንደኔ የሚያነባት አልነበረም።አፌን ያዝ ከሚያደርገኝ የገጠር አማርኛ በስተቀር ምንም የሚወጣልኝ አልነበረም።ከባድ ጥያቄ በተጠየቀ ቁጠር መምህራን አይናቸውን ወደኔ ነበር የሚያቆለቁሉት።
ውሸት የሚባል አላውቅም ነበር።አሁንም ይተናነቀኛል።"እናትክን" የሚል ስድብ የሰማሁት እዛው ከትምህርት ቤታችን ፊትለፊት ከጉሊቱ መካከል ነበር።የዛን ቀን ከሰማይ እሳት እና ምስማር ቀላቅሎ የሚጥል ነበር የመሰለኝ።ያለወላጅ እናት ስላደግኩ በሱዋ ምትክ በልቤ እመቤታችን ንጽህት ድንግል ማርያም እናቴ እያልኩ ስላደግኩ እሱዋ የተሰደበች ያክል ነበር የሰቀጠጠኝ።በዛ ላይ ደግሞ "በእንተ ስሙዋ ለማርያም" ያልኩበት በስሙዋ ተማጽኜ ጎርሼ ያደርኩበት ዘመን ውልብ አለብኝ።
ምንም እንኩዋን አዲስ አበባ አቀባበሉዋ እንደ ደንባራ በቅሎ መንቃራ ቢሆንም።ኢለመንታሪ ፈለገ ዮርዳኖስ፣ ሀይስኩል 9 እና 10 አብዮት ቅርስ፣ 11 እና 12 ቦሌ ሀይስኩል፣ እንዲሁም እስከ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ድረስ አንቀባርራ አሳድጋኛለች።ከገጠር ይዤ የወጣሁት ስብእና ለዛሬው ማንነቴ እጅጉን አስተዋጽኦ አድርጉዋል።አንዳንዱም ጎጂ ባህል ነበር ለምሳሌ ሳልደርስበት የደረሰብኝን ሰው ሳልበቀል መተው ሽንፈት ይመስለኛል።እርቅም ከታሰበ ከተመጣጣኝ አጻፋ በቀል በሁዋላ እንጂ እንዲሁ አንተም ተው አንተም ተው አይሰራም።
ለማንኛውም አዲስ አበባ ቤቴ፣አሳዳጊዬ ክፉውንም፣ ደጉንም ያሳለፍኩብሽ፣ የኔ ሁሉን ቻይ ኑሪልኝ።ምንም እንኳን ባህር ብሻገርም ልቤ ግን ያለው ካንቺው ዘንድ ነው።•••የሰው ልጅ ከመኖር የሚያተርፈው ትዝታ ነው።
እኔም እነሆ ትዝታዬን አጋራኋችሁ!
መልካም ሰንበት!
Sponsored by
Surafel
2 months ago
የኢራን እስላማዊ አብዮት ዘብ ማሳሰቢያ
የኢራን እስላማዊ አብዮት ዘብ ስቪል ዜጎች በቀጠናው ካሉ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች እራሳቸውን እንዲያርቁ አሳሰበ። አብዮታዊ ዘቡ ዛሬ ባሰራጨው መግለጫ «ፈሪዎቹ የአሜሪካና የፅዮናዊት እስራኤል ሃይሎች ስቪሎች የሚኖሩባቸው አካባቢዎች እና ንጹሃን ስቪሎች እንደ ሰብአዊ ጋሻ እየተጠቀሙ ነው» ብሏል።
በመሆኑም «እራሳችሁን ከጥቃት ለመከላከል አሜሪካውያን ወታደሮች ከሰፈሩባቸው ቦታዎች እራሳችሁን አርቁ» ሲል ማሳሰቡን የዘገበው የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ነው።
seledadotio
seledadotio
የኢራን እስላማዊ አብዮት ዘብ ስቪል ዜጎች በቀጠናው ካሉ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች እራሳቸውን እንዲያርቁ አሳሰበ። አብዮታዊ ዘቡ ዛሬ ባሰራጨው መግለጫ «ፈሪዎቹ የአሜሪካና የፅዮናዊት እስራኤል ሃይሎች ስቪሎች የሚኖሩባቸው አካባቢዎች እና ንጹሃን ስቪሎች እንደ ሰብአዊ ጋሻ እየተጠቀሙ ነው» ብሏል።
በመሆኑም «እራሳችሁን ከጥቃት ለመከላከል አሜሪካውያን ወታደሮች ከሰፈሩባቸው ቦታዎች እራሳችሁን አርቁ» ሲል ማሳሰቡን የዘገበው የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ነው።
seledadotio
seledadotio
2 months ago
ራፐሩ የኔፓል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኑ
በኔፓል የቀድሞው ታዋቂ ራፐር እና የካትማንዱ ከንቲባ የነበሩት ባሌንድራ ሻህ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን ቃለ መሃላ ፈጸሙ።
የ35 ዓመቱ ወጣት ኢንጂነርና ድምፃዊ፣ በሹመት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ጥቁር ልብስና ጥቁር መነጽር አድርጎ በመቅረብ የብዙዎችን ቀልብ ስቧል።
የእሱ "ብሔራዊ ነፃነት ፓርቲ" ባለፈው መጋቢት ወር በተካሄደው ምርጫ አሸናፊ መሆኑ ይታወሳል።
ይህ ድል የመጣው እ.ኤ.አ. በ2025 በወጣቶች በተመራውና "የጄነሬሽን ዜድ አብዮት" በተባለው ተቃውሞ የቀድሞው መንግሥት ከወደቀ በኋላ ነው።
ባሌንድራ ሻህ በበዓሉ ላይ ሕገ-መንግሥቱን ለማክበርና ግዴታውን በታማኝነት ለመወጣት ቃል ገብቷል።
ይህ ክስተት በኔፓል ፖለቲካ ውስጥ የወጣቶች የበላይነት የመጣበት አዲስ ምዕራፍ ተደርጎ ተወስዷል።
በኔፓል የቀድሞው ታዋቂ ራፐር እና የካትማንዱ ከንቲባ የነበሩት ባሌንድራ ሻህ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን ቃለ መሃላ ፈጸሙ።
የ35 ዓመቱ ወጣት ኢንጂነርና ድምፃዊ፣ በሹመት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ጥቁር ልብስና ጥቁር መነጽር አድርጎ በመቅረብ የብዙዎችን ቀልብ ስቧል።
የእሱ "ብሔራዊ ነፃነት ፓርቲ" ባለፈው መጋቢት ወር በተካሄደው ምርጫ አሸናፊ መሆኑ ይታወሳል።
ይህ ድል የመጣው እ.ኤ.አ. በ2025 በወጣቶች በተመራውና "የጄነሬሽን ዜድ አብዮት" በተባለው ተቃውሞ የቀድሞው መንግሥት ከወደቀ በኋላ ነው።
ባሌንድራ ሻህ በበዓሉ ላይ ሕገ-መንግሥቱን ለማክበርና ግዴታውን በታማኝነት ለመወጣት ቃል ገብቷል።
ይህ ክስተት በኔፓል ፖለቲካ ውስጥ የወጣቶች የበላይነት የመጣበት አዲስ ምዕራፍ ተደርጎ ተወስዷል።
2 months ago
የካሙዙ ካሳ ላላ መልዕክት
ሠላም ጤና ይስጥልኝ የተከበራችሁ ውድ ኢትዮጵያውያን
#ethiopia | በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ጉምቱ የተባሉ የኪነጥበብ ባለሞያዎች እና በተለያዩ የሞያ ዘርፎች ላይ አንቱታን ያተረፉ ግለሰቦች ለህዝብ ጥቅም ለሀገር መፅናት ሲሉ በፖለቲካ ተሳትፈዉ ለህዝባቸዉ ይበጃል ያሉትን ታሪክ ሰርተዋል ፣ እየሰሩም ይገኛሉ። በአለም የፖለቲካ ጉዞም ቢሆን የኪነጥበብ ባለሞያዎች እና ስፖርተኞች ከረጅም ጊዜ ጀምሮ በማኅበራዊና ፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ብርቱ ተሳትፎ ሲያደርጉ ቆይተዋል።
የነበራቸውን ተሳትፎ በወፍ በረር ለመቃኘት ያክል:-
————
ሴኔጋል – ኢሱኑ ንዱር (Youssou N'Dour)
በዓለም የሙዚቃ መድረክ ተወዳጁ የሴኔጋል ዘፋኝ ኢሱኑ ንዱር፣ ለረጅም ዓመታት በማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ድምጹን ካሰማ በኋላ፣ በ2012 የሴኔጋል የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሆነው ተሾመ። በዚህ ሥልጣን የሀገሪቱን ቅርስ በማስጠበቅ ወጣቶችን በማብቃት ረገድ ትልቅ አሻራ አስቀርቷል።
————-
ላይቤሪያ – ጆርጅ ዊሃ (George Weah)
ከዓለም እግር ኳስ ታላላቅ ኮከቦች አንዱ የሆነው አፍሪካዊ የባሎን ዶር ተሸላሚ ጆርጅ ዌአ፣ ከሜዳ ጡረታ በኋላ ወደ ላይቤሪያ ፖለቲካ በመግባት ከፍተኛ ድምፅ በማግኘት በ2018 የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሆኖ ተመረጠ። የእርሱ ጉዞ ከስፖርት ወደ ከፍተኛ የፖለቲካ አመራር ከሚታወቁት ደማቅ ምሳሌዎች አንዱ ነው።
—————
ናይጄሪያ – ፌላ ኩቲ (Fela Kuti)
የአፍሮቢት ሙዚቃ አባት ተብሎ የሚጠራው ናይጄሪያዊው ፌላ ኩቲ፣ በዘፈኖቹ ብቻ ሳይሆን በጠንካራ የፖለቲካ ንቅናቄውም ይታወቃል። መንግሥትን ጥሩ ሲሰራ ደግፎ በደልና ብልሹ አስተዳደርን በግልጽ ተቃዉሞ የካላኩታ ሪፐብሊክ በመባል በሚታወቀው ማኅበረሰቡ ውስጥ ተደጋጋሚ ቅጣትና እስራት ቢደርስበትም፣ የአፍሪካን የሕዝብ ተነሳሽነት በሙዚቃ አብይ ምሳሌ ሆኖ ቆይቷል።
——————
ዩናይትድ ስቴትስ – ሮናልድ ሬገን (Ronald Reagan)
ከሆሊዉድ ታዋቂ ተዋናዮች አንዱ የነበረው ሮናልድ ሬገን፣ ከስክሪን ወደ ፖለቲካ በመሻገር ከ1967 እስከ 1975 የካሊፎርኒያ ገዥ ሆኖ አገልግሏል፣ በኋላም በ1981 የአሜሪካ 40ኛ ፕሬዚዳንት ሆኖ ተመረጠ። በሁለት የሥልጣን ዘመኑ በቀዝቃዛው ጦርነት ማብቂያ ላይ ትልቅ ሚና በመጫወት፣ የአሜሪካን ኢኮኖሚ በሪጋኖሚክስ ፖሊሲ በማሻሻል ከተዋንያን ወደ ዓለም አለቃነት የተሸጋገሩ ብርቱ ምሳሌ ነዉ።
———————-
ቦብ ማርሊ (Bob Marley)
የሬጌ ሙዚቃ ምልክት ቦብ ማርሊ በዘፈኖቹ የሰላም፣ የአንድነትና የፖለቲካ ነፃነት መልእክት አሰማ። በጃማይካ ከፍተኛ የፖለቲካ ግጭት በነበረበት ወቅት ሁለት ተቀናቃኝ አንጃዎችን በአንድ መድረክ ላይ በማሰባሰብ “One Love” ኮንሰርት በማዘጋጀት ታሪካዊ ስራን ሰርቷል። ምንም እንኳ መደበኛ የፖለቲካ ሹመት ባይይዝም፣ በዓለም ዙሪያ እንደ ታላቅ የሰላም አራማጅና ተጽዕኖ ፈጣሪ ይታወሳል።
——————-//
ካሊፎርኒያ – አርኖልድ ሽዋርዜኔገር (Arnold Schwarzenegger)
በሆሊዉድ ፊልሞች ተወዳጁ የቀድሞ የሰውነት ግንባታ ሻምፒዮንና ተዋናይ አርኖልድ ሽዋርዜኔገር፣ ወደ ፖለቲካ በመግባት ከ2003 እስከ 2011 የካሊፎርኒያ ግዛት 38ኛ ገዥ ሆኖ አገልግሏል። በሁለት ወገን በተካሄደ ልዩ ምርጫ ተመርጦ፣ በአካባቢ ጥበቃና በጀት ማሻሻያ ላይ ትኩረት በማድረግ ከፊልም ስኬት ወደ እውነተኛ አመራር የተሻገረ ምሳሌ ነዉ።
———————-
ዩክሬን – ቮሎዲሚር ዘለንስኪ (Volodymyr Zelenskyy)
ዩክሬናዊው ኮሜዲያንና ተዋናይ ቮሎዲሚር ዘለንስኪ፣ በሰራዉ ተከታታይ ድራማ ውስጥ ፕሬዚዳንትን በመጫወት ታዋቂነትን ካገኘ በኋላ፣ በ2019 በእውነት የዩክሬን ፕሬዚዳንት ሆኖ ተመረጠ። ከሥልጣን ላይ በነበረበት ወቅት ሀገሩ ከባድ ጦርነት የገጠማት ሲሆን፣ ዘለንስኪ በአለም አቀፍ መድረክ የዩክሬንን ድምጽ በማሰማት የኮሜዲ ተዋናይነትን ወደ ጀግንነት የለወጠ አመራር አሳይቷል።
———————-
ቼክ ሪፐብሊክ – ቫችላቭ ሃቬል (Václav Havel)
የቼክ ጸሐፊ፣ ተውኔት ደራሲና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ቫችላቭ ሃቬል፣ በኮሚኒስት አገዛዝ ዘመን በፅሑፎቹና በተግባሮቹ የሰላማዊ አብዮት (ቬልቬት አብዮት) መሪ ሆነ። ከአገዛዙ ውድቀት በኋላ በ1989 የቼኮዝሎቫኪያ ፕሬዚዳንት ሆኖተመረጠ፣ በኋላም የቼክ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ሆኖ እስከ 2003 አገልግሏል። የጸሐፊነት ብልሃቱን ወደ ዴሞክራሲ ግንባታ በመምራት ከባህል ወደ ፖለቲካ ከፍተኛ ለውጥ ካደረጉ ታላላቅ ሰዎች አንዱ
ነዉ።
ኔፓል ፣ ባለንድራ ሻህ(Balendra Shah) ፣
በሰፊው እሚታወቀዉ መጠሪያዉ Balen ነዉ፣ የቀድሞ ራፐር፣ ሂፕ-ሆፕ አርቲስት እና ስትራክቸራል መሐንዲስ ሲሆን ፣ የኔፓል አዲስ ብሔራዊ መሪ ሆኖ ተነስቷል። ይህም የባለን ፓርቲ የ Rastriya Swatantra Party (RSP) በማርች 5፣ 2026 ምርጫዎች ላይ ታሪካዊ አሸናፊነትን ተጎናፅፏል።
ባለንም በኔፓል ፖለቲካ ከወጣት መሪዎች አንዱ ያደርገዋል ።
———- #እናም የኪነጥበብ ባለሞያዎች በማኅበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ መሳተፍ ለሀገርና ለሕዝብ የጎላ ጥቅም ከማበርከት ባለፈ፣ ለኪነጥበብ ዘርፉ ከፍተኛ መነቃቃትን እንደሚፈጥር በጽኑ አምናለሁ ::ይሄም እድል ለኢትዮጵያ ኪነጥበብ እድገትም ትልቅ ሚና እንዳለው በማመንና አርቱን ሌሎች አገራት በደረሱበት ለማድረስ እንዲሁም ሀገርን በፅኑ ከማገልገል አላማ በመነሳት በተጨባጭ ለሀገር እየሰራ ነዉ ፣ ህዝቤን እና ሀገሬን ወደ ብልፅግና ማማ ያደርሳል ያልኩትን የብልጽግና ፓርቲን ወክዬ ለመወዳደር እጩ መሆኔን ሳበስር ደስታ ይሰማኛል።
—-////—-///—-
በስተመጨረሻም : እነሆ በኢትዮጵያ ታሪክ ወርቃማ ጊዜ ላይ እንገኛለን
የኢትዮጵያ ስብራቶች እየተጠገኑ ነው። በኢትዮጵያ እምቅ ሀብቶች እየወጡ ነው።
የኢትዮጵያ ጂኦ ፓለቲካዊ ቁመና እየተቀየረ ነው፣
ሀገር በምክክር እና በሽግግር ፍትህ ቁርሾዋን እየሻረች፣ ነገዋን እየተለመች ነው፣
ኢትዮጵያ በብዙ ነገሮች እራስዋን የመቻል ዕቅዷን እያሳካች ነው፣
የኢትዮጵያ ህልም እውን ሆኖ፣ ሁለንተናዊ ብልፅግና በኢትዮጵያ እንዲረጋገጥ፣ ጉዞው በውጤት ተጀምሯል።
ይሄን ውጤታማ ጉዞ ይበልጥ ለማሳካት ብልፅግናን መምረጥ ወሳኙ ነገር ነው።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን ይባርክ!!!
ካሙዙ ካሣ
ሠላም ጤና ይስጥልኝ የተከበራችሁ ውድ ኢትዮጵያውያን
#ethiopia | በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ጉምቱ የተባሉ የኪነጥበብ ባለሞያዎች እና በተለያዩ የሞያ ዘርፎች ላይ አንቱታን ያተረፉ ግለሰቦች ለህዝብ ጥቅም ለሀገር መፅናት ሲሉ በፖለቲካ ተሳትፈዉ ለህዝባቸዉ ይበጃል ያሉትን ታሪክ ሰርተዋል ፣ እየሰሩም ይገኛሉ። በአለም የፖለቲካ ጉዞም ቢሆን የኪነጥበብ ባለሞያዎች እና ስፖርተኞች ከረጅም ጊዜ ጀምሮ በማኅበራዊና ፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ብርቱ ተሳትፎ ሲያደርጉ ቆይተዋል።
የነበራቸውን ተሳትፎ በወፍ በረር ለመቃኘት ያክል:-
————
ሴኔጋል – ኢሱኑ ንዱር (Youssou N'Dour)
በዓለም የሙዚቃ መድረክ ተወዳጁ የሴኔጋል ዘፋኝ ኢሱኑ ንዱር፣ ለረጅም ዓመታት በማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ድምጹን ካሰማ በኋላ፣ በ2012 የሴኔጋል የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሆነው ተሾመ። በዚህ ሥልጣን የሀገሪቱን ቅርስ በማስጠበቅ ወጣቶችን በማብቃት ረገድ ትልቅ አሻራ አስቀርቷል።
————-
ላይቤሪያ – ጆርጅ ዊሃ (George Weah)
ከዓለም እግር ኳስ ታላላቅ ኮከቦች አንዱ የሆነው አፍሪካዊ የባሎን ዶር ተሸላሚ ጆርጅ ዌአ፣ ከሜዳ ጡረታ በኋላ ወደ ላይቤሪያ ፖለቲካ በመግባት ከፍተኛ ድምፅ በማግኘት በ2018 የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሆኖ ተመረጠ። የእርሱ ጉዞ ከስፖርት ወደ ከፍተኛ የፖለቲካ አመራር ከሚታወቁት ደማቅ ምሳሌዎች አንዱ ነው።
—————
ናይጄሪያ – ፌላ ኩቲ (Fela Kuti)
የአፍሮቢት ሙዚቃ አባት ተብሎ የሚጠራው ናይጄሪያዊው ፌላ ኩቲ፣ በዘፈኖቹ ብቻ ሳይሆን በጠንካራ የፖለቲካ ንቅናቄውም ይታወቃል። መንግሥትን ጥሩ ሲሰራ ደግፎ በደልና ብልሹ አስተዳደርን በግልጽ ተቃዉሞ የካላኩታ ሪፐብሊክ በመባል በሚታወቀው ማኅበረሰቡ ውስጥ ተደጋጋሚ ቅጣትና እስራት ቢደርስበትም፣ የአፍሪካን የሕዝብ ተነሳሽነት በሙዚቃ አብይ ምሳሌ ሆኖ ቆይቷል።
——————
ዩናይትድ ስቴትስ – ሮናልድ ሬገን (Ronald Reagan)
ከሆሊዉድ ታዋቂ ተዋናዮች አንዱ የነበረው ሮናልድ ሬገን፣ ከስክሪን ወደ ፖለቲካ በመሻገር ከ1967 እስከ 1975 የካሊፎርኒያ ገዥ ሆኖ አገልግሏል፣ በኋላም በ1981 የአሜሪካ 40ኛ ፕሬዚዳንት ሆኖ ተመረጠ። በሁለት የሥልጣን ዘመኑ በቀዝቃዛው ጦርነት ማብቂያ ላይ ትልቅ ሚና በመጫወት፣ የአሜሪካን ኢኮኖሚ በሪጋኖሚክስ ፖሊሲ በማሻሻል ከተዋንያን ወደ ዓለም አለቃነት የተሸጋገሩ ብርቱ ምሳሌ ነዉ።
———————-
ቦብ ማርሊ (Bob Marley)
የሬጌ ሙዚቃ ምልክት ቦብ ማርሊ በዘፈኖቹ የሰላም፣ የአንድነትና የፖለቲካ ነፃነት መልእክት አሰማ። በጃማይካ ከፍተኛ የፖለቲካ ግጭት በነበረበት ወቅት ሁለት ተቀናቃኝ አንጃዎችን በአንድ መድረክ ላይ በማሰባሰብ “One Love” ኮንሰርት በማዘጋጀት ታሪካዊ ስራን ሰርቷል። ምንም እንኳ መደበኛ የፖለቲካ ሹመት ባይይዝም፣ በዓለም ዙሪያ እንደ ታላቅ የሰላም አራማጅና ተጽዕኖ ፈጣሪ ይታወሳል።
——————-//
ካሊፎርኒያ – አርኖልድ ሽዋርዜኔገር (Arnold Schwarzenegger)
በሆሊዉድ ፊልሞች ተወዳጁ የቀድሞ የሰውነት ግንባታ ሻምፒዮንና ተዋናይ አርኖልድ ሽዋርዜኔገር፣ ወደ ፖለቲካ በመግባት ከ2003 እስከ 2011 የካሊፎርኒያ ግዛት 38ኛ ገዥ ሆኖ አገልግሏል። በሁለት ወገን በተካሄደ ልዩ ምርጫ ተመርጦ፣ በአካባቢ ጥበቃና በጀት ማሻሻያ ላይ ትኩረት በማድረግ ከፊልም ስኬት ወደ እውነተኛ አመራር የተሻገረ ምሳሌ ነዉ።
———————-
ዩክሬን – ቮሎዲሚር ዘለንስኪ (Volodymyr Zelenskyy)
ዩክሬናዊው ኮሜዲያንና ተዋናይ ቮሎዲሚር ዘለንስኪ፣ በሰራዉ ተከታታይ ድራማ ውስጥ ፕሬዚዳንትን በመጫወት ታዋቂነትን ካገኘ በኋላ፣ በ2019 በእውነት የዩክሬን ፕሬዚዳንት ሆኖ ተመረጠ። ከሥልጣን ላይ በነበረበት ወቅት ሀገሩ ከባድ ጦርነት የገጠማት ሲሆን፣ ዘለንስኪ በአለም አቀፍ መድረክ የዩክሬንን ድምጽ በማሰማት የኮሜዲ ተዋናይነትን ወደ ጀግንነት የለወጠ አመራር አሳይቷል።
———————-
ቼክ ሪፐብሊክ – ቫችላቭ ሃቬል (Václav Havel)
የቼክ ጸሐፊ፣ ተውኔት ደራሲና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ቫችላቭ ሃቬል፣ በኮሚኒስት አገዛዝ ዘመን በፅሑፎቹና በተግባሮቹ የሰላማዊ አብዮት (ቬልቬት አብዮት) መሪ ሆነ። ከአገዛዙ ውድቀት በኋላ በ1989 የቼኮዝሎቫኪያ ፕሬዚዳንት ሆኖተመረጠ፣ በኋላም የቼክ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ሆኖ እስከ 2003 አገልግሏል። የጸሐፊነት ብልሃቱን ወደ ዴሞክራሲ ግንባታ በመምራት ከባህል ወደ ፖለቲካ ከፍተኛ ለውጥ ካደረጉ ታላላቅ ሰዎች አንዱ
ነዉ።
ኔፓል ፣ ባለንድራ ሻህ(Balendra Shah) ፣
በሰፊው እሚታወቀዉ መጠሪያዉ Balen ነዉ፣ የቀድሞ ራፐር፣ ሂፕ-ሆፕ አርቲስት እና ስትራክቸራል መሐንዲስ ሲሆን ፣ የኔፓል አዲስ ብሔራዊ መሪ ሆኖ ተነስቷል። ይህም የባለን ፓርቲ የ Rastriya Swatantra Party (RSP) በማርች 5፣ 2026 ምርጫዎች ላይ ታሪካዊ አሸናፊነትን ተጎናፅፏል።
ባለንም በኔፓል ፖለቲካ ከወጣት መሪዎች አንዱ ያደርገዋል ።
———- #እናም የኪነጥበብ ባለሞያዎች በማኅበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ መሳተፍ ለሀገርና ለሕዝብ የጎላ ጥቅም ከማበርከት ባለፈ፣ ለኪነጥበብ ዘርፉ ከፍተኛ መነቃቃትን እንደሚፈጥር በጽኑ አምናለሁ ::ይሄም እድል ለኢትዮጵያ ኪነጥበብ እድገትም ትልቅ ሚና እንዳለው በማመንና አርቱን ሌሎች አገራት በደረሱበት ለማድረስ እንዲሁም ሀገርን በፅኑ ከማገልገል አላማ በመነሳት በተጨባጭ ለሀገር እየሰራ ነዉ ፣ ህዝቤን እና ሀገሬን ወደ ብልፅግና ማማ ያደርሳል ያልኩትን የብልጽግና ፓርቲን ወክዬ ለመወዳደር እጩ መሆኔን ሳበስር ደስታ ይሰማኛል።
—-////—-///—-
በስተመጨረሻም : እነሆ በኢትዮጵያ ታሪክ ወርቃማ ጊዜ ላይ እንገኛለን
የኢትዮጵያ ስብራቶች እየተጠገኑ ነው። በኢትዮጵያ እምቅ ሀብቶች እየወጡ ነው።
የኢትዮጵያ ጂኦ ፓለቲካዊ ቁመና እየተቀየረ ነው፣
ሀገር በምክክር እና በሽግግር ፍትህ ቁርሾዋን እየሻረች፣ ነገዋን እየተለመች ነው፣
ኢትዮጵያ በብዙ ነገሮች እራስዋን የመቻል ዕቅዷን እያሳካች ነው፣
የኢትዮጵያ ህልም እውን ሆኖ፣ ሁለንተናዊ ብልፅግና በኢትዮጵያ እንዲረጋገጥ፣ ጉዞው በውጤት ተጀምሯል።
ይሄን ውጤታማ ጉዞ ይበልጥ ለማሳካት ብልፅግናን መምረጥ ወሳኙ ነገር ነው።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን ይባርክ!!!
ካሙዙ ካሣ
3 months ago
መካከለኛው ምስራቅ ወደለየለት ጦርነት? ኢራን ከፍተኛ ባለስልጣኖቿ መገደላቸውን አረጋገጠች!
ኢራን የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ጸሐፊዋ አሊ ላሪጃኒ በእስራኤል የአየር ጥቃት መገደላቸውን በይፋ አረጋገጠች።
ላሪጃኒ የፓርላማ አፈ-ጉባኤ እና የሀገሪቱ የበላይ መሪ አማካሪ የነበሩ ሲሆን፣ በኢራን የፖለቲካ እና የደህንነት መዋቅር ውስጥ ቁልፍ ሚና የነበራቸው ግለሰብ ናቸው።
በተጨማሪም የባሲጅ ጦር አዛዥ ጎላምሬዛ ሶለይማኒ መገደላቸውን ተከትሎ፣ የኢራን አብዮት ጥበቃ ጦር ጠንካራ የአጸፋ እርምጃ እንደሚወስድ ዝቷል።
በሌላ በኩል፦
አሜሪካ፦ ለእስራኤል ሙሉ ድጋፏን በመግለጽ ጥቃቱ እንዲቀጥል አሳስባለች።
ኢራን፦ አሜሪካ እግረኛ ጦር የምትልክ ከሆነ "አዲስ ቬትናም" ይጠብቃታል ስትል አስጠንቅቃለች።
ውጥረት፦ ቴህራን ለመጀመሪያ ጊዜ አዳዲስ ሚሳኤሎችን በእስራኤል እና በባህረ ሰላጤው ሀገራት ላይ መተኮሷ ተዘግቧል።
ኢራን የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ጸሐፊዋ አሊ ላሪጃኒ በእስራኤል የአየር ጥቃት መገደላቸውን በይፋ አረጋገጠች።
ላሪጃኒ የፓርላማ አፈ-ጉባኤ እና የሀገሪቱ የበላይ መሪ አማካሪ የነበሩ ሲሆን፣ በኢራን የፖለቲካ እና የደህንነት መዋቅር ውስጥ ቁልፍ ሚና የነበራቸው ግለሰብ ናቸው።
በተጨማሪም የባሲጅ ጦር አዛዥ ጎላምሬዛ ሶለይማኒ መገደላቸውን ተከትሎ፣ የኢራን አብዮት ጥበቃ ጦር ጠንካራ የአጸፋ እርምጃ እንደሚወስድ ዝቷል።
በሌላ በኩል፦
አሜሪካ፦ ለእስራኤል ሙሉ ድጋፏን በመግለጽ ጥቃቱ እንዲቀጥል አሳስባለች።
ኢራን፦ አሜሪካ እግረኛ ጦር የምትልክ ከሆነ "አዲስ ቬትናም" ይጠብቃታል ስትል አስጠንቅቃለች።
ውጥረት፦ ቴህራን ለመጀመሪያ ጊዜ አዳዲስ ሚሳኤሎችን በእስራኤል እና በባህረ ሰላጤው ሀገራት ላይ መተኮሷ ተዘግቧል።
3 months ago
የሜትር ታክሲ ድርጅቶች "የቴክኖሎጂ አውታር ወይንስ የገንዘብ መሰብሰቢያ?" ከአሽከርካሪዎች የቀረበ ከባድ ወቀሳ
በፋስት መረጃ ሪፖርተር #fastmereja I በኢትዮጵያ የትራንስፖርት ዘርፍ ውስጥ አብዮት የፈጠሩት የሜትር ታክሲ ድርጅቶች፣ በአሁኑ ወቅት በአሽከርካሪዎችና በባለንብረቶች ዘንድ "ቸልተኞች" የሚል ስያሜ እየተሰጣቸው ነው። ድርጅቶቹ ከእያንዳንዱ ጉዞ ኮሚሽን ከመሰብሰብ ባለፈ፣ አሽከርካሪው በየመንገዱ ለሚገጥሙት መዋቅራዊ ችግሮች ድምጽ ለመሆን ፍቃደኛ አይደሉም የሚሉ ቅሬታዎች በዝርዝር እየቀረቡ ነው።
📍የመቆሚያና የመጫኛ ቦታ እጥረት
አሽከርካሪዎች ከሚያነሱት ዋነኛ ችግር አንዱ ተሳፋሪ ለመጫንና ለማውረድ፣ እንዲሁም ትዕዛዝ እስኪመጣ ቆመው የሚጠብቁበት ቦታ አለመኖሩ ነው።
ድርጅቶቹ በሺዎች የሚቆጠሩ መኪኖችን ወደ ስራ ቢያሰማሩም፣ እነዚህ መኪኖች የት ቆመው ትዕዛዝ እንደሚጠብቁ ከአስተዳደሩ ጋር ተነጋግረው መፍትሄ አላመጡም።
ተሳፋሪ ለመጫን ለአፍታ የቆመ አሽከርካሪ በትራፊክ ፖሊሶች "ህገ-ወጥ ማቆም" ተብሎ ለከፍተኛ ቅጣት ይዳረጋል። ድርጅቶቹ ግን ይህንን የአሰራር ችግር ለመፍታት ከመንግስት ጋር ድርድር ሲያደርጉ አይታዩም።
📍የበዙ ቅጣቶችና የአሽከርካሪው መከላከል አቅም ማጣት
በአሁኑ ወቅት የትራፊክ ቅጣቶች ከመጠን በላይ መጨመራቸው ይታወቃል። አሽከርካሪዎች እንደሚሉት፦
"ተሳፋሪው በፈለገበት ቦታ ቁም ይላል፤ እምቢ ካልን መጥፎ ደረጃ (Rating) ይሰጡናል። ከቆምን ደግሞ ፖሊስ ይቀጣናል።"
ድርጅቶቹ አሽከርካሪዎቻቸው በስራ ላይ እያሉ ለሚገጥማቸው አድሏዊ ቅጣት የህግ ከለላ ወይም ድምጽ የመሆን ዝንባሌ የላቸውም።
📍"የሚቆጥረው አይቆጥርም" የቴክኖሎጂ ስህተቶችና የታሪፍ ኢ-ፍትሃዊነት
ሌላው አሳሳቢ ቅሬታ በድርጅቶቹ መተግበሪያ (App) ላይ የሚታየው የርቀትና የዋጋ ስሌት አለመጣጣም ነው።
መተግበሪያዎቹ ብዙ ጊዜ የሚሰላው በኪሎሜትር እንጂ በትራፊክ መጨናነቅ ውስጥ ለሚባክነው ጊዜ እና ርቀት ተገቢውን ክፍያ አያካትቱም።
"አፕሊኬሽኑ የሚቆጥረው ርቀትና መኪናው በትክክል የሄደበት ርቀት አይጣጣምም፤ በዚህም የተነሳ አሽከርካሪው የሚገባውን ክፍያ አያገኝም" ሲሉ ቅሬታቸውን ይገልጻሉ።
📍የታክስ ጫና እና የኮሚሽን ግትርነት
የነዳጅ ዋጋ በየጊዜው ቢጨምርም፣ ድርጅቶቹ የሚወስዱት የኮሚሽን መቶኛ ግን ዝቅ እንዲል አይደረግም።
ባለንብረቶች እንደሚሉት ድርጅቶቹ ከመንግስት ጋር ተነጋግረው ለአሽከርካሪዎች የነዳጅ ድጎማ ወይም የቀለለ የታክስ ስርዓት እንዲዘረጋ ግፊት ማድረግ ሲገባቸው፣ ትኩረታቸው ኮሚሽን መሰብሰብ ላይ ብቻ ሆኗል።
📍ማጠቃለያ
አሽከርካሪዎችና ባለንብረቶች ድርጅቶቹን "ፕላትፎርሙን ብቻ ዘርግቶ ገንዘብ መሰብሰብ እንጂ ለአሽከርካሪው መብትና ለስራው ምቹ ሁኔታ መፈጠር ግድ የማይላቸው ከሆነ፣ ዘርፉ ወደ ቀውስ ሊያመራ ይችላል" ሲሉ የዘርፉ ተዋንያን ያስጠነቅቃሉ።
በፋስት መረጃ ሪፖርተር #fastmereja I በኢትዮጵያ የትራንስፖርት ዘርፍ ውስጥ አብዮት የፈጠሩት የሜትር ታክሲ ድርጅቶች፣ በአሁኑ ወቅት በአሽከርካሪዎችና በባለንብረቶች ዘንድ "ቸልተኞች" የሚል ስያሜ እየተሰጣቸው ነው። ድርጅቶቹ ከእያንዳንዱ ጉዞ ኮሚሽን ከመሰብሰብ ባለፈ፣ አሽከርካሪው በየመንገዱ ለሚገጥሙት መዋቅራዊ ችግሮች ድምጽ ለመሆን ፍቃደኛ አይደሉም የሚሉ ቅሬታዎች በዝርዝር እየቀረቡ ነው።
📍የመቆሚያና የመጫኛ ቦታ እጥረት
አሽከርካሪዎች ከሚያነሱት ዋነኛ ችግር አንዱ ተሳፋሪ ለመጫንና ለማውረድ፣ እንዲሁም ትዕዛዝ እስኪመጣ ቆመው የሚጠብቁበት ቦታ አለመኖሩ ነው።
ድርጅቶቹ በሺዎች የሚቆጠሩ መኪኖችን ወደ ስራ ቢያሰማሩም፣ እነዚህ መኪኖች የት ቆመው ትዕዛዝ እንደሚጠብቁ ከአስተዳደሩ ጋር ተነጋግረው መፍትሄ አላመጡም።
ተሳፋሪ ለመጫን ለአፍታ የቆመ አሽከርካሪ በትራፊክ ፖሊሶች "ህገ-ወጥ ማቆም" ተብሎ ለከፍተኛ ቅጣት ይዳረጋል። ድርጅቶቹ ግን ይህንን የአሰራር ችግር ለመፍታት ከመንግስት ጋር ድርድር ሲያደርጉ አይታዩም።
📍የበዙ ቅጣቶችና የአሽከርካሪው መከላከል አቅም ማጣት
በአሁኑ ወቅት የትራፊክ ቅጣቶች ከመጠን በላይ መጨመራቸው ይታወቃል። አሽከርካሪዎች እንደሚሉት፦
"ተሳፋሪው በፈለገበት ቦታ ቁም ይላል፤ እምቢ ካልን መጥፎ ደረጃ (Rating) ይሰጡናል። ከቆምን ደግሞ ፖሊስ ይቀጣናል።"
ድርጅቶቹ አሽከርካሪዎቻቸው በስራ ላይ እያሉ ለሚገጥማቸው አድሏዊ ቅጣት የህግ ከለላ ወይም ድምጽ የመሆን ዝንባሌ የላቸውም።
📍"የሚቆጥረው አይቆጥርም" የቴክኖሎጂ ስህተቶችና የታሪፍ ኢ-ፍትሃዊነት
ሌላው አሳሳቢ ቅሬታ በድርጅቶቹ መተግበሪያ (App) ላይ የሚታየው የርቀትና የዋጋ ስሌት አለመጣጣም ነው።
መተግበሪያዎቹ ብዙ ጊዜ የሚሰላው በኪሎሜትር እንጂ በትራፊክ መጨናነቅ ውስጥ ለሚባክነው ጊዜ እና ርቀት ተገቢውን ክፍያ አያካትቱም።
"አፕሊኬሽኑ የሚቆጥረው ርቀትና መኪናው በትክክል የሄደበት ርቀት አይጣጣምም፤ በዚህም የተነሳ አሽከርካሪው የሚገባውን ክፍያ አያገኝም" ሲሉ ቅሬታቸውን ይገልጻሉ።
📍የታክስ ጫና እና የኮሚሽን ግትርነት
የነዳጅ ዋጋ በየጊዜው ቢጨምርም፣ ድርጅቶቹ የሚወስዱት የኮሚሽን መቶኛ ግን ዝቅ እንዲል አይደረግም።
ባለንብረቶች እንደሚሉት ድርጅቶቹ ከመንግስት ጋር ተነጋግረው ለአሽከርካሪዎች የነዳጅ ድጎማ ወይም የቀለለ የታክስ ስርዓት እንዲዘረጋ ግፊት ማድረግ ሲገባቸው፣ ትኩረታቸው ኮሚሽን መሰብሰብ ላይ ብቻ ሆኗል።
📍ማጠቃለያ
አሽከርካሪዎችና ባለንብረቶች ድርጅቶቹን "ፕላትፎርሙን ብቻ ዘርግቶ ገንዘብ መሰብሰብ እንጂ ለአሽከርካሪው መብትና ለስራው ምቹ ሁኔታ መፈጠር ግድ የማይላቸው ከሆነ፣ ዘርፉ ወደ ቀውስ ሊያመራ ይችላል" ሲሉ የዘርፉ ተዋንያን ያስጠነቅቃሉ።
3 months ago
"የእስላማዊው አብዮት ድል"፦ ሁቲዎች ስለ ሞጅታባ ሹመት
በቴህራን የሚደገፉት የየመኑ የሁቲ አማፂያን፣ የሞጅታባ ካሜኒን የኢራን አዲስ መንፈሳዊ መሪ ሆኖ መሾም "ለእስላማዊው አብዮት የተገኘ ታላቅ ድል" ሲሉ አወደሱ።
ቡድኑ በቴሌግራም ገጹ ባስተላለፈው መልዕክት፣ ይህ ሹመት በሪፐብሊኩ ጠላቶች ላይ የተሰነዘረ "ከባድ ድብደባ" መሆኑን ገልጿል።
የሞጅታባ ወደ ስልጣን መምጣት በኢራን እና በደጋፊዎቿ ዘንድ እንደ ትልቅ ስትራቴጂካዊ ስኬት ተቆጥሯል።
በቴህራን የሚደገፉት የየመኑ የሁቲ አማፂያን፣ የሞጅታባ ካሜኒን የኢራን አዲስ መንፈሳዊ መሪ ሆኖ መሾም "ለእስላማዊው አብዮት የተገኘ ታላቅ ድል" ሲሉ አወደሱ።
ቡድኑ በቴሌግራም ገጹ ባስተላለፈው መልዕክት፣ ይህ ሹመት በሪፐብሊኩ ጠላቶች ላይ የተሰነዘረ "ከባድ ድብደባ" መሆኑን ገልጿል።
የሞጅታባ ወደ ስልጣን መምጣት በኢራን እና በደጋፊዎቿ ዘንድ እንደ ትልቅ ስትራቴጂካዊ ስኬት ተቆጥሯል።
Sponsored by
Surafel
3 months ago
📌 ስለ አዲሱ የኢራን መንፈሳዊ መሪ ሙጅተባ ኻሜኒ ማወቅ ያለባችሁ ነጥቦች፦
ዕድሜ፦ የ56 ዓመቱ ሙጅተባ ኻሜኒ የተወለዱት ጳጉሜ 3 ቀን 1961 ዓ.ም. ነው። በወጣትነታቸው በኢራን-ኢራቅ ጦርነት ወቅት በውትድርና አገልግለዋል።
አመራረጣቸው፦ 88 አባላት ያሉት የሊቃውንት ምክር ቤት በህገ-መንግስቱ መሰረት መርጧቸዋል። ይህም ከ1971 ዓ.ም. አብዮት በኋላ ሀገሪቱን የሚመሩ 3ኛው መንፈሳዊ መሪ ያደርጋቸዋል።
የደረሰባቸው ጉዳት፦ በቴህራን በተፈጸመው በዚሁ ጥቃት ሙጅተባ አባታቸውን ፣ እናታቸውን፣ ባለቤታቸውን፣ ልጃቸውንና እህታቸውን ጨምሮ በርካታ የቤተሰብ አባላትን አጥተዋል። እሳቸው ግን ከጥቃቱ ተርፈዋል።
ተጽዕኖ፦ ምንም እንኳን እስካሁን ይፋዊ የመንግስት ስልጣን ባይኖራቸውም፣ ከትዕይንቱ በስተጀርባ በአብዮታዊ ዘብ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንዳላቸው ይታወቃል።
⚠️ ያሚነሳባቸው ጥያቄ እና ተግዳሮት ፦
የማዕረግ ጥያቄ፦ በአሁኑ ወቅት ያላቸው የሃይማኖት ማዕረግ "ሁጃቱል ኢስላም" በመሆኑ፣ ለቦታው ከሚያስፈልገው "አያቶላ" ዝቅ ያለ ነው በሚል ትችት እየቀረበባቸው ነው።
የእስራኤል ዛቻ፦ የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ፣ ማንኛውም የኻሜኒን ፖሊሲ የሚቀጥል መሪ የእስራኤል "ህጋዊ የጥቃት ኢላማ" እንደሚሆን አስጠንቅቀዋል።
🔍 የታሪክ ማስታወሻ፦
ሙጅተባ ስልጣን የያዙት አባታቸው ከ1981 ዓ.ም. ጀምሮ ለ37 ዓመታት የመሩትን መንበር ተረክበው ነው።
አሜሪካ በ2012 ዓ.ም. በእሳቸው ላይ ማዕቀብ ጥላባቸው እንደነበር ይታወሳል።
ይህ የሹመት ዜና በክልሉ ያለውን ጦርነት ወደ የትኛው አቅጣጫ ሊወስደው እንደሚችል ዓለም በጉጉት እየጠበቀ ነው።
ዕድሜ፦ የ56 ዓመቱ ሙጅተባ ኻሜኒ የተወለዱት ጳጉሜ 3 ቀን 1961 ዓ.ም. ነው። በወጣትነታቸው በኢራን-ኢራቅ ጦርነት ወቅት በውትድርና አገልግለዋል።
አመራረጣቸው፦ 88 አባላት ያሉት የሊቃውንት ምክር ቤት በህገ-መንግስቱ መሰረት መርጧቸዋል። ይህም ከ1971 ዓ.ም. አብዮት በኋላ ሀገሪቱን የሚመሩ 3ኛው መንፈሳዊ መሪ ያደርጋቸዋል።
የደረሰባቸው ጉዳት፦ በቴህራን በተፈጸመው በዚሁ ጥቃት ሙጅተባ አባታቸውን ፣ እናታቸውን፣ ባለቤታቸውን፣ ልጃቸውንና እህታቸውን ጨምሮ በርካታ የቤተሰብ አባላትን አጥተዋል። እሳቸው ግን ከጥቃቱ ተርፈዋል።
ተጽዕኖ፦ ምንም እንኳን እስካሁን ይፋዊ የመንግስት ስልጣን ባይኖራቸውም፣ ከትዕይንቱ በስተጀርባ በአብዮታዊ ዘብ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንዳላቸው ይታወቃል።
⚠️ ያሚነሳባቸው ጥያቄ እና ተግዳሮት ፦
የማዕረግ ጥያቄ፦ በአሁኑ ወቅት ያላቸው የሃይማኖት ማዕረግ "ሁጃቱል ኢስላም" በመሆኑ፣ ለቦታው ከሚያስፈልገው "አያቶላ" ዝቅ ያለ ነው በሚል ትችት እየቀረበባቸው ነው።
የእስራኤል ዛቻ፦ የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ፣ ማንኛውም የኻሜኒን ፖሊሲ የሚቀጥል መሪ የእስራኤል "ህጋዊ የጥቃት ኢላማ" እንደሚሆን አስጠንቅቀዋል።
🔍 የታሪክ ማስታወሻ፦
ሙጅተባ ስልጣን የያዙት አባታቸው ከ1981 ዓ.ም. ጀምሮ ለ37 ዓመታት የመሩትን መንበር ተረክበው ነው።
አሜሪካ በ2012 ዓ.ም. በእሳቸው ላይ ማዕቀብ ጥላባቸው እንደነበር ይታወሳል።
ይህ የሹመት ዜና በክልሉ ያለውን ጦርነት ወደ የትኛው አቅጣጫ ሊወስደው እንደሚችል ዓለም በጉጉት እየጠበቀ ነው።
3 months ago
በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የF35 RC ጀት በረራ ተሳካ
#fastmereja I ወጣቱ የቴክኖሎጂ ባለሙያ ኢብራሂም አሊ (Ibrahim Ali)፣ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የሆነውን የF35 RC የጀት ሞዴል በተሳካ ሁኔታ ማብረር መቻሉን አስታወቀ።
ወጣቱ የፈጠራ ሰው ይህ ውጤት የተመዘገበው ተከታታይ ጥረትና ትግል ከተደረገ በኋላ መሆኑን ገልጾ፤ "ይህ የጀት ፕሮጀክት ከ8 ሙከራዎች በኋላ በ9ኛው በተሳካ ሁኔታ ከመሬት ተነስቶ በረረ" ሲል የጉዞውን ፈታኝነት አስረድቷል።
ከትንሽ ጅማሮ ወደ ትልቅ የአየር ቴክኖሎጂ ኃይል
ኢብራሂም አሊ ለስራው መነሻ ያደረገው የቱርክን የድሮን ቴክኖሎጂ አብዮት የመራውን የሰልቹክ ባይራክታር (Selçuk Bayraktar) ታሪክ መሆኑን ገልጿል። ባይራክታር እ.ኤ.አ. በ2005 በትንሽ የድሮን ፕሮቶታይፕ ጀምሮ ዛሬ ቱርክን በዘርፉ የዓለም ኃያል እንዳደረጋት ሁሉ፣ የእሱም ራዕይ ኢትዮጵያን በአየር ቴክኖሎጂ ጠንካራ ኃይል ማድረግ እንደሆነ ገልጿል።
"ዛሬ በትንንሽ የሪሞት ኮንትሮል ጀቶች እንጀምራለን፤ ነገ ግን የኢትዮጵያን አየር ኃይልና አቪዬሽን ቴክኖሎጂ ለማጠናከር የሚረዳ ትልቅ ተቋም እንገነባለን" ሲል የወደፊት ተስፋውን አጋርቷል።
#ሳይ_ቴክ
#fastmereja I ወጣቱ የቴክኖሎጂ ባለሙያ ኢብራሂም አሊ (Ibrahim Ali)፣ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የሆነውን የF35 RC የጀት ሞዴል በተሳካ ሁኔታ ማብረር መቻሉን አስታወቀ።
ወጣቱ የፈጠራ ሰው ይህ ውጤት የተመዘገበው ተከታታይ ጥረትና ትግል ከተደረገ በኋላ መሆኑን ገልጾ፤ "ይህ የጀት ፕሮጀክት ከ8 ሙከራዎች በኋላ በ9ኛው በተሳካ ሁኔታ ከመሬት ተነስቶ በረረ" ሲል የጉዞውን ፈታኝነት አስረድቷል።
ከትንሽ ጅማሮ ወደ ትልቅ የአየር ቴክኖሎጂ ኃይል
ኢብራሂም አሊ ለስራው መነሻ ያደረገው የቱርክን የድሮን ቴክኖሎጂ አብዮት የመራውን የሰልቹክ ባይራክታር (Selçuk Bayraktar) ታሪክ መሆኑን ገልጿል። ባይራክታር እ.ኤ.አ. በ2005 በትንሽ የድሮን ፕሮቶታይፕ ጀምሮ ዛሬ ቱርክን በዘርፉ የዓለም ኃያል እንዳደረጋት ሁሉ፣ የእሱም ራዕይ ኢትዮጵያን በአየር ቴክኖሎጂ ጠንካራ ኃይል ማድረግ እንደሆነ ገልጿል።
"ዛሬ በትንንሽ የሪሞት ኮንትሮል ጀቶች እንጀምራለን፤ ነገ ግን የኢትዮጵያን አየር ኃይልና አቪዬሽን ቴክኖሎጂ ለማጠናከር የሚረዳ ትልቅ ተቋም እንገነባለን" ሲል የወደፊት ተስፋውን አጋርቷል።
#ሳይ_ቴክ
3 months ago
የኢራን ሴት እግር ኳስ ተጫዋቾች ወታደራዊ ሰላምታ
#ethiopia | በእስያ ዋንጫ ተሳትፎ ላይ የሚገኘው የኢራን የሴቶች ብሔራዊ ቡድን፣ በመክፈቻው ጨዋታ ካሳየው የዝምታ ተቃውሞ በተለየ መልኩ ከአውስትራሊያ ጋር በነበረው ጨዋታ ብሔራዊ መዝሙሩን ሲዘምር ታይቷል።
ቡድኑ ሰኞ ዕለት ከደቡብ ኮሪያ ጋር በነበረው ጨዋታ ወቅት ብሔራዊ መዝሙሩን ከመዘመር ይልቅ ዝምታን መርጦ የነበረ ቢሆንም፣ በሮቢና ስቴዲየም ከአውስትራሊያ ጋር ከመጋጠሙ በፊት ግን "ሜህር-ኢ ካቫራን" (የምስራቃዊ ፀሐይ) የተሰኘውን የሀገሪቱን መዝሙር ዘምሯል።
ተጫዋቾቹና የቡድኑ አመራሮች ቀደም ሲል ኢራን ከዩናይትድ ስቴትስና ከእስራኤል ጋር ባላት ግጭት ምክንያት በሀገር ቤት ለሚገኙ ቤተሰቦቻቸው ያላቸውን ስጋት ገልጸው ነበር። ይሁን እንጂ በትናንትናው ዕለት አቋማቸውን ለምን እንደቀየሩ በይፋ የተገለጸ ምክንያት የለም።
በሜዳው የታየው ተቃውሞ
ተጫዋቾቹ ብሔራዊ መዝሙሩን ቢዘምሩም፣ በስቴዲየሙ የነበሩ ኢራናውያን ግን ግልጽ የሆነ ተቃውሞ ማሰማታቸውን የአል-ጀዚራ ዘገባ ያመለክታል። በስቴዲየሙ የታዩ ሁኔታዎች፦
* የቀድሞው ባንዲራ፦ በርካታ ተመልካቾች ከ1979 አብዮት በፊት የነበረውን የኢራን ባንዲራ በመያዝ አሁን ያለውን አገዛዝ ተቃውመዋል።
* ፖለቲካዊ መልዕክቶች፦ አንዳንድ ደጋፊዎች ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን የሚደግፉ ባነሮችን ይዘው ታይተዋል።
በውድድሩ ደካማ አጀማመር ያደረገችው ኢራን፣ በመክፈቻው በደቡብ ኮሪያ 3 ለ 0፣ በትናንትናው ጨዋታ ደግሞ በአውስትራሊያ 4 ለ 0 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ቡድኑ የመጨረሻ የምድብ ጨዋታውን እሁድ ዕለት ድል ካልቀናው የፊሊፒንስ ብሔራዊ ቡድን ጋር ያደርጋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ኢራን #እግር_ኳስ #የሴቶች_እስያ_ዋንጫ #nbc #ብሔራዊ_መዝሙር #አውስትራሊያ #ፖለቲካና_ስፖርት #iranwomenfootball #asiancup
#ethiopia | በእስያ ዋንጫ ተሳትፎ ላይ የሚገኘው የኢራን የሴቶች ብሔራዊ ቡድን፣ በመክፈቻው ጨዋታ ካሳየው የዝምታ ተቃውሞ በተለየ መልኩ ከአውስትራሊያ ጋር በነበረው ጨዋታ ብሔራዊ መዝሙሩን ሲዘምር ታይቷል።
ቡድኑ ሰኞ ዕለት ከደቡብ ኮሪያ ጋር በነበረው ጨዋታ ወቅት ብሔራዊ መዝሙሩን ከመዘመር ይልቅ ዝምታን መርጦ የነበረ ቢሆንም፣ በሮቢና ስቴዲየም ከአውስትራሊያ ጋር ከመጋጠሙ በፊት ግን "ሜህር-ኢ ካቫራን" (የምስራቃዊ ፀሐይ) የተሰኘውን የሀገሪቱን መዝሙር ዘምሯል።
ተጫዋቾቹና የቡድኑ አመራሮች ቀደም ሲል ኢራን ከዩናይትድ ስቴትስና ከእስራኤል ጋር ባላት ግጭት ምክንያት በሀገር ቤት ለሚገኙ ቤተሰቦቻቸው ያላቸውን ስጋት ገልጸው ነበር። ይሁን እንጂ በትናንትናው ዕለት አቋማቸውን ለምን እንደቀየሩ በይፋ የተገለጸ ምክንያት የለም።
በሜዳው የታየው ተቃውሞ
ተጫዋቾቹ ብሔራዊ መዝሙሩን ቢዘምሩም፣ በስቴዲየሙ የነበሩ ኢራናውያን ግን ግልጽ የሆነ ተቃውሞ ማሰማታቸውን የአል-ጀዚራ ዘገባ ያመለክታል። በስቴዲየሙ የታዩ ሁኔታዎች፦
* የቀድሞው ባንዲራ፦ በርካታ ተመልካቾች ከ1979 አብዮት በፊት የነበረውን የኢራን ባንዲራ በመያዝ አሁን ያለውን አገዛዝ ተቃውመዋል።
* ፖለቲካዊ መልዕክቶች፦ አንዳንድ ደጋፊዎች ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን የሚደግፉ ባነሮችን ይዘው ታይተዋል።
በውድድሩ ደካማ አጀማመር ያደረገችው ኢራን፣ በመክፈቻው በደቡብ ኮሪያ 3 ለ 0፣ በትናንትናው ጨዋታ ደግሞ በአውስትራሊያ 4 ለ 0 በሆነ ውጤት ተሸንፋለች። ቡድኑ የመጨረሻ የምድብ ጨዋታውን እሁድ ዕለት ድል ካልቀናው የፊሊፒንስ ብሔራዊ ቡድን ጋር ያደርጋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ኢራን #እግር_ኳስ #የሴቶች_እስያ_ዋንጫ #nbc #ብሔራዊ_መዝሙር #አውስትራሊያ #ፖለቲካና_ስፖርት #iranwomenfootball #asiancup