1 month ago
የመደመር መንግሥት ስንል?
********
ታሪክን ወደ ኋላ መለስ ብለን ስንቃኝ፣ ኢትዮጵያ የነፃነት ተምሳሌት፣ የጥንታዊ ስልጣኔ ባለቤት፣ እና የብዙ ፀጋዎች ማህደር ሆና እናገኛታለን።
አባቶቻችን በደማቸው አቅንተውና ጠብቀው ያቆዩልንን ይህች ምድር፣ ሀብቷ ሳይደመርና አ ቅሟ ሳይቀናጅ ለዘመናት በመቆየቱ ምክንያት፣ በእጦት አዙሪትና በድህነት ማጥ ውስጥ ስትዳክር ኖራለች።
“የኢትዮጵያውያንን ህይወት እንለውጣለን” የሚለው መፈክር በተፈራረቁ መንግስታትና ትውልዶች ዘንድ በተደጋግሚ ቢነገርም፣ በተግባር ግን እንደ ጉም ርቆን፣ እንደ ህልም ተንሳፎ ቆይቷል።
ዘመናት ነጎዱ፣ ትውልዶች ተፈራረቁ፤ እኛ ግን በተረገጥንበት ቦታ መቆማችንን አልተውንም። በዚህ የታሪክ መስቀለኛ መንገድ እና በተከማቸ የቤት ስራ አጣብቂኝ ውስጥ ነው እንግዲህ "የመደመር መንግስት" ብቅ ያለው።
ለመሆኑ የመደመር መንግስት ምንነት ምንድን ነው?
የመደመር መንግስት ማለት መከፋፈልን፣ መነጠልን፣ እና የአንዱን መቃብር የሌላው ዙፋን የሚያደርገውን የዜሮ ድምር ጨዋታ በመፀየፍ፣ ሀገራዊ ፀጋዎችንና አቅሞችን ወደ አንድ የብልፅግና ወንዝ የሚያፈስ ስርዓት ነው። በመደመር ፍልስፍና መነፅር፣ የመንግስት ሚና እንደ ባለፈው ዘመን ሁሉን አድራጊ ፈጣሪ ወይም ጨቋኝ መሆን ሳይሆን፣ የትብብር ሞተር መሆን ነው።
ይህ መንግስት ዜጎችን፣ የግሉን ዘርፍ፣ እና ሀገራዊ አቅሞችን በማስተባበር፤ ትላንት ያመለጠንን የባከነ ጊዜ "በፈጠራ እና በፍጥነት" የሚያካክስ፣ ገቢር ነበብ (Pragmatic) የሆነ የዘመነ መንግስታዊ መዋቅር ነው።
መሰረታዊ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ዲፓርቸሩም ይሄው ነው፡ ትናንትን ከስህተቱ ተምሮ ማረም፣ ዛሬን በትጋት መስራት፣ እና ነገን በምናብ ተልሞ ማለም።
የመደመር መንግሥት ስንል፣ በፍልስፍና መሠረቱ ከታሕታይ መዋቅር (እንደ ኢኮኖሚ እና መሠረተ ልማት) ለውጥ ይልቅ ለላዕላይ መዋቅር (አስተሳሰብ እና ባህል) ለውጥ ቅድሚያ የሚሰጥ ሥርዓት ማለታችን ነው። ይህ መንግሥት የማኅበረሰብን ልዩ ልዩ ጸጋዎች፣ ዕሴቶች፣ እና አቅሞች ማሰባሰብ ለብልጽግና ወሳኝ መሆኑን በፅኑ ያምናል።
የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ኃይሎች በሚፈጥሩት ፍትጊያ ውስጥ ሚዛን (ወርቃማውን አማካይ) በመጠበቅ ሁሉንም አቅፎ የሚጓዝ ነው።
ይህንን እውነት ይበልጥ ለመረዳት የመደመርን መንግሥት መሠረታዊ መለያዎች ካለፉት መንግሥታት ታሪክ ጋር ማነፃፀር ግድ ይላል።
የሀገራችን የፖለቲካ ጉዞ ከውጭ ሀገር (ከምዕራብም ሆነ ከምሥራቅ) የልማት ሞዴሎችን እንዳለ ገልብጦ በማምጣት የኢትዮጵያን ነባራዊ እውነታ ለማሳጣት ሲጥር የኖረ ፤የንጉሡ ሥርዓት "ሰማይ አይታረስ፣ ንጉሥ አይከሰስ" በሚል መርህ አይነኬነትን ያነገሠ፣ ለውጥን የሚጠላና ቆሞ-ቀርነትን ያተረፈ ፊውዳላዊ ሥርዓት ሆና የተካው የደርግ መንግሥት ደግሞ የሶቪየትን ሞዴል በጭፍን በመከተል "ትሻልን ሰድጄ ትብስን አመጣሁ" እንዲሉ፣ በኅብረተሰብአዊነት ስም የግሉን ዘርፍ አቀጭጮ፣ ሀብት ፈጣሪነትን አውግዞ ሀገርን ለከፋ የኢኮኖሚ ቀውስና አዙሪት ዳርጓል።
የኢሕአዴግ መንግሥት በበኩሉ ብሔርን ከአስተዳደራዊ ወሰን ጋር በማስተሳሰሩ ጽንፈኝነትን ያቀጣጠለ፣ ሀገራዊ አንድነትን የሸረሸረ እና በመጨረሻም የሀገር ሀብት በጥቂት የፖለቲካ ልሂቃን እጅ እንዲወድቅ ያደረገ ፣እነዚህ ሁሉ መንግሥታት ከዜሮ ድምር ፖለቲካ፣ ተቀናቃኝን አሳዶ ከማጥፋት፣ እና የሕዝብን እያደገ የሚመጣ ፍላጎት በጊዜው ካለመመለስ አባዜ አልወጡም ነበር።
ከዚህ በተቃራኒ፣ የመደመር መንግሥት የገበያ መር እና የመንግሥት መር ፅንፎችን በማስወገድ "የትብብር ሞዴልን" ገንዘቡ ያደርጋል። የግሉ ዘርፍ ሀብት እንዲፈጥር ሲያበረታታ፣ መንግሥትም ራሱ በኢንተርፕረነርሺፕ (ስራ ፈጣሪነት)ዕሳቤ አዳዲስ ዘርፎችን በመፍጠርና ሀገራዊ ሀብትን በማከማቸት ይተጋል።
የመደመር መንግሥት ሌላው ግዙፍ መለያው "የዔሊ ጉዞን" ሰብሮ በ"ፍጥነት፣ ፈጠራ እና ዝላይ" መገስገሱ ነው። አዳጊ ሀገራት የበለፀጉት ሀገራት የሄዱበትን የክፍለ ዘመናት አዝጋሚ (ደረጃ በደረጃ) ጉዞ መከተል የለባቸውም በማለት፣ ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ በቀጥታ በመቀላቀል "የዝላይ መንገድን" (Leapfrogging) በመጠቀም ኢትዮጵያን ተወዳዳሪ ለማድረግ ይሠራል።
ከዚህም ባሻገር፣ የመደመር መንግሥት "ምናባዊ ከፍታን" ተላብሷል። የይድረስ ይድረስ ጊዜያዊ ማስታገሻዎችን ትቶ፣ እንደ አዲስ አበባ ወንዞች ልማት (ገበታ ለሸገር) እና የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብሮችን በመሰሉ ሩቅ አላሚ ፕሮጀክቶች ሀሳብን ወደ መሬት በማውረድ "የማድረግ ዐቅሙን" በተግባር አረጋግጧል።
በአጠቃላይ የመደመር መንግሥት የትናንትናውን የተከማቸ ዕዳ በፈጠራ የሚያቃልል፣ ያመለጠንን የኢንዱስትሪ አብዮት ጊዜ የሚያካክስ፣ እና ኢትዮጵያን በጠንካራ ሥርዓታዊ መዋቅርና ትብብር ወደ ብልጽግና ማማ የሚያሸጋግር መሪ ብርሃን ነው።
በአዶኒያስ ወ/አረጋይ
#ethiopianbroadcastingcorporation #medemer #philosophyofmedemer #nationalunity
********
ታሪክን ወደ ኋላ መለስ ብለን ስንቃኝ፣ ኢትዮጵያ የነፃነት ተምሳሌት፣ የጥንታዊ ስልጣኔ ባለቤት፣ እና የብዙ ፀጋዎች ማህደር ሆና እናገኛታለን።
አባቶቻችን በደማቸው አቅንተውና ጠብቀው ያቆዩልንን ይህች ምድር፣ ሀብቷ ሳይደመርና አ ቅሟ ሳይቀናጅ ለዘመናት በመቆየቱ ምክንያት፣ በእጦት አዙሪትና በድህነት ማጥ ውስጥ ስትዳክር ኖራለች።
“የኢትዮጵያውያንን ህይወት እንለውጣለን” የሚለው መፈክር በተፈራረቁ መንግስታትና ትውልዶች ዘንድ በተደጋግሚ ቢነገርም፣ በተግባር ግን እንደ ጉም ርቆን፣ እንደ ህልም ተንሳፎ ቆይቷል።
ዘመናት ነጎዱ፣ ትውልዶች ተፈራረቁ፤ እኛ ግን በተረገጥንበት ቦታ መቆማችንን አልተውንም። በዚህ የታሪክ መስቀለኛ መንገድ እና በተከማቸ የቤት ስራ አጣብቂኝ ውስጥ ነው እንግዲህ "የመደመር መንግስት" ብቅ ያለው።
ለመሆኑ የመደመር መንግስት ምንነት ምንድን ነው?
የመደመር መንግስት ማለት መከፋፈልን፣ መነጠልን፣ እና የአንዱን መቃብር የሌላው ዙፋን የሚያደርገውን የዜሮ ድምር ጨዋታ በመፀየፍ፣ ሀገራዊ ፀጋዎችንና አቅሞችን ወደ አንድ የብልፅግና ወንዝ የሚያፈስ ስርዓት ነው። በመደመር ፍልስፍና መነፅር፣ የመንግስት ሚና እንደ ባለፈው ዘመን ሁሉን አድራጊ ፈጣሪ ወይም ጨቋኝ መሆን ሳይሆን፣ የትብብር ሞተር መሆን ነው።
ይህ መንግስት ዜጎችን፣ የግሉን ዘርፍ፣ እና ሀገራዊ አቅሞችን በማስተባበር፤ ትላንት ያመለጠንን የባከነ ጊዜ "በፈጠራ እና በፍጥነት" የሚያካክስ፣ ገቢር ነበብ (Pragmatic) የሆነ የዘመነ መንግስታዊ መዋቅር ነው።
መሰረታዊ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ዲፓርቸሩም ይሄው ነው፡ ትናንትን ከስህተቱ ተምሮ ማረም፣ ዛሬን በትጋት መስራት፣ እና ነገን በምናብ ተልሞ ማለም።
የመደመር መንግሥት ስንል፣ በፍልስፍና መሠረቱ ከታሕታይ መዋቅር (እንደ ኢኮኖሚ እና መሠረተ ልማት) ለውጥ ይልቅ ለላዕላይ መዋቅር (አስተሳሰብ እና ባህል) ለውጥ ቅድሚያ የሚሰጥ ሥርዓት ማለታችን ነው። ይህ መንግሥት የማኅበረሰብን ልዩ ልዩ ጸጋዎች፣ ዕሴቶች፣ እና አቅሞች ማሰባሰብ ለብልጽግና ወሳኝ መሆኑን በፅኑ ያምናል።
የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ኃይሎች በሚፈጥሩት ፍትጊያ ውስጥ ሚዛን (ወርቃማውን አማካይ) በመጠበቅ ሁሉንም አቅፎ የሚጓዝ ነው።
ይህንን እውነት ይበልጥ ለመረዳት የመደመርን መንግሥት መሠረታዊ መለያዎች ካለፉት መንግሥታት ታሪክ ጋር ማነፃፀር ግድ ይላል።
የሀገራችን የፖለቲካ ጉዞ ከውጭ ሀገር (ከምዕራብም ሆነ ከምሥራቅ) የልማት ሞዴሎችን እንዳለ ገልብጦ በማምጣት የኢትዮጵያን ነባራዊ እውነታ ለማሳጣት ሲጥር የኖረ ፤የንጉሡ ሥርዓት "ሰማይ አይታረስ፣ ንጉሥ አይከሰስ" በሚል መርህ አይነኬነትን ያነገሠ፣ ለውጥን የሚጠላና ቆሞ-ቀርነትን ያተረፈ ፊውዳላዊ ሥርዓት ሆና የተካው የደርግ መንግሥት ደግሞ የሶቪየትን ሞዴል በጭፍን በመከተል "ትሻልን ሰድጄ ትብስን አመጣሁ" እንዲሉ፣ በኅብረተሰብአዊነት ስም የግሉን ዘርፍ አቀጭጮ፣ ሀብት ፈጣሪነትን አውግዞ ሀገርን ለከፋ የኢኮኖሚ ቀውስና አዙሪት ዳርጓል።
የኢሕአዴግ መንግሥት በበኩሉ ብሔርን ከአስተዳደራዊ ወሰን ጋር በማስተሳሰሩ ጽንፈኝነትን ያቀጣጠለ፣ ሀገራዊ አንድነትን የሸረሸረ እና በመጨረሻም የሀገር ሀብት በጥቂት የፖለቲካ ልሂቃን እጅ እንዲወድቅ ያደረገ ፣እነዚህ ሁሉ መንግሥታት ከዜሮ ድምር ፖለቲካ፣ ተቀናቃኝን አሳዶ ከማጥፋት፣ እና የሕዝብን እያደገ የሚመጣ ፍላጎት በጊዜው ካለመመለስ አባዜ አልወጡም ነበር።
ከዚህ በተቃራኒ፣ የመደመር መንግሥት የገበያ መር እና የመንግሥት መር ፅንፎችን በማስወገድ "የትብብር ሞዴልን" ገንዘቡ ያደርጋል። የግሉ ዘርፍ ሀብት እንዲፈጥር ሲያበረታታ፣ መንግሥትም ራሱ በኢንተርፕረነርሺፕ (ስራ ፈጣሪነት)ዕሳቤ አዳዲስ ዘርፎችን በመፍጠርና ሀገራዊ ሀብትን በማከማቸት ይተጋል።
የመደመር መንግሥት ሌላው ግዙፍ መለያው "የዔሊ ጉዞን" ሰብሮ በ"ፍጥነት፣ ፈጠራ እና ዝላይ" መገስገሱ ነው። አዳጊ ሀገራት የበለፀጉት ሀገራት የሄዱበትን የክፍለ ዘመናት አዝጋሚ (ደረጃ በደረጃ) ጉዞ መከተል የለባቸውም በማለት፣ ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ በቀጥታ በመቀላቀል "የዝላይ መንገድን" (Leapfrogging) በመጠቀም ኢትዮጵያን ተወዳዳሪ ለማድረግ ይሠራል።
ከዚህም ባሻገር፣ የመደመር መንግሥት "ምናባዊ ከፍታን" ተላብሷል። የይድረስ ይድረስ ጊዜያዊ ማስታገሻዎችን ትቶ፣ እንደ አዲስ አበባ ወንዞች ልማት (ገበታ ለሸገር) እና የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብሮችን በመሰሉ ሩቅ አላሚ ፕሮጀክቶች ሀሳብን ወደ መሬት በማውረድ "የማድረግ ዐቅሙን" በተግባር አረጋግጧል።
በአጠቃላይ የመደመር መንግሥት የትናንትናውን የተከማቸ ዕዳ በፈጠራ የሚያቃልል፣ ያመለጠንን የኢንዱስትሪ አብዮት ጊዜ የሚያካክስ፣ እና ኢትዮጵያን በጠንካራ ሥርዓታዊ መዋቅርና ትብብር ወደ ብልጽግና ማማ የሚያሸጋግር መሪ ብርሃን ነው።
በአዶኒያስ ወ/አረጋይ
#ethiopianbroadcastingcorporation #medemer #philosophyofmedemer #nationalunity
1 month ago
በጠቅላላ ምርጫው በርካታ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምክር ቤት ወንበር ማሸነፋቸው የዴሞክራሲ ምህዳሩን መስፋት ያረጋገጠ ነው፡- የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች
*******************
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በስኬት የተካሄደውን የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ይፋ ማድረጉን ተከትሎ፣ በርካታ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምክር ቤት ወንበሮችን ማሸነፋቸው በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ምህዳሩ እየሰፋ መመጣቱን በተግባር ያሳየ መሆኑን የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ።
ይህ ስኬት በክልል እና በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተሻለ የሀሳብ ብዝኃነት እንዲኖርና ጠንካራ የመንግሥት ተቋማትን የመገንባት ሂደትን ለማሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተጠቁሟል።
በተገለጸው የምርጫ ውጤት መሠረት ብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 438 መቀመጫዎችን ሲያገኝ፤ ኢዜማ 13፣ አብን 6፣ ነእፓ 3፣ መድረክ 3፣ አዴኃን 3፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት 2 ወንበሮችን ያሸነፉ ሲሆን ሌሉች 10 ተፎካካሪ ፓርቲዎች ደግሞ እያንዳንዳቸው አንድ የምክር ቤት ወንበር አግኝተዋል።
ለክልል ምክር ቤት በተደረገው ውድድርም ኢዜማ 73፣ ነእፓ 35፣ ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት 34፣ ኦብነግ 20፣ ጉህዴን 14፣ መድረክ 11፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት 6፣ ሕዳሴ ፓርቲ 5 እና ቤህነን 5 ወንበሮችን ማሸነፍ ችለዋል።
የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወይዘሮ ነቢሃ መሀመድ ምርጫው የሕዝብ ድምፅ መንግሥት ለመመስረት ብቸኛው መንገድ መሆኑንና መንግሥት የሚመሰረተው በኃይል ሳይሆን በሐሳብ ብቻ መሆኑን ያስተማረ ነው ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
አያይዘውም ፓርቲያቸው በሀገራዊ ጥቅም፣ በሉዓላዊነት፣ በወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራና በምግብ ዋስትና ዙሪያ ከብልጽግና ፓርቲ ጋር በትብብር ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል የወሎ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ፕሬዝዳንት አቶ ነጻነት ጣሰው ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር እስከ ታችኛው መዋቅር ተቀራርቦ መሥራት ሀገር ለማሻገር ቁልፍ ሚና እንዳለው በመጥቀስ፣ ለሀገረ መንግሥት ግንባታና ለሀገራዊ ምክክሩ መሳካት ፓርቲያቸው የፖሊሲ ምክረ ሐሳቦችን በጥናት ለይቶ በማቅረብ ኃላፊነቱን እንደሚወጣ አስታውቀዋል።
#ethiopiaelections #democracy #politicalpluralism #nationalunity #ethiopianbroadcastingcorporation
*******************
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በስኬት የተካሄደውን የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ይፋ ማድረጉን ተከትሎ፣ በርካታ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምክር ቤት ወንበሮችን ማሸነፋቸው በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ምህዳሩ እየሰፋ መመጣቱን በተግባር ያሳየ መሆኑን የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ገለጹ።
ይህ ስኬት በክልል እና በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተሻለ የሀሳብ ብዝኃነት እንዲኖርና ጠንካራ የመንግሥት ተቋማትን የመገንባት ሂደትን ለማሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተጠቁሟል።
በተገለጸው የምርጫ ውጤት መሠረት ብልፅግና ፓርቲ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 438 መቀመጫዎችን ሲያገኝ፤ ኢዜማ 13፣ አብን 6፣ ነእፓ 3፣ መድረክ 3፣ አዴኃን 3፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት 2 ወንበሮችን ያሸነፉ ሲሆን ሌሉች 10 ተፎካካሪ ፓርቲዎች ደግሞ እያንዳንዳቸው አንድ የምክር ቤት ወንበር አግኝተዋል።
ለክልል ምክር ቤት በተደረገው ውድድርም ኢዜማ 73፣ ነእፓ 35፣ ሰላም ለኢትዮጵያ ጥምረት 34፣ ኦብነግ 20፣ ጉህዴን 14፣ መድረክ 11፣ ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት 6፣ ሕዳሴ ፓርቲ 5 እና ቤህነን 5 ወንበሮችን ማሸነፍ ችለዋል።
የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወይዘሮ ነቢሃ መሀመድ ምርጫው የሕዝብ ድምፅ መንግሥት ለመመስረት ብቸኛው መንገድ መሆኑንና መንግሥት የሚመሰረተው በኃይል ሳይሆን በሐሳብ ብቻ መሆኑን ያስተማረ ነው ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
አያይዘውም ፓርቲያቸው በሀገራዊ ጥቅም፣ በሉዓላዊነት፣ በወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራና በምግብ ዋስትና ዙሪያ ከብልጽግና ፓርቲ ጋር በትብብር ለመሥራት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል የወሎ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ፕሬዝዳንት አቶ ነጻነት ጣሰው ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር እስከ ታችኛው መዋቅር ተቀራርቦ መሥራት ሀገር ለማሻገር ቁልፍ ሚና እንዳለው በመጥቀስ፣ ለሀገረ መንግሥት ግንባታና ለሀገራዊ ምክክሩ መሳካት ፓርቲያቸው የፖሊሲ ምክረ ሐሳቦችን በጥናት ለይቶ በማቅረብ ኃላፊነቱን እንደሚወጣ አስታውቀዋል።
#ethiopiaelections #democracy #politicalpluralism #nationalunity #ethiopianbroadcastingcorporation
2 months ago
ሚዲያዎች የማኅበረሰብ ትስስርን በማጉላት ለሀገራዊ አንድነት መጠናከር ሊሰሩ ይገባል፡- የሰላም ሚኒስቴር
****************
የሰላም ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ጋር በመቀናጀት "የሚዲያ ተቋማት ሚና ለሰላም ግንባታ" በሚል ርዕስ ያዘጋጁት የምክክር መድረክ በሐዋሳ ከተማ ተካሂዷል።
በምክክር መድረኩ ላይ የሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ እና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኬይረዲን ተዘራ (ዶ/ር) ተገኝተው ባደረጉት ንግግር፤ ሚዲያ በአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ሂደት ላይ በአዎንታዊም ሆነ በአሉታዊ ጎኑ የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ተቋማቱ በኃላፊነት ስሜትና በአግባቡ ጥቅም ላይ ከዋሉ ለዘላቂ ሰላምና ለብሔራዊ መግባባት ያላቸው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ሚዲያዎች የማኅበረሰቡን የጋራ እሴቶች በማጉላት ለብሔራዊ ጥቅሞች ስኬት ዜጎች የጋራ አረዳድ እንዲኖራቸው ሊሠሩ እንደሚገባ የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፤ በተለይም አሁን ባለንበት የድኅረ-እውነት ዘመን መገናኛ ብዙኃን ሕዝቡ ለዘመናት ጠብቆ ያኖራቸውን ማኅበረ-ባህላዊ ሀብቶች በማስተዋወቅና ሰላምን በማስረጽ ረገድ የማይተካ ሚናቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛው ተስፋዬ በበኩላቸው፤ ሚዲያዎች የሕዝብን ወንድማማችነት፣ አንድነትና ሰላምን በመገንባት ቴክኖሎጂው የፈጠረውን የሐሰተኛ መረጃ ስርጭት የማክሸፍ ከፍተኛ ኃላፊነት እንዳለባቸውና ከግጭት ጋር የተያያዙ ችግሮችን በዲጂታል ሥርዓት ለመፍታት መሥራት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።
መገናኛ ብዙኃን የማኅበረሰቡ የምክክር ማዕከል ሆነው ለማገልገል ከፍተኛ ሚና ያላቸው በመሆኑ መንግሥት ከእነሱ ጋር ያለውን የጋራ ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው፣ የሰላም ሚኒስቴር የብዙኃን መገናኛ ተቋማትን በማስተባበር ለሀገራዊ ሰላም እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
በመድረኩ ላይ በሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አወቀ አጥናፉ (ዶ/ር) "ሚዲያን የሚመሩ እና የሚያስተዳድሩ ሕጎች" በሚል ርዕስ የመወያያ ሰነድ አቅርበው ሰፊ ውይይት የተደረገበት ሲሆን፤ ከተለያዩ ክልሎች የመጡ የሚዲያ አመራሮች፣ የኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊዎች፣ የቴሌቪዥንና የማኅበረሰብ ሬዲዮ ባለሙያዎች እንዲሁም የማኅበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች በጋራ ተሳትፈውበታል።
በአስረሳው ወገሼ
#ethiopianbroadcastingcorporation #ministryofpeace #mediaforpeace #nationalunity #ethiopia
****************
የሰላም ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ጋር በመቀናጀት "የሚዲያ ተቋማት ሚና ለሰላም ግንባታ" በሚል ርዕስ ያዘጋጁት የምክክር መድረክ በሐዋሳ ከተማ ተካሂዷል።
በምክክር መድረኩ ላይ የሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ እና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኬይረዲን ተዘራ (ዶ/ር) ተገኝተው ባደረጉት ንግግር፤ ሚዲያ በአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ሂደት ላይ በአዎንታዊም ሆነ በአሉታዊ ጎኑ የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ተቋማቱ በኃላፊነት ስሜትና በአግባቡ ጥቅም ላይ ከዋሉ ለዘላቂ ሰላምና ለብሔራዊ መግባባት ያላቸው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ሚዲያዎች የማኅበረሰቡን የጋራ እሴቶች በማጉላት ለብሔራዊ ጥቅሞች ስኬት ዜጎች የጋራ አረዳድ እንዲኖራቸው ሊሠሩ እንደሚገባ የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፤ በተለይም አሁን ባለንበት የድኅረ-እውነት ዘመን መገናኛ ብዙኃን ሕዝቡ ለዘመናት ጠብቆ ያኖራቸውን ማኅበረ-ባህላዊ ሀብቶች በማስተዋወቅና ሰላምን በማስረጽ ረገድ የማይተካ ሚናቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛው ተስፋዬ በበኩላቸው፤ ሚዲያዎች የሕዝብን ወንድማማችነት፣ አንድነትና ሰላምን በመገንባት ቴክኖሎጂው የፈጠረውን የሐሰተኛ መረጃ ስርጭት የማክሸፍ ከፍተኛ ኃላፊነት እንዳለባቸውና ከግጭት ጋር የተያያዙ ችግሮችን በዲጂታል ሥርዓት ለመፍታት መሥራት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።
መገናኛ ብዙኃን የማኅበረሰቡ የምክክር ማዕከል ሆነው ለማገልገል ከፍተኛ ሚና ያላቸው በመሆኑ መንግሥት ከእነሱ ጋር ያለውን የጋራ ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው፣ የሰላም ሚኒስቴር የብዙኃን መገናኛ ተቋማትን በማስተባበር ለሀገራዊ ሰላም እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
በመድረኩ ላይ በሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አወቀ አጥናፉ (ዶ/ር) "ሚዲያን የሚመሩ እና የሚያስተዳድሩ ሕጎች" በሚል ርዕስ የመወያያ ሰነድ አቅርበው ሰፊ ውይይት የተደረገበት ሲሆን፤ ከተለያዩ ክልሎች የመጡ የሚዲያ አመራሮች፣ የኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊዎች፣ የቴሌቪዥንና የማኅበረሰብ ሬዲዮ ባለሙያዎች እንዲሁም የማኅበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች በጋራ ተሳትፈውበታል።
በአስረሳው ወገሼ
#ethiopianbroadcastingcorporation #ministryofpeace #mediaforpeace #nationalunity #ethiopia
2 months ago
ምክክር፦ ብቸኛው የፈተናዎቻችን ማለፊያ
*****************
ኢትዮጵያ በዘመናት ፈተና ውስጥ አልፋ ለዛሬ የደረሰችው በሕዝቦቿ ልዩ መስተጋብር እና ጥብቅ አንድነት ነው።
ታሪካችንን ወደኋላ ስንቃኝ በሕብረት ጦርነቶችን አሸንፈን የጋራ ነጻነታችንን ያስከበርን፣ በአንድ መሶብ ዙሪያ ከብበን በጋራ የበላን፣ "እኔ ልደፋልህ/ልደፋልሽ" መባባልን የመሰለ ድንቅ ባህል ያዳበርን ሕዝቦች ነን።
ሀገር በባዕዳን ተደፈረች ሲባል የውስጥ ልዩነታችንን ወደ ጎን ትተን ወደ ጦር ሜዳ የተመምነው እና ኢትዮጵያን በፈተናዎች ውስጥ ጠብቀን ያኖርነው በዚህ የጋራ ሥነ-ልቦና ነው።
ይሁን እና ይህ ሁሉ ታሪክ እያለን ዛሬ ላይ "በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብለን በመመካከር ችግሮቻችንን መፍታት ለምን ተሳነን?" የሚለው ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ የሚሻ ጉዳይ ነው።
የዘመናዊው የኢትዮጵያ ፖለቲካ አመጣጥ ከታሪካዊ እሴቶቻችን ጋር በእጅጉ የተላተመ ነው። የፖለቲካው ስብራት ያመጣው ትልቁ መጥፎ ጠባሳ የጋራ ትርክትን አዳክሞ የልዩነት፣ የመጠፋፋት እና የጥላቻ ትርክትን ማንገሡ ነው።
አንዱን አግልሎ እና ሙሉ ለሙሉ አሸንፎ ሥልጣን ላይ የመውጣት የዜሮ ድምር ፖለቲካ የኢትዮጵያ ትልቁ በሽታ ነው።
ይህ አካሄድ እርስ በርስ የመደጋገፍና ችግርን የመካፈል መልካም ባህላችንን በመሸርሸር፣ “እኔ ካልመራሁ ሀገር ትፍረስ” ወደሚል አደገኛና ራስ ወዳድነት የተሞላበት አስተሳሰብ አሸጋግሮናል።
ይህ የውስጥ መከፋፈልና ቀውስ ደግሞ ለውጭ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትና ተፅዕኖ ሰፊ በር ከፍቷል።
ኢትዮጵያ በዚህ የታሪክ አዙሪት ውስጥ ስታልፍ ሥጣኔዋን ማስቀጠል ተስኗታል። በሕብረት ለነጻነት በጦር የተዋደቁት ልጆቿ ድህነትን ለማጥፋት ባለመተባበራቸው የተሟላ ሉዓላዊነቷን ማረጋገጥ ተስኗት ኖራለች።
የሚያሳዝነው እውነታ ይህን የፖለቲካ ቋጠሮ ለመፍታት የሚያስችል ለዘመናት የኖረ ድንቅ ሀገር በቀል የሽምግልና እና የዕርቅ ባህል እያለን በበቂ ሁኔታ አለመጠቀማችን ነው።
ችግሮቻችንን ከማኅበረሰባዊ እሴቶቻችን፣ ከሃይማኖት አባቶች ተሰሚነት እንዲሁም እንደ ገዳ፣ የጆካ፣ አባጋር፣ መካባን ከመሳሰሉ ጠንካራ ማኅበረሰባዊ የፍትሕ እና የዕርቅ ሥርዓቶቻችን ማዕቀፍ ውጪ በሆነ መንገድ ለመፍታት መሞከራችን ከባድ ዋጋ አስከፍሎናል።
ከውጭ በገቡ ፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለሞች ብቻ ለመጓዝ መሞከራችን እና ባህላዊ የዕርቅ ሥርዓቶቻችንን ከፖለቲካ መጠቀሚያነት ነጻ አድርገን አለማጎልበታችን ለዛሬው የውይይት ባህል መጥፋት ትልቁን ድርሻ ይወስዳል።
ታዲያ አሁን ምን ማድረግ አለብን?
መፍትሔው ወደ አውዳችን መመለስ ነው። የውጭ ተፅዕኖን ለመቋቋም መጀመሪያ የራስን ቤት ማጽዳት እና ሕብረትን ማጠናከር የግድ ይላል።
ፖለቲከኞች እና የሐሳብ መሪዎች የመሸናነፍ ሳይሆን የመደማመጥ እንዲሁም ለሀገር ሰላም ሲሉ ግትር የሆነ አቋምን የማለዘብ ባህልን በተግባር ሊያሳዩ ይገባል።
በተለይም ወጣቱ ትውልድ በዲጂታሉ ዓለም ያለውን ስሜታዊነት ወደ ጎን በመተው ምክንያታዊ ውይይቶችን ሊያበረታታ ይገባል።
ሚዲያው፣ የትምህርት ሥርዓቱ፣ የኪነ-ጥበብ ዘርፉ ካለፉት ቁስሎች ይልቅ ወደ ፊት በሚያገናኙን የጋራ እሴቶች እና የወደፊት ዕጣ ፈንታችን ላይ ሊያተኩር ግድ ይላል።
በዚህ ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ላይ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሚና እጅግ የጎላ ነው። ኮሚሽኑ የጠፋውን የጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት ለመመለስ የተዘረጋ ዘመናዊ የቤተሰብ መሶባችን ሊሆን ይገባዋል።
አሁን የተጀመሩት የምክክር ሂደቶች ሁሉን አሳታፊ፣ ከፖለቲካዊ ጨዋታ ነጻ የሆኑ እና እውነተኛ ማኅበረሰባዊ ስብራቶቻችንን የሚጠግኑ እንዲሆኑ የሚቻለው ሁሉ ተደርጓል።
ሀገራዊ ምክክሩ ባህላዊ የዕርቅ እሴቶቻችንን ከዘመናዊ የመንግሥት ግንባታ ጋር አዋሕዶ የዘለቄታ ሰላም የምናመጣበት ታላቅ ዕድል ነው።
በጠረጴዛ ዙሪያ የማይፈታ የትኛውም የፖለቲካ ችግር በጦር ሜዳ ዘላቂ መፍትሔ እንደማያገኝ ታሪካችን ከበቂ በላይ አስተምሮናል።
በመሆኑም ሁላችንም ወደኋላ ከጎተተን የ“እኔ እበልጥ” ክፉ ልማድ ወጥተን ለምክክሩ ስኬት የበኩላችንን ልንወጣ ይገባል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #nationaldialogue #dotstream #peacebuilding #nationalunity
*****************
ኢትዮጵያ በዘመናት ፈተና ውስጥ አልፋ ለዛሬ የደረሰችው በሕዝቦቿ ልዩ መስተጋብር እና ጥብቅ አንድነት ነው።
ታሪካችንን ወደኋላ ስንቃኝ በሕብረት ጦርነቶችን አሸንፈን የጋራ ነጻነታችንን ያስከበርን፣ በአንድ መሶብ ዙሪያ ከብበን በጋራ የበላን፣ "እኔ ልደፋልህ/ልደፋልሽ" መባባልን የመሰለ ድንቅ ባህል ያዳበርን ሕዝቦች ነን።
ሀገር በባዕዳን ተደፈረች ሲባል የውስጥ ልዩነታችንን ወደ ጎን ትተን ወደ ጦር ሜዳ የተመምነው እና ኢትዮጵያን በፈተናዎች ውስጥ ጠብቀን ያኖርነው በዚህ የጋራ ሥነ-ልቦና ነው።
ይሁን እና ይህ ሁሉ ታሪክ እያለን ዛሬ ላይ "በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብለን በመመካከር ችግሮቻችንን መፍታት ለምን ተሳነን?" የሚለው ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ የሚሻ ጉዳይ ነው።
የዘመናዊው የኢትዮጵያ ፖለቲካ አመጣጥ ከታሪካዊ እሴቶቻችን ጋር በእጅጉ የተላተመ ነው። የፖለቲካው ስብራት ያመጣው ትልቁ መጥፎ ጠባሳ የጋራ ትርክትን አዳክሞ የልዩነት፣ የመጠፋፋት እና የጥላቻ ትርክትን ማንገሡ ነው።
አንዱን አግልሎ እና ሙሉ ለሙሉ አሸንፎ ሥልጣን ላይ የመውጣት የዜሮ ድምር ፖለቲካ የኢትዮጵያ ትልቁ በሽታ ነው።
ይህ አካሄድ እርስ በርስ የመደጋገፍና ችግርን የመካፈል መልካም ባህላችንን በመሸርሸር፣ “እኔ ካልመራሁ ሀገር ትፍረስ” ወደሚል አደገኛና ራስ ወዳድነት የተሞላበት አስተሳሰብ አሸጋግሮናል።
ይህ የውስጥ መከፋፈልና ቀውስ ደግሞ ለውጭ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትና ተፅዕኖ ሰፊ በር ከፍቷል።
ኢትዮጵያ በዚህ የታሪክ አዙሪት ውስጥ ስታልፍ ሥጣኔዋን ማስቀጠል ተስኗታል። በሕብረት ለነጻነት በጦር የተዋደቁት ልጆቿ ድህነትን ለማጥፋት ባለመተባበራቸው የተሟላ ሉዓላዊነቷን ማረጋገጥ ተስኗት ኖራለች።
የሚያሳዝነው እውነታ ይህን የፖለቲካ ቋጠሮ ለመፍታት የሚያስችል ለዘመናት የኖረ ድንቅ ሀገር በቀል የሽምግልና እና የዕርቅ ባህል እያለን በበቂ ሁኔታ አለመጠቀማችን ነው።
ችግሮቻችንን ከማኅበረሰባዊ እሴቶቻችን፣ ከሃይማኖት አባቶች ተሰሚነት እንዲሁም እንደ ገዳ፣ የጆካ፣ አባጋር፣ መካባን ከመሳሰሉ ጠንካራ ማኅበረሰባዊ የፍትሕ እና የዕርቅ ሥርዓቶቻችን ማዕቀፍ ውጪ በሆነ መንገድ ለመፍታት መሞከራችን ከባድ ዋጋ አስከፍሎናል።
ከውጭ በገቡ ፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለሞች ብቻ ለመጓዝ መሞከራችን እና ባህላዊ የዕርቅ ሥርዓቶቻችንን ከፖለቲካ መጠቀሚያነት ነጻ አድርገን አለማጎልበታችን ለዛሬው የውይይት ባህል መጥፋት ትልቁን ድርሻ ይወስዳል።
ታዲያ አሁን ምን ማድረግ አለብን?
መፍትሔው ወደ አውዳችን መመለስ ነው። የውጭ ተፅዕኖን ለመቋቋም መጀመሪያ የራስን ቤት ማጽዳት እና ሕብረትን ማጠናከር የግድ ይላል።
ፖለቲከኞች እና የሐሳብ መሪዎች የመሸናነፍ ሳይሆን የመደማመጥ እንዲሁም ለሀገር ሰላም ሲሉ ግትር የሆነ አቋምን የማለዘብ ባህልን በተግባር ሊያሳዩ ይገባል።
በተለይም ወጣቱ ትውልድ በዲጂታሉ ዓለም ያለውን ስሜታዊነት ወደ ጎን በመተው ምክንያታዊ ውይይቶችን ሊያበረታታ ይገባል።
ሚዲያው፣ የትምህርት ሥርዓቱ፣ የኪነ-ጥበብ ዘርፉ ካለፉት ቁስሎች ይልቅ ወደ ፊት በሚያገናኙን የጋራ እሴቶች እና የወደፊት ዕጣ ፈንታችን ላይ ሊያተኩር ግድ ይላል።
በዚህ ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ላይ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሚና እጅግ የጎላ ነው። ኮሚሽኑ የጠፋውን የጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት ለመመለስ የተዘረጋ ዘመናዊ የቤተሰብ መሶባችን ሊሆን ይገባዋል።
አሁን የተጀመሩት የምክክር ሂደቶች ሁሉን አሳታፊ፣ ከፖለቲካዊ ጨዋታ ነጻ የሆኑ እና እውነተኛ ማኅበረሰባዊ ስብራቶቻችንን የሚጠግኑ እንዲሆኑ የሚቻለው ሁሉ ተደርጓል።
ሀገራዊ ምክክሩ ባህላዊ የዕርቅ እሴቶቻችንን ከዘመናዊ የመንግሥት ግንባታ ጋር አዋሕዶ የዘለቄታ ሰላም የምናመጣበት ታላቅ ዕድል ነው።
በጠረጴዛ ዙሪያ የማይፈታ የትኛውም የፖለቲካ ችግር በጦር ሜዳ ዘላቂ መፍትሔ እንደማያገኝ ታሪካችን ከበቂ በላይ አስተምሮናል።
በመሆኑም ሁላችንም ወደኋላ ከጎተተን የ“እኔ እበልጥ” ክፉ ልማድ ወጥተን ለምክክሩ ስኬት የበኩላችንን ልንወጣ ይገባል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #nationaldialogue #dotstream #peacebuilding #nationalunity
Sponsored by
Surafel
2 months ago
2 months ago
ሀገርነት የሚገነባው ከመውሰድ ይልቅ በመስጠት ነው፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
********************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ (ዐረፋ) በዓል ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት፣ ዜጎች ከግል ጥቅማቸው ይልቅ ለሀገርና ለሉዓላዊነት ቅድሚያ በመስጠት መስዋዕትነት ሊከፍሉ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው የዐረፋን በዓል ታሪካዊ ዳራ በማስታወስ፣ ወስነብዩ ኢብራሂም ልጃቸውን እስማኤልን ለመስዋዕትነት ለማቅረብ ያሳዩትን ቆራጥነት እንደ ትልቅ ማሳያ ጠቅሰዋል።
"ሀገር የምትገነባው ከራስ ጥቅም በላይ በሚያስቡ እና ከግላዊ ፍላጎታቸው በላይ ለመፈጸም በቆረጡ ዜጎች ነው" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ኢትዮጵያም ጠንካራና ጽኑ ሀገር መሆን የምትችለው የሚወዱትን ነገር ሳይቀር ለሀገራቸው ለመሠዋት ዝግጁ የሆኑ ዜጎች ሲበዙላት መሆኑን አስገንዝበዋል።
በተጨማሪም "የለመድናቸው፣ የምንወዳቸው፣ የራሳችን ገንዘብ ያደረግናቸው ብዙ ነገሮች ይኖራሉ። ከእነዚህ የሚበልጥ ዓላማ ግን አለ፤ እሱም 'ሀገርነት እና ሉዓላዊነት' ይሰኛል" በማለት፣ ሉዓላዊነት የሚጸናው በፈተና ሳይወድቁ በመቆምና በወጀብ ሳይናወጡ መጓዝ በመቻል እንደሆነ አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ የበለጸገች ሀገር ሆና እንድትወጣ የሚመኙ ሁሉ ምኞታቸውን በተግባር እንዲገልጹ፣ ድህነትን ለማሸነፍና የሀገርን ክብር ለመመለስ ሌት ተቀን እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።
"ሀገር መውደዳችን ከልብ ከሆነ መስዋዕት ለመሆን አናመንታ" ሲሉም ጠንካራ ሀገራዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
#eidaladha #pmabiyahmed #ethiopia #patriotism #nationalunity #ethiopianbroadcastingcorporation
********************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ (ዐረፋ) በዓል ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት፣ ዜጎች ከግል ጥቅማቸው ይልቅ ለሀገርና ለሉዓላዊነት ቅድሚያ በመስጠት መስዋዕትነት ሊከፍሉ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው የዐረፋን በዓል ታሪካዊ ዳራ በማስታወስ፣ ወስነብዩ ኢብራሂም ልጃቸውን እስማኤልን ለመስዋዕትነት ለማቅረብ ያሳዩትን ቆራጥነት እንደ ትልቅ ማሳያ ጠቅሰዋል።
"ሀገር የምትገነባው ከራስ ጥቅም በላይ በሚያስቡ እና ከግላዊ ፍላጎታቸው በላይ ለመፈጸም በቆረጡ ዜጎች ነው" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ኢትዮጵያም ጠንካራና ጽኑ ሀገር መሆን የምትችለው የሚወዱትን ነገር ሳይቀር ለሀገራቸው ለመሠዋት ዝግጁ የሆኑ ዜጎች ሲበዙላት መሆኑን አስገንዝበዋል።
በተጨማሪም "የለመድናቸው፣ የምንወዳቸው፣ የራሳችን ገንዘብ ያደረግናቸው ብዙ ነገሮች ይኖራሉ። ከእነዚህ የሚበልጥ ዓላማ ግን አለ፤ እሱም 'ሀገርነት እና ሉዓላዊነት' ይሰኛል" በማለት፣ ሉዓላዊነት የሚጸናው በፈተና ሳይወድቁ በመቆምና በወጀብ ሳይናወጡ መጓዝ በመቻል እንደሆነ አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ የበለጸገች ሀገር ሆና እንድትወጣ የሚመኙ ሁሉ ምኞታቸውን በተግባር እንዲገልጹ፣ ድህነትን ለማሸነፍና የሀገርን ክብር ለመመለስ ሌት ተቀን እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።
"ሀገር መውደዳችን ከልብ ከሆነ መስዋዕት ለመሆን አናመንታ" ሲሉም ጠንካራ ሀገራዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
#eidaladha #pmabiyahmed #ethiopia #patriotism #nationalunity #ethiopianbroadcastingcorporation
3 months ago
የባሕር በር አያስፈልግም ያለ ጋዜጠኛ ነገ ከልጁ ጋር እንዴት ይቆማል? #ethiopia #abiyahmed #mediaethics #nationalunity #peace #news #ethiopianpolitics
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
4 months ago
ሁሉም ቆም ብሎ ያስብ! — አገር እንደ ዕንቁላል ናት
#ethiopia | የዓለማችን ሁኔታ በተለይም በመካከለኛው ምስራቅ (ቴህራንና ቴል አቪቭ) የሚታየው እልቂትና ውድመት ተስፋ አስቆራጭ እየሆነ መጥቷል።
ለዘመናት የተገነቡ የቴክኖሎጂ ማምረቻዎች፣ የጥበብ ውጤቶችና ውብ ከተሞች በአንድ ጀምበር ወደ አመድነት ሲቀየሩ ማየት "ማውደም እንዴት ቀላል ነው?" ያስብላል።
የዓለምን ጥፋት ቆመን የምንመለከት ኢትዮጵያውያን ሁሉ፣ ዛሬ ከትንንሽ የሴራና የመጠፋፋት አዙሪቶች የምንወጣበት ጊዜ አሁን ነው።
ከግጭትና ከጦርነት አሸናፊ/ተሸናፊነት ትምክህት ወጥተን አገርን በንቃት እንጠብቅ።
ቂም፣ ጥላቻና መገፋፋት አገርን አያጸኑም፤ ይልቁንም ያፈርሳሉ። አገር እንደ ዕንቁላል ናትና ከወደቀች መጠገን እንደማይቻል ከታሪክ እንማር።
"እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል" እና "እኔ ምን አገባኝ" የሚሉ አጥፊ አስተሳሰቦች እሳት ታቅፎ እንደ መተኛት አደገኛ ናቸው።
መንግስትም ሆነ መሪ ያልፋሉ፤ ቀሪዋ ግን አገር ናት። ለትውልድ የምትተርፍ አገር እንድትኖረን መተሳሰብና መከባበር ምርጫ የሌለው መንገድ ነው።
"አረረም መረረም ለአገር ሰላምና ደህንነት፣ ለህዝቦች ሉአላዊ ክብርና ማህበራዊ እሴቶች ሁሉም ዘብ ይቁም!"
🙏 የጋራ ጸሎታችን፡
አምላክ ከምድር ጥፋት ሁሉ ይጠብቀን! አገራችንንና ሕዝባችንን በሰላም ያቆይልን። አሜን!
(ንጉሥ ወዳጅ ነው)
#getu #getutemesgen #ጌጡ #ethiopia #peace #nationalunity #humanity #nowar #ኢትዮጵያ #ሰላም #አንድነት #ንቁ_እንጠብቅ
#ethiopia | የዓለማችን ሁኔታ በተለይም በመካከለኛው ምስራቅ (ቴህራንና ቴል አቪቭ) የሚታየው እልቂትና ውድመት ተስፋ አስቆራጭ እየሆነ መጥቷል።
ለዘመናት የተገነቡ የቴክኖሎጂ ማምረቻዎች፣ የጥበብ ውጤቶችና ውብ ከተሞች በአንድ ጀምበር ወደ አመድነት ሲቀየሩ ማየት "ማውደም እንዴት ቀላል ነው?" ያስብላል።
የዓለምን ጥፋት ቆመን የምንመለከት ኢትዮጵያውያን ሁሉ፣ ዛሬ ከትንንሽ የሴራና የመጠፋፋት አዙሪቶች የምንወጣበት ጊዜ አሁን ነው።
ከግጭትና ከጦርነት አሸናፊ/ተሸናፊነት ትምክህት ወጥተን አገርን በንቃት እንጠብቅ።
ቂም፣ ጥላቻና መገፋፋት አገርን አያጸኑም፤ ይልቁንም ያፈርሳሉ። አገር እንደ ዕንቁላል ናትና ከወደቀች መጠገን እንደማይቻል ከታሪክ እንማር።
"እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል" እና "እኔ ምን አገባኝ" የሚሉ አጥፊ አስተሳሰቦች እሳት ታቅፎ እንደ መተኛት አደገኛ ናቸው።
መንግስትም ሆነ መሪ ያልፋሉ፤ ቀሪዋ ግን አገር ናት። ለትውልድ የምትተርፍ አገር እንድትኖረን መተሳሰብና መከባበር ምርጫ የሌለው መንገድ ነው።
"አረረም መረረም ለአገር ሰላምና ደህንነት፣ ለህዝቦች ሉአላዊ ክብርና ማህበራዊ እሴቶች ሁሉም ዘብ ይቁም!"
🙏 የጋራ ጸሎታችን፡
አምላክ ከምድር ጥፋት ሁሉ ይጠብቀን! አገራችንንና ሕዝባችንን በሰላም ያቆይልን። አሜን!
(ንጉሥ ወዳጅ ነው)
#getu #getutemesgen #ጌጡ #ethiopia #peace #nationalunity #humanity #nowar #ኢትዮጵያ #ሰላም #አንድነት #ንቁ_እንጠብቅ
7 months ago
የ“ኪን ኢትዮጵያ” የባህልና ኪነ-ጥበባት ልዑካን ቡድን ጎንደር ገባ
#ethiopia | የሕዝብ ለሕዝብ ትስስርን ለማጠናከርና የአብሮነት እሴቶችን ለማጎልበት ያለመው የ“ኪን ኢትዮጵያ” የባህልና ኪነ-ጥበባት ልዑካን ቡድን በታሪካዊቷ ጎንደር ከተማ ደመቅ ያለ አቀባበል ተደረገለት።
ከሁሉም የሀገሪቱ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የተወጣጡ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የያዘው የልዑካን ቡድኑ ጎንደር አጼ ቴዎድሮስ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተው ተቀብለዋቸዋል።
በአቀባበል ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ መልካሙ ጸጋዬ፤ ለመላው የልዑካን ቡድን አባላት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ይህ መድረክ ኢትዮጵያውያን ያላቸውን ባህላዊ መስተጋብር ይበልጥ ለማቀራረብና ወንድማማችነትን ለማጽናት ትልቅ ፋይዳ እንዳለውም ተገልጿል።
ይህ የባህልና የኪነ-ጥበብ መድረክ በፌዴራል ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከአማራ ክልል ባህል፣ ቱሪዝም እና ስፖርት ቢሮ ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ሲሆን፣ በቆይታውም የተለያዩ ጥናታዊ ጽሁፎች፣ የባህል ትርኢቶችና የሕዝብ ለሕዝብ ውይይቶች ይካሄዱበታል ተብሎ ይጠበቃል።
መርሐ-ግብሩ በዋናነት በሕዝቦች መካከል ያለውን አብሮነት በኪነ-ጥበብ አማካኝነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ያለመ መሆኑ ተመላክቷል።
ጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia #gondar #culturalexchange #nationalunity #ethiopianarts
#ethiopia | የሕዝብ ለሕዝብ ትስስርን ለማጠናከርና የአብሮነት እሴቶችን ለማጎልበት ያለመው የ“ኪን ኢትዮጵያ” የባህልና ኪነ-ጥበባት ልዑካን ቡድን በታሪካዊቷ ጎንደር ከተማ ደመቅ ያለ አቀባበል ተደረገለት።
ከሁሉም የሀገሪቱ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የተወጣጡ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የያዘው የልዑካን ቡድኑ ጎንደር አጼ ቴዎድሮስ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተው ተቀብለዋቸዋል።
በአቀባበል ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ መልካሙ ጸጋዬ፤ ለመላው የልዑካን ቡድን አባላት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ይህ መድረክ ኢትዮጵያውያን ያላቸውን ባህላዊ መስተጋብር ይበልጥ ለማቀራረብና ወንድማማችነትን ለማጽናት ትልቅ ፋይዳ እንዳለውም ተገልጿል።
ይህ የባህልና የኪነ-ጥበብ መድረክ በፌዴራል ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከአማራ ክልል ባህል፣ ቱሪዝም እና ስፖርት ቢሮ ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ሲሆን፣ በቆይታውም የተለያዩ ጥናታዊ ጽሁፎች፣ የባህል ትርኢቶችና የሕዝብ ለሕዝብ ውይይቶች ይካሄዱበታል ተብሎ ይጠበቃል።
መርሐ-ግብሩ በዋናነት በሕዝቦች መካከል ያለውን አብሮነት በኪነ-ጥበብ አማካኝነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ያለመ መሆኑ ተመላክቷል።
ጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia #gondar #culturalexchange #nationalunity #ethiopianarts
Comments