2 days ago
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ
📌 የ6ኛ ክፍል ውጤቱ ከባለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር የተሻለ ነው
#ethiopia |የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤትን አስመልክቶ ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ ይፋ አድርጓል።
የቢሮው ኃላፊ አቶ አብዮት ደምሴ እንደገለጹት፣ የዘንድሮው ማለፊያ ነጥብ ለሁለቱም ክፍሎች ክልላዊ 50 እና ከዚያ በላይ እንዲሆን የተወሰነ ሲሆን፣ ልዩ ድጋፍ ለሚሹ አካባቢዎች ደግሞ 48 እና ከዚያ በላይ እንዲሆን ተደርጓል።
በዚህም መሠረት በ8ኛ ክፍል ፈተናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡት 86 ሺህ 502 ተማሪዎች መካከል 78 ሺህ 203 የሚሆኑት ተፈትነው 47 ሺህ 307 ተማሪዎች ማለፊያ ነጥቡን በማስመዝገብ ወደ ቀጣይ ክፍል ተዛውረዋል።
ይህም የክልሉን አጠቃላይ የማለፍ ምጣኔ 60.4 በመቶ የሚያደርሰው ሲሆን፣ ከአምናው የ63 በመቶ ውጤት ጋር ሲነፃፀር የ3 በመቶ ቅናሽ አሳይቷል።
በተቃራኒው በ6ኛ ክፍል ከተፈተኑት 110 ሺህ 566 ተማሪዎች ውስጥ 70 ሺህ 584ቱ ማለፊያ ነጥብ በማምጣት ያለፉ ሲሆን፣ የክልሉ የማለፍ ምጣኔ 63.8 በመቶ ሆኖ ተመዝግቧል። ይህ ውጤት ከአምናው የ56 በመቶ አፈፃፀም ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ እድገት የታየበት ነው።
ከትምህርት ቤቶች አፈፃፀም አኳያም በ8ኛ ክፍል 540 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን ማሳለፍ ሲችሉ፣ 155 ትምህርት ቤቶች ግን አንድም ተማሪ ማሳለፍ አልቻሉም።
በ6ኛ ክፍል ደግሞ 476 ትምህርት ቤቶች 100 በመቶ የማሳለፍ ስኬት ሲያስመዘግቡ፣ 81 ትምህርት ቤቶች ምንም ተማሪ ሳያሳልፉ ቀርተዋል።
የክልል ትምህርት ቢሮ
#southethiopia #ethiopiaeducation #ministryofeducation #grade8exam #grade6exam
📌 የ6ኛ ክፍል ውጤቱ ከባለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር የተሻለ ነው
#ethiopia |የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤትን አስመልክቶ ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ ይፋ አድርጓል።
የቢሮው ኃላፊ አቶ አብዮት ደምሴ እንደገለጹት፣ የዘንድሮው ማለፊያ ነጥብ ለሁለቱም ክፍሎች ክልላዊ 50 እና ከዚያ በላይ እንዲሆን የተወሰነ ሲሆን፣ ልዩ ድጋፍ ለሚሹ አካባቢዎች ደግሞ 48 እና ከዚያ በላይ እንዲሆን ተደርጓል።
በዚህም መሠረት በ8ኛ ክፍል ፈተናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡት 86 ሺህ 502 ተማሪዎች መካከል 78 ሺህ 203 የሚሆኑት ተፈትነው 47 ሺህ 307 ተማሪዎች ማለፊያ ነጥቡን በማስመዝገብ ወደ ቀጣይ ክፍል ተዛውረዋል።
ይህም የክልሉን አጠቃላይ የማለፍ ምጣኔ 60.4 በመቶ የሚያደርሰው ሲሆን፣ ከአምናው የ63 በመቶ ውጤት ጋር ሲነፃፀር የ3 በመቶ ቅናሽ አሳይቷል።
በተቃራኒው በ6ኛ ክፍል ከተፈተኑት 110 ሺህ 566 ተማሪዎች ውስጥ 70 ሺህ 584ቱ ማለፊያ ነጥብ በማምጣት ያለፉ ሲሆን፣ የክልሉ የማለፍ ምጣኔ 63.8 በመቶ ሆኖ ተመዝግቧል። ይህ ውጤት ከአምናው የ56 በመቶ አፈፃፀም ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ እድገት የታየበት ነው።
ከትምህርት ቤቶች አፈፃፀም አኳያም በ8ኛ ክፍል 540 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን ማሳለፍ ሲችሉ፣ 155 ትምህርት ቤቶች ግን አንድም ተማሪ ማሳለፍ አልቻሉም።
በ6ኛ ክፍል ደግሞ 476 ትምህርት ቤቶች 100 በመቶ የማሳለፍ ስኬት ሲያስመዘግቡ፣ 81 ትምህርት ቤቶች ምንም ተማሪ ሳያሳልፉ ቀርተዋል።
የክልል ትምህርት ቢሮ
#southethiopia #ethiopiaeducation #ministryofeducation #grade8exam #grade6exam
4 days ago
u1273u120bu1241 u12d8u1218u127b... u12a2u1275u12eeu1335u12eb u12e8u122bu1237u1295 u122au12a8u122du12f5 u120du1275u1230u1265u1228u12cd u1290u12cd...u12e8u12a0u1228u1295u1313u12f4u12cd u12a0u1265u12eeu1275 u1275u12cdu120du12f5 u1300u1265u12f1
#u12e8u1200u1308u122du1309u12f3u12ed ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ታላቁ ዘመቻ... ኢትዮጵያ የራሷን ሪከርድ ልትሰብረው ነው...የአረንጓዴው አብዮት ትውልድ ጀብዱ
#የሀገርጉዳይ
8 days ago
ከቀዩ አብዮት ወደ አረንጓዴው አብዮት፡ የትውልድ እና የተግባር ሽግግር
*********************
(የዕለቱ መልዕክት)
የኢትዮጵያን የፖለቲካ ማህደር ገልጠን ስንመረምር፣ የ1960ዎቹ "ያ ትውልድ" ያቀጣጠለው ንቅናቄ በታሪክ ጎልቶ ይወጣል። ይህ አብዮተኛ ትውልድ ዘመናትን የተሻገረውን የንጉሣዊ ሥርዓት በታላቅ ህዝባዊ ማዕበል ለመገርሰስ ቢችልም፣ ያንን ለውጥ ወደ ተረጋጋ ሀገረ-መንግሥት ግንባታ ማሸጋገር ግን አቅቶት ነበር። ከጊዜ በኋላ ንቅናቄው ወደ አስከፊ የደም መፋሰስ ስላመራ፣ ያን የትናንት የታሪክ ምዕራፍ "ቀይ አብዮት" ብለን ልንጠራው እንችላለን። ቀይ አብዮት፥ ደም ያፋሰሰ፣ የተለየ ሀሳብን በጠብመንጃ ያዳፈነ፣ እና "አብዮት ልጆቿን ትበላለች" በሚል ጭካኔ የተሞላበት ዲስኮርስ ትውልድ ያመከነ የጥፋት ዘመን ነበር።
በዚህ የቀይ አብዮት አዙሪት ውስጥ፣ የአንድ ትውልድ አቅምና ሀገርን የመቀየር ጉጉት የነበረው ወጣት ኃይል እርስ በርሱ ተከፋፈለ፣ ተገዳደለ። በመደማመጥና በመተጋገዝ ሀገርን በጋራ ከመገንባት ይልቅ፣ አንዱ አብዮተኛ ሌላውን አብዮተኛ እያሳደደ በማጥፋቱ ምክንያት፣ የተረጋጋ መንግሥት መመስረት ሳይቻል ቀረ።
በዚህ ክፍተት ወታደራዊው ሥርዓት ስልጣኑን በኃይል ተቆጣጥሮ፣ ሀገሪቱን መውጫ ወደሌለው ደም አፋሳሽ የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ከተታት። ጦርነቱን ተከትሎ የዚያው ትውልድ አካል የነበሩ ኃይሎች መንግሥትን በኃይል በመገልበጣቸው፣ "የመጠፋፋት ፖለቲካ" ሥር ሰዶ ለዘመናት የዚህች ሀገር ፖለቲካዊና ማህበራዊ ስብራት ሆኖ ቆይቷል።
ዛሬ ግን በዚህች ታላቅ ሀገር ምድር ላይ የተለየ ንጋት ፈንጥቋል። አዲሱ የመደመር ትውልድ የትናንቱን ቁርሾ የሚያብስ፤ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ስብራትን የሚጠግን አዲስ ታሪክ እየጻፈ ይገኛል። ይህ ትውልድ ያስነሳው አብዮት፣ መንግሥትን በጉልበት ለመቀየር፣ ሥርዓትን አፈራርሶ በሌላ ለመተካት፣ ወይም የተለየ ሃሳብ ያለውን ለማጥፋት ያለመ አይደለም። ይህ አብዮት፣ ከቀይ አብዮት ወደ አረንጓዴ አብዮት የተደረገ የሰለጠነ የልዕልና ሽግግር ነው።
አረንጓዴ አብዮት የሕይወት፣ የልምላሜ እና የብልጽግና አብዮት ነው። ቀዩ አብዮት አንዱን በማግለልና በመጠፋፋት ላይ የተመሠረተ ሲሆን፤ አረንጓዴው አብዮት ግን በመደመር፣ በትብብርና በአንድነት ላይ የቆመ ነው። ይህ አብዮት ለዘመናት የተራቆተችውን፣ በድርቅና በረሃብ ስትፈተን የኖረችውን እናት ሀገር፣ በተፈጥሮ ጸጋዋ ዳግም እንድታንሰራራ፣ ቁስሏ እንዲሽርና ወደ አረንጓዴ ምድርነት እንድትመለስ የሚያደርግ የሕልውና ትግል ነው። ዛሬ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በዘር፣ በሃይማኖት፣ ወይም በፖለቲካ አመለካከት ሳይከፋፈል፣ በየአቅጣጫው ተሰልፎ እናት ሀገሩን ውብ አረንጓዴ ልብስ እያለበሳት ይገኛል።
ይህ የሕይወት አብዮት ዛሬ በሀገሪቱ ተቀጣጥሏል፣ ተፋፍሟልም። የዚህ ሥር-ነቀል አብዮት ማሳያ ደግሞ፣ የፊታችን ሐምሌ 27 በመላ ሀገሪቱ የሚተገበረው ታሪካዊ የክተት አዋጅ ነው። በዚህ ዕለት፣ አረንጓዴው አብዮተኛ ትውልድ በአንድ ጀንበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል አብዮቱን ወደማይቀለበስ የታሪክ ከፍታ ያሸጋግረዋል።
በጥቅሉ፣ ያለፈው ትውልድ በቀይ አብዮት ባፈሰሰው ደምና ባመከነው ዘመን ፈንታ፣ የዛሬው የመደመር ትውልድ በአረንጓዴ አብዮት የትጋት ላቡን በማፍሰስ እና የሕይወት ችግኞችን በመትከል ሀገሩን እያንቆጠቆጠ ይገኛል። ሀገርን ከማፍረስ ይልቅ በመገንባት፣ ከመገዳደል ይልቅ የሕይወት ዘር በመዝራት የሚፋፋመው ይህ አረንጓዴ አብዮት፣ በዓለም መድረክ ኢትዮጵያን የልዕልና ማማ ላይ የሚያስቀምጣት፣ ትውልድን አሻጋሪ ሕያው ንቅናቄ ነው!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
*********************
(የዕለቱ መልዕክት)
የኢትዮጵያን የፖለቲካ ማህደር ገልጠን ስንመረምር፣ የ1960ዎቹ "ያ ትውልድ" ያቀጣጠለው ንቅናቄ በታሪክ ጎልቶ ይወጣል። ይህ አብዮተኛ ትውልድ ዘመናትን የተሻገረውን የንጉሣዊ ሥርዓት በታላቅ ህዝባዊ ማዕበል ለመገርሰስ ቢችልም፣ ያንን ለውጥ ወደ ተረጋጋ ሀገረ-መንግሥት ግንባታ ማሸጋገር ግን አቅቶት ነበር። ከጊዜ በኋላ ንቅናቄው ወደ አስከፊ የደም መፋሰስ ስላመራ፣ ያን የትናንት የታሪክ ምዕራፍ "ቀይ አብዮት" ብለን ልንጠራው እንችላለን። ቀይ አብዮት፥ ደም ያፋሰሰ፣ የተለየ ሀሳብን በጠብመንጃ ያዳፈነ፣ እና "አብዮት ልጆቿን ትበላለች" በሚል ጭካኔ የተሞላበት ዲስኮርስ ትውልድ ያመከነ የጥፋት ዘመን ነበር።
በዚህ የቀይ አብዮት አዙሪት ውስጥ፣ የአንድ ትውልድ አቅምና ሀገርን የመቀየር ጉጉት የነበረው ወጣት ኃይል እርስ በርሱ ተከፋፈለ፣ ተገዳደለ። በመደማመጥና በመተጋገዝ ሀገርን በጋራ ከመገንባት ይልቅ፣ አንዱ አብዮተኛ ሌላውን አብዮተኛ እያሳደደ በማጥፋቱ ምክንያት፣ የተረጋጋ መንግሥት መመስረት ሳይቻል ቀረ።
በዚህ ክፍተት ወታደራዊው ሥርዓት ስልጣኑን በኃይል ተቆጣጥሮ፣ ሀገሪቱን መውጫ ወደሌለው ደም አፋሳሽ የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ከተታት። ጦርነቱን ተከትሎ የዚያው ትውልድ አካል የነበሩ ኃይሎች መንግሥትን በኃይል በመገልበጣቸው፣ "የመጠፋፋት ፖለቲካ" ሥር ሰዶ ለዘመናት የዚህች ሀገር ፖለቲካዊና ማህበራዊ ስብራት ሆኖ ቆይቷል።
ዛሬ ግን በዚህች ታላቅ ሀገር ምድር ላይ የተለየ ንጋት ፈንጥቋል። አዲሱ የመደመር ትውልድ የትናንቱን ቁርሾ የሚያብስ፤ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ስብራትን የሚጠግን አዲስ ታሪክ እየጻፈ ይገኛል። ይህ ትውልድ ያስነሳው አብዮት፣ መንግሥትን በጉልበት ለመቀየር፣ ሥርዓትን አፈራርሶ በሌላ ለመተካት፣ ወይም የተለየ ሃሳብ ያለውን ለማጥፋት ያለመ አይደለም። ይህ አብዮት፣ ከቀይ አብዮት ወደ አረንጓዴ አብዮት የተደረገ የሰለጠነ የልዕልና ሽግግር ነው።
አረንጓዴ አብዮት የሕይወት፣ የልምላሜ እና የብልጽግና አብዮት ነው። ቀዩ አብዮት አንዱን በማግለልና በመጠፋፋት ላይ የተመሠረተ ሲሆን፤ አረንጓዴው አብዮት ግን በመደመር፣ በትብብርና በአንድነት ላይ የቆመ ነው። ይህ አብዮት ለዘመናት የተራቆተችውን፣ በድርቅና በረሃብ ስትፈተን የኖረችውን እናት ሀገር፣ በተፈጥሮ ጸጋዋ ዳግም እንድታንሰራራ፣ ቁስሏ እንዲሽርና ወደ አረንጓዴ ምድርነት እንድትመለስ የሚያደርግ የሕልውና ትግል ነው። ዛሬ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በዘር፣ በሃይማኖት፣ ወይም በፖለቲካ አመለካከት ሳይከፋፈል፣ በየአቅጣጫው ተሰልፎ እናት ሀገሩን ውብ አረንጓዴ ልብስ እያለበሳት ይገኛል።
ይህ የሕይወት አብዮት ዛሬ በሀገሪቱ ተቀጣጥሏል፣ ተፋፍሟልም። የዚህ ሥር-ነቀል አብዮት ማሳያ ደግሞ፣ የፊታችን ሐምሌ 27 በመላ ሀገሪቱ የሚተገበረው ታሪካዊ የክተት አዋጅ ነው። በዚህ ዕለት፣ አረንጓዴው አብዮተኛ ትውልድ በአንድ ጀንበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል አብዮቱን ወደማይቀለበስ የታሪክ ከፍታ ያሸጋግረዋል።
በጥቅሉ፣ ያለፈው ትውልድ በቀይ አብዮት ባፈሰሰው ደምና ባመከነው ዘመን ፈንታ፣ የዛሬው የመደመር ትውልድ በአረንጓዴ አብዮት የትጋት ላቡን በማፍሰስ እና የሕይወት ችግኞችን በመትከል ሀገሩን እያንቆጠቆጠ ይገኛል። ሀገርን ከማፍረስ ይልቅ በመገንባት፣ ከመገዳደል ይልቅ የሕይወት ዘር በመዝራት የሚፋፋመው ይህ አረንጓዴ አብዮት፣ በዓለም መድረክ ኢትዮጵያን የልዕልና ማማ ላይ የሚያስቀምጣት፣ ትውልድን አሻጋሪ ሕያው ንቅናቄ ነው!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
19 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ለአሥራ ስድስት ዓመታት ያህል.. “ጆሃንስበርግ” የምትለው ቃል ለስፔን እግር ኳስ ፍጹም ወርቃማ እና የተቀደሰች ትርጉም ነበራት። እሷ ከማድሪድ 8,000 ኪሎ ሜትር ርቃ የምትገኝ ከተማ ብቻ አልነበረችም፤ ይልቁንም አይከር ካሲያስ የወርቅ ጽዋውን ወደ ሰማይ የሰቀለባት፣ አንድሬስ ኢኒየስታ በ116ኛው ደቂቃ ላይ ያስቆጠራት ግብ ታሪክን ዘላለም ያደረገባት እና ስፔን “አንድ ቀን የዓለም ሻምፒዮን መሆን እችል ይሆን?” የሚለውን ጥያቄ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የቀበረችባት የታሪክ ማህደር እንጂ!
አሁን ግን የእግር ኳሱ የክብር ካርታ ወደ አዲሱ ዓለም፣ ወደ ኒውዮርክ እየመራን ነው። በሁድሰን ወንዝ ማዶ በኒው ጀርሲ፣ ሌላኛዋ አዲስ እና አስፈሪዋ የስፔን ብሔራዊ ቡድን እያንዳንዱ ታዳጊ በሕልሙ ሊጫወተው የሚመኘውን ያንን ታላቅ የፍፃሜ ጨዋታ ልታደርግ ተዘጋጅታለች። በዚያ በጆሃንስበርግ የኢኒየስታ ታሪካዊ ግብ ሲቆጠር አንዳንዶቹ የቡድኑ ተጫዋቾች ገና ዳዴ በማለት ላይ ነበሩ፤ ሌሎቹ ደግሞ በየሰፈሩና በየፓርኩ ያንን ግብ እየደገሙ ያደጉ ታዳጊዎች ናቸው። ዛሬ ግን ያቺ የመጀመሪያዋ የክብር ኮከብ በእነሱ ላይ ከባድ ሸክም መሆኗ ቀርቶ ወደ ቀጣዩ ታሪክ የሚመራቸው ፋኖስ ሆናለች።
ይህ ጉዞ ግን በምቾት የተሞላ ቀጥተኛ መንገድ አልነበረም። ለአሥራ ስድስት ዓመታት የፈጀ፣ ስድስት አሰልጣኞችን የቀያየረ እና የቡድኑን ማንነት ሙሉ በሙሉ የለወጠ ከባድ ጉዞ እንጂ። የመጀመሪያው ምዕራፍ የወርቃማው ትውልድ ቀጣይ ክፍል ነበር። ቪሴንቴ ዴል ቦስኬ የዓለም ሻምፒዮኑን ቡድን ይዘት ሳይበርዝ አስቀጥሎ፣ ከሁለት ዓመት በኋላ በኪየቭ ጣሊያንን 4 ለ 0 በሆነ አስደናቂ እግር ኳስ በማሸነፍ የዩሮ 2012 ዋንጫን በድጋሚ አነሳ። ያ ስብስብ በታሪክ ተወዳዳሪ የሌለው ታላቅ ታሪክ ጻፈ - የአውሮፓ ዋንጫን፣ የዓለም ዋንጫን እና የአውሮፓ ዋንጫን በተከታታይ በማሸነፍ ዓለምን በበላይነት የገዛበት ዘመን ነበር።
ነገር ግን ምንም ዓይነት ታላቅ ግዛት ለዘላለም አይኖርም! የ2014ቱ የብራዚል የዓለም ዋንጫ የዚያ ወደር የለሽ ትውልድ የውድቀት ማብሰሪያ ሆነ። በኔዘርላንድስ የደረሰባቸው አስደንጋጭ ሽንፈት እና በቺሊ መረታት ያንን ታሪካዊ ምዕራፍ በድንገት ዘጋው። ስፔን ከዓለም ሻምፒዮንነት ተነስታ በምድብ ደረጃ ተሸኝታ ወጣች። እግር ኳስ ለስፔናውያን ታላቅ ትምህርት ሰጣቸው - ክብር ለዘላለም የሚሰጥ ስጦታ አይደለም! ከሁለት ዓመት በኋላ በፈረንሳዩ ዩሮ፣ ጣሊያን ስፔንን በሩብ ፍፃሜ ስታስወጣ፣ የዴል ቦስኬ ዘመን እና ዋና የነበረው ያ ትውልድ ሙሉ በሙሉ ማክተሙ ታወጀ።
ከዚያ በኋላ ስፔን ወደ መልሶ ግንባታ ገባች። ጁለን ሎፔቴጊ የቡድኑን ታሪካዊ ቅርስ ሳይበታትን አዲስ ትውልድ የመፍጠር ከባድ ኃላፊነት ተረከበ። ቡድኑን በብቃት ለሩሲያው የዓለም ዋንጫ ቢያሳልፍም፣ ጨዋታው ከመጀመሩ ሁለት ቀን በፊት ከሪያል ማድሪድ ጋር ውል ማሰሩን ተከትሎ ከኃላፊነቱ መባረሩ በዓለም እግር ኳስ ታሪክ ትልቁ ድራማ ሆነ። ፈርናንዶ ሄሮ ቡድኑን በድንገተኛ አደጋ ቢረከብም፣ ስፔን በሩሲያ በፔናሊቲ ተመትታ ስትወጣ ስሜቱ እጅግ መራራ ነበር።
በመቀጠል የመጣው ሉዊስ ኤንሪኬ ግን ፍጹም አዲስ አብዮት ይዞ መጣ። ያረጁ ተዋናዮችን በማስወገድ፣ ወጣቶችን ወደ ፊት በማምጣት ፈጣንና ኃይለኛ ቡድን ፈጠረ። በልጃቸው ሕመም ምክንያት ለጥቂት ጊዜ ቢርቁም፣ በረዳታቸው ሮበርት ሞሬኖ አማካኝነት ቡድኑ ሳይሸነፍ ጉዞውን ቀጠለ። ኤንሪኬ ሲመለሱም ፕሮጀክቱን አፋጠኑት። በ2021 ዩሮ ስፔን እስከ ግማሽ ፍፃሜ ተጉዛ በጣሊያን ብትሸነፍም፣ ቡድኑ ወደ ቀድሞ አስፈሪነቱ መመለሱን አበሰረ። ነገር ግን በኳታር የዓለም ዋንጫ ኮስታሪካን 7 ለ 0 በማሸነፍ በደመቀ ሁኔታ የጀመረው ጉዞ፣ በሞሮኮ የቅጣት ምት (ፔናሊቲ) ተረቶ በከባድ ሐዘን ተጠናቀቀ። ስፔን በተከታታይ ሦስት ትላልቅ ውድድሮች ሩብ ፍጻሜ እንኳን መድረስ አለመቻሏ ፌዴሬሽኑ አዲስ መንገድ እንዲፈልግ አስገደደው።
ሉዊስ ዴ ላ ፉየንቴ ለዓመታት በታችኛው የዕድሜ ክልል ውስጥ የስፔንን ወጣቶች ሲቀርጽ የቆየ ጥልቅ መሃንዲስ ነው። የዩሮ ከ19 እና ከ21 ሻምፒዮን፣ የኦሊምፒክ ሜዳሊያ ባለቤት በመሆኑ የወደፊቱን ትውልድ በደብ ያውቀው ነበር። የእሱ ስልት ግለሰብን ሳይሆን እንደ አንድ ጠንካራ ቤተሰብ መጫወትን ማዕከል ያደረገ ነበር። ውጤቱም ወዲያውኑ መጣ!
መጀመሪያ የኔሽንስ ሊግን አሸነፈ... በመቀጠልም የ2024ቱን የአውሮፓ ዋንጫ በታላቅ የበላይነት በማንሳት ስፔንን ዳግም ወደ አውሮፓ የክብር ማማ መለሳት። ያ ቡድን በሮድሪ፣ ፔድሪ፣ ፋቢያን፣ ላሚን ያማል እና ኒኮ ዊሊያምስ የሚመራ፣ ወጣቶችና አንጋፋዎች የተቀላቀሉበት፣ ፍጹም የማይፈራ ስብስብ ሆነ። አሰልጣኙ እንደተናገሩት ያ ዩሮ ገና ጅምር እንጂ ማሳረጊያ አልነበረም።
ባለፉት ሁለት ዓመታት ዴ ላ ፉየንቴ ኳስን መቆጣጠር ብቻ ሳይሆን፣ መሮጥ፣ መጫን፣ እና አስፈላጊ ሲሆን መከላከል የሚችል ሁለገብ ቡድን ገንብቷል። ይህ ቡድን በአጨዋወቱ ከ2010ዱ ቡድን ቢለይም፣ በአሸናፊነት ስነ-ልቦናው ግን ፍጹም አንድ አይነት ነው።
ከጆሃንስበርግ እስከ ኒውዮርክ በትክክል 5,852 ቀናት አልፈዋል። ተዋናዮቹ ተቀይረዋል፣ ስታዲየሞቹ ሌላ ሆነዋል፣ ተቀናቃኞቹም ተለውጠዋል። አይከር ካሲያስ የአምበልነቱን ማዕረግ ለአዲሱ ትውልድ አስረክቧል። ዣቪ፣ ኢኒየስታ እና ቪያ ቦታቸውን ለሮድሪ፣ ላሚን ያማል እና ኦያርዛባል ለቀዋል። ነገር ግን የዴል ቦስኬን ታሪካዊ መንገድ ዛሬ ዴ ላ ፉየንቴ በዚያው ወርቃማ ስሜት እያስቀጠለው ይገኛል—ያንን የመጀመሪያዋን የክብር ኮከብ በቴሌቪዥን እያዩ ያደጉት ታዳጊዎች፣ ዛሬ ሁለተኛዋን ኮከብ ለመጨበጥ በኒውዮርክ ሜዳ ላይ ታሪክ ለመጻፍ ተዘጋጅተዋል!
አሁን ግን የእግር ኳሱ የክብር ካርታ ወደ አዲሱ ዓለም፣ ወደ ኒውዮርክ እየመራን ነው። በሁድሰን ወንዝ ማዶ በኒው ጀርሲ፣ ሌላኛዋ አዲስ እና አስፈሪዋ የስፔን ብሔራዊ ቡድን እያንዳንዱ ታዳጊ በሕልሙ ሊጫወተው የሚመኘውን ያንን ታላቅ የፍፃሜ ጨዋታ ልታደርግ ተዘጋጅታለች። በዚያ በጆሃንስበርግ የኢኒየስታ ታሪካዊ ግብ ሲቆጠር አንዳንዶቹ የቡድኑ ተጫዋቾች ገና ዳዴ በማለት ላይ ነበሩ፤ ሌሎቹ ደግሞ በየሰፈሩና በየፓርኩ ያንን ግብ እየደገሙ ያደጉ ታዳጊዎች ናቸው። ዛሬ ግን ያቺ የመጀመሪያዋ የክብር ኮከብ በእነሱ ላይ ከባድ ሸክም መሆኗ ቀርቶ ወደ ቀጣዩ ታሪክ የሚመራቸው ፋኖስ ሆናለች።
ይህ ጉዞ ግን በምቾት የተሞላ ቀጥተኛ መንገድ አልነበረም። ለአሥራ ስድስት ዓመታት የፈጀ፣ ስድስት አሰልጣኞችን የቀያየረ እና የቡድኑን ማንነት ሙሉ በሙሉ የለወጠ ከባድ ጉዞ እንጂ። የመጀመሪያው ምዕራፍ የወርቃማው ትውልድ ቀጣይ ክፍል ነበር። ቪሴንቴ ዴል ቦስኬ የዓለም ሻምፒዮኑን ቡድን ይዘት ሳይበርዝ አስቀጥሎ፣ ከሁለት ዓመት በኋላ በኪየቭ ጣሊያንን 4 ለ 0 በሆነ አስደናቂ እግር ኳስ በማሸነፍ የዩሮ 2012 ዋንጫን በድጋሚ አነሳ። ያ ስብስብ በታሪክ ተወዳዳሪ የሌለው ታላቅ ታሪክ ጻፈ - የአውሮፓ ዋንጫን፣ የዓለም ዋንጫን እና የአውሮፓ ዋንጫን በተከታታይ በማሸነፍ ዓለምን በበላይነት የገዛበት ዘመን ነበር።
ነገር ግን ምንም ዓይነት ታላቅ ግዛት ለዘላለም አይኖርም! የ2014ቱ የብራዚል የዓለም ዋንጫ የዚያ ወደር የለሽ ትውልድ የውድቀት ማብሰሪያ ሆነ። በኔዘርላንድስ የደረሰባቸው አስደንጋጭ ሽንፈት እና በቺሊ መረታት ያንን ታሪካዊ ምዕራፍ በድንገት ዘጋው። ስፔን ከዓለም ሻምፒዮንነት ተነስታ በምድብ ደረጃ ተሸኝታ ወጣች። እግር ኳስ ለስፔናውያን ታላቅ ትምህርት ሰጣቸው - ክብር ለዘላለም የሚሰጥ ስጦታ አይደለም! ከሁለት ዓመት በኋላ በፈረንሳዩ ዩሮ፣ ጣሊያን ስፔንን በሩብ ፍፃሜ ስታስወጣ፣ የዴል ቦስኬ ዘመን እና ዋና የነበረው ያ ትውልድ ሙሉ በሙሉ ማክተሙ ታወጀ።
ከዚያ በኋላ ስፔን ወደ መልሶ ግንባታ ገባች። ጁለን ሎፔቴጊ የቡድኑን ታሪካዊ ቅርስ ሳይበታትን አዲስ ትውልድ የመፍጠር ከባድ ኃላፊነት ተረከበ። ቡድኑን በብቃት ለሩሲያው የዓለም ዋንጫ ቢያሳልፍም፣ ጨዋታው ከመጀመሩ ሁለት ቀን በፊት ከሪያል ማድሪድ ጋር ውል ማሰሩን ተከትሎ ከኃላፊነቱ መባረሩ በዓለም እግር ኳስ ታሪክ ትልቁ ድራማ ሆነ። ፈርናንዶ ሄሮ ቡድኑን በድንገተኛ አደጋ ቢረከብም፣ ስፔን በሩሲያ በፔናሊቲ ተመትታ ስትወጣ ስሜቱ እጅግ መራራ ነበር።
በመቀጠል የመጣው ሉዊስ ኤንሪኬ ግን ፍጹም አዲስ አብዮት ይዞ መጣ። ያረጁ ተዋናዮችን በማስወገድ፣ ወጣቶችን ወደ ፊት በማምጣት ፈጣንና ኃይለኛ ቡድን ፈጠረ። በልጃቸው ሕመም ምክንያት ለጥቂት ጊዜ ቢርቁም፣ በረዳታቸው ሮበርት ሞሬኖ አማካኝነት ቡድኑ ሳይሸነፍ ጉዞውን ቀጠለ። ኤንሪኬ ሲመለሱም ፕሮጀክቱን አፋጠኑት። በ2021 ዩሮ ስፔን እስከ ግማሽ ፍፃሜ ተጉዛ በጣሊያን ብትሸነፍም፣ ቡድኑ ወደ ቀድሞ አስፈሪነቱ መመለሱን አበሰረ። ነገር ግን በኳታር የዓለም ዋንጫ ኮስታሪካን 7 ለ 0 በማሸነፍ በደመቀ ሁኔታ የጀመረው ጉዞ፣ በሞሮኮ የቅጣት ምት (ፔናሊቲ) ተረቶ በከባድ ሐዘን ተጠናቀቀ። ስፔን በተከታታይ ሦስት ትላልቅ ውድድሮች ሩብ ፍጻሜ እንኳን መድረስ አለመቻሏ ፌዴሬሽኑ አዲስ መንገድ እንዲፈልግ አስገደደው።
ሉዊስ ዴ ላ ፉየንቴ ለዓመታት በታችኛው የዕድሜ ክልል ውስጥ የስፔንን ወጣቶች ሲቀርጽ የቆየ ጥልቅ መሃንዲስ ነው። የዩሮ ከ19 እና ከ21 ሻምፒዮን፣ የኦሊምፒክ ሜዳሊያ ባለቤት በመሆኑ የወደፊቱን ትውልድ በደብ ያውቀው ነበር። የእሱ ስልት ግለሰብን ሳይሆን እንደ አንድ ጠንካራ ቤተሰብ መጫወትን ማዕከል ያደረገ ነበር። ውጤቱም ወዲያውኑ መጣ!
መጀመሪያ የኔሽንስ ሊግን አሸነፈ... በመቀጠልም የ2024ቱን የአውሮፓ ዋንጫ በታላቅ የበላይነት በማንሳት ስፔንን ዳግም ወደ አውሮፓ የክብር ማማ መለሳት። ያ ቡድን በሮድሪ፣ ፔድሪ፣ ፋቢያን፣ ላሚን ያማል እና ኒኮ ዊሊያምስ የሚመራ፣ ወጣቶችና አንጋፋዎች የተቀላቀሉበት፣ ፍጹም የማይፈራ ስብስብ ሆነ። አሰልጣኙ እንደተናገሩት ያ ዩሮ ገና ጅምር እንጂ ማሳረጊያ አልነበረም።
ባለፉት ሁለት ዓመታት ዴ ላ ፉየንቴ ኳስን መቆጣጠር ብቻ ሳይሆን፣ መሮጥ፣ መጫን፣ እና አስፈላጊ ሲሆን መከላከል የሚችል ሁለገብ ቡድን ገንብቷል። ይህ ቡድን በአጨዋወቱ ከ2010ዱ ቡድን ቢለይም፣ በአሸናፊነት ስነ-ልቦናው ግን ፍጹም አንድ አይነት ነው።
ከጆሃንስበርግ እስከ ኒውዮርክ በትክክል 5,852 ቀናት አልፈዋል። ተዋናዮቹ ተቀይረዋል፣ ስታዲየሞቹ ሌላ ሆነዋል፣ ተቀናቃኞቹም ተለውጠዋል። አይከር ካሲያስ የአምበልነቱን ማዕረግ ለአዲሱ ትውልድ አስረክቧል። ዣቪ፣ ኢኒየስታ እና ቪያ ቦታቸውን ለሮድሪ፣ ላሚን ያማል እና ኦያርዛባል ለቀዋል። ነገር ግን የዴል ቦስኬን ታሪካዊ መንገድ ዛሬ ዴ ላ ፉየንቴ በዚያው ወርቃማ ስሜት እያስቀጠለው ይገኛል—ያንን የመጀመሪያዋን የክብር ኮከብ በቴሌቪዥን እያዩ ያደጉት ታዳጊዎች፣ ዛሬ ሁለተኛዋን ኮከብ ለመጨበጥ በኒውዮርክ ሜዳ ላይ ታሪክ ለመጻፍ ተዘጋጅተዋል!
25 days ago
''አትመጣም ወይ ማርቆስ ከተድላው ከተማ
ቢሻህ በአውሮፕላን ቢሻህ በሎንቺና''
📌የደብረ ማርቆስ አውሮፕላን ማረፊያ ተመረቀ፤ ለከተማዋ የኢንዱስትሪ አብዮት በር ከፈተ
#ethiopia | ለበርካታ ዓመታት በናፍቆት ሲጠበቅ የነበረው የደብረ ማርቆስ ንጉስ ተክለ ሃይማኖት አውሮፕላን ማረፊያ ራዕዩን ዕውን አድርጎ በዛሬው እለት በይፋ ተመርቆ ሥራ ጀምሯል።
የአውሮፕላን ማረፊያው አገልግሎት መጀመር ለከተማዋና ለአካባቢው ከፍተኛ የኢኮኖሚ መነቃቃትን ይዞ የመጣ ሲሆን በቀጣይም በከተማዋ ላይ ትልቅ የኢንዱስትሪ አብዮት ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ መደበኛ የሥራ መጀመሪያ ከዚህ ቀደም ተቀዛቅዞ የነበረውን የከተማዋን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማነቃቃት አልሚ ባለሀብቶች ያለምንም ስጋት መጥተው እንዲያለሙ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።
ከአሚኮ እንደሰማነው ከሆነ በአውሮፕላን ማረፊያው የሙከራ በረራ ወቅት ትልልቅ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች መምጣት የጀመሩ ሲሆን አሁን ደግሞ የውጭ ባለሀብቶችም ጭምር መዋዕለ ንዋያቸውን ለማፍሰስ በርከት ብለው መምጣት ጀምረዋል።
ከዚህም ባሻገር የአውሮፕላን ማረፊያው አገልግሎት አምራቾች ምርቶቻቸው ሳይበላሹ በአጭር ጊዜ ለገበያ እንዲያቀርቡ በማስቻል የምርት እጥረትን በዘላቂነት ይረዳል፤ ጥራትንም በእጅጉ ይጨምራል።
ከኢንቨስትመንት ባለፈ የከተማዋን የቱሪዝም ዘርፍና አጠቃላይ ኢኮኖሚ በከፍተኛ ደረጃ የሚያነቃቃው ይህ ዕድል ሰፊ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ይዞ የመጣ በመሆኑ ባለሀብቶች መጥተው በከተማዋ እንዲያለሙ የከተማው አስተዳደር ጥሪውን አቅርቧል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
ቢሻህ በአውሮፕላን ቢሻህ በሎንቺና''
📌የደብረ ማርቆስ አውሮፕላን ማረፊያ ተመረቀ፤ ለከተማዋ የኢንዱስትሪ አብዮት በር ከፈተ
#ethiopia | ለበርካታ ዓመታት በናፍቆት ሲጠበቅ የነበረው የደብረ ማርቆስ ንጉስ ተክለ ሃይማኖት አውሮፕላን ማረፊያ ራዕዩን ዕውን አድርጎ በዛሬው እለት በይፋ ተመርቆ ሥራ ጀምሯል።
የአውሮፕላን ማረፊያው አገልግሎት መጀመር ለከተማዋና ለአካባቢው ከፍተኛ የኢኮኖሚ መነቃቃትን ይዞ የመጣ ሲሆን በቀጣይም በከተማዋ ላይ ትልቅ የኢንዱስትሪ አብዮት ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ መደበኛ የሥራ መጀመሪያ ከዚህ ቀደም ተቀዛቅዞ የነበረውን የከተማዋን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ በማነቃቃት አልሚ ባለሀብቶች ያለምንም ስጋት መጥተው እንዲያለሙ ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።
ከአሚኮ እንደሰማነው ከሆነ በአውሮፕላን ማረፊያው የሙከራ በረራ ወቅት ትልልቅ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች መምጣት የጀመሩ ሲሆን አሁን ደግሞ የውጭ ባለሀብቶችም ጭምር መዋዕለ ንዋያቸውን ለማፍሰስ በርከት ብለው መምጣት ጀምረዋል።
ከዚህም ባሻገር የአውሮፕላን ማረፊያው አገልግሎት አምራቾች ምርቶቻቸው ሳይበላሹ በአጭር ጊዜ ለገበያ እንዲያቀርቡ በማስቻል የምርት እጥረትን በዘላቂነት ይረዳል፤ ጥራትንም በእጅጉ ይጨምራል።
ከኢንቨስትመንት ባለፈ የከተማዋን የቱሪዝም ዘርፍና አጠቃላይ ኢኮኖሚ በከፍተኛ ደረጃ የሚያነቃቃው ይህ ዕድል ሰፊ የኢንቨስትመንት አማራጮችን ይዞ የመጣ በመሆኑ ባለሀብቶች መጥተው በከተማዋ እንዲያለሙ የከተማው አስተዳደር ጥሪውን አቅርቧል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Sponsored by
Surafel
28 days ago
የኢራን አብዮታዊ ዘብ ለቀድሞ ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ካሜኒ ግድያ በቀል እንደሚፈጸም ቃል ገባ
የኢራን አብዮታዊ ዘብ ከፍተኛ አዛዥ የጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ካሜኒ ግድያ በአሜሪካ እና በእስራኤል ላይ የበቀል እርምጃ እንደሚወስድ ቃል ገብተዋል፣ “ከታሪካዊው ትውስታ አይጠፋም” ሲሉ ግድያዉን አዉግዘዋል።ብርጋዴር ጄኔራል አህመድ ቫሂዲ “ፍትህ ሙሉ በሙሉ እንዲረጋገጥ እና ለወንጀለኞቹ፣ በተለይም ለህፃናት ገዳይ የአሜሪካ ጦር፣ ተገቢ ምላሽ እንዲሰጥ” ጥሪ አቅርበዋል።
“የአሜሪካ ወንጀለኛ መሪዎች እና የኢራን አብዮት ጠላቶች በሙሉ እና የተቃውሞ ግንባር በዚህ መለኮታዊ መሪ ላይ በፈሪነት በመገደል፣ የመቋቋም ኃይላችንን ወደ መሬት እንደማያወርዱትማወቅ አለባቸው” ሲሉ ቫሂዲ በሴፓህ የዜና ወኪል ባወጡት መግለጫ ተናግረዋል።“ሰማዕታትን መበቀል እና የጥፋተኞቹን ቅጣት፣ ህጋዊ እና የማይረሳ ጥያቄ ሆኖ ይቀጥላል።” ሲሉ አክለዋል፡፡
የቫሂዲ አስተያየት የተሰደማዉ ካሜኒ ሐሙስ ዕለት በትውልድ ከተማቸው ማሽሃድ ከተቀበሩ በኋላ ነው፣ የካሜኒ አራት የቤተሰብ አባላት በአሜሪካ እና በእስራኤል የአየር ጥቃት ከሞቱ ከአራት ወራት በኋላ የቀብር ስነስርዓታቸዉ ተፈጽሟል።የኢራን ሚዲያዎች 43 ሚሊዮን ሰዎች የመሪውን የቀብር ሥነ ሥርዓት እንደተከታተሉ ዘግበዋል።
የኢራን ሚዲያዎች እንደዘገቡት ከ41 እስከ 43 ሚሊዮን የሚደርሱ ሰዎች በስድስት ቀናት ውስጥ የቀድሞ የኢራን ጠቅላይ መሪ አሊ ካሜኒ የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ተሳትፈዋል።የኢራን ፕሬስ ቲቪ የካሜኒ የቀብር ሥነ ሥርዓትን “በዓለም ላይ እስካሁን ካየናቸው ትላልቅ ሰልፎች” ሲል ጠርቶታል። ሥነ ሥርዓቱ የተካሄደው በአምስት ከተሞች ማለትም ቴህራን፣ ኩም፣ ናጃፍ፣ ካርባላ እና ማሽሃድ ነው።
Dagu
Addis_News
Addis_News
የኢራን አብዮታዊ ዘብ ከፍተኛ አዛዥ የጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ካሜኒ ግድያ በአሜሪካ እና በእስራኤል ላይ የበቀል እርምጃ እንደሚወስድ ቃል ገብተዋል፣ “ከታሪካዊው ትውስታ አይጠፋም” ሲሉ ግድያዉን አዉግዘዋል።ብርጋዴር ጄኔራል አህመድ ቫሂዲ “ፍትህ ሙሉ በሙሉ እንዲረጋገጥ እና ለወንጀለኞቹ፣ በተለይም ለህፃናት ገዳይ የአሜሪካ ጦር፣ ተገቢ ምላሽ እንዲሰጥ” ጥሪ አቅርበዋል።
“የአሜሪካ ወንጀለኛ መሪዎች እና የኢራን አብዮት ጠላቶች በሙሉ እና የተቃውሞ ግንባር በዚህ መለኮታዊ መሪ ላይ በፈሪነት በመገደል፣ የመቋቋም ኃይላችንን ወደ መሬት እንደማያወርዱትማወቅ አለባቸው” ሲሉ ቫሂዲ በሴፓህ የዜና ወኪል ባወጡት መግለጫ ተናግረዋል።“ሰማዕታትን መበቀል እና የጥፋተኞቹን ቅጣት፣ ህጋዊ እና የማይረሳ ጥያቄ ሆኖ ይቀጥላል።” ሲሉ አክለዋል፡፡
የቫሂዲ አስተያየት የተሰደማዉ ካሜኒ ሐሙስ ዕለት በትውልድ ከተማቸው ማሽሃድ ከተቀበሩ በኋላ ነው፣ የካሜኒ አራት የቤተሰብ አባላት በአሜሪካ እና በእስራኤል የአየር ጥቃት ከሞቱ ከአራት ወራት በኋላ የቀብር ስነስርዓታቸዉ ተፈጽሟል።የኢራን ሚዲያዎች 43 ሚሊዮን ሰዎች የመሪውን የቀብር ሥነ ሥርዓት እንደተከታተሉ ዘግበዋል።
የኢራን ሚዲያዎች እንደዘገቡት ከ41 እስከ 43 ሚሊዮን የሚደርሱ ሰዎች በስድስት ቀናት ውስጥ የቀድሞ የኢራን ጠቅላይ መሪ አሊ ካሜኒ የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ተሳትፈዋል።የኢራን ፕሬስ ቲቪ የካሜኒ የቀብር ሥነ ሥርዓትን “በዓለም ላይ እስካሁን ካየናቸው ትላልቅ ሰልፎች” ሲል ጠርቶታል። ሥነ ሥርዓቱ የተካሄደው በአምስት ከተሞች ማለትም ቴህራን፣ ኩም፣ ናጃፍ፣ ካርባላ እና ማሽሃድ ነው።
Dagu
Addis_News
Addis_News
1 month ago
የ5ቱ ዓመታት ገፆች፤ ታሪክ ተሰርቷል!
***************
የዘመናት ታሪክ ገፆች ሲገለጡ የአንድ ሀገር ዕጣ ፈንታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከስር መሰረቱ ተነቅንቆ አዲስ መልክ የሚይዝበት አጋጣሚ እጅግ ጥቂት ነው።
ላለፉት አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ የተዘረጉትን የልማትና የለውጥ ገፆች ስናነብ፣ የተካሄደው ጉዞ "ለውጥ" ወይም "ሪፎርም" በሚሉ ቃላት ብቻ የሚገለፅ አይደለም።
ይልቁንም ከሪፎርም ባሻገር ወደ አብዮት የተጠጋ፣ የኢትዮጵያን አጠቃላይ ገፅታ የለወጠና ሥር ነቀል መዋቅራዊ ሽግግርን ያረጋገጠ ታላቅ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው።
በዓለም የኢኮኖሚ ታሪክ ውስጥ፣ ጥቂት ሀገራት ብቻ ናቸው በፈጣን ጊዜ ውስጥ አስደናቂ የሚባል የዕድገት ዝላይ (Leapfrogging) ማሳየት የቻሉት።
ቻይና በሰላሳ ዓመታት ያመጣችው መዋቅራዊ ለውጥ፣ ደቡብ ኮሪያ በጄኔራል ፓርክ ቹንግ ሂ ቆራጥ መሪነት የተጓዘችው የኢንዱስትሪ ሽግግር፣ እንዲሁም ታይዋን ያስመዘገበችው የቴክኖሎጂ ስኬት ሁሌም በምሳሌነት ይነሳሉ።
ነገር ግን፣ ኢትዮጵያ በአምስት ዓመታት ውስጥ ብቻ እያስመዘገበች ያለው የለውጥ ፍጥነትና ስፋት እጅግ አስደናቂ ሆኖ እናገኘዋለን። በጠንካራና ቁርጠኛ አመራር እየተመራች፣ ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ ወደ ታላቅነት የምታደርገው ሽግግር ከግምት በላይ የሆነ ጉዞ ነው።
ይህ ተአምራዊ የሚባል ዝላይ በገሃድ ከሚታይባቸው መስኮች አንዱ ግብርና ነው። ለዘመናት በልመናና በስንዴ ዕርዳታ ጥገኝነት ስትታወቅ የነበረችው ሀገር፣ በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ የምግብ ሉዓላዊነቷን አረጋግጣ ወደ ስንዴ ላኪነት መሸጋገሯ እውነተኛ የኢኮኖሚ "ሉዓላዊነት" ማረጋገጫ ነው።
በተጠናከረ የኩታገጠም እና የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት፣ የስንዴ ምርት በ2017 በጀት ዓመት 280 ሚሊዮን ኩንታል መድረሱ የዚህ ፈጣን ስኬት ማሳያ ነው። ኢኮኖሚው ከአንድ ወጥ ጥገኝነት ወጥቶ ወደ ብዝሃ-ዘርፍ ልማት በማደግ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገቡ በጥቂት ሀገራት ብቻ የሚሳካ ታላቅ ድል ነው።
የለውጡ ጅረት በግብርና ብቻ አልተገታም። በአረንጓዴ ኢኮኖሚው ዘርፍ፣ እስከ ኮፕ ጉባኤ ድረስ ከ65 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል በእስካሁኑ ጉዞ የሀገራችንን የደን ሽፋን ከ17 በመቶ ወደ 23.6 በመቶ ከፍ በማድረግ ኢትዮጵያ የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ መከላከያ ተምሳሌት ሆናለች።
በውሃና ኃይል (ኤነርጂ) ሽግግር፣ ታላቁን የሕዳሴ ግድብን ጨምሮ በርካታ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ የኃይል ማመንጨት አቅምን ወደ 9,554 ሜጋ ዋት አሳድጋለች።
በተለይም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን (EV) በመጠቀም የነዳጅ ጥገኝነትን መቀነስና የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ሌላው የዘርፉ ስኬት ነው።
በከተማ ልማት ዘርፍም የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች ከተሞቻችንን የውበት፣ የንፅህናና የሥልጣኔ ማዕከል አድርገዋቸዋል።
በኢንዱስትሪና በዲጂታል ዘርፍ፣ "ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄንና የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን በመተግበር፣ እንዲሁም ከ58 ሚሊዮን በላይ የቴሌብር ተጠቃሚዎችን በማፍራትና የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ቁጥር በማስፋፋት ዘመኑን የዋጀ የቴክኖሎጂ አብዮት ተካሂዷል።
በማዕድን ዘርፍ የተከናወኑት የሪፎርም ስራዎችም እንዲሁ እጅግ አስደናቂ ናቸው። የኮንትሮባንድ ንግድን በመግታትና የወርቅ ምርትን ከ3.3 ቶን ወደ 38.8 ቶን በማሳደግ፣ ዘርፉ የውጭ ምንዛሬ ግኝታችንን ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሯል።
የቱሪዝም ዘርፉም በተመሳሳይ በገበታ ለሀገርና በሌሎች የቱሪዝም መዳረሻዎች ልማት፣ የውጭ ቱሪስት ፍሰትን ወደ 1.3 ሚሊዮን በማድረስ ሀገራችንን ወደ ተፈጥሯዊ የቱሪዝም መዳረሻነት ቀይሯታል።
በዲፕሎማሲውና በፖለቲካው መስክም የተመዘገበው ስኬት የሚያስደምም ነው። ኢትዮጵያ የነበሩባትን ውስብስብ ጫናዎች በብልሃት ተቋቁማ፣ የውጭ ፖሊሲዋን ሚዛናዊ በማድረግ ወደ ብሪክስ (BRICS) አባልነት መቀላቀሏ ዓለም አቀፍ ተደማጭነቷን አረጋግጧል።
በድምሩ ሲታይ እነዚህ ሁሉ ስኬቶች በአንድ ላይ ሲገመገሙ ኢትዮጵያ በእርግጥም ተአምራዊ በሚባል የለውጥ ጎዳና ላይ ትገኛለች። ይህን ሁሉ ውስብስብ ሀገራዊ፣ ቀጠናዊና ዓለም አቀፍ ጫና ተቋቁሞ ማሳካት የቻለው "መፍጠር፣ መፍጠንና መዝለል" በሚል መርህ የተቃኘው የፖለቲካ ኢኮኖሚ ሥርዓትና ቆራጥ አመራር በመኖሩ ነው።
ይህ እንደ አዲስ የጀመረው የለውጥና የዝላይ ጉዞ በአጭር ጊዜ ከግብ ሲደርስ፣ ኢትዮጵያ በብልፅግና ማማ ላይ ደምቃ በመውጣት የአፍሪካዊ ተምሳሌትነትን አልፋ የዓለም የብልፅግና ተምሳሌት እንደምትሆን አያጠራጥርም።
የ5ቱ ዓመታት ገፆች፣ የዚህችን ታላቅ ሀገር አይበገሬነትና ትንሣኤ በደማቁ የፃፉ ህያው የድል ድርሳናት ናቸው!
በአዶኒያስ ወ/አረጋይ
#ethiopiarising #historyinthemakinget #foodsovereigntyet #greenlegacyethiopia #ethiopiainbrics
***************
የዘመናት ታሪክ ገፆች ሲገለጡ የአንድ ሀገር ዕጣ ፈንታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከስር መሰረቱ ተነቅንቆ አዲስ መልክ የሚይዝበት አጋጣሚ እጅግ ጥቂት ነው።
ላለፉት አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ የተዘረጉትን የልማትና የለውጥ ገፆች ስናነብ፣ የተካሄደው ጉዞ "ለውጥ" ወይም "ሪፎርም" በሚሉ ቃላት ብቻ የሚገለፅ አይደለም።
ይልቁንም ከሪፎርም ባሻገር ወደ አብዮት የተጠጋ፣ የኢትዮጵያን አጠቃላይ ገፅታ የለወጠና ሥር ነቀል መዋቅራዊ ሽግግርን ያረጋገጠ ታላቅ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው።
በዓለም የኢኮኖሚ ታሪክ ውስጥ፣ ጥቂት ሀገራት ብቻ ናቸው በፈጣን ጊዜ ውስጥ አስደናቂ የሚባል የዕድገት ዝላይ (Leapfrogging) ማሳየት የቻሉት።
ቻይና በሰላሳ ዓመታት ያመጣችው መዋቅራዊ ለውጥ፣ ደቡብ ኮሪያ በጄኔራል ፓርክ ቹንግ ሂ ቆራጥ መሪነት የተጓዘችው የኢንዱስትሪ ሽግግር፣ እንዲሁም ታይዋን ያስመዘገበችው የቴክኖሎጂ ስኬት ሁሌም በምሳሌነት ይነሳሉ።
ነገር ግን፣ ኢትዮጵያ በአምስት ዓመታት ውስጥ ብቻ እያስመዘገበች ያለው የለውጥ ፍጥነትና ስፋት እጅግ አስደናቂ ሆኖ እናገኘዋለን። በጠንካራና ቁርጠኛ አመራር እየተመራች፣ ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ ወደ ታላቅነት የምታደርገው ሽግግር ከግምት በላይ የሆነ ጉዞ ነው።
ይህ ተአምራዊ የሚባል ዝላይ በገሃድ ከሚታይባቸው መስኮች አንዱ ግብርና ነው። ለዘመናት በልመናና በስንዴ ዕርዳታ ጥገኝነት ስትታወቅ የነበረችው ሀገር፣ በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ የምግብ ሉዓላዊነቷን አረጋግጣ ወደ ስንዴ ላኪነት መሸጋገሯ እውነተኛ የኢኮኖሚ "ሉዓላዊነት" ማረጋገጫ ነው።
በተጠናከረ የኩታገጠም እና የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት፣ የስንዴ ምርት በ2017 በጀት ዓመት 280 ሚሊዮን ኩንታል መድረሱ የዚህ ፈጣን ስኬት ማሳያ ነው። ኢኮኖሚው ከአንድ ወጥ ጥገኝነት ወጥቶ ወደ ብዝሃ-ዘርፍ ልማት በማደግ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገቡ በጥቂት ሀገራት ብቻ የሚሳካ ታላቅ ድል ነው።
የለውጡ ጅረት በግብርና ብቻ አልተገታም። በአረንጓዴ ኢኮኖሚው ዘርፍ፣ እስከ ኮፕ ጉባኤ ድረስ ከ65 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል በእስካሁኑ ጉዞ የሀገራችንን የደን ሽፋን ከ17 በመቶ ወደ 23.6 በመቶ ከፍ በማድረግ ኢትዮጵያ የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ መከላከያ ተምሳሌት ሆናለች።
በውሃና ኃይል (ኤነርጂ) ሽግግር፣ ታላቁን የሕዳሴ ግድብን ጨምሮ በርካታ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ የኃይል ማመንጨት አቅምን ወደ 9,554 ሜጋ ዋት አሳድጋለች።
በተለይም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን (EV) በመጠቀም የነዳጅ ጥገኝነትን መቀነስና የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ሌላው የዘርፉ ስኬት ነው።
በከተማ ልማት ዘርፍም የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች ከተሞቻችንን የውበት፣ የንፅህናና የሥልጣኔ ማዕከል አድርገዋቸዋል።
በኢንዱስትሪና በዲጂታል ዘርፍ፣ "ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄንና የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን በመተግበር፣ እንዲሁም ከ58 ሚሊዮን በላይ የቴሌብር ተጠቃሚዎችን በማፍራትና የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ቁጥር በማስፋፋት ዘመኑን የዋጀ የቴክኖሎጂ አብዮት ተካሂዷል።
በማዕድን ዘርፍ የተከናወኑት የሪፎርም ስራዎችም እንዲሁ እጅግ አስደናቂ ናቸው። የኮንትሮባንድ ንግድን በመግታትና የወርቅ ምርትን ከ3.3 ቶን ወደ 38.8 ቶን በማሳደግ፣ ዘርፉ የውጭ ምንዛሬ ግኝታችንን ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሯል።
የቱሪዝም ዘርፉም በተመሳሳይ በገበታ ለሀገርና በሌሎች የቱሪዝም መዳረሻዎች ልማት፣ የውጭ ቱሪስት ፍሰትን ወደ 1.3 ሚሊዮን በማድረስ ሀገራችንን ወደ ተፈጥሯዊ የቱሪዝም መዳረሻነት ቀይሯታል።
በዲፕሎማሲውና በፖለቲካው መስክም የተመዘገበው ስኬት የሚያስደምም ነው። ኢትዮጵያ የነበሩባትን ውስብስብ ጫናዎች በብልሃት ተቋቁማ፣ የውጭ ፖሊሲዋን ሚዛናዊ በማድረግ ወደ ብሪክስ (BRICS) አባልነት መቀላቀሏ ዓለም አቀፍ ተደማጭነቷን አረጋግጧል።
በድምሩ ሲታይ እነዚህ ሁሉ ስኬቶች በአንድ ላይ ሲገመገሙ ኢትዮጵያ በእርግጥም ተአምራዊ በሚባል የለውጥ ጎዳና ላይ ትገኛለች። ይህን ሁሉ ውስብስብ ሀገራዊ፣ ቀጠናዊና ዓለም አቀፍ ጫና ተቋቁሞ ማሳካት የቻለው "መፍጠር፣ መፍጠንና መዝለል" በሚል መርህ የተቃኘው የፖለቲካ ኢኮኖሚ ሥርዓትና ቆራጥ አመራር በመኖሩ ነው።
ይህ እንደ አዲስ የጀመረው የለውጥና የዝላይ ጉዞ በአጭር ጊዜ ከግብ ሲደርስ፣ ኢትዮጵያ በብልፅግና ማማ ላይ ደምቃ በመውጣት የአፍሪካዊ ተምሳሌትነትን አልፋ የዓለም የብልፅግና ተምሳሌት እንደምትሆን አያጠራጥርም።
የ5ቱ ዓመታት ገፆች፣ የዚህችን ታላቅ ሀገር አይበገሬነትና ትንሣኤ በደማቁ የፃፉ ህያው የድል ድርሳናት ናቸው!
በአዶኒያስ ወ/አረጋይ
#ethiopiarising #historyinthemakinget #foodsovereigntyet #greenlegacyethiopia #ethiopiainbrics
1 month ago
ሰላም፤ እንደምን አደራችሁ?
ሀገራዊ ምክክር የኢትዮጵያ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ …
ታሪክ የሰዎች ርምጃ ውጤት ብቻ አይደለም፤ የተወሰኑ ውሳኔዎች እና ያልተወሰኑ ውሳኔዎች ድምር ነው። አንዳንድ ሀገራት በጦርነት ይቀየራሉ፤ አንዳንዶቹ በአብዮት፤ ሌሎች ደግሞ በሕገ መንግሥት። ነገር ግን እጅግ የተረጋጉና ዘላቂ ለውጦች የሚወለዱት ከመሣሪያ ጩኸት ሳይሆን ከውይይት ጸጥታ ውስጥ ነው። የመድፍ ድምፅ ጦርነትን ሊያቆም ይችላል፤ የልብ ውይይት ግን ጥላቻን ያቆማል።
ኢትዮጵያ ዛሬ በምክክር ችግሮችን የሚፈታ ቁርሾና ጥላቻን እንዲሁም የዘመናት የህዝብ ጥያቄዎችን በምክክር የመፍታት ታሪካዊ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የሚካሄደው የሀገራዊ ምክክር ዋና ጉባኤ የመደበኛ የሥራ መርሐ ግብር አይደለም፤ ኢትዮጵያ ካለፈችባቸው አስቸጋሪ ዘመናት በኋላ ራሷን በአዲስ መንገድ ለመግለጽ የምታደርገው የታሪክ ሙከራ ነው።
የሰላም ተመራማሪዎችና ፈላስፋዎች፥ “ፖለቲካ የሚጀምረው ሰዎች እርስ በርስ ሲነጋገሩ ነው” ይላሉ። በዚህ አባባል ውስጥ የተደበቀው እውነት አንድ ነው፤ ውይይት የዴሞክራሲ ማስዋቢያ ሳይሆን መሠረቱ ነው። ሀገር የሚገነባው ሰዎች ሲመሳሰሉ ሳይሆን ልዩነታቸውን በሥርዓት ሲያስተዳድሩ ነው።
ኢትዮጵያም ዛሬ በታሪኳ አንድ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ለብዙ ዓመታት ያጋጠሟትን ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ እና ደኅንነታዊ ፈተናዎች በአጠቃላይ እየገመገመች፣ ወደ ተሻለ የጋራ ነገ ለመሻገር የምታደርገው ጥረት አዲስ ተስፋ ሰንቋል።
በዚህ መንገድ ውስጥ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሚያካሂደው ዋና ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሀገርን የወደፊት አቅጣጫ የሚወስን ታሪካዊ ክስተት እንደሚሆን ይጠበቃል።
ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የሚካሄደው ይህ ጉባኤ፥ ከ4 ሺህ በላይ ሰዎችን ያሳትፋል።
ኢትዮጵያ የራሷ ታሪክ፣ የራሷ ማህበራዊ መዋቅር እና የራሷ የፖለቲካ ተሞክሮ አላት። ስለዚህ መፍትሔውም ከሌሎች የተገለበጠ ሳይሆን ከኢትዮጵያውያን ልምድ፣ ባህል እና የጋራ እሴቶች ይመነጫል።
በዚህ ረገድ የባህላዊ የእርቅ ሥርዓቶችን ከዘመናዊ የሕግ እና የዴሞክራሲ መርሆዎች ጋር በጥበብ ማጣመር ትልቅ ዕድል ይፈጥራል። የአካባቢ ሽማግሌዎች ጥበብ፣ የሃይማኖት ተቋማት የሰላም አስተምህሮ፣ የሕግ የበላይነት እና የዜጎች እኩልነት ሲጣመሩ ዘላቂ ሰላም የሚያመጣ መሠረት ይጥላሉ።
ለዚህ ነው ምክክር የድል መድረክ ሳይሆን የመግባባት መድረክ ነው የሚባለው። ሀገራዊ ምክክር ማለት አንዱ ወገን የሚያሸንፍበት ሌላው የሚሸነፍበት የፖለቲካ ውድድር አይደለም። የምክክሩ እውነተኛ ድል “ማን አሸነፈ?” በሚለው ሳይሆን “ሀገር ምን አተረፈች?” በሚለው ይለካል።
የፖለቲካ ፈላስፋው ዩርገን ሀበርማስ እንደሚለው፥ የሕዝብ ውይይት ዓላማው ተቃዋሚን ማሸነፍ ሳይሆን የተሻለ እውነትን በጋራ መፈለግ ነው። ይህ መርህ ለኢትዮጵያ የዛሬ ፖለቲካ በተለይ ትልቅ ትርጉም አለው።
በታሪክ ውስጥ አንዳንድ ቀናት የቀን መቁጠሪያ ቁጥር ብቻ አይደሉም፤ የትውልድ እጣ ፈንታ የሚወሰንባቸው መለያ ምልክቶች ናቸው። የሀገራዊ ምክክሩ ጉባኤም እንዲሁ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
የዛሬው ውይይት የነገውን ታሪክ ይጽፋል። የዛሬው መደማመጥ የነገውን መተማመን ይገነባል። የዛሬው ማስተዋል የነገውን ሰላም ይወልዳል።
ኢትዮጵያ ብዙ ድሎችን በጦር ሜዳ አስመዝግባለች። አሁን ግን የምትፈልገው ታላቁ ድል በጠረጴዛ ዙሪያ የሚደረግ ውይይትን ነው። ምክንያቱም ጦርነት ድንበር ሊጠብቅ ይችላል፤ ውይይት ግን ሀገርን ይጠብቃል።
ብዙ ጊዜ ታሪክ የሚያስታውሰው ጩኸትን ሳይሆን ድምፅ ያገኘውን ጥበብ ነው። የሀገራዊ ምክክሩ ስኬትም ሁሉም ተናገሩ በሚለው ሳይሆን፣ ሁሉም ተደምጠዋል በሚለው ይለካል። ከዚያ የሚወለደው ሰላም የአንድ መንግሥት ስኬት ብቻ ሳይሆን የአንድ ትውልድ አሻራ ይሆናል።
ሀገራዊ ምክክር የኢትዮጵያ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ …
ታሪክ የሰዎች ርምጃ ውጤት ብቻ አይደለም፤ የተወሰኑ ውሳኔዎች እና ያልተወሰኑ ውሳኔዎች ድምር ነው። አንዳንድ ሀገራት በጦርነት ይቀየራሉ፤ አንዳንዶቹ በአብዮት፤ ሌሎች ደግሞ በሕገ መንግሥት። ነገር ግን እጅግ የተረጋጉና ዘላቂ ለውጦች የሚወለዱት ከመሣሪያ ጩኸት ሳይሆን ከውይይት ጸጥታ ውስጥ ነው። የመድፍ ድምፅ ጦርነትን ሊያቆም ይችላል፤ የልብ ውይይት ግን ጥላቻን ያቆማል።
ኢትዮጵያ ዛሬ በምክክር ችግሮችን የሚፈታ ቁርሾና ጥላቻን እንዲሁም የዘመናት የህዝብ ጥያቄዎችን በምክክር የመፍታት ታሪካዊ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የሚካሄደው የሀገራዊ ምክክር ዋና ጉባኤ የመደበኛ የሥራ መርሐ ግብር አይደለም፤ ኢትዮጵያ ካለፈችባቸው አስቸጋሪ ዘመናት በኋላ ራሷን በአዲስ መንገድ ለመግለጽ የምታደርገው የታሪክ ሙከራ ነው።
የሰላም ተመራማሪዎችና ፈላስፋዎች፥ “ፖለቲካ የሚጀምረው ሰዎች እርስ በርስ ሲነጋገሩ ነው” ይላሉ። በዚህ አባባል ውስጥ የተደበቀው እውነት አንድ ነው፤ ውይይት የዴሞክራሲ ማስዋቢያ ሳይሆን መሠረቱ ነው። ሀገር የሚገነባው ሰዎች ሲመሳሰሉ ሳይሆን ልዩነታቸውን በሥርዓት ሲያስተዳድሩ ነው።
ኢትዮጵያም ዛሬ በታሪኳ አንድ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ለብዙ ዓመታት ያጋጠሟትን ፖለቲካዊ፣ ማኅበራዊ እና ደኅንነታዊ ፈተናዎች በአጠቃላይ እየገመገመች፣ ወደ ተሻለ የጋራ ነገ ለመሻገር የምታደርገው ጥረት አዲስ ተስፋ ሰንቋል።
በዚህ መንገድ ውስጥ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሚያካሂደው ዋና ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የሀገርን የወደፊት አቅጣጫ የሚወስን ታሪካዊ ክስተት እንደሚሆን ይጠበቃል።
ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የሚካሄደው ይህ ጉባኤ፥ ከ4 ሺህ በላይ ሰዎችን ያሳትፋል።
ኢትዮጵያ የራሷ ታሪክ፣ የራሷ ማህበራዊ መዋቅር እና የራሷ የፖለቲካ ተሞክሮ አላት። ስለዚህ መፍትሔውም ከሌሎች የተገለበጠ ሳይሆን ከኢትዮጵያውያን ልምድ፣ ባህል እና የጋራ እሴቶች ይመነጫል።
በዚህ ረገድ የባህላዊ የእርቅ ሥርዓቶችን ከዘመናዊ የሕግ እና የዴሞክራሲ መርሆዎች ጋር በጥበብ ማጣመር ትልቅ ዕድል ይፈጥራል። የአካባቢ ሽማግሌዎች ጥበብ፣ የሃይማኖት ተቋማት የሰላም አስተምህሮ፣ የሕግ የበላይነት እና የዜጎች እኩልነት ሲጣመሩ ዘላቂ ሰላም የሚያመጣ መሠረት ይጥላሉ።
ለዚህ ነው ምክክር የድል መድረክ ሳይሆን የመግባባት መድረክ ነው የሚባለው። ሀገራዊ ምክክር ማለት አንዱ ወገን የሚያሸንፍበት ሌላው የሚሸነፍበት የፖለቲካ ውድድር አይደለም። የምክክሩ እውነተኛ ድል “ማን አሸነፈ?” በሚለው ሳይሆን “ሀገር ምን አተረፈች?” በሚለው ይለካል።
የፖለቲካ ፈላስፋው ዩርገን ሀበርማስ እንደሚለው፥ የሕዝብ ውይይት ዓላማው ተቃዋሚን ማሸነፍ ሳይሆን የተሻለ እውነትን በጋራ መፈለግ ነው። ይህ መርህ ለኢትዮጵያ የዛሬ ፖለቲካ በተለይ ትልቅ ትርጉም አለው።
በታሪክ ውስጥ አንዳንድ ቀናት የቀን መቁጠሪያ ቁጥር ብቻ አይደሉም፤ የትውልድ እጣ ፈንታ የሚወሰንባቸው መለያ ምልክቶች ናቸው። የሀገራዊ ምክክሩ ጉባኤም እንዲሁ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
የዛሬው ውይይት የነገውን ታሪክ ይጽፋል። የዛሬው መደማመጥ የነገውን መተማመን ይገነባል። የዛሬው ማስተዋል የነገውን ሰላም ይወልዳል።
ኢትዮጵያ ብዙ ድሎችን በጦር ሜዳ አስመዝግባለች። አሁን ግን የምትፈልገው ታላቁ ድል በጠረጴዛ ዙሪያ የሚደረግ ውይይትን ነው። ምክንያቱም ጦርነት ድንበር ሊጠብቅ ይችላል፤ ውይይት ግን ሀገርን ይጠብቃል።
ብዙ ጊዜ ታሪክ የሚያስታውሰው ጩኸትን ሳይሆን ድምፅ ያገኘውን ጥበብ ነው። የሀገራዊ ምክክሩ ስኬትም ሁሉም ተናገሩ በሚለው ሳይሆን፣ ሁሉም ተደምጠዋል በሚለው ይለካል። ከዚያ የሚወለደው ሰላም የአንድ መንግሥት ስኬት ብቻ ሳይሆን የአንድ ትውልድ አሻራ ይሆናል።
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በአያቶላ ሆሚኒ የቀብር ስነስርአት 3 ልጆቻቸው ቢገኙም ሞጅታባ ሆሚኒ ግን እስካሁን አልታዩም፡፡ የቀድሞው የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላ ሆሚኒ የቀብር ስነስርአት ሁለተኛ ቀን ዛሬ የተከናወነ ሲሆን በርካታ ህዝብ ተገኝቶ አሸኛኘት አድርጎላቸዋል፡፡
በቴሄራን በሚገኘው ግራንድ ሞሳይላ ኮምፕሌክስ ውስጥ በተከናወነው ይህ ስነስርአት ዋነኛ ፕሮግራሙ ፀሎት ማድረግ ብቻ ነበር፡፡ በዚህ ፀሎት ላይ የአያቶላው ልጆች ከሆኑት ውስጥ መሱድ፣ ሙስጠፋና መይሳም መገኘታቸውን የኢራን ቴሌቪዥን ዘግቧል፡፡ ይሁንና የአባታቸውን ስልጣን የተኩት የ56 አመቱ ሞጅታባ ሆሚኒ አልታዩም፡፡
በፕሮግራሙ ላይ የኢራን ፕሬዝደንት የሆኑት መሱድ ፔስኪሺያን፣ የፓርላማ አፈጉባኤና ዋና ተደራዳሪው መሀመድ ባከር ጋሊባፍ፣ የኢራን አብዮታዊ ዘብ የቁድስ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ጄኔራል ኢስማኤሊ ቃኒ እና ሌሎችም ከፍተኛ የአገሪቱ ባለስልጣናት ተገኝተው ነበር፡፡ የአያቶላው አስከሬን ወደዚህ ቦታ የመጣው አርብ እለት ሲሆን ዛሬ ከፀሎት በኋላ ዋናው የሽኝት ፕሮግራም ወደሚደረግበት የቴሄራን አብዮት አደባባይ ይወሰዳል፡፡ ለቀብሩ ስነስርአት በሚል ዛሬና ነገ የመንግስትም ሆኑ የግል መስሪያ ቤቶች እንዲዘጉ ተደርገዋል፡፡
በነገው የየሽኝት ፕሮግራም ከ15 እስከ 20 ሚሊዮን የሚሆን ህዝብ ይገኛል የሚል ግምት እንዳላቸው የኢራን ባለስልጣናት በመናገር ላይ ናቸው፡፡ ለዝግጅቲ ሲባልም የኢራን ቀይ ጨረቃ ማህበር በቴሄራን ዋና ዋና አደባባዮችና ፓርኮች ላይ ከ400 በላይ ድንኳን ጥሏል፡፡
በቴሄራን በሚገኘው ግራንድ ሞሳይላ ኮምፕሌክስ ውስጥ በተከናወነው ይህ ስነስርአት ዋነኛ ፕሮግራሙ ፀሎት ማድረግ ብቻ ነበር፡፡ በዚህ ፀሎት ላይ የአያቶላው ልጆች ከሆኑት ውስጥ መሱድ፣ ሙስጠፋና መይሳም መገኘታቸውን የኢራን ቴሌቪዥን ዘግቧል፡፡ ይሁንና የአባታቸውን ስልጣን የተኩት የ56 አመቱ ሞጅታባ ሆሚኒ አልታዩም፡፡
በፕሮግራሙ ላይ የኢራን ፕሬዝደንት የሆኑት መሱድ ፔስኪሺያን፣ የፓርላማ አፈጉባኤና ዋና ተደራዳሪው መሀመድ ባከር ጋሊባፍ፣ የኢራን አብዮታዊ ዘብ የቁድስ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ጄኔራል ኢስማኤሊ ቃኒ እና ሌሎችም ከፍተኛ የአገሪቱ ባለስልጣናት ተገኝተው ነበር፡፡ የአያቶላው አስከሬን ወደዚህ ቦታ የመጣው አርብ እለት ሲሆን ዛሬ ከፀሎት በኋላ ዋናው የሽኝት ፕሮግራም ወደሚደረግበት የቴሄራን አብዮት አደባባይ ይወሰዳል፡፡ ለቀብሩ ስነስርአት በሚል ዛሬና ነገ የመንግስትም ሆኑ የግል መስሪያ ቤቶች እንዲዘጉ ተደርገዋል፡፡
በነገው የየሽኝት ፕሮግራም ከ15 እስከ 20 ሚሊዮን የሚሆን ህዝብ ይገኛል የሚል ግምት እንዳላቸው የኢራን ባለስልጣናት በመናገር ላይ ናቸው፡፡ ለዝግጅቲ ሲባልም የኢራን ቀይ ጨረቃ ማህበር በቴሄራን ዋና ዋና አደባባዮችና ፓርኮች ላይ ከ400 በላይ ድንኳን ጥሏል፡፡
1 month ago
የኢትዮጵያ የማዕድን አብዮት - ከ0.2 በመቶ የኢኮኖሚ ድርሻ ወደ ዋነኛ የኢኮኖሚ ሞተርነት
*************************
የኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ ለበርካታ አሥርት ዓመታት በፖሊሲ ክፍተት፣ በሕገ-ወጥ የኮንትሮባንድ ንግድ እና በተደራጀ ብክነት ምክንያት እምቅ አቅሙ ሙሉ በሙሉ ተዘንግቶ ቆይቷል።
ዛሬ ላይ ግን በአዲሱ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ከሀገራችን 5 ዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ በመሆን ታሪካዊ ትንሣኤውን አብስሯል።
ሀገራችን ስትገነባው የቆየችው በመንግሥት ከፍተኛ ወጪ ላይ የተመሠረተ እና ለዕዳ ተጋላጭ ያደረጋት የኢኮኖሚ ሞዴል ፈታኝ ሆኖ መቆየቱ ይታወቃል።
ይህን በማክሮ ኢኮኖሚ አለመረጋጋት፣ በዋጋ ግሽበት እና በውጭ ምንዛሬ እጥረት የተተበተበ ማነቆ በዘላቂነት ለመቅረፍ የተተገበረው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ፣ ማዕድንን ከመረሳት ወደ ብሔራዊ ኢኮኖሚ አንቀሳቃሽነት በውጤታማነት አሸጋግሮታል።
ይህ መዋቅራዊ ለውጥ በመረጃ እና በቁጥር ሲመዘን እጅግ አስደናቂ ሆኖ እናገኘዋለን። በ2010 ዓ.ም የማዕድን ዘርፍ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) የነበረው ድርሻ 0.2 በመቶ ብቻ ነበረ። በ2017 ዓ.ም ይህ ቁጥር የ7 እጥፍ ብልጫ በማሳየት ወደ 1.4 በመቶ ማደግ ችሏል።
በተለይም በወርቅ ምርት እና ኤክስፖርት ላይ የታየው ለውጥ በታሪካችን ወደር የማይገኝለት እመርታ ነው።
ባህላዊ የማዕድን ቁፋሮን ወደ መደበኛ የንግድ ሥርዓት በማስገባት በተደረገው ስኬታማ የፖሊሲ ማሻሻያ፣ የሀገራችን የወርቅ ኤክስፖርት ገቢ ከ100 ሚሊዮን ዶላር ወደ 3.48 ቢሊዮን ዶላር በማደግ የ35 እጥፍ ጭማሪ አስመዝግቧል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በቅርቡ የተገበረው በገበያ ላይ የተመሠረተ የውጭ ምንዛሬ ተመን ሥርዓት ደግሞ አምራቾች ምርታቸውን በመደበኛው የፋይናንስ ሥርዓት እንዲያቀርቡ በማድረግ ለዚህ ስኬት ትልቅ ሞተር ሆኗል።
በሌላ በኩል "ኢትዮጵያ ታምርት" በተሰኘው ሀገራዊ ንቅናቄ የማዕድን ዘርፉ ከማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪው ጋር በጥብቅ በመተሳሰሩ፣ ገቢ ምርትን በሀገር ውስጥ በመተካት ከፍተኛ ድል ተመዝግቧል።
ለአብነት ያህል የአርጆ የድንጋይ ከሰል ማበልጸጊያ ፋብሪካን መመልከት በቂ ነው። ይህ ዘመናዊ ፋብሪካ በየዓመቱ የከሰል ድንጋይ ለማስገባት ይወጣ የነበረውን ከ300 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ምርት እንዲተካ አስችሏል።
በተመሳሳይ የኖራ ድንጋይ የሀገር ውስጥ ምርት ድርሻ ከ17 በመቶ ወደ 75 በመቶ ከፍ ማለቱ፣ እንደ ለሚ ናሽናል ሲሚንቶ እና ሙገር የመሳሰሉ ግዙፍ ፋብሪካዎች የማምረቻ ወጪያቸውን በከፍተኛ ደረጃ እንዲቀንሱ አድርጓል።
ይህ በማዕድን ዘርፉ የታየው ዕድገት በማክሮ ኢኮኖሚው ላይ ብቻ ሳይሆን፣ ሰፊ ማኅበራዊ ፋይዳንም አምጥቷል።
በአሁኑ ወቅት ኢንዱስትሪው ከ1 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎቻችን ቀጥተኛ የሥራ ዕድል ፈጥሯል። ከ4 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን ደግሞ ኑሯቸውን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በዚህ ዘርፍ ላይ መስርተዋል።
በአጠቃላይ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው የማዕድን ዘርፉን ከድቅድቅ ጨለማ አውጥቶ የሀገራችንን የኢንዱስትሪ ሽግግር የሚያፋጥን ሞተር አድርጎታል።
ይህ የማዕድን ዘርፍ ስኬት ዘርፉ የኢትዮጵያን የብልጽግና ጉዞ ዕውን የሚያደርግ አስተማማኝ ምሰሶ መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #mining #madeinethiopia #economicreform #goldexport #ebc
*************************
የኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ ለበርካታ አሥርት ዓመታት በፖሊሲ ክፍተት፣ በሕገ-ወጥ የኮንትሮባንድ ንግድ እና በተደራጀ ብክነት ምክንያት እምቅ አቅሙ ሙሉ በሙሉ ተዘንግቶ ቆይቷል።
ዛሬ ላይ ግን በአዲሱ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ከሀገራችን 5 ዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ በመሆን ታሪካዊ ትንሣኤውን አብስሯል።
ሀገራችን ስትገነባው የቆየችው በመንግሥት ከፍተኛ ወጪ ላይ የተመሠረተ እና ለዕዳ ተጋላጭ ያደረጋት የኢኮኖሚ ሞዴል ፈታኝ ሆኖ መቆየቱ ይታወቃል።
ይህን በማክሮ ኢኮኖሚ አለመረጋጋት፣ በዋጋ ግሽበት እና በውጭ ምንዛሬ እጥረት የተተበተበ ማነቆ በዘላቂነት ለመቅረፍ የተተገበረው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ፣ ማዕድንን ከመረሳት ወደ ብሔራዊ ኢኮኖሚ አንቀሳቃሽነት በውጤታማነት አሸጋግሮታል።
ይህ መዋቅራዊ ለውጥ በመረጃ እና በቁጥር ሲመዘን እጅግ አስደናቂ ሆኖ እናገኘዋለን። በ2010 ዓ.ም የማዕድን ዘርፍ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) የነበረው ድርሻ 0.2 በመቶ ብቻ ነበረ። በ2017 ዓ.ም ይህ ቁጥር የ7 እጥፍ ብልጫ በማሳየት ወደ 1.4 በመቶ ማደግ ችሏል።
በተለይም በወርቅ ምርት እና ኤክስፖርት ላይ የታየው ለውጥ በታሪካችን ወደር የማይገኝለት እመርታ ነው።
ባህላዊ የማዕድን ቁፋሮን ወደ መደበኛ የንግድ ሥርዓት በማስገባት በተደረገው ስኬታማ የፖሊሲ ማሻሻያ፣ የሀገራችን የወርቅ ኤክስፖርት ገቢ ከ100 ሚሊዮን ዶላር ወደ 3.48 ቢሊዮን ዶላር በማደግ የ35 እጥፍ ጭማሪ አስመዝግቧል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በቅርቡ የተገበረው በገበያ ላይ የተመሠረተ የውጭ ምንዛሬ ተመን ሥርዓት ደግሞ አምራቾች ምርታቸውን በመደበኛው የፋይናንስ ሥርዓት እንዲያቀርቡ በማድረግ ለዚህ ስኬት ትልቅ ሞተር ሆኗል።
በሌላ በኩል "ኢትዮጵያ ታምርት" በተሰኘው ሀገራዊ ንቅናቄ የማዕድን ዘርፉ ከማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪው ጋር በጥብቅ በመተሳሰሩ፣ ገቢ ምርትን በሀገር ውስጥ በመተካት ከፍተኛ ድል ተመዝግቧል።
ለአብነት ያህል የአርጆ የድንጋይ ከሰል ማበልጸጊያ ፋብሪካን መመልከት በቂ ነው። ይህ ዘመናዊ ፋብሪካ በየዓመቱ የከሰል ድንጋይ ለማስገባት ይወጣ የነበረውን ከ300 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ምርት እንዲተካ አስችሏል።
በተመሳሳይ የኖራ ድንጋይ የሀገር ውስጥ ምርት ድርሻ ከ17 በመቶ ወደ 75 በመቶ ከፍ ማለቱ፣ እንደ ለሚ ናሽናል ሲሚንቶ እና ሙገር የመሳሰሉ ግዙፍ ፋብሪካዎች የማምረቻ ወጪያቸውን በከፍተኛ ደረጃ እንዲቀንሱ አድርጓል።
ይህ በማዕድን ዘርፉ የታየው ዕድገት በማክሮ ኢኮኖሚው ላይ ብቻ ሳይሆን፣ ሰፊ ማኅበራዊ ፋይዳንም አምጥቷል።
በአሁኑ ወቅት ኢንዱስትሪው ከ1 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ዜጎቻችን ቀጥተኛ የሥራ ዕድል ፈጥሯል። ከ4 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን ደግሞ ኑሯቸውን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በዚህ ዘርፍ ላይ መስርተዋል።
በአጠቃላይ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው የማዕድን ዘርፉን ከድቅድቅ ጨለማ አውጥቶ የሀገራችንን የኢንዱስትሪ ሽግግር የሚያፋጥን ሞተር አድርጎታል።
ይህ የማዕድን ዘርፍ ስኬት ዘርፉ የኢትዮጵያን የብልጽግና ጉዞ ዕውን የሚያደርግ አስተማማኝ ምሰሶ መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #mining #madeinethiopia #economicreform #goldexport #ebc
Sponsored by
Surafel
1 month ago
የመደመር መንግሥት ስንል?
********
ታሪክን ወደ ኋላ መለስ ብለን ስንቃኝ፣ ኢትዮጵያ የነፃነት ተምሳሌት፣ የጥንታዊ ስልጣኔ ባለቤት፣ እና የብዙ ፀጋዎች ማህደር ሆና እናገኛታለን።
አባቶቻችን በደማቸው አቅንተውና ጠብቀው ያቆዩልንን ይህች ምድር፣ ሀብቷ ሳይደመርና አ ቅሟ ሳይቀናጅ ለዘመናት በመቆየቱ ምክንያት፣ በእጦት አዙሪትና በድህነት ማጥ ውስጥ ስትዳክር ኖራለች።
“የኢትዮጵያውያንን ህይወት እንለውጣለን” የሚለው መፈክር በተፈራረቁ መንግስታትና ትውልዶች ዘንድ በተደጋግሚ ቢነገርም፣ በተግባር ግን እንደ ጉም ርቆን፣ እንደ ህልም ተንሳፎ ቆይቷል።
ዘመናት ነጎዱ፣ ትውልዶች ተፈራረቁ፤ እኛ ግን በተረገጥንበት ቦታ መቆማችንን አልተውንም። በዚህ የታሪክ መስቀለኛ መንገድ እና በተከማቸ የቤት ስራ አጣብቂኝ ውስጥ ነው እንግዲህ "የመደመር መንግስት" ብቅ ያለው።
ለመሆኑ የመደመር መንግስት ምንነት ምንድን ነው?
የመደመር መንግስት ማለት መከፋፈልን፣ መነጠልን፣ እና የአንዱን መቃብር የሌላው ዙፋን የሚያደርገውን የዜሮ ድምር ጨዋታ በመፀየፍ፣ ሀገራዊ ፀጋዎችንና አቅሞችን ወደ አንድ የብልፅግና ወንዝ የሚያፈስ ስርዓት ነው። በመደመር ፍልስፍና መነፅር፣ የመንግስት ሚና እንደ ባለፈው ዘመን ሁሉን አድራጊ ፈጣሪ ወይም ጨቋኝ መሆን ሳይሆን፣ የትብብር ሞተር መሆን ነው።
ይህ መንግስት ዜጎችን፣ የግሉን ዘርፍ፣ እና ሀገራዊ አቅሞችን በማስተባበር፤ ትላንት ያመለጠንን የባከነ ጊዜ "በፈጠራ እና በፍጥነት" የሚያካክስ፣ ገቢር ነበብ (Pragmatic) የሆነ የዘመነ መንግስታዊ መዋቅር ነው።
መሰረታዊ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ዲፓርቸሩም ይሄው ነው፡ ትናንትን ከስህተቱ ተምሮ ማረም፣ ዛሬን በትጋት መስራት፣ እና ነገን በምናብ ተልሞ ማለም።
የመደመር መንግሥት ስንል፣ በፍልስፍና መሠረቱ ከታሕታይ መዋቅር (እንደ ኢኮኖሚ እና መሠረተ ልማት) ለውጥ ይልቅ ለላዕላይ መዋቅር (አስተሳሰብ እና ባህል) ለውጥ ቅድሚያ የሚሰጥ ሥርዓት ማለታችን ነው። ይህ መንግሥት የማኅበረሰብን ልዩ ልዩ ጸጋዎች፣ ዕሴቶች፣ እና አቅሞች ማሰባሰብ ለብልጽግና ወሳኝ መሆኑን በፅኑ ያምናል።
የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ኃይሎች በሚፈጥሩት ፍትጊያ ውስጥ ሚዛን (ወርቃማውን አማካይ) በመጠበቅ ሁሉንም አቅፎ የሚጓዝ ነው።
ይህንን እውነት ይበልጥ ለመረዳት የመደመርን መንግሥት መሠረታዊ መለያዎች ካለፉት መንግሥታት ታሪክ ጋር ማነፃፀር ግድ ይላል።
የሀገራችን የፖለቲካ ጉዞ ከውጭ ሀገር (ከምዕራብም ሆነ ከምሥራቅ) የልማት ሞዴሎችን እንዳለ ገልብጦ በማምጣት የኢትዮጵያን ነባራዊ እውነታ ለማሳጣት ሲጥር የኖረ ፤የንጉሡ ሥርዓት "ሰማይ አይታረስ፣ ንጉሥ አይከሰስ" በሚል መርህ አይነኬነትን ያነገሠ፣ ለውጥን የሚጠላና ቆሞ-ቀርነትን ያተረፈ ፊውዳላዊ ሥርዓት ሆና የተካው የደርግ መንግሥት ደግሞ የሶቪየትን ሞዴል በጭፍን በመከተል "ትሻልን ሰድጄ ትብስን አመጣሁ" እንዲሉ፣ በኅብረተሰብአዊነት ስም የግሉን ዘርፍ አቀጭጮ፣ ሀብት ፈጣሪነትን አውግዞ ሀገርን ለከፋ የኢኮኖሚ ቀውስና አዙሪት ዳርጓል።
የኢሕአዴግ መንግሥት በበኩሉ ብሔርን ከአስተዳደራዊ ወሰን ጋር በማስተሳሰሩ ጽንፈኝነትን ያቀጣጠለ፣ ሀገራዊ አንድነትን የሸረሸረ እና በመጨረሻም የሀገር ሀብት በጥቂት የፖለቲካ ልሂቃን እጅ እንዲወድቅ ያደረገ ፣እነዚህ ሁሉ መንግሥታት ከዜሮ ድምር ፖለቲካ፣ ተቀናቃኝን አሳዶ ከማጥፋት፣ እና የሕዝብን እያደገ የሚመጣ ፍላጎት በጊዜው ካለመመለስ አባዜ አልወጡም ነበር።
ከዚህ በተቃራኒ፣ የመደመር መንግሥት የገበያ መር እና የመንግሥት መር ፅንፎችን በማስወገድ "የትብብር ሞዴልን" ገንዘቡ ያደርጋል። የግሉ ዘርፍ ሀብት እንዲፈጥር ሲያበረታታ፣ መንግሥትም ራሱ በኢንተርፕረነርሺፕ (ስራ ፈጣሪነት)ዕሳቤ አዳዲስ ዘርፎችን በመፍጠርና ሀገራዊ ሀብትን በማከማቸት ይተጋል።
የመደመር መንግሥት ሌላው ግዙፍ መለያው "የዔሊ ጉዞን" ሰብሮ በ"ፍጥነት፣ ፈጠራ እና ዝላይ" መገስገሱ ነው። አዳጊ ሀገራት የበለፀጉት ሀገራት የሄዱበትን የክፍለ ዘመናት አዝጋሚ (ደረጃ በደረጃ) ጉዞ መከተል የለባቸውም በማለት፣ ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ በቀጥታ በመቀላቀል "የዝላይ መንገድን" (Leapfrogging) በመጠቀም ኢትዮጵያን ተወዳዳሪ ለማድረግ ይሠራል።
ከዚህም ባሻገር፣ የመደመር መንግሥት "ምናባዊ ከፍታን" ተላብሷል። የይድረስ ይድረስ ጊዜያዊ ማስታገሻዎችን ትቶ፣ እንደ አዲስ አበባ ወንዞች ልማት (ገበታ ለሸገር) እና የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብሮችን በመሰሉ ሩቅ አላሚ ፕሮጀክቶች ሀሳብን ወደ መሬት በማውረድ "የማድረግ ዐቅሙን" በተግባር አረጋግጧል።
በአጠቃላይ የመደመር መንግሥት የትናንትናውን የተከማቸ ዕዳ በፈጠራ የሚያቃልል፣ ያመለጠንን የኢንዱስትሪ አብዮት ጊዜ የሚያካክስ፣ እና ኢትዮጵያን በጠንካራ ሥርዓታዊ መዋቅርና ትብብር ወደ ብልጽግና ማማ የሚያሸጋግር መሪ ብርሃን ነው።
በአዶኒያስ ወ/አረጋይ
#ethiopianbroadcastingcorporation #medemer #philosophyofmedemer #nationalunity
********
ታሪክን ወደ ኋላ መለስ ብለን ስንቃኝ፣ ኢትዮጵያ የነፃነት ተምሳሌት፣ የጥንታዊ ስልጣኔ ባለቤት፣ እና የብዙ ፀጋዎች ማህደር ሆና እናገኛታለን።
አባቶቻችን በደማቸው አቅንተውና ጠብቀው ያቆዩልንን ይህች ምድር፣ ሀብቷ ሳይደመርና አ ቅሟ ሳይቀናጅ ለዘመናት በመቆየቱ ምክንያት፣ በእጦት አዙሪትና በድህነት ማጥ ውስጥ ስትዳክር ኖራለች።
“የኢትዮጵያውያንን ህይወት እንለውጣለን” የሚለው መፈክር በተፈራረቁ መንግስታትና ትውልዶች ዘንድ በተደጋግሚ ቢነገርም፣ በተግባር ግን እንደ ጉም ርቆን፣ እንደ ህልም ተንሳፎ ቆይቷል።
ዘመናት ነጎዱ፣ ትውልዶች ተፈራረቁ፤ እኛ ግን በተረገጥንበት ቦታ መቆማችንን አልተውንም። በዚህ የታሪክ መስቀለኛ መንገድ እና በተከማቸ የቤት ስራ አጣብቂኝ ውስጥ ነው እንግዲህ "የመደመር መንግስት" ብቅ ያለው።
ለመሆኑ የመደመር መንግስት ምንነት ምንድን ነው?
የመደመር መንግስት ማለት መከፋፈልን፣ መነጠልን፣ እና የአንዱን መቃብር የሌላው ዙፋን የሚያደርገውን የዜሮ ድምር ጨዋታ በመፀየፍ፣ ሀገራዊ ፀጋዎችንና አቅሞችን ወደ አንድ የብልፅግና ወንዝ የሚያፈስ ስርዓት ነው። በመደመር ፍልስፍና መነፅር፣ የመንግስት ሚና እንደ ባለፈው ዘመን ሁሉን አድራጊ ፈጣሪ ወይም ጨቋኝ መሆን ሳይሆን፣ የትብብር ሞተር መሆን ነው።
ይህ መንግስት ዜጎችን፣ የግሉን ዘርፍ፣ እና ሀገራዊ አቅሞችን በማስተባበር፤ ትላንት ያመለጠንን የባከነ ጊዜ "በፈጠራ እና በፍጥነት" የሚያካክስ፣ ገቢር ነበብ (Pragmatic) የሆነ የዘመነ መንግስታዊ መዋቅር ነው።
መሰረታዊ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ዲፓርቸሩም ይሄው ነው፡ ትናንትን ከስህተቱ ተምሮ ማረም፣ ዛሬን በትጋት መስራት፣ እና ነገን በምናብ ተልሞ ማለም።
የመደመር መንግሥት ስንል፣ በፍልስፍና መሠረቱ ከታሕታይ መዋቅር (እንደ ኢኮኖሚ እና መሠረተ ልማት) ለውጥ ይልቅ ለላዕላይ መዋቅር (አስተሳሰብ እና ባህል) ለውጥ ቅድሚያ የሚሰጥ ሥርዓት ማለታችን ነው። ይህ መንግሥት የማኅበረሰብን ልዩ ልዩ ጸጋዎች፣ ዕሴቶች፣ እና አቅሞች ማሰባሰብ ለብልጽግና ወሳኝ መሆኑን በፅኑ ያምናል።
የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ኃይሎች በሚፈጥሩት ፍትጊያ ውስጥ ሚዛን (ወርቃማውን አማካይ) በመጠበቅ ሁሉንም አቅፎ የሚጓዝ ነው።
ይህንን እውነት ይበልጥ ለመረዳት የመደመርን መንግሥት መሠረታዊ መለያዎች ካለፉት መንግሥታት ታሪክ ጋር ማነፃፀር ግድ ይላል።
የሀገራችን የፖለቲካ ጉዞ ከውጭ ሀገር (ከምዕራብም ሆነ ከምሥራቅ) የልማት ሞዴሎችን እንዳለ ገልብጦ በማምጣት የኢትዮጵያን ነባራዊ እውነታ ለማሳጣት ሲጥር የኖረ ፤የንጉሡ ሥርዓት "ሰማይ አይታረስ፣ ንጉሥ አይከሰስ" በሚል መርህ አይነኬነትን ያነገሠ፣ ለውጥን የሚጠላና ቆሞ-ቀርነትን ያተረፈ ፊውዳላዊ ሥርዓት ሆና የተካው የደርግ መንግሥት ደግሞ የሶቪየትን ሞዴል በጭፍን በመከተል "ትሻልን ሰድጄ ትብስን አመጣሁ" እንዲሉ፣ በኅብረተሰብአዊነት ስም የግሉን ዘርፍ አቀጭጮ፣ ሀብት ፈጣሪነትን አውግዞ ሀገርን ለከፋ የኢኮኖሚ ቀውስና አዙሪት ዳርጓል።
የኢሕአዴግ መንግሥት በበኩሉ ብሔርን ከአስተዳደራዊ ወሰን ጋር በማስተሳሰሩ ጽንፈኝነትን ያቀጣጠለ፣ ሀገራዊ አንድነትን የሸረሸረ እና በመጨረሻም የሀገር ሀብት በጥቂት የፖለቲካ ልሂቃን እጅ እንዲወድቅ ያደረገ ፣እነዚህ ሁሉ መንግሥታት ከዜሮ ድምር ፖለቲካ፣ ተቀናቃኝን አሳዶ ከማጥፋት፣ እና የሕዝብን እያደገ የሚመጣ ፍላጎት በጊዜው ካለመመለስ አባዜ አልወጡም ነበር።
ከዚህ በተቃራኒ፣ የመደመር መንግሥት የገበያ መር እና የመንግሥት መር ፅንፎችን በማስወገድ "የትብብር ሞዴልን" ገንዘቡ ያደርጋል። የግሉ ዘርፍ ሀብት እንዲፈጥር ሲያበረታታ፣ መንግሥትም ራሱ በኢንተርፕረነርሺፕ (ስራ ፈጣሪነት)ዕሳቤ አዳዲስ ዘርፎችን በመፍጠርና ሀገራዊ ሀብትን በማከማቸት ይተጋል።
የመደመር መንግሥት ሌላው ግዙፍ መለያው "የዔሊ ጉዞን" ሰብሮ በ"ፍጥነት፣ ፈጠራ እና ዝላይ" መገስገሱ ነው። አዳጊ ሀገራት የበለፀጉት ሀገራት የሄዱበትን የክፍለ ዘመናት አዝጋሚ (ደረጃ በደረጃ) ጉዞ መከተል የለባቸውም በማለት፣ ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ በቀጥታ በመቀላቀል "የዝላይ መንገድን" (Leapfrogging) በመጠቀም ኢትዮጵያን ተወዳዳሪ ለማድረግ ይሠራል።
ከዚህም ባሻገር፣ የመደመር መንግሥት "ምናባዊ ከፍታን" ተላብሷል። የይድረስ ይድረስ ጊዜያዊ ማስታገሻዎችን ትቶ፣ እንደ አዲስ አበባ ወንዞች ልማት (ገበታ ለሸገር) እና የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብሮችን በመሰሉ ሩቅ አላሚ ፕሮጀክቶች ሀሳብን ወደ መሬት በማውረድ "የማድረግ ዐቅሙን" በተግባር አረጋግጧል።
በአጠቃላይ የመደመር መንግሥት የትናንትናውን የተከማቸ ዕዳ በፈጠራ የሚያቃልል፣ ያመለጠንን የኢንዱስትሪ አብዮት ጊዜ የሚያካክስ፣ እና ኢትዮጵያን በጠንካራ ሥርዓታዊ መዋቅርና ትብብር ወደ ብልጽግና ማማ የሚያሸጋግር መሪ ብርሃን ነው።
በአዶኒያስ ወ/አረጋይ
#ethiopianbroadcastingcorporation #medemer #philosophyofmedemer #nationalunity
1 month ago
የኢትዮጵያ አዲሱ የዲጂታል ዘመን ስኬቶች
*************
ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በዲጂታል ቴክኖሎጂ እና በቴሌኮሙኒኬሽን ዘርፍ እያስመዘገበች ያለችው ፈጣን ዕድገት ከተበታተኑ አሠራሮች ወጥታ የተቀናጀ የኢኮኖሚ መሠረት እንድትጥል እያስቻላት ይገኛል።
የቴሌኮም ዘርፉን በማዘመን እና ለገበያ ክፍት በማድረግ የተጀመረው ይህ ጉዞ ሀገራችንን ወደ ላቀ የዲጂታል ዘመን እያሸጋገራት ነው።
የመሠረተ ልማት እና የክፍያ ሥርዓት አብዮት
በቅርብ ዓመታት የቴሌኮም ደንበኞች ቁጥር ከ37.9 ሚሊዮን ወደ 85 ሚሊዮን በላይ መድረሱ ለሀገራዊው የዲጂታል ትሥሥር እና ለገበያ ተሳትፎ የማይናወጥ መሠረት ጥሏል።
የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት መስፋፋት ደግሞ ሌላው ታሪካዊ ስኬት ነው። ከዚህ ቀደም በውል የማይታወቀው ዓመታዊ የዲጂታል ግብይት መጠን አሁን ላይ ወደ 24.2 ትሪሊዮን የኢትዮጵያ ብር ከፍ ብሏል።
ይህ ግዙፍ አሃዝ በጥሬ ገንዘብ ላይ የተመሠረተውን ግብይት በመቀነስ ግልጽነትን የፈጠረ ሲሆን፣ ለፖሊሲ አውጪዎች ግልጽ የሆነ እና የታለመ የፋይናንስ እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችል ምቹ ሥርዓት ፈጥሯል።
አካታችነትን ያረጋገጠው ዲጂታል መታወቂያ
የፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ሥርዓት የዜጎችን ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎ በማሳደግ በኩል ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ነው።
ይህ ፕሮጀክት ከባዶ ተነሥቶ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከ46.4 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን መመዝገብ ቸሏል።
ፋይዳ በገበያ የሚጠየቀውን የምዝገባ እና የማረጋገጫ ወጪዎችን በእጅጉ በመቀነስ ረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል።
አስተማማኝ የማንነት ማረጋገጫ በመስጠትም የፋይናንስ አካታችነትን ይበልጥ እውን እያደረገ ነው።
ሀገር በቀል የቴክኖሎጂ አቅም እና የወደፊቱ ራዕይ
በሦስት ዓመታት ውስጥ ለማሳካት ታቅዶ ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ የተሳካው የ"5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች" ኢኒሼቲቭ የዲጂታል ኢትዮጵያን መጻኢ ተስፋ ያረጋገጠ ነው።
ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም ከተጀመረበት ጊዜ አንሥቶ በኮምፒውተር ፕሮግራሚንግ፣ በመረጃ ትንተና፣ በአንድሮይድ ሶፍትዌር ልማት እና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ 5 ሚሊዮን 5 ሺህ 146 ሰልጣኞች ተመዝግበዋል።
ከ4 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ደግሞ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለውን የምስክር ወረቀት አግኝተዋል።
ይህ በዲጂታሉ ዓለም የተጀመረው ታሪካዊ ምዕራፍ የጉዞው ማብቂያ ሳይሆን ብሔራዊ ራዕይን ይበልጥ ማፋጠኛ መነሻ ነው።
በመሆኑም እስከ ነሐሴ 2018 ዓ.ም ድረስ የሠልጣኞችን ቁጥር 7 ሚሊዮን ለማድረስ አዲስ ግብ ተሰንቋል።
በተለይም ወጣት ተማሪዎች የክረምቱን ወቅት በዋዛ ከማሳለፍ ይልቅ ሙሉ በሙሉ በነጻ የሚሰጠውን ይህንን ሥልጠና በመውሰድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና ያላቸው የዲጂታል መሪዎች እንዲሆኑ ጥሪ ቀርቧል።
እነዚህ ሁሉ እመርታዎች ኢትዮጵያ በዓለም አቀፉ የዲጂታል ኢኮኖሚ ፉክክር ውስጥ ተወዳዳሪ ብቻ ሳትሆን መሪም እንድትሆን የሚያደርጓት ጽኑ መሠረቶች ናቸው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #digitalethiopia #digitaltransformation #techinnovation
*************
ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በዲጂታል ቴክኖሎጂ እና በቴሌኮሙኒኬሽን ዘርፍ እያስመዘገበች ያለችው ፈጣን ዕድገት ከተበታተኑ አሠራሮች ወጥታ የተቀናጀ የኢኮኖሚ መሠረት እንድትጥል እያስቻላት ይገኛል።
የቴሌኮም ዘርፉን በማዘመን እና ለገበያ ክፍት በማድረግ የተጀመረው ይህ ጉዞ ሀገራችንን ወደ ላቀ የዲጂታል ዘመን እያሸጋገራት ነው።
የመሠረተ ልማት እና የክፍያ ሥርዓት አብዮት
በቅርብ ዓመታት የቴሌኮም ደንበኞች ቁጥር ከ37.9 ሚሊዮን ወደ 85 ሚሊዮን በላይ መድረሱ ለሀገራዊው የዲጂታል ትሥሥር እና ለገበያ ተሳትፎ የማይናወጥ መሠረት ጥሏል።
የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት መስፋፋት ደግሞ ሌላው ታሪካዊ ስኬት ነው። ከዚህ ቀደም በውል የማይታወቀው ዓመታዊ የዲጂታል ግብይት መጠን አሁን ላይ ወደ 24.2 ትሪሊዮን የኢትዮጵያ ብር ከፍ ብሏል።
ይህ ግዙፍ አሃዝ በጥሬ ገንዘብ ላይ የተመሠረተውን ግብይት በመቀነስ ግልጽነትን የፈጠረ ሲሆን፣ ለፖሊሲ አውጪዎች ግልጽ የሆነ እና የታለመ የፋይናንስ እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችል ምቹ ሥርዓት ፈጥሯል።
አካታችነትን ያረጋገጠው ዲጂታል መታወቂያ
የፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ሥርዓት የዜጎችን ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎ በማሳደግ በኩል ቁልፍ ሚና እየተጫወተ ነው።
ይህ ፕሮጀክት ከባዶ ተነሥቶ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከ46.4 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን መመዝገብ ቸሏል።
ፋይዳ በገበያ የሚጠየቀውን የምዝገባ እና የማረጋገጫ ወጪዎችን በእጅጉ በመቀነስ ረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል።
አስተማማኝ የማንነት ማረጋገጫ በመስጠትም የፋይናንስ አካታችነትን ይበልጥ እውን እያደረገ ነው።
ሀገር በቀል የቴክኖሎጂ አቅም እና የወደፊቱ ራዕይ
በሦስት ዓመታት ውስጥ ለማሳካት ታቅዶ ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ የተሳካው የ"5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች" ኢኒሼቲቭ የዲጂታል ኢትዮጵያን መጻኢ ተስፋ ያረጋገጠ ነው።
ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም ከተጀመረበት ጊዜ አንሥቶ በኮምፒውተር ፕሮግራሚንግ፣ በመረጃ ትንተና፣ በአንድሮይድ ሶፍትዌር ልማት እና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ 5 ሚሊዮን 5 ሺህ 146 ሰልጣኞች ተመዝግበዋል።
ከ4 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ደግሞ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለውን የምስክር ወረቀት አግኝተዋል።
ይህ በዲጂታሉ ዓለም የተጀመረው ታሪካዊ ምዕራፍ የጉዞው ማብቂያ ሳይሆን ብሔራዊ ራዕይን ይበልጥ ማፋጠኛ መነሻ ነው።
በመሆኑም እስከ ነሐሴ 2018 ዓ.ም ድረስ የሠልጣኞችን ቁጥር 7 ሚሊዮን ለማድረስ አዲስ ግብ ተሰንቋል።
በተለይም ወጣት ተማሪዎች የክረምቱን ወቅት በዋዛ ከማሳለፍ ይልቅ ሙሉ በሙሉ በነጻ የሚሰጠውን ይህንን ሥልጠና በመውሰድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና ያላቸው የዲጂታል መሪዎች እንዲሆኑ ጥሪ ቀርቧል።
እነዚህ ሁሉ እመርታዎች ኢትዮጵያ በዓለም አቀፉ የዲጂታል ኢኮኖሚ ፉክክር ውስጥ ተወዳዳሪ ብቻ ሳትሆን መሪም እንድትሆን የሚያደርጓት ጽኑ መሠረቶች ናቸው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #digitalethiopia #digitaltransformation #techinnovation
1 month ago
የዲጂታል ኢኮኖሚው አብዮት፤ ቴሌብር 5ኛ ዓመት
#fastmereja | የኢትዮጵያን የፋይናንስ ሥርዓት በቴክኖሎጂ ያዘመነው እና በዲጂታል ክፍያ ዘርፍ አዲስ ምዕራፍ የከፈተው "ቴሌብር" አገልግሎት መስጠት ከጀመረ 5 ዓመታት ተቆጠሩ። ኩባንያው በተለይም የገንዘብ ዝውውርን ፈጣንና ተደራሽ በማድረግ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን ከዘመናዊ የባንክ አገልግሎት ጋር አስተሳስሯል።
ላለፉት አምስት ዓመታት ቴሌብር በኢትዮጵያ የገበያ ሁኔታ ውስጥ ትልቅ የለውጥ ኃይል ሆኖ ቆይቷል። በተለይም በባንክ አገልግሎት ያልተደራሱ የኅብረተሰብ ክፍሎችን በዲጂታል መረብ ውስጥ በማካተት የፋይናንስ አካታችነትን (Financial Inclusion) በከፍተኛ ደረጃ አሳድጓል። በጥሬ ገንዘብ ይፈጸሙ የነበሩ የዕለት ተዕለት ግብይቶች፣ የፍጆታ ክፍያዎች እና የገንዘብ ልውውጦች ዛሬ በቴሌብር አማካኝነት በሰከንዶች ውስጥ የሚከናወኑበት ዕድል ተፈጥሯል።
ቴሌብር በዘርፉ ባስመዘገበው ፈጣን እድገት፣ ከአገልግሎት ክፍያ ባሻገር ብድርን እና ቁጠባን የሚያካትቱ ውስብስብ የፋይናንስ መፍትሔዎችን በማቅረብ የኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ዋና አከርካሪ ሆኗል። በተለይ በገጠር እና በከተማ መካከል ያለውን የገንዘብ ፍሰት በማቀላጠፍ፣ ለአነስተኛ ነጋዴዎች እና ለግለሰቦች አስተማማኝ የግብይት አማራጭ ሆኖ ተገኝቷል።
በአምስት ዓመታት የሥራ ጉዞው ቴሌብር በርካታ ፈተናዎችን በመሻገር፣ አዳዲስ የቴክኖሎጂ አቅሞችን በመዘርጋት እና ከተለያዩ የፋይናንስ ተቋማት ጋር በመዋሃድ የተጠቃሚዎቹን ቁጥር ወደ አስደናቂ ደረጃ ከፍ አድርጓል።
ወደፊት በሚኖረው ጉዞ፣ ቴሌብር ከዲጂታል ክፍያ ባለፈ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ሥርዓት ወደ ላቀ የቴክኖሎጂ ደረጃ ለማሸጋገር እና አለም አቀፍ የክፍያ ሥርዓቶችን ለመቀላቀል ትኩረት እንደሚያደርግ ይጠበቃል። ይህ የ5 ዓመት ጉዞ ኢትዮጵያ በዲጂታል ኢኮኖሚ ሽግግር ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየ እንደሆነ ታዛቢዎች ይገልጻሉ።
#fastmereja | የኢትዮጵያን የፋይናንስ ሥርዓት በቴክኖሎጂ ያዘመነው እና በዲጂታል ክፍያ ዘርፍ አዲስ ምዕራፍ የከፈተው "ቴሌብር" አገልግሎት መስጠት ከጀመረ 5 ዓመታት ተቆጠሩ። ኩባንያው በተለይም የገንዘብ ዝውውርን ፈጣንና ተደራሽ በማድረግ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን ከዘመናዊ የባንክ አገልግሎት ጋር አስተሳስሯል።
ላለፉት አምስት ዓመታት ቴሌብር በኢትዮጵያ የገበያ ሁኔታ ውስጥ ትልቅ የለውጥ ኃይል ሆኖ ቆይቷል። በተለይም በባንክ አገልግሎት ያልተደራሱ የኅብረተሰብ ክፍሎችን በዲጂታል መረብ ውስጥ በማካተት የፋይናንስ አካታችነትን (Financial Inclusion) በከፍተኛ ደረጃ አሳድጓል። በጥሬ ገንዘብ ይፈጸሙ የነበሩ የዕለት ተዕለት ግብይቶች፣ የፍጆታ ክፍያዎች እና የገንዘብ ልውውጦች ዛሬ በቴሌብር አማካኝነት በሰከንዶች ውስጥ የሚከናወኑበት ዕድል ተፈጥሯል።
ቴሌብር በዘርፉ ባስመዘገበው ፈጣን እድገት፣ ከአገልግሎት ክፍያ ባሻገር ብድርን እና ቁጠባን የሚያካትቱ ውስብስብ የፋይናንስ መፍትሔዎችን በማቅረብ የኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ዋና አከርካሪ ሆኗል። በተለይ በገጠር እና በከተማ መካከል ያለውን የገንዘብ ፍሰት በማቀላጠፍ፣ ለአነስተኛ ነጋዴዎች እና ለግለሰቦች አስተማማኝ የግብይት አማራጭ ሆኖ ተገኝቷል።
በአምስት ዓመታት የሥራ ጉዞው ቴሌብር በርካታ ፈተናዎችን በመሻገር፣ አዳዲስ የቴክኖሎጂ አቅሞችን በመዘርጋት እና ከተለያዩ የፋይናንስ ተቋማት ጋር በመዋሃድ የተጠቃሚዎቹን ቁጥር ወደ አስደናቂ ደረጃ ከፍ አድርጓል።
ወደፊት በሚኖረው ጉዞ፣ ቴሌብር ከዲጂታል ክፍያ ባለፈ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ሥርዓት ወደ ላቀ የቴክኖሎጂ ደረጃ ለማሸጋገር እና አለም አቀፍ የክፍያ ሥርዓቶችን ለመቀላቀል ትኩረት እንደሚያደርግ ይጠበቃል። ይህ የ5 ዓመት ጉዞ ኢትዮጵያ በዲጂታል ኢኮኖሚ ሽግግር ያላትን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየ እንደሆነ ታዛቢዎች ይገልጻሉ።
1 month ago
ኢትዮጵያ ታከናውናለች፡- ፈተናዎችን የተሻገረው የኢትዮጵያ የመሠረተ-ልማት ግንባታ
*************************
ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ያከናወነቻቸው ግዙፍ የመሠረተ-ልማት ግንባታዎች የሀገር ውስጥ ምጣኔ-ሀብትን ከማሳደግ ባለፈ፣ የአፍሪካ ቀንድን የኢኮኖሚ ገጽታ እየቀየረ ይገኛል።
"ኢትዮጵያ ታከናውናለች" በሚለው ብሔራዊ ተስፋ እና በ"መደመር" እሳቤ የታገዘው ይህ ጉዞ፣ ሀገራችንን የምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና ማዕከል ማድረጉን ቀጥሏል።
በተለይም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ኢትዮጵያ በመሠረተ-ልማት ረገድ ካስመዘገበቻቸው ስኬቶች የኢነርጂ ሉዓላዊነት እና የ"አረንጓዴ ወርቅ" ሽግግር ተጠቃሽ ነው።
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቁ እና በሙሉ አቅም ኃይል ማመንጨት መጀመሩ ለሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች አስተማማኝ ግብዓት ከመሆን ባለፈ፣ ለጎረቤት ሀገራት በተለይም ለሱዳን፣ ጅቡቲ እና ኬንያ የሚላከውን የኃይል መጠን አሳድጎታል።
ይህ ንፁህ ታዳሽ ኃይል ሀገራችንን ከካርቦን ሽያጭ የምታገኘውን ገቢ የሚያሳድግ እና የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል የምታደርገውን የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄን በምጣኔ-ሀብት የሚያጠናክር ነው።
ሌላው የትራንስፖርት እና የኮሪደር ልማት ሥራዎች ሲሆኑ፣ በዚህም ከአዲስ አበባ - ጅቡቲ የባቡር መስመር ባሻገር፣ ኢትዮጵያን ከኬንያ በሞያሌ በኩል እና ከሌሎች ጎረቤቶች ጋር የሚያገናኙ ዘመናዊ አውራ ጎዳናዎች ተገንብተዋል። ይህም የኢትዮጵያን "ቅድሚያ ለጎረቤት" የዲፕሎማሲ ፖሊሲ በተግባር ያሳየ ነው።
የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች በዋና ዋና ከተሞች በተለይም በአዲስ አበባ የተከናወኑት የኮሪደር ልማት ሥራዎች የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ የንግድ እንቅስቃሴን ያቃለሉ እና የከተማ ኑሮ ደረጃን ያሻሻሉ ናቸው።
ኢትዮጵያ በአቪዬሽን ዘርፍ ያከናወነቻቸው ተግባራት ለዘርፉ ስኬታማነት ትልቁን ሚና በመጫወት ላይ ይገኛሉ። በዚህም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ ቀዳሚነቱን ሚና በመያዝ በሀገር ውስጥ የአውሮፕላን ማረፊያ መመሠረተ-ልማቶችን በማስፋፋትና አዳዲስ የጭነት ተርሚናሎችን በመገንባት የዓለም አቀፍ ንግድ ድልድይነቱን በማጽናት ላይ ይገኛል።
የዲጂታል መሠረተ-ልማት አብዮት ሌላኛው የኢትዮጵያ ስኬታማ ስራዎች ማሳያ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ በቴሌኮም ዘርፍ ያደረገችው የፖሊሲ ማሻሻያ እና የገበያ ክፍትነት፣ የዲጂታል መሠረተ-ልማቱን ፈጣን አድርጎታል።
የ5G ኔትወርክ መስፋፋት፣ የዳታ ማዕከላት መገንባት እና የዲጂታል ክፍያ ሥርዓቶች እንደ ኢ-ብር እና ቴሌብር ያሉ መስፋፋት ሀገራችንን ለዲጂታል ኢኮኖሚ ዝግጁ አድርገዋታል።
ይህም የሚያሳየው የኢትዮጵያ የመሠረተ-ልማት ጉዞ የሀገር ግንባታ፣ የኢኮኖሚ ሪፎርም እና የትውልድ ቅብብሎሽ መሆኑን ነው። ፈተናዎች ቢኖሩም፣ የተዘረጉት መሠረተ-ልማቶች ለሀገራችን ዕድገት የማይናወጥ መሠረት ጥለዋል፤ እየጣሉም ይገኛሉ።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopia #ebc #infrastructure #construction #success
*************************
ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ያከናወነቻቸው ግዙፍ የመሠረተ-ልማት ግንባታዎች የሀገር ውስጥ ምጣኔ-ሀብትን ከማሳደግ ባለፈ፣ የአፍሪካ ቀንድን የኢኮኖሚ ገጽታ እየቀየረ ይገኛል።
"ኢትዮጵያ ታከናውናለች" በሚለው ብሔራዊ ተስፋ እና በ"መደመር" እሳቤ የታገዘው ይህ ጉዞ፣ ሀገራችንን የምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና ማዕከል ማድረጉን ቀጥሏል።
በተለይም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ኢትዮጵያ በመሠረተ-ልማት ረገድ ካስመዘገበቻቸው ስኬቶች የኢነርጂ ሉዓላዊነት እና የ"አረንጓዴ ወርቅ" ሽግግር ተጠቃሽ ነው።
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ መጠናቀቁ እና በሙሉ አቅም ኃይል ማመንጨት መጀመሩ ለሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች አስተማማኝ ግብዓት ከመሆን ባለፈ፣ ለጎረቤት ሀገራት በተለይም ለሱዳን፣ ጅቡቲ እና ኬንያ የሚላከውን የኃይል መጠን አሳድጎታል።
ይህ ንፁህ ታዳሽ ኃይል ሀገራችንን ከካርቦን ሽያጭ የምታገኘውን ገቢ የሚያሳድግ እና የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል የምታደርገውን የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄን በምጣኔ-ሀብት የሚያጠናክር ነው።
ሌላው የትራንስፖርት እና የኮሪደር ልማት ሥራዎች ሲሆኑ፣ በዚህም ከአዲስ አበባ - ጅቡቲ የባቡር መስመር ባሻገር፣ ኢትዮጵያን ከኬንያ በሞያሌ በኩል እና ከሌሎች ጎረቤቶች ጋር የሚያገናኙ ዘመናዊ አውራ ጎዳናዎች ተገንብተዋል። ይህም የኢትዮጵያን "ቅድሚያ ለጎረቤት" የዲፕሎማሲ ፖሊሲ በተግባር ያሳየ ነው።
የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች በዋና ዋና ከተሞች በተለይም በአዲስ አበባ የተከናወኑት የኮሪደር ልማት ሥራዎች የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ የንግድ እንቅስቃሴን ያቃለሉ እና የከተማ ኑሮ ደረጃን ያሻሻሉ ናቸው።
ኢትዮጵያ በአቪዬሽን ዘርፍ ያከናወነቻቸው ተግባራት ለዘርፉ ስኬታማነት ትልቁን ሚና በመጫወት ላይ ይገኛሉ። በዚህም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ ቀዳሚነቱን ሚና በመያዝ በሀገር ውስጥ የአውሮፕላን ማረፊያ መመሠረተ-ልማቶችን በማስፋፋትና አዳዲስ የጭነት ተርሚናሎችን በመገንባት የዓለም አቀፍ ንግድ ድልድይነቱን በማጽናት ላይ ይገኛል።
የዲጂታል መሠረተ-ልማት አብዮት ሌላኛው የኢትዮጵያ ስኬታማ ስራዎች ማሳያ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ በቴሌኮም ዘርፍ ያደረገችው የፖሊሲ ማሻሻያ እና የገበያ ክፍትነት፣ የዲጂታል መሠረተ-ልማቱን ፈጣን አድርጎታል።
የ5G ኔትወርክ መስፋፋት፣ የዳታ ማዕከላት መገንባት እና የዲጂታል ክፍያ ሥርዓቶች እንደ ኢ-ብር እና ቴሌብር ያሉ መስፋፋት ሀገራችንን ለዲጂታል ኢኮኖሚ ዝግጁ አድርገዋታል።
ይህም የሚያሳየው የኢትዮጵያ የመሠረተ-ልማት ጉዞ የሀገር ግንባታ፣ የኢኮኖሚ ሪፎርም እና የትውልድ ቅብብሎሽ መሆኑን ነው። ፈተናዎች ቢኖሩም፣ የተዘረጉት መሠረተ-ልማቶች ለሀገራችን ዕድገት የማይናወጥ መሠረት ጥለዋል፤ እየጣሉም ይገኛሉ።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopia #ebc #infrastructure #construction #success
2 months ago
ኢትዮጵያ በ2030 በኃላፊነት በተመራ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የቱሪዝምና ሆስፒታሊቲ ተቋማዊ ብቃቷን ማጠናከር አለባት ተባለ
ሮቤ፣ ባሌ – ሰኔ 15፣ 2018 ዓ.ም.
#ethiopia | ኢትዮጵያ በ2030 የቱሪዝምና ሆስፒታሊቲ ዘርፍ ተወዳዳሪ ለመሆን ከቴክኖሎጂ አጠቃቀም ባሻገር ጠንካራ ተቋማዊ አቅም፣ የሰው ኃይል ብቃት እና የዲጂታል ሥርዓት ግንባታ ላይ ማተኮር እንዳለባት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የሚኒስትሩ አማካሪ ገለጹ።
ዶ/ር አብዮት ይህን ያሉት በመዳ ዋላቡ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደው 2ኛው ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ላይ “The Responsible AI Revolution: Building Ethiopia's Institutional Edge in Tourism and Hospitality by 2030” በሚል ርዕስ ባቀረቡት ቁልፍ ንግግር ነው።
እንደ አማካሪው ገለጻ፣ ኢትዮጵያ በዲጂታል ሽግግር ጉዞዋ ከዜሮ እየተነሳች አይደለችም። ባለፉት ሰባት ዓመታት በቴሌኮም ሪፎርም፣ በዲጂታል መሠረተ ልማት፣ በዲጂታል መታወቂያ፣ በክፍያ ሥርዓቶችና በመንግሥት አገልግሎቶች ዘርፍ ጉልህ እድገቶች ተመዝግበዋል ብለዋል።
በታኅሣሥ 2018 ዓ.ም. የተጀመረው “Digital Ethiopia 2030” የተሰኘው ብሔራዊ ስትራቴጂ ሁሉም ዜጎች በዲጂታል ኢኮኖሚው ተጠቃሚ እንዲሆኑ፣ እኩል ዕድል እንዲያገኙ እና የዲጂታል አገልግሎቶች በእምነትና በደህንነት እንዲሰጡ የሚያስችል መሆኑንም አብራርተዋል።
ዶ/ር አብዮት እንዳሉት፣ የቱሪዝም ዘርፉ ከዲጂታል ለውጥ በፍጥነት ተጠቃሚ ሊሆን ከሚችሉ ዘርፎች አንዱ ሲሆን፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የተደገፉ የቱሪዝም መድረኮች፣ የዲጂታል ትኬትና ክፍያ ሥርዓቶች፣ የጎብኚዎች ፍሰት ትንተና እና የተቀናጀ የቱሪዝም መረጃ ሥርዓት ለዘርፉ አዲስ ዕድሎችን እንደሚፈጥሩ ገልጸዋል።
በንግግራቸው የ“MESOB” የተባለውን የተቀናጀ የመንግሥት አገልግሎት መድረክ በአርአያነት ያነሱት አማካሪው፣ ቱሪስቶች ኢትዮጵያን እንደ አንድ የጉዞ ልምድ እንጂ እንደ ተለያዩ ተቋማት እንደማያዩ ገልጸው፣ የቱሪዝም መረጃ፣ የሆቴል አገልግሎቶች፣ የመጓጓዣ አማራጮች፣ የክፍያ ሥርዓቶችና የደህንነት መረጃዎች በአንድ የተቀናጀ ሥርዓት መሰጠት እንዳለባቸው ጠቁመዋል።
ለዚህም የቴክኖሎጂ፣ የሂደት እና የሰው ኃይል ሦስት ዋና ምሰሶዎች በአንድነት መሠራት እንዳለባቸው ገልጸዋል። ብሮድባንድ ግንኙነት፣ ዲጂታል መድረኮች፣ የመረጃ አስተዳደር፣ የAI ሥነ-ምግባር መመሪያዎች እና የሰው ኃይል ብቃት በጋራ ሲጠናከሩ ብቻ ዘላቂ ለውጥ እንደሚመጣ አስገንዝበዋል።
አማካሪው ኢትዮጵያ በ“5 Million Ethiopian Coders” መርሃ ግብር ከ5 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን በኮዲንግ፣ በዳታ ትንተናና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ ክህሎቶች ማሠልጠን መቻሏ ለዘርፉ ጠንካራ የሰው ኃይል መሠረት እየፈጠረች መሆኑን ገልጸዋል።
በመጨረሻም ዶ/ር አብዮት ባዩ፣ በ2030 የኢትዮጵያ ስኬት የሚለካው በተጠቀመችባቸው የAI መሣሪያዎች ብዛት ሳይሆን በዩኒቨርሲቲዎች የተሻሻሉ ሥርዓተ ትምህርቶች፣ በተቋማት የመረጃ ጥራት፣ በዲጂታል ብቃት፣ በግላዊነት ጥበቃ እና በሕዝብ እምነት ላይ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ኮንፈረንሱ በመዳ ዋላቡ ዩኒቨርሲቲ በቱሪዝምና ሆስፒታሊቲ ትምህርት ዘርፍ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የሚያመጣውን ዕድልና ተግዳሮት መወያየት ቀጥሏል።
#ethiopia #bale #tourism #getutemesgen #ጌጡተመስገን #artificialintelligence #digitalethiopia2030 #mwu
ሮቤ፣ ባሌ – ሰኔ 15፣ 2018 ዓ.ም.
#ethiopia | ኢትዮጵያ በ2030 የቱሪዝምና ሆስፒታሊቲ ዘርፍ ተወዳዳሪ ለመሆን ከቴክኖሎጂ አጠቃቀም ባሻገር ጠንካራ ተቋማዊ አቅም፣ የሰው ኃይል ብቃት እና የዲጂታል ሥርዓት ግንባታ ላይ ማተኮር እንዳለባት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የሚኒስትሩ አማካሪ ገለጹ።
ዶ/ር አብዮት ይህን ያሉት በመዳ ዋላቡ ዩኒቨርሲቲ በተካሄደው 2ኛው ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ላይ “The Responsible AI Revolution: Building Ethiopia's Institutional Edge in Tourism and Hospitality by 2030” በሚል ርዕስ ባቀረቡት ቁልፍ ንግግር ነው።
እንደ አማካሪው ገለጻ፣ ኢትዮጵያ በዲጂታል ሽግግር ጉዞዋ ከዜሮ እየተነሳች አይደለችም። ባለፉት ሰባት ዓመታት በቴሌኮም ሪፎርም፣ በዲጂታል መሠረተ ልማት፣ በዲጂታል መታወቂያ፣ በክፍያ ሥርዓቶችና በመንግሥት አገልግሎቶች ዘርፍ ጉልህ እድገቶች ተመዝግበዋል ብለዋል።
በታኅሣሥ 2018 ዓ.ም. የተጀመረው “Digital Ethiopia 2030” የተሰኘው ብሔራዊ ስትራቴጂ ሁሉም ዜጎች በዲጂታል ኢኮኖሚው ተጠቃሚ እንዲሆኑ፣ እኩል ዕድል እንዲያገኙ እና የዲጂታል አገልግሎቶች በእምነትና በደህንነት እንዲሰጡ የሚያስችል መሆኑንም አብራርተዋል።
ዶ/ር አብዮት እንዳሉት፣ የቱሪዝም ዘርፉ ከዲጂታል ለውጥ በፍጥነት ተጠቃሚ ሊሆን ከሚችሉ ዘርፎች አንዱ ሲሆን፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የተደገፉ የቱሪዝም መድረኮች፣ የዲጂታል ትኬትና ክፍያ ሥርዓቶች፣ የጎብኚዎች ፍሰት ትንተና እና የተቀናጀ የቱሪዝም መረጃ ሥርዓት ለዘርፉ አዲስ ዕድሎችን እንደሚፈጥሩ ገልጸዋል።
በንግግራቸው የ“MESOB” የተባለውን የተቀናጀ የመንግሥት አገልግሎት መድረክ በአርአያነት ያነሱት አማካሪው፣ ቱሪስቶች ኢትዮጵያን እንደ አንድ የጉዞ ልምድ እንጂ እንደ ተለያዩ ተቋማት እንደማያዩ ገልጸው፣ የቱሪዝም መረጃ፣ የሆቴል አገልግሎቶች፣ የመጓጓዣ አማራጮች፣ የክፍያ ሥርዓቶችና የደህንነት መረጃዎች በአንድ የተቀናጀ ሥርዓት መሰጠት እንዳለባቸው ጠቁመዋል።
ለዚህም የቴክኖሎጂ፣ የሂደት እና የሰው ኃይል ሦስት ዋና ምሰሶዎች በአንድነት መሠራት እንዳለባቸው ገልጸዋል። ብሮድባንድ ግንኙነት፣ ዲጂታል መድረኮች፣ የመረጃ አስተዳደር፣ የAI ሥነ-ምግባር መመሪያዎች እና የሰው ኃይል ብቃት በጋራ ሲጠናከሩ ብቻ ዘላቂ ለውጥ እንደሚመጣ አስገንዝበዋል።
አማካሪው ኢትዮጵያ በ“5 Million Ethiopian Coders” መርሃ ግብር ከ5 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን በኮዲንግ፣ በዳታ ትንተናና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ ክህሎቶች ማሠልጠን መቻሏ ለዘርፉ ጠንካራ የሰው ኃይል መሠረት እየፈጠረች መሆኑን ገልጸዋል።
በመጨረሻም ዶ/ር አብዮት ባዩ፣ በ2030 የኢትዮጵያ ስኬት የሚለካው በተጠቀመችባቸው የAI መሣሪያዎች ብዛት ሳይሆን በዩኒቨርሲቲዎች የተሻሻሉ ሥርዓተ ትምህርቶች፣ በተቋማት የመረጃ ጥራት፣ በዲጂታል ብቃት፣ በግላዊነት ጥበቃ እና በሕዝብ እምነት ላይ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ኮንፈረንሱ በመዳ ዋላቡ ዩኒቨርሲቲ በቱሪዝምና ሆስፒታሊቲ ትምህርት ዘርፍ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የሚያመጣውን ዕድልና ተግዳሮት መወያየት ቀጥሏል።
#ethiopia #bale #tourism #getutemesgen #ጌጡተመስገን #artificialintelligence #digitalethiopia2030 #mwu
2 months ago
ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ ችግር ያበረከተችው ፍቱን መፍትሔ፦ አረንጓዴ ዐሻራ
***************
ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ያስመዘገበችው ውጤት ከአካባቢ ጥበቃ የዘለለ ሰፊና ስትራቴጂያዊ ፋይዳ ያለው ነው።
ይህ ሀገራዊ ንቅናቄ የኢትዮጵያን ገጽታ በመገንባት፣ የዲፕሎማሲ ግንኙነቶቿን በማጠናከር እና ለቀጣናዊ የአየር ንብረት መዛባት መፍትሄ በመስጠት ረገድ የማይተካ ሚና ተጫውቷል።
አረንጓዴ ዐሻራ ሀገራችን ለልማት እና ለአካባቢ ጥበቃ ባላት ቁርጠኝነት በዓለም አቀፍ ደረጃ የምትታወቅ ሀገር አድርጓታል።
የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ አረንጓዴ በማልበስ እና የደን ሽፋንን በማሳደግ የተገኘው ውጤት ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ ፈተናዎች ያሏት በፈጠራ የታገዙ ምላሾች ማሳያ ነው።
አረንጓዴ ዐሻራ ኢትዮጵያን ለዘላቂ ልማት እንደምትሠራ የተፈጥሮ ሀብት ተንከባካቢ አርዓያ አድርጎ በማቅረብ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያላትን ተቀባይነት ከፍ አድርጓል።
ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ የደን ልማት ሥራዎች ላይ በማሳተፍ በጋራ ሰላምና ጥቅም ላይ የተመሠረተ ቀጣናዊ ትስስርን አጠናክሯል።
በዚህም በአካባቢው ሀገራት መካከል የጋራ መተማመንን በመገንባት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች ይበልጥ እንዲጠናከሩ አስችሏል።
አረንጓዴ ዐሻራ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞችን በጋራ ከመትከል ባሻገር የተተከሉትን በመንከባከብ በዜጎች ዘንድ የባለቤትነት ስሜት እንዲዳብር አድርጓል።
በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂ የታገዘ የዲጂታል ልህቀትን ከአረንጓዴ ዐሻራ ጋር በማጣመር ለቀጣዩ ትውልድ የማይጠፋ የልማት ዐሻራ እያኖረች ነው።
በጥቅሉ የኢትዮጵያን የብልጽግና ጉዞ በማፋጠን ላይ የሚገኘው የዚህ አረንጓዴ አብዮት ስኬት፣ ሕዝብ ለሀገሩ በአንድነት ሲቆም ምን ያህል ታላላቅ ሥራዎችን መከወን እንደሚችል ሕያው ምስክር ነው።
በሃና ምንዳሁን
#ethiopia #climateaction #greenlegacy #greendiplomacy #sustainabledevelopment #nationalpride #ebc
***************
ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ያስመዘገበችው ውጤት ከአካባቢ ጥበቃ የዘለለ ሰፊና ስትራቴጂያዊ ፋይዳ ያለው ነው።
ይህ ሀገራዊ ንቅናቄ የኢትዮጵያን ገጽታ በመገንባት፣ የዲፕሎማሲ ግንኙነቶቿን በማጠናከር እና ለቀጣናዊ የአየር ንብረት መዛባት መፍትሄ በመስጠት ረገድ የማይተካ ሚና ተጫውቷል።
አረንጓዴ ዐሻራ ሀገራችን ለልማት እና ለአካባቢ ጥበቃ ባላት ቁርጠኝነት በዓለም አቀፍ ደረጃ የምትታወቅ ሀገር አድርጓታል።
የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ አረንጓዴ በማልበስ እና የደን ሽፋንን በማሳደግ የተገኘው ውጤት ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ ፈተናዎች ያሏት በፈጠራ የታገዙ ምላሾች ማሳያ ነው።
አረንጓዴ ዐሻራ ኢትዮጵያን ለዘላቂ ልማት እንደምትሠራ የተፈጥሮ ሀብት ተንከባካቢ አርዓያ አድርጎ በማቅረብ በዓለም አቀፍ መድረኮች ያላትን ተቀባይነት ከፍ አድርጓል።
ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ የደን ልማት ሥራዎች ላይ በማሳተፍ በጋራ ሰላምና ጥቅም ላይ የተመሠረተ ቀጣናዊ ትስስርን አጠናክሯል።
በዚህም በአካባቢው ሀገራት መካከል የጋራ መተማመንን በመገንባት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች ይበልጥ እንዲጠናከሩ አስችሏል።
አረንጓዴ ዐሻራ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞችን በጋራ ከመትከል ባሻገር የተተከሉትን በመንከባከብ በዜጎች ዘንድ የባለቤትነት ስሜት እንዲዳብር አድርጓል።
በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂ የታገዘ የዲጂታል ልህቀትን ከአረንጓዴ ዐሻራ ጋር በማጣመር ለቀጣዩ ትውልድ የማይጠፋ የልማት ዐሻራ እያኖረች ነው።
በጥቅሉ የኢትዮጵያን የብልጽግና ጉዞ በማፋጠን ላይ የሚገኘው የዚህ አረንጓዴ አብዮት ስኬት፣ ሕዝብ ለሀገሩ በአንድነት ሲቆም ምን ያህል ታላላቅ ሥራዎችን መከወን እንደሚችል ሕያው ምስክር ነው።
በሃና ምንዳሁን
#ethiopia #climateaction #greenlegacy #greendiplomacy #sustainabledevelopment #nationalpride #ebc
Sponsored by
Surafel
2 months ago
የመደመር አንቀጽ
ሀገራዊ ምክክር፡- በሀገራችን የሚደረገው ሀገራዊ ምክክር የተለያዩ ሐሳቦች በአንድ መድረክ ቀርበው፣ በውይይትና በምክክር ጎልብተው፣ አሰባሳቢና አስማሚ ሆነው የሚወጡበት መድረክ ነው። ሁሉም ስለ ሀገር የሚያገባው አካል በመሠረታዊ ጉዳዮች ላይ አዋጥቶና ተነጋግሮ መግባባት የሚፈጥርበት ምኅዳር ነው። በውይይትና በምክክር ወደ መግባባት የሚደረስበት መንገድ ነው።
በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ከገጠሙን እጥረቶች አንዱ ሀገራዊ ምክክር ነው። በሀገረ መንግሥት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ሕዝብ ተመካክሮ፣ የጋራ መግባባት ላይ ደርሶ፣ የተግባባባቸውን በሕግና በሥርዓት አጽንቶ፣ ያልተግባባባቸውን ደግሞ ለወደፊት ምክክሮች አቆይቶ አልተጓዘም። በዚህ የተነሣ በየጊዜው ቅሬታ፣ ኩርፊያ፣ አብዮት፣ ዐመጽ ይፈጠራል። ነገሮች በተናጠል እየቀረቡ ለፖለቲካ ነጋዴዎች ምቹ ሁኔታ ይመቻቻል። ሁለንተናዊ ዕይታ ይጠፋል። ሀገራዊ ምክክር ይሄን የዘመናት ስብራት የሚጠግን ነው::
የመደመር መንግሥት
ገጽ 384
ሀገራዊ ምክክር፡- በሀገራችን የሚደረገው ሀገራዊ ምክክር የተለያዩ ሐሳቦች በአንድ መድረክ ቀርበው፣ በውይይትና በምክክር ጎልብተው፣ አሰባሳቢና አስማሚ ሆነው የሚወጡበት መድረክ ነው። ሁሉም ስለ ሀገር የሚያገባው አካል በመሠረታዊ ጉዳዮች ላይ አዋጥቶና ተነጋግሮ መግባባት የሚፈጥርበት ምኅዳር ነው። በውይይትና በምክክር ወደ መግባባት የሚደረስበት መንገድ ነው።
በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ከገጠሙን እጥረቶች አንዱ ሀገራዊ ምክክር ነው። በሀገረ መንግሥት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ሕዝብ ተመካክሮ፣ የጋራ መግባባት ላይ ደርሶ፣ የተግባባባቸውን በሕግና በሥርዓት አጽንቶ፣ ያልተግባባባቸውን ደግሞ ለወደፊት ምክክሮች አቆይቶ አልተጓዘም። በዚህ የተነሣ በየጊዜው ቅሬታ፣ ኩርፊያ፣ አብዮት፣ ዐመጽ ይፈጠራል። ነገሮች በተናጠል እየቀረቡ ለፖለቲካ ነጋዴዎች ምቹ ሁኔታ ይመቻቻል። ሁለንተናዊ ዕይታ ይጠፋል። ሀገራዊ ምክክር ይሄን የዘመናት ስብራት የሚጠግን ነው::
የመደመር መንግሥት
ገጽ 384
2 months ago
ዓለም በዝምታ ቢያዘግምም ኢትዮጵያ ምድርን እያከመች ነው!
********************
በዓለማችን ላይ አሳዛኝ እና ዐይን ያወጣ ኢፍትሐዊነት ቢኖር፣ ምድራችንን በበካይ ጋዝ እያፈኗት ያሉት ኃያላን ሀገራት ሲሆኑ፣ የጥፋታቸው ገፈት ቀማሽ ደግሞ ለብክለቱ ኢምንት የማያበረክቱ ደሃ ሀገራት መሆናቸው ነው።
አስቡት፤ አጠቃላይ የዓለማችንን የበካይ ጋዝ ልቀት ከ75 እስከ 80 በመቶ የሚያመነጩት ግዙፍ ኢኮኖሚ ያላቸው የቡድን 20 ሀገራት ናቸው።
በአንጻሩ፣ 54 ሀገራትን አቅፋ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት አፍሪካ ለዚህ በካይ ጋዝ ያላት አስተዋፅኦ ከ3 እስከ 4 በመቶ ብቻ ነው። ይሁን እንጂ ኢትዮጵያን ጨምሮ አፍሪካውያን ለችግሩ ያበረከቱት አስተዋፅኦ እዚህ ግባ የሚባል ባይሆንም በድርቅ፣ በጎርፍ እና በሙቀት መጨመር ግንባር ቀደም ሰለባ ሆነው ዘመናትን አሳልፈዋል።
የፈረሱ ስምምነቶች እና የወረቀት ላይ ቃላት
የኢንዱስትሪ ባለቤቶች የሆኑት እነዚህ ኃያላን ሀገራት፣ ምድርን በካርቦን ጋዝ እያፈኗት መሆኑን አምነው፣ ልቀትን ለማስቀረትና ለችግሩ ሰለባ ለሆኑት ሀገራት ካሳ ለመክፈል በፓሪስ ታሪካዊ ስምምነት ፈረሙ።
ነገር ግን ዘመናት ተቆጠሩ፤ የወረቀት ላይ ቃላት ወደ ተግባር ሳይቀየሩ፣ ስምምነቶች የሚዲያ ፍጆታ ብቻ ሆነው ቀሩ። በኃያላኑ ቸልተኝነትና ቃል ማጠፍ ምክንያት ዓለማችን በድርቅ፣ በጎርፍ መጥለቅለቅ፣ በበረሃማነት መስፋፋት እና ባልተጠበቀ የአየር ጸባይ መዛባት ክፉኛ መታመሷን ቀጥላለች።
ከንግግር ወደ ተግባር፤ የኢትዮጵያ አረንጓዴ አብዮት
ዓለም መፍትሔ አጥቶ በየስብሰባ አዳራሹ ሲባዝን፣ ቃሉን ሲያጥፍና ከንግግር ያለፈ አንዳች መፍትሔ ማምጣት ሲሳነው፣ ኢትዮጵያ ግን እጆቿን አጣጥፋ የኃያላኑን ምፅዋት አልጠበቀችም። ይልቁንም ተፈጥሮን እና አካባቢን ለማከም ቆርጣ በመነሳት ዓለምን ያስደመመ ተዓምራዊ የድል ትርክት መፃፍ ጀመረች።
ይህ ታሪካዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ጉዞ፣ በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በይፋ ሲበሰር፣ ገና በዕለቱ 350 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር በመትከል የህንድን የዓለም ክብረ-ወሰን በታላቅ ጀግንነት በመስበር ነበር የተጀመረው።
ዓለም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ክፉኛ በተረበሸችበት በ2012 ዓ.ም እንኳን፣ ኢትዮጵያውያን ተስፋ ሳይቆርጡ 5 ቢሊዮን ችግኞችን በመትከል ጽናታቸውን አሳይተዋል። በ2013 እና 2014 ዓ.ም ከ6 ነጥብ 8 እና 7 ነጥብ 2 ቢሊዮን በላይ ችግኞች በምድሪቱ ላይ ሲያርፉ፣ እንደ ሐሮማያ ሐይቅ ያሉ ጠፍተው የነበሩ የውሃ አካላት ዳግም ህያው ሆነዋል።
የድል መዳረሻዎቻችን በዚህ አላበቁም፤ በ2015 ዓ.ም ለምግብ ዋስትና የሚሆኑ የፍራፍሬ ተክሎች ላይ በማተኮር 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች ተተከሉ። በ2016 ዓ.ም ይህ አሃዝ ወደ 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ሲሻገር፣ በአንድ ጀንበር ብቻ ከ600 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል የራሳችንን ክብረ-ወሰን ደግመን ሰበርን።
በመጨረሻም በ2017 ዓ.ም ከ8 ቢሊዮን በላይ ዐሻራዎችን በማኖር፣ በሰባት ዓመታት ጉዞ ብቻ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል ኢትዮጵያ በዓለም የደን ልማት መዝገብ ላይ ወደር የማይገኝለት የልዕልና ስፍራ ተቀመጠች። በየዓመቱ ከ25 እስከ 35 ሚሊዮን ዜጎች በፈቃደኝነት የሚሳተፉበት ይህ ግዙፍ ንቅናቄ፣ ብሔራዊ አንድነትን ያጠናከረ የአረንጓዴ ማዕበል ሆኗል።
ይህ የ7 ዓመታት ጉዞ ያመጣው ሥነ-ምህዳራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተዓምር ቃላት ከሚገልጹት በላይ ነው። አስቀድሞ ወደ 3 በመቶ አሽቆልቁሎ የነበረው የሀገራችን የደን ሽፋን፣ በማይታመን ፍጥነት አድጎ 23 ነጥብ 6 በመቶ ደርሷል።
የተተከሉት ችግኞች ከ80 እስከ 85 በመቶ በሚደርስ የፅድቀት ምጣኔ ጸድቀው፣ በአማካይ 64 ሚሊዮን በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች የሚያወጡትን በካይ ጋዝ ከከባቢ አየር ላይ በማጽዳት ዓለምን እየታደጉ ይገኛሉ።
መሬቱ ውሃን የመምጠጥ አቅሙ ከ16 ነጥብ 9 በመቶ ወደ 68 ነጥብ 9 በመቶ በከፍተኛ ደረጃ በማደጉ፣ የተፋሰስ ልማቱ ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጨምሮ የሌሎች የኃይል ማመንጫ ግድቦችን የዕድሜ ጣሪያ ቢያንስ በ50 ዓመታት እንዲራዘም አድርጓል።
ከዚህም ባሻገር በተቋቋሙ ከ120 ሺህ በላይ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ለሚበልጡ ዜጎች የስራ ዕድል ሲፈጠር፤ ተፈጥሮ በማገገሟም የሀገራችን የቡና ወጪ ንግድ ከ230 ሺህ ቶን ወደ 475 ሺህ ቶን በማደግ ትልቅ የውጭ ምንዛሪ እያስገኘ ነው።
በአጠቃላይ፣ ኃያላን ሀገራት ዛሬም ስለ አየር ንብረት ለውጥ ይነጋገራሉ፣ ስምምነት ያፈርሳሉ፣ ይከራከራሉ። ኢትዮጵያ ግን ንግግርን ወደ ተግባር ቀይራ፣ ቆስላ የነበረችውን ምድር በቢሊዮኖች አረንጓዴ ዐሻራ በተግባር እያከመች ነው።
አረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ የመትከል ዘመቻ ብቻ ሳይሆን፣ ተፈጥሮን ማዳን፣ ማክሮ-ኢኮኖሚን መገንባት እና ትውልድን ማሻገር መሆኑን አሃዞች አፍ አውጥተው እየመሰከሩ ነው።
የዓለምን የሥነ-ምህዳር ህመም ለመፈወስ እውነተኛው እና ህያው መድኃኒት ከኢትዮጵያ ተገኝቷል፤ ወደ 50 ቢሊዮን የሚያልመው የድል ትርክታችንም በብልጽግና ጎዳና ላይ አሁንም ተጠናክሮ ይቀጥላል።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #climatechange #greenlegacy #climateresilience
********************
በዓለማችን ላይ አሳዛኝ እና ዐይን ያወጣ ኢፍትሐዊነት ቢኖር፣ ምድራችንን በበካይ ጋዝ እያፈኗት ያሉት ኃያላን ሀገራት ሲሆኑ፣ የጥፋታቸው ገፈት ቀማሽ ደግሞ ለብክለቱ ኢምንት የማያበረክቱ ደሃ ሀገራት መሆናቸው ነው።
አስቡት፤ አጠቃላይ የዓለማችንን የበካይ ጋዝ ልቀት ከ75 እስከ 80 በመቶ የሚያመነጩት ግዙፍ ኢኮኖሚ ያላቸው የቡድን 20 ሀገራት ናቸው።
በአንጻሩ፣ 54 ሀገራትን አቅፋ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት አፍሪካ ለዚህ በካይ ጋዝ ያላት አስተዋፅኦ ከ3 እስከ 4 በመቶ ብቻ ነው። ይሁን እንጂ ኢትዮጵያን ጨምሮ አፍሪካውያን ለችግሩ ያበረከቱት አስተዋፅኦ እዚህ ግባ የሚባል ባይሆንም በድርቅ፣ በጎርፍ እና በሙቀት መጨመር ግንባር ቀደም ሰለባ ሆነው ዘመናትን አሳልፈዋል።
የፈረሱ ስምምነቶች እና የወረቀት ላይ ቃላት
የኢንዱስትሪ ባለቤቶች የሆኑት እነዚህ ኃያላን ሀገራት፣ ምድርን በካርቦን ጋዝ እያፈኗት መሆኑን አምነው፣ ልቀትን ለማስቀረትና ለችግሩ ሰለባ ለሆኑት ሀገራት ካሳ ለመክፈል በፓሪስ ታሪካዊ ስምምነት ፈረሙ።
ነገር ግን ዘመናት ተቆጠሩ፤ የወረቀት ላይ ቃላት ወደ ተግባር ሳይቀየሩ፣ ስምምነቶች የሚዲያ ፍጆታ ብቻ ሆነው ቀሩ። በኃያላኑ ቸልተኝነትና ቃል ማጠፍ ምክንያት ዓለማችን በድርቅ፣ በጎርፍ መጥለቅለቅ፣ በበረሃማነት መስፋፋት እና ባልተጠበቀ የአየር ጸባይ መዛባት ክፉኛ መታመሷን ቀጥላለች።
ከንግግር ወደ ተግባር፤ የኢትዮጵያ አረንጓዴ አብዮት
ዓለም መፍትሔ አጥቶ በየስብሰባ አዳራሹ ሲባዝን፣ ቃሉን ሲያጥፍና ከንግግር ያለፈ አንዳች መፍትሔ ማምጣት ሲሳነው፣ ኢትዮጵያ ግን እጆቿን አጣጥፋ የኃያላኑን ምፅዋት አልጠበቀችም። ይልቁንም ተፈጥሮን እና አካባቢን ለማከም ቆርጣ በመነሳት ዓለምን ያስደመመ ተዓምራዊ የድል ትርክት መፃፍ ጀመረች።
ይህ ታሪካዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ጉዞ፣ በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በይፋ ሲበሰር፣ ገና በዕለቱ 350 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር በመትከል የህንድን የዓለም ክብረ-ወሰን በታላቅ ጀግንነት በመስበር ነበር የተጀመረው።
ዓለም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ክፉኛ በተረበሸችበት በ2012 ዓ.ም እንኳን፣ ኢትዮጵያውያን ተስፋ ሳይቆርጡ 5 ቢሊዮን ችግኞችን በመትከል ጽናታቸውን አሳይተዋል። በ2013 እና 2014 ዓ.ም ከ6 ነጥብ 8 እና 7 ነጥብ 2 ቢሊዮን በላይ ችግኞች በምድሪቱ ላይ ሲያርፉ፣ እንደ ሐሮማያ ሐይቅ ያሉ ጠፍተው የነበሩ የውሃ አካላት ዳግም ህያው ሆነዋል።
የድል መዳረሻዎቻችን በዚህ አላበቁም፤ በ2015 ዓ.ም ለምግብ ዋስትና የሚሆኑ የፍራፍሬ ተክሎች ላይ በማተኮር 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች ተተከሉ። በ2016 ዓ.ም ይህ አሃዝ ወደ 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ሲሻገር፣ በአንድ ጀንበር ብቻ ከ600 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል የራሳችንን ክብረ-ወሰን ደግመን ሰበርን።
በመጨረሻም በ2017 ዓ.ም ከ8 ቢሊዮን በላይ ዐሻራዎችን በማኖር፣ በሰባት ዓመታት ጉዞ ብቻ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል ኢትዮጵያ በዓለም የደን ልማት መዝገብ ላይ ወደር የማይገኝለት የልዕልና ስፍራ ተቀመጠች። በየዓመቱ ከ25 እስከ 35 ሚሊዮን ዜጎች በፈቃደኝነት የሚሳተፉበት ይህ ግዙፍ ንቅናቄ፣ ብሔራዊ አንድነትን ያጠናከረ የአረንጓዴ ማዕበል ሆኗል።
ይህ የ7 ዓመታት ጉዞ ያመጣው ሥነ-ምህዳራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተዓምር ቃላት ከሚገልጹት በላይ ነው። አስቀድሞ ወደ 3 በመቶ አሽቆልቁሎ የነበረው የሀገራችን የደን ሽፋን፣ በማይታመን ፍጥነት አድጎ 23 ነጥብ 6 በመቶ ደርሷል።
የተተከሉት ችግኞች ከ80 እስከ 85 በመቶ በሚደርስ የፅድቀት ምጣኔ ጸድቀው፣ በአማካይ 64 ሚሊዮን በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች የሚያወጡትን በካይ ጋዝ ከከባቢ አየር ላይ በማጽዳት ዓለምን እየታደጉ ይገኛሉ።
መሬቱ ውሃን የመምጠጥ አቅሙ ከ16 ነጥብ 9 በመቶ ወደ 68 ነጥብ 9 በመቶ በከፍተኛ ደረጃ በማደጉ፣ የተፋሰስ ልማቱ ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጨምሮ የሌሎች የኃይል ማመንጫ ግድቦችን የዕድሜ ጣሪያ ቢያንስ በ50 ዓመታት እንዲራዘም አድርጓል።
ከዚህም ባሻገር በተቋቋሙ ከ120 ሺህ በላይ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ለሚበልጡ ዜጎች የስራ ዕድል ሲፈጠር፤ ተፈጥሮ በማገገሟም የሀገራችን የቡና ወጪ ንግድ ከ230 ሺህ ቶን ወደ 475 ሺህ ቶን በማደግ ትልቅ የውጭ ምንዛሪ እያስገኘ ነው።
በአጠቃላይ፣ ኃያላን ሀገራት ዛሬም ስለ አየር ንብረት ለውጥ ይነጋገራሉ፣ ስምምነት ያፈርሳሉ፣ ይከራከራሉ። ኢትዮጵያ ግን ንግግርን ወደ ተግባር ቀይራ፣ ቆስላ የነበረችውን ምድር በቢሊዮኖች አረንጓዴ ዐሻራ በተግባር እያከመች ነው።
አረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ የመትከል ዘመቻ ብቻ ሳይሆን፣ ተፈጥሮን ማዳን፣ ማክሮ-ኢኮኖሚን መገንባት እና ትውልድን ማሻገር መሆኑን አሃዞች አፍ አውጥተው እየመሰከሩ ነው።
የዓለምን የሥነ-ምህዳር ህመም ለመፈወስ እውነተኛው እና ህያው መድኃኒት ከኢትዮጵያ ተገኝቷል፤ ወደ 50 ቢሊዮን የሚያልመው የድል ትርክታችንም በብልጽግና ጎዳና ላይ አሁንም ተጠናክሮ ይቀጥላል።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #climatechange #greenlegacy #climateresilience
2 months ago
የ5ቱ ዓመታት ገፆች፦ የኢትዮጵያ ዲጂታል ክፍያ ሥርዓት እመርታ እና የኢኮኖሚው አዲስ ምዕራፍ
*********************
ባለፉት አምስት ዓመታት በሀገራችን የተከናወኑ መጠነ ሰፊ የዲጂታል መሠረተ ልማት ግንባታዎችና የፖሊሲ ማሻሻያዎች በኢትዮጵያ የክፍያ ሥርዓት ላይ ታላቅ አብዮት ፈጥረዋል።
"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" እና "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂዎች ይፋ ከሆኑ ወዲህ፣ በኢትዮጵያ ከባህላዊው የጥሬ ገንዘብ ዝውውር ወደ ዘመናዊው የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት ያደረገችው ሽግግር አስገራሚ ዕድገት አስመዝግቧል።
ቀደም ሲል በኦፕሬተር የሚመራ የሞባይል ገንዘብ ሥርዓት ባለመኖሩ የጥሬ ገንዘብ ጥገኝነት መላቀቅ ተስኖ የነበረ ቢሆንም፣ የፖሊሲ ማሻሻያ ተደርጎ የኢትዮ ቴሌኮም "ቴሌብር" ወደ ሥራ መግባቱ ሁኔታዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ቀይሮታል።
ቴሌብር በሦስት ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከ45 ሚሊዮን በላይ ተጠቃሚዎችን ማፍራቱ የሀገራችንን የዲጂታል አቅም ለዓለም ያሳየ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የሞባይል ዋሌት አካውንቶች ቁጥር 161 ሚሊዮን በላይ ደርሷል።
ይህም ከአጠቃላይ የሕዝብ ቁጥር በላይ መሆኑ የአገልግሎቱን ተደራሽነት የሚያሳይ ሲሆን፣ በፕላትፎርሙ የሚከናወነው የገንዘብ ዝውውርም ከኢትዮጵያ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) 82 በመቶ ደርሷል።
ይህ የዲጂታል ክፍያ አብዮት ለሀገራዊ ኢኮኖሚው በርካታ ጥቅሞችን እያስገኘ ይገኛል።
የመጀመሪያው የፋይናንስ አካታችነት ሲሆን፣ የባንክ አገልግሎት ባልደረሰባቸው ገጠራማ አካባቢዎች ዜጎች በስልካቸው ብቻ ገንዘብ መቆጠብ፣ መላክ እና መቀበል በመቻላቸው ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች ወደ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴው እንዲገቡ አድርጓል።
በሌላ በኩል፣ መንግሥት እንደ ነዳጅ ግብይት፣ የትራፊክ ቅጣት፣ የግብር ክፍያ እና የውኃና መብራት አገልግሎቶችን በዲጂታል መንገድ በማድረጉ ብክነትን በመቀነስ ገቢው በቀጥታ ወደ ካዝናው እንዲገባ አስችሏል፤ ለምሳሌ የነዳጅ ግብይት በዲጂታል ብቻ መሆኑ ሕገ-ወጥ ዝውውርን በከፍተኛ ሁኔታ ቀንሷል።
በተጨማሪም ብሔራዊ ባንክ ለገንዘብ ሕትመትና ጥገና የሚያወጣውን በቢሊዮን የሚቆጠር የውጭ ምንዛሬ ለማዳን የተቻለ ሲሆን፣ የገንዘብ ምንጭና መድረሻው ስለሚታወቅ ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለመከላከልና የጥቁር ገበያን ለመቆጣጠር የተሻለ አቅም ተፈጥሯል።
ባጠቃላይ ይህ ዕድገት ወደ ዘመናዊ ኢኮኖሚ ለምናደርገው ጉዞ ትልቅ ሞተር እየሆነ ሲሆን፣ ዘርፉ በፖሊሲ መደገፉን መቀጠሉ ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ ከሆኑት የዲጂታል ምጣኔ ሀብት ተጠቃሚ ሀገራት ተርታ እንደሚያሰልፋት ይጠበቃል።
በላሉ ኢታላ
#digitalethiopia #telebirr #cashlesssociety #digitaleconomy #ethiopianbroadcastingcorporation Ethiopian Broadcasting Corporation
*********************
ባለፉት አምስት ዓመታት በሀገራችን የተከናወኑ መጠነ ሰፊ የዲጂታል መሠረተ ልማት ግንባታዎችና የፖሊሲ ማሻሻያዎች በኢትዮጵያ የክፍያ ሥርዓት ላይ ታላቅ አብዮት ፈጥረዋል።
"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" እና "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂዎች ይፋ ከሆኑ ወዲህ፣ በኢትዮጵያ ከባህላዊው የጥሬ ገንዘብ ዝውውር ወደ ዘመናዊው የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት ያደረገችው ሽግግር አስገራሚ ዕድገት አስመዝግቧል።
ቀደም ሲል በኦፕሬተር የሚመራ የሞባይል ገንዘብ ሥርዓት ባለመኖሩ የጥሬ ገንዘብ ጥገኝነት መላቀቅ ተስኖ የነበረ ቢሆንም፣ የፖሊሲ ማሻሻያ ተደርጎ የኢትዮ ቴሌኮም "ቴሌብር" ወደ ሥራ መግባቱ ሁኔታዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ቀይሮታል።
ቴሌብር በሦስት ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከ45 ሚሊዮን በላይ ተጠቃሚዎችን ማፍራቱ የሀገራችንን የዲጂታል አቅም ለዓለም ያሳየ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የሞባይል ዋሌት አካውንቶች ቁጥር 161 ሚሊዮን በላይ ደርሷል።
ይህም ከአጠቃላይ የሕዝብ ቁጥር በላይ መሆኑ የአገልግሎቱን ተደራሽነት የሚያሳይ ሲሆን፣ በፕላትፎርሙ የሚከናወነው የገንዘብ ዝውውርም ከኢትዮጵያ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) 82 በመቶ ደርሷል።
ይህ የዲጂታል ክፍያ አብዮት ለሀገራዊ ኢኮኖሚው በርካታ ጥቅሞችን እያስገኘ ይገኛል።
የመጀመሪያው የፋይናንስ አካታችነት ሲሆን፣ የባንክ አገልግሎት ባልደረሰባቸው ገጠራማ አካባቢዎች ዜጎች በስልካቸው ብቻ ገንዘብ መቆጠብ፣ መላክ እና መቀበል በመቻላቸው ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች ወደ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴው እንዲገቡ አድርጓል።
በሌላ በኩል፣ መንግሥት እንደ ነዳጅ ግብይት፣ የትራፊክ ቅጣት፣ የግብር ክፍያ እና የውኃና መብራት አገልግሎቶችን በዲጂታል መንገድ በማድረጉ ብክነትን በመቀነስ ገቢው በቀጥታ ወደ ካዝናው እንዲገባ አስችሏል፤ ለምሳሌ የነዳጅ ግብይት በዲጂታል ብቻ መሆኑ ሕገ-ወጥ ዝውውርን በከፍተኛ ሁኔታ ቀንሷል።
በተጨማሪም ብሔራዊ ባንክ ለገንዘብ ሕትመትና ጥገና የሚያወጣውን በቢሊዮን የሚቆጠር የውጭ ምንዛሬ ለማዳን የተቻለ ሲሆን፣ የገንዘብ ምንጭና መድረሻው ስለሚታወቅ ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለመከላከልና የጥቁር ገበያን ለመቆጣጠር የተሻለ አቅም ተፈጥሯል።
ባጠቃላይ ይህ ዕድገት ወደ ዘመናዊ ኢኮኖሚ ለምናደርገው ጉዞ ትልቅ ሞተር እየሆነ ሲሆን፣ ዘርፉ በፖሊሲ መደገፉን መቀጠሉ ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ ከሆኑት የዲጂታል ምጣኔ ሀብት ተጠቃሚ ሀገራት ተርታ እንደሚያሰልፋት ይጠበቃል።
በላሉ ኢታላ
#digitalethiopia #telebirr #cashlesssociety #digitaleconomy #ethiopianbroadcastingcorporation Ethiopian Broadcasting Corporation
2 months ago
የ5ቱ ዓመታት ገፆች፦ መደመር ያዋለዳቸው የገበታ ፕሮጀክቶች
**************
ታሪክ በየዘመኑ የራሱን ዐሻራ ጥሎ ያልፋል። ከስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ አንስቶ ወደ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዋዜማ ስንሸጋገር የተፃፉት የአምስቱ ዓመታት ገፆች ደግሞ፣ ኢትዮጵያ ድብቅ የተፈጥሮ ውበቷንና ፀዳሏን አውጥታ ለዓለም ያሳየችባቸው የውበት አብዮት ድርሳናት ናቸው።
ለዘመናት "የ13 ወር ፀጋ" በሚለው የቱሪዝም መሪ ቃል ብቻ ስትጠራ የነበረችው ሀገራችን፣ ዛሬ ከመፈክር ባለፈ "ምድረ ቀደምት" በሚለው ከፍታዋ ልክ በተጨባጭ በዓለም አቀፍ መድረክ ደምቃ እንድትታይ ያደረጋት አስደናቂ የታሪክ እጥፋት ተፈጥሯል። የዚህ ታላቅ ሀገራዊ ትራንስፎርሜሽን የጀርባ አጥንትና ሞተር ደግሞ ከመደመር እሳቤ የተወለዱት የ"ገበታ" ፕሮጀክቶች ናቸው።
የገበታ ፕሮጀክቶች “ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ” ተራ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች አይደሉም። ይልቁንም ሃብትን አስተባብሮ ከተፈጥሮ ፀጋዎች ጋር በማዋሀድ ኢትዮጵያን ወደ ተፈጥሯዊ የቱሪዝም መስህብነት የቀየሩና ከመደመር እሳቤ የፈለቁ እውነተኛ ኢትዮጵያዊ ትርክቶች ናቸው። የመደመር ትውልድ ሀገርን ማልማት ማለት የውጭ ዕርዳታን መጠበቅ ሳይሆን፣ የራስን እምቅ አቅም፣ የተፈጥሮ ውበትና ታሪክን ወደ ኢኮኖሚያዊ እሴት መቀየር መሆኑን በተግባር አሳይቶበታል።
ይህ የገበታ ጉዞ የተጀመረው በ"ገበታ ለሸገር" ሲሆን፣ ለዘመናት በቆሻሻ ተውጠው የነበሩ የከተማ ቦታዎችንና የተተው ተራራዎችን ወደ ምድር ገነት ቀይሯቸዋል። ጫካና ገደል የነበረው የእንጦጦ ተራራ ወደ ማራኪው "እንጦጦ ፓርክ" ሲቀየር፣ የአዲስ አበባን የልብ ትርታ ያደሰው "ወዳጅነት ፓርክ" እና ታሪክን ከተፈጥሮ ጋር ያዋሀደው ግዙፉ "አንድነት ፓርክ" የዚህ ስኬት በኩር ፍሬዎች ሆነዋል።
ይህ ስኬት በመዲናዋ ብቻ አልተገታም፤ የመደመር እሳቤ "ገበታ ለሀገር" በሚል አዲስ ሀገራዊ ንቅናቄ መላዋን ኢትዮጵያ አዳረሰ። ማራኪው የ"ወንጪ" ሐይቅ ከተፈጥሮ አቀማመጡ ጋር በተዋሀደ መልኩ በዓለም አቀፍ ስታንዳርድ ለቱሪዝም ክፍት ሆነ። የጣናን ሐይቅ ሞገድ የሚያማትረው የ"ጎርጎራ" ፕሮጀክት ታሪካዊቷን ከተማ ዳግም ሲያነቃ፣ በደቡብ ምዕራብ የሚገኘው "ኮይሻ" እና የታላቁ ሸለቆ ድንቅ ስጦታ የሆነው "ሀላላ ኬላ ሎጅ" እንዲሁም በጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ የተገነባው “ጨበራ የዝሆን ዳና ሎጅ” የኢትዮጵያን የተፈጥሮ ውበትና የባህል ብዝኃነት ቁልጭ አድርገው አሳይተዋል።
በዚህ ያላቆመው የመደመር ትውልድ "ገበታ ለትውልድ" በማለት ሌላ ምዕራፍ ከፈተ። የደንዲ ሐይቅ፣ የጢስ አባይ ፏፏቴ፣ የጅማ ዞን ቦንጋ አካባቢ እና የሶፍ ኡመር ዋሻን ጨምሮ በርካታ ድንቅ የቱሪስት መዳረሻዎች በተፈጥሮ ላይ ምንም ዓይነት አሉታዊ ተፅዕኖ በማያሳድር (eco-friendly) እና ከዓለም አቀፍ ስታንዳርድ ጋር በተናበበ አኳኋን እየተገነቡ ይገኛሉ።
እነዚህ ሁሉ የገበታ ፕሮጀክቶች ስኬታማ ሊሆኑ የቻሉበት ትልቁ ምስጢር የሥራ ባህል ለውጥ ነው። ፕሮጀክቶቹ የተመሩት "ጥራትና ፍጥነት"ን ባማከለ ጽኑ መርህ ነው። ለዘመናት ሲንከባለሉና ሲጓተቱ የነበሩ የመንግሥት ፕሮጀክቶችን ልማድ በመስበር፣ የገበታ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው በጀት፣ በተቀመጠላቸው እጅግ አጭር ጊዜ እና ዓለም አቀፍ ጥራታቸውን በጠበቀ መልኩ ተጠናቅቀዋል። ፕሮጀክቶቹ ከተፈጥሮ ጋር የፈጠሩት አስደናቂ መስተጋብር ሳይነካ የአካባቢን ሥነ-ምህዳር በጠበቀ መልኩ የተከናወኑ በመሆናቸው፣ ሀገራችንን የዓለም ጎብኚዎች ተመራጭ መዳረሻ አድርገዋታል።
የገበታ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን እውነተኛ ፀዳል የገለጡ፣ የመደመር ትውልድ ሀገሩን በዓለም አቀፍ የቱሪዝም ካርታ ላይ ቀዳሚ ለማድረግ ያለውን ብቃት፣ ፍጥነትና የፈጠራ ጥበብ ያረጋገጡ ሕያው ሐውልቶች ናቸው።
ኢትዮጵያም "ምድረ ቀደምት" መሆኗን በኩራት እያወጀች፣ የተፈጥሮና የሰው ልጅ ጥበብ የተዋሀደበትን አዲሱን ገፅታዋን ለዓለም እየገለጠች ትገኛለች።
በአጠቃላይ፣ ከስድስተኛው እስከ ሰባተኛው ምርጫ የተጓዝንባቸው የአምስቱ ዓመታት ገፆች፣ የኢትዮጵያ ውበት ከግጥምና ከዘፈን ወጥቶ መሬት የነካባቸው የክብር ዘመናት ናቸው።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #tourism #ecotourism #greentourism #sustainabletourism #ebc
**************
ታሪክ በየዘመኑ የራሱን ዐሻራ ጥሎ ያልፋል። ከስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ አንስቶ ወደ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዋዜማ ስንሸጋገር የተፃፉት የአምስቱ ዓመታት ገፆች ደግሞ፣ ኢትዮጵያ ድብቅ የተፈጥሮ ውበቷንና ፀዳሏን አውጥታ ለዓለም ያሳየችባቸው የውበት አብዮት ድርሳናት ናቸው።
ለዘመናት "የ13 ወር ፀጋ" በሚለው የቱሪዝም መሪ ቃል ብቻ ስትጠራ የነበረችው ሀገራችን፣ ዛሬ ከመፈክር ባለፈ "ምድረ ቀደምት" በሚለው ከፍታዋ ልክ በተጨባጭ በዓለም አቀፍ መድረክ ደምቃ እንድትታይ ያደረጋት አስደናቂ የታሪክ እጥፋት ተፈጥሯል። የዚህ ታላቅ ሀገራዊ ትራንስፎርሜሽን የጀርባ አጥንትና ሞተር ደግሞ ከመደመር እሳቤ የተወለዱት የ"ገበታ" ፕሮጀክቶች ናቸው።
የገበታ ፕሮጀክቶች “ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ” ተራ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች አይደሉም። ይልቁንም ሃብትን አስተባብሮ ከተፈጥሮ ፀጋዎች ጋር በማዋሀድ ኢትዮጵያን ወደ ተፈጥሯዊ የቱሪዝም መስህብነት የቀየሩና ከመደመር እሳቤ የፈለቁ እውነተኛ ኢትዮጵያዊ ትርክቶች ናቸው። የመደመር ትውልድ ሀገርን ማልማት ማለት የውጭ ዕርዳታን መጠበቅ ሳይሆን፣ የራስን እምቅ አቅም፣ የተፈጥሮ ውበትና ታሪክን ወደ ኢኮኖሚያዊ እሴት መቀየር መሆኑን በተግባር አሳይቶበታል።
ይህ የገበታ ጉዞ የተጀመረው በ"ገበታ ለሸገር" ሲሆን፣ ለዘመናት በቆሻሻ ተውጠው የነበሩ የከተማ ቦታዎችንና የተተው ተራራዎችን ወደ ምድር ገነት ቀይሯቸዋል። ጫካና ገደል የነበረው የእንጦጦ ተራራ ወደ ማራኪው "እንጦጦ ፓርክ" ሲቀየር፣ የአዲስ አበባን የልብ ትርታ ያደሰው "ወዳጅነት ፓርክ" እና ታሪክን ከተፈጥሮ ጋር ያዋሀደው ግዙፉ "አንድነት ፓርክ" የዚህ ስኬት በኩር ፍሬዎች ሆነዋል።
ይህ ስኬት በመዲናዋ ብቻ አልተገታም፤ የመደመር እሳቤ "ገበታ ለሀገር" በሚል አዲስ ሀገራዊ ንቅናቄ መላዋን ኢትዮጵያ አዳረሰ። ማራኪው የ"ወንጪ" ሐይቅ ከተፈጥሮ አቀማመጡ ጋር በተዋሀደ መልኩ በዓለም አቀፍ ስታንዳርድ ለቱሪዝም ክፍት ሆነ። የጣናን ሐይቅ ሞገድ የሚያማትረው የ"ጎርጎራ" ፕሮጀክት ታሪካዊቷን ከተማ ዳግም ሲያነቃ፣ በደቡብ ምዕራብ የሚገኘው "ኮይሻ" እና የታላቁ ሸለቆ ድንቅ ስጦታ የሆነው "ሀላላ ኬላ ሎጅ" እንዲሁም በጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ የተገነባው “ጨበራ የዝሆን ዳና ሎጅ” የኢትዮጵያን የተፈጥሮ ውበትና የባህል ብዝኃነት ቁልጭ አድርገው አሳይተዋል።
በዚህ ያላቆመው የመደመር ትውልድ "ገበታ ለትውልድ" በማለት ሌላ ምዕራፍ ከፈተ። የደንዲ ሐይቅ፣ የጢስ አባይ ፏፏቴ፣ የጅማ ዞን ቦንጋ አካባቢ እና የሶፍ ኡመር ዋሻን ጨምሮ በርካታ ድንቅ የቱሪስት መዳረሻዎች በተፈጥሮ ላይ ምንም ዓይነት አሉታዊ ተፅዕኖ በማያሳድር (eco-friendly) እና ከዓለም አቀፍ ስታንዳርድ ጋር በተናበበ አኳኋን እየተገነቡ ይገኛሉ።
እነዚህ ሁሉ የገበታ ፕሮጀክቶች ስኬታማ ሊሆኑ የቻሉበት ትልቁ ምስጢር የሥራ ባህል ለውጥ ነው። ፕሮጀክቶቹ የተመሩት "ጥራትና ፍጥነት"ን ባማከለ ጽኑ መርህ ነው። ለዘመናት ሲንከባለሉና ሲጓተቱ የነበሩ የመንግሥት ፕሮጀክቶችን ልማድ በመስበር፣ የገበታ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው በጀት፣ በተቀመጠላቸው እጅግ አጭር ጊዜ እና ዓለም አቀፍ ጥራታቸውን በጠበቀ መልኩ ተጠናቅቀዋል። ፕሮጀክቶቹ ከተፈጥሮ ጋር የፈጠሩት አስደናቂ መስተጋብር ሳይነካ የአካባቢን ሥነ-ምህዳር በጠበቀ መልኩ የተከናወኑ በመሆናቸው፣ ሀገራችንን የዓለም ጎብኚዎች ተመራጭ መዳረሻ አድርገዋታል።
የገበታ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን እውነተኛ ፀዳል የገለጡ፣ የመደመር ትውልድ ሀገሩን በዓለም አቀፍ የቱሪዝም ካርታ ላይ ቀዳሚ ለማድረግ ያለውን ብቃት፣ ፍጥነትና የፈጠራ ጥበብ ያረጋገጡ ሕያው ሐውልቶች ናቸው።
ኢትዮጵያም "ምድረ ቀደምት" መሆኗን በኩራት እያወጀች፣ የተፈጥሮና የሰው ልጅ ጥበብ የተዋሀደበትን አዲሱን ገፅታዋን ለዓለም እየገለጠች ትገኛለች።
በአጠቃላይ፣ ከስድስተኛው እስከ ሰባተኛው ምርጫ የተጓዝንባቸው የአምስቱ ዓመታት ገፆች፣ የኢትዮጵያ ውበት ከግጥምና ከዘፈን ወጥቶ መሬት የነካባቸው የክብር ዘመናት ናቸው።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #tourism #ecotourism #greentourism #sustainabletourism #ebc
2 months ago
ከባንክ ሰልፍ ወደ አንድ ንክኪ፦ የኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ እውነታዎች
**********************
ዛሬ መረጃ እና ገንዘብ ፍጥነታቸውን ጨምረው በእጅ ስልካችን ውስጥ የገቡበት ዘመን ላይ ደርሰናል።
በትናንቱ የወረቀት የገንዘብ ቁጠባ ደብተር እና በባንክ ቅርንጫፎች ረጅም ሰልፍ የምናውቃት ኢትዮጵያ፣ ዛሬ በአንድ ንክኪ ወደሚፈጸም ዘመናዊ የዲጂታል አሠራር ተሸጋግራለች።
ይህ ሽግግር የቅንጦት ጉዳይ ሳይሆን የሀገርን የኢኮኖሚ ደኅንነት እና ነፃነት የማስከበር የ"ዲጂታል ኢኮኖሚ ሉዓላዊነት" ጉዳይ ነው።
ለመሆኑ ሀገራችን በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂ አማካኝነት እያካሄደችው ያለው ይህ አብዮት የት ደረሰ?
የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ቴክኖሎጂን በመግዛት ብቻ የሚመጣ ሳይሆን ሕዝብ፣ መንግሥት፣ ባንክ እና ቴሌኮም ተደምረው የሚፈጥሩት አዲስ ሀገራዊ አቅም ነው።
ቴሌብር ወይም የፋይዳ መታወቂያ ብቻቸውን የፋይናንስ ክፍተትን ሊሞሉ አይችሉም። ነገር ግን የፋይዳ መታወቂያ ከግብር ሥርዓቱ እና ከባንክ ጋር ሲተሳሰር የተሟላ የዲጂታል መሠረተ-ልማት ይሆናል።
ይህን መሠረት ይበልጥ ለማጠናከር የአፍሪካ የመጀመሪያው የሆነው የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ኢንስቲትዩት መቋቋሙ እና አሁን ደግሞ የሰው ሠራሽ ዩኒቨርሲቲ በሂደት ላይ መሆኑ ሀገራችን በዕውቀት ላይ ለተመሠረተው የነገ ኢኮኖሚ እየተዘጋጀች መሆኗን በተጨባጭ ያሳያል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የ"5 ሚሊዮን ኮደሮች" የዘመቻ ሥልጠና ሀገራችንን ለነገው ተወዳዳሪነት እያበቃት ይገኛል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የፋይናንስ ኢንዱስትሪውን ከመጭበርበር እና ከደኅንነት ሥጋት ለመጠበቅ የ"ፋይዳ" ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያን ከባንክ ሂሳብ ጋር ማገናኘትን ግዴታ ማድረጉ ይታወቃል።
በአሁኑ ወቅት ከ40 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት መሆን የቻሉ ሲሆን፣ የቁጥጥር ሥርዓቱም በጊዜ ገደብ እየተተገበረ ይገኛል።
በዚህም መሠረት በአዲስ አበባ፣ ሐረሪ እና 25 ዋና ዋና ከተሞች የመጨረሻው የጊዜ ገደብ ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም የነበረ ሲሆን፣ ያላገናኙ ደንበኞች ላይ የወጪ እገዳ ተጥሏል።
በተቀሩት ከተሞች እና የገጠር ቅርንጫፎች ደግሞ የመጨረሻው የጊዜ ገደብ ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ሲሆን፣ በተመሳሳይ የወጪ እገዳ ይጣልባቸዋል።
በውጭ ለሚኖሩ ዳያስፖራዎች ግን የ2 ዓመት ማቅለያ የተሰጣቸው በመሆኑ ጊዜያዊ እገዳ ሳይጣልባቸው መደበኛ ግብይት መቀጠል ይችላሉ።
በሌላ በኩል የቴሌኮም ዘርፉ ክፍት መደረግ እና የሳፋሪኮም ወደ ኢትዮጵያ ገበያ መግባት የቴሌኮም ሞኖፖልን በመስበር ጤናማ ውድድር ፈጥሯል።
ይህ ውድድር የ3G ኔትወርክ ሽፋንን በ50 በመቶ ሲያሳድግ፣ የ4G የሕዝብ ተደራሽነትን በ8 እጥፍ ማሳደግ ችሏል።
በአሁኑ ወቅት የኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ቁጥር 87.1 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን፣ የሞባይል ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ቁጥር 49 ሚሊዮንን አልፏል።
የብሮድባንድ ኢንተርኔት ተደራሽነትም በ2012 ዓ.ም ከነበረበት 20 በመቶ በታች አሁን ወደ 45 በመቶ ያደገ ሲሆን፣ የፋይበር ኦፕቲክስ መስመር ዝርጋታም 23 ሺህ 26 ኪሎ ሜትር ደርሷል።
ከዚህም በላይ የሀገራችን የሞባይል ክፍያ አካውንት በ2012 ዓ.ም ከነበረበት 12.2 ሚሊዮን አሁን ወደ 139.5 ሚሊዮን አድጓል።
በዚህ ዘርፍ የዲጂታል ክፍያ ፈርቀዳጅ የሆነው ቴሌብር የደንበኞቹን ቁጥር 58.61 ሚሊዮን ያደረሰ ሲሆን፣ በቴሌብር የተቀመጠው የጥቃቅን ቁጠባ መጠን 34.41 ቢሊዮን ብር ደርሶ ከመደበኛ ባንክ ውጭ ለነበሩ 16 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የጥቃቅን ብድር ማድረስ ተችሏል።
ሳፋሪኮም በበኩሉ ኤም-ፔሳን (M-Pesa) ከኢትዮ ስዊች ጋር በማዋሃድ የደንበኞቹን ቁጥር ከ5.2 ሚሊዮን በላይ አድርሷል።
ይህን ዕመርታ በስትራቴጂ ለመምራት የወጣው የBRIDGE 2030 ዕቅድ ደግሞ እስከ 2022 ዓ.ም ድረስ የዲጂታል ክፍያዎችን አጠቃላይ ዋጋ ከሀገራችን ጠቅላላ ምርት (GDP) አንፃር 750 በመቶ ለማድረስ አልሟል።
ኢኮኖሚውን ከጥቁር ገበያ አደጋ ለመታደግ እና የፍራንኮ ቫሉታ አሠራርን ግልጽ ለማድረግ በአዲሱ መመሪያ (FVD/01/2018 ዓ.ም) መሠረት ግዙፍ መዋቅራዊ ለውጥ ተደርጓል።
ማንኛውም የፍራንኮ ቫሉታ ግብይት ከግንቦት 2018 ዓ.ም ጀምሮ FEMoUS በተባለው የብሔራዊ ባንክ እና ጉምሩክ ኮሚሽን የተቀናጀ የዲጂታል ሥርዓት ውስጥ ማለፍ ግዴታ ሆኖ መደበኛ ያልሆኑ ነጋዴዎች እንዳይጠቀሙበት ተከልክሏል።
በዚህ አሠራር መሠረት የሐኪም ማዘዣ እና የጤና ሚኒስቴር የድጋፍ ደብዳቤ ያላቸው ለሕክምና የሚሆኑ አስቸኳይ መድኃኒቶች ምንም የዋጋ ገደብ የሌላቸው ሲሆን፣ ለዳያስፖራዎች እና የውጭ ባለሀብቶች በኢንቨስትመንት ፈቃድ እስከ 10 ሺህ ዶላር፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሚመጡ ዜጎች በነዋሪነት ፈቃድ እስከ 5 ሺህ ዶላር (ከቀረጥ ነፃ)፥ እንዲሁም ለንግድ ናሙናዎች ከሕጋዊ የንግድ ሥራ ጋር የሚያስተሳስር የጉምሩክ ሰነድ በማቅረብ እስከ 4 ሺህ ዶላር የገንዘብ ጣሪያ ተቀምጦባቸዋል።
በተጨማሪም መንግሥት ከብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት (NISS) ጋር በመሆን 657 ሕገወጥ የባንክ ሂሳቦችን ያገደ ሲሆን፣ ሸጌ፣ አዱሊስ፣ ታጅ እና ረመዳ የተባሉ 4 ሕገወጥ የሐዋላ ድርጅቶች እንዲዘጉ አድርጓል።
ብሔራዊ የገንዘብ ሉዓላዊነትን ለማስከበር እንደ ባይናንስ (Binance) እና ሜክስክስሲ (MEXC) ያሉ የክሪፕቶ መገበያያ መድረኮች ከኢትዮጵያ ገበያ ሙሉ በሙሉ እንዲወጡ ተደርጓል።
ይህ ደፋር እርምጃ የሀገር ውስጥ መረጃ ማከማቻ አሠራር ከመዘርጋቱ እና የዳታ ማስተላለፊያ ፍጥነት ከ500 ጊጋ ባይት በሰከንድ ወደ 3 ቴራ ባይት በሰከንድ ከፍ ካለበት ስኬት ጋር ተዳምሮ የውጭ ምንዛሬ ወጪን ለመታደግ አስችሏል።
ይህም የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙን በማገዝ የብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ ክምችትን ወደ 2.7 ቢሊዮን ዶላር ከፍ እንዲል እና የማክሮ-ኢኮኖሚ መረጋጋት እንዲፈጠር ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
የኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ሽግግር የሚያስተምረን ትልቁ እውነት ቴክኖሎጂ በራሱ ብቻ ተዓምር እንደማያመጣ ነው።
እውነተኛ እና ዘላቂ ልማት የሚረጋገጠው ቴክኖሎጂ ከተቋማዊ ውህደት፣ ከሕግ ቁጥጥር እና ከሕዝብ ተሳትፎ ጋር በ"መደመር" ፍልስፍና ሲቀናጅ ብቻ ነው።
ይህ ቅንጅት በተሳካ ሁኔታ ሲቀጥል፣ ዲጂታል ኢኮኖሚው ሀገርን ወደ ብሔራዊ ብልጽግና የሚመራ እውነተኛ የልማት ጎዳና መሆኑ ይረጋገጣል።
በበረከት ሽመልስ
#ethiopia #digitaleconomy #banking #digitalfinance #digitalethiopia #ebc
**********************
ዛሬ መረጃ እና ገንዘብ ፍጥነታቸውን ጨምረው በእጅ ስልካችን ውስጥ የገቡበት ዘመን ላይ ደርሰናል።
በትናንቱ የወረቀት የገንዘብ ቁጠባ ደብተር እና በባንክ ቅርንጫፎች ረጅም ሰልፍ የምናውቃት ኢትዮጵያ፣ ዛሬ በአንድ ንክኪ ወደሚፈጸም ዘመናዊ የዲጂታል አሠራር ተሸጋግራለች።
ይህ ሽግግር የቅንጦት ጉዳይ ሳይሆን የሀገርን የኢኮኖሚ ደኅንነት እና ነፃነት የማስከበር የ"ዲጂታል ኢኮኖሚ ሉዓላዊነት" ጉዳይ ነው።
ለመሆኑ ሀገራችን በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂ አማካኝነት እያካሄደችው ያለው ይህ አብዮት የት ደረሰ?
የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ቴክኖሎጂን በመግዛት ብቻ የሚመጣ ሳይሆን ሕዝብ፣ መንግሥት፣ ባንክ እና ቴሌኮም ተደምረው የሚፈጥሩት አዲስ ሀገራዊ አቅም ነው።
ቴሌብር ወይም የፋይዳ መታወቂያ ብቻቸውን የፋይናንስ ክፍተትን ሊሞሉ አይችሉም። ነገር ግን የፋይዳ መታወቂያ ከግብር ሥርዓቱ እና ከባንክ ጋር ሲተሳሰር የተሟላ የዲጂታል መሠረተ-ልማት ይሆናል።
ይህን መሠረት ይበልጥ ለማጠናከር የአፍሪካ የመጀመሪያው የሆነው የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ኢንስቲትዩት መቋቋሙ እና አሁን ደግሞ የሰው ሠራሽ ዩኒቨርሲቲ በሂደት ላይ መሆኑ ሀገራችን በዕውቀት ላይ ለተመሠረተው የነገ ኢኮኖሚ እየተዘጋጀች መሆኗን በተጨባጭ ያሳያል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የ"5 ሚሊዮን ኮደሮች" የዘመቻ ሥልጠና ሀገራችንን ለነገው ተወዳዳሪነት እያበቃት ይገኛል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የፋይናንስ ኢንዱስትሪውን ከመጭበርበር እና ከደኅንነት ሥጋት ለመጠበቅ የ"ፋይዳ" ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያን ከባንክ ሂሳብ ጋር ማገናኘትን ግዴታ ማድረጉ ይታወቃል።
በአሁኑ ወቅት ከ40 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት መሆን የቻሉ ሲሆን፣ የቁጥጥር ሥርዓቱም በጊዜ ገደብ እየተተገበረ ይገኛል።
በዚህም መሠረት በአዲስ አበባ፣ ሐረሪ እና 25 ዋና ዋና ከተሞች የመጨረሻው የጊዜ ገደብ ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም የነበረ ሲሆን፣ ያላገናኙ ደንበኞች ላይ የወጪ እገዳ ተጥሏል።
በተቀሩት ከተሞች እና የገጠር ቅርንጫፎች ደግሞ የመጨረሻው የጊዜ ገደብ ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ሲሆን፣ በተመሳሳይ የወጪ እገዳ ይጣልባቸዋል።
በውጭ ለሚኖሩ ዳያስፖራዎች ግን የ2 ዓመት ማቅለያ የተሰጣቸው በመሆኑ ጊዜያዊ እገዳ ሳይጣልባቸው መደበኛ ግብይት መቀጠል ይችላሉ።
በሌላ በኩል የቴሌኮም ዘርፉ ክፍት መደረግ እና የሳፋሪኮም ወደ ኢትዮጵያ ገበያ መግባት የቴሌኮም ሞኖፖልን በመስበር ጤናማ ውድድር ፈጥሯል።
ይህ ውድድር የ3G ኔትወርክ ሽፋንን በ50 በመቶ ሲያሳድግ፣ የ4G የሕዝብ ተደራሽነትን በ8 እጥፍ ማሳደግ ችሏል።
በአሁኑ ወቅት የኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ቁጥር 87.1 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን፣ የሞባይል ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ቁጥር 49 ሚሊዮንን አልፏል።
የብሮድባንድ ኢንተርኔት ተደራሽነትም በ2012 ዓ.ም ከነበረበት 20 በመቶ በታች አሁን ወደ 45 በመቶ ያደገ ሲሆን፣ የፋይበር ኦፕቲክስ መስመር ዝርጋታም 23 ሺህ 26 ኪሎ ሜትር ደርሷል።
ከዚህም በላይ የሀገራችን የሞባይል ክፍያ አካውንት በ2012 ዓ.ም ከነበረበት 12.2 ሚሊዮን አሁን ወደ 139.5 ሚሊዮን አድጓል።
በዚህ ዘርፍ የዲጂታል ክፍያ ፈርቀዳጅ የሆነው ቴሌብር የደንበኞቹን ቁጥር 58.61 ሚሊዮን ያደረሰ ሲሆን፣ በቴሌብር የተቀመጠው የጥቃቅን ቁጠባ መጠን 34.41 ቢሊዮን ብር ደርሶ ከመደበኛ ባንክ ውጭ ለነበሩ 16 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የጥቃቅን ብድር ማድረስ ተችሏል።
ሳፋሪኮም በበኩሉ ኤም-ፔሳን (M-Pesa) ከኢትዮ ስዊች ጋር በማዋሃድ የደንበኞቹን ቁጥር ከ5.2 ሚሊዮን በላይ አድርሷል።
ይህን ዕመርታ በስትራቴጂ ለመምራት የወጣው የBRIDGE 2030 ዕቅድ ደግሞ እስከ 2022 ዓ.ም ድረስ የዲጂታል ክፍያዎችን አጠቃላይ ዋጋ ከሀገራችን ጠቅላላ ምርት (GDP) አንፃር 750 በመቶ ለማድረስ አልሟል።
ኢኮኖሚውን ከጥቁር ገበያ አደጋ ለመታደግ እና የፍራንኮ ቫሉታ አሠራርን ግልጽ ለማድረግ በአዲሱ መመሪያ (FVD/01/2018 ዓ.ም) መሠረት ግዙፍ መዋቅራዊ ለውጥ ተደርጓል።
ማንኛውም የፍራንኮ ቫሉታ ግብይት ከግንቦት 2018 ዓ.ም ጀምሮ FEMoUS በተባለው የብሔራዊ ባንክ እና ጉምሩክ ኮሚሽን የተቀናጀ የዲጂታል ሥርዓት ውስጥ ማለፍ ግዴታ ሆኖ መደበኛ ያልሆኑ ነጋዴዎች እንዳይጠቀሙበት ተከልክሏል።
በዚህ አሠራር መሠረት የሐኪም ማዘዣ እና የጤና ሚኒስቴር የድጋፍ ደብዳቤ ያላቸው ለሕክምና የሚሆኑ አስቸኳይ መድኃኒቶች ምንም የዋጋ ገደብ የሌላቸው ሲሆን፣ ለዳያስፖራዎች እና የውጭ ባለሀብቶች በኢንቨስትመንት ፈቃድ እስከ 10 ሺህ ዶላር፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሚመጡ ዜጎች በነዋሪነት ፈቃድ እስከ 5 ሺህ ዶላር (ከቀረጥ ነፃ)፥ እንዲሁም ለንግድ ናሙናዎች ከሕጋዊ የንግድ ሥራ ጋር የሚያስተሳስር የጉምሩክ ሰነድ በማቅረብ እስከ 4 ሺህ ዶላር የገንዘብ ጣሪያ ተቀምጦባቸዋል።
በተጨማሪም መንግሥት ከብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት (NISS) ጋር በመሆን 657 ሕገወጥ የባንክ ሂሳቦችን ያገደ ሲሆን፣ ሸጌ፣ አዱሊስ፣ ታጅ እና ረመዳ የተባሉ 4 ሕገወጥ የሐዋላ ድርጅቶች እንዲዘጉ አድርጓል።
ብሔራዊ የገንዘብ ሉዓላዊነትን ለማስከበር እንደ ባይናንስ (Binance) እና ሜክስክስሲ (MEXC) ያሉ የክሪፕቶ መገበያያ መድረኮች ከኢትዮጵያ ገበያ ሙሉ በሙሉ እንዲወጡ ተደርጓል።
ይህ ደፋር እርምጃ የሀገር ውስጥ መረጃ ማከማቻ አሠራር ከመዘርጋቱ እና የዳታ ማስተላለፊያ ፍጥነት ከ500 ጊጋ ባይት በሰከንድ ወደ 3 ቴራ ባይት በሰከንድ ከፍ ካለበት ስኬት ጋር ተዳምሮ የውጭ ምንዛሬ ወጪን ለመታደግ አስችሏል።
ይህም የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙን በማገዝ የብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ ክምችትን ወደ 2.7 ቢሊዮን ዶላር ከፍ እንዲል እና የማክሮ-ኢኮኖሚ መረጋጋት እንዲፈጠር ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
የኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ሽግግር የሚያስተምረን ትልቁ እውነት ቴክኖሎጂ በራሱ ብቻ ተዓምር እንደማያመጣ ነው።
እውነተኛ እና ዘላቂ ልማት የሚረጋገጠው ቴክኖሎጂ ከተቋማዊ ውህደት፣ ከሕግ ቁጥጥር እና ከሕዝብ ተሳትፎ ጋር በ"መደመር" ፍልስፍና ሲቀናጅ ብቻ ነው።
ይህ ቅንጅት በተሳካ ሁኔታ ሲቀጥል፣ ዲጂታል ኢኮኖሚው ሀገርን ወደ ብሔራዊ ብልጽግና የሚመራ እውነተኛ የልማት ጎዳና መሆኑ ይረጋገጣል።
በበረከት ሽመልስ
#ethiopia #digitaleconomy #banking #digitalfinance #digitalethiopia #ebc
2 months ago
''ሰውየውን ማግኘት እፈልጋለሁ''
#ethiopia | የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራኑ ከፍተኛ መንፈሳዊ መሪ ሞጅታባ ኻሚኒ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ለመፍጠር ፍላጎት እንዳላቸው የገለጹ ሲሆን፣ የውይይቱ መሳካት ግን በሁለቱ ሀገራት መካከል በተጀመሩት ስምምነቶች ውጤት ላይ እንደሚወሰን አስታውቀዋል።
ፕሬዝደንት ትራምፕ በነጩ ቤተ መንግስት በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ የኢራንን ሃይማኖታዊ መሪ ለማግኘት ፍላጎት እንዳላቸውና ስብሰባው ሊካሄድ የሚችለው ዋሽንግተንና ቴህራን በኒውክሌር ፕሮግራም፣ በዩራኒየም ክምችት፣ በክልላዊ ደህንነትና በተኩስ አቁም ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ መድረስ ሲችሉ ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከ1979 የኢራን አብዮት በኋላ በሁለቱ ሀገራት መካከል የነበረውን የረጅም ጊዜ ውጥረት ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ይህ የታሰበው መገናኘት እውን ቢሆን በዓለም አቀፍ ፖለቲካ ላይ ታሪካዊ ለውጥ ሊያመጣ እንደሚችል ተነግሯል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#አሜሪካ #ኢራን #ዶናልድትራምፕ #ሞጅታባኻሚኒ #ዓለምአቀፍዲፕሎማሲ #የኒውክሌርውል #ዋሽንግተን #ቴህራን
#ethiopia | የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራኑ ከፍተኛ መንፈሳዊ መሪ ሞጅታባ ኻሚኒ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ለመፍጠር ፍላጎት እንዳላቸው የገለጹ ሲሆን፣ የውይይቱ መሳካት ግን በሁለቱ ሀገራት መካከል በተጀመሩት ስምምነቶች ውጤት ላይ እንደሚወሰን አስታውቀዋል።
ፕሬዝደንት ትራምፕ በነጩ ቤተ መንግስት በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ የኢራንን ሃይማኖታዊ መሪ ለማግኘት ፍላጎት እንዳላቸውና ስብሰባው ሊካሄድ የሚችለው ዋሽንግተንና ቴህራን በኒውክሌር ፕሮግራም፣ በዩራኒየም ክምችት፣ በክልላዊ ደህንነትና በተኩስ አቁም ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ መድረስ ሲችሉ ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከ1979 የኢራን አብዮት በኋላ በሁለቱ ሀገራት መካከል የነበረውን የረጅም ጊዜ ውጥረት ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ይህ የታሰበው መገናኘት እውን ቢሆን በዓለም አቀፍ ፖለቲካ ላይ ታሪካዊ ለውጥ ሊያመጣ እንደሚችል ተነግሯል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#አሜሪካ #ኢራን #ዶናልድትራምፕ #ሞጅታባኻሚኒ #ዓለምአቀፍዲፕሎማሲ #የኒውክሌርውል #ዋሽንግተን #ቴህራን
2 months ago
''ሰውየውን ማግኘት እፈልጋለሁ''
#ethiopia | የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራኑ ከፍተኛ መንፈሳዊ መሪ ሞጅታባ ኻሚኒ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ለመፍጠር ፍላጎት እንዳላቸው የገለጹ ሲሆን፣ የውይይቱ መሳካት ግን በሁለቱ ሀገራት መካከል በተጀመሩት ስምምነቶች ውጤት ላይ እንደሚወሰን አስታውቀዋል።
ፕሬዝደንት ትራምፕ በነጩ ቤተ መንግስት በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ የኢራንን ሃይማኖታዊ መሪ ለማግኘት ፍላጎት እንዳላቸውና ስብሰባው ሊካሄድ የሚችለው ዋሽንግተንና ቴህራን በኒውክሌር ፕሮግራም፣ በዩራኒየም ክምችት፣ በክልላዊ ደህንነትና በተኩስ አቁም ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ መድረስ ሲችሉ ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከ1979 የኢራን አብዮት በኋላ በሁለቱ ሀገራት መካከል የነበረውን የረጅም ጊዜ ውጥረት ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ይህ የታሰበው መገናኘት እውን ቢሆን በዓለም አቀፍ ፖለቲካ ላይ ታሪካዊ ለውጥ ሊያመጣ እንደሚችል ተነግሯል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#አሜሪካ #ኢራን #ዶናልድትራምፕ #ሞጅታባኻሚኒ #ዓለምአቀፍዲፕሎማሲ #የኒውክሌርውል #ዋሽንግተን #ቴህራን
#ethiopia | የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራኑ ከፍተኛ መንፈሳዊ መሪ ሞጅታባ ኻሚኒ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ለመፍጠር ፍላጎት እንዳላቸው የገለጹ ሲሆን፣ የውይይቱ መሳካት ግን በሁለቱ ሀገራት መካከል በተጀመሩት ስምምነቶች ውጤት ላይ እንደሚወሰን አስታውቀዋል።
ፕሬዝደንት ትራምፕ በነጩ ቤተ መንግስት በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ የኢራንን ሃይማኖታዊ መሪ ለማግኘት ፍላጎት እንዳላቸውና ስብሰባው ሊካሄድ የሚችለው ዋሽንግተንና ቴህራን በኒውክሌር ፕሮግራም፣ በዩራኒየም ክምችት፣ በክልላዊ ደህንነትና በተኩስ አቁም ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ መድረስ ሲችሉ ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከ1979 የኢራን አብዮት በኋላ በሁለቱ ሀገራት መካከል የነበረውን የረጅም ጊዜ ውጥረት ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ይህ የታሰበው መገናኘት እውን ቢሆን በዓለም አቀፍ ፖለቲካ ላይ ታሪካዊ ለውጥ ሊያመጣ እንደሚችል ተነግሯል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#አሜሪካ #ኢራን #ዶናልድትራምፕ #ሞጅታባኻሚኒ #ዓለምአቀፍዲፕሎማሲ #የኒውክሌርውል #ዋሽንግተን #ቴህራን
2 months ago
አዲስ አበባ ባለፉት 5 ዓመታት የልማት አብዮት አካሂዳለች - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መዲናችን አዲስ አበባ ባለፉት 5 ዓመታት የልማት አብዮት አካሂዳለች አሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ።
ከንቲባዋ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ በባለፉት 10 ቀናት ብቻ 11 ፕሮጀክቶችን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል ብለዋል።
ለአብነትም ፦
1. በኢንዱስትሪ እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ፤ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። ይህ ፓርክ ከ20 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጥር ነው።
2. የማህበራዊ ልማት (የመኖሪያ ቤቶች)፤ ሶስቱ የበጎነት መንደሮችን በአዲስ ከተማ፣ በኮልፌ ቀራንዮ እና የካ ክፍለ ከተሞች የተገነቡ የመኖርያ ቤቶች ለሀገር ባለውለታዎች፣ ለአቅመ ደካማዎች እና ለአካል ጉዳተኞች የማስተላለፍ ስራ ተሰርቷል፡፡
3. የመዝናኛ እና የህዝብ ፓርኮች ፤በአዲስ ከተማ (አስኮ አዲስ ሰፈር) በ30 ሺህ ካሬ ሜትር እና በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ18 ሄክታር ቦታ ላይ የተገነቡ የወንዝ ዳርቻ እና የህዝብ መዝናኛ ፓርኮች ተመርቀዋል። እነዚህ ማዕከላት ህፃናትን፣ ወጣቶችን እና አረጋውያንን ያካተቱ፣ ማህበረሰቡ በጋራ የሚጠቀምባቸው ናቸው።
4. የኑሮ ውድነትን ለማቃለል የግብይት ማዕከላትን የማስፋት ስራ አካል የሆነው 7ኛው የለሚ ሁለገብ የገበያ ማዕከል፣ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል።
5. ዘመናዊ የገበያና የትራንስፖርት ማዕከል፤ አይነቱ የመጀመሪያ የሆነው የአድዋ የገበያ ማዕከል እና ዘመናዊ የትራንስፖርት ተርሚናል ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል። የዚህ ማዕከል ሱቆች እና ካፍቴሪያዎች ለፒያሳ ልማት ተነሺዎች በዕጣ ተላልፈዋል።
6. በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ3 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባውን ፣ 16 ሱቆችን እና 18 ሼዶችን የያዘ የተቀናጀ የከተማ ግብርና ማዕከል አገልግሎት ክፍት ተደርጓል ።
7. የስፖርት እና የወጣቶች ማዕከል፡ በቦሌ ክፍለ ከተማ የሚገኘው የለሚ ኮሚኒቲ ስታዲየም፣ 5 ስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ 95 የህፃናት መጫወቻዎች፣ 6 የህፃናት ማቆያ (Daycare) ማዕከላት፣ ካፍቴሪያዎች እና አምፊ ቲያትሮችን ጨምሮ ለወጣቶች ተጠቃሚነት የሚያገለግሉ መሠረተ ልማቶችን አሟልቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
8. በልደታ ክ/ከተማ ለትውልድ ግንባታ መሰረት የሚጥሉ ሁለት ት/ቤቶች እና ሶስት የህፃናት ማቆያ ማእከል ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ተደረገዋል ።
9. የተስፋ ብርሀን የምገባ ማዕከላት ተጠቃሚዎች ለነበሩ 400 ነዋሪዎቻችን መነሻ ካፒታልና የመስሪያ ቁሳቁስ በማሟሟላት ከተረጂነት ወደ የስራ እድል ተጠቃሚነት እንዲሸጋገሩ ተደርጓል።
10. 7ኛውን የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት በላፍቶ ክፍለ ከተማ ተመርቋል።
11. ዘመናዊ የጤና አገልግሎት ፤ በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የሆነው፣ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂ የተደገፈው እና እጅግ ዘመናዊ የሆነው የላፍቶ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለምርቃት በቅቷል።
አንዳንዶች እነዚህ ፕሮጀክቶች ለምርጫ ተብሎ እንደተከናወነ ያነሳሉ ያሉት ከንቲባዋ፤ ነገር ግን እውነታው ቀድሞ ያልተሰራ ለምርጫም ሊደርስ አይችልም፤ ተሰርቶም ለምርጫ ከዋለ ዋናው ህዝቡና ሀገር ተጠቃሚ ይሁን እንጂ ችግር የለውም ብለዋል፡፡
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መዲናችን አዲስ አበባ ባለፉት 5 ዓመታት የልማት አብዮት አካሂዳለች አሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ።
ከንቲባዋ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ በባለፉት 10 ቀናት ብቻ 11 ፕሮጀክቶችን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል ብለዋል።
ለአብነትም ፦
1. በኢንዱስትሪ እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ፤ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። ይህ ፓርክ ከ20 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጥር ነው።
2. የማህበራዊ ልማት (የመኖሪያ ቤቶች)፤ ሶስቱ የበጎነት መንደሮችን በአዲስ ከተማ፣ በኮልፌ ቀራንዮ እና የካ ክፍለ ከተሞች የተገነቡ የመኖርያ ቤቶች ለሀገር ባለውለታዎች፣ ለአቅመ ደካማዎች እና ለአካል ጉዳተኞች የማስተላለፍ ስራ ተሰርቷል፡፡
3. የመዝናኛ እና የህዝብ ፓርኮች ፤በአዲስ ከተማ (አስኮ አዲስ ሰፈር) በ30 ሺህ ካሬ ሜትር እና በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ18 ሄክታር ቦታ ላይ የተገነቡ የወንዝ ዳርቻ እና የህዝብ መዝናኛ ፓርኮች ተመርቀዋል። እነዚህ ማዕከላት ህፃናትን፣ ወጣቶችን እና አረጋውያንን ያካተቱ፣ ማህበረሰቡ በጋራ የሚጠቀምባቸው ናቸው።
4. የኑሮ ውድነትን ለማቃለል የግብይት ማዕከላትን የማስፋት ስራ አካል የሆነው 7ኛው የለሚ ሁለገብ የገበያ ማዕከል፣ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል።
5. ዘመናዊ የገበያና የትራንስፖርት ማዕከል፤ አይነቱ የመጀመሪያ የሆነው የአድዋ የገበያ ማዕከል እና ዘመናዊ የትራንስፖርት ተርሚናል ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል። የዚህ ማዕከል ሱቆች እና ካፍቴሪያዎች ለፒያሳ ልማት ተነሺዎች በዕጣ ተላልፈዋል።
6. በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ3 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባውን ፣ 16 ሱቆችን እና 18 ሼዶችን የያዘ የተቀናጀ የከተማ ግብርና ማዕከል አገልግሎት ክፍት ተደርጓል ።
7. የስፖርት እና የወጣቶች ማዕከል፡ በቦሌ ክፍለ ከተማ የሚገኘው የለሚ ኮሚኒቲ ስታዲየም፣ 5 ስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ 95 የህፃናት መጫወቻዎች፣ 6 የህፃናት ማቆያ (Daycare) ማዕከላት፣ ካፍቴሪያዎች እና አምፊ ቲያትሮችን ጨምሮ ለወጣቶች ተጠቃሚነት የሚያገለግሉ መሠረተ ልማቶችን አሟልቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
8. በልደታ ክ/ከተማ ለትውልድ ግንባታ መሰረት የሚጥሉ ሁለት ት/ቤቶች እና ሶስት የህፃናት ማቆያ ማእከል ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ተደረገዋል ።
9. የተስፋ ብርሀን የምገባ ማዕከላት ተጠቃሚዎች ለነበሩ 400 ነዋሪዎቻችን መነሻ ካፒታልና የመስሪያ ቁሳቁስ በማሟሟላት ከተረጂነት ወደ የስራ እድል ተጠቃሚነት እንዲሸጋገሩ ተደርጓል።
10. 7ኛውን የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት በላፍቶ ክፍለ ከተማ ተመርቋል።
11. ዘመናዊ የጤና አገልግሎት ፤ በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የሆነው፣ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂ የተደገፈው እና እጅግ ዘመናዊ የሆነው የላፍቶ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለምርቃት በቅቷል።
አንዳንዶች እነዚህ ፕሮጀክቶች ለምርጫ ተብሎ እንደተከናወነ ያነሳሉ ያሉት ከንቲባዋ፤ ነገር ግን እውነታው ቀድሞ ያልተሰራ ለምርጫም ሊደርስ አይችልም፤ ተሰርቶም ለምርጫ ከዋለ ዋናው ህዝቡና ሀገር ተጠቃሚ ይሁን እንጂ ችግር የለውም ብለዋል፡፡
2 months ago
የማዕድን ዘርፍ እና አዲስ የኢኮኖሚ ምዕራፍ
******************
(የዕለቱ መልዕክት)
በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ትንሳኤ ውስጥ ለዓመታት ተኝቶ የነበረው የማዕድን ሀብታችን አሁን ለሀገር ኢኮኖሚ ትከሻውን እየሰጠ ይገኛል። ከባህላዊ የግብርና አጥር ወጥተን አገራችንን ወደ አፍሪካ የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማሸጋገር በሚደረገው ጥረት ኢትዮጵያ ያሏትን የሀብት ክምችት በዕውቀትና በቴክኖሎጂ አቀነባብራ መጠቀም ጀምራለች። በዚህም የከርሰ ምድርና ገጸ ምድር ሀብቷን ወደ ብሔራዊ ምርታማነት የመቀየር አዲስ ምዕራፍ ከፍታለች።
የማምረቻው ዘርፍ እንደ ወንዝ ውሃ የኢኮኖሚውን አቅጣጫ የሚቀይር ከሆነ ማዕድን ደግሞ የዚያ ወንዝ ምንጭ ነው። አገራችንን የኢንዱስትሪ ፋና ለማድረግ የጀመርነው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፣ የማዕድን ዘርፉን ከምድር ውስጥ አውጥቶ ወደ ፋብሪካዎች ግብዓትነት የመቀየር ግዴታ አለበት።
የኢንዱስትሪ ፓርኮቻችን እያሳዩት ባለው አቅም የማዕድን ዘርፉን በቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ጥገኝነታችንን መቀነስ የምንችለው አሁን ነው። በገዛ መሬታችን ያለውን ሀብት በጥራትና በክህሎት ተጠቅመን የውጭ ገበያን በዋጋና በጥራት መፎካከር የሚችል አቅም መገንባትም አለብን።
ከውጥን ወደ እውነታ እየተሸጋገርን ባለበት በዚህ ወቅት የማዕድን ልማታችን ከጥሬ ዕቃ ሽያጭ አልፎ እሴት በተጨመረባቸው ምርቶች መደገፍ አለበት። የወርቅ፣ የኦፓል፣ የታንታለም እና የሌሎች ማዕድናት ፍሰት ለሀገር ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት መሆን የሚችለው፣ የማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች በፓርኮቻችን ውስጥ ሲጠናከሩ ብቻ ነው።
የኢኮኖሚ ነፃነት ማለት በውጭ ምንዛሪ መግዛት ሳይሆን በእጅ ያለን ሀብት በአገር አቅም አምርቶ ለዓለም ማቅረብ ነው። ይህ ጉዞ በሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል ጥያቄ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ የሉዓላዊነትና የብልጽግና መለኪያ ነው።
የማዕድን ዘርፉን ወደ ኢንዱስትሪ ማቀናጀት ማለት የአገርን የቴክኖሎጂ አቅም መፈተን ማለት ነው። ዘመናዊ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለዓለም አቀፍ ደረጃ ያላቸው ማዕድናት ማቀነባበሪያ ማዕከላት ሲሆኑ ኢትዮጵያ ከጥሬ ዕቃ ላኪነት ወደ ምርት አምራችነት ትሸጋገራለች።
ይህ ሽግግር በተለይም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን፣ የፀሐይ ኃይል መሣሪያዎችን እና የሕክምና መሣሪያዎችን ለማምረት ወሳኝ የሆኑ ማዕድናትን በአገር ውስጥ መጠቀምን ይጠይቃል።
"ውኃ ካልጠራ አይጠጣም፣ ሰው ካልተማረ አይጠቅም" እንደተባለው የምንፈልገውን የኢንዱስትሪ ለውጥ የምናመጣው በትምህርት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በዘርፉ በሰለጠነ የሰው ኃይል ብቻ ነው።
የኢትዮጵያ ትንሳኤ በወረቀት ላይ የተጻፈ ራዕይ ሳይሆን በየፋብሪካው መጋዘን የሚከማች ምርት፣ በየኢንዱስትሪ ፓርኩ የሚሰማ የቴክኖሎጂ ምት እና በምድር የተገኙ ማዕድናት በኢትዮጵያዊ ክህሎት ሲቀረጹ የሚታይ እውነት ነው።
በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪ ፓርኮቻችን እየሳቡት ያለው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት፣ የማዕድን ዘርፉን እንደ ታላቅ የኢኮኖሚ ምንጭ ለመጠቀም ያለንን አቅም ያሳያል። የልዩ ኢኮኖሚ ዞን አዋጁም ለዚህ ዘርፍ የሚሰጠው የግብርና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች፣ ባለሀብቶች ወደ ማዕድን ልማት እንዲገቡ ትልቅ ማበረታቻ ሆኗል።
የማዕድን ሀብታችንን በዘመናዊ አሠራር ፈትሸን፣ የኢንዱስትሪው ዘርፍ እንዲያንሰራራ ማድረጉ የጊዜው ትልቁ አገራዊ ጥሪ ነው።
ኢትዮጵያ በምርቷ ትከበራለች፤ በምድሯ የተከማቸው ሀብትም ለቀጣዩ ትውልድ የብልጽግና ፋና ሆኖ ይደምቃል። ይህ የኢንዱስትሪ አብዮት የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ከፍ የሚያደርግ፣ የኢኮኖሚ መዋቅራችንን ለዘመናት የሚያጸና የትንሳኤ ብሥራት ነው።
በየደረጃው ያለው የማዕድን ምርታችን ሲጎለብት ኢትዮጵያ የራሷን የኢንዱስትሪ ሉዓላዊነት ታውጃለች። ነገ የምናያት ኢትዮጵያ በምርቷ የምትኩራራ፣ በሀብቷ የምትበለጽግ እና ለአፍሪካ የብልጽግና ፋና የምትሆን አገር ናት።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #ebcdotstream #ethiopia #ebc #ማዕድን #ኢኮኖሚ
******************
(የዕለቱ መልዕክት)
በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ትንሳኤ ውስጥ ለዓመታት ተኝቶ የነበረው የማዕድን ሀብታችን አሁን ለሀገር ኢኮኖሚ ትከሻውን እየሰጠ ይገኛል። ከባህላዊ የግብርና አጥር ወጥተን አገራችንን ወደ አፍሪካ የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማሸጋገር በሚደረገው ጥረት ኢትዮጵያ ያሏትን የሀብት ክምችት በዕውቀትና በቴክኖሎጂ አቀነባብራ መጠቀም ጀምራለች። በዚህም የከርሰ ምድርና ገጸ ምድር ሀብቷን ወደ ብሔራዊ ምርታማነት የመቀየር አዲስ ምዕራፍ ከፍታለች።
የማምረቻው ዘርፍ እንደ ወንዝ ውሃ የኢኮኖሚውን አቅጣጫ የሚቀይር ከሆነ ማዕድን ደግሞ የዚያ ወንዝ ምንጭ ነው። አገራችንን የኢንዱስትሪ ፋና ለማድረግ የጀመርነው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ፣ የማዕድን ዘርፉን ከምድር ውስጥ አውጥቶ ወደ ፋብሪካዎች ግብዓትነት የመቀየር ግዴታ አለበት።
የኢንዱስትሪ ፓርኮቻችን እያሳዩት ባለው አቅም የማዕድን ዘርፉን በቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ የውጭ ምንዛሪ ጥገኝነታችንን መቀነስ የምንችለው አሁን ነው። በገዛ መሬታችን ያለውን ሀብት በጥራትና በክህሎት ተጠቅመን የውጭ ገበያን በዋጋና በጥራት መፎካከር የሚችል አቅም መገንባትም አለብን።
ከውጥን ወደ እውነታ እየተሸጋገርን ባለበት በዚህ ወቅት የማዕድን ልማታችን ከጥሬ ዕቃ ሽያጭ አልፎ እሴት በተጨመረባቸው ምርቶች መደገፍ አለበት። የወርቅ፣ የኦፓል፣ የታንታለም እና የሌሎች ማዕድናት ፍሰት ለሀገር ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት መሆን የሚችለው፣ የማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪዎች በፓርኮቻችን ውስጥ ሲጠናከሩ ብቻ ነው።
የኢኮኖሚ ነፃነት ማለት በውጭ ምንዛሪ መግዛት ሳይሆን በእጅ ያለን ሀብት በአገር አቅም አምርቶ ለዓለም ማቅረብ ነው። ይህ ጉዞ በሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል ጥያቄ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ የሉዓላዊነትና የብልጽግና መለኪያ ነው።
የማዕድን ዘርፉን ወደ ኢንዱስትሪ ማቀናጀት ማለት የአገርን የቴክኖሎጂ አቅም መፈተን ማለት ነው። ዘመናዊ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ለዓለም አቀፍ ደረጃ ያላቸው ማዕድናት ማቀነባበሪያ ማዕከላት ሲሆኑ ኢትዮጵያ ከጥሬ ዕቃ ላኪነት ወደ ምርት አምራችነት ትሸጋገራለች።
ይህ ሽግግር በተለይም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን፣ የፀሐይ ኃይል መሣሪያዎችን እና የሕክምና መሣሪያዎችን ለማምረት ወሳኝ የሆኑ ማዕድናትን በአገር ውስጥ መጠቀምን ይጠይቃል።
"ውኃ ካልጠራ አይጠጣም፣ ሰው ካልተማረ አይጠቅም" እንደተባለው የምንፈልገውን የኢንዱስትሪ ለውጥ የምናመጣው በትምህርት፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና በዘርፉ በሰለጠነ የሰው ኃይል ብቻ ነው።
የኢትዮጵያ ትንሳኤ በወረቀት ላይ የተጻፈ ራዕይ ሳይሆን በየፋብሪካው መጋዘን የሚከማች ምርት፣ በየኢንዱስትሪ ፓርኩ የሚሰማ የቴክኖሎጂ ምት እና በምድር የተገኙ ማዕድናት በኢትዮጵያዊ ክህሎት ሲቀረጹ የሚታይ እውነት ነው።
በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪ ፓርኮቻችን እየሳቡት ያለው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት፣ የማዕድን ዘርፉን እንደ ታላቅ የኢኮኖሚ ምንጭ ለመጠቀም ያለንን አቅም ያሳያል። የልዩ ኢኮኖሚ ዞን አዋጁም ለዚህ ዘርፍ የሚሰጠው የግብርና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች፣ ባለሀብቶች ወደ ማዕድን ልማት እንዲገቡ ትልቅ ማበረታቻ ሆኗል።
የማዕድን ሀብታችንን በዘመናዊ አሠራር ፈትሸን፣ የኢንዱስትሪው ዘርፍ እንዲያንሰራራ ማድረጉ የጊዜው ትልቁ አገራዊ ጥሪ ነው።
ኢትዮጵያ በምርቷ ትከበራለች፤ በምድሯ የተከማቸው ሀብትም ለቀጣዩ ትውልድ የብልጽግና ፋና ሆኖ ይደምቃል። ይህ የኢንዱስትሪ አብዮት የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ከፍ የሚያደርግ፣ የኢኮኖሚ መዋቅራችንን ለዘመናት የሚያጸና የትንሳኤ ብሥራት ነው።
በየደረጃው ያለው የማዕድን ምርታችን ሲጎለብት ኢትዮጵያ የራሷን የኢንዱስትሪ ሉዓላዊነት ታውጃለች። ነገ የምናያት ኢትዮጵያ በምርቷ የምትኩራራ፣ በሀብቷ የምትበለጽግ እና ለአፍሪካ የብልጽግና ፋና የምትሆን አገር ናት።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #ebcdotstream #ethiopia #ebc #ማዕድን #ኢኮኖሚ
Sponsored by
Surafel
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) —የቀድሞው የኩባ መሪ ራውል ካስትሮ እና ሌሎች አምስት ግለሰቦች በፍሎሪዳ በሚገኝ የአሜሪካ የህግ አስከባሪ ክስ እንደተመሰረተባቸው ዛሬ ረቡዕ ይፋ የተደረጉ የፍርድ ቤት ሰነዶች አመለከቱ።
በ94 ዓመቱ ራውል ካስትሮ ላይ የቀረበው ይህ አዲስ የፌደራል ወንጀል ክስ፣ የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በኩባ መንግስት ላይ እያካሄደ ያለውን የጫና ዘመቻ ከፍ ወዳለ እና ወደተባባሰ ደረጃ ያሸጋገረው መሆኑ ተገልጿል።
ተከሳሹ ራውል ካስትሮ የሟቹ የኩባ አብዮት መሪ ፊደል ካስትሮ ወንድም ሲሆኑ፣ አሁንም ድረስ በሀገሪቱ ውስጥ እጅግ ከፍተኛ ተጽዕኖ እና ስልጣን ካላቸው ቁልፍ የፖለቲካ ሰዎች መካከል በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው።
በ94 ዓመቱ ራውል ካስትሮ ላይ የቀረበው ይህ አዲስ የፌደራል ወንጀል ክስ፣ የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በኩባ መንግስት ላይ እያካሄደ ያለውን የጫና ዘመቻ ከፍ ወዳለ እና ወደተባባሰ ደረጃ ያሸጋገረው መሆኑ ተገልጿል።
ተከሳሹ ራውል ካስትሮ የሟቹ የኩባ አብዮት መሪ ፊደል ካስትሮ ወንድም ሲሆኑ፣ አሁንም ድረስ በሀገሪቱ ውስጥ እጅግ ከፍተኛ ተጽዕኖ እና ስልጣን ካላቸው ቁልፍ የፖለቲካ ሰዎች መካከል በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው።
3 months ago
የመደመር አንቀጽ
የመደመር መንግሥት የውስጥ የኢኮኖሚ ሽግግርን በታቀደ መልኩ የሚመራ ብቻ ሳይሆን ከባቢያዊና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታን ይተነትናል። ራሱን ለመለወጥና ከእነዚህ ሁኔታዎች ጋር ራሱን ለማላመድ አስቀድሞ ይዘጋጃል። ዓለም ከአንዱ የኢኮኖሚ አብዮት ወለ ሌው እየዘለለ ከተለምዷዊው አሰራር ወጥቶ ወደ ዲጂታል ተሸጋግሯል። ከዚያም አልፎ አልፎ እንደ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ዓይነት ጨዋታ ቀያሪ ዐቅም ያላቸው ቴክኖሎጂዎችን እየታጠቀ ነው።
ከዚያም አልፎ እንደ ሰው ሠራሽ አስተውሎት ዓይነት ጨዋታ ቀያሪ ዐቅም ያላቸው ይሄንን ለውጥ በቶሎ የተላመዱ ሀገራትን ዛሬ የበለጸጉ ብለን እንጠራቸዋለን። ምክንያቱም ለውጥ የሚላመዱትን ያከብራል፤ የማይላመዱትን ደግሞ ይሰብራል። የነገው የበለጸጉ ሀገራት ዝርዝር ማለት፣ የሚቀጥሉትን አብዮቶች መላመድ የቻሉና ራሳቸውን በለውጡ ውስጥ ያሸጋገሩ ሀገራት ዝርዝር ነው።
የመደመር መንግስት
ገፅ 133
Ethiopian Broadcasting Corporation #digitalethiopia #የመረጃ_ሉዓላዊነት #data #ኢትዮጵያ
የመደመር መንግሥት የውስጥ የኢኮኖሚ ሽግግርን በታቀደ መልኩ የሚመራ ብቻ ሳይሆን ከባቢያዊና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታን ይተነትናል። ራሱን ለመለወጥና ከእነዚህ ሁኔታዎች ጋር ራሱን ለማላመድ አስቀድሞ ይዘጋጃል። ዓለም ከአንዱ የኢኮኖሚ አብዮት ወለ ሌው እየዘለለ ከተለምዷዊው አሰራር ወጥቶ ወደ ዲጂታል ተሸጋግሯል። ከዚያም አልፎ አልፎ እንደ ሰው ሰራሽ አስተውሎት ዓይነት ጨዋታ ቀያሪ ዐቅም ያላቸው ቴክኖሎጂዎችን እየታጠቀ ነው።
ከዚያም አልፎ እንደ ሰው ሠራሽ አስተውሎት ዓይነት ጨዋታ ቀያሪ ዐቅም ያላቸው ይሄንን ለውጥ በቶሎ የተላመዱ ሀገራትን ዛሬ የበለጸጉ ብለን እንጠራቸዋለን። ምክንያቱም ለውጥ የሚላመዱትን ያከብራል፤ የማይላመዱትን ደግሞ ይሰብራል። የነገው የበለጸጉ ሀገራት ዝርዝር ማለት፣ የሚቀጥሉትን አብዮቶች መላመድ የቻሉና ራሳቸውን በለውጡ ውስጥ ያሸጋገሩ ሀገራት ዝርዝር ነው።
የመደመር መንግስት
ገፅ 133
Ethiopian Broadcasting Corporation #digitalethiopia #የመረጃ_ሉዓላዊነት #data #ኢትዮጵያ
3 months ago
የኢራን የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ቀጥታ የስናይፐር እና የክላሽንኮቭ ስልጠና ማስተላለፍ ጀመሩ!
#ethiopia | በኢራን፣ በአሜሪካ እና በእስራኤል መካከል ያለው ወታደራዊ ፍጥጫ እና ውጥረት እጅግ አስፈሪ ደረጃ ላይ በደረሰበት በዚህ ወቅት፣ የኢራን ብሔራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች (IRIB) ታሪክ ከየቀኑ የዜና እወጃ ወጥተው የቀጥታ የስልጠና መድረክ መሆናቸውን ዓለም በደነገጠ ስሜት እየተከታተለው ይገኛል።
የጣቢያዎቹ የዜና አቅራቢዎችና ጋዜጠኞች ራሳቸው የጦር መሣሪያዎችን በአደባባይ በመያዝ እና የቀጥታ ተኩስ ልምምድ በማድረግ ላይ ናቸው።
በእነዚህ የቀጥታ የቴሌቪዥን ሥርጭቶች ላይ በስፋት ጥቅም ላይ እየዋለ የሚገኘው የምሥራቅ ጀርመን ስሪት የሆነው እና በ7.62×39 ሚሊሜትር ጥይት የሚተኩሰው ‘MPi-KMS’ የተባለው የክላሽንኮቭ (AK-47) የጦር መሣሪያ ዓይነት ነው።
የቴሌቪዥን አቅራቢዎቹ የጦር መሣሪያውን እንዴት መፍታት፣ መግጠም፣ ጥይት መክተት እና ኢላማን መምታት እንደሚቻል ከእስላማዊ አብዮት ጥበቃ ጦር (IRGC) መኮንኖች ጋር በመሆን ለሕዝብ ቀጥታ ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ።
ኢራን ይህንን ያልተለመደ የቴሌቪዥን ስርጭት “ሕይወትን ለኢራን መስዋዕት ማድረግ” (Sacrifice Life For Iran) ከሚለው አገር አቀፍ የዝግጁነት ዘመቻ ጋር ያገናኘችው ሲሆን፣ እስካሁን ድረስ ከ31 ሚሊዮን በላይ ዜጎች በፈቃደኝነት ለዚህ የክተት ጥሪ መመዝገባቸውን የመንግስት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ከዚህም በተጨማሪ በቴህራን እና በኬርማንሻህ ከተሞች የሚገኙ ታዳጊ ወጣቶች በአደባባዮች እና በመስጊዶች በተዘጋጁ ወታደራዊ ድንኳኖች ውስጥ የጦር መሣሪያ አያያዝ፣ የውጊያ ስልቶች እና የአገር መከላከያ ስልጠናዎችን እየወሰዱ ይገኛሉ።
የኢራን ብሔራዊ ቴሌቪዥን ከፍተኛ ባለሥልጣን የሆኑት ሞህሴን ባርመህኒ የሀገሪቱ ሚዲያዎች ሙሉ በሙሉ “የጦርነት አቋም” (Wartime Posture) መያዝ እንዳለባቸው በይፋ ያወጁ ሲሆን፣ በአንድ የቀጥታ ስርጭት ፕሮግራም ላይ የቴሌቪዥን አቅራቢው ክላሽንኮቭ መሣሪያውን ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬትስ (UAE) ባንዲራ አነጣጥሮ ሲተኩስ የታየበት ትዕይንት በባህረ ሰላጤው ሀገራት ዘንድ ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ቁጣንና ውግዘትን አስከትሏል ሲል መናኸሪያ ኤፍ ኤም ዘግቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #iran #war #television
#usarmy #peace
#ethiopia | በኢራን፣ በአሜሪካ እና በእስራኤል መካከል ያለው ወታደራዊ ፍጥጫ እና ውጥረት እጅግ አስፈሪ ደረጃ ላይ በደረሰበት በዚህ ወቅት፣ የኢራን ብሔራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች (IRIB) ታሪክ ከየቀኑ የዜና እወጃ ወጥተው የቀጥታ የስልጠና መድረክ መሆናቸውን ዓለም በደነገጠ ስሜት እየተከታተለው ይገኛል።
የጣቢያዎቹ የዜና አቅራቢዎችና ጋዜጠኞች ራሳቸው የጦር መሣሪያዎችን በአደባባይ በመያዝ እና የቀጥታ ተኩስ ልምምድ በማድረግ ላይ ናቸው።
በእነዚህ የቀጥታ የቴሌቪዥን ሥርጭቶች ላይ በስፋት ጥቅም ላይ እየዋለ የሚገኘው የምሥራቅ ጀርመን ስሪት የሆነው እና በ7.62×39 ሚሊሜትር ጥይት የሚተኩሰው ‘MPi-KMS’ የተባለው የክላሽንኮቭ (AK-47) የጦር መሣሪያ ዓይነት ነው።
የቴሌቪዥን አቅራቢዎቹ የጦር መሣሪያውን እንዴት መፍታት፣ መግጠም፣ ጥይት መክተት እና ኢላማን መምታት እንደሚቻል ከእስላማዊ አብዮት ጥበቃ ጦር (IRGC) መኮንኖች ጋር በመሆን ለሕዝብ ቀጥታ ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ።
ኢራን ይህንን ያልተለመደ የቴሌቪዥን ስርጭት “ሕይወትን ለኢራን መስዋዕት ማድረግ” (Sacrifice Life For Iran) ከሚለው አገር አቀፍ የዝግጁነት ዘመቻ ጋር ያገናኘችው ሲሆን፣ እስካሁን ድረስ ከ31 ሚሊዮን በላይ ዜጎች በፈቃደኝነት ለዚህ የክተት ጥሪ መመዝገባቸውን የመንግስት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ከዚህም በተጨማሪ በቴህራን እና በኬርማንሻህ ከተሞች የሚገኙ ታዳጊ ወጣቶች በአደባባዮች እና በመስጊዶች በተዘጋጁ ወታደራዊ ድንኳኖች ውስጥ የጦር መሣሪያ አያያዝ፣ የውጊያ ስልቶች እና የአገር መከላከያ ስልጠናዎችን እየወሰዱ ይገኛሉ።
የኢራን ብሔራዊ ቴሌቪዥን ከፍተኛ ባለሥልጣን የሆኑት ሞህሴን ባርመህኒ የሀገሪቱ ሚዲያዎች ሙሉ በሙሉ “የጦርነት አቋም” (Wartime Posture) መያዝ እንዳለባቸው በይፋ ያወጁ ሲሆን፣ በአንድ የቀጥታ ስርጭት ፕሮግራም ላይ የቴሌቪዥን አቅራቢው ክላሽንኮቭ መሣሪያውን ወደ ተባበሩት አረብ ኤምሬትስ (UAE) ባንዲራ አነጣጥሮ ሲተኩስ የታየበት ትዕይንት በባህረ ሰላጤው ሀገራት ዘንድ ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ቁጣንና ውግዘትን አስከትሏል ሲል መናኸሪያ ኤፍ ኤም ዘግቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #iran #war #television
#usarmy #peace
Sponsored by
Surafel
Comments